ከጥንት ታሪካችን ከዛሬ ተግባራችን ከራስ በላይ ለሀገር ከራስ በላይ ለህዝብ በማስቀደም በላብ ተጠምቀን ደማችን አፍሰን አጥንታችን ከስክሰን አንጡራ ንብረት አባክነን በድልና በክብር ሀገር ፀንቶ እንደቆየና ዛሬም የህዝባችን ማንነታዊ ህልው ዕጣ አስቀጣይነት አርበኝነታችን መሆኑን እንገነዘባለን።
ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ አጅሬ የተሰኘች አነስተኛ ከተማ የጠላትን የእጅ አዙር ተልዕኮ ሳያነግቡ እንዳልቀረ በተጠረጠሩ ግለሰቦች በተተኮሰ ጥይት የሰሜን አምባራስ ክ/ጦር አዛዥና የራስ አሞራው 3ኛ ኮር አስተዳደር ኃላፊ የሆነው ጀግናው አርበኛ ጌትነት መሳፍንት መስዕዋትነት ከፍሏል።
ከአስር ዓመት በላይ ከወላጅ አባቱ ከአይበገሬው አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ጋር በመሰለፍ የለጋነት ዕድሜውን ሁሉ በአርበኝነት በላቀ ወታደራዊ ብቃት በተሻለ ፖለቲካዊ ንቃት ፍዳ የገጠመውን የአማራ ህዝብ ለመታደግ አያሌ የጦር ግንባሮችን በድል የቋጨው ጌትነት መሳፍንት በተለያዩ ግንባር ተጋድሎዎች አምስት ጊዜ ቆስሎ የነበረ ቢሆንም ከቁስሉ ሳያገግም ፍልሚያ ተመልሶ እየተሰለፈ ሲሻው በክላሽ ሲሻው በብሬን ጠላትን እየገረፈ ድል ሲነሳ ኑሯል።
ወላጅ አባቱ አርበኛ መሳፍንት ተስፉ፣አጎቱ መከተ ተስፉን፣ወንድሞቹ ሻምበል መሳፍንት፣ገብሬ መሳፍንትን ጨምሮ ከ30 በላይ ቤተሰቦቹ በነቂስ በተሰለፉበት የአስርት ዓመታት የአማራ ትግል የጨለማው ዘመን ፅልመት አለንልህ አማራ ብለው የተስፋ ጮራ ከፈነጠቁት ጀግና አርበኞች መካከል በለጋ ዕድሜያቸው የተሰለፉት ብላቴናዎች ጌትነት መሳፍንትና ሻምበል መሳፍንት እንደነበሩ ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ሀቅ ነው።
አርበኛ ጌትነት መሳፍንት ተስፉ በድንገተኛ አጋጣሚ የህይወት መስዕዋትነት
ሱፐር ደብል ቲ ያሰራቸው እና ያሳሰራቸው የቀድሞ ሰራተኞች በስም እና ምስል እየተለዩ ነው፣ ያሉበትን ያላወቀ ቤተሰብ ካለ እዚህ ነን እያሉ ነው፣ እነማን ናቸው?
– ድርጅቱ ሰራተኞች ላይ የሚፈፅመው በደል እና ወንጀል ሚድያ ላይ መውጣቱን ተከትሎ በቅጥር ግቢ ውስጥ ከ5 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰራተኞች ስልካቸው በየቀኑ እየተፈተሸ መሆኑ ታውቋል
– የቀድሞ ሰራተኞች የሆኑት እስር ላይ የሚገኘው ወጣት ጉታታ እና ክፉኛ ተደብድቦ ለነርቭ መጎዳት የተዳረገው ወጣት መንክርን ዝርዝር ታሪክ ይዘናል
– ዳለቲ ላይ 42፣ ፉሪ 17 እንዲሁም ገላን ጉዳ ካንተሪ 13 የቀድሞ የድርጅቱ ሰራተኞች ታስረው ይገኛሉ፣ እስር ቤት ሆነው ድረሱልን እያሉ ያሰሙት መልዕክት ተካቷል
– የታሳሪዎቹን ስም እና ፎቶ በከፊል አሰባስበናል፣ በርካቶች በፍርሀት ተበታትነው በሀገሪቱ ዙርያ ተሸሽገው እንደሚገኙ ለሚድያችን እያሳወቁ ነው
– በዊልቼር ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የተገኘው ተደብዳቢው ወጣት መንክር ህክምና ላይ የነበረ ሳይሆን ከአዳማ ከተማ ከፀበል ቦታ ተወስዶ ጋዜጠኞቹ ጋር እንዲናገር መወሰዱ ታውቋል
– አዲስ አበባ ውስጥ ለመንክር ባሳለፍነው ቅዳሜ ዊልቼር በመኪና ተጭኖ ሲወሰድለት የሚያሳይ ምስል ደርሶናል፣ ከጋዜጣ መግለጫው በኋላ ወጣት መንክር ወደ መቄዶንያ መወሰዱም ታውቋል
– የዛሬ ሳምንት ወደ ድርጅቱ ተጋብዘው የሄዱ ጋዜጠኞች በባንክ አካውንታቸው ይገባላችኋል የተባለውን አበል እንደተከለከሉ ለሚድያችን ጠቁመዋል
ለሁሉም ክፍት ሆኖ የቀረበውን ይህን ዘገባ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/2wyybr9e
ግብፅ የኤርትራን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በፅኑ ትደግፋለች – አል ሲሲ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መንግሥት “የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት እንዲያረጋግጥ” ጠየቀች
የተቃውሞ ትችት ኃላፊነትን መወጣት እንጂ ባንዳነት አይሆንም!ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ በፓርላማ ያቀረብኳቸው ጥያቄዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ሕይወት የሚመለከቱ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ናቸው። እኔ እንደ ሕዝብ ተወካይና ተቃዋሚ ፖለቲከኛነቴ፣ የመንግሥትን ሥራ መተቸትና ለሕዝብ ጥቅም መቆም ስራየም፣ ግዴታዬም ጭምር ነው።የምመራባቸው ብቸኛ መርሆዎች የአማራ ሕዝብ ህልውናና የኢትዮጵያ ዘላቂ ብሔራዊ ጥቅሞች ናቸው። ከዚህ በመነሳት ማክሰኞ ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረብኳቸው ጥያቄዎች ላይ የገዢው ፓርቲ የማህበራዊ ሚዲያ ሰራዊት እና ወዶ ገብ መሸጦ “ተቃዋሚዎች” ላቀረቡት ሦስት ክሶች ግልጽ ምላሽ እሰጣለሁ። ይሄን የማደርገው የተነሱት ክሶች ክብደት ምላሽ የሚገባቸው በመሆናቸው ሳይሆን አጋጣሚውን በመጠቀም ባቀረብኋቸው በርካታ የፖሊሲና የትግበራ ጉዳዮች ላይ የበለጠ ግንዛቤ እንዲፈጠር ውይይት እንዲካሄድባቸው ምልከታዎቼን በተብራራ ሁኔታ ለማጋራት ነው።ክስ አንድ፦ የአስመራ መንግሥት ወኪል፣ አገልጋይና ባንዳ ነህይህ ክስ መሰረተ-ቢስ፣ ተራ ስም ማጥፋት ነው። የፖለቲካ ትችትን በባንዳነትና በክህደት ስም ለመምታት የሚደረግ አሳፋሪ ሙከራም ነው። የቤተሰቤ ታሪክ የጀግንነት ታሪክ፣ በላብና በጥረት ሰርቶ የማደር እንጂ በመሸጦነት እና በባንዳነት የማደር አንዳችም ነገር የለበትም። አባቴ ወታደር ጫኔ ዳኜው በዘውዳዊ ስርዓቱ፣ ወንድሜ መቶ አለቃ አያሌው ጫኔ (የሀረር ጦር ት/ቤት ምሩቅ እና የነብሮ ክፍለ ጦር መኮንን) በወታደራዊ ደርግ ዘመን፣ እንዲሁም ሌላው ወንድሜ ተስፋሚካኤል ጫኔ (የሁርሶ ወታደራዊ ት/ቤት አሠልጣኝ) በኢሕአዴግ ዘመን፣ ሶስቱም ኢትዮጵያን በከፍተኛ ጀግንነት እና ብቃት ያገለገሉ ወታደሮች ናቸው። ቅድመ አያቶቼም በሁለቱም በኩል እነ ቀኛዝማች ደስታ ብሩ እና ብላታ ጥሩነህ ኪዳኑ እንደአብዛኛው የጎጃም፣ አማራ ገበሬ
፡
ለዝርዝሩ ይህን ይጫኑ ፡ በአርሲው ጥቃት እናት እና ሦስት ልጆችን ጨምሮ ስምንት ሰዎች የተገደሉበት ቤተሰብ
ከ 30 ደቂቃዎች በፊ
ተጨማሪ ለማንበብ ፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ንግግር “ቅዠት” ያለችው ኤርትራ መሪዋ ወደ ግብፅ አቀኑ
ለዝርዝሩ ይህን ይጫኑ ፡ የአማራ ክልል ግጭት፡ “ልጆቼ እንደ እኔ ሳይማሩ እንዳይቀሩ ነበር ስታገል የነበረው፤ መላም የለው”
በፆታዊ ትንኮሳ ተፈርዶበት ከዩኬ ወደ ኢትዮጵያ የተባረረውን ግለሰብ መልቀቁን ፌደራል ፖሊስ ገለጸ