Blog Archives

ከፋኖ ጋር ጦርነቱ ይቀጥላል ( ጄኔራሉ )……. ;አደጋው የከፋ ይሆናል (አቡነ ማትያስ)


Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, አዉሮጳ, አፍሪቃ, ኢትዮጵያ, ኤኮኖሚ, ፖለቲካ

የአዲስ አበባው ታላቅ ‘የማፊያ ስራ’!

(መሠረት ሚድያ)- አራት ኪሎ የሚገኘው ‘አምባሳደር ህንፃ’ ላይ ይገኝ የነበረው የድርጅቱ ቢሮ ውስጥ ሲገባ በመጀመርያ ቀልብን የሚስበው በብዙ የመንግስት ቢሮዎች ውስጥ እንደሚደረገው በትልቁ ታትሞ እና በፍሬም ተዘጋጅቶ የተሰቀለው የጠ/ሚር አብይ አህመድ እና የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ፎቶ ነው። ድርጅቱ ቢሮው ብቻ ሳይሆን ማስታወቂያውም ቀልቢ ሳቢ ነበር። “ልጄ ውጭ ሀገር ሄዳ ነው ትምህርቷን መከታተል የምትፈልገው፣ አገሯን የምታስጠራ ምሁር እንድትሆንልኝ እፈልጋለሁ” ትላለች ዝነኛዋ የማስታወቂያ ባለሙያ ሙሉአለም ታደሰ ከሌላኛዋ ታዋቂ የሚድያ ሰው ዳናይት መክብብ ጋር በመሆን በጋራ የሰሩት የዚህ ድርጅት ማስታወቂያ። ይህ ዛሬ የምናቀርብላችሁ የከባድ ማጭበርበር ድርጊት ዋና ተዋናይ ቀላል ሰውም አይደለችም። ከጥቂት አመታት በፊት በአዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ላይ ከ ‘ተስፋ ሰጪ’ ‘እና ‘ስራ ፈጣሪ’ አምስት የሀገራችን ግለሰቦች አንዷ ሆና ቀርባለች፣ በተጨማሪም ከሴቶች እና ህፃናት ማህበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጌጎ ተስፋዬ ልዩ ሽልማት ተበርክቶላታል። ግለሰቧ ቤተልሄም ታደሰ ይማም ትባላለች፣ ታድያ ተሸላሚ ያረጋት ስራዋ ምን ይሆን? ድርጅቷ ከ120 ሚልዮን በላይ ብርስ ከህዝብ እንዴት ማጭበርበር ቻለ? ቤተልሄም ታደሰ ይማም ከቅርብ ግዜ ወዲህ ለስራ ወይም ለትምህርት ወደ ውጪ ሀገር ሰው እንልካለን በማለት ገንዘብ የሚሰበስቡ ድርጅቶች መብዛታቸውን ብዙ ሰው ታዝቧል፣ ከነዚህም አንዱ Aim Ultra Consultancy የተባለው ድርጅት ነው። “እኔ Aim Ultra ን ለደቂቃ እንኳን አልተጠራጠርኩም። ማስታወቂያውን ታዋቂ ሰዎች በቲቪ እና በሶሻል ሚድያ ሲሰሩ ስላየሁ እውነት ይሆናል ብዬ ከቤተሰብ ያገኘሁት ገንዘብ ላይ ከብድር እና ቁጠባ ተጨማሪ በመበደር 520,000 ብር ከፈልኩ”
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, አዉሮጳ, አፍሪቃ, ኢትዮጵያ, ኤኮኖሚ

አብይ አሕመድ እና በአውሮፓ የገጠመው ተቃውሞ

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, አዉሮጳ, አፍሪቃ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

የአብይ አህመድ አቀባበል በለንደን ……. የአማራ ፋኖ በእንግሊዝ !

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, አዉሮጳ, አፍሪቃ, ኢትዮጵያ

ሩሲያ የናዚ ጀርመን በሁለተኛው የአለም ጦርነት በይፋ የተሸነፈበትን 80ኛ አመት የድል በዓሏን አክብራለች።

ሩሲያ የናዚ ጀርመን በሁለተኛው የአለም ጦርነት በይፋ የተሸነፈበትን 80ኛ አመት የድል በዓሏን አክብራለች። በድል በዓሉ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ፣ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ እና የቻይናውን ፕሬዚዳንት ጨምሮ የተለያዩ ሃገራት መሪዎች ተሳትፈዋል። በተጨማሪ የቡርኪናፋሶው መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ በፕሬዚዳንት ፑቲን ግብዣ የግል አውሮፕላን ከሞስኮ ተልኮለት በፕሮግራሙ እንዲሳተፍ ተደርጓል። መሪዎቹ ትናንት በክሬምሊን የእራት ግብዣ የተደረገላቸው ሲሆን ዛሬ በዓሉ በአደባባይ በወታደራዊ ትርዒቶች ተከብሯል። የዛሬው ወታደራዊ ሰልፍ ሞስኮ ወደ ዩክሬን ጦሯን ካዘመተች በኋላ ትልቁ ነው ሲባል ከ10 አመታት በኋላ የበርካታ ሃገራት መሪዎች የተገኙበትም ነው ተብሏል። ፕሬዚዳንት ፑቲን ባደረጉት ንግግርም በአሁኑ ወቅት በዩክሬን እየተፋለሙ ያሉ የጦር ሰራዊታቸውን አሞግሰዋል። በወታደራዊ ሰልፉ ላይ ከ11,500 በላይ ወታደሮቼ እና ከ180 በላይ ወታደራዊ መኪኖች ተካፋይ ሆነዋል። የሩሲያ የአየር ኃይል ቡድንም የአየር ላይ ትርኢቶችንም አሳይተዋል። የፑቲን የውጪ ጉዳይ አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ ይህንን የጋራ በዓላችንን በማስመልከት ፕሬዚዳንት ፑቲን እና ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሃሳብ መለዋወጣቸውን እና የእንኳን አደረሰህ መልዕክት እንደተለዋወጡ ለሚዲያዎች ገልፀዋል። ሶቪየት ህብረት በሁለተኛው የአለም ጦርነት ንቁ ተሳታፊ የነበረች ሲሆን ከ21 ሚሊየን ሰዎች በላይም በጦርነቱ አጥታለች። የናዚ ጀርመን በይፋ በሁለተኛው የአለም ጦርነት የተሸነፈበትን ምክንያት በማድረግ ሩሲያ ቀኑን እንደ ድል በዓል የምታከብር ሲሆን ዘንድሮ 80ኛ አመቱን እያከበረች ትገኛለች። Source: AP , Sputnik
Posted in News, አዉሮጳ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

የፕሬዝዳንት ትራምፕ የዩክሬንን ጦርነት የማስቆም ዕቅድ

ተመራጭ ፕሬዝዳንት ትራም እራሳቸውም ሰኞ እለት ለአንድ ሜዲያ በሰጡት አስተያየት ፕሬዝዳንት ፑቲንም ከሳቸው ጋር መገናኛኘቱን እንደሚፈለጉትና ከሰኞው በዓለ ሹመት በሗላ እንደሚገናኙ ያላቸው እመነት በመግለጽ ይህ ሁለቱንም በተለይም ዩክሬንን እያወድመ ያለ ጦርነት ባስችኳይ መቆም እንድላበት እንደሚያምኑ አስታውቀዋል።
Posted in አዉሮጳ