Blog Archives
ጥብቅ ወታደራዊ መረጃ!በእግረኛ ሰራዊቱ ተስፋ የቆረጠው የዐብይ አህመድ አገዛዝ ሰው ከልባ አውሮፕላንን በመጠቀም በተመሣሣይ ሰዓት በተለያዩ ቦታዎች ላይ ጥቃት ለመፈፀም መዘጋጀቱ ተሰምቷል።ጥቃቱ ይፈፀማል የተባለው ጨለማን ተገን በማድረግ ሲሆን፡ ጥቃት ይፈፀምባቸዋል የተባሉ አከባቢዎች ተለይተዋል ሲሉ የመረብ ሚዲያ ወታደራዊ ምንጮች ገልፀዋል።ጥቃቱ የሚፈፀመው የፋኖ ጦር ቤዝ ተብለው በተለዩ ቀጠናዎችና የፋኖ አመራሮች በስፋት ይገኙባቸዋል በተባሉ ቦታዎች ላይ ነው።የመረብ ሚዲያ ወታደራዊ ምንጭ እንደገለፁት፡ ጥቃቱ የሚፈፀመው በተመሳሳይ ሰዓት በተለያዩ ቦታዎች ላይ ነው ያሉ ሲሆን፡ ለዚህም ሰው አልባ አውሮፕላኖች ተዘጋጅተዋል ብለዋል።ጥቃቱ የሚፈፀመው ጨለማን ተገን በማድረግ(አጥቢያ ለሊት ላይ) ነው የሚሉት ምንጫችን፡ ኦፕሬሽኑ የሚመራው አዲስ አበባ መገናኛ አከባቢ በሚገኝ የወታደራዊ ደህንነት ቢሮ ነው ሲሉ ለጣቢያችን ተናግረዋል።ጥቃቱ ዛሬ መስከረም 21/2018 ዓ/ም አጥቢያ ለሊቱን ወይም በቀጣዮቹ ቀናት ሊፈፀም ይችላል ተብሏል።ስለሆነም፡ ሕዝቡ በቂ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክት ያስተላለፉት ምንጫችን፡ በተለይ የፋኖ አመራሮችና አባላት ለጥቃት ከሚያጋልጡ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠቡ አሳበዋል።

በአማራ ክልል ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን የተሰራ ርብራብ እንጨት ተደርሞሶ የ30 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
መረጃውን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አዣዥ ዋና ኢንስፔክተር አሕመድ ገበየሁ ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነግረውታል፡፡
የአደጋው ምክንያት ለቤተክርስቲያኑ ሕንጻ ግንባታ በተሠራ የእንጨት መወጣጫ ርብራብ ላይ መሸከም ከሚችለው በላይ ሰዎች ለጉብኝት በመውጣታቸው ነው ብለዋል።
በአደጋው የ30 ሰዎች ሕይዎት ወዲያውኑ አልፏል ሲሉ ዋና ኢንስፔክተር አሕመድ አስረድተዋል።
ከ200 በላይ ሰዎች ከቀላል እስከ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ሲኾን ይህም የሟቾችን ቁጥር ከፍ ሊያደርገው ይችላል ተብሏል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ርብራብ እንጨት ተደርሞሶ ሕይወታቸውን ባጡ ምእመናን የተሰማቸውን ጥልቅ ኃዘን ግልጸዋል፡፡
“የቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ተጠናቆ ምርቃቱን በጉጉት እየጠብቀን ባለንበት ይህ አስከፊ ኀዘን በመከሰቱ ጥልቅ ኃዘን ተሰምቶናል” ብለዋል።
በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን የቅዱሳን አምላክ ነፍሳቸውን በደጋጎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን አጠገብ ያሳርፍልን ጉዳት ደርሶባቸው በጤና በሆስፒታል በሕክምና ለሚገኙ ወገኖቻችን ፈጣሪ በምሕረቱ እንዲጎበኛቸው እንጸልያለን ብለዋል።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ኢትዮጵያ ከ10 ዓመታት በፊት ለሸጠችው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ከዓለም አቀፍ የቦንድ ገዢዎች ጋር የእዳ ሽግሽግ እንዴት ማድረግ እንዳለባቸው መደበኛ ንግግር መጀመሯን ሮይተርስ የዜና ወኪል ምንጮቹን ጠቅሶ ዘገበ።
ሮይተርስ ቀደም ብሎ በብሉምበርግ የወጣውን ዘገባ በማረጋገጥ ከዓለም አቀፍ ባለሃብቶች ጋር በእዳ ሽግሽግ ዙሪያ በፓሪስ ፈረንሳይ ድርድር መጀመሩን ዘግቧል።
አንድ የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሥልጣን ዝርዝር መረጃ ሳይጠቅሱ የመንግሥት ልዑክ ወደ ፓሪስ ማቅናቱን አረጋግጠዋል።
“ከቦንድ አበዳሪዎች ጋር የተያዙ አንዳንድ ስብሰባዎች ነበሩ” ሲሉ ለሮይተርስ የተናገሩት ምንጩ የስብስበዎቹ ውጤት መጨረሻ ላይ የሚገለፅ እንደሆነ በመጠቆም ስምምነነት ላይ ግን እንዳልተደረሰ ገልፀዋል።
አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) አስተያየት እንዲሰጡ ተጠይቀው ወዲያ ምላሽ አልሰጡም።
የቦንድ አበዳሪዎች ኮሚቴ ተወካዮችም እንዲሁ ምላሽ አልሰጡም።
“ለመሠረተ ልማት ግንባታዎች” እንደሚውል የተነገረለት የቦንድ ሽያጭ በ10 ዓመታት ተመልሶ የሚከፈል እና የ6.625 በመቶ ወለድ ያለው መሆኑ በወቅቱ ተነግሮ ነበር።
ኢትዮጵያ ያወጣችውን ቦንድ 50 በመቶ የአሜሪካ ባለሃብቶች፣ 35 በመቶ የእንግሊዝ ባለሀብቶች፣ 14 በመቶ የአውሮፓ አገራት ባለሃብቶች እና ሌሎች ገዝተዋል፡፡
በውሉ መሰረት ኢትዮጵያ በ2016 ዓ.ም. የቦንድ ብዱሩን ክፍያ መክፈል ያልቻለች ሲሆን፤ በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ በኩል የእዳ ሽግሽግ እንዲደረግ መርጣለች። በዚህ አካሄድ የሁለትዮሽ ብድር፣ ዩሮ ቦንድ እና ሌሎች የንግድ ብድሮች አንድ አይነት አመላለስ አላቸው።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከቦንድ ገዥዎች ጋር የእዳ ሽግግር ማድረጊያ መንገዶችን ለመለየት ለወራት ንግግር ሲያደርግ ቆይቷል።
በቦንድ ገዥዎች እና በተበዳሪ መንግሥታት መካከል

የፎቶው ባለመብት, SM
የምስሉ መግለጫ, ጥቃት የተፈፀመበት ሳንቃ ጤና ጣቢያ ከፊል ገጽታ
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ቅዳሜ መስከረም 17/2018 ዓ.ም. ጤና ጣቢያ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ነፍሰ ጡር እናትን ጨምሮ የአራት “ሰላማዊ ሰዎች” ሕይወት ሲያልፍ 10 በላይ ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች እና የሕክምና ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ።
ጥቃቱ ከዞኑ እና ከወረዳው ዋና ከተማ ወልዲያ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሳንቃ በተባለች የክላስተር ከተማ በሚገኝ ጤና ጣቢያ ላይ ከቀኑ 06፡00 አካባቢ መፈፀሙን አራት የዓይን እማኞች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
የዞኑ አስተዳደር ስለጥቃቱ እና ስለደረሰው ጉዳት ለመናገር እንደማይችል ለቢቢሲ ተናግሯል።
በስፍራው የነበሩ የጤና ጣቢያው አንድ ባለሙያ መሣሪያው በዋናነት ፊት ለፊት በሆነው እና ታካሚዎች ተኝተው በሚታከሙበት “5 ቁጥር” በተባለው ክፍል ላይ ማረፉን ተናግረዋል።
ከጥቃቱ እንደተረፉ የተናገሩት የጤና ጣቢያው ባልደረባ ጥቃቱ የደረሰበትን ቅፅበት ሲገልፁ “ምንም ራሴን አላውቅም፤ መሬት ተሰንጥቆ የዋጠን ነው የመሰለን። ከጎኔ የነበሩት ሲወድቁ እኔን እግዚአብሔር ነው የከለለኝ” ሲሉ እማኝነታቸውን ሰጥተዋል።
ፍንዳታውን ሰምተው በፍጥነት አካባቢው ላይ መድረሳቸውን የተናገሩ ሌላ የዓይን እማኝ ጤና ጣቢያው ውስጥ የነበረ የቤተሰብ አባላቸው ከጥቃቱ መትረፉን ገልፀው፤ ዘግናኝ ሁኔታ መመልከታቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ወከባ እና ተጨማሪ የጥቃት ስጋት በመፈጠሩ “በደመ-ነፍስ . . .የደማውም፤ የተመታውም እየተዛዘለ ነው የወጣው” ሲሉ ክስተቱን ተናግረዋል።
የቆሰሉ ሰዎችን ማውጣታቸውን እና አስከሬን ማንሳታቸውን የተናገሩ ሌላ የዓይን እማኝ ደግሞ ለመግለፅ የሚከብድ ሁነት ማየታቸውን ተናግረዋል።
“ፍንጣሪው
የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምክንያት “በታችኛው ተፋሰስ የሚኖሩ የሚሊዮኖችን ሕይወት አደጋ ላይ ጥላለች” ብለው በመክሰስ አገራቸው ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፉ የፍትሕ ፍርድ ቤት እንደምትወስድ ተናገሩ።
በተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ምክትል ቋሚ ተወካይ ዮሴፍ ካሳዬ ለግብፁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሰጡት ምላሽ፤ “ግብፅ ስለ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ያደረገችው ንግግር መሠረት አልባ እና አሳሳች ነው” ሲሉ አጣጥለዋል።
ግብፅ “ስለ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ተዓማኒ ያልሆኑ ክሶችን በተደጋጋሚ ወደ ተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት አቅርባለች” ሲሉም አክለዋል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/ce9rmpxe88do
የዩናይድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ፣ ኢትዮጵያ ለዉጪ የኢንቨስትመንት ፈታኝ ሐገር ናት » አለ
የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሰሞኑን ባወጣዉ መረጃ “የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ኹኔታ “ለአሜሪካ እና ለሌሎች የውጭ ኩባንዮች ፈታኝ ነው” ሲል አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መንግሥት የከተሞች የመንገድና የወንዝ የዳርቻ ወይም የኮሪደር ልማት የባለሃብቶችን መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ የማድረግ ፍላጎት “ገድቧል” ሲል ነው የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በሪፖርቱ ያመለከተው። ዘገባዉ “የውጭ ይዞታዎችን ጨምሮ በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች እና የንግድ ድርጅቶች ንብረታቸው ያለ በቂ ማስጠንቀቂ መፍረሱን ተከትሎ እዚህ ድምዳሜ ላይ መድረሱን ይጠቅሳል።
ግጭት በሚካሄድባቸው አማራና ኦሮሚያ ክልሎች የመንቀሳቀስ ሁኔታ ገደብ መኖሩን የጠቀሰው ይህ ሪፖርት ባለሥልጣናት ወይም ታጣቂ ቡድኖች በተደጋጋሚ የግል ንብረቶችን እንደሚነጥቁ፣ የንብረት ባለቤትነት መብቶች በቂ ጥበቃ እያገኙ እንዳልሆነ ጭምር አመልካቾችን ጠቅሷል።
የፖለቲካ ኢኮኖሚ ተንታኙ አቶ ሸዋፈራሁ ሽታሁን በሰጡት አስተያየት፤ «የመጀመርያው የሰላም ጠቋሚ – ሰላምና ፀጥታ ነው። ሁለተኛው ደግሞ ግልጽነት እና ተጠያቂነት። ለምሳሌ አንድ ምርት ወይም አገልግሎት ከአንድ አካባቢ ወደ ሌላ አካባቢ ሲንቀሳቀስ ምን ያህል ዋስትና አለው? የሚለው ነገር ይታያል። ዋስትና ብቻም ሳይሆን ለዚያ ለንብረትህ ሕጋዊ ጥበቃ የሚያደርግ የመንግሥት የአሠራር ሥርዓት ጥብቀቱ ምን ያህል ነው? የሚለውም ይጠናል።» ማለታቸውን የአዲስ አበባው ወኪላችን ሰሎሞን ሙጬ ዘግቧል።
የትግል ስልት በጠላት አይመረጥም
ትግል ጠላት ምን ይለኛል ተብሎ እንደማይደረግ ሁሉ ስልቱንም ከጠላት መጠበቅ አይቻለም
=========================================
ትግል ሲታሰብ ታጋዩ የመታገያ ምክኛቶቹ በስኬት እንዲቋጩ የመታገያ ስልቶች ከወዲሁ ይቀይሳል፡፡ ስልቶቹ የአጭር እና የረጅም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በየግዜው እንደ ሁኔታ ለውጥ የሚቀየሱ ስልቶች ግዜን እና የጠላትን ጥንካሬ ማለፊያ እና ማዳከሚያ ናቸው፡፡ እረጅሙ የትግል ስልት ግን በጠላት በኩል ወይንም አለማቀፋዊ እና ሐገራዊ ሁኔታ እስካልተቀየረ እስከድል የሚቀጥል ስልት ነው፡፡ ለምሳሌ የመሳርያ ትግል ምርጫው የሆነው ባለው ሁኔታ ተገዶ መሳርያ እንዲያነሳ የተገደደ ትግል በመሆኑ ስለሆነ የመሳሪያ አፈሙዝ የሚዘቀዘቀው ከድል በኋላ ነው፡፡ ወይንም ትግሉ የታሰበለትን አላማ ሲያሟላ ብቻ ነው፡፡
የፋኖን ትግል በዚህ ልናይ እንችላለን፡፡ በሐገራችን የሰፈነው ዘር ተኮር ፖለቲካ መሰረቱ ጸረ አማራ እና ጸረ ኢትዮጵያ ነው፡፡ የስርአቱ አቀንቃኞች አማራን ማጥፋት ኢምፔሪያል ኢትዮጵያን ማዳከም እና የተከፋፈሉ ትንንሽ ሀገራት መመስረት ነበር ባብዛኛው አሟልተዋል፡፡ በጠላትነት የፈረጁትን ሕዝብም እስካሁን የጥፋት ጦርነት ከፍተው እየገደሉት፤ እያፈናቀሉት እና በሐገሩ ስደተኛ እያረጉት ነው፡፡
ይህ ሁኔታ የወረደበት የዚህ ትውልድ የአማራ ወጣት ወዶ ሳይሆን ተገዶ መሳርያ አንስቷል ይህ መሳርያ እስከ ድል ይቀጥላል፡፡ ትውልዱ የተነሱበትን ጠላቶቹን ለመመከት ብሎም ለማቸነፍ የአጭር እና እረጅም ስልቶቹን በስራ ያውላል፡፡ ይህ ሲሆን መታገያ ስልቱን ጠላት ሊወስንለት አይችልም፡፡ ጠላት አናጥሎ ሊያጠፋው ስለሆነ አላማው በአጭር የትግል ስልቶች በተለያየ ግዜ ለግዜው በሚመጥኑ ስልቶችን በመጠቀም ጠላትን ይታገላል ትግሉን ከግብ ያደርሳል፡፡
ትብብር አስፈላጉ ሆኖ ሲገኝ ትብብሩን ለፋኖ ታጋዮች የሚመርጥለት የአብይ
ከአውሮፓዊያኑ 2016 እስከ 2024 ባሉት ዓመታት ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዘጋት ከአፍሪካ የቀዳሚነት ደረጃ መያዟን “ኢንተርኔት ሸትዳውን ኢን አፍሪካ” የተሠኘ ጥናት አመልክቷል።
በአሕጉር ደረጃ በተጠቀሠው ጊዜ 190 ያህል የኢንተርኔት መዘጋት ክስተቶች እንደተመዘገቡ የጠቀሠው ጥናቱ፣ ኢትዮጵያ በዚህ ጊዜ ውስጥ 30 ጊዜ ኢንተርኔት ማቋረጧን ገልጧል።
የኢንተርኔት መቋረጥ በኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ተጽዕኖ እንደሚፈጥርም ጥናቱ አመልክቷል።
21 ጊዜ ኢንተርኔትን በመዝጋት ሁለተኛ ደረጃ የያዘችው ሱዳን ስትኾን፣ በሦስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው አልጀሪያ ናት። በ2016 ዓ፣ም በአሕጉር ደረጃ 14 የነበረው የኢንተርኔት መዘጋት ብዛት፣ በ2024 ዓ፣ም ወደ 28 ጨምሮ እንደነበር በጥናቱ ላይ ተጠቅሷል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧቱ 12:00 ሰዓት የተጀመረው ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በአምስቱም ኮሮች እና በዕዙ ልዩ ዘመቻ ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ አስደናቂ ድሎችን እያስመዘገበ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
2ተኛ ቀኑን በያዘው “ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በዛሬው ዕለት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም ተጠንክሮ የቀጠለ ሲሆን በዚህ ተጋድሎም አገዛዙ ለሁለት ዓመት የሰሜን ወሎ ዞን የጦር ማዘዣ ጣቢያ አድርጎት የነበረው የግዳን ወረዳ ሙጃ ከተማ በርካታ ምሽጎችን በመስበር በምኒልክ ዕዝ ሰራዊት በቁጥጥር ስር ውሏል።
በዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በትላንትናው ዕለትና በዛሬው ዕለት ነጻ የወጡ ቦታዎች:-
• ሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ ዋና መቀመጫ የሆነችው ሙጃ ከተማ ጨምሮ ሙሉ ለሙሉ ወረዳው በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።
• ሰሜን ወሎ ዞን ጋዞ ወረዳ መቀመጫ የሆነችው አስታይሽን ጨምሮ ወረዳው ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።
• ሰሜን ወሎ ዞን ራስ አንጎት ወረዳ መቀመጫ የሆነችውን አሁን ተገኝ ከተማን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።
• ሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ ብልባለ ከተማን ጨምሮ ከሹምሽሃ ቀበሌ ውጭ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።
• ሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ከወልደያ ከተማ ውጭ ያለው ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውሏል።
• ሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ ዋና መቀመጫ የሆነችው ኩርባ ከተማን ጨምሮ ወረዳውን ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር
የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት፣ የሸገር ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጋዜጠኞች ትዕግስት ዘሪሁንና ምንታምር ፀጋው በዋስ እንዲለቀቁ የስር ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ አፀደቀ፡፡የፌዴራሉ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ፣ጋዜጠኞቹን ትዕግስት ዘሪሁንና ምንታምር ፀጋው በ50 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ፣ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በሰጠው ውሳኔ ቅር በመሰኘት፣ ለፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ጠይቆ ነበር፡፡ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዛሬው ችሎቱ ፣ ተጠርጣሪዎቹ ከእስር ቢለቀቁ ማስረጃ ያጠፉብኛል ፣ የሚለውን የፖሊስ ማመልከቻ ባለመቀበል፣ የዋስ መብታቸው እንዲከበር ወስኗል፡፡በሸገር ኤፍ ኤም ጋዜጠኞች አርታኢ ትዕግስት ዘሪሁንና ሪፖርተር ምንታምር ፀጋው፣ ባለፉት ቀናት፣ የተካሄደው የፍርድ ቤት ውሎ የሚከተለውን ይመስላል፡፡ ነሀሴ 24 ቀን 2017፣ በሸገር ኤፍ ኤም ሬዲዮ የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ያቀረቡት የህክምና ባለሙያዎች ፣ ከጤና ሚኒስቴር የተሰጠውን መፍትሄ ሰርኩላር በመጥቀስ፣ እንዴት እንደሚመለከቱት የሚጠይቅ ዜና ተላልፎ ነበር፡፡ በቃለ መጠየቅ የተደገፈው ዜና፣ “የሽብር ፈጠራ ወንጀል ነው” ብሎ አርታኢዋን ትዕግስት ዘሪሁንና ሪፖርተሯን ምንታምር ፀጋውን የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ነሐሴ 28/2017 ከመስሪያ ቤት እና ከቤት አግኝቶ በቁጥጥር ስር አዋላቸው፡፡በማግስቱ፣ ብሔራዊ በዓል በመሆኑ፣ ጋዜጠኞቹ ፍርድ ቤት የቀረቡት፣ በታሰሩ በሁለተኛ ቀን ነሀሴ 30/2017 ነበር፡፡ያንለትም ፍርድ ቤቱ፣ በፋይል ብዛት ምክንያት፣ ከሶስት ቀናት በኋላ፣ ጳጉሜ 3/2017 እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡በቀጠሮው ቀን፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራና ጋዜጠኞቹ እነ ትዕግስት ዘሪሁን በጠበቃቸው ተወክለው ቀረቡ፡፡ፖሊስ፣ ጋዜጠኞቹን በቁጥጥር ስር ያዋለበትን ምክንያትና፣ ይቀረኛል የሚላቸውን የምርመራ ሂደቶች፣ ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል፡፡የፌዴራል ፖሊስ ትዕግስት ዘሪሁንና
በተመድ ዓመታዊ የፈጠራ ሪፖርት ኢትዮጵያ ከ139 አገሮች 134ኛ ደረጃ ተሰጣት – ሪፖርተር
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) አዕምሯዊ ንብረት መብቶች ድርጅት እ.ኤ.አ. የ2025 ዓመታዊ የፈጠራ ብቃት ሪፖርት፣ ኢትዮጵያን ከዓለም 139 አገሮች 134ኛ፣ ከአፍሪካ ደግሞ 28ኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አስታወቀ፡፡
የአገሪቱን የፈጠራ ቁመና ለመለካት ከ80 በላይ አመላካች መሥፈርቶችን መጠቀሙን በማስታወቅ የጥናትና ምርምር፣ የካፒታል ፍሰት፣ ከፍተኛ ቴክኖሎጂዎችን ለውጭ አገር ገበያ የማቅረብ አቅም፣ የአዕምሯዊ ንብረት አያያዝና በርካታ ጉዳዮችን በመዳሰስ ባለ 300 ገጽ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡
ዓመታዊ ሪፖርቱ ሌሴቶን በ132ኛ፣ ጊኒን በ23ኛ፣ ኢትዮጵያን በ134ኛ፣ ማሊን በ35ኛ፣ ቬኑዘዌላን በ136ኛ፣ ኮንጎን በ137ኛ፣ አንጎላን በ38ኛ እና ኒጀርን በ39ኛ ደረጃ መድቧቸዋል፡፡
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2024 130ኛ ደረጃ ይዛ የነበረ ሲሆን፣ በዚህኛው ዓመት ደረጃዋ ማሽቆልቆሉን ሪፖርቱ ያመላክታል፡፡ ይሁን አንጂ በኢትዮጵያ ቴክኖሎጂን ከኢንቨስትመንት ጋር በማስተሳሰርና የተሻለ ምኅዳር በመፍጠር ረገድ መሻሻል መኖሩን ያስረዳል፡፡
ዓመታዊ ጥናቱ እንደሚያሳየው አጠቃላይ የፈጠራ ደረጃዋ 134ኛ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በተቋማት ብቃት 122ኛ፣ በሰው ሀብትና ጥናትና ምርምር 139ኛ፣ በመሠረተ ልማት 130ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች ይላል፡፡ በተሰባጠረ የቴክኖሎጂ ገበያ 133ኛ፣ በቢዝነስ ምኅዳር 134ኛ፣ በዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር 82ኛ፣ እንዲሁም በቴክኖሎጂ የፈጠራ ሥራዎች 139ኛ ላይ መድቧታል፡፡
ዓመታዊ ሪፖርቱ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ኬንያና ሩዋንዳ ያነሰ አፈጻጸም ብታሳይም፣ በኦንላይን የመንግሥት አገልግሎት መልካም ጅማሮ፣ የብሮድባንድ የሞባይል ኢንተርኔት ተደራሽነትና ዲጂታል ምኅዳሮች ላይ መሻሻል እያሳች ያለች አገር መሆኗን አስረድቷል፡፡
ኢትዮጵያ በፈጠራ የተሻሉ የወደፊት ዕድሎች እንዳሏት ቢያሳይም፣ አሁንም የቀጠሉ መሰናክሎቿ፣ በተለይም
‹‹በሁለተኛው የሥልጣን ዘመኔ ሰባት ወራት የኢትዮጵያና ግብፅን ጨምሮ ሰባት ጦርነቶችን አስቁሜያለሁ›› ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ
የተባበሩት መንግሥታት የመሪዎች ጠቅላላ ጉባዔ በትናንትናው ዕለት በኒውዮርክ ከተማ በተከፈተበት ወቅት ንግግር ያደረጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው የመጀመሪያዎቹ ሰባት ወራት ውስጥ ብቻ ሊቆሙ አይችሉም የተባሉ ሰባት ጦርነቶችን ማስቆም መቻላቸውን ገለጹ። ከእነዚህ ጦርነቶች መካከል አንዱ የኢትዮጵያና የግብፅ ጦርነት መሆኑን ተናግረዋል። ‹‹ሁለተኛውን የሥልጣን ዘመኔን በጀመርኩ በሰባት ወራት ውስጥ ብቻ ሊቆሙ… https://ethiopianreporter.com/146191/
ኬንያ፣ የሙስሊም ወንድማማቾችንና “ሒዝብ ኡር ጣህሪር” የተባለውን ቡድን አሸባሪ ድርጅት በማለት ፈርጃለች።
ሙስሊም ወንድማማቾችን በአሸባሪነት ከፈረጁ አገራት መካከል፣ ግብጽ፣ ሳዑዲ ዓረቢያ፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች፣ ባሕሬን እና ሩሲያ ይገኙበታል። ሁለቱ ቡድኖች በአገሪቱ ውስጥ የሽብር ጥቃት መፈጸማቸውን የሚያሳይ መረጃ ባይኖርም፣ የአሸባሪነት ፍረጃው ግን ኬንያ የጽንፈኝነት ርዕዮተ ዓለምን ከወዲሁ ለመቅጨት የወሰደችው ርምጃ እንደኾነ ታምኖበታል። በፍረጃው መሰረት፣ የቡድኖቹ አባል መሆን፣ ለቡድኖቹ የገንዘብ መዋጮ ማሰባሰብ ወይም ከቡድኖቹ ጋር የተገናኘ ፕሮፓጋንዳ ማሠራጨት በወንጀል የሚያስጠይቁ ይኾናሉ።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ አሜሪካዊ ዜግነት ያላቸው ሰዎች የቪዛ ጊዜያቸው ሲያልፍ የሚጣልባቸውን ቅጣት ለመክፈል ኢምባሲው ከእንግዲህ ብድር ለመስጠት ፍቃድ እንደሌለው አስታውቀዋል። ማሲንጋ አሜሪካዊያን ቪዛቸው ከማብቃቱ በፊት ከኢሚግሬሽን የቪዛ ማራዘሚያ ወይም የመኖሪያ ፍቃድ እንዲጠይቁ አሳስበዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ አሜሪካዊያን የአገሪቱን የኢሚግሬሽን ደንቦች እንዲያከብሩና ቪዛቸው ወይም የመኖሪያ ፍቃዳቸው ጊዜ ከማለፉ በፊት እንዲያሳድሱም ማሲንጋ መክረዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት የቪዛ ጊዜ አሳልፎ መቆየትንና ሕገወጥ ስደትን ለመቀነስ ሲል የቪዛ ጊዜ አሳልፈው የሚቆዩ የውጭ ዜጎች ላይ የሚጣለውን ቅጣት ባንድ ቀን ወደ 30 የአሜሪካ ዶላር ማሳደጉን በኅዳር ወር ማሳወቁ ይታወሳል። መንግሥት አሜሪካዊያን እዳቸውን በሙሉ በዶላር እስኪከፍሉ ከአገር እንዳይወጡ መከልከል እንደሚችል መታወቅ አለበት ብለዋል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልን ከኦሮሚያ ክልል ጋር የሚያገናኘው መንገድ በጸጥታ ችግር ለዓመታት በመዘጋቱ፣ የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች ለማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መጋለጣቸውን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ልዑካን ቡድን መናገራቸው ምክር ቤቱ ገልጧል፡፡ ይታወቃል። በውይይቱ ወቅት፣ በክልሉ የሪፈራል ሆስፒታል ባለመኖሩ የክልሉ ነዋሪዎች ወደ አጎራባች ክልሎችና አዲስ አበባ በመሄድ ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆኑን አውስተዋል ተብሏል። ነዋሪዎቹ፣ መንግሥት በክልሉ ውስጥ አንድ ሪፈራል ሆስፒታል እንዲገነባላቸው መጠየቃቸውንም መረጃው አመልክቷል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌትናንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ፣ ፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ላይ ሌላ ዙር ጦርነት ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ ይገኛል በማለት ዛሬ በኢትዮጵያ ከተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ሃላፊ ጋር በተወያዩበት ወቅት መናገራቸውን የክልሉ ኮምንኬሽን አስታውቋል። ጀኔራል ታደሰ፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ የጦርነት ደመናን ለመግፈፍና ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑን ለሃላፊው እንዳረጋገጡላቸው ቢሮው ገልጧል። በትግራይ በኩል የሚጀመር ጦርነት አይኖርም ያሉት ጀኔራል ታደሰ፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ በትግራይ የተሟላና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከፌደራል መንግሥቱ፣ ከዓለማቀፍ ድርጅቶችና ከውጭ ዲፕሎማቶች ጋር የቅርብ ግንኙነት በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጸዋል ተብሏል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር ቤተ-አማራ ክፍለ ጦር በደሴ ዙሪያ ከፍተኛ ውጊያ በማድረግ ድል ተቀናጁ፡፡
በቀን 11/01/2018 ዓ.ም እና በቀን 12/01/2018 ዓ.ም በደሴ እና በግሸን ዙሪያ ጠላት በከባድ መሳሪያ የታገዘ ዉጊያ ቢከፍትም የቤተ-አማራዎቹ ንስሮች ከፍተኛ ድል እየተቀናጁ ይገኛሉ::
አገዛዙ አመታዊ ግሸን ደብረ ከርቤ ክብረ በዓል በፋኖ መከበር የለበትም በሚል እብሪት ከደሴ ከተማ ውስጥ ጀምሮ እስከ አምባሰልና ተለያየን ዙ23ን ጨምሮ የተለያዩ ከባድ መሳሪያዎችን እየተጠቀመ ቢሆንም በነበልባሎቹ ቤተ-አማራ ልጆች በአግባቡ እየተመከተ እና በመልሶ ማጥቃት በርካታ የጠላት ሃይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ብሎም ይዞታቸውን በማስከበር ድል እየተቀዳጁ ይገኛሉ::
ተጋድሎው ለሁለት ተከታታይ ቀናት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በዛሬው ዕለት ንጋት ጀምሮ ጠላት ከኩታበር እና ደላንታ ያመጣውን ሃይል ይዞ ውጊያ ቢያደርግም ተለያየን ላይ አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ ለማፈግፈግ ተገዷል:: ጠላት በደረሰበት ሽንፈት ምክንያት እየሸሸ ባለበት ሁኔታ ንስሮቹ እንዳይከተሉት ቢራ የጫነ ተሳቢ መኪና ጎማ በመምታት መንገድ ዘግቶ ውሏል::
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
“አድማ ብተና ግልገል ፋኖ ነው፡ ካሁኑ መጥፋት አለበት” የመከላከያ ሰራዊት አዛዦች!
የአገዛዙ ወታደሮች በተስፋ መቁረጥ ተሞልተዋል። በለስ የቀናቸው ከስምሪት ቀጠናቸው እየጠፉ ሕይወታቸውን ሲታደጉ፡ ይሄንን ወርቃማ እድል ማገኘት ያልቻሉት ደግሞ እርስ በእርሳቸው ተኩስ ከፍተው እየተገዳደሉ ነው።
መከላከያ ሰራዊቱ የቡድን መሣሪያ ጭምር አዙሮ በመተኮስ በርካታ የሚሊሻና አድማ ብተና አባላትን ገድሏል።
የግጭቱ መነሻ “በተሳሳተ መንገድ እየመራችሁ ወስዳችሁ በፋኖ እንድንጠቃ አድርጋችሁናል” በሚልና “በውጊያ ወቅት በቂ እገዛ እያደረጋችሁልን አይደለም” በሚሉ ምክኒያቶች ነው ተብሏል።
የመከላከያ ሰራዊት አዛዦችም “አድማ ብተና ግልገል ፋኖ ነው፡ ካሁኑ መጥፋት አለበት” የሚል መመሪያ መስጠታቸው ተሰምቷል።
ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤዶንጎሮ ወረዳ የታጠቂዎች እንቅስቃሴ እና ጥቃት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መጨመሩን የአካባቢው ነዋሪዎች አስታውቋል፡፡ በገጠራማ አካባቢዎች ላይ የነበረው የታጣቂዎች ጥቃት ወደ ከተማ ተዛምተው ትናንት ምሽት ወደ ወረዳው ዋና ከተማ ታጣቂዎች መግባታቸውንና በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ወደጫካ ሸሽተው እንደነበር ተገለፀ፡፡
DW Amharic ፡ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤዶንጎሮ ወረዳ የታጠቂዎች ጥቃት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየጨመረ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች አስታውቋል፡፡ በገጠራማ አካባቢዎች ላይ ይስተዋል የነበረዉ የታጣቂዎች ጥቃት ወደ ከተማ ተዛምቶ ትናንት ምሽት ወደ ወረዳው ዋና ከተማ ታጣቂዎች መግባታቸው እና በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ወደጫካ ሸሽተው እንደነበር ዶቼ ቬሌ ያነጋገራቸዉ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ ከባለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ በወረዳው የሚስተዋለው የታጣቂዎች ጥቃት የነዋሪውን የዕለት ተዕለት እንቅስቅስቃሴ እያወከ ነዉ፡፡ የወረዳው አስተዳደር በበኩሉ ትናንት ምሽት ጽንፈኛ ሐይሎች ያላቸው ታጣቂዎቸ በወረዳው ከተማ ተኩስ ከፍቶ እንደነበር አረጋግጧል። ታጣቂዎቹ ጸረ ሽምቅ ተብሎ በሚጠሩ የጸጥታ ኃይሎች ከአካባቢው እንዲባረሩ መደረጋቸዉንም አመልክተዋል፡፡
ከወረዳው ዋና ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ ጫካ ሸሽቶ ቆይተዋል
ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አስተዳደር ዋና ከተማ ሻምቡ በ 47 ኪሜ ገደማ ርቀት ላይ በሚትገኘው የአቤዶንሮ ወረዳ ትናንት ምሽት ታጣቂዎች ወደ ወረዳው መግባታቸውን ተከትሎ ከ 3 ሺ በላይ ነዋሪዎች ወደ ጫካ መሸሻቸውን ያነጋርናቸው ነዋሪዎች አመልክተዋል። በወረዳው መሰል ጥቃቶች የተደጋገሙ ሲሆን ትናንት ምሽት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኃይል ቱሉ ዋዩ ወደ ተባለው የወረዳው ዋና ከተማ መግባታቸውን በአካባቢው ከሚገኙ ጸረ ሽምቅ ከተባሉ
የሸገር ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጋዜጠኞች ትዕግስት ዘሪሁንና ምንታምር ጸጋው ላለፉት 17 ቀናት በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ ሸገር ዘግቧል።
ፖሊስ ጋዜጠኞቹን በቁጥጥር ስር ያዋላቸው፣ ለጤና ባለሞያዎች ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ጤና ሚንስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ ዙሪያ ባአንድ የሕክምና ባለሙያ አስተያየት ላይ ጣቢያው በሠራው ዘገባ ሳቢያ መኾኑን ለፍርድ ቤት አስረድቷል ተብሏል።
ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጋዜጠኞቹ በገንዘብ ዋስትና እንዲለቀቁ ወስኖ የነበረ ቢኾንም፣ ፖሊስ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ እንደጠየቀና ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ለመስከረም 12፣ ቀጠሮ እንደሠጠ ዘገባው አመልክቷል።
ኢሕአፓ፣ መኢአድ፣ እናት ፓርቲ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞከራሲያዊ ፓርቲና የአማራ ግዮናዊ ንቅናቄ ቅንጅት መስርተዋል።
ፓርቲዎቹ ቀድም የመሠረቱት፣ ኃይላቸውን ለማሰባሰብና በምርጫ ወቅት ትብብር ለማድረግ መኾኑን የኢሕአፓ ዋና ጸሐፊ ሚስጥረሥላሴ ታምራት ለዋዜማ ተናግረዋል፡፡
ኾኖም ፓርቲዎቹ በቀጣዩ ምርጫ ስለመሳተፍ ገና ያልወሰኑ ሲኾን፣ ቅንጅቱ ወደፊት አስቻይ ኹኔታ መኖር አለመኖሩን አጥንቶ ይወስናል ተብሏል።
ቅንጅቱ መስከረም 10 በይፋዊ ፊርማ እውን እንደሚሆን ሰምተናል፡፡
የኢትዮጵያ የእዳ ጫና አስተማማኝ ደረጃ ላይ አይደለም ሲል ዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም ባወጣው አዲስ ሪፖርት አስጠንቅቋል።
ተቋሙ፣ አገሪቱ ከፍተኛ እዳ እንደተጫናትና ከፍተኛ የጥሬ ገንዘብ እጥረትና የውጭ እዳ የመክፈል አቅም ውስንነት እንደገጠማት ገልጧል።
የአገሪቱ የውጭ እዳ ጫና ወሳኝ ደረጃዎችን ማለፉን፣ ከአጠቃላይ ዓመታዊ የአገሪቱ የወጪ ንግድ 206 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱንና አገሪቱ እዳዋን ለመክፈል የምታወጣው ወጪ በተያዘው ዓመት ከመንግሥት አጠቃላይ ገቢ 37 ነጥብ 7 በመቶውን እንደሚሸፍንም ተቋሙ ጠቅሷል።
ተቋሙ፣ የፖለቲካና ማኅበራዊ ተጽዕኖዎች የመንግሥትን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሊያዘገዩት ወይም ሊቀለብሱት ይችላሉ በማለትም አስጠንቅቋል።
የጠ/ሚሩን አዲስ መፅሀፍ በግዴታ ግዙ እየተባልን ነው በማለት የንግድ ባንክ ሰራተኞች አማረሩ
(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በሚድያዎች አበይት ክስተት ሆነው ከሰነበቱ ጉዳዮች አንዱ መስከረም 6 ቀን ለንባብ የበቃው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የተፃፈው ”የመደመር መንግሥት” የተባለው መፅሀፍ ነው።
በመደመር እሳቤ ላይ ተመርኩዞ ለአራተኛ ግዜ ለንባብ የበቃው መፅሀፍ በርካታ የመንግስት ባለሰልጣናት በተገኙ…
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/mvuudc7h
(መሠረት ሚድያ)- ሁለት የሸገር ኤፍ ኤም ጋዜጠኞች ከሁለት ሳምንት በፊት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እና ሜክሲኮ ታስረው እንደሚገኙ በወቅቱ መረጃ ማቅረባችን ይታወሳል።
ዋና አዘጋጁ ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ በወቅቱ ከታሰረ ከሰዓታት በኋላ መለቀቁ የሚታወስ ሲሆን አርታኢዋ ትግስት ዘሪሁን እና ሪፖርተሯ ምንተአምር ፀጋው ግን አሁንም ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ማቆያ እንደሚገኙ ሚድያችን አረጋግጧል።

በትናንትናው ዕለት ፍርድ ቤት እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ ቢፈቅድም ጋዜጠኞቹ እስካሁን አለመፈታታቸው ታውቋል።
ሸገር ኤፍ ኤም በበኩሉ በጉዳዩ ዙርያ ዝምታን የመረጠ ሲሆን በራሱ ጋዜጠኞች እስር ዙርያ የሰራውን የዜና ዘገባ ከገጾቹ አንስቷል።
“ትናንት ዋስትናቸው ከተፈቀደ በኋላ ይፈታሉ የሚል ተስፋ ነበረን፣ እስካሁኑ ሰዓት ግን ይህ አልሆነም” ያለው አንድ የመረጃ ምንጭ ሁለቱ ሴት ጋዜጠኞች በዓልን ጭምር በእስር ማሳለፋቸው ለቤተሰባቸው ከፍተኛ የስነ-ልቦና ጉዳት አምጥቷል ብሏል።
“ተቋሙ እንኳን ድምፅ ሊሆናቸው አልቻለም፤ እንደታሰሩ መታሰራቸውን ከዘገበ በኋላ አጥፉ ተብለው ነው አሉ አጠፉት” በማለት አስተያየት የሰጠ አንድ የሙያ አጋራቸው ሁለቱም ታሳሪዎች ታታሪ ጋዜጠኞች መሆናቸውን ገልጿል።
“ሁለቱም ሴት ጋዜጠኞች ናቸው፣ ይሁንንና የሙያ ማህበራትም ሆኑ ሚዲያዎችም እንዲሁም የሴት መብት ተቆርቋሪዎችም ሁሉም ጉዳዩን እያነሱት እንኳን አይደለም። ማንም ድምፅ እየሆናቸው አይደለም” በማለት የተሰማውን ለሚድያችን አጋርቷል።
ጋዜጠኞቹ የታሰሩት በጤና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ ዙርያ ከሁለት ሳምንት በፊት በነበረ ዜና ዙርያ መሆኑን የሚድያው ምንጮች ጠቁመው ዋና አዘጋጁ የተለቀቀው ዜናው ሲለቀቅ በስራ ላይ እንዳልነበር በመታወቁ ነው ብለዋል።
“ሸገር ኤፍኤም ለበርካታ አመታት እጅግ የበዙ
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ እንደቶ ቀበሌ ሰኞ’ለት ታጣቂዎች በፈጸሙት “ሐይማኖት ተኮር” ጥቃት ሁለት የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ተከታይ ምዕመናን መገደላቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል።
“ሐይማኖት ተኮር” ነው በተባለው ጥቃት፣ ከበደ ማሞ የተባሉ የ65 ዓመት አዛዉንትና የ6 ልጆች አባት እንዲሁም አበሬ ስዩም የተባሉ የሁለት ልጆች እናት በጥይት ተመትተው ሕይወታቸው ማለፉን የዜና ምንጩ ከነዋሪዎች መስማቱን ጠቅሶ አስነብቧል።
ከሳምንታት በፊት በዞኑ ሮቤ ወረዳ የመሰራንጄ ኦዳ ቅዱስ ጊዎርጊስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ መምሬ ንጉሤ ወልደ መድኅን ካህን በመኖሪያ ቤታቸው በታጣቂዎች በጥይት ተደብድበው መገደላቸው ይታወሳል።
ብሪታንያ፣ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር በገባችበት የባሕር በር ውጥረት ጋር በተያያዘ የተሳሳተ ስሌት እንዳትይዝ የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዴቪድ ላሚ ለኢትዮጵያ አቻቸው ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ባለፈው ነሃሴ ማስጠንቀቂያ አዘል ምክር ሰጥተው እንደነበር የብሪታኒያ ፓርላማ አባላት ማክሰኞ’ላት ባደረጉት አንድ ውይይት ተገልጧል።
ላሚ ኢትዮጵያ ይልቁንም ውጥረቱን ለማርገብ ድርድርን እንድትመርጥ መምከራቸውን፣ በብሪታንያ ፓርላማ የመንግሥት ተጠሪ ጀራርድ ሌሞስ ፓርላማው በሁለቱ አገሮች ውጥረት ዙሪያ ባደረገው ውይይት ላይ ተናግረዋል። የብሪታንያ መንግሥት ለኤርትራ ባለስልጣናትም ተመሳሳይ መልዕክት አስተላልፏል ተብሏል።
ሌሞስ፣ ማንም አገር ለንግድ አገልግሎት የባሕር በር ማግኘት ያለበት በሰላማዊ ድርድር ብቻ ነው የሚል አቋም እንዳላትና በሌላ አገር ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ላይ የሚቃጣ የኃይል ዛቻ እንደማትደግፍ ተናግረዋል።
ብሪታንያ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለችና አገራቱ ውጥረቱን ከሚያባብሱ ድርጊቶች እንዲቆጠቡ እያስጠነቀቀችና ድርድር እንዲጀምሩ ግፊት እያደረገች እንደሆነም ሌምስ ገልጸዋል።