Home › Archive for Amharic News
Blog Archives
የኬንያው ፕረዚዳንት 14 ሚሊየን የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ሰዓት አድርገው መታየታቸው ግርምትን ፈጥሯል።
ፕሬዚዳንት ሩቶ ሮሌክስ ደይቶና የተባለውን ቅንጡ ሰዓት አድርገው የታዩት በአፍሪካ ከሚገኙት ትላልቅ ፓርኮች መካከል አንዱ በሆነው በማሳይ ማራ ብሔራዊ ፓርክ ጉብኝት ባረጉበት ወቅት ነው።
ሮሌክስ ደይቶና ለገበያ የቀረበው በፈረንጆቹ 1963 ሲሆን የተሰራው በዋነኝነት ለመኪና ውድድር ሹፌሮች ነው።
ሰዓቱ እስከ 72 ሰዓት ኃይል ማቆየት እንደሚችል ሲነገር እስከ 400 ማይልስ በሰዓት ድረስ አማካይ ፍጥነትንም ያሰላል ተብሏል።
በ2024 ዊሊያም ሩቶ እንደዚሁ 425,000 የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ቀበቶ አድርገው መታየታቸው የሚታወስ ነው።
በቅርቡ ዊሊያም ሩቶ 8000 ሰዎችን መያዝ የሚችል ቤተክርስቲያን በቤተመንግስታቸው ውስጥ ለመገንባት ማቀዳቸውን ተናግረው የነበረ ሲሆን አጠቃላይ የግንባታ ወጪውም 1.2 ቢሊየን የኬንያ ሽልንግ ተገምቷል።
ፕሬዚዳንቱ ቤተክርስቲያኑን ለመገንባት ከህዝብ የሚሰበሰብ ገንዘብ እንደሌለና በራሳቸው ወጪ እንደሚገነቡት ቢናገሩም ከትችት አልተረፉም።
የኬንያ ባለስልጣናት ቅንጦት በማዘውተር ሲወቀሱ በቅርቡ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 900,000 የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ሰዓት፣ 80,000 ሽልንግ የሚያወጣ ጫማ እና የ20,000 ሽልንግ ከረቫት አለኝ ብለው መናገራቸው ቁጣን ቀስቅሶ ነበር።
በአፍሪካ መሪዎች የሚኖሩት ኑሮ ከህዝቡ በተቃራኒ እንደሆነና የቅንጦት ኑሮን የሚያዘወትሩ እንደሆነ በተደጋጋሚ የሚነገር ቢሆንም ባለስልጣናት አሁንም ቢሆን የቅንጦት ኑሮን ከማዘውተር አልቦዘኑም።
Source: The Kenya Times, Tuko News, Standard Media
አልሸባብ ከሞቃዲሾ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ያለችን ከተማ ዳግም መያዙን ገለፀ።
አልሸባብ ባለፉት ቀናት ከሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለችው ሳቢድ ከተማ ከባድ ውጊያ ማድረጉን ገልፆ በኡጋንዳ እና ሶማሊያ ጦር ላይ ከፍተኛ ጥቃት ሰንዝሮ ከተማዋን ዳግም መቆጣጠሩን ገልጿል።
በተጨማሪ አልሸባብ በከተማዋ ያለን የሶማሊያ ጦር እና የኡጋንዳ ሰላም አስከባሪ ጦር ማዘዣዎችን እንደዚሁም መኪኖችን እና መሳሪያዎችን መያዙን ገልጿል።
የሳቢድ ከተማን ከወር በፊት የሶማሊያና የኡጋንዳ ጦር ከአልሸባብ ነፃ አውጥተውት የነበረ ሲሆን ከተማዋ በአልሸባብ እጅ ዳግም በመወደቋ ላይ የሶማሊያ ጦርም ሆኑ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ያሉት ነገር የለም።
አልሸባብ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ኃይሉን እያጠናከረ በርካታ ከተሞችን መያዝ ሲጀምር በሶማሊያ ያለው የህብረቱ ተልዕኮ ከበጀት ድጋፍ ጋር በተገናኘ የሚፈልገውን ያህል እየተንቀሳቀሰ እንዳልሆነ ሲዘገብ መቆየቱ ይታወሳል።
Source: Somali Guardian
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ለግብፅ የ4.7 ቢሊየን ዶላር የመሳሪያ ሽያጭን አፅድቋል።
በመሳሪያ ሽያጩ መሰረት ግብፅ ራዳር፣ ሚሳኤሎች እና የሎጅስቲክስ እንደዚሁም የኢንጂነሪንግ ድጋፎችን ከአሜሪካ ታገኛለች።
አሜሪካ ለግብፅ የምትሰጠው የአየር ስርዓት መሳሪያ ሂሊኮፕተሮችን፣ ድሮኖችን እንደዚሁም ክሩዝ ሚሳኤሎችን ለመመከት ያስችላል።
አሜሪካ ይህንን ሽያጭ የኔቶ አባል ሃገር ካልሆኑት ዋነኛ አጋሮቿ ውስጥ የሆነችው የግብፅን ደህንነት ለማሻሻል መሆኑን ገልፃ ይህም በመካከለኛው ምስራቅ ሰላም እና የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲኖር ያስችላል ብሏል።
በተጨማሪ ለግብፅ ጦር ስልጠና እና የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ 26 የአሜሪካ መንግስት ሰራተኞች እና 34 ኮንትራክተሮች ወደ ግብፅ ያመራሉ ተብሏል።
የመሳሪያ ሽያጩን የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ያፀደቀው ሲሆን በቀጣይ የኮንግረሱ ውሳኔ ይቀረዋል።
ከ1979 ጀምሮ ግብፅ ከእስራኤል ጋር የሰላም ስምምነት በመፈራረሟ ከአሜሪካ የመሳሪያ ሽያጭ እና ድጋፍ በገፍ እያገኘች እንደሆነች ይታወቃል።
ግብፅ በተመሳሳይ በ2024 የ5 ቢሊየን ዶላር የመሳሪያ ግዢን ከአሜሪካ ፈፅማለች።
ሃገረ ግብፅ ከእስራኤል በመቀጠል ከአሜሪካ ሁለተኛዋ ከፍተኛ የወታደራዊ ድጋፍ የሚደረግላት ሃገር ስትሆን ከ1979 ጀምሮ በየአመቱ የ1.3 ቢሊየን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ ከአሜሪካ ታገኛለች።
Source: Al Jazeera, Madamasr, Defensepost
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከበላይ አካላት በደረሰበት ጫና የአመቱን ሪፖርት በተመለከተ ሊሰጠው የነበረውን ጋዜጣዊ መግለጫ መሰረዙ ታወቀ
ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ መንግስታዊ ተቋማት በአንፃራዊነት ነፃነት እንዳለው በስፋት ይነገርለት የነበረው የፌደራል ዋና ኦዲተር ቢሮ ከቅርብ አመታት ወዲህ፣ በተለይ ደግሞ ባለፈው አንድ አመት ‘ከበላይ አካላት’ ከፍተኛ ተፅእኖ እየደረሰበት መሆኑ ታውቋል።
የፕሪሚየም አባል ከሆኑ ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/bde9y4sm
በIMF የተማረሩ ሀገራት! በመጨረሻ IMF ኢትዮጲያ ደርሷል!
በ IMF ድጋፍ ዙሪያ ክርክር አለ! ለሀገራት ይጠቅማል እና ይጎዳል!
ከ IMF ድጋፍ ተከትለው ስለሚመጡ የጉዳት ማስረጃዎች ከጥቅሙ ይበዛሉ!
ከ IMF ጋር ሪፎርም በማድረግ ከፍተኛ መማረር ውስጥ ስለገቡ ሀገራት እና ምክንያት በምሳሌ እመለከታለን!
ኢትዮጲያ ከIMF ጋር የቅርብ ሪፎርም አካል ነች! የአንድ ዓመቱን ምልክት ከሌሎች ሀገራት ጋር እያነጻጸርን እመለከታለን! https://youtu.be/T631z06d49g
መቀጣጫው ለእኔ ሳይሆን ለእናንተ ነው! ( ልደቱ አያሌው )በቅርቡ- “መኖሪያ ቤትህን በ10 ቀን ውስጥ የማህበረሰብ ፖሊስ ጣቢያ ላደርገው ነው” ብሎ የዛተው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አገዛዝ ዛቻውን ለመፈጸም 10 ቀንም መታገስ አልቻለም። ከሁለት ቀን በፊት ያለምንም የፍርድ ቤት ውሳኔ የቤተሰቤ ንብረት የሆነውን መኖሪያ ቤቴን ከነ ሙሉ እቃው በመቀማት (መውረስ አይደለም) ፖሊሶች ገብተውበታል። ቀደም ሲል እንዳሉት የማህበረሰብ ፖሊስ ጣቢያ ያድርጉትወይም የባለስልጣን መኖሪያ እስካሁን በግልፅ አላዎቅነም። ይህንን ማድረግ አልበቃቸው ብሎም የቤቴን ጠባቂያለምንም ምክኒያት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደው አስረውታል።ይህ አገዛዝ አይፈጽመውም ብዬ የምገምተው ምንም ዓይነት ነውርና ወንጀል ባይኖርም፣ ይህ የጠቅላይሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዐይን ያዎጣ የወንጀል ድርጊት የፖለቲካ አንደምታው ምን እንደሆነ እይታየንለህዝብ ማካፈል ስለፈለግሁ ይህችን አጭር መጣጥፍ ላስነብባችሁ ወደድኩ።በኢትዮዽያ ፖለቲካ ተሳታፊ ከሆንኩ 33 ዓመት ሆኖኛል። በ27 ዓመቱ የኢህአዴግ አገዛዝ 5 ጊዜ ታስሬ ተፈትቻለሁ። ለ18 ቀናት የቤትና የቢሮ ውስጥ እገታ፣ ለ120 ተከታታይ ቀናት የደህንነት ክትትልና ማዋከብ፣ቢያንስ ለ20 ተከታታይ ዓመታት የስም ማጥፋት ዘመቻ ተካሂዶብኛል። አጸያፊ ስድብና መለስተኛ ድብደባ የደረሰብኝ ወቅትም ነበር። በእነዚህ ሁሉ ተጽዕኖዎች ምክኒያት ለተለያዩ የማህበራዊ፣ የኢኮኖሚና የጤና ችግሮች ተጋላጭ ሆኛለሁ።ይህ ሁሉ በደል ሲደርስብኝ ግን በወቅቱ በስልጣን ላይ የነበረው የኢህአዴግ አገዛዝ በእኔ ላይ ለሚፈጽማቸውህገ-ወጥ ድርጊቶች ቢያንስ ህጋዊ ሽፋን ለመስጠትና ለማስመሰል በተቻለው አቅም ይሞክር ነበር። በእኔየፖለቲካ ተሳትፎ ምክኒያትም በቤተሰቦቸና በጓደኞቸ ላይ አንድም ጊዜ ችግር ለመፍጠርና የግል ንብረቴን ለመውረስ ሞክሮ አያውቅም። አባል የነበርኩበትን ፓርቲም ለመከፋፈልና ለማዳከም እንጂ

በደምቢዶሎ ከተማ በሁለተኛ ዲግሪ (ማስተርስ) ተመርቃ መንገድ ላይ አትክልት እና ፍራፍሬ በመቸርቸር የምትተዳደረው መምህርት ፎቶ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ተጋርቶ በርካቶች ዘንድ አነጋጋሪ ሆኗል።
አባይነሽ ሐምቢሳ የተባለችው ይህች መምህርት ከደምቢደሎ ዩኒቨርስቲ በሒሳብ የትምህርት ዘርፍ የማስተርስ ዲግሪዋን ያገኘችው በማዕረግ ነው።
ይህች መምህርት ላለፉት ዓመታት ትምህርት በሚዘጋበት በክረምት ወቅት እንዲሁም በእረፍት ቀኗ ቅዳሜዎችን መንገድ ላይ በመቸርቸር ነው ኑሮዋን የምትደግፈው።
ለ13 ዓመታት በመምህርነት ያገለገለችው አባይነሽ በየወሩ የምታገኛት 7,500 ብር ደመወዝ ካለው የዋጋ ግሽበት ጋር ተያይዞ ኑሮዋን መደጎም ስላዳገታት ነው ወደ ጉሊት የወጣችው።
“የማገኘው ደሞዝ ልጆቼን ለማስተዳደር፣ ማኅበራዊ ሕይወቴን ለመደገፍ፣ ለትምህርት፤ ለአጠቃላይ ለኑሮዬ በቂ አይደለም። በአሁኑ ሰዓት ለመንግሥት ሠራተኞች የሚከፈለው ደመወዝ በቂ አይደለም፤ ያለውን የኑሮ ውድነትን ያገናዘበ አይደለም” ትላለች።
ከማስተማር ሥራዋ ጎን ለጎን ትምህርቷን በከፍተኛ ደረጃ መቀጠሉ አስፈላጊ ሆና ያገኘችው አባይነሽ፣ የማስተርስ ትምህርቷን ለመደጎምም ሌላኛው አማራጩ ጉሊት ነበር።
“በወር ደሞዜ የትምህርቴን ከፍዬ፣ ኑሮዬን ደግፌ፣ ለልጆቼ አውጥቼ አይሆንም” ስትል የአራት ልጆች እናት የሆነችው አባይነሽ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ገልጻለች።
በምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ዩብዶ ወረዳ የተወለደችው አባይነሽ የጉሊት ችርቻሮዋን የጀመረችው ከሁለት ዓመታት በፊት ነው።
ሙዝ፣ ብርቱካን፣ ሎሚ እና አቮካዶ የመሳሰሉ ፍራፍሬዎችን ከደምቢዶሎ ከ20 አስከ 25 ደቂቃ በእግር የሚያስኬድ መንገድ ከሚጠይቀው ስፍራ ተሸክማ አምጥታ በከተማዋ ትችረችራለች።
ገበያ በደራበትም ቀንም ከ200 አስከ 500 ብር ታገኛለች።
“ከማገኘው ትርፍ 100 ወይም 200 ብር አስቀምጬ ቀሪውን ደግሞ ለቤተሰቤ የሚያስፈልጉ እንደ ሳሙና፣ ስኳር ወይም
በዘንድሮው የ6ኛ እና የ8ኛ ፈተና ወቅት በአንዳንድ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ መምህራን ለተማሪዎች መልስ እንዲሞሉ ሲደረግ እንደነበር ታወቀ
– “በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል ያለዉን የውጤት ልዩነት እጅግ እየተቀራረበ መጥቷል”- የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
– “ሚሽኑ የተሰጣቸው መምህራን ድርጊቱን ባያምኑበት እንኳን አማራጭ አልነበራቸውም”- መምህራን
ከሆኑ ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/y4a2fhnw
በአዲስ አበባ ከተማ ከትናንት ጀምሮ ተመልሶ የመጣው መጠነ-ሰፊ የወጣቶች አፈሳ
“ሲቪል ፖሊስ በየመንገዱ እወስድሀለው እያለ ይደራደራል፣ ሌብነቱ ሀላል ወጥቷል። በየቀኑ ከመዝናኛ ቦታ እየወሰዱ በብር ተደራድረው ይለቋቸዋል።”
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/6mcu6xfd
የእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ የምስክር አሰማም ሂደት ለጊዜው ታግዶ እንዲቆይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ
የተከሳሽ ጠበቆች በይግባኙ አቤቱታ ላይ እንደገለፁት አቃቤ ሕግ 15 ምስክሮችን ካሰማ በኋላ ቀድሞ በስም ዝርዝሩ ውስጥ ያልተካተተን ምስክር በመጋረጃ ጀርባ እንዲመሰክር ብሎ ማቅረቡ የተከሳሾችን መብት በእጅጉ የሚጎዳ በመሆኑ ይሄው የስር ፍርድ ቤቱ ብይን ሊነሳ ይገባል የሚል ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/65f?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
የጠላት 78ኛ ክ/ጦር ተደመሰሰች።
በአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ 4ተኛ ደጅ አዝማች ኮር የጎቤ ክፍለ ጦር ዛሬ ሐምሌ 15/2017 ዓ.ም
በቁጥር አንድ እና በኪኒቸሩ መካከል ባደረገው ውጊያ የተገኘ ከፊል ምርኮ:-
1.አስር/10 ተሺከርካሪ
2.አንድ ሞርታር ከ6 ቅንቡላ ጋር
3.አንድ ዲሽቃ ከ18 ሳጥን /አስቃጥላ ተተኳሺ ጋር
4.ከ 117 በላይ ነፍስ ወከፍ
5.ቁጥሩ ያልታወቀ ብሬን እና ስናይፐር
6.ብዙ የክላሺ እና ብሬን ተተኳሺ
7.ቁጥሩ ያልታወቀ ምርኮኛ

የጠላት ኃይል 78ኛ ክፍለ ጦር(የቅጥረኛው ግርማ ኃይል ነው )

2 ሬጅመንት የጠላት ኃይል ተደምስሷል::

ሻለቃ አስረስ የተባለው የጠላት ጦር መሪም ተገሏል::

ኦፕሬሺኑን በበላይነት የመሩት የጎቤ ክፍለ ጦር አመራሮች
1ኛ. አርበኛ ኢሳያስ ሰጠኝ=ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
2ኛ. አርበኛ መንገሻ አስራት=ም/ዋ/አዛዥ
3ኛ.አርበኛ እሸቱ ምስጋናው=ኦርዲናንስ ኃላፊ
4ኛ.አርበኛ እርታው ታገለ=ሕዝብ አደረጃጀት ኃላፊ ናቸው::
ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ
አሜሪካ ከተመድ የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ተቋም (UNESCO) ልትወጣ ነው።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዳግም ወደ ነጩ ቤተመንግስት ከተመለሱ በኋላ አሜሪካ ከአለም አቀፍ ተቋማት እንድትወጣ እየሰሩ ሲሆን አሁን ከዩኔስኮ እንድትወጣ መወሰናቸውን የነጩ ቤተመንግሥት ምክትል ቃለ አቀባይ አና ኬሊ ተናግረዋል።
አና ኬሊ የዩኔስኮ የባህል እና ማህበራዊ ፖሊሲ አሜሪካውያን ድምፃቸውን ከሰጡበት ፖሊሲ ጋር ስለሚቃረን ፕሬዚደንቱ አሜሪካ እንድትወጣ መወሰናቸውን ገልፀዋል።
በተጨማሪ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ቃለ አቀባይ ታሚ ብሩስ የአሜሪካ በዩኔስኮ መቀጠል ከብሔራዊ ጥቅሟ በተቃራኒ መሆኑን ገልፀዋል።
ታሚ ብሩስ ተቋሙ ውስጥ ፀረ ሴማዊነት አለ ያሉ ሲሆን ተቋሙ ፍልስጤምን እንደ አባል ሃገር መቀበሉ ከአሜሪካ ጥቅም በተቃራኒ ነው ብለዋል።
የዩኔስኮ ዳይሬክተር ኦድሪ አዙላይ ተቋማቸውን ይህንን ውሳኔ ሲጠብቅ እንደነበር ገልፀው ሲዘጋጁበት እንደነበርም ገልፀዋል።
አሜሪካ ከተመድ የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ተቋምም በፈረንጆቹ ታህሳስ 31፥2026 ትወጣለች ተብሏል።
አሜሪካ በ1945 ዩኔስኮን ከመሰረቱ ሃገራት አንዷ ስትሆን በ1984 ከፋይናንስ አያያዝ እና ከአሜሪካ በተቃራኒ ቆሟል በሚል ከወጣች በኋላ ተቋሙን በ2003 ዳግም ተቀላቅላለች።
በተመሳሳይ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፕሬዚዳንት ሆነው በተመረጡ ጊዜ አሜሪካን ከተቋሙ አስወጥተው የነበረ ቢሆንም ጆ ባይደን ዳግም መልሰዋት እንደነበር የቅርብ ጊዜ ሁነት መሆኑ ይታወሳል።
Source: CNN
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና
በላይ ዘለቀ ዕዝ
ጀግናው ሰራዊታችን ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም የአገዛዙን ሰራዊት የሚደመስስ የረቀቀ ወታደራዊ ዕቅድ በማቀድ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በመተማ ወረዳ ሽመለ ጋራ፣ደለሎ ቁጥር አንድና ቁጥር አምስት በከፈተው ወታደራዊ ማጥቃት ከ170 በላይ የተደመሰሰ፣ከ40 ጠላት እጅ ሰቶ ተማርኳል፣ከ100 በላይ የነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያ ሲማረክ 06 የቡድን የጦር መሳሪያ ብሬንና ስናይፐር ተማረኳል።
አንድ ዲሽቃ ሞተራይዝድ የተማረከ ሲሆን 05 አይኮም ወታደራዊ ሬድዮን ጨምሮ 01 ሽጉጥ የተማረከበት ስኬታማው ኦፕሬሽን ነው።
ዘግይቶ በደረሰን መረጃ መሰረት ደጃዝማች 4ኛ ኮርና ከመይሳው ካሳ 2ኛ ኮር አጣናው ዋሴ ክ/ጦር በቅንጅት የብርሃኑ ጁላ ታጣቂን በበርሃማው ጠረፋማ ቀጠና አንጀቱን በጎተቱበት ውጊያ የጠላት 78ኛ ክ/ጦር 1ኛ ሬጅመንት ሙሉ በሙሉ ሲደመሰስ 2ኛ ሬጅመንትም በከፊል ተደምስሳለች።
የዓብይ አህመድ 78ኛ ክ/ጦር 1ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ኤፍሬምም በደለሎ ቁጥር አንድ ከተደመሰሱት መካከል እንደሚገኝበት ማረጋገጥ ተችሏል።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ በላይ ዘለቀ ዕዝ
ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ
Amhara Fano National Force
@AmharaFanoNF
·
39m

አሁን ያለው የኑሮ ውድነት በምን ኹኔታ የሚገለጽ ነው?
አሁን ያለው የኑሮ ውድነት በምን ኹኔታ የሚገለጽ ነው?
ሰሜን ኢትዮጵያ እያየለ የመጣው ፖለቲካዊ ውጥረት፦ ውይይት
በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት የመቀስቀሱ ሥጋት እንዳጠላ በርካቶች ይናገራሉ ። በፖለቲከኞች ዘንድ የቃላት መወራወር እና ማስጠንቀቂያዎችም ይደመጣሉ ።

“ሰላምን ማስፈን ለነጻና ገለልተኛ ምርጫ መሰረት ነው” ኦፌኮ
“ሰላምን ማስፈን ለነጻና ገለልተኛ ምርጫ መሰረት ነው” ኦፌኮ

የጎደቤ ብሔራዊ ፓርክ የገጠመው ፈተና

ትራምፕ የሕዳሴ ግድብ “የተገነባው በአብዛኛው በአሜሪካ ገንዘብ ነው” ሲሉ ለሦስተኛ ጊዜ ተናገሩ

“የ2010ሩ ተስፋ፣ አምባገነናዊ መንግሥት ለመገንባት በታቀደ ፕሮጀክት ተከድቷል” – ኦፌኮ
ዘወትር የሚባርቁት የአብይ አህመድ ጥይቶች
““““““““““““““““““““““““`
አብይ “አነጣጥሮ” የሚተኩሰው ጥይት ሁሉ የሚባረቅበት ሰው ነው። ጥቂት ማሳያወችን እንመልከት:-
በአግባቡ ወንበሩን ሳያደላድል በጀመረው “የቀንጅብ ፖለቲካው” ከትግራይ የፖለቲካ ኃይል ጋር በገባው እሰጥ አገባ ምክንያት ብዙ እልቂት ያስከተለውን የሰሜኑን ጦርነት አዋለደ።
ለግዜያዊ የፖለቲካ ትርፍ ብሎ ኦሮምያ ክልልን ለኦነግ እንደሚሰጥ አስመራ ላይ የገባው ስዉር ስምምነት ዛሬ በአብይ እና በOLA መካከል በወለጋ፣ በሸዋ እና በቦረና አካባቢወች ቀጣይነት ያለው ጦርነት እንዲካሄድ ምክንያት ሆነ።
ከህወሃት ጋር ያደረገዉን ጦርነት ለመቋጨት ከአማራ ህዝብ ጀርባ የቆመረው የፕሪቶሪያውን ውል ለመተግበር አጣብቂኝ ውስጥ ገባ። ከዚህ አጣብቂኝ ለመውጣት 2015 ላይ የጀመረው አማራን ትጥቅ የማስፈታት እቅድ ዓለም በቂ ትኩረት ያልሰጠውን ግዙፍ ጦርነትን ይዞ መጣ። በዚህም ማርኮ የሚታጠቅ፣ መከላከያዉን የሚያንበረክክ የተደራጀ የአማራ ኃይል ተፈጠረ።
በራሱ የውስጥ ጦርነት ኤርትራንን የሙጥኝ ካለ በኋላ ፕሮጀክቱን ጨርሻለሁ ብሎ ሲያስብ ሻዕቢያን በመግፋት ይልቁንም የውስጥ ጉዳዩን አጀንዳ ለማስቀዬር ብሎ የቀይ ባህር ጌታ እሆናለሁ ማለት ሲጀምር በቀጠናው ላይ ይፈጠራል ተብሎ ያልተገመተን አዲስ ፀረ-አብይ የኃይል አሰላለፍ ወለደ።
ሱዳን ውስጥ መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎን በመደገፍ እና በአሶሳ ኤርፖርት በኩል ሎጅስቲክስ በማቅረብ አልቡራሃንን በማስገደድ ከኤርትራ እና ከትግራይ ኃይሎች እነጥላለሁ ብሎ የገባበት ጨዋታ የፖርት ሱዳንን መንግስት ፀረ-አብይ አሰላለፍ አፀናው።
ሱማሊያ ላይ እቀብጣለሁ ብሎ ሶማሊ ላንድን እውቅና ለመስጠት በአደባባይ የገባው ስምምነት ግብፅን ከነ ጦሯ ወደ ሶማሊያ ጎትቶ አመጣ። ከዚህ አጣብቂኝ ለመውጣት አንካራ ሂዶ ሶማሊያን ይቅር በይኝ ብሎ ስምምነት ቢያደርግም
የኤርትራው ፕሬዝደንት የብልፅግና ፓርቲን ‘ርካሽ ውሸት’ በማሰራጨት እና ለጦርነት ዝግጅት በማድረግ ከሰሱ
ከኢትዮጵያ የባህር በር አጀንዳ ጀርባ የኤምሬቶች ወደብ የማስፋት ፍላጎት አለ በማለት የኤርትራው ፕሬዝደንት ሲናገሩ ተደመጡ የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከሀገሪቱ የቴሌቭዥን ጣብያ ጋር ረዘም ያለ ቃለ-መጠይቅ አድርገው ነበር። በቃለ-መጠይቃቸው አብዛኛውን ከኢትዮጵያ ጋር እየተካረረ ስለመጣው ግንኙነት እና የግጭት ስጋት አንስተዋል።
“በግልፅ ሲታይ እነዚህ የብልፅግና ፓርቲ አጀንዳዎች ሳይሆኑ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዝደንት [መሐመድ ቢን ዛይድ] በቀጠናው ወደቦችን አስፋፍቶ የመያዝ አጀንዳ አካል ነው።” https://shabait.com/2025/07/19/highlights-of-president-isaias-afwerkis-interview-with-local-media-outlets-2/
እናት ፓርቲ፣ የመንግሥት ሠራተኞች “የፖለቲካ ቁማር መያዣ” ተደርገዋል ብሎ እንደሚያምን ባወጣው መግለጫ ገልጧል። ፓርቲው፣ ኑሮ የከበዳቸው ተቀጣሪ ሠራተኞች ለመብታቸው በሕጋዊና ሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ ጥሪ አድርጓል። ከወቅታዊው የገንዘብ የመግዛት አቅም መውደቅ አኳያ የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ባስቸኳይ እንዲታይና መንግሥት የኑሮ ውድነትን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ፖሊሲዎችን እንዲቀይስም ፓርቲው ጠይቋል። ፓርቲው፣ የፌደራል ሲቪል ሠርቪስ ኮሚሽን ሊተገብረው አስቧል ያለው የሠራተኛ ቅነሳ “ከጅምላ ፍጅት” ተነጥሎ አይታይም በማለትም ቅነሳ እንዳይካሄድ አሳስቧል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ አወዛጋቢውንና የተሻሻለውን የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅ ለውጥ ሳይደረግበት በ5 ተቃውሞና በ12 ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል። ግብር የሚቆረጥበት ዝቅተኛ ደመወዝ ከ2 ሺሕ ብር ወደ 8 ሺሕ 324 ብር ከፍ እንዲደረግ የቀረበው ሃሳብም ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል። አንዳንድ የምክር ቤቱ አባላት፣ ማሻሻያው የመንግሥት ሠራተኞችን የኑሮ ሁኔታ ታሳቢ አላደረገም በማለት ተችተው ነበር። የገንዘብ ሚንስትር ደኤታ እዮብ ተካልኝ፣ የመንግስት ሠራተኞችን ኑሮ ለማሻሻል፣ የመኖሪያ ቤት ጥናት እየተደረገ መኾኑን ተናግረዋል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የተሻሻለውን የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ዛሬ በሁለት ተቃውሞና በአራት ድምጸ ተዓቅቦ አጽድቋል። በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የነበረው የቅሬታ ሠሚ ኮሚቴ ለምን እንደቀረ አንድ የምክር ቤት አባል የጠየቁ ሲሆን፣ የዲሞክራሲና ፍትሕ ቋሚ ኮሚቴም በክልል ደረጃ ብቻ ቅሬታ ሠሚ ኮሚቴ ማዋቀሩ የተሻለ ኾኖ ስለተገኘ እንደኾነ አስረድቷል።
አዲስ አገር ዓቀፍ ፓርቲዎች በአራት ክልሎች የድርጅት መስራች አባል ማፍራት እንዳለባቸው የሚለው ድንጋጌም፣ ስድስት ክልሎች እንዲኾን ተደርጓል።
“አዲሱ የደመወዝ ገቢ ግብር ረቂቅ የኑሮ ጫናን ያገናዝብ” የሰራተኞች ኮንፌዴሬሽን
በትናንትናው እለት ለኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ በርካቶችን አከራክሯል፡፡
በምክር ቤቱ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አዘጋጅነት የቀረበው ረቂቁ ግብር የሚቆረጥበት የደመወዝ መነሻ ከዚህ በፊት ከነበረው 600 ብር ወደ 2000 ብር ከፍ እንዲል ሃሳብ ያቀረበ ቢሆንም በበርካቶች እይታ ግን አመርቂ አለሆነም፡፡
በተለይም ከዚህ በፊት ግብር የሚቆረጥበት የደመወዝ ክፍያ መጠን መነሾ በትንሹ 8 ሺህ 300 ብር ገደማ መሆን አለበት በሚል ምክረሃሳብ አቅርቦ የነበረው የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኮንፌዴሬሽን ትናንት የቀረበውን ረቂቅ ከመጽደቁ በፊት ዳግም እንዲታይ አሳስቧል፡፡
የደሞዝ ጭማሪው «ሳይመጣ የሄደ ተስፋ» ወይስ ደጓሚ ?
ስሜ ይቆይ ብለው አስተያየታቸውን ያጋሩን አንድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ውስጥ የሚያስተምሩ መምህር የኑሮ ጫና ለሰራተኛው የሚከፈለውን ደመወዝ ጥሎት በመሄዱ በብዙ መልኩ እልባት ይሻል ይላሉ፡፡ ትናንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመከረበት አዲሱ የገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅ የኑሮና የታክስ ጫና ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ታሳቢ ያደረገ እና ከታክስ ስርአት ጋር ያሉ ችግሮችን ለመፍታት አበክሮ የሚያገናዝም መሆን አለበት የሚሉ ድምጾች ክፍ ብለው ተሰምተውበታል፡፡ ታዲያ በዚሁ ላይ አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ ያቀረቡት የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መምህሩ፤ አሁን ያለው የኑሮ ጫና እንኳን ከፍተኛ ቀረጥ (ታክስ) ኑሮበት በምንም የማይያዝ እየሆነ ነው ይላሉ፡፡ “ገቢያችን ከኑሮ ውድነቱ አኳያ በጣም ወደ ኋላ ቀርቷል” ያሉን አስተያየት ሰጪው “አሁን የሚከፈለውን የሰራተኛው ደመወዝ
በአፋር ክልል ካሉ ታጣቂዎች ወደ ትግራይ ክልል ማንኛውም ትንኮሳ የሚመጣ ከሆነ ተጠያቂው የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ነው ሲሉ የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለፁ። በአፋር ካሉ የቀድሞ የትግራይ ሐይሎች ታጣቂዎች ጋር ያለው ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት ይደረጋል ያሉት ፕሬዝደንቱ፥ ይሁንና የውክልና ግጭት ለመፍጠር ከተሞከረ ግን ጉዳዮ ከፌደራል መንግስት ጋር ነው የሚሆነው ሲሉ ጀነራል ታደሰ ወረደ አስታውቀዋል። ህወሓትም በበኩሉ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ አውጥቶት በነበረ መግለጫ የፌደራሉ መንግስት ታጣቂዎች እያሰባሰበ እና እያስታጠቀ ነው ሲል ከሷል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጥሪ
ትላንት በመቐለ ሓወልቲ ሰማእታት አደራሽ በነበረ የትግራይ ሰማእታት መታሰብያ መዝግያ ስነስርዓት ንግግር ያሰሙት የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ በክልሉ ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከፍተኛ ጥረት እንደሚደረግ አስታውቀዋል። ከህወሓት ክፍፍል በኃላ የተለየ ፖለቲካዊ አቋም በመያዝ ከነባር የትግራይ ሐይሎች በመለየት በአፋር ክልል እየተደራጁ የቆዩት ታጣቂዎች ጉዳይ በዝርዝር ያነሱት ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ ከእነዚህ ታጣቂዎች በኩል የሚደረግ ማነኛውም ትንኮሳ ግዚያዊ አስተዳደሩ ጉዳዩ የእነሱ አድርጎ ሳይሆን የፌደራሉ መንግስት ትንኮሳ አድርጎ እንደሚያየው ገልፀዋል።
በትግራይ የግብርና ምርት በግብአቶች እጥረት ተመናምኗል ተባለ
ጀነራል ታደሰ “በእዛ አቅጣጫ የሚደረግ ማንኛውም ዓይነት ትንኮሳ እንደ የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ጉዳዮ እዛ ያሉት [ታጣቂዎች] አድርጎ አይወስደውም። ወይም የፌደራል መንግስት ነው፣ አልያም የአፋር ነው። እዛ ካሉት [ታጣቂዎች] ጋር ያለው ነገር በሰላም መፈታት አለበት። የሆነ ይሁን ትንኮሳ ግን ከአፋር አቅጣጫ ከመጣ

የፎቶው ባለመብት, EHRC
የምስሉ መግለጫ, ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መለሰ (በስተግራ) እና ኮሚሽነር ርግበ ገ/ሐዋርያ (በስተቀኝ)
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ምክትል ዋና ኮሚሽነር እና የዘርፍ ኮሚሽነር የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ።
የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መለሰ እና የሴቶች፣ ሕፃናት፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋዊያን መብቶች ኮሚሽነር የሆኑት ርግበ ገ/ሐዋርያ ባለፈው ሳምንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ምንጮችች ገልፀዋል።
ኮሚሽነሮቹ ለምክር ቤቱ የሦስት ወር ማስጠንቀቂያ ጊዜ መስጠታቸውን ምንጮች የተናገሩ ሲሆን፤ ስለ ሥራ መልቀቂያው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ለተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች በዋና ኮሚሽነሩ በኩል እንደተነገረ ቢቢሲ ከምንጮቹ ተረድቷል።
የከፍተኛ ኮሚሽነሮቹ የሥራ መልቀቅ ከአዲሱ ዋና ኮሚሽነር “የአመራር ስልት” ጋር በተያያዘ “ተገፍተው” እንደሆነ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የኮሚሽኑ ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል።
“አሳታፊነትን” ይከተል የተነበረው የተቋሙ አሠራር ባለፉት ወራት ለሥራ ኃላፊዎች እና ለሠራተኞቹ ውሳኔዎቹን “አለማሳወቅ፣ አለማሳተፍ እና መመካከርን” ወደ ጎን ማለቱ ለኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራሮች መልቀቅ እንደ አንድ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል።
ባለፉት ዓመታት ኮሚሽኑ ገለልተኛነቱን እና ነፃነቱን ለማስጠበቅ ባደረጋቸው መዋቅራዊ እና ተጨባጭ ለውጦች ሲወደስ የነበረ ሲሆን፤ በ2013 ዓ.ም. የተባበሩት መንግሥታ “የፓሪስ መርሆዎች” በተሰኘው መለኪያ በተአማኒነቱ ከፍተኛውን ደረጃ ‘ኤ’ ተሰጥቶታል።
ኮሚሽኑ ባለፈው ሰኔ ወር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለብሔራዊው ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ “የተዛባ” ሪፖርት ያወጣል የሚል ይፋዊ ወቀሳ የገጠመው ሲሆን፤ “እኛ ነፃ ሆነው ይሥሩ ስንል የጠለፏቸው . . .” በማለት
የፌዴራል ገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅ ተግባራዊ ከተደረገ የአገሪቱን የውጭ ኢንቨስትመንት ሊጎዳ እንደሚችል ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አሳሰበ፡፡
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ የጀትና የፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በፌዴራል የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. በጠራው የምክክር መድረክ የንግድ ማኅበረሰብ ተወካዮች፣ የሒሳብ ባለሙያዎች፣ የፌዴራልና ክልል መንግሥታት ተወካዮች፣ የሙያ ማኅበራት፣ የንግድ ተቋማትና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ነው ማሳሰቢያው የተሰጠው፡፡
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በውይይት መድረኩ ከተገኙ ተቋማት መካከል አንዱ ሲሆን፣ ድርጅቱን ወክለው የተገኙት አቶ ዳዊት ፍሰሐ በረቂቅ ሕጉ ላይ ቢስተካከሉ ያሏቸውን ጉዳዮች አንስተዋል፡፡
አንድ ድርጅት እየከሰረ መቀጠል እንደማይችልና ኪሳራው ከቀጠለ እንደሚዘጋ በረቂቅ ሕጉ ላይ መጠቀሱን ገልጸው፣ ነገር ግን እንደ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ላለ ልዩ የኢንቨስትመንት ባህሪ ላለው ተቋም የማይሠራ በመሆኑ ማስተካከያ እንዲደረግበት ጠይቀዋል፡፡
‹‹ያለን የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለ15 ዓመታት የሚል ነው፡፡ ይህ ፈቃድ በየ15 ዓመት እንደሚታደስ ሆኖ ለ30 ዓመት የሚቆይ ነው ብለን ነው የምናስበው፡፡ ኢንቨስትመንታችን በሙሉ ለ30 ዓመታት መቆየትን ከግምት ውስጥ ያስገቡ ናቸው፡፡ ኢንቨስትመንታችን ትርፍ አለ ብለን በምናስብባቸው ቦታዎች ሁሉ አይደሉም፡፡ በየቦታው ታወሮችን መገንባትን ጨምሮ ብዙ ካፒታል የሚያስወጡ ሥራዎች አሉብን፡፡ የኔትወርክ ሽፋን ለማስፋት የመገንባት ግዴታዎች አሉብን፡፡ በአራት ዓመታት ውስጥ ለመሠረተ ልማት ማስፋፊያና ግንባታ ከ350 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርገናል፡፡ ይህን የምናደርገው በረዥም ጊዜ ትርፍ ይመጣል በሚል ዕቅድ ነው፤›› ብለዋል፡፡
አቶ ዳዊት አክለውም፣ ‹‹ኢንቨስት የምናደርገው ትርፍ በሚገኝባቸው ላይ ብቻ አይደለም፡፡ ይህ ባለበት ሁኔታ
ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላትና ከሲቪል ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር የሕዝብ ውይይት አድርጎ ነበር
ከፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት በኋላ የተነሳው የሕወሓት ሕጋዊ ሰውነቴ ይመለስልኝ ጥያቄ ፓርቲውን ከመንግሥት ብቻ ሳይሆን፣ ከምርጫ ቦርድም ጋር ሲያወዛግብ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ምርጫ ቦርዱ በአሸባሪነት ተፈርጆ የቆየ፣ እንዲሁም በፓርቲነት ለመንቀሳቀስ የሚያስችለው ሕጋዊ ዕውቅና ተሰርዞ የነበረ አንድ ድርጅትን ሕጋዊ ሰውነት ለመመለስ የሚፈቅድ የሕግ አሠራር እንደሌለው ጠቅሶ ሕወሓት ከፈለገ እንደ አዲስ ድርጅት መመዝገብ እንደሚችል ምላሽ ሰጠ፡፡ ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ የፍትሕ ሚኒስቴር እንደ አሸማጋይ ሆኖ ምርጫ ቦርድን ሕወሓት በልዩ ሁኔታ እንዲመዘገብ በደብዳቤ ጠየቀ፡፡ ከብዙ ክርክር በኋላ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 እንዲሻሻል ሐሳብ ቀረበ፡፡ ነባሩ አዋጅ ግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም. በአዋጅ ቁጥር 1332/2016 ተሻሻለ፡፡ ቀጥሎ ደግሞ መመርያ ቁጥር 25/2016 ወጣ፡፡ አሸባሪ ተብሎ ተሰርዞ የነበረው ሕወሓት በልዩ ሁኔታ ድጋሚ መመዝገብ ይችላል የሚል ሕጋዊ አሠራር ተበጀ፡፡
በእርግጥ ይህ ሁሉ መንገድ ተኪዶም የሕወሓት ሕጋዊ ሰውነት የመመለስ ጥያቄ ዕልባት አላገኘም፡፡ ነባሩ ሕጋዊ ሰውነቱን መልሶ ማግኘት እንደሚፈልግ የጠቀሰው ፓርቲው፣ በልዩ ሁኔታ ሲመዘገብ እንደ አዲስ ድርጅት የሚመዘገብበትን አሠራር ስላልተቀበለው ጉዳዩ ማወዛገቡን ቀጥሏል፡፡ በሒደት ቦርዱ ሕወሓትን የሰረዘ ሲሆን ነገር ግን የሕወሓት ዕውቅና ማስመለስ አጀንዳ በዚህም የተቋጨ አይመስልም፡፡
ይህ
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የታላቁ ህዳሴ ግድብን አስመልክተው ስላደረጉት ንግግርም ሆነ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተጠርተው ስለነበራቸው ውይይት ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጠቡ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጹ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታው ሀደራ አበራ (አምባሳደር)፣ ከአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋ ጋር ማክሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም. ውይይት ማድረጋቸውን ገልጾ ነበር፡፡
ውይይቱን በተመለከተም ሆነ የፕሬዚዳንት ትራምፕን ንግግር አስመልክቶ ሪፖርተር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚመለከታቸውን ኃላፊዎች ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ያልተሳካ ሲሆን፣ በዋትስአፕ ጥያቄ የቀረበላቸው አምባሳደር ማሲንጋ ከሚኒስትር ደኤታው ጋር ስለነበራቸው ቆይታም ሆነ ስለትራምፕ ንግግር ለመናገር ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በመግለጽ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሰኔ ወር ውስጥ ‹‹ትሩዝ›› በተሰኘው የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ በከፍተኛ መጠን ወደ ግብፅ የሚፈሰውን ውኃ ለሚገድበው ለግዙፉ የህዳሴ ግድብ አገራቸው ‹‹በሞኝነት›› የገንዘብ ድጋፍ ማድረጓን አስታውቀው፣ ነገር ግን በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል ሰላም እንዲወርድ ጥረት ማድረጋቸውን በመጥቀስ፣ የሰላም ኖቤል ሽልማት ይገባቸው እንደነበር መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡
ሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት ትራምፕ ከሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ዋና ጸሐፊ ፒት ረትና ከተለያዩ ሹማምንቶቻቸው ጋር በዋይት ሐውስ ሲወያዩ፣ በዓለም ግዙፍ ከሆኑ ግድቦች አንዱ የሆነውና ‹‹ከግብፅ ወጣ ብሎ የሚገኘው›› ያሉትን የታላቁ የህዳሴ ግድብ አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፣ ትልቅ ችግር መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በዚህኛውም ንግግራቸው አገራቸው አሜሪካ ግድቡን ፋይናንስ ማድረጓን ጠቅሰው፣ የግድቡ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት ችግሩ ለምን እንዳልተፈታ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ትራምፕ የዓባይ
ዳንጎቴ ግሩፕ በኦሮሚያ ክልል ሙገር አቅራቢያ ከሚገኘው የሲሚንቶ ፋብሪካ በተጨማሪ፣ ሁለተኛውን የሲሚንቶ ፋብሪካ በሸገር ከተማ አስተዳደር ውስጥ ለመገንባት ፈቃድ ማግኘቱ ተገለጸ፡፡
ኩባንያው ከአንድ ወር በፊት የሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ከከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንት ቦርድ ፈቃድ ማግኘቱን፣ ፈቃዱን ያገኘውም የሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት መሆኑን ሪፖርተር ከሸገር ከተማ አስተዳደር ምንጮቹ አረጋግጧል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ገና በማደግ ላይ ያለ በመሆኑና ለኢንቨስትመንት የሚመቹ በርካታ ቦታዎችን ለመጠቀም በተያዘው ዕቅድ መሠረት፣ የዳንጎቴ ግሩፕ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ ታውቋል፡፡ መሬቱን ለመቀበልም መሟላት ያለበት ቅድመ ሁኔታዎች እየተሠራባቸው መሆኑም ታውቋል፡፡
ፈቃዱ በተሰጠበት ወቅት ከአሥር በላይ ለሚሆኑ ድርጅቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጣቸው መሆኑን፣ በአሁኑ ጊዜ የሁሉም ፕሮጀክቶች ሳይት ፕላን ተነስቶ እየተሠራ መሆኑን የሸገር ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ነብዩ ዓብይ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
‹‹አሁን የኢንቨስትመንት ፈቃድ ደብዳቤ ወስደዋል፤›› ያሉት አቶ ነብዩ፣ ቀጣይ የሊዝ ውልና ክፍያ በመፈጸም የመሬት ርክብብ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ ነገር ግን ዳንጎቴ በምን ያህል ካፒታል ለመገንባት እንዳቀደ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
ጉዳዩን በማስመልከት ሪፖርተር ጥያቄ ያቀረበላቸው አንድ የዳንጎቴ ግሩፕ የሥራ ኃላፊ ዝርዝር መረጃውን ለመስጠት ፈቃኛ ባይሆኑም፣ በሸገር ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ፈቃድ ማግኘታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ፋብሪካው የሚገነባበትን መሬት ምልከታ በመከናወን ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዳንጎቴ ግሩፕ እ.ኤ.አ በ2015 ሥራ የመጀመርያውን የሲሚንቶ ፋብሪካው በ500 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ግንባትውን አጠናቆ ሥራ ከጀመረ በኋላ፣ በዓመት 2.5 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ እንደሚያመርት መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ፋብሪካው በሚገኝበት ኦሮሚያ ክልል
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፅህፈት ቤት ውስጥ የሚሰሩ ከ40 በላይ ሰራተኞች ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ይዘው ተገኙ
“ሐሰተኛ ማስረጃ ይዘው ከተገኙት ውስጥ እንደ የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴዎች ባለሙያዎች እና ዳይሬክተሮች ይገኙበታል”
የመሠረት ሚድያ የፕሪሚየም አባል ከሆኑ በፅሁፍ የተዘጋጀውን ይህን መረጃ ይከታተሉ

https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/40?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
” እሳተ ገሞራው እንደፈነዳ መረጃው ደርሶናል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ በጣም ከፍተኛ አቧራ እየወጣ ነው ” – ሰመራ ዩኒቨርሲቲ
በአፋር ክልል የኤርታሌ እሳተ ገሞራ እየፈነዳ መሆኑን ሰመራ ዩኒቨርሲቲና አንድ የዘርፉ ባለሙያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የጂዖሎጂ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ኖራ ያኒሚኦ በሰጡን ገለጻ፣ እሳተ ገሞራው መፈንዳቱን ከአካባቢው ማህበረሰብ ማረጋገጣቸውን ገልጸው፣ ለነዋሪዎቹ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈዋል።
” እሳተ ገሞራው እንደፈነዳ መረጃው ደርሶናል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ በጣም ከፍተኛ አቧራ እየወጣ ነው ” ያሉት ተመራማሪው፣ ” በአካባቢው በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጉዳት ሊያስከትል ስለሚችል ቢያንስ እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ ማራቅ የሚቻልበት መንገድ ቢፈጠር ጥሩ ነው ” ሲሉ አስገንዝበዋል።
” ኤርታሌ በቀን በጣም ብዙ ሰው የሚጎበኘው ቦታ ስለሆነ ወደዚያ የሚሄዱ ጎብኝዎች ጥንቃቄ ያድርጉ፣ ምክንያቱም የሚፈጠረው ነገር አይታወቅም ” ሲሉም ተናግረዋል።
” ከዚህ በፊት ኤርታሌ ላይ እንደዚህ አይነት ነገር የተለመደ አልነበረም፣ እሳት ገሞራ ከመፍሰስ ውጭ፣ አሁን ግን ብናኞቹ ወደሰማይ እየወጡ ስለሆነ ጉዳትም ሊያስከትል ይችላል ” ያሉት አቶ ኖራ፣ ክስተቱ እስከሚረጋጋ ድረስ ወደ አካባቢው ቀርበው ፎቶ የሚያነሱ ሰዎች እየተስተዋሉ በመሆኑ ከዚህ ተግባር እንዲታቀቡ አሳስበዋል።
አክለው፣ ” አንድ ልጅ በጣም ተጠባብሶ ፎቶ እያነሳ ነበር ” ሲሉ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸው አንድ የዘርፉ ባለሙያ በበኩላቸው፣ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታው እንደተከሰተ ገልጸው፣ ጉዳዩን ይበልጥ ለማጣራት በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ባለሙያዎች ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ፣ መረጃውን አጣርተውም ተጨማሪ ማብራሪያ እንደሚሰጡን ነግረውናል።
ግን
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አሜሪካ የኢትዮጵያውን ታላቁ ሕዳሴ ግድብ በገንዘብ ደግፋለች ሲሉ ርግጠኝነት በሌለው መልኩ ትናንት በድጋሚ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ፣ ግድቡ ወደ ናይል ወንዝ የሚሄደውን ውሃ ይዘጋዋል በማለትም ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም፣ አሁን በዚህ ጉዳይ ላይ እየሠሩበት መኾኑንና ችግሩ መፍትሄ እንደሚያገኝ በደፈናው ጠቁመዋል። ፕሬዝዳንቱ “መፍትሄ” ያሉት ምን እንደኾነ ግን አላብራሩም። መንግሥት፣ ከአንድ ወር በፊት ፕሬዝዳንት ትራምፕ ካኹን ቀደምም ይኹን ትናንት ለተናገሩት አወዛጋቢና አሳሳች አስተያየት፣ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ይፋዊ ምላሽ አልሰጠም።
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን የጭልጋ ወረዳ አስተዳደር፣ “በቅማንት ስም የሚንቀሳቀስ ጽንፈኛ” ሲል የጠራው ታጣቂ ቡድን ሰኔ 7 ቀን በጎዶ ሞላሊት ቀበሌ በትንሹ 8 ንጹሃን አርሶ አደሮች ገድለዋል በማለት ከሷል።
የወረዳው አስተዳደር፣ ቡድኑ አርሶ አደሮችን ማገቱንና በሃብትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱንና ሌሎች 5 ሰዎች እንደቆሰሉና 6ቱ ታፍነው እንደተወሰዱ ገልጧል።
ጥቃቱን ተከትሎ፣ መከላከያ ሠራዊት ወደ ቀበሌው ገብቷል ተብሏል። ቡድኑ በአማራና ቅማንት መካከል ድጋሚ “የብሔር ግጭት” እንዲቀሰቀስ ሙከራ ሲያደርግ መቆየቱንም የወረዳው አስተዳደር ገልጧል።
መንግሥት “ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ” ያላቸውን 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ማዋሉን የመንግሥት የዜና ምንጮች ማምሻውን ዘግበዋል። በቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ የሽብር ቡድኑ በሶማሊያዋ ፑንትላንድ ራስ ገዝ አሰልጥኖ ወደተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ያሠማራቸውና ለቡድኑ “ሁለንተናዊ ድጋፍ” ሲያደርጉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች እንደኾኑ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ተጠርጣሪዎቹ ከተያዙባቸው አካባቢዎች መካከል፣ አዲስ አበባ፣ የኦሮሚያው ሸገር ከተማ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ፣ ጅማ እንዲኹም በአማራ ክልል ከሚሴ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሥልጤ ዞንና ሃላባ ቁሊቶ ከተማ፤ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማና ሐረሪ ክልል እንደሚገኙበት ተገልጧል፡፡ ቡድኑ ለምልመላና ለጥፋት ተልዕኮው የሃይማኖት ተቋማትን በሽፋንነት ሲጠቀም እንደነበርና ሕዝብን “ለአመጽ” እና “ሁከት” የሚያነሳሱ አስተምህሮዎችን ለማስፋፋት ሙከራ ሲያደርግ ነበር ተብሏል።
የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፓርላማው ፍቃደኛ ከሆነ በስራ መውጫ ስዓት ፌስታል ይዘው ከሆቴል ተመላሸ ምግብ የሚለምኑ ሰራተኞች መኖራቸውን ማሳየት እንደሚችል ተናገረ፡፡
ኮንፌዴሬሽን ይህን ያለው በቅርብ ይጸድቃል ተብሎ በሚጠበቀው የፌዴራል ገቢ ግብር ማሻሽያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ባካሄደበት ወቅት ነው፡፡
ከገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከሰራተኛው ለመቁረጥ የቀረበው ሃሳብ ውስብስብ የዋጋ ንረትን እና የድህነት መጠንን ያላገናዘብ ከመሆኑም በላይ ማጭበርበር ሳይኖር በአግባቡ ከደሞዙ ግብር የሚከፍለውን ሰራተኛ ከችግር የሚውጣ ሳይሆን ችግር ውስጥ የሚከት እንደሆነ የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዘዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ተናግረዋል፡፡

ሰራተኛው በቀን አንድ ጊዜ በልቶ መዋል አልቻለም ያሉት ፕሬዝዳንቱ ምክንያቱ ደግሞ በርካታ ወጪዎች ስላሉበት ነው ብለዋል፡፡
ተቀጣሪው ሰራተኛ ህክምና ሄዶ መታከም የማይችልበት ሁኔታ ላይ ደርሷል ሲሉ ያስረዱት አቶ ካሳሁን እውነት ለመናገር አንድ ሰው በ5 ሺ ብር ደሞዝ ቤት ኪራይ ይከፍላል ፣ ይበላል፣ ልብስ ይለብሳል ፣ ህክምና ይሄዳል ብለዋል፡፡
ህክምናውን እንተው እየጸለየ ይኑር ፤ቤት ኪራይውንም እንተወው በበረንዳ በሰዎች ላይ በጥገኝነት ይኑር ግን በቀን አንድ ጊዜ እየበላ መኖር የለበትም ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
አንድ ድርጅት ከትርፉ 35 በመቶ ግብር ይከፍላል ያሉት የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ሰራተኛውም 35 በመቶ ይከፍላል ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲሉ ጥያቄ