
የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ኢትዮጵያ ከ10 ዓመታት በፊት ለሸጠችው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ከዓለም አቀፍ የቦንድ ገዢዎች ጋር የእዳ ሽግሽግ እንዴት ማድረግ እንዳለባቸው መደበኛ ንግግር መጀመሯን ሮይተርስ የዜና ወኪል ምንጮቹን ጠቅሶ ዘገበ።
ሮይተርስ ቀደም ብሎ በብሉምበርግ የወጣውን ዘገባ በማረጋገጥ ከዓለም አቀፍ ባለሃብቶች ጋር በእዳ ሽግሽግ ዙሪያ በፓሪስ ፈረንሳይ ድርድር መጀመሩን ዘግቧል።
አንድ የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሥልጣን ዝርዝር መረጃ ሳይጠቅሱ የመንግሥት ልዑክ ወደ ፓሪስ ማቅናቱን አረጋግጠዋል።
“ከቦንድ አበዳሪዎች ጋር የተያዙ አንዳንድ ስብሰባዎች ነበሩ” ሲሉ ለሮይተርስ የተናገሩት ምንጩ የስብስበዎቹ ውጤት መጨረሻ ላይ የሚገለፅ እንደሆነ በመጠቆም ስምምነነት ላይ ግን እንዳልተደረሰ ገልፀዋል።
አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) አስተያየት እንዲሰጡ ተጠይቀው ወዲያ ምላሽ አልሰጡም።
የቦንድ አበዳሪዎች ኮሚቴ ተወካዮችም እንዲሁ ምላሽ አልሰጡም።
“ለመሠረተ ልማት ግንባታዎች” እንደሚውል የተነገረለት የቦንድ ሽያጭ በ10 ዓመታት ተመልሶ የሚከፈል እና የ6.625 በመቶ ወለድ ያለው መሆኑ በወቅቱ ተነግሮ ነበር።
ኢትዮጵያ ያወጣችውን ቦንድ 50 በመቶ የአሜሪካ ባለሃብቶች፣ 35 በመቶ የእንግሊዝ ባለሀብቶች፣ 14 በመቶ የአውሮፓ አገራት ባለሃብቶች እና ሌሎች ገዝተዋል፡፡
በውሉ መሰረት ኢትዮጵያ በ2016 ዓ.ም. የቦንድ ብዱሩን ክፍያ መክፈል ያልቻለች ሲሆን፤ በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ በኩል የእዳ ሽግሽግ እንዲደረግ መርጣለች። በዚህ አካሄድ የሁለትዮሽ ብድር፣ ዩሮ ቦንድ እና ሌሎች የንግድ ብድሮች አንድ አይነት አመላለስ አላቸው።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከቦንድ ገዥዎች ጋር የእዳ ሽግግር ማድረጊያ መንገዶችን ለመለየት ለወራት ንግግር ሲያደርግ ቆይቷል።
በቦንድ ገዥዎች እና በተበዳሪ መንግሥታት መካከል