Blog Archives
(መሠረት ሚድያ)- አራት ኪሎ የሚገኘው ‘አምባሳደር ህንፃ’ ላይ ይገኝ የነበረው የድርጅቱ ቢሮ ውስጥ ሲገባ በመጀመርያ ቀልብን የሚስበው በብዙ የመንግስት ቢሮዎች ውስጥ እንደሚደረገው በትልቁ ታትሞ እና በፍሬም ተዘጋጅቶ የተሰቀለው የጠ/ሚር አብይ አህመድ እና የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ፎቶ ነው።
ድርጅቱ ቢሮው ብቻ ሳይሆን ማስታወቂያውም ቀልቢ ሳቢ ነበር።
“ልጄ ውጭ ሀገር ሄዳ ነው ትምህርቷን መከታተል የምትፈልገው፣ አገሯን የምታስጠራ ምሁር እንድትሆንልኝ እፈልጋለሁ” ትላለች ዝነኛዋ የማስታወቂያ ባለሙያ ሙሉአለም ታደሰ ከሌላኛዋ ታዋቂ የሚድያ ሰው ዳናይት መክብብ ጋር በመሆን በጋራ የሰሩት የዚህ ድርጅት ማስታወቂያ።
ይህ ዛሬ የምናቀርብላችሁ የከባድ ማጭበርበር ድርጊት ዋና ተዋናይ ቀላል ሰውም አይደለችም። ከጥቂት አመታት በፊት በአዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ላይ ከ ‘ተስፋ ሰጪ’ ‘እና ‘ስራ ፈጣሪ’ አምስት የሀገራችን ግለሰቦች አንዷ ሆና ቀርባለች፣ በተጨማሪም ከሴቶች እና ህፃናት ማህበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጌጎ ተስፋዬ ልዩ ሽልማት ተበርክቶላታል።
ግለሰቧ ቤተልሄም ታደሰ ይማም ትባላለች፣ ታድያ ተሸላሚ ያረጋት ስራዋ ምን ይሆን? ድርጅቷ ከ120 ሚልዮን በላይ ብርስ ከህዝብ እንዴት ማጭበርበር ቻለ?

ቤተልሄም ታደሰ ይማም
ከቅርብ ግዜ ወዲህ ለስራ ወይም ለትምህርት ወደ ውጪ ሀገር ሰው እንልካለን በማለት ገንዘብ የሚሰበስቡ ድርጅቶች መብዛታቸውን ብዙ ሰው ታዝቧል፣ ከነዚህም አንዱ Aim Ultra Consultancy የተባለው ድርጅት ነው።
“እኔ Aim Ultra ን ለደቂቃ እንኳን አልተጠራጠርኩም። ማስታወቂያውን ታዋቂ ሰዎች በቲቪ እና በሶሻል ሚድያ ሲሰሩ ስላየሁ እውነት ይሆናል ብዬ ከቤተሰብ ያገኘሁት ገንዘብ ላይ ከብድር እና ቁጠባ ተጨማሪ በመበደር 520,000 ብር ከፈልኩ”
የኤርትራው ፕሬዝደንት በትናንት ምሽት ብዙዎችን ባስደመመ ንግግራቸው ስለ ኢትዮጵያ ምን አሉ?
– “የውጭ ሀይሎች በብልፅግና ወኪላቸው አማካኝነት የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ላለፉት አምስት አመታት ያወጁት ጦርነት ምን ያህል ተስፋ እንደቆረጡ ያሳያል”
– “ሊያቀርቡ የሚፈልጓቸው ምክንያቶች; ናይል እና ቀይ ባህር፣ የባህር በር ማግኘት፣ የኦሮሞ ህዝብን የማይወክል የኦሮሙማ አስተሳሰብ፣ የኩሽ እና የሴም ግጭት… ናቸው”
– “የኢትዮጵያ ህዝብ የራሱን ምርጫ መርጧል፣ ተቃውሞውን ለማጠንከር እየተዘጋጀ ነው”
ሙሉ ዜናውን ያንብቡ፣ የሚድያችን ቤተሰብ ይሁኑ ⤵️
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/3bf?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
” በደብረብርሃን ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች ላልተፈለገ እርግዝና እና በአባላዘር በሽታ እየተጠቁ ነው ” የተፈናቃይ ሴት ወጣት ተወካዮች
⚫ ” የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት ይሰጡ የነበሩ ድርጅቶች አሁን ላይ ሁሉም ወጥተዋል ” የቻይና ካምፕ ተፈናቃይ አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ
በደብረብርሃን መጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚሰጠው የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት ጥራቱን ያልጠበቀ በመሆኑ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን የተፈናቃዮቾ ሴት ወጣት ተወካዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
በህክምና ባለሙያዎች ዘንድም ሚስጥር ጠባቂ አለመሆን አገልግሎት ለማግኘት በምንሄድበት ወቅት የማሸማቀቂያ ቃላቶችን የሚጠቀሙ በመሆኑ አገልግሎቱን ማግኘት ከብዶናል ብለዋል።
“የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት እየሰጠ ያለው ዩኒሴፍ ብቻ ነው፣ አገልግሎት የሚሰጠውም ግቢ ውስጥ ቢሆንም ሴት ልጅ ስትገባ የእንትና ልጅ የወሊድ መቆጣጠሪያ ልትጠቀም ገበች ይላሉ፣ ስንወጣ ደግሞ ወጣት ወንዶች ይጠብቁና ያሸማቅቁናል” ሲሉ ችግራቸውን ይገልጻሉ።
በተጨማሪም ” የህክምና ባለሙያው ወንድ ነው፣ ይህ ደግሞ ሴቶች በነፃነት የሚፈልጉት እንዳይናገሩ አድርጓል፣ በከተማው ጤና ጣቢያዎች ስንሄድም በነፃ ስለሆነ የሚሰጠው ምን ልታደርጊ ትመጫለሽ ውጪ ይላሉ። እነሱ የሚፈልጉት ብር የሚከፍለውን ሰው ብቻ ነው” ሲሉ አክለዋል።
ወጣት ሴቶችም በየፋርማሲው መድሀኒት እየገዙ ይውጣሉ፣ አብዛኞቹም ለህመም እየተዳረጉ ነው ብለዋል።
በስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት እጥረት በርካታ ወጣቶች ላልተፈለገ እርግዝና፣ ለአባላዘር እና ለመሳሰሉ ተላላፊ በሽታዎች መጋለጣቸውንም አስረድተዋል።
“በተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ ውስጥ ያሉ ወጣት ወንዶች ተስፋ እየቆረጡ አልኮል እየጠጡ ሴት ልጆችንን አስገድደው እየደፈሩን ነው፣ ስንጠይቅም በቸልተኝነት ሁሉም ይስተካከላል ይላሉ” ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርቧል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቻይና ካምፕ የተፈናቃይ ኮሚቴ
” መንግስታት ውጤት አልባ ከሆነ የIMF የበጀት መቀነስና ዕዳ መክፈል ፖሊሲ ወጥተው ትኩረታቸውን ዜጎቻቸው ላይ ማድረግ አለባቸው ” – አክሽን ኤድ
በአፍሪካ ስድስት ሃገራት በጤና እና ትምህርት ዘርፉ በጀት በመቀነሱ ሰራተኞች የከፋ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን አዲስ ጥናት (https://actionaid.org/sites/default/files/publications/The%20Human%20Cost%20of%20Public%20Cuts%20May%202025.pdf) አመላከተ።
ጥናቱን አክሽን ኤድ የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት የሰራው ሲሆን ፦
– በኢትዮጵያ
– በጋና
– በኬንያ
– በላይቤሪያ
– በማላዊ
– በናይጄሪያ 600 የጤና ባለሙያዎች፣ መምህራንና የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ ነው ተብሏል።
በጥናቱ ከተሳተፉት መሃል 97 በመቶ የሚሆኑት የጤና ባለሙያዎች የሚያገኙት ደመወዝ መሰረታዊ የሚባለውን ወጪያቸውን ለመሸፈን እንደማያስችላቸው ተናግረዋል።
97 በመቶ የሚሆኑት የጤና ባለሙያዎች በደመወዛቸው የቤት ኪራይ መክፈል፣ የምግብ እና ሌሎች ወጪዎችን መሸፈን እንዳልቻሉ አንስተዋል።
በጥናቱ በ6ቱ ሀገራት የሚገኙ የጤና ተቋማት ተገልጋዮች በሃኪሞች እጥረት እና በዋጋ መጨመር ደስተኛ አይደሉም ሲል ያስቀመጠ ሲሆን መንግስታት ውጤት አልባ ከሆነ የIMF የበጀት መቀነስና ዕዳ መክፈል ፖሊሲ ወጥተው ትኩረታቸውን ዜጎቻቸው ላይ ማድረግ አለባቸው ብሏል።
ህመምተኞች ወደ ጤና ተቋማት ለመሄድ ረጅም መንገዶችን እንደሚጓዙ፤ የወባ መድኃኒትም በ10 እጥፍ ዋጋው መጨመሩ በጥናቱ የተካተተ ነው።
ለአብነትም በኢትዮጵያ ሙያከላ ቀበሌ የምትኖር ሴትን በመጥቀስ ከ5 አመት በፊት የወባ መድሃኒት በ50 ብር ትገዛ እንደነበር እና አሁን ግን ከግል ተቋማት በ500 ብር እንደሚገዛ መናገሯን ገልጿል።
በሌላ በኩል ፥ በጥናቱ ከተሳተፉት 87 በመቶ የሚሆኑት መምህራን የክፍል ውስጥ ቁሳቁሶች /የማስተማሪያ ቁሳቁሶች እንዳልተሟሉላቸው ሲገልፁ ፤ 73 በመቶ ያህሉ የትምህርት ማስተማሪያ
Posted in
News,
አፍሪቃ,
ኢትዮጵያ

ልክ የዛሬ አመት በዚህ ወር በምርመራ ክፍል ውስጥ በአሰቃቂ ሁኔታ ስለተገደለው ኢሳያስ በላይ የተሰራ የምርመራ ዘገባ!ለስድስት አመታት ያህል በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) ውስጥ ከፍተኛ የሳይበር ደኅንነት ባለሙያ ሆኖ አገልግሏል።በ2014 ዓ/ም የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የክልሉ ሰላምና ደኅንነት የሚጠቀምበት ወታደራዊ ሬዲዮ የመለያ ኮዱ በቀላሉ ተጋላጭ ሆኖ ተገኘ። ይህንን የሬዲዮ ትስስር እንደ አዲስ ማስተሳሰር ግድም ሆነ።ኢሳያስ በላይ የወታደራዊ ሬዲዮ ትስስሮች እንዲሁ በቀላሉ የሚከወኑ አይደለም። በዘርፉ ልምድ ያላቸው አለም አቀፍ ተቋማት ተወዳድረው በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሚጠይቁበት ስራ ነው።አገርን ለከፍተኛ ወጪ የዳረገ የሬዲዮ ግንኙነት መረብ እንዲሁ በቀላሉ የይለፍ ቃሉ ተሰብሮ ሚስጥሮች የሚባክኑ ከሆነ ደግሞ ሌላ የአገራዊ ደኅንነት ስጋት ነው። ይህ ስጋት በ2014 ዓ/ም በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የሰላም እና ደኅንነት የሬዲዮ መገናኛ ላይ በግልፅ ታየ።ችግሩ እንዴት ይቀረፍ? በሚል ኢንሳ መፍትሄ ሲያፈላልግ ኢሳያስ በላይ በተቋሙ ውስጥ ያገኘውን አለም አቀፍ ልምድ በመውሰድ የክልሉን የሬዲዮ አውታር እንደ አዲስ ለማቀናጀት ሀሳቡን አቀረበ። ኢንሳ ሰባት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን አዋቅሮ ኢሳያስን የቡድኑ መሪ አድርጎ ወደ አማራ ክልል ሸኘው።ቡድኑን በማስተባበር የአማራ ክልልን ከወረዳ ጀምሮ እስከ ዋናው ቢሮ ድረስ ያለውን የሬዲዮ ትስስር በዘመናዊ መልኩ አቀናጅቶ ለክልሉ መንግስት በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ አስረክቧል። ኢሳያስ ዛሬ በሕይወት ባይኖርም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እና የሰላምና ደኅንነት ቢሮ እስከ ወረዳ ድረስ የሚጠቀሙበት የሬዲዮ መገናኛ መረብ በዚህ ድንቅ ወጣት የተሳሰረ ነው።ኢሳያስ በላይ ለምን ተገደለ?የአማራ
ከኢግል ሂልስ ‘ላጋር ዋን’ ሳይት ቤት የገዙ ደንበኞች ገጠመን ያሉት አነጋጋሪ ክስተት
– “ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ቅድሚያ የከፈልነው ገንዘብ እና ቤቱ ራሱ እንደሚወሰድብን ማስጠንቀቂያ ደርሶናል”
– “አጥብቀን ስንጠይቅ ‘ይህ እኮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግላቸው የሚከታተሉት ፕሮጀክት ነው’ የሚል ማስፈራርያ አዘል ማሳሰቢያ ይሰጠናል”
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/fda?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
በመላው አዲስ አበባ የሚገኙ መምህራን ለነገ መቅረትም ሆነ ማርፈድ የማይቻልበት ቀጠሮ ተጠርተዋል
– ስልክ እና ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክስ ይዘው እንዳይመጡ ማስጠንቀቂያ ደርሷቸዋል
“በየትኛውም ሴክተር የሚገኝ የመንግስት ሰራተኛ ተምሮ እንዳልተማረ በመሃይም ካድሬዎችና የቢሮ ኃላፊዎች መብቱ እየተረገጠ፤ እንዳይረጋጋ በመንግስት የታቀደ ኢኮኖሚያዊ ጫና እየደረሰበት ይገኛል። የሰሞኑ የጤና ባለሙያዎችም ጥያቄ የሁሉም የመንግስት ሰራተኛ ጥያቄ ነው፤ ከእንግዲህ መሃይም ሹመኞች እራት እንዲበሉ ሻማ ይዘን የምንቆምበት ወቅት አልፏል”- መምህራን
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/73e?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
አቶ ጌታቸው ረዳ ሶስት ከፍተኛ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች “በዘረፋ እና በሰዎች ንግድ ላይ ተሳትፈዋል” ሲሉ ወነጀሉ
የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፤ ሶስት ከፍተኛ የትግራይ ወታደራዊ አመራሮች “በወርቅ ቁፋሮ እና ንግድ”፣ “የመንግስት ገንዘብ በመዝረፍ” እንዲሁም ”በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሳትፈዋል” ሲሉ ወነጀሉ።
አቶ ጌታቸው ረዳ ከፋና ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ በስም ጠቅሰው የወነጀሏቸው ሶስቱ አመራሮች፤ ብርጋዴር ጀነራል ምግበይ ሃይለ፣ ብርጋዴር ጀነራል ሃይለስላሴ ግርማይ እና ኮሎኔል ተወልደ ገብረትንሳኤ ናቸው።
ትላንት ሰኞ ግንቦት 4፤ 2017 ምሽት በፋና ቴሌቪዥን የተላለፈው የቀድሞው የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ክፍል አንድ ቃለ መጠይቅ፤ ስለ እርሳቸው የፖለቲካ ተሳትፎ አጀማመር፣ በትግራይ ክልል ስለ ተካሄደው ጦርነት፣ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አመራሮች እና የትግራይ ሰራዊት አዛዦች “ፈጽመዋቸዋል” ስላሏቸው ወንጀሎች የዘረዘሩበት ነበር።
አቶ ጌታቸው ተፈጽመዋል ካሏቸው ወንጀሎች ቅድሚያውን የሰጡት ለወርቅ ንግድ ነው። በትግራይ ክልል በህገወጥ መንገድ የሚካሄደው የወርቅ ንግድ የተጀመረው፤ ህወሓት እና የኢትዮጵያ መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነትን ከተፈራረሙ ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. በኋላ የሚመስለው በርካታ ሰው እንዳለ አቶ ጌታቸው በቃለ መጠይቃቸው ላይ አንስተዋል።
ሆኖም በክልሉ ህገወጥ የወርቅ ቁፋሮም ሆነ ንግድ የተጀመረው፤ የትግራይ ጦርነት እየተካሄደ በነበረበት ወቅት ጭምር እንደሆነ የቀድሞው የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ይፋ አድርገዋል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15872/
” እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ እስካሁን የታገስኩት ይበቃኛል ” – አቶ ጌታቸው ረዳ
በትግራይ ያለው ህገወጥ የወርቅ ንግድ ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኃላ የጀመረ ሳይሆን በጦርነቱ ጊዜም ሳይቀር ሲሰራ የነበረ እንደሆነ የቀድሞው የጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና የአሁኑ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አደረጉ።
አቶ ጌታቸው፤ “ብዙ ሰው የወርቅ ንግድ የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈራረምን በኃላ የጀመር ይመስለዋል” ያሉ ሲሆን ግን ጦርነቱም እየተካሄደ ንግዱ ነበር ብለዋል።

“እኔ የማምንበትን ትግል ነው ያካሄድኩት ብዬ አምናለሁ በዛ በማምንበት ትግል ውስጥ የትግራይን ህዝብ አጀንዳ ይዘው የታገሉ ብዙ የጦር መኮንኖች አሉ ለሰሩት ስራ ያለኝ ክብር በፍጹም አይቀንስም ግን ደግሞ ገና ገና ጦርነቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ይበላ በነበረበት ወቅት ሳይቀር ምሽግ ለመቆፈር ብለን የወሰድነው ኤክስካቫተር ወርቅ ለመልቀም ይጠቀሙበት የነበሩ አዛዦችም ነበሩ” ሲሉ አጋልጠዋል።
“ሲዋሹ በጣም ነው የሚገርመኝ” ያሉት አቶ ጌታቸው “እኔ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል እስካሁን የታገስኩትም ይበቃኛል” ብለዋል።
አቶ ጌታቸው “የኤርትራን ሰራዊት እናፍርሰው” በሚል አላማ ዘመቻ የጀመረና ዘመቻውን የሚመራው አመራር ሰዎችን እያፈነ ገንዘብ ሲበስብ እንደነበር ተናግረዋል።
“ሰው ሲሸጡ የሚኖሩ ሰዎች አሉ፤ ኤርትራዊ መሸጥ ‘ ንብረት ‘ ነው የሚባለው ወርዷል ወይ ? ይባላል፤ ታፍንና ይዘህ 27 ወጣት አንድ ቤት ትዘጋና ቤተሰቦች አላቸው ውጭ ሀገር የሚባሉት ሰዎች አካውንት እየተጠየቀ እያንዳንዱ ሰው በትንሹ 4000 ዶላር እንዲያስገባ ተደርጎ (20 ሰው ካፈንክ 80 ሺህ ዶላር ታስገባለህ) በዚህ የውጭ አካውንት ከፍተው በሺዎች የሚቆጠሩ

የፎቶው ባለመብት, sm
የምስሉ መግለጫ, ዶ/ር በርናባስ ሳሙኤል፣ ዮናታን ዳኛው፣ ዶ/ር ሀብታሙ ጌታቸው እና ዶ/ር መላኩ አልማው
የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት አቶ ዮናታን ዳኛው እንዲሁም ሦስት የአርባ ምንጭ ጠቅላላ ሆስፒታል ዶክተሮች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።
በአዲስ አበባ ከተማ እንዲሁም በአማራ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በቀናት ልዩነት የታሰሩ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር አምስት ደርሷል። በአዲስ አበባ ከተማ ሌሎች አምስት የጤና ባለሙያዎች ደግሞ ከሁለት ቀን እስር በኋላ ተለቅቀዋል።
የጤና ባለሙያዎች ከሰሞኑ እያደረጉት ላለው እንቅስቃሴ ድጋፉን የገለጸው የጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ዮናታን የታሰሩት ትናንት እሁድ ግንቦት 3/2017 ዓ.ም. እንደሆነ የማኅበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መለስ ባታ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በ2015 ዓ.ም. የተመሠረተውን ማኅበር የሚመሩት አቶ ዮናታን፤ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን በሚገኘው ቢቸና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የጤና ባለሙያ መሆናቸውን አቶ መለሰ ገልጸዋል።
ምክትል ፕሬዝዳንቱ እንደሚናገሩት አቶ ዮናታን እሁድ ከሰዓት የተያዙት ከመኖሪያ ቤታቸው ነው። “ከመያዙ በፊት ከትናንት ወዲያ [ቅዳሜ] የሚሠራበት ሆስፒታል አካባቢ እና በሚኖርበት ሰፈር [በሚገኝ የፖሊስ ጣቢያ] ለምርመራ እንደሚፈለግ ደውለው እንዳስታወቁት ነግሮኝ ነበር” የሚሉት አቶ መለስ፤ ይህ ከሆነ ከአንድ ቀን በኋላ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።
ከማኅበሩ ፕሬዝዳንት ጋር አጭር የስልክ ንግግር ማድረጋቸውን የሚጠቅሱት አቶ መለስ፤ በአሁኑ ሰዓት በፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እንደሚገኝ እና “ብዙ ችግር እንዳልደረሰበበት” ከራሱ መስማታቸውን ገልጸዋል። ይሁንና የስልክ ጥሪው በመቋረጡ ምክንያት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት የታሰሩበትን ምክንያትም ሆነ ስለተደረገባቸው ምርመራ በዝርዝር መነጋገር እንዳልቻሉ
የምርመራ ዘገባ ጫንጮ ላይ የከተሙ ‘ሪጴ ሎላ’ የተባሉ የኦሮሚያ ልዩ ሀይል አባላት አነጋጋሪ ድርጊት ላይ ምርመራ አርገናል
(መሠረት ሚድያ)- ከአዲስ አበባ 40 ኪ/ሜ ገደማ ርቀት ላይ የምትገኘው የጫንጮ ከተማ ከቅርብ አመታት ወዲህ ሰላም ርቋታል። ተስማሚ አየር እና መልካም ገፀ ምድር ያላት የኦሮሚያ ክልሏ ጫንጮ በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግስት ኦነግ ሸኔ የሚለው) እና በመንግስት ሀይሎች መካከል በሚደረግ ግጭት ምክንያት ፀጥታዋ ደፍርሷል።
ታድያ በከተማዋ ተወልደው ያደጉትም ይሆን ከሌላ ቦታ ወደ ከተማዋ ሄደው የሚኖሩ ነዋሪዎች ከቅርብ ወራት ወዲህ ‘ሪጴ ሎላ’ በተባሉ የኦሮሚያ ልዩ ሀይል አባላት አበሳቸውን እያዩ እንደሆነ መሠረት ሚድያ ባደረገው ክትትል ደርሶበታል።
“የምኖረውም ተወልጄ ያደኩትም እዚሁ ጫንጮ ከተማ ነው፣ ለስራ የተሰማራሁትም በሞባይል ሽያጭ ላይ ነው” የሚለው አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ ነዋሪ ሰሞኑን የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከተማውን ለቀው ወደ ሌላ ቦታ መንቀሳቀሳቸውን ተከትሎ እነዚህ ‘ሪጲ ሎላ’ የተባሉት የመንግስት ሀይሎች የጫንጮን ነዋሪ እያሰቃዩ እንደሆነ ይናገራል።
“እኔ ላይ የደረሰውን ለመናገር፣ አንድ ቀን ሶስት ሆነው መጡና ብር አምጣ አሉኝ። ካሽ የለኝም ስላቸው ‘ካዝና ውጥ ይጠፋል? እናየዋለን!’ ሲሉኝና ሲቆጡ የእቁብ ብር ነው ስል አንዱ በጥፊ መታኝና 3,000 አርግ አለኝ፣ ሰጠኋቸው። የሆነውን ለጓደኞቼ ስናገር እኔንም፣ እኔንም 4,000 ብር ምናምን ወሰዱብን አሉኝ” በማለት ሁኔታውን አስረድቷል።
ይህን ተከትሎ የጫንጮ ከተማ የፀጥታ ሀላፊ ጋር ሄደው ሲያመለክቱ “ከአቅማችን በለይ ነው፣ የኛን ፖሊስ ራሱ ደበደቡብን፣ ዝም በሉ በቃ” ብሎ ምላሽ እንደሰጣቸው አክሎ
ዘንድሮ 47 ቢሊዮን ብር የከሰረው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፤ በሁለት ዓመት ውስጥ ወደ ትርፋማነት እንደሚሸጋገር የኩባንያው ኃላፊዎች ገለጹ
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት ኪሳራ ቢያጋጥመውም፤ በሁለት ዓመታት ውስጥ ወደ ትርፋማነት ይሸጋገራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የእናት ኩባንያው ኃላፊዎች ተናገሩ። መቀመጫውን በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ያደረገው ሳፋሪኮም ኩባንያ፤ እስከ መጋቢት ወር ባለው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ካገኘው 3 ቢሊዮን ዶላር የአገልግሎት ገቢ 10 በመቶ ገደማ የሚሆነው የኢትዮጵያ ገበያ ድርሻ እንደሆነ አስታውቋል።
ኩባንያው የሚመራበት በጀት ዓመት መጠናቀቁን በማስመልከት ባለፈው ሐሙስ ይፋ የተደረገ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ገቢ ባለፈው ዓመት 2.7 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን ዘንድሮ 7.2 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ270 ፐርሰንት እድገት ቢያሳይም፤ 47 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ኪሳራ እንደገጠመው ዋና ስራ አስፈጻሚው ዊም ቫንሔለንፑት ገልጸዋል።
“ይህ ኪሳራ በአብዛኛው ኩባንያው በሚገኝበት ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ምዕራፍ ከምንጠብቀው ጋር የተስማማ ነው” ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚው፤ ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በሐምሌ 2016 ዓ.ም. ተግባራዊ ያደረገው የውጭ ምንዛሬ ግብይት ስርዓት ለውጥ በኩባንያው ላይ ተጽዕኖ እንዳሳደረ ጠቁመዋል።
የውጭ ምንዛሬ ግብይት ስርዓት ለውጡ፤ በአጭር እና መካከለኛ ጊዜ የሚያሳድራቸውን ተጽዕኖዎች ለመቋቋም “እርምጃዎች መወሰዳቸውን” የሳፋሪኮም ኃላፊዎች አብራርተዋል። እርምጃው በውጭ በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የተቀጠሩ የውጪ ሀገር ዜጎችን መቀነስን የካተተ ነው።
🔴ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15849/
በዘጠኝ ወራት ከ37 ሺሕ በላይ ሠራተኞች መልቀቃቸው ተነግሯል
በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ በሚገኘው ኢንዱስትሪ ፓርክ የተሰማሩ ጦርነት ሸሽተው የወጡ ባለሀብቶች፣ ማሽኖቻቸውን ከአገር ለማስወጣት ጥያቄ እያቀረቡ መሆናቸውን፣ የኢንዱስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ገለጸ።
ኮርፖሬሽኑ ይህንን የገለጸው የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሜቴ ሲያቀርብ ነው፡፡

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት ከአገር ሸሽተው የሄዱ ባለሀብቶችን ለረዥም ጊዜያት በኢንተርኔትና በአካል በመገናኘት ኩባንያዎቻቸው ተመልሰው ወደ ልማት እንዲገቡ ጥረቶች ቢደረጉም ፍላጎት አለማሳየታቸውን፣ በኢንዱስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽንና ማኔጅመንት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ካሚል ኢብራሂም ተናግረዋል፡፡
‹‹ኩባንያዎቹ ወደ ሌላ አገር ሄደው ለማልማት ማሽናቸውን ከአገር ይዘው ለመውጣት ጥያቄ በማቅረባቸው፣ እኛ እንደ መፍትሔ እያቀረብንላቸው ያለው አገር ውስጥ የገባና በአጠቃላይ አገራዊ ምርት የተመዘገቡ ማሽኖችን ወደ ሌላ አገር ከሚወስዱ፣ በአገር ውስጥ ወደ ሌላ አካባቢ በማዘዋወር ለማሠራት ጥያቄ አቅርበን እየጠበቅን፤›› ነው ብለዋል።
ነገር ግን ወ/ሮ ሶስና ጌታሁን የተባሉ የቋሚ ኮሚቴው አባል፣ መቀሌ የነበሩ ኢንቨስተሮች እዚያው መቆየት ካልፈለጉ ቦሌ ለሚ ወይም አዳማ እንዲያለሙ ለማድረግ እየተሠራ ነው የሚለው ምላሽ ትክክል አለመሆኑን፣ ኢንቨስተሮች በመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምን እንደጎደላቸው መጠየቅና ችግሩን መፍታት እንጂ ከአንድ አካባቢ አስነስቶ ወደ ሌላ ቦታ ለመውሰድ መሞከር ትክክል አይደለም ብለዋል። አክለውም ያልተመቹ ጉዳዮች ካሉ ኢንቨስተሮቹ ተጠይቀው መፍትሔ በማፈላለግ ሁኔታዎችን በማመቻቸት እዚያው ማቆየት እንጂ፣ ከአንድ አካባቢ ወደ ሌላ አካባቢ ማዘዋወር አግባብ አይደለም በማለት አሳስበዋል፡፡
ይህ በዚህ
መንግሥት፣ በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች የሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች እንደየአገልግሎታቸው ዓይነት “ወጥ ቀለም” እና መለያ ኮድ እንዲኖራቸው እቅድ መያዙን ዋዜማ ሠምታለች። የተሽከርካሪዎች ቀለምና መለያ ኮድ ከከተማ ከተማ የተለያየ ይሆናል ተብሏል። የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሠጪ ተሽከርካሪዎች ሹፌሮችም፣ ወጥ የደንብ ልብስ እንዲለብሱ ለማድረግ እቅድ እንደተያዘ ዋዜማ ተረድታለች። የትራንስፖርት ሚንስትር ዓለሙ ስሜ፣ ያረጁ ተሽከርካሪዎችን ከሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ውጭ ለማድረግ እንደተወሰነ ሰሞኑን ባንድ ስብሰባ ላይ መናገራቸውንም ዋዜማ ተረድታለች።
አቶ ኮስሞስ ገብረ ሚካኤል ለወጣት ኢትዮጵያውያን የተስፋይቱ ምድር ተደርጋ በምትታየው በደቡብ አፍሪቃ በደላሎች የሚፈጽምባቸው በደል መክፋቱን ገልጸዋል።። በሕገ ወጥ መንገድ ደቡብ አፍሪቃ ከደረሱ በኋላ ለእገታ የሚዳረጉት አስቀድሞ ከደላሎች ጋር የተስማሙበትን ውል በጊዜው አላሟሉም የሚባሉት ኢትዮፕያውያን መሆናቸውንም ተናግረዋል።