Home › Archive for Amharic News
Blog Archives
“አዲሱ የደመወዝ ገቢ ግብር ረቂቅ የኑሮ ጫናን ያገናዝብ” የሰራተኞች ኮንፌዴሬሽን
በትናንትናው እለት ለኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ በርካቶችን አከራክሯል፡፡
በምክር ቤቱ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አዘጋጅነት የቀረበው ረቂቁ ግብር የሚቆረጥበት የደመወዝ መነሻ ከዚህ በፊት ከነበረው 600 ብር ወደ 2000 ብር ከፍ እንዲል ሃሳብ ያቀረበ ቢሆንም በበርካቶች እይታ ግን አመርቂ አለሆነም፡፡
በተለይም ከዚህ በፊት ግብር የሚቆረጥበት የደመወዝ ክፍያ መጠን መነሾ በትንሹ 8 ሺህ 300 ብር ገደማ መሆን አለበት በሚል ምክረሃሳብ አቅርቦ የነበረው የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኮንፌዴሬሽን ትናንት የቀረበውን ረቂቅ ከመጽደቁ በፊት ዳግም እንዲታይ አሳስቧል፡፡
የደሞዝ ጭማሪው «ሳይመጣ የሄደ ተስፋ» ወይስ ደጓሚ ?
ስሜ ይቆይ ብለው አስተያየታቸውን ያጋሩን አንድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ውስጥ የሚያስተምሩ መምህር የኑሮ ጫና ለሰራተኛው የሚከፈለውን ደመወዝ ጥሎት በመሄዱ በብዙ መልኩ እልባት ይሻል ይላሉ፡፡ ትናንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመከረበት አዲሱ የገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅ የኑሮና የታክስ ጫና ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ታሳቢ ያደረገ እና ከታክስ ስርአት ጋር ያሉ ችግሮችን ለመፍታት አበክሮ የሚያገናዝም መሆን አለበት የሚሉ ድምጾች ክፍ ብለው ተሰምተውበታል፡፡ ታዲያ በዚሁ ላይ አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ ያቀረቡት የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መምህሩ፤ አሁን ያለው የኑሮ ጫና እንኳን ከፍተኛ ቀረጥ (ታክስ) ኑሮበት በምንም የማይያዝ እየሆነ ነው ይላሉ፡፡ “ገቢያችን ከኑሮ ውድነቱ አኳያ በጣም ወደ ኋላ ቀርቷል” ያሉን አስተያየት ሰጪው “አሁን የሚከፈለውን የሰራተኛው ደመወዝ
በአፋር ክልል ካሉ ታጣቂዎች ወደ ትግራይ ክልል ማንኛውም ትንኮሳ የሚመጣ ከሆነ ተጠያቂው የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ነው ሲሉ የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለፁ። በአፋር ካሉ የቀድሞ የትግራይ ሐይሎች ታጣቂዎች ጋር ያለው ልዩነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት ይደረጋል ያሉት ፕሬዝደንቱ፥ ይሁንና የውክልና ግጭት ለመፍጠር ከተሞከረ ግን ጉዳዮ ከፌደራል መንግስት ጋር ነው የሚሆነው ሲሉ ጀነራል ታደሰ ወረደ አስታውቀዋል። ህወሓትም በበኩሉ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ አውጥቶት በነበረ መግለጫ የፌደራሉ መንግስት ታጣቂዎች እያሰባሰበ እና እያስታጠቀ ነው ሲል ከሷል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጥሪ
ትላንት በመቐለ ሓወልቲ ሰማእታት አደራሽ በነበረ የትግራይ ሰማእታት መታሰብያ መዝግያ ስነስርዓት ንግግር ያሰሙት የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ በክልሉ ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከፍተኛ ጥረት እንደሚደረግ አስታውቀዋል። ከህወሓት ክፍፍል በኃላ የተለየ ፖለቲካዊ አቋም በመያዝ ከነባር የትግራይ ሐይሎች በመለየት በአፋር ክልል እየተደራጁ የቆዩት ታጣቂዎች ጉዳይ በዝርዝር ያነሱት ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ ከእነዚህ ታጣቂዎች በኩል የሚደረግ ማነኛውም ትንኮሳ ግዚያዊ አስተዳደሩ ጉዳዩ የእነሱ አድርጎ ሳይሆን የፌደራሉ መንግስት ትንኮሳ አድርጎ እንደሚያየው ገልፀዋል።
በትግራይ የግብርና ምርት በግብአቶች እጥረት ተመናምኗል ተባለ
ጀነራል ታደሰ “በእዛ አቅጣጫ የሚደረግ ማንኛውም ዓይነት ትንኮሳ እንደ የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ጉዳዮ እዛ ያሉት [ታጣቂዎች] አድርጎ አይወስደውም። ወይም የፌደራል መንግስት ነው፣ አልያም የአፋር ነው። እዛ ካሉት [ታጣቂዎች] ጋር ያለው ነገር በሰላም መፈታት አለበት። የሆነ ይሁን ትንኮሳ ግን ከአፋር አቅጣጫ ከመጣ

የፎቶው ባለመብት, EHRC
የምስሉ መግለጫ, ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መለሰ (በስተግራ) እና ኮሚሽነር ርግበ ገ/ሐዋርያ (በስተቀኝ)
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ምክትል ዋና ኮሚሽነር እና የዘርፍ ኮሚሽነር የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ።
የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መለሰ እና የሴቶች፣ ሕፃናት፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋዊያን መብቶች ኮሚሽነር የሆኑት ርግበ ገ/ሐዋርያ ባለፈው ሳምንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ምንጮችች ገልፀዋል።
ኮሚሽነሮቹ ለምክር ቤቱ የሦስት ወር ማስጠንቀቂያ ጊዜ መስጠታቸውን ምንጮች የተናገሩ ሲሆን፤ ስለ ሥራ መልቀቂያው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ለተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች በዋና ኮሚሽነሩ በኩል እንደተነገረ ቢቢሲ ከምንጮቹ ተረድቷል።
የከፍተኛ ኮሚሽነሮቹ የሥራ መልቀቅ ከአዲሱ ዋና ኮሚሽነር “የአመራር ስልት” ጋር በተያያዘ “ተገፍተው” እንደሆነ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የኮሚሽኑ ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል።
“አሳታፊነትን” ይከተል የተነበረው የተቋሙ አሠራር ባለፉት ወራት ለሥራ ኃላፊዎች እና ለሠራተኞቹ ውሳኔዎቹን “አለማሳወቅ፣ አለማሳተፍ እና መመካከርን” ወደ ጎን ማለቱ ለኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራሮች መልቀቅ እንደ አንድ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አመልክተዋል።
ባለፉት ዓመታት ኮሚሽኑ ገለልተኛነቱን እና ነፃነቱን ለማስጠበቅ ባደረጋቸው መዋቅራዊ እና ተጨባጭ ለውጦች ሲወደስ የነበረ ሲሆን፤ በ2013 ዓ.ም. የተባበሩት መንግሥታ “የፓሪስ መርሆዎች” በተሰኘው መለኪያ በተአማኒነቱ ከፍተኛውን ደረጃ ‘ኤ’ ተሰጥቶታል።
ኮሚሽኑ ባለፈው ሰኔ ወር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለብሔራዊው ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ “የተዛባ” ሪፖርት ያወጣል የሚል ይፋዊ ወቀሳ የገጠመው ሲሆን፤ “እኛ ነፃ ሆነው ይሥሩ ስንል የጠለፏቸው . . .” በማለት
የፌዴራል ገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅ ተግባራዊ ከተደረገ የአገሪቱን የውጭ ኢንቨስትመንት ሊጎዳ እንደሚችል ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አሳሰበ፡፡
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ የጀትና የፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በፌዴራል የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. በጠራው የምክክር መድረክ የንግድ ማኅበረሰብ ተወካዮች፣ የሒሳብ ባለሙያዎች፣ የፌዴራልና ክልል መንግሥታት ተወካዮች፣ የሙያ ማኅበራት፣ የንግድ ተቋማትና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ነው ማሳሰቢያው የተሰጠው፡፡
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በውይይት መድረኩ ከተገኙ ተቋማት መካከል አንዱ ሲሆን፣ ድርጅቱን ወክለው የተገኙት አቶ ዳዊት ፍሰሐ በረቂቅ ሕጉ ላይ ቢስተካከሉ ያሏቸውን ጉዳዮች አንስተዋል፡፡
አንድ ድርጅት እየከሰረ መቀጠል እንደማይችልና ኪሳራው ከቀጠለ እንደሚዘጋ በረቂቅ ሕጉ ላይ መጠቀሱን ገልጸው፣ ነገር ግን እንደ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ላለ ልዩ የኢንቨስትመንት ባህሪ ላለው ተቋም የማይሠራ በመሆኑ ማስተካከያ እንዲደረግበት ጠይቀዋል፡፡
‹‹ያለን የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለ15 ዓመታት የሚል ነው፡፡ ይህ ፈቃድ በየ15 ዓመት እንደሚታደስ ሆኖ ለ30 ዓመት የሚቆይ ነው ብለን ነው የምናስበው፡፡ ኢንቨስትመንታችን በሙሉ ለ30 ዓመታት መቆየትን ከግምት ውስጥ ያስገቡ ናቸው፡፡ ኢንቨስትመንታችን ትርፍ አለ ብለን በምናስብባቸው ቦታዎች ሁሉ አይደሉም፡፡ በየቦታው ታወሮችን መገንባትን ጨምሮ ብዙ ካፒታል የሚያስወጡ ሥራዎች አሉብን፡፡ የኔትወርክ ሽፋን ለማስፋት የመገንባት ግዴታዎች አሉብን፡፡ በአራት ዓመታት ውስጥ ለመሠረተ ልማት ማስፋፊያና ግንባታ ከ350 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርገናል፡፡ ይህን የምናደርገው በረዥም ጊዜ ትርፍ ይመጣል በሚል ዕቅድ ነው፤›› ብለዋል፡፡
አቶ ዳዊት አክለውም፣ ‹‹ኢንቨስት የምናደርገው ትርፍ በሚገኝባቸው ላይ ብቻ አይደለም፡፡ ይህ ባለበት ሁኔታ
ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላትና ከሲቪል ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር የሕዝብ ውይይት አድርጎ ነበር
ከፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት በኋላ የተነሳው የሕወሓት ሕጋዊ ሰውነቴ ይመለስልኝ ጥያቄ ፓርቲውን ከመንግሥት ብቻ ሳይሆን፣ ከምርጫ ቦርድም ጋር ሲያወዛግብ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ምርጫ ቦርዱ በአሸባሪነት ተፈርጆ የቆየ፣ እንዲሁም በፓርቲነት ለመንቀሳቀስ የሚያስችለው ሕጋዊ ዕውቅና ተሰርዞ የነበረ አንድ ድርጅትን ሕጋዊ ሰውነት ለመመለስ የሚፈቅድ የሕግ አሠራር እንደሌለው ጠቅሶ ሕወሓት ከፈለገ እንደ አዲስ ድርጅት መመዝገብ እንደሚችል ምላሽ ሰጠ፡፡ ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ የፍትሕ ሚኒስቴር እንደ አሸማጋይ ሆኖ ምርጫ ቦርድን ሕወሓት በልዩ ሁኔታ እንዲመዘገብ በደብዳቤ ጠየቀ፡፡ ከብዙ ክርክር በኋላ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 እንዲሻሻል ሐሳብ ቀረበ፡፡ ነባሩ አዋጅ ግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም. በአዋጅ ቁጥር 1332/2016 ተሻሻለ፡፡ ቀጥሎ ደግሞ መመርያ ቁጥር 25/2016 ወጣ፡፡ አሸባሪ ተብሎ ተሰርዞ የነበረው ሕወሓት በልዩ ሁኔታ ድጋሚ መመዝገብ ይችላል የሚል ሕጋዊ አሠራር ተበጀ፡፡
በእርግጥ ይህ ሁሉ መንገድ ተኪዶም የሕወሓት ሕጋዊ ሰውነት የመመለስ ጥያቄ ዕልባት አላገኘም፡፡ ነባሩ ሕጋዊ ሰውነቱን መልሶ ማግኘት እንደሚፈልግ የጠቀሰው ፓርቲው፣ በልዩ ሁኔታ ሲመዘገብ እንደ አዲስ ድርጅት የሚመዘገብበትን አሠራር ስላልተቀበለው ጉዳዩ ማወዛገቡን ቀጥሏል፡፡ በሒደት ቦርዱ ሕወሓትን የሰረዘ ሲሆን ነገር ግን የሕወሓት ዕውቅና ማስመለስ አጀንዳ በዚህም የተቋጨ አይመስልም፡፡
ይህ
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የታላቁ ህዳሴ ግድብን አስመልክተው ስላደረጉት ንግግርም ሆነ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተጠርተው ስለነበራቸው ውይይት ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጠቡ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጹ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታው ሀደራ አበራ (አምባሳደር)፣ ከአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋ ጋር ማክሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም. ውይይት ማድረጋቸውን ገልጾ ነበር፡፡
ውይይቱን በተመለከተም ሆነ የፕሬዚዳንት ትራምፕን ንግግር አስመልክቶ ሪፖርተር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚመለከታቸውን ኃላፊዎች ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ያልተሳካ ሲሆን፣ በዋትስአፕ ጥያቄ የቀረበላቸው አምባሳደር ማሲንጋ ከሚኒስትር ደኤታው ጋር ስለነበራቸው ቆይታም ሆነ ስለትራምፕ ንግግር ለመናገር ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በመግለጽ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሰኔ ወር ውስጥ ‹‹ትሩዝ›› በተሰኘው የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ በከፍተኛ መጠን ወደ ግብፅ የሚፈሰውን ውኃ ለሚገድበው ለግዙፉ የህዳሴ ግድብ አገራቸው ‹‹በሞኝነት›› የገንዘብ ድጋፍ ማድረጓን አስታውቀው፣ ነገር ግን በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል ሰላም እንዲወርድ ጥረት ማድረጋቸውን በመጥቀስ፣ የሰላም ኖቤል ሽልማት ይገባቸው እንደነበር መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡
ሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት ትራምፕ ከሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ዋና ጸሐፊ ፒት ረትና ከተለያዩ ሹማምንቶቻቸው ጋር በዋይት ሐውስ ሲወያዩ፣ በዓለም ግዙፍ ከሆኑ ግድቦች አንዱ የሆነውና ‹‹ከግብፅ ወጣ ብሎ የሚገኘው›› ያሉትን የታላቁ የህዳሴ ግድብ አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፣ ትልቅ ችግር መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ በዚህኛውም ንግግራቸው አገራቸው አሜሪካ ግድቡን ፋይናንስ ማድረጓን ጠቅሰው፣ የግድቡ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት ችግሩ ለምን እንዳልተፈታ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
ትራምፕ የዓባይ
ዳንጎቴ ግሩፕ በኦሮሚያ ክልል ሙገር አቅራቢያ ከሚገኘው የሲሚንቶ ፋብሪካ በተጨማሪ፣ ሁለተኛውን የሲሚንቶ ፋብሪካ በሸገር ከተማ አስተዳደር ውስጥ ለመገንባት ፈቃድ ማግኘቱ ተገለጸ፡፡
ኩባንያው ከአንድ ወር በፊት የሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ከከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንት ቦርድ ፈቃድ ማግኘቱን፣ ፈቃዱን ያገኘውም የሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት መሆኑን ሪፖርተር ከሸገር ከተማ አስተዳደር ምንጮቹ አረጋግጧል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ገና በማደግ ላይ ያለ በመሆኑና ለኢንቨስትመንት የሚመቹ በርካታ ቦታዎችን ለመጠቀም በተያዘው ዕቅድ መሠረት፣ የዳንጎቴ ግሩፕ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ ታውቋል፡፡ መሬቱን ለመቀበልም መሟላት ያለበት ቅድመ ሁኔታዎች እየተሠራባቸው መሆኑም ታውቋል፡፡
ፈቃዱ በተሰጠበት ወቅት ከአሥር በላይ ለሚሆኑ ድርጅቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጣቸው መሆኑን፣ በአሁኑ ጊዜ የሁሉም ፕሮጀክቶች ሳይት ፕላን ተነስቶ እየተሠራ መሆኑን የሸገር ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ነብዩ ዓብይ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
‹‹አሁን የኢንቨስትመንት ፈቃድ ደብዳቤ ወስደዋል፤›› ያሉት አቶ ነብዩ፣ ቀጣይ የሊዝ ውልና ክፍያ በመፈጸም የመሬት ርክብብ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ ነገር ግን ዳንጎቴ በምን ያህል ካፒታል ለመገንባት እንዳቀደ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
ጉዳዩን በማስመልከት ሪፖርተር ጥያቄ ያቀረበላቸው አንድ የዳንጎቴ ግሩፕ የሥራ ኃላፊ ዝርዝር መረጃውን ለመስጠት ፈቃኛ ባይሆኑም፣ በሸገር ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ፈቃድ ማግኘታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ፋብሪካው የሚገነባበትን መሬት ምልከታ በመከናወን ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዳንጎቴ ግሩፕ እ.ኤ.አ በ2015 ሥራ የመጀመርያውን የሲሚንቶ ፋብሪካው በ500 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ግንባትውን አጠናቆ ሥራ ከጀመረ በኋላ፣ በዓመት 2.5 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ እንደሚያመርት መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ፋብሪካው በሚገኝበት ኦሮሚያ ክልል
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፅህፈት ቤት ውስጥ የሚሰሩ ከ40 በላይ ሰራተኞች ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ይዘው ተገኙ
“ሐሰተኛ ማስረጃ ይዘው ከተገኙት ውስጥ እንደ የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴዎች ባለሙያዎች እና ዳይሬክተሮች ይገኙበታል”
የመሠረት ሚድያ የፕሪሚየም አባል ከሆኑ በፅሁፍ የተዘጋጀውን ይህን መረጃ ይከታተሉ ⤵️
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/40?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
” እሳተ ገሞራው እንደፈነዳ መረጃው ደርሶናል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ በጣም ከፍተኛ አቧራ እየወጣ ነው ” – ሰመራ ዩኒቨርሲቲ
በአፋር ክልል የኤርታሌ እሳተ ገሞራ እየፈነዳ መሆኑን ሰመራ ዩኒቨርሲቲና አንድ የዘርፉ ባለሙያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የጂዖሎጂ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ኖራ ያኒሚኦ በሰጡን ገለጻ፣ እሳተ ገሞራው መፈንዳቱን ከአካባቢው ማህበረሰብ ማረጋገጣቸውን ገልጸው፣ ለነዋሪዎቹ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈዋል።
” እሳተ ገሞራው እንደፈነዳ መረጃው ደርሶናል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ በጣም ከፍተኛ አቧራ እየወጣ ነው ” ያሉት ተመራማሪው፣ ” በአካባቢው በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጉዳት ሊያስከትል ስለሚችል ቢያንስ እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ ማራቅ የሚቻልበት መንገድ ቢፈጠር ጥሩ ነው ” ሲሉ አስገንዝበዋል።
” ኤርታሌ በቀን በጣም ብዙ ሰው የሚጎበኘው ቦታ ስለሆነ ወደዚያ የሚሄዱ ጎብኝዎች ጥንቃቄ ያድርጉ፣ ምክንያቱም የሚፈጠረው ነገር አይታወቅም ” ሲሉም ተናግረዋል።
” ከዚህ በፊት ኤርታሌ ላይ እንደዚህ አይነት ነገር የተለመደ አልነበረም፣ እሳት ገሞራ ከመፍሰስ ውጭ፣ አሁን ግን ብናኞቹ ወደሰማይ እየወጡ ስለሆነ ጉዳትም ሊያስከትል ይችላል ” ያሉት አቶ ኖራ፣ ክስተቱ እስከሚረጋጋ ድረስ ወደ አካባቢው ቀርበው ፎቶ የሚያነሱ ሰዎች እየተስተዋሉ በመሆኑ ከዚህ ተግባር እንዲታቀቡ አሳስበዋል።
አክለው፣ ” አንድ ልጅ በጣም ተጠባብሶ ፎቶ እያነሳ ነበር ” ሲሉ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸው አንድ የዘርፉ ባለሙያ በበኩላቸው፣ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታው እንደተከሰተ ገልጸው፣ ጉዳዩን ይበልጥ ለማጣራት በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ባለሙያዎች ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ፣ መረጃውን አጣርተውም ተጨማሪ ማብራሪያ እንደሚሰጡን ነግረውናል።
ግን
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አሜሪካ የኢትዮጵያውን ታላቁ ሕዳሴ ግድብ በገንዘብ ደግፋለች ሲሉ ርግጠኝነት በሌለው መልኩ ትናንት በድጋሚ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ፣ ግድቡ ወደ ናይል ወንዝ የሚሄደውን ውሃ ይዘጋዋል በማለትም ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም፣ አሁን በዚህ ጉዳይ ላይ እየሠሩበት መኾኑንና ችግሩ መፍትሄ እንደሚያገኝ በደፈናው ጠቁመዋል። ፕሬዝዳንቱ “መፍትሄ” ያሉት ምን እንደኾነ ግን አላብራሩም። መንግሥት፣ ከአንድ ወር በፊት ፕሬዝዳንት ትራምፕ ካኹን ቀደምም ይኹን ትናንት ለተናገሩት አወዛጋቢና አሳሳች አስተያየት፣ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ይፋዊ ምላሽ አልሰጠም።
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን የጭልጋ ወረዳ አስተዳደር፣ “በቅማንት ስም የሚንቀሳቀስ ጽንፈኛ” ሲል የጠራው ታጣቂ ቡድን ሰኔ 7 ቀን በጎዶ ሞላሊት ቀበሌ በትንሹ 8 ንጹሃን አርሶ አደሮች ገድለዋል በማለት ከሷል።
የወረዳው አስተዳደር፣ ቡድኑ አርሶ አደሮችን ማገቱንና በሃብትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱንና ሌሎች 5 ሰዎች እንደቆሰሉና 6ቱ ታፍነው እንደተወሰዱ ገልጧል።
ጥቃቱን ተከትሎ፣ መከላከያ ሠራዊት ወደ ቀበሌው ገብቷል ተብሏል። ቡድኑ በአማራና ቅማንት መካከል ድጋሚ “የብሔር ግጭት” እንዲቀሰቀስ ሙከራ ሲያደርግ መቆየቱንም የወረዳው አስተዳደር ገልጧል።
መንግሥት “ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ” ያላቸውን 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ማዋሉን የመንግሥት የዜና ምንጮች ማምሻውን ዘግበዋል። በቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ የሽብር ቡድኑ በሶማሊያዋ ፑንትላንድ ራስ ገዝ አሰልጥኖ ወደተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ያሠማራቸውና ለቡድኑ “ሁለንተናዊ ድጋፍ” ሲያደርጉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች እንደኾኑ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ተጠርጣሪዎቹ ከተያዙባቸው አካባቢዎች መካከል፣ አዲስ አበባ፣ የኦሮሚያው ሸገር ከተማ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ፣ ጅማ እንዲኹም በአማራ ክልል ከሚሴ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሥልጤ ዞንና ሃላባ ቁሊቶ ከተማ፤ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማና ሐረሪ ክልል እንደሚገኙበት ተገልጧል፡፡ ቡድኑ ለምልመላና ለጥፋት ተልዕኮው የሃይማኖት ተቋማትን በሽፋንነት ሲጠቀም እንደነበርና ሕዝብን “ለአመጽ” እና “ሁከት” የሚያነሳሱ አስተምህሮዎችን ለማስፋፋት ሙከራ ሲያደርግ ነበር ተብሏል።
የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፓርላማው ፍቃደኛ ከሆነ በስራ መውጫ ስዓት ፌስታል ይዘው ከሆቴል ተመላሸ ምግብ የሚለምኑ ሰራተኞች መኖራቸውን ማሳየት እንደሚችል ተናገረ፡፡
ኮንፌዴሬሽን ይህን ያለው በቅርብ ይጸድቃል ተብሎ በሚጠበቀው የፌዴራል ገቢ ግብር ማሻሽያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ባካሄደበት ወቅት ነው፡፡
ከገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከሰራተኛው ለመቁረጥ የቀረበው ሃሳብ ውስብስብ የዋጋ ንረትን እና የድህነት መጠንን ያላገናዘብ ከመሆኑም በላይ ማጭበርበር ሳይኖር በአግባቡ ከደሞዙ ግብር የሚከፍለውን ሰራተኛ ከችግር የሚውጣ ሳይሆን ችግር ውስጥ የሚከት እንደሆነ የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዘዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ተናግረዋል፡፡

ሰራተኛው በቀን አንድ ጊዜ በልቶ መዋል አልቻለም ያሉት ፕሬዝዳንቱ ምክንያቱ ደግሞ በርካታ ወጪዎች ስላሉበት ነው ብለዋል፡፡
ተቀጣሪው ሰራተኛ ህክምና ሄዶ መታከም የማይችልበት ሁኔታ ላይ ደርሷል ሲሉ ያስረዱት አቶ ካሳሁን እውነት ለመናገር አንድ ሰው በ5 ሺ ብር ደሞዝ ቤት ኪራይ ይከፍላል ፣ ይበላል፣ ልብስ ይለብሳል ፣ ህክምና ይሄዳል ብለዋል፡፡
ህክምናውን እንተው እየጸለየ ይኑር ፤ቤት ኪራይውንም እንተወው በበረንዳ በሰዎች ላይ በጥገኝነት ይኑር ግን በቀን አንድ ጊዜ እየበላ መኖር የለበትም ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
አንድ ድርጅት ከትርፉ 35 በመቶ ግብር ይከፍላል ያሉት የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ሰራተኛውም 35 በመቶ ይከፍላል ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲሉ ጥያቄ
ኢሕአፓ ከሀገር ከወጣ በኋላ የተለያዩ አንጃዎች ተፈጥረዋል። ከመካከላቸው በውጭ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ሀገራቸው እንዲገቡ የቀረበውን ጥሪ በመቀበል ወደ ሀገር ቤት የገባው የኢሕአፓ ቡድን ከዛሬ 6 ዓመት አንስቶ እየተንቀሳቀሰ ነው። መርኁም ሶሻል ዴሞክራሲ ነው። መጋቤ ብሊይ አብርሀም ሃይማኖት የፓርቲው ተቃዳሚ ምክትል ሊ/መንበር ናቸው።
ከአንጋፋዎቹ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ ነው። ከተመሰረተ 53 ዓመታት አልፈዋል። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ታሪክ በርካታ ወጣቶችን በማቀፍ ግንባር ቀደሙ ነበር ሊባል ይችላል፤የኢትዮጵያ ህዞቦች አብዮታዊ ፓርቲ በምህጻሩ ኢሕአፓ።
5 የፖለቲካ ድርጅቶች በፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ላይ ያነሱት ቅሬታ
በማርክሲስት ሌኒኒስት ርዕዮተ ዓለም ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ለውጥ ለማምጣት አልሞ የተቋቋመው ኢሕአፓ ከደርግ ጋር ባካሄደው የከተማና የገጠር ውጊያ በርካታ አባላትና ደጋፊዎቹ ተገድለዋል፤ ታስረዋል የደረሱበት ያልታወቀም ጥቂት የሚባሉ አይደሉም።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ጋር ተወያዩ


የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ(ኢሕአፓ) ዓርማ ምስል፦ Megabe Beluiey Abrham Haimanot/DW
አወዛጋቢ ታሪክ ያለው ፓርቲው ከኢትዮጵያ ከወጣ በኋላ የተለያዩ አንጃዎች ተፈጥረዋል። ከመካከላቸው በውጭ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ ሀገራቸው እንዲገቡ የቀረበውን ጥሪ በመቀበል ወደ ሀገር ቤት የገባው የኢሕአፓ ቡድን፣ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ ከዛሬ ስድስት ዓመት አንስቶ እየተንቀሳቀሰ ነው ። የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ ብሊይ አብርሀም ሃይማኖት የዛሬው አንድ-ለ-አንድ ዝግጅታችን እንግዳ ናቸው ። ሙሉውን ቃለ ምልልስ ከድምጽ ማዕቀፉ ማዳመጥ ይቻላል።
የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ላይ ሊደረጉ የታቀዱ ማሻሻያዎችን የመረመሩ ባለሙያዎች ኢሕአዴግ ሥልጣን ላይ ሳለ ዘርፉን ቀፍድደው የያዙ ገደቦች እና አሠራሮች ተመልሰው ተግባራዊ ሊሆኑ ነው የሚል ብርቱ ሥጋት አላቸው። ሦስት እንግዶች የተሳተፉበት ውይይት ማሻሻያዎቹን እና ተጽዕኖዎቻቸውን ይፈትሻል።
ኢትዮጵያ መንግሥት “አፋኝ” ይባል የነበረውን የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና ማኅበራት አዋጅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሥልጣን ከያዙ በኋላ በየካቲት 2011 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጸደቀው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ሲተካ አድናቆት እና ቅቡልነት አግኝቶ ነበር።
የዐቢይ መንግሥት በኢትዮጵያውያን እና በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሞገስ የተቸረው ፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ መገናኛ ብዙኃን እና የሲቪል ድርጅቶችን የተመለከቱትን ጨምሮ የኢሕአዴግ አስተዳደር ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግባቸውን ሕግጋትን በማሻሻሉ ነበር።
መንግሥት ለስድስት ዓመታት ገደማ ሥራ ላይ የቆየውን የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ለማሻሻል ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛል። ሕጉ የሚሻሻለው ነባሩ አዋጅ “ተግባራዊ መሆን ከጀመረ በኋላ የተስተዋሉ ክፍተቶችን ለማስተካከል” እንደሆነ የፍትኅ ሚኒስቴር ለውይይት ያቀረበው እና ዶይቼ ቬለ የተመለከተው ሠነድ መግቢያ ላይ ሠፍሯል።
ኦፊሴላዊ ባልሆነው ሠነድ “የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንቅስቃሴ የህዝብ እና የአገርን ጥቅም ባረጋገጠ መልኩ እንዲሆን ለማድረግ” የሚለው ከማሻሻያው ዓላማች መካከል ተካትቶ ቀርቧል። ሠነዱ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ ቦርድ አደረጃጀት፣ የድርጅቶች ምዝገባ፣ የሥራ ነጻነት፣ የሐብት አሰባሰብ እና አስተዳደር በመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ ለውጦች እንዲደረጉ ምክረ-ሐሳቦች የቀረቡበት ነው።
ሠነዱ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ ቦርድ አባላት ቁጥር ከአስራ አንድ ወደ ሰባት ዝቅ እንዲል ምክረ-ሐሳብ ቀርቧል። ከሰባቱ የቦርድ
የተጠናቀቀው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ “በዲፕሎማሲው መስክ ውጤታማ የሥራ ስኬት ያስመዘገበችበት” እንደነበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። ግንኙነትን ማጠናከር፣ ብሔራዊ ጥቅምን ማሳደግ፣ ከጎረቤት እና ሌሎች ሀገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ትብብርን ማጉላት ውጤት ተመዝግቦባቸዋል የተባሉት መስኮች መሆናቸውንም ተቋሙ ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ የዓመቱ የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ሲመዘን
የተጠናቀቀው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ “በዲፕሎማሲው መስክ ውጤታማ የሥራ ስኬት ያስመዘገበችበት” እንደነበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። ግንኙነትን ማጠናከር፣ ብሔራዊ ጥቅምን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሥራ እንቅስቃሴማሳደግ፣ ከጎረቤት እና ሌሎች ሀገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ትብብርን ማጉላት ውጤት ተመዝግቦባቸዋል የተባሉት መስኮች መሆናቸውንም ተቋሙ ይፋ አድርጓል።
ኢትዮጵያ ከምዕራባዊያን ሀገራት እና ተቋሞቻቸው ጋር ባላት ግንኙነት “ተቀባይነቷ የጨመረበት” ዓመት መሆኑን የጠቀሱ አንድ የዘርፉ ተንታኝ፣ የገንዘብ ተቋማት እያደረጉት ያለውን የብድር ድጋፍ አስረጂ አድርገዋል። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላት የሁለትዮሽ ግንኙነት “አስጊነቱ አሁንም የቀጠለ” እና በጥቅሉ ሲመዘን “አድገናልም፣ ወድቀናልም የሚያስብል ኹኔታ ያልተፈጠረበት” ነው ብለዋል።
የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስለ ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ግንኙነት
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቃል ዐቀባዩ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በኩል እንዳለው የተቋሙ የዚህ ዓመት የዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ “ውጤታማ” ነበር። ቃል ዐቀባዩ ለዚህ ዝርዝር ጉዳዮችን የጠቀሱ ቢሆንም ዋና ዋናዎቹ ግን እነዚህ ናቸው። “የዲፕሎማሲ ግንኙነታችንን በማጠናከር፣ ብሔራዊ ጥቅማችንን በማሳደግ፣ ከጎረቤት ሀገሮች እና ከተለያዩ ሀገራት ጋር በጋራ ጥቅም ላይ የተመሠረተ ትብብር እንዲቀጥል፣ ቀጣናዊ ትስስርን፣ አሕጉራዊ እና አለማቀፋዊ ትብብርን ለማጠናከር የሚያስችሉ ሥራዎች ተሠርተዋል”።የሰላም
DW Amharic : የቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (RSADO) በኤርትራ የሚያደርገውን የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡ በኤርትራ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው የቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና በሌሎች የሲቪክ ማህበራት አዘጋጅነት ኢትዮጵያ ውስጥ ትናንት እሁድ ተዘጋጀ በተባለው የቀይ ባሕር አፋር ጉባኤ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ተገኝተዋል፡፡
የቀይ ባሕር አፋር በኢትዮጵያ ያካሄደው ሕዝባዊ ጉባኤ
የቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (RSADO) በኤርትራ የሚያደርገውን የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡ በኤርትራ በተቃዋሚነት የምንቀሳቀሰው የቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እና በሌሎች የሲቪክ ማህበራት አዘጋጅነት ኢትዮጵያ ውስጥ ትናንት እሁድ ተዘጋጀ በተባለው የቀይ ባሕር አፋር ህዝባዊ ጉባኤ በሺዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ የማህበረሰቡ አካላት ታዳሚ ነበሩም ተብሏል፡፡
የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሽኩቻ መሰል ዉጥረት በጎላበት ባሁን ወቅት በኤርትራ መንግስት በቀይ ባህር አፋር ህዝብ ላይ ይፈጸማል የተባለው ሰቆቃ መጉላቱን ያሳወቀው ጉባኤው ለዓለማቀፉ ማህበረሰብ የትኩረት ጥሪ አሰምቷልም።ትግራይ ክልል የእርስበርስ ግጭት እንዳይከሰት ሥጋት መፈጠሩን የሲቪክ ተቋማት ገለጹ
የቀይ ባሕር አፋር ሕዝብ ድርጅት አመራሮች፣ የስደተኞች ተወካዮች፣ የጎሳ መሪዎች እና የተለያዩ የማህበረሰብ አካላት ተሳትፈውበታል የተባለው ትናንት በአፋር ክልል ሰመራ-ሎጊያ ከተማ ላይ የተካሄደው ህዝባዊ ኮንፌረንስ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ባለስልጣናት መካከል የቃላት ጦርነትን ተከትለሎ ባሁኑ ወቅት በድንበር አከባቢዎች ላይ ውጥረት መንገሱን ያመለከተው አንዱና ዋነኛው የጉባኤው ተሳታፊና አዘጋጅ የቀይ ባህር አፋር ህዝብ ድርጅት ((RSADO) የቀይ ባሕር አፋር ህዝብ የጦርነት ሜዳ እንዳይሆን አስግቶናል ይላል፡፡ ከአከባቢው ድንበር ዙሪያ የህዝብ ማፈናቀል ብሎም እሰከ
DW Amharic : ፕሬዝደንት አብዱልፈታሕ አልሲሲ ሐገራቸዉ ድንበር ጋዛ ዉስጥ የሚደርሰዉ እልቂት፣የቀይ ባሕር ጥቃት፣የየመን መደብደብ፣ የሱዳንና የሊቢያ ትርምስ ያሳስባቸዉ ይሆናል።ሰሞኑን በጣም ያሳሰባቸዉ ግን ከሶማሊያ ፕሬዝደት ሐሰን ሼኽ ማሕሙድ ጋር አምና ነሐሴ የተፈራረሙት ሥልታዊ ወዳጅነት ነዉ …..
የየመን ሁቲዎች ከእስራኤል-ዩናይትድ ስቴትስና ከተባባሪዎቻቸዉ ጋር የገጠሙት መጠቃቃት ለቀይ ባሕር አካባቢ ሐገራት «የሩቅ» ጠብ ተብሎ የሚታለፍ ዓይደለም።የአዲስ አበባና የአሥመራ ገዢዎች የቃላት ጦርነትና የዲፕሎማሲ ሽኩቻ እየናረ ነዉ።በህግ የታገደዉ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይና የትግራይ ኃይሎች የሚባለዉ ጦር ለሁለት ተገመሰዉ አንደኛዉ አንጃ ከአሥመራ፣ሌለኛዉ ከአዲስ አበባ ገዢዎች ጋር «ፍቅር እንደገናን እያቀነቀኑ ነዉ።» ይባላል።የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ በትግራይ ክልል ጦርነት «እንዲጫር አንፈልግም» ባሉ በሳምንቱ የትግራይ ቀሳዉስት «ለሽምግልና» አዲስ አበባ ገብተዋል።ጠቅላይ ሚንስትሩ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁን ባሳወቁ በአራተኛዉ ቀን ደግሞ የግብፅና የሶማሊያዉ ገዢዎች«ሥልታዊ» ያሉትን ዉይይት አድርገዋል።ከዚያስ?
የተቃራኒዎች አንድ አቋም አብነት፣ የቀይ ባሕር ሥጋት
እሥራኤል በጋዛ ፍልስጤማዉያን ላይ የምትፈፅመዉ ግድያ፣እመቃና ማስራብን ፓኪስታን በተደጋጋሚ አዉግዛለች።የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቢኒያሚን ኔታንያሁ በፍልስጤሞች ላይ በተፈፀመዉ የጦር ወንጀል ተጠርጥረዉ የዓለም የጦር ወንጀለኞች መዳኛ ፍርድ ቤት (ICC) እንዲታሰሩ አዝዟል።
በፍልስጤሞች ላይ የሚደርሰዉን ግፍ የምታወግዘዉ ፓኪስታንም፣ በፍፍልስጤሞች ላይ በተፈጸመ የጦር ወንጀል የሚጠረጠሩት ኔታንያሁም የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የዓለም ታላቅ ሽልማት ኖቤል እንዲሸለሙ እኩል አጭተዋቸዋል።የተቃርኖ «አንድነት» ይባል ይሆን?


ዋሽግተን ዲሲ።የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቢኒያሚን ኔታንያሁ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንትን ለኖቤል የሰላም ሽልማት ያጩበትን ደብዳቤ ለፕሬዝደንት ዶናልድ ትራም ሲያስረክቡ።ምስል፦ Kevin
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከማክሮ ኢኮኖሚ ለውጡ ጋር ተያይዞ የመጣው አዲስ የውጭ ምንዛሬ ተመን የ36.9 ቢልዮን ብር ኪሳራ እንዳስከተለበት ታወቀ
“ባንኮች በእንዲህ አይነት የምንዛሬ ተመን ለውጥ ወቅት ኪሳራ እንደሚያጋጥማቸው ቢታወቅም የዚህ የኪሳራ መጠን ግን እጅግ ከፍተኛ ተብሎ ሊወሰድ ይችላል”
የመሠረት ሚድያ የፕሪሚየም አባል ከሆኑ በፅሁፍ የተዘጋጀውን ይህን መረጃ ይከታተሉ ⤵️
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/369?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
በጀኔቫ የተመድ ጽሕፈት ቤት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ጸጋአብ ክበበው፣ አምባሳደር ጸጋአብ፣ የኤርትራ ድርጊት በኢትዮጵያ ላይ ቀጥተኛ የጦርነት ስጋት የሚደቅን ነው በማለት ከሰዋል። የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በኤርትራ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተር የጊዜ ቆይታን ለማራዘም ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ላይ በተሰበሰበበት ወቅት፣ አምባሳደር ጸጋአብ የኤርትራ ወታደሮች በተቆጣጠሯቸው የትግራይ አካባቢዎች የከፉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን እየፈጸሙ ይገኛሉ ብለዋል። አምባሳደሩ ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ ደቅነዋለች ላሉት ስጋት፣ የኤርትራ ወታደሮች የትግራይ አንዳንድ አካባቢዎችን ተቆጣጥረው እንደሚገኙ የተመድ ልዩ ራፖርተር ለምክር ቤቱ ያቀረቡትን ሪፖርት በአስረጅነት ጠቅሰዋል።
በተመድ የጀኔቫ ቋሚ ጽሕፈት ቤት የኤርትራ ልዑክ ሃብቶም ዘርዓይ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ውንጀላ ካለፉት ድርጊቶቿና አቋሞቿ ጋር የማቃረንና ወጥነት የሌለው መኾኑን በመጥቀስ በምክር ቤቱ ውስጥ ምላሽ ሠጥተዋል። የኤርትራ ጦር በዓለማቀፍ ሕግ በሚታወቀው የኤርትራ ግዛት ብቻ እንደሚገኝ የጠቀሱት ሃብቶም፣ የኤርትራ ጦር የኢትዮጵያን ግዛቶች ይዟል የሚባለው ትርክት “ጦርነት ለመቀስቀስ” እና “ለጦርነት ሽፋን ለመፍጠር ያለመ ሴራ” ነው በማለት ውድቅ አድርገውታል። ኢትዮጵያ ባኹኑ ወቅት በይፋ ዛቻዎችን መሠንዘር፣ ጦር መሳሪያ ማከማቸትና ቀጠናዊ ሰላምና ጸጥታን የሚያደፈርሱ ድርጊቶችን መፈጸም ቀጥላለች ያሉት ሃብቶም፣ ኢትዮጵያ ይህን የምታደርገው ውስጣዊ ችግሮቿን ለመሸፋፈን መኾኑን ምክር ቤቱ መረዳት አለበት ብለዋል።
አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ በአዲስ መዋቅር ስር ሆኖ እንደሚቀጥል አስታወቀች
የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (USAID) ቢዘጋም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈጸሙ “የሁለትዮሽ የእርዳታ ስምምነቶች” በሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ስር በተዘረጋው አዲስ መዋር እንደሚቀጥሉ የአሜሪካ ኤምባሲ አስታወቀ። ኤምባሲው ዋነኛ ናቸው ያላቸው የሰብአዊ እርዳታ፣ ዓለም አቀፍ ጤና እና የምግብ ዋስትና መርሃ ግብሮች በአዲሱ መዋቅር እንደሚቀጥሉ ዛሬው ባወጣው መግለጫ አረጋግጧል።
አሜሪካ በእነዚህ ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ እንደሚቀጥል ኤምባሲው ማረጋገጫ የሰጠው፤ የሀገሪቱ ተራድኦ ደርጅት የሆነው USAID ባለፈው ምንት በይፋ መዘጋቱን ተከትሎ ነው። ላለፉት 64 ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሰብአዊ እና የልማት እርዳታ ሲያቀርብ የቆየው ይህ ተቋም የተዘጋው፤ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ድርጅቱን ቀስ በቀስ ሲያዳክመው ከቆየ በኋላ ነው።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት፤ ድርጅቱ የነበሩትን ኃላፊነቶች ካለፈው ሰኞ ሰኔ 24፤ 2017 ጀምሮ በይፋ ተረክቧል። ሽግግሩ “ድግግሞሽን ለመቀነስ”፣ “ተጠያቂነትን ለማጠናከር” እና የእርዳታ መርሃ ግብሮችን ከዩናይትድ ስቴትስ “የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ እና የብሔራዊ ደህንነት ዓላማዎች ጋር ለማጣጣም የሚያስችል” ሆኖ እንደተቀረጸ የአሜሪካ ኤምባሲ በዛሬው መግለጫ ጠቁሟል።
በሽፋን ምርመራ ወቅት “ከግድያ በስተቀር” የሚፈጸም ወንጀልን ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርገው አወዛጋቢ ድንጋጌ ተሰረዘ
በወንጀል የተገኘ ንብረትን ህጋዊ ማስመሰል እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን “በሽፋን ስር” ሆኖ የመመርመር ኃላፊነት የተሰጠው ሰው፤ “ከግድያ በስተቀር” የሚፈጽማቸውን የወንጀል ድርጊቶች ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርገው ድንጋጌ ተሰረዘ። ድንጋጌው የተሰረዘው አዋጁ “በሰፊው እንዲተረጎም ስለሚያደርግ” እና በአተገባበሩም ላይ “አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያስከትል ስለሆነ ነው” ተብሏል።
አወዛጋቢው ድንጋጌ ተካትቶ የነበረው፤ በወንጀል የተገኘ ንብረትን ህጋዊ ማስመሰል እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በወጣ አዋጅ ላይ ነበር። እነዚህን ወንጀሎች ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ከ12 ዓመት በፊት የወጣውን ህግ ያሻሻለው አዲሱ አዋጅ በፓርላማ የጸደቀው ሰኔ 10፤ 2017 ነበር።
በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራን በተመለከተ በአዋጁ የተካተተ ድንጋጌ፤ በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እና በሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ትችት ቀስቅሶ ሰንብቷል። ድንጋጌው “በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ ወይም በቁጥጥር ስር የሚደረግ ማስተላለፍን እንዲያስፈጽም የተመደበ ሰው፤ በግዴታው ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት እና ከፈቃዱ ውጭ ሆኖ ከግድያ ወንጀል በስተቀር ለሚፈጽመው የወንጀል ድርጊት የወንጀል ክስ አይቀርብበትም” ይላል።
አዋጁ በጸደቀበት ዕለት የውሳኔ ሃሳብ ለፓርላማ ያቀረበው የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚቴ፤ ድንጋጌው እንዲካተት የተደረገው “ልዩ የምርመራ ስራን” “ውጤታማ የሚያደርግ በመሆኑ” ምክንያት እንደሆነ ገልጾ ነበር።
🔴ዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16248/
አል-ፋሽጋ ዳግም በኢትዮጵያውያን እጅ ገባ
ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል።
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት በትግራይ ክልል የህግ ማስከበር ዘመቻ ላይ በነበረበት ወቅት የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም፣በሱዳን ጦር ተወርሮ የነበረው ሰፊና ለም መሬት፣ አሁን በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ገበሬዎችና ሚሊሻዎች ቁጥጥር ስር ውሏል።
የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን የውስጥ ችግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር፣ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የመተማና የቋራ ወረዳ ለም መሬቶችን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር።
በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ሁኔታውን በትዕግስት ሲከታተል የነበረ ሲሆን፣ መንግሥትም ችግሩን በዲፕሎማሲና በውይይት ለመፍታት ያለውን ፍላጎት በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል፡፡
በዚህ የሱዳን ወረራ ወቅት ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ከእርሻቸው ከመፈናቀላቸውም በላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብልና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው አይዘነጋም፡፡
የሱዳን ባለሥልጣናት ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት በመታገዝ የአማራ ክልል አዋሳኝ ወደኾኑ የሱዳን ለም መሬቶች በመስፋፋት ላይ ናቸው ሲሉ መክሰሳቸው ተዘግቦ ነበር፡፡
andafta
ዘንድሮ 23 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ከሴፍቲኔት ተረጂነት ወጥተዋል በሚል ትናንት በጠ/ሚሩ የቀረበው መረጃ የተሳሳተ መሆኑ ተጠቆመ
“ባለፈው አመትም ይሁን ዘንድሮ፣ ወይም ከዛ በቀደሙት አመታት የሴፍቲ ኔት ፕሮግራም ውስጥ 23 ሚልዮን ወይም 27 ሚልዮን ሰዎች አልነበሩም። ፕሮግራሙ በ1997 ዓ/ም ከጀመረ ወዲህ ከፍተኛው የሴፍቲ ኔት ተጠቃሚ ቁጥር በአመት ከ8 ሚልዮን በልጦ አያውቅም”- የሴፍቲ ኔት ፕሮግራም አስተባባሪ………….. https://meseretmedia.substack.com/p/23