Home › Archive for Ethiopia News
Blog Archives
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ ‘ምጥጥን’ አዲስ አሰራር እና 40 ፐርሰንት የሚሆነውን ሰራተኛ እጣ ፈንታ
– የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የፌዴራል ተቋማት ኢትዮጵያን እየመሰሉ የመጡበት ሁኔታ ተፈጥሯል በማለት በዛሬው ዕለት ተናግረዋል
– ሰራተኞች ደግሞ ብሄርን መሰረት ባደረገ ‘ምጥጥን’ የሚባል አሰራር ከስራችን ተባረን ጎዳና ልንወጣ ነው በማለት ለሚድያችን ተናግረዋል
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/40-fd7
የኢትዮጵያ ብር ዋጋ በተያዘው የአውሮፓዊያን ዓመት ብቻ ከአሜሪካ ዶላር አንጻር ዋጋው በ15 በመቶ ማሽቆልቆሉን ብሉምበርግ ዘገበ። ብር ባሁኑ ወቅት ከአርጀንቲናው ፔሶ እና ከቱርኩ ሊሬ ቀጥሎ በዓለም ደካማው መገበያያ ገንዘብ መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል። የብር ዋጋ ወደፊትም ኢትዮጵያ የውጭ እዳዋን ማሸጋሸግ ከመቻሏ ጋር የተሳሰረ ሆኖ እንደሚቀጥል ዘገባው አመልክቷል። መንግሥት የአገሪቱን 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ብድር መልሶ ለማዋቀር ከወራት በፊት ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ላይ መድርሱ ይታወሳል። ኾኖም የአገሪቱ የወጪ ገቢ ማደግ፣ የመንግሥት የበጀት ክፍተት መቀነስ እንዲሁም መንግሥት ከ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ ያዥ ዓለማቀፍ ኢንቨስተሮች ጋር በቦንዱ አከፋፈል ላይ ስምምነት ሊደርስ ይችላል የሚለው ተስፋ፣ በብር ላይ ያለውን ጫና ሊያቃልለው እንደሚችል ባለሙያዎች እምነታቸውን ገልጸዋል ተብሏል። ባኹኑ ወቅት መደበኛው የ1 ዶላር መግዣ ዋጋ 151 ብር ሲሆን፣ በትይዩ ገበያ ደሞ ወደ 180 ብር አሻቅቧል።
በአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 55ኛ ክ/ጦር ከዛሬ ታህሳስ 13/2018 ዓ/ም ጀምሮ ከባህር ዳር ጭንባ ቁንዝላ ደለጎ፣ ከዱርቤቴ ዝህብስት ወገዳ፣ ከዱርቤቴ ሀሙሲት ማማላ፣ ከዱርቤቴ ቀደምት ላሊበላ ልሁዲ ያለው አውራ ጎዳና ላልተወሰነ ጊዜ ዝግ ሆኖ እንደሚቆይ አስታውቋል።
ክፍለጦሩ በጠቀሳቸው ቀጠናዎች የአገዛዙን ተልዕኮ ተቀብለው ተሽከርካሪን በማገት ማውደምና አሽከርካሪን አግቶ ገንዘብ መጠየቅ፣ ተጓዦችን መዝረፍና መሰል እኩይ ተግባራትን በሚፈፅሙ ዘራፊ ባንዳዎች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ያመቸኝ ዘንድና በኦፕሬሽኑ ንፁኋኖች እንዳይጎዱብኝ በማሰብ ነው መንገዱ የሚዘጋው ሲል መግለፁን መረብ ሚዲያ ከክፍለጦሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ተመልክቷል።
በተጨማሪም ክፍለጦሩ፡ በተጠቀሱት ቀጠናዎች የተጣለውን እገዳ ተላልፎ የተገኘ አሽከርካሪም ይሁኑ ሌሎች ተጓዦች ለሚደርስባቸው ማንኛውም ችግር ኃላፊነቱን እራሳቸው ይወስዳሉ ሲል አሳስቧል።
ዘረፋ፣ እገታና መሰል እኩይ ተግባራትን በሚፈፅሙ ባንዳና ዘራፊዎች ላይ በአጭር ጊዜ ተገቢውን እርምጃ ወስጄ እስከማጠናቅቅ ሕዝቡ በትግስት ይጠብቀኝ ሲል ክፍለጦሩ በሕዝብ ግንኙነት ክፍሉ በኩል መልዕክት ማስተላለፉንም መረብ ሚዲያ ተመልክቷል።
ፋኖ፡ አገዛዙ የአማራ ሕዝብን በማሕበራዊና በኢኮንሚያዊ ሕይወቱ እረፍት እንዲነሱለት አደራጅቶ ያሰማራቸው ዘራፊ ወንበዴዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
በተመሣሣይ በሰሜን አማራ ቀጠና ከደብረ ታቦር ወረታ ያለው መስመርን የዘጋ በዘራፊዎች ላይ የተለየ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ጣቢያችን ከሰሞኑ መዘገቡ አይዘነጋም።
“በጋምቤላ ክልል ያሉ ስደተኞችን በተመለከተ የሚሰራጨው ሐሰተኛ መረጃ አሳስቦኛል” የተመድ የስደተኞች ኤጀንሲ
የተመድ የስደተኞች ኤጀንሲ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በጋምቤላ ክልል የሚገኙ ስደተኞችን ኢላማ ያደረጉ የተሳሳቱ መረጃዎች መሰራጨታቸው እንዳሳሰበው ገልጿል።
ኤጀንሲው ስደተኞቹ በሃገራቸው ካጋጠማቸው ግጭት የተነሳ ደኅንነትና ጥበቃ ፈልገው መጥተዋል ያለ ሲሆን ሁሉም ሰው ስደተኞች እና ስደተኞቹን የተቀበሉ ማኅበረሰቦች ላይ የጥላቻ ንግግርን እንዳይደረግ ጠይቋል።
የተመድ ኤጀንሲ በክልሉ የተከሰተው ሁኔታ የምግብ እና ውሃ ሥርጭትን ጨምሮ አንዳንድ አገልግሎቶች በጊዜያዊነት እንዲቆሙ ማስገደዱን አንስቶ ሁኔታውን እየተከታተለ ስለመሆኑና ከአስተዳደር አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
እንደ የስደተኞች ኤጀንሲው ዘገባ ከ482 ሺህ በላይ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በኢትዮጵያ የሚገኙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ከ447 ሺህ በላዩ የሚገኙት በጋምቤላ ክልል ነው።
ከባለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ ደግሞ ከ50,000 በላይ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ወደ ጋምቤላ ክልል መግባታቸውም ተገልጿል።
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ የሚገኝ የንፁህ መጠጥ ውሀ መስመር በታጣቂዎች በመቆረጡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አደጋ ላይ መውደቃቸው ታወቀ
የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የፌደራል የፀጥታ ሀይሎች ካሳለፍነው ሀሙስ ጀምሮ ወደ ክልሉ በብዛት መግባታቸውን ተከትሎ ግጭቱ በአብዛኛው ቢቆምም የውሀ መቋረጡ በፍጥነት ካልተገታ በርካቶችን ሊጎዳ እንደሚችል የሚድያችን ምንጮች ተናግረዋል
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/8c6
” ቤቴና መሶቤ ሙሉ ነበር ከቀዬ ከተፈናቀለኩ በኃላ ግን ሁሉ ባዶ ታሪክ ሆኗል ፤ እኔና 6 ቤተሰቦቼ ከምንበላው ጦማችን የምናድርበት ጊዜ ይበዛል ድረሱልን ” – በመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃይ
➡️ ” ጊዚያዊ አስተዳደሩና የመንግስት መዋቅሩ ረሀቡ መከሰቱ በማህበራዊ የትስስር ገፃች ከመነገሩ በኃላ መንቃቱ የአመራር ክፍተት ዋነኛ ማሳያ ነው ” – አስተያየየት ሰጪዎች

በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አስገደ ወረዳ ከእንዳስላሰ-ሽረ ከተማ አቅራቢያ የምትገኘው #ሕፃፅ ከደም አፈሳሹ የትግራይ ጦርነት በፊት የኤርትራ ስደተኞች ማቆያ በመሆን ትታወቃለች።
በሕፃፅ የስደተኞችና የተፈናቃዮች የመጠለያ ጣብያ የዛሬውን ያህል በእህል፤ ውሃና ህክምና እጦት የገረጡ ፊቶች ታይተው አያውቁም።
ሕፃፅ በዙሪያዋ ከሚገኘው የወርቅ ማዕድን ሀብት በሚሊዮን የሚገመት ብር የሚዛቅበት ሆና ሳለ በጉያዋ ግን በሀይለኛ ረሀብና ውሃ ጥም ተፈናቃዮች ወደ መቃብር ይሸኙባታል።
አርሶ አደር ጉዕሽ በትግራዩ ጦርነት ምክንያት ከምዕራባዊ ዞን አደባይ ከተባለ ሰፊ እርሻ ያለበት ቦታ ተፈናቅለው በሕፃፅ የመጠለያ ጣብያ በአሮጌ ፕላስቲክ በተሰራ ቤት መኖር ከጀመሩ 5 ዓመታት ተቆጥረዋል።
አርሶ አደሩ በመጠለያ ጣብያዋ ከሚገኙ 16 ሺህ ተፈናቃዮች መካከል ሲሆኑ ‘ አስቸኳይ እርዳታ ካላገኙ ለቀናት እንኳን በህይወት መቆየት ይከብዳቸዋል ‘ ተብለው በዞኑ ከተጠኑ 1,700 በላይ የተቸገሩ ወገኖች አንዱ ናቸው።
በድስት ያረረ ወጥ እያሳዩ ” ቤቴና መሶቤ ሙሉ ነበር ከቀዬ ከተፈናቀለኩ በኃላ ግን ሁሉ ባዶ ታሪክ ሆኗል ፤ እኔና 6 ቤተሰቦቼ ከምንበላው እራት ጦማችን የምናድርበት ጊዜ ይበዛል ድረሱልን ” ሲሉ ተማፅነዋል።
ሌላኛዋ ራሷና ሁለት
” ቤቴና መሶቤ ሙሉ ነበር ከቀዬ ከተፈናቀለኩ በኃላ ግን ሁሉ ባዶ ታሪክ ሆኗል ፤ እኔና 6 ቤተሰቦቼ ከምንበላው ጦማችን የምናድርበት ጊዜ ይበዛል ድረሱልን ” – በመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃይ
➡️ ” ጊዚያዊ አስተዳደሩና የመንግስት መዋቅሩ ረሀቡ መከሰቱ በማህበራዊ የትስስር ገፃች ከመነገሩ በኃላ መንቃቱ የአመራር ክፍተት ዋነኛ ማሳያ ነው ” – አስተያየየት ሰጪዎች
በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አስገደ ወረዳ ከእንዳስላሰ-ሽረ ከተማ አቅራቢያ የምትገኘው #ሕፃፅ ከደም አፈሳሹ የትግራይ ጦርነት በፊት የኤርትራ ስደተኞች ማቆያ በመሆን ትታወቃለች።
በሕፃፅ የስደተኞችና የተፈናቃዮች የመጠለያ ጣብያ የዛሬውን ያህል በእህል፤ ውሃና ህክምና እጦት የገረጡ ፊቶች ታይተው አያውቁም።
ሕፃፅ በዙሪያዋ ከሚገኘው የወርቅ ማዕድን ሀብት በሚሊዮን የሚገመት ብር የሚዛቅበት ሆና ሳለ በጉያዋ ግን በሀይለኛ ረሀብና ውሃ ጥም ተፈናቃዮች ወደ መቃብር ይሸኙባታል።
አርሶ አደር ጉዕሽ በትግራዩ ጦርነት ምክንያት ከምዕራባዊ ዞን አደባይ ከተባለ ሰፊ እርሻ ያለበት ቦታ ተፈናቅለው በሕፃፅ የመጠለያ ጣብያ በአሮጌ ፕላስቲክ በተሰራ ቤት መኖር ከጀመሩ 5 ዓመታት ተቆጥረዋል።
አርሶ አደሩ በመጠለያ ጣብያዋ ከሚገኙ 16 ሺህ ተፈናቃዮች መካከል ሲሆኑ ‘ አስቸኳይ እርዳታ ካላገኙ ለቀናት እንኳን በህይወት መቆየት ይከብዳቸዋል ‘ ተብለው በዞኑ ከተጠኑ 1,700 በላይ የተቸገሩ ወገኖች አንዱ ናቸው።
በድስት ያረረ ወጥ እያሳዩ ” ቤቴና መሶቤ ሙሉ ነበር ከቀዬ ከተፈናቀለኩ በኃላ ግን ሁሉ ባዶ ታሪክ ሆኗል ፤ እኔና 6 ቤተሰቦቼ ከምንበላው እራት ጦማችን የምናድርበት ጊዜ ይበዛል ድረሱልን ” ሲሉ ተማፅነዋል።
ሌላኛዋ ራሷና
በእነ የተከበሩ አቶ ዮሐንስ ቧያለው መዝገብ ከመጋረጃ ጀርባ የመሰከረው ግለሰብ መቶ አለቃ አሰፋ አድማሱ መሆኑ ተረጋገጠ።
ግለሰቡ በምዕራብ ጎጃም ዞን የቋሪት ወረዳ ተወላጅ ሲሆን እስከ 2016 ዓ.ም ታህሳስ አጋማሽ ድረስ በገረመው ወንዳወቅ ብርጌድ የፋኖ አባል ነበር።
ግለሰቡ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊና የቀድሞው የባህርዳር ከንቲባ ድረስ ሳህሉ የቅርብ ዘመድ ሲሆን ከዚሁ ባለስልጣንም ሽልማት ተቀብሏል። ከዚህ በተጨማሪም በእስር ላይ ከሚገኙት የምክር ቤት አባሉ ከአቶ ክርስቲያን ታደለ ጋር የቅርብ ዘመድም መሆኑ ተገልጿል። አቶ ክርስቲያን ታደለ ምርጫ ሲወዳደሩ ምርጫውን አሸንፈው የምክርቤት አባል እንዲሆኑ ቅስቀሳ ሲያደርግ ነበር።
ይሁን እንጅ ግለሰቡ ጥቅም ፈላጊ በመሆን በመንግስትም በታጋዮቹም ዘንድ ለመመስገን ጥረት ያደርግ እንደነበር የቅርብ ማስረጃዎች አሉ። በዚህም በቋሪት፣ በፍኖተ ሰላምና በባህርዳር ቤትና ሌላ ንብረት ያለው ሲሆን በአሁኑ ወቅት ፋኖን በመክዳት ከመንግስትና ከብልጽግና ፓርቲ ጋር እየሰራ ይገኛል።
በነገራችን ላይ ግለሰቡ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ የተለየ ጥበቃ እየተደረገለት ይገኛል።
ግለሰቡ ለፍትሕ ሚኒስቴር ቃል በገባኸውና እኛ ባልንህ መሰረት አልመሰከርክም፤ ይህንን ያደረከው ደግሞ ከተከሳሾች ጋር ተደራድረህ ነው የሚል ዛቻና ማስፈራሪያ እየደረሰበት እንደሆነ የዐቃቤ ሕግና የደህንነት ምንጮች አረጋግጠዋል።
ከመጋረጃ ጀርባ የመሰከረው ይህ ግለሰብ ሊታሰርና ክስ ሊመሰረትበት እንደሚችልም ተገልጿል።
ላልተገራ ሥልጣን መታዘዝ እና ከአንባገነናዊ ባህሪ ጋር መዋሃድ፤ (ያሬድ ኃይለ ማርያም )
Obedience to authoritarian and internalization of authoritarian attitudes
+++++
“Blind obedience to authority is the greatest enemy of truth”
Albert Einstein
እንደምን ከረማችሁ የመልዕክተ ቅዳሜ ታዳሚዎች? አሰልሳ ብቅ ባለችው የዛሬዋ መልዕክተ ቅዳሜ ዋነኛ የትኩረት ነጥብ አንድ ማህበረሰብ ከአምባገነናዊ ሥርዓቶች ሳይላቀቅ ለረዥም ጊዜ በአፈና ውስጥ ሲቆይ እና በግፍ፣ ጭካኔ እና ሰቆቃ ውስጥ ሲኖር ከገዢዎቹ ከሚወርሳቸው ነገሮች አንዱ በሆነው ግፍን የመላመድና አንባገነናዊ ባህሪን የመላበስ ዝንባሌ ላይ የሚያተኩር ይሆናል፡፡
በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ልጽፍ ያሰብኩት ያለፈው ሳምንት ቅዳሜ ነበር፡፡ ምክንያቱም ሃሳቡ የመነጨው የብልጽግና አገዛዝ በአለባበሳችሁ ባህልን እና ልማድን አጉድፋችኋል በሚል ለተወሰኑ ቀናት ወይም ከሳምንት በላይ ለቆየ ጊዜ ያሰራቸውን ቲክቶከሮች ተከትሎ በማህበረሰባችን በጉል የነበረው ግብረ ምላሽ ያጫረብኝ ነገር ነበር፡፡ ቲክቶከሮቹ የአገሪቱን ባህል፣ ወግ እና ልማድ በሚጥስ መልኩ ለብሰው በአደባባይ በመታየታቸው በወንጀል ጠርጥሬ አስሬያቸዋለሁ ብሎ የፌደራል ፖሊስ መግለጫ ሲሰጥ በደቦ እልል እያለ ድጋፉን የሰጠው አብላጫው የማህበረሰባችን ክፍል ልጆቹ ሲፈቱ እና መንግስት ለምን እና እንዴት ሊፈታቸው እንደቻለ ምንም መግለጫ ሳይሰጥ ሲቀር ደግሞ ያሁሉ የባህል ተቆርቋሪ እና ተሟጋች እንዴት ተፈቱ? የወንጀሉሱ ጉዳይ? ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎችን አለማንሳቱ አግራሞት ስለጫረብኝ ነው ርዕሱን ሰፋ ባለ መንገድ ከማህበረሰብ ባህሪ ጋር በማያያዝ ልመለስበት የወደድኩት፡፡
የልጆቹን ጉዳይ ላቆየውና ከላይ በርዕሱ ላይ እንደገለጽኩት አንድ ማህበረሰብ ወይም የአንድ አገር ሕዝብ ምን ሁኔታዎች ሲገጥሙት
ካሜራ የተገጠመላቸው ገቢ ሰብሳቢዎች 11 ሰዓት ላይ ካሜራ ለቢሯቸው ካስረከቡ በኋላ ድጋሜ በመውጣት ዘረፋ ላይ እየተሰማሩ መሆኑ ታወቀ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ካሜራው ‘ሙሉ ለሙሉ ችግሩን ይቀርፋል’ ቢልም ገና ካሁኑ አንዳንድ ሰራተኞች የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ገንዘብ ዘረፋ መጀመራቸውን መሠረት ሚድያ አረጋግጧል።
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/11
ኢትዮጵያ በጋዛ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ እንድትሳተፍ ከአሜሪካ ጥሪ እንደቀረበላት ተገለጸ።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከቀናት በፊት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ጋር በስልክ መነጋገራቸው መገለጹ ይታወሳል።
በወቅቱ በውይይቱ ሁለቱ ሀገራት ለቀጠናዊ መረጋጋት እና በአፍሪካ ቀንድ ሰላምን ለመገንባት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የገለጹበት እንደነበር ስቴት ዲፖርትምንት በወቅቱ ገልጾ ነበር።
ዛሬ ታይምስ ኦፍ እስራኤል ይዞ በወጣው ዘገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በዚህ ውይይት ወቅት ኢትዮጵያ በጋዛ ሰርጥ በሚቋቋመው ዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይል ተሳታፊ እንድትሆን መጠየቃቸውን አንስቷል። ይሁን እንጂ ዘገባው የኢትዮጵያን ምላሽም ሆነ ዝርዝር ጉዳዮችን አላካተተም።
ማርኮ ሩቢዮ በአንድ ጋዜጣዊ መግለጫቸው “ያነጋገርናቸው ሀገራት ሁሉም በሚባል ደረጃ ወታደሮቻቸውን ለመላክ ምን ዓይነት ግዳጅ ውስጥ እንደሚገቡ እና የፋይናንስ አቅርቦቱ ምን እንደሚመስል ማወቅ እንደሚፈልጉ ጠቁመዋል።
ማርክ ሮቢዮ ይህንን የተናገሩት ፓኪስታን ወታደሮቿን ለማሰማራት ፈቃደኝነቷን መግለጿን ተከትሎ በቀረበላቸው ጥያቄ ውቅት ሲሆን የፓኪስታንን ጥያቄ “እያጤነው ነው” ሲሉም መልሰዋል።
አብዛኞቹ የአረብ ሀገራት ወታደሮቻቸውን ለመላክ “የፍልስጤም መንግስት ምስረታ የጊዜ ሰሌዳ በግልጽ እንዲቀመጥ” የሚል ጥብቅ ቅድመ ሁኔታ ሲያስቀምጡ አንዳንዶቹ የሰላም አስከባሪ ኃይሉ የእስራኤልን ወታደራዊ ፍላጎት ብቻ የሚያስፈጽም እንዳይሆን እና በሕዝባቸው ዘንድ “ተቃውሞ” እንዳያስነሳ ስጋት ገብቷቸዋል።
ማርኮ ሩቢዮ ሀገራት ወታደሮቻቸው ምን ዓይነት ግዳጅ ውስጥ እንደሚገቡ ሳያውቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ አንጠብቅም ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የጋዛ ዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይል (ISF) በዋናነት ሰብዓዊ እርዳታዎች ለተጎጂዎች እንዲደርሱ ጥበቃ ማድረግን፣ የሲቪል አስተዳደሩን መደገፍ እና አካባቢው ዳግም
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት በታጣቂዎች ታግተው መሰዳቸውን፣ ሁለቱ ቢመለሱም ሦስቱ ባለመለቀቃቸው የአካባቢው አመራሮች ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ነዋሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ጠየቁ።
እገታው የተፈጸመው ከአርሲ ሮቤ 6 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ “አኪያ” በሚባል ቦታ መሆኑን ገልጸው፣ “አምስት የአንድ ቤተሰብ ወንዶች አዝመራ በውቂያ ሳሉ በአካባቢው ባሉ የሸኔ ታጣቂዎች ተወስደዋል” ሲሉ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የታጋቾች አባትና አያት የሆኑ የ90 አመት የእድሜ ባለጸጋ ደግሞ፣ ሦስት ልጆቻቸው እና ሁለት የልጅ ልጆቻቸውን በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
” ይህን ሊያሰማኝ አቆየኝ ” በማለት ሳግ የሚተናነቃቸው እኚሁ የእድሜ ባለጸጋ በገለጹት መሰረት፣ ልጆችና የልጅ ልጆቻቸው እህል ለመውቃት ነዶ ወደአውድማ እያስገቡ ባለበት ነው ” ከጫካ በወጡ የሸኔ ታጣቂዎች ” ታግተው የተወሰዱት።
እኝሁ አባት፣ ” ሐሙስ ታህሳስ 9 ቀን 2018 ዓ/ም ጠዋት 2 ሰዓት ተኩል ነው የእህል ነዶ እያጋዙ ባለበት የተወሰዱት። ነዶውን አውድማ አስገብተው ሊወቁ ነበር ” ነው ያሉት።
ምን ያክል ሰዎች እንደተወሰዱ ሲያስረዱም፣ “መጀመሪያ የተወሰዱት አምስት ናቸው፤ መጀመሪያ የተወሰዱት ሁለቱ የልጅ ልጆቼ ነበሩ ለቀቋቸው። ሦስቱን እንደወሰዷቸው ቀሩ ሦስቱ ልጆቼ ናቸው። ወደ ቄርቄር ውስጥ ከረዩ ስር ነው የወሰዷቸው” ብለዋል።
“አቆሙንና ‘የማናችሁ? አሉን’፣ ‘የአምዴ ነን አልናቸው’፤ ‘በሉ እናንተ ተመለሱ አሉን'” ሲሉ ከእገታ ተመላሾች መግለጻቸውን አስረድተው፣ “የተለቀቁት አባት አብሮ የታገተ ነው፤ የወሰዷቸው ከጫካ የወጡ ባለትጥቅ ናቸው” ብለዋል።
“እዚህ ነው ያሉት እንኳ አልተባልንም፤ ዝም ብለን ቁጭ ብለናል፤
” በሁለት ቀናት እስከ 20 ሰዎች ተገድለዋል፣ በአንድ ወረዳ ብቻ። በሌሎችም አሉ። ከሁለት ቀናት በፊትም በአቦል ወረዳ ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቁ በርካቶች ሞተዋል ” – የጋምቤላ ነዋሪዎች
➡️ ” በርካታ ቁስለኞች ወደ ህክምና ይላካሉ። በኛ ሆስፒታሉ የመጡት ብቻ ወደ 8 ይደርሳሉ። ጉዳት የደረሰባቸው ሦስት ሰዎች ወደ ጅማ ሪፈር ተደርገዋል” – በክልሉ በሚገኝ ሆስፒታል የሚሰሩ ሀኪም
በጋምቤላ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች በተለይ ከህዳር 30 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በተፈጠረው የሰላም መደፍረስ የበርካታ ንጹሐን ህይወት እየተቀጠፈ መሆኑን የሟች ቤተሰብ፣ ነዋሪዎችና በሆስፒታል የሚሰሩ ሀኪም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
አንዳንዶቹ የሟቾችንና ቁስለኞችን ቁጥር “ከ50 እስከ 60” ያደረሱት ሲሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ “ከዚያም የበለጠ ነው” ይላሉ። ከቀናት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ አንድ የክልሉ ባለስልጣን “የሟቾች ቁጥር ከ10 በላይ ሊሆን ይችላል” ብለው ነበር።
የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ማበር ኮር ደግሞ፣ ሰዎች መሞታቸውን አምነው፣ ብዛታቸው ግን “10 እንደማይሆን” ሰሞኑን ነግረውን የነበረ ሲሆን፣ ነዋሪዎችና ጤና ባለሙያዎች ዛሬ እንደነገሩን ከሆነ ደግሞ ጥቃቱ ባለመቆሙ የሟቾና ተጎጅዎች ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ ነው።
በሆስፒታል የሚሰሩ ሀኪምና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
ነዋሪዎቹ በሰጡን ቃል፣ “በሁለት ቀናት እስከ 20 ሰዎች ተገድለዋል በአንድ ወረዳ ብቻ። በሌሎችም አሉ። ከሁለት ቀናት በፊትም በአቦል ወረዳ ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቁ በርካቶች ሞተዋል” ብለዋል።
የ27 አመት ወጣት በጸጥታው ችግር የተገደለባቸው ነዋሪ፣ “በጥይት ተመትቶ ነው ያረፈው። ብዙ መንገዶች ዝግ ስለሆኑ በጥይት የተመቱ ሰዎች
ብፁዕ አቡነ ያሬድ ከምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ተነሱ። ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ሀገረ ስብከቱን እንዲመሩ ተመድበዋል።
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የምሥራቅ አርሲ ሀገረስብከትን እስከ ግንቦት የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ ድረስ ደርበው እንዲመሩ በቋሚ ሲኖዶስ ተመደቡ።
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ከሚመሩት ሀገረ ስብከት በተጨማሪ የምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከትን እስከ ግንቦት 2018 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ ድረስ ደርበው እየመሩ እንዲቆዩ በቋሚ ሲኖዶስ ተወስኖ በቅዱስ ፓትርያርኩ በተጻፈ ደብዳቤ ተመድበዋል።
ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከሚገኙ ካህናት፣ አባ ገዳዎች፣ሀደ ሲንቄዎች፣ ወጣቶችና ምዕመናን የቀረበለትን ተደጋጋሚ አቤቱታ ሲቀርብለት ነበር።
ይህን መነሻ በማድረግ አጣሪ ልዑክ መድቦ ችግሩ በዝርዝር ተጠንቶ እንዲቀርብለት ካደረገ በኋላ ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ብፁዕ አቡነ ያሬድ ከምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ተነስተው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሰቲያን የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስነት ሥራቸውን እያከናወኑ እስከ ግንቦት የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ እንዲቆዩ ውሳኔ አስተላልፏል።
የቅዱስ ሲኖስ ምልዐተ ጉባኤ ጥቅምት 2018 ዓ.ም ባደረገደው ጉባኤ ቋሚ ሲኖዶስ የተከሰተውን ችግር በመመርመር መፍትሔ እንዲሰጥ ውሳኔ ማሰተላለፉ ይታወሳል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው
ፓርላማ ውስጥ ያሉ አንዳንድ የመንግስት ተጠሪዎችና የፅህፈት ቤት ሀላፊዎች በውጭ ጉዞ ስም የሚቀበሉት የአየር ትኬት ላይ ማጭበርበር እንደሚፈፅሙ ታወቀ
“ከጉዞ ከቀሩ ለመንግስት ተመላሽ ይደረጋል እንጂ እንዴት ይሰረቃል?”
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/ba0
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ የአሜሪካን ግሪን ካርድ ሎተሪን (ዲቪ) አገደ። የዲቪ ሎተሪ ፕሮግራም የታገደው፣ ከቀናት በፊት አንድ በዲቪ ሎተሪ ወደ አሜሪካ የገባ የፖርቹጋል ተወላጅ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በኹለት ሰዎች ላይ ከፈጸመው ግድያ ጋር በተያያዘ እንደኾነ ተገልጧል።
የአሜሪካ ባለሥልጣናት፣ በዲቪ ፕሮግራም ወደ አገሪቱ በሚገቡ ሰዎች ምክንያት በአሜሪካዊያን ላይ ከእንግዲህ ጉዳት እንዳይደርስ ለማረጋገጥ እገዳውን መጣል እንዳስፈለገ ተናግረዋል።
ፕሮግራሙ ለተለያዩ አገራት ዜጎች በየዓመቱ 50 ሺሕ የመኖሪያና ዜግነት ማግኛ ቪዛዎችን ሲሠጥ የቆየ ሲኾን፣ ባለፉት 30 ዓመታት ከ3 ሺሕ 600 በላይ ኢትዮጵያዊያን የእድሉ ተጠቃሚ ኾነዋል።
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረመስቀል፣ የኢትዮጵያው ብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች ኤርትራ ከኢጋድ መውጣቷ “የመነጠል አጀንዳዋ” እና “ለበይነ መንግሥታታት መድረኮች ያላት ጥላቻ” ማሳያ ነው በማለት ላይ ይገኛሉ ሲሉ ተቹ። የማነ፣ ኾኖም ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ስትፈራረም እና ከዚያም ኢትዮጵያ ራሷ የምትቆጣጠረው የባሕር በር አጀንዳ ስታራምድ ኢጋድ ዝምታን መምረጡ፣ ለኤርትራ እና ሌሎች ተጎጂ አገራት እዳ እንዲሆን አድርጎታል በማለት ወቅሠዋል። የብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች ባኹኑ ወቅት በኤርትራ ላይ የማጥላላት ዘመቻ የሚያካሂዱት፣ የፓርቲውን “የራስ የባሕር በር አጀንዳ አቅጣጫ በማስቀየር የተጎጂነትና ራስን የመከላከል ዘመቻ አድርጎ ለማቅረብ ነው” በማለትም የማነ አጣጥለዋል። ለዚህ ግብ አንዱ ስልት ኤርትራን የኢትዮጵያ እና የቀጠናው “በጥባጭ” አድርጎ ማቅረብ ነው ያሉት የማነ፣ ይህ ተቀባይነት እንዲኖረው ማድረግ ግን እጅግ ይከብዳቸዋል ብለዋል።
በትግራይ መልሶ ማቋቋም ኢንዶውመንት ፈንድ (ኢፈርት) ስር በሚንቀሳቀሱ 22 ኩባንያዎች የባንክ ሂሳብ ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ መነሳቱን ታወቀ፡፡ ዝርዝሩን ያንብቡት–https://cutt.ly/utssnYrZ
ለጥይት መግዣ እና ለብልፅግና ፓርቲ ህንፃ ግንባታ የሚል አዲስ አስገዳጅ የህዝብ መዋጮ በበርካታ ቦታዎች መጀመሩ ታወቀ
“ለአስተዳደር ህንጻ ግንባታ ከደሞዛችን ስንቆርጥ ከርመን የጨረስነው ከወር በፊት ነው፣ አሁን ደግሞ ለፓርቲ ተባልን”- የካፋ ዞን ጎባ ወረዳ የመንግስት ሠራተኞች
– “ለጥይት መግዣ ብር አምጡ ብለው እያስፈራሩን ነው። በዚህ ስራ በሌለበት ወቅት ከየት አምጥተን ነው ምንከፍለው?”- የምዕራብ ሸዋ ዞን አደአ በርጋ ወረዳ ነዋሪዎች
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/0af
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ለተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች በየአመቱ በጀት ሲመደብ ነበር !
ፕሮጀክቶች ከተጠናቀቁ በኋላ ከአንድ እስከ ሦስት ዓመት ለሚሆን ጊዜ በየዓመቱ በጀት ሲመደብላቸው መቆየቱን የፌዴራሉ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ካቀረበለት የኦዲት ሪፖርት ያረጋገጠው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ጉዳዩ በአስቸኳይተመርምሮ ሪፖርት እንዲቀርብለት አዘዘ።
ሰሞኑን በሕ/ተ/ም/ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት ላይ የፌዴራሉ ዋና ኦዲተር ያካሄደውን የክዋኔ ኦዲትና በኦዲቱ የተገኙ ክፍተቶችን መሠረት አድርጎ፣ ጉዳዩ ከሚመለከተው የፕላን ልማት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አድርጎ ነበር።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) ፥ የፌዴራል ዋና ኦዲተር የክዋኔ ኦዲት ግኝትን መሠረት በማድረግ የአዋጭነት ጥናት ሳይጠና በጀት የተመደበላቸው ፕሮጀክቶች መኖራቸውን፣ የፋይናንስና የፊዚካል ሪፖርት የማያቀርቡና በተቀመጠላቸው ጊዜና በጀት ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን በመጥቀስ ሚኒስቴሩ ይህንን ለማስተካከል የወሰደውን ዕርምጃ ጠይቀዋል። ከዚህ በተጨማሪ ተጠናቀው ሥራ ለጀመሩ ፕሮጀክቶች በጀት ሲመደብ መቆየቱን በመግለጽ፣ ይህ እንዴት ሊሆን እንደቻለ ሚኒስቴሩ ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል። የፌዴራል ዋና ኦዲተር ባለፈው ዓመት የኦዲት ግኝት ሪፖርቱን ለሕ/ተ/ም/ቤት ማቅረቡ የሚታወስ ሲሆን፣ የክዋኔ ኦዲት ካደረገባቸው ተቋማት እንዱ የፕላን ልማት ሚኒስቴር ነበር። በዚህ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርቱ ላይም ናሙና በመውሰድ ኦዲት ካደረጋቸው የመንግሥት ፕሮጀክቶች ውስጥ በ2 ዩኒቨርሲቲዎች የተገነቡ በርካታ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ሥራ ከጀመሩ ከ1 ዓመት እስከ 3 ዓመት የቆዩ መሆናቸውን፣ ነገር ግን ለእነዚህ ፕሮጀክቶች በየዓመቱ በጀት ሲመደብ እንደነበር አረጋግጧል፡፡
የተጠቀሱት ዩኒቨርሲቲዎች ፦

ዋቸሞ
” ልጃችን መንገድ ላይ ተገድላ ከ600 ሺህ ብር በላይ ተወስዶባታል ” – የቡናዬ ቤተሰቦች
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ኬሌ ከተማ መቅሬዲ ቀበሌ ነዋሪዋና የቀድሞ የእግርኳስ እና ቦክስ ስፖርቶች በክልል ደረጃ ተወዳዳሪ አሁን ላይ ታታሪ ነጋዴ ቡናዬ ብርቅነህ በትናንትናው ዕለት ከኮሬ ዞን ወደ አጎራባች ምዕራብ ጉጂ ዞን ለገበያ በመጓዝ ላይ እያለች እስካሁን ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች መገደሏን ቤተሰቦቿ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የቡናዬ ወላጅ አባት አቶ ብርቅነህ ባሩድ እና ታላቅ ወንድሟ መምህር አዳነ ብርቅነህ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ለቲክቫህ በሰጡት ቃል፥ ቡናዬ ገና የ29 ዓመት ወጣት መሆኗን የቀድሞውን የደቡብ ክልልን በመወከል የቦክስና እግር ኳስ ተወዳዳሪ የነበረች ስፖርተኛ እንደነበረች ግለጸዋል። ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ደግሞ የቀንድ ከብት እንዲሁም የሸቀጣሸቀጥ ነጋዴ በመሆን እየሰራች እንደነበር ጠቁመው በትናንትናው ዕለት ከምዕራብ ጉጂ ዞን ጋላና ሻሞሌ ሺዳ ቀበሌ ወደ ሚገኘው ፋታ ገበያ በመጓዝ ላይ እያለች በጥይት ተመታ መገደሏንና በሬና ፍየሎችን ለመግዛት የያዘችዉ ከ600 ሺህ ብር በላይ እንዲሁም የእጅ ስልኳ መዘረፉን ተናግረዋል። ቡናዬ የ4 ዓመት ልጅ እናት እንደነበረች የገለፁት ቤተሰቦቿ ፥ ሴት ልጅ በዚህ ሁኔታ ስትገደል ይህ የመጀመሪያው መሆኑንና የሁለቱ ዞን መንግስታት የልጃቸዉን ገዳዮችን ለሕግ እንዲያቀርቡ ጠይቀዋል።
የኮሬ ዞን ፖሊስ ምን አለ ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገራቸው የኮሬ ዞን ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ሲዳሞ ማዳሞ ፤ በምዕራብ ጉጂና ኮሬ ዞኖች አዋሳኝ አከባቢ ወ/ሮ ቡናዬ
የአማራ ማሕበር በሎሳንጀለስ አንዳንድ አካላት በሕገወጥ መንገድ የማህበራችንን ስምና አርማ እየተጠቀሙ ነው ሲል ከሰሰ

https://x.com/Amharas_Of_LA/status/2002243576424772088
ታፍነው ወደ ማሰልጠኛ ቦታ ሲወሰዱ የነበሩ ምልምል ታዳጊ ልጆች በፋኖ ነፃ!
ሕፃናትን ለጦርነት ማዋል አለማቀፋዊ ወንጀል ነው። ይህን በመተላለፍ የብልፅግና አረመኔ አመራር በተደጋጋሚ ህፃናትን ከትምህርት ቤት እየመለመለ ወደ ስልጠና እየላከ በጦርነት እያስጨፍጭፍቸው ይገኛል። በውጊያ የማረክናቸው ሕፃናትም የስነልቦና ጫና ውስጥ በመግባታቸው የጤና መታወክና የአዕምሮ ሰላም እንዳጡ በተለያዩ ጊዜ ያረጋግጠው ጉዳይ ነው።
ይህን የመከላከል ሀላፊነት የወደቀበት የአማራ ፍኖ በተለያዩ ጊዜ ስልጠና እንዳይገቡ በደፈጣ ከነመኪና በመማረክ የስነልቦና ስልጠና እና የተሀድሶ ስልጠና እየሰጠ ወደ ቤተሰቦቻቸው መላኩን ተያይዞታል። ከዚህ በፊትም ደብረማርቆስ ዙሪያ በበረኸኛው ጅበላ ብርጌድ በርካታ ህፃናትን በ2016ዓ.ም ማስለቀቁ የሚታወስ ነው።
ዛሬም ታፍነው ወደ ማሰልጠኛ ቦታ ሲሄዱ የነበሩ የአማራ ህጻናት በአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 77ኛ ክ/ጦር ቃኝና መሀንዲስ ሻለቃ ከመንገድ ላይ በመማረክ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
©አፋብኃ| ቴወድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በውጫሌ ዙሪያ በተደረገ ተጋድሎ በልጅ እያሱ ኮር 24ኛ ክፍለ ጦር ድል አስመዘገበች!
ልጅ እያሱ ኮር 24ኛ ክፍለ ጦር የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ውጫሌ ከተማ ዙሪያ ዛሬ ታህሳስ 9/2018 ዓ.ም ንጋት 12:00 ጀምሮ ወደ ጠላት ምሽግ ዘልቀው በመግባት ባደረጉት ከባድ ተጋድሎ እስከ ቦምብ ጭምር በመጫበጥ በርካታ የጠላት ሃይል ደምስሰውና አቁስለው ታላቅ ጀብድ ፈፅመው ድል አስመዝግበዋል::
24ኛ ክፍለጦር በተጋድሎው ውጫሌ ከተማ ቁንጥሮ ላይ የጠላትን ምሽግ ሁሉ ደምስሰው በመግባት ትልቅ ጀብድ የፈፀሙ ሲሆን ከ40 በላይ የጠላት ሃይል ሙትና ቁስለኛ አድርገው ለጊዜው ቁጥሩ ያልታወቀ የነፍስ ወከፍ ክላሽና የተለያዩ ተተኳሾችንም ማርከዋል::
የፋሽስቱ ብልፅግና ሰራዊት ከተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢ እና ከኦሮሞ ብልፅግና ልዩ ሃይል ጭምር ታፍሶ ሲመጣ በምድር በመካናይዝድና በአየር ሃይል ጄትና ድሮን ከፍተኛ ድጋፍ ሊደረግለት ቃል ተገብቶለት መጥቶ ውጊያ እያደረገ ያለ ሲሆን አየር ንብረቱ ለድሮን በማይመችበት በዳመና ጊዜ ወኔው ተሰልቦና ውጊያ ከብዶት በጅምላ እየተደመሰሰ እና እየተማረከ ይገኛል::
በደብረወርቅ ከተማ በተደረገ ውጊያ ከተገደሉ የወረዳ አመራሮችና የአድማ ብተና እንዲሁም የሚኒሻ አባላት መካከል የጥቂቶቹ ስም ዝርዝር ይፋ ሆኗል!
በደብረወርቅ ከተማ ትናንት ታህሳስ 07/2018 ዓ/ም በተደረገ ውጊያ ከ50 በላይ የበአዴን ወታደሮች ሲገደሉ 27 ክላሽንኮቭ መሣሪያ መማረኩን መረብ ሚዲያ የቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያን ዋቢ አድርጎ መዘገቡ አይዘነጋም።
በከተማዋ በተካሄደው ውጊያ በወቅታዊ ጉዳይ ማለትም ፋኖን ትደግፋላችሁ፣ የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ በሚል ታስረው የነበሩ ከ100 በላይ የግፍ እስረኞች ፋኖ እንዳስለቀቃቸው ታውቋል።
በዚህም በውጊያው ከተገደሉት መካከል፦
1ኛ ደመላሽ ካሳ የወረዳ አስተዳደር መረጃ ሀላፊ
2ኛ ሳጅን ምትኩ ሞላ ፖሊስ
3ኛ ሳጅን እንዳወቀ አማረ ፖሊስ
4ኛ አልኸኝ አያል ሚኒሻ
5ኛ ይሔነው እንዳላመው ሚኒሻ
6ኛ ጌታየ ቢረሰው ሚኒሻ
7ኛ ባየ አልሀኝ ሚኒሻ
8ኛ ያለው ታረቀኝ ሚኒሻ
9ኛ ተዋቸው አፍኔ ሚኒሻ
10ኛ ጌታሠው እስካሁን ሚኒሻ
11ኛ ካሰው አቻም ሚኒሻ
12ኛ አሰፋ ማርኬ ሚኒሻ
13ኛ ጌታሰው ቢረሰው ሚኒሻ
እነዚህ በስም የታወቁት ሲሆኑ በስም ያልተጠቀሱ በርካታ የጠላት አባላት ተገድለዋል።
ጥብቅና የሚቆም በሌለበትና ገዳይ “በማይታወቅበት” የቀጠለው የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮችን የማጽዳት ተልዕኮ አኹንም ቀጥሏል!
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)
በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች በኦርቶዶክስ እምነትና ንጹሓን ዜጎች ላይ የተጀመረው የማጽዳት ዘመቻ ከአርሲ ወደ ወለጋ ፊቱን በማቅናት የሆሮ ጉድሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ኡፋ እና ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ በዓል ለማክበር በወጡበት ከኅዳር 21 ጀምረው ሻምቡ መግቢያ አካባቢ ታግተው ቅዳሜ ታኅሣስ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአጋቾች መገደላቸውንና በአባትነት በተመላለሱበት ምድር የቀብር አፈር ተነፍገው አስከሬናቸውም እንዳልተገኘ እንዳልተቀበሩ ከቦታው ለማረጋገጥ ችለናል። አኹንም ገዳዮቹ ለላፉት 7 ዓመታት በሚገድሉብት የዳቦ ስም “ታጣቂዎች” ናቸው በሚል መሸፈኑ ነገሩን አስገራሚም ግራ አጋቢም አድርጎታል። ከቦታው በደረሰን መረጃ መሠረት ግድያውን የፈጸሙት አስከሬንም የከለከሉት በሻምቡ አካባቢ ይንቀሳቀሳል የሚባለው ኦነግ ሸኔ(ራሱን ኦነሰ ብሎ የሚጠራው) ኃይል መኾኑን ደርሰንበታል፤ በከተማ የሚኖሩ በተባባሪነትና በጥቆማም የተሳተፉ ሊኖሩ እንደሚችሉ ፍንጮች አሉ፡፡
የቤተ ክርስቲያን አባቶችንና ምዕመናን ግድያ ስልታዊ በኾነ የሚፈጸም የዘር ማጽዳት ዘመቻ አካል እንጂ ድንገቴ እንዳልኾነ በጽኑ እናምናለን። እንደ ቀደሙት ግድያዎች ኹሉ በዚኽም ላይ ገዳዮችን አድኖ ፍትሕ እንዲሰፍን የሚወሰድ እርምጃ አይደለም ለሞቱ እውቅና እንኳን ያለመስጠት ብሎም ለወትሮው እንደሚደረገው የማስተባበል አዝማሚያ ነገሩ ምን ያኽል የተቀናጀና በጥንቃቄ የሚፈጸም ስለመኾኑ ማሳያ አድርጎ መውሰድ ይቻላል። ቀሲስ ዱጉማ የ6 ልጆች አባት ሲኾኑ ቀሲስ ደሳለኝ የመንግሥት ሠራተኛና የኹለት ልጆች አባት ናቸው፡፡
በአንጻሩ ለእነዚህ በእምነታቸውና በሃይማኖታዊ ተልዕኮዋቸው ምክንያት ለተገደሉ ወገኖቻችን

የፎቶው ባለመብት,Getty Images
የምስሉ መግለጫ,ባለፈው ዓመት ሐምሌ ላይ የአሜሪካ የፀጥታ ሠራተኞች አንድ ስደተኛን የስደተኞች ጉዳይ ከሚታይበት ችሎት ይዘው ሲወጡ
16 ታህሳስ 2025
የአሜሪካ መንግሥት ከሦስት ዓመት በፊት ኢትዮጵያውያን በጊዜያዊ የሕግ ከለላ በአገሪቱ ውስጥ እንዲኖሩ እንዲሠሩ የፈቀደበትን አሠራር እንዲያከትም ወስኗል።
በትግራይ ጦርነት ምክንያት በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ለኢትዮጵያውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ሲሰጥ የነበረው ጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ መነሳቱን ተከትሎ፤ ከለላው ተሰጥቷቸው የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከአሜሪካ ለመውጣት የ60 ቀናት ጊዜ ተሰጥቷቸዋል።
የአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖም “የአገሪቱን ሁኔታ በመመርመር እና ከሚመለከታቸው የአሜሪካ መንግሥት አካላት ጋር በመመካከር” ኢትዮጵያ ለጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎችን “የማታሟላ አገር ናት” የሚል ውሳኔ መተላለፉን አስታውቀዋል።
በ60 ቀናት አሜሪካን ለቅቀው እንዲወጡ የተነገራቸው ኢትዮጵያዊያን ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይችላል? ጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ የሚሰጥባቸው ሁኔታዎችስ የትኞቹ ናቸው? የሚለውን በተመለከተ በአሜሪካ ከአሥር ዓመት በላይ የሠሩትን የሕግ ባለሙያ ሙሉዓለም ጌታቸው አድገህ አነጋግረናል።
ጊዜያዊ ከለላ ምንድን ነው? በምን ዓይነት ሁኔታስ ይሰጣል?
የአሜሪካ መንግሥት ጊዜያዊ ጥበቃ ወይም ከለላ መስጠት የጀመረው በአውሮፓውያኑ 1991 ሲሆን፤ ይህ መብት የሚሰጠው በአገራቸው ግጭት፣ ጦርነት፣ የተፈጥሮ አደጋ ወይም ሌላ ለደኅንነታቸው አስጊ የሆነ ክስተት ለገጠማቸው ስደተኞች ነው።
Temporary Protected Status ወይም TPS ከተሰጣቸው አገራት መካከል ሶማሊያ እና ሶሪያ (ከጦርነት ጋር በተያያዘ) እንዲሁም ኤል ሳልቫዶር (ከርዕደ መሬት ጋር በተያያዘ) ይጠቀሳሉ።
ለአንዳንድ አገራት እስከ 20 ዓመት የዘለቀ ከለላ ተሰጥቷል። ለምሳሌ የሶማሊያ ጊዜያዊ ጥበቃ

የፎቶው ባለመብት,EOTC
የምስሉ መግለጫ,በታጣቂዎች ከተገደሉት መካከል መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ
16 ታህሳስ 2025
በኦሮሚያ ክልል፣ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሁለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች በታጣቂዎች ከተገደሉ ቀናት ቢቆጠርም አስከሬናቸው እንዳልተገኘ ተገለጸ።
ኅዳር 21 ቀን 2016 ዓ. ም. ቀሳውስቱ በሀራቶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ ክብረ በዓል ታድመው ወደ ሻምቡ ከተማ እየተመለሱ ሳለ ነበር መኪናቸው በታጣቂዎች እንዲቆም ከተደረገ በኋላ ወደ ጫካ ተወስደው የተገደሉት።
በጉዞው ላይ አብረዋቸው ከነበሩት ቀሳውስት አንደኛው “በጅማ ገነቲ አካባቢ የቅድስት ማርያም ክብረ በዓል ነበር። ከሥነ ሥርዓቱ ስንመለስ 9 ሰዓት አካባቢ ታጣቂዎች አስቆሙን” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
እኝህ የዐይን እማኝ በመኪናው ተሳፍረው የነበሩት “20 ሰዎች” እንደሆኑ ገልጸው፤ “ከ20ዎቹ መካከል አስሩን አስወርደው ወደ ጫካ ወሰዷቸው። የተቀሩት በበቆሎ ማሳ ውስጥ ተበታትነው በመሮጥ አመለጡ” ብለዋል።
ቄሱ እንደገለጹት፤ ታጣቂዎቹ በሻምቡ ከተማ መግቢያ ላይ መንገድ ዘግተው እና ስናይፐር መሣሪያ ይዘው ነበር።
ወደ ጫካ አካባቢ ከተወሰዱት ቀሳውስት መካከል የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ አገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ ሕጻናት እና መዘምራን እንደሚገኙበትም ተናግረዋል።
“ጫካው ውስጥ ወስደው በስም ጠሯቸው። አንድ በአንድ በስም ከጠሯቸው በኋላ ልጆቹ ታጣቂዎቹ ከያዙት የስም ዝርዝር ውስጥ ስላልነበሩ ለቀቋቸው” ብለዋል።
“አራቱ ሰዎች የሆሮ ጉዱሩ አገረ ስብከት ዋና ኃላፊ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ፣ ቄስ ቀናሳ ጊዲሳ፣ ቄስ ደሳለኝ ነሞምሳ እና ቄስ ባቡሽን ጠሩ ናቸው” ሲሉም በስም ጠቅሰዋል።
ታጣቂዎቹ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባላት ናቸው ሲሉም
ከኦፌኮ በመውጣት አዲስ መንገድ በማማተር ላይ ያሉ ፖለቲከኛ
በኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) በከፍተኛ አመራርነት ለዓመታት ያገለገሉ ፖለቲከኛ ደስታ ዲንቃ ከፓርቲው መውጣታቸውን አረጋገጡ፡፡
ፖለቲከኛው ከሌሎች የትግል አጋሮቻቸው ጋር በመሆን በሌላ የፖለቲካ ድርጅት ለመምጣት መንገድ ስለመጀመራቸውም ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡
የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት..
ከአንጋፋውየኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረንስ (ኦፌኮ)የመውጣት ውሳኔያቸው እራሳቸውን ከፖለቲካው ዓለም የማራቅ ፍላጎት ተደርጎ እንዳይወሰድ የገለጹት ፖለቲከኛ ደስታ ዲንቃ፤ ለዓመታት በትላልቅ ኃላፊነቶች ካገለገሉት የፖለቲካ ድርጅት ለመውጣት የገፋቸው ዋናው ምክንያት በእርሳቸው እና በኦፌኮ መካከል ያለው የፖለቲካ አመለካከት አለመግባባት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
“የእኔ የፖለቲካ አመለካከትና የፖለቲካ አስተዳደር ከሌሎች የተለየ እንደሆነ እረዳለሁ” ያሉት ፖለቲከኛ ደስታ ባሁን ወቅት በአገሪቱ “ከጫፍ ጫፍ የሚስተዋሉ አለመረጋጋቶች” እንቅልፍ እንደሚነሱአቸው በመግለጽ ከሳቸው ጋር ተመሳሳይ ሃሳብ ካላቸው ዜጎች ጋር በመሆን በተለየ አቀራረብና አያያዝ በአዲስ የፖለቲካ ድርጅት ለመምጣት ማቀዳቸውንም አስረድተዋል፡፡
የፖለቲካው ውጣ ውረድ
በኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረንስ ውስጥ ከሌሎች ጓዶቻቸው ጋር በመሆን በርካታ የፖለቲካ ስራዎችን መስራታቸውን የሚያምኑት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ምሩቅና የቀድሞ ጠበቃና የህግ ባለሙያ የአሁኑ ፖለቲከኛ አቶ ደስታ ዲንቃ፤ በፖለቲካው ህይወታቸው ከአካላዊ ጥቃት እስከ ቤተሰብ ስቃይ ያደረሳቸው አባጣ ጎባጣ መንገድ ላይ ማለፋቸውንም ያስታውሳሉ፡፡

ከፖለቲከኛ ደስታ ዲንቃ ጋር ኦፌኮን የለቀቁ ስለመኖራቸው ይነገራልምስል፦ Desta Dinka via Seyoum Getu DW
ፖለቲከኛው ከምስረታው ጀምሮ አባልና አመራር ከነበሩበት ኦፌኮ በተለየ መንገድ ላይ እንዲቆሙ ካደረጉአቸው ጉዳዮች ከ2013 ዓ.ም. ስድስተኛው ብሔራዊ ምርጫ የመገለል ውሳኔ እና ሌሎችም መኖራቸውን ጠቃቅሰዋል፡፡ “መድረክ ውስጥ
ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሒውማን ራይትስ ዎች፦ የዶይቸ ቬለ ሁለት ወኪሎች በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለ ሥልጣን ለዘለቄታው መታገዳቸውን አወገዘ ። ድርጅቱ፦ «ኢትዮጵያ ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ነጻነት ላይ ሌላ አሉታዊ ተግዳሮት» በሚል ዐቢይ ርእስ ባወጣው መግለጫው በንዑስ ርእሱ፦ «ዶይቸ ቬለ ላይ የተሰነዘረው ጥቃት ገለልተኛው ፕሬስ ላይ የተደቀነ መጠነ ሰፊ ሥጋት መሆኑን ያረጋግጣል» ብሏል።
«እነዚህን ጋዜጠኞች ማገድ የኢትዮጵያ መንግሥት ለማንም የማይወግኑ ገለልተኛ እና ሂሳዊ ዘገባዎች ላይ ያለውን ባላንጣነት የሚያረጋግጥ ነው» ሲልም ተችቷል ። በሒውማን ራይትስ ዎች የአፍሪቃው ክፍል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ማውሲ ሴጉን ትናንት (ታኅሣሥ 6 ቀን፣ 2018 ዓ.ም) የወጣው መግለጫ፦ ጋዜጠኞች ኢትዮጵያ ውስጥ ለዓመታት በባለሥልጣናት ያላሰለሰ ክትትል፤ ፍርሐት ባጠላበት ድባብ ውስጥ እንደሚሠሩ አመልክቷል። «የመብቶች ጥሰቶችን ያጋለጡ አለያም መንግሥትን የሚያሒሱ ዘገባዎችን የሚያቀርቡ» ጋዜጠኞች ላይ «ተከታታይ ክትትል፣ እስር፣ እና ዘብጥያ መውረድ» እንደሚከተልም ሒውማን ራይትስ ዎች ዘርዝሯል። በዐሥራዎቹ የሚቆጠሩ ጋዜጠኞችም አገር ጥለው መሰደዳቸውን ድርጅቱ በመግለጫው አክሏል። ለ«ኢትዮጵያ መንግሥት» ጥሪ ያስተላለፈው ሒውማን ራይትስ ዎች፦ «በዶይቸ ቬለ ጋዜጠኞች ላይ የጣለውን እገዳ በአስቸኳይ እንዲያነሳ፤ በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚያደርሰውን ተጨማሪ ጥቃት እንዲያቆም» ሲልም ጥሪ አስተላልፏል ።
ሙሉ የእንግሊዝኛ መግለጫውን ይህን ማገናኛ ጠቆም በማድረግ ማንበብ ይቻላል ።
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ አቅራቢያ ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቤተክርስቲያን አገልግሎት በሚመለሱበት ወቅት በታጠቁ አካላት ተይዘው ከተወሰዱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን አገልጋዮች መካከል ሁለት ካህናት ተገደሉ፡፡
ከታገቱ ከሁለት ሳምንታት ግድም በኋላ ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ታህሳስ 04 ቀን 2018 ዓ.ም. መገደላቸው ይፋ የሆነው የአገረስብከቱ ስራአስከያጅ እና አንድ ሌላ አገልጋይ የታገቱት በዞኑ በጅማ ገነቲ ወረዳ የምትገኝ ቀዲዳ ማሪያም ቤተክርስቲያን አገልግሎት ውለው ወደ ሻምቡ ከተማ በምመለሱበት ወቅት በመንገድ ላይ ባደፈጡ ታጣቂዎች እንደሆነ የአይን እማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡
በእለቱ ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ወደ ጅማ-ገነቲ ወረዳ ሀራቶ ከተማ ቀዲዳ ማሪያም ለአገልግሎት ተጉዘው የነበሩት የሀገረስብከቱ አገልጋዮች ላይ እገታው የተፈጸመው ጬካ-አባጀና በሚባል ደናማ ስፍራ ነው ተብሏል፡፡ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው ሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ከነበሩት የቤተክርስቲያን አገልጋዮች መካከል የሀሮሮጉዱሩ ሀገረስብከት ስራአስከያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ እና ሌላው የቤተክስቲያን አገልጋይ ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ ቅዳሜ ዕለት መገደላቸው ተረጋግጧልም ተብሏል::
እገታው እንዴት ተፈጸመ?
በእለቱ በታጣቂዎች ተገድለዋል ከተባሉት ሁለቱ ካህናት ጋር ከአገልግሎት ስመለሱ የነበሩና በታጣቂዎች እገታ ወቅት በዚያው የነበሩ አንድ ለደህንነታቸው ስባል ግን ስማቸውን ከመግለጽ የተቆጠቡት የአይን እማኝ ለዶይቼ ቬለ እንደነገሩት፤ እገታው የተፈጸመባቸው በአገረስብከቱ ተሽከርካሪ ወደ ሻምቡ ከተማ በመጓዝ ላይ ሳሉ ነበር፡፡ “በእለቱ ከታገቱት መካከል እኔ አንዱ ነበርኩ” ያሉን የአይን እማኙ በርካቶች ያመለጥነው ታጣቂዎች ወደ ሚፈልጉት አቅጣጫ ከመጓዝ ይልቅ
በኢትዮጵያ እዳ እና ሀብት ዙርያ በፓርላማ ሊደረግ የነበረ ወሳኝ ውይይት አነጋጋሪ በሆነ ምክንያት ለሌላ ግዜ መተላለፉ ተሰማ፣ ዝርዝሩን ይዘናል
“የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ‘ይህ ሁሉ ሚዲያ ምንድን ነው? ብለው ከአዳራሹ ወጥተው ስልክ ካወሩ በኋላ ውሳኔውን አሳውቀዋል”
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/7f9
በደቡብ ኦሞ ዞን እንደ አዲስ እየተስፋፋ በመጣው የማርበርግ ቫይረስ ሁለት ወንድማማቾች በቀናት ልዩነት ህይወታቸው ማለፉ ታወቀ
“ወጣቱ በታመመ ሰዓት ሊጠይቁት የሄዱ በርካታ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ስለነበሩ እነሱም በሙሉ ተለይተው ወደ ለይቶ ማቆያ ገብተዋል”
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/da4
ለአሜሪካ ፍሎሪዳው አገር አቋራጭ ውድድር ከሚሳተፉ አትሌቶች፣አሠልጣኞች እና አመራሮች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ቪዛ ተከለከሉ

የኤምባሲው ውሳኔ ብዙዎችን አስደንግጧል

የቪዛ ጥያቄው በድጋሚ እንዲታይ ጥረቶች እየተደረጉ ነው
አሁን ማምሻውን እጅግ አስደንጋጭ ዜና ደርሶናል፤እ.ኤ.አ ጃንዋሪ 10 በአሜሪካ ፍሎሪዳ ታላሃስ ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው 46ኛው ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ውድድር ለመሳተፍ በዝግጅት ላይ ካሉ አትሌቶች፣አሠልጣኞች እና አመራሮች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ቪዛ መከለከላቸው ታውቋል።
ታማኝ የፌዴሬሽን ምንጮቻችን እንዳደረሱን መረጃ ከሆነ በ46ኛው የአሜሪካ ፍሎሪዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ውድድር ለመሳተፍ በዝግጅት ላይ የሚገኙት አትሌቶች፣አሠልጣኞች እና አመራሮች ቪዛ ለማግኘት ቀደም ብለው ፎርማሊቲውን አሟልተው ዛሬ ሽሮሜዳ ወደሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ቢጓዙም ካመለከቱት አመልካቾች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የቪዛ ጥያቄያቸው ተቀባይነት አጥቶ መከለከላቸው ነው ታማኝ ምንጮቻችን ያደረሱን መረጃ የሚጠቁመው።
የአሜሪካ መግቢያ የቪዛ ማመልከቻቸው ውድቅ ከሆነባቸው አትሌቶችና አሠልጣኞች በተጨማሪ በቅርቡ ወደ ፌዴሬሽኑ የፅ/ቤት ኃላፊነት የመጡት አመንሲሳ ከበደ(ዶ/ር) የሚገኙበት ሲሆን ከእሳቸው በተጨማሪ ፊዚዮቴራፒስቶችም የቪዛ ማመልከቻ ጥያቄያቸው ውድቅ ከሆነባቸው ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።
የቪዛ ጥያቄያቸው ውድቅ የሆነባቸውና የተፈቀደላቸው እነማን እንደሆኑ የጠየቅናቸው ምንጮቻችን ስሜታቸው እንዳይጎዳ ስማቸውን መግለፅ ባለመፈለጋቸውና ይቆይ በማለታቸው በዚህ ዘገባ ውስጥ ማንነታቸውን አላካተትንም።
የአሜሪካ ኤምባሲ አመልካቾቹ ወደ አሜሪካ የሚጓዙት ለውድድር እንደሆነና አንዳንዶቹም የጉዞ ታሪክና በአትሌቲክስ ትልቅ ስምና ንብረት(አሴት) ያላቸው እንደሆነ እየታወቀ ለምን ከግማሽ በላይ የሚሆኑትን አትሌቶች፣አሠልጣኞች እና የአመራሮቹን የቪዛ ጥያቄ ለምን ውድቅ እንዳደረገ የተገለፀ ነገር ባይኖርም ቪዛ የሚያሠጥ አሳማኝ ምክንያት አላገኘሁም በማለት ከግማሽ በላይ
“የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅና አንድ አብሯቸው የነበረ አገልጋይ ተገድለዋል፤ በትክክል ግድያው እንደተፈጸመ አረጋግጠናል” – ቤተክርስቲያኗ
“ምዕመናን የተረጋጋ ኑሮ እየቀጠሉ አይደለም በቦታው፣ አገልጋዩም ይሄ ይከተለኛል ብሎ ከአገልግሎቱ ተቆጥቦ ነው ያለው!”
የሆሮጉድሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መላከ ኤዶም ቀሲስ ድጉማ እና ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ የተባሉ አገልጋይ በታጣቂዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸች። በቤተክርስቲያኗ በኃላፊነት ደረጃ የሚገኙ አካል፣ “ሰሞኑን የህዳር ፅዮን በዓል አክብረው ሲመለሱ የነበሩ የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅና ሌላ አገልጋይ፣ ሌሎችም በአጠቃላይ አምስት ሰዎች ታግተው ነበር። ሁለቱ ተገድለዋል” ብለዋል። “በትክክል ግድያው እንደተፈጸመ አረጋግጠናል። ሌሎቹን ግን እንደለቀቋቸው ነው የደረሰን መረጃ የሚመላክተው፤ ገዳዮቹ ህገወጥ ታጣቂዎች ናቸው” ያሉት እኚሁ አካል፣ “በአካባቢው ግን አብረዋቸው የሄዱ በርካታ ወጣቶች ነበሩ ወደ አረቶ ማርያም” ሲሉም ገልጸዋል። “ከአረቶ ማርያም ሲመለሱ ነው ሻምቦ አካባቢ ለመድረስ ጥቂት ሲቀራቸው በህገወጥ ታጣቂዎች የታገቱት። ከብዙ ጥረት በኋላ ሌሎቹን ሲለቋቸው ሁለቱ ግን እንደተገደሉ ነው መረጃው ያለን” ሲሉም ሟቾቹ መጀመሪያ ታግተው እንደነበር አስረድተዋል።
ስጋት እንዳላቸው ገልጸውላችሁ ነበር? አካባቢው ምን የተለየ ነገር አለ? ስንል የጠየቅናቸው የቤተክርስቲያኗን አመራር ምን መለሱ ? “በአካባቢው የክርስቲያኖች መገደል እና ሞት አዲስ አይደለም። ለረጅም ጊዜ በርካታ ምዕመናን እና አገልጋዮች ህይወታቸው አልፏል። ባለፈው አንድ አመታት ከስድስት ወራት ግን ምዕራብም ምስራቅ ወለጋም ላይ ቆም ብሎ ነበር። አሁን ደግሞ ከፍተኛ የሆነ የቤተክርስቲያን አባቶችን፣ ትልልቅ ኃላፊነት የተሰጣቸውን አገልጋዮችን በእንዲህ አይነት መልኩ ማጥቃት በጣም
ባለፈው ዓመት የጤና ባለሙያዎችን የሥራ ማቆም አድማ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ ያስተባበረው ቡድን፣ ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ሁለተኛ ዙር የሥራ ማቆም አድማ ጠራ። ቡድኑ፣ ጤና ሚንስቴርም ሆነ የክልሎች ጤና ቢሮዎች የጤና ባለሙያዎችን ሕጋዊ እና የኅልውና ጥያቄዎች እስካልመለሱ ድረስ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በተለያዩ የማስተማሪያና ሌሎች ሆስፒታሎች የሚሠሩ ጥቂት ባለሙያዎች የትርፍ ሰዓት ክፍያ መስተካከሉን ተከትሎ የስራ ማቆም አድማውን ለመቀላቀል ፍላጎት የሌላቸው መሆኑን ተረድቻለሁ ያለው አስተባባሪ ቡድኑ፣ ሁለተኛውን የስራ ማቆም አድማ የማይቀላቀሉ ባለሙያዎች ወደፊት ለሚደርሱባቸው የመብት ጥሠቶች ሃላፊነት አልወስድም በማለት አስጠንቅቋል።
ቡድኑ፣ በተለያዩ ክልሎች የጤና ባለሙያዎች ማስፈራራት እና የእገዳ ዛቻ እየደረሰባቸው ይገኛል በማለትም ድርጊቶቹን አውግዟል።
ጆሮ ዳባ ልበስ የተባለው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ቢሮ ዜጎች ላይ የሚደርሰው እንግልት
“እንኳን የፋይናንስ ተቋም ይቅርና ሌሎች ተቋማትም ቢሆኑም የተነሳባቸውን ቅሬታ ለማረም ነገ ዛሬ እንደማይሉ መታወቅ አለበት”
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/7df
የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የማኅበረ ቅዱሳን አባል በታጣቂዎች ተገደሉ
የኅዳር ጽዮን ማርያምን በዓል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው በሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ሻንቡ ከተማ መዳረሻ ሲደርሱ የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዹጉማ እና በርካታ የሀገረ ስብከቱ ሠራተኞችና ወጣት የማኅበራት አገልጋዮች በሕገ ወጥ ታጣቂዎች መወሰዳቸው ይታወቃል።
ሌሎቹ ተፈትተው ቆይተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የተመለሱ ሲሆን በትናንትናው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዹጉማ ኡፋ እና የማኅበረ ቅዱሳን አገልጋይ የሆኑት ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ በሕገ ወጥ ታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል።
==== ነፍስ ይማር አባቶቻችን። እግዚአብሔር አምላክ ቤተሰቦቻችሁን፣ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን እንዲሁም መላውን ሕዝበ ክርስቲያን ያጽናናልን።
(ምንጭ @የኢኦተ ቤተ ክርስቲያን ቴሌቪዥን)