Blog Archives

በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ካህናት እንዴት ተገደሉ?

በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ አቅራቢያ ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቤተክርስቲያን አገልግሎት በሚመለሱበት ወቅት በታጠቁ አካላት ተይዘው ከተወሰዱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን አገልጋዮች መካከል ሁለት ካህናት ተገደሉ፡፡ ከታገቱ ከሁለት ሳምንታት ግድም በኋላ ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ታህሳስ 04 ቀን 2018 ዓ.ም. መገደላቸው ይፋ የሆነው የአገረስብከቱ ስራአስከያጅ እና አንድ ሌላ አገልጋይ የታገቱት በዞኑ በጅማ ገነቲ ወረዳ የምትገኝ ቀዲዳ ማሪያም ቤተክርስቲያን አገልግሎት ውለው ወደ ሻምቡ ከተማ በምመለሱበት ወቅት በመንገድ ላይ ባደፈጡ ታጣቂዎች እንደሆነ የአይን እማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡ በእለቱ ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ወደ ጅማ-ገነቲ ወረዳ ሀራቶ ከተማ ቀዲዳ ማሪያም ለአገልግሎት ተጉዘው የነበሩት የሀገረስብከቱ አገልጋዮች ላይ እገታው የተፈጸመው ጬካ-አባጀና በሚባል ደናማ ስፍራ ነው ተብሏል፡፡ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው ሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ከነበሩት የቤተክርስቲያን አገልጋዮች መካከል የሀሮሮጉዱሩ ሀገረስብከት ስራአስከያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ እና ሌላው የቤተክስቲያን አገልጋይ ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ ቅዳሜ ዕለት መገደላቸው ተረጋግጧልም ተብሏል:: እገታው እንዴት ተፈጸመ? በእለቱ በታጣቂዎች ተገድለዋል ከተባሉት ሁለቱ ካህናት ጋር ከአገልግሎት ስመለሱ የነበሩና በታጣቂዎች እገታ ወቅት በዚያው የነበሩ አንድ ለደህንነታቸው ስባል ግን ስማቸውን ከመግለጽ የተቆጠቡት የአይን እማኝ ለዶይቼ ቬለ እንደነገሩት፤ እገታው የተፈጸመባቸው በአገረስብከቱ ተሽከርካሪ ወደ ሻምቡ ከተማ በመጓዝ ላይ ሳሉ ነበር፡፡ “በእለቱ ከታገቱት መካከል እኔ አንዱ ነበርኩ” ያሉን የአይን እማኙ በርካቶች ያመለጥነው ታጣቂዎች ወደ ሚፈልጉት አቅጣጫ ከመጓዝ ይልቅ
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ, ጀርመን, ፖለቲካ

Marburg Virus in Ethiopia : የቫይረሱ ስርጭት ከዕለት እለት አስከፊ እየሆነ በመምጣቱ ለ1 ሣምንት ትራንስፖርት ዝግ ይሆናል

” በማርበርግ ቫይረስ ምክንያት ከዛሬ ህዳር 20/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ1 ሣምንት ትራንስፖርት ዝግ ይሆናል” – የዞኑ መንግስት ‎ ‎በጂንካ ተከስቶ ለሰዎች ሞት ምክንያት እየሆነ ያለዉን የማርበርግ ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር ያስችል ዘንድ ወደ በሽታዉ መነሻ የአሪ ዞን የሚገባም ሆነ የሚወጣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ለ1 ሣምንት ዝግ እንዲሆን በአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብር ሃይል መወሰኑን የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ደምመላሽ አቦነህ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። ‎ ‎የቫይረሱ ስርጭት ከዕለት እለት አስከፊ እየሆነ በመምጣቱ የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር በአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብረሀይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኃላፊዉ እስካሁን በነበረው ሂደት ትምህርት ቤቶች የተዘጉና ፣ ሕዝብ የሚሰበሰብባቸዉ ጉዳዮች ላይ እቀባ የተጣለ ቢሆንም ስርጭቱን በሚፈለገዉ ልክ መግታት ባለመቻሉ የትራንስፖርት ዘርፉን ለ1 ሳምንት መዝጋት አስፈላጊ በመሆኑ ከዛሬ ህዳር 20/2018ዓም ጀምሮ ለ1 ሳምንት ዝግ እንዲሆን ግብረሀይሉ መወሰኑን ተናግረዋል። ‎ ‎ጂንካ ከተማን ጨምሮ ለሁሉም መዋቅር የትራፊክ ፍሰት እና የፀጥታ ዘርፍ አስተባባሪዎች ይህ መልዕክት መተላለፉንም አቶ ደምመላሽ አስታዉቀዋል። ‎ ‎በዚህ መሰረት ከክልል በወረደው አቅጣጫ መሰረት አገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ለ1 ሳምንት የታገደ ሲሆን በከተማ የሁለት እግር ተሽከርካሪዎችና የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ብሎም በዞኑ ውስጥ የሚኖሩ የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች በቀጣይ ቀናት ውስጥ ውሳኔ እንደሚሰጥባቸው ገልፀዋል። ‎ ‎ኃላፊው አያይዘውም በአሁኑ ወቅት የማርበርግ በሽታ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ የተከሰተ ቢሆንም ጂንካ ለቅሶ መጥቶ የተመለሰ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ በበሽታዉ  መሞቱን መስማታቸዉንና የስርጭት
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, NRS-Import, VIDEO ቪዲዮ, አዉሮጳ, አፍሪቃ, ኢትዮጵያ, ኤኮኖሚ, ጀርመን, ፖለቲካ

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል አጣጥለውታል

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል፣ የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ በባሕር በር ጉዳይ ላይ የሚከተለው “አምታች የኾነ አካሄድ” በቀጠናው ጦርነት ሊቀሰቅስ ይችላል በማለት አስጠንቅቀዋል። የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም እና ሌሎች የአገሪቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች በኤርትራ ላይ “የጦርነት ዛቻ” ማሰማት ቀጥለዋል በማለት የከሠሡት የማነ፣ በሌላ በኩል ደሞ ብልጽግና ኢትዮጵያን ከምጽዋ፣ አሰብ እና ከጅቡቲዋ ታጁራ ወደብ ጋር የሚያገናኝ የባቡር ሐዲድ ለመገንባት እንዳቀደ በመግለጽ “አምታች አካሄድ” ይከተላል በማለት ተችተዋል። ይሄ የፓርቲው እሳቤ ግን “ከቅን ልቦና ከመነጨ ፍላጎት” እና “ከቀጠናዊ የሰላምና ትብብር ፖሊሲ” ጋር አንዳችም ግንኙነት የለውም ሲሉ የማነ አጣጥለውታል።
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, አፍሪቃ, ጀርመን

ኢትዮጵያ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር አበዳሪዎቿ ጋር መደበኛ የእዳ ሽግሽግ ድርድር ጀመረች

የአዲስ አበባ ከተማ ከፊል ገጽታ የፎቶው ባለመብት, Getty Images ኢትዮጵያ ከ10 ዓመታት በፊት ለሸጠችው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ከዓለም አቀፍ የቦንድ ገዢዎች ጋር የእዳ ሽግሽግ እንዴት ማድረግ እንዳለባቸው መደበኛ ንግግር መጀመሯን ሮይተርስ የዜና ወኪል ምንጮቹን ጠቅሶ ዘገበ። ሮይተርስ ቀደም ብሎ በብሉምበርግ የወጣውን ዘገባ በማረጋገጥ ከዓለም አቀፍ ባለሃብቶች ጋር በእዳ ሽግሽግ ዙሪያ በፓሪስ ፈረንሳይ ድርድር መጀመሩን ዘግቧል። አንድ የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሥልጣን ዝርዝር መረጃ ሳይጠቅሱ የመንግሥት ልዑክ ወደ ፓሪስ ማቅናቱን አረጋግጠዋል። “ከቦንድ አበዳሪዎች ጋር የተያዙ አንዳንድ ስብሰባዎች ነበሩ” ሲሉ ለሮይተርስ የተናገሩት ምንጩ የስብስበዎቹ ውጤት መጨረሻ ላይ የሚገለፅ እንደሆነ በመጠቆም ስምምነነት ላይ ግን እንዳልተደረሰ ገልፀዋል። አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) አስተያየት እንዲሰጡ ተጠይቀው ወዲያ ምላሽ አልሰጡም። የቦንድ አበዳሪዎች ኮሚቴ ተወካዮችም እንዲሁ ምላሽ አልሰጡም። “ለመሠረተ ልማት ግንባታዎች” እንደሚውል የተነገረለት የቦንድ ሽያጭ በ10 ዓመታት ተመልሶ የሚከፈል እና የ6.625 በመቶ ወለድ ያለው መሆኑ በወቅቱ ተነግሮ ነበር። ኢትዮጵያ ያወጣችውን ቦንድ 50 በመቶ የአሜሪካ ባለሃብቶች፣ 35 በመቶ የእንግሊዝ ባለሀብቶች፣ 14 በመቶ የአውሮፓ አገራት ባለሃብቶች እና ሌሎች ገዝተዋል፡፡ በውሉ መሰረት ኢትዮጵያ በ2016 ዓ.ም. የቦንድ ብዱሩን ክፍያ መክፈል ያልቻለች ሲሆን፤ በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ በኩል የእዳ ሽግሽግ እንዲደረግ መርጣለች። በዚህ አካሄድ የሁለትዮሽ ብድር፣ ዩሮ ቦንድ እና ሌሎች የንግድ ብድሮች አንድ አይነት አመላለስ አላቸው። የኢትዮጵያ መንግሥት ከቦንድ ገዥዎች ጋር የእዳ ሽግግር ማድረጊያ መንገዶችን ለመለየት ለወራት ንግግር ሲያደርግ ቆይቷል። በቦንድ ገዥዎች እና በተበዳሪ መንግሥታት መካከል
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, አዉሮጳ, አፍሪቃ, ኢትዮጵያ, ኤኮኖሚ, ጀርመን, ፖለቲካ

ሆሮ ጉዱሩ :- በአቤዶንጎሮ ወረዳ የታጣቂዎቸ ጥቃት

ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤዶንጎሮ ወረዳ የታጠቂዎች እንቅስቃሴ እና ጥቃት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መጨመሩን የአካባቢው ነዋሪዎች አስታውቋል፡፡ በገጠራማ አካባቢዎች ላይ የነበረው የታጣቂዎች ጥቃት ወደ ከተማ ተዛምተው ትናንት ምሽት ወደ ወረዳው ዋና ከተማ ታጣቂዎች መግባታቸውንና በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ወደጫካ ሸሽተው እንደነበር ተገለፀ፡፡ DW Amharic ፡ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤዶንጎሮ ወረዳ የታጠቂዎች ጥቃት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጨመረ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች አስታውቋል፡፡ በገጠራማ አካባቢዎች ላይ ይስተዋል የነበረዉ የታጣቂዎች ጥቃት ወደ ከተማ ተዛምቶ  ትናንት ምሽት ወደ ወረዳው ዋና ከተማ ታጣቂዎች መግባታቸው እና በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ወደጫካ ሸሽተው እንደነበር ዶቼ ቬሌ ያነጋገራቸዉ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ ከባለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ በወረዳው የሚስተዋለው የታጣቂዎች ጥቃት የነዋሪውን የዕለት ተዕለት እንቅስቅስቃሴ እያወከ ነዉ፡፡ የወረዳው አስተዳደር በበኩሉ ትናንት ምሽት ጽንፈኛ ሐይሎች ያላቸው ታጣቂዎቸ በወረዳው ከተማ ተኩስ ከፍቶ እንደነበር አረጋግጧል። ታጣቂዎቹ ጸረ ሽምቅ ተብሎ በሚጠሩ የጸጥታ ኃይሎች ከአካባቢው እንዲባረሩ መደረጋቸዉንም  አመልክተዋል፡፡ ከወረዳው ዋና ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ ጫካ ሸሽቶ ቆይተዋል ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አስተዳደር ዋና ከተማ ሻምቡ በ 47 ኪሜ ገደማ ርቀት ላይ በሚትገኘው የአቤዶንሮ ወረዳ ትናንት ምሽት ታጣቂዎች ወደ ወረዳው መግባታቸውን ተከትሎ ከ 3 ሺ በላይ ነዋሪዎች ወደ ጫካ መሸሻቸውን ያነጋርናቸው ነዋሪዎች አመልክተዋል። በወረዳው መሰል ጥቃቶች የተደጋገሙ ሲሆን ትናንት ምሽት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኃይል ቱሉ ዋዩ ወደ ተባለው የወረዳው ዋና ከተማ መግባታቸውን በአካባቢው ከሚገኙ ጸረ ሽምቅ ከተባሉ
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, ኢትዮጵያ, ጀርመን, ፖለቲካ

የኑርንበርጉ ነዋሪ የኤሌክትሪካል ኢንጅነር ሳምሶን በቀለ ስኬት

የውጭ ዜጎች እድሉን ካገኙና ከተጣጣሩ በጀርመን ስኬታማ መሆን መቻላቸው ማሳያ የሆኑት አቶ ሳምሶን በአሁኑ ጊዜ ስደተኞች በምርጫ ዘመቻ ወቅት ስማቸው መጉደፉና ስብእናቸውም ዝቅ ተድርጎ መቅረቡ በጣም ይሰማቸዋል።ስደተኛን የሚጠሉት ቀኝ አክራሪዎች ጀርመን ውስጥ እየተጠናከሩ መምጣታቸው ከሚያሳስባቸው አንዱ ኤሌክትሪካል ኢንጅነር ሳምሶን በቀለ ናቸው።
Posted in ጀርመን