Blog Archives

ዘመነ እና ብርሃኑ ነጋ ከ6 ዓመት በኋላ! ዐቢይ ተከበዋል! የአበባው ታደሰ ምላሽ! የህወሃትና ኤርትራ የመሳሪያ ልውውጥ!

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

ፋኖ ቅድመ ሁኔታዎችና ድርድሩ

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, አፍሪቃ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

ለኦሮሞ ተወላጅ ወታደሮች የተሀዲሶ ስልጠና ተሰጠ! …. “ነፍጠኛ መጣብህ ተብለን ነው የተነሳነው” ወታደሩ

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ

የፋኖ የድርድር ቅድመ ሁኔታ

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

መንግስት ለምርጫ ሳይደርስ ይበተናል ( ፋኖ ማርሸት ጸሀዩ )


Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ

ወታደሩ ተንዶ አለቀ፤ ካምፑ ባዶውን ቀረ ………. ፋኖ ወደ ከተማዋ ዘልቆ ገባ ፤ ከ48 በላይ ተገደለ!

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

ከጎንደር ዳባት….አጅሬ ጃኖራ! የገባው አልወጣም! ….አስደንጋጭ ጥቃት ተፈፅሟል!

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

ቤተክርስቲያንን ለሁለት በመክፈል የሚታወቁት አቡነ ሳዊሮስ በሲኖዶሱ ተመረጡ ተባለ

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, ኢትዮጵያ

የአሜሪካ ኢምባሲ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መልዕክታቸው ላይ ማሻሻያ አድርጓል

የአሜሪካ ኢምባሲ፣ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መንግሥት የድሮን ጥቃቶችን “በራሱ ሕዝብ ላይ” መፈጸምን “በአፋጣኝ እንዲያቆም” በጠየቁበት የዛሬው መልዕክታቸው ላይ ማሻሻያ አድርጓል። በተሻሻለው መልዕክት፣ ይህ መልዕክት ተነስቶ በምትኩ መንግሥት ለግጭቶች “ከኃይል ውጪ ያሉ ሰላማዊ አማራጮችን” መፈለግ እንዲቀጥልና “የዜጎቹን ደኅንነት እንዲያስቀድም” አምባሳደሩ መጠየቃቸው ብቻ ተጠቅሷል። የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የኦሮሚያው ግጭት እንዲያበቃ የሰላም ድርድሩን እንዲቀጥል፣ የፋኖ ቡድንም “ተጨባጭ” እና “ሰላማዊ የኾኑ” ግቦችን እንዲይዝና “በትጥቅ ትግል ስም የሚካሄድ ሕገወጥነት እንዲያበቃ” አምባሳደሩ በቀደመውም ኾነ በተሻሻለው መልዕክታቸው ጠይቀዋል። ኢምባሲው፣ የአምባሳደሩ መልዕክት በምን ምክንያት እንደተሻሻለ አላብራራም። https://www.facebook.com/profile.php?id=100007836377373
Posted in Amharic News, Ethiopia News, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

ፋኖ የድርድር ቅድመ ሁኔታዎችን አሳወቀ / የአፋብኃ ምላሽ ለአሜሪካ ጥሪ

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

አንዳንድ ምግባረ ብልሹ የፀጥታ አካላት በመዲናዋ ነዋሪዎች ላይ በግልፅ ዝርፊያ መፈፀም እንደጀመሩ ታወቀ

አንዳንድ ምግባረ ብልሹ የፀጥታ አካላት በመዲናዋ ነዋሪዎች ላይ በግልፅ ዝርፊያ መፈፀም እንደጀመሩ ታወቀ (መሠረት ሚድያ)- የፀጥታ አካላት በአቅራቢያችን ሲገኙ ደህንነት ይሰማናል፣ ከሌላው ግዜ በተለየ ህግ አስከባሪ እንዳለ ተሰምቶን ሰላም ይታየናል። ይህ የተለመደ ስሜት ግን በቅርብ ግዜያት በተለይ በመዲናዋ አዲስ አበባ እየጠፋ ይገኛል፣ ለዚህ ደግሞ እየበዙ የመጡት ምግባረ ብልሹ የፀጥታ አካላት ናቸው። https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/0be?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, ኢትዮጵያ, ኤኮኖሚ, ፖለቲካ

አሜሪካ ስለፋኖ ድሮንና ጦርነቱ …………… የተሾሙት ጳጳስና ብልፅግና

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

አሜሪካ ዛሬ አዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ በኩል ለፌዴራል መንግሥት እና ለታጣቂዎች መልዕክት አስተላልፋለች።

አሜሪካ ምን አለች ? ➡️ ” ፋኖ ተጨባጭ እና ሰላማዊ የሆነ ዓላማ ይዞ ይምጣ። ” ➡️ ” የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) በኦሮሚያ ያለውን ግጭት ለማስቆም ድርድሩን ይቀጥል። ” ➡️ ” የፌዴራል መንግሥት በራሱ ዜጎች ላይ የሚያደርገውን የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ ያቁም። ” አሜሪካ ዛሬ አዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ በኩል ለፌዴራል መንግሥት እና ለታጣቂዎች መልዕክት አስተላልፋለች። በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ዛሬ ባስተላለፉት መልዕክት በመላው ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለጉዳት የዳረጉ ግጭቶች ሰላማዊና ትክክለኛ መፍትሔ እንዲፈለግላቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። አምባሳደሩ፥ ለታጣቂ ኃይሎች እና ለፌደራል መንግስት ባስተላለፉት መልዕክት ህዝብን እንዲያስቀድሙ ጥሪ አቅርበዋል። ” ጦርነቱን ማቆም፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ መርዳት እና ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ እና የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ ነው ” ሲሉ አስገንዝበዋል። ” በትጥቅ ትግል ስም የሚፈጸሙ ህገወጥ እና የኃይል እርምጃዎች ሊቆሙ ይገባል ” ብለዋል። አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በመልዕክታቸው ለፋኖ ፣ ለኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) እና ለፌደራል መንግስት የተናጠል መልዕክት አስተላልፈዋል። በዚህም ፥ – ፋኖ ተጨባጭ የሆነ እና ሰላማዊ የሆነ ዓላማ/ግብ ይዞ እንዲመጣ፤ – የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) ደግሞ በኦሮሚያ ያለውን ግጭት ለማስቆም ድርድሩን እንዲቀጥል፡ – የፌደራል መንግስት በራሱ ዜጎች ላይ የሚያደርገውን የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ እንዲያቆምና ረጅም እርምጃ ወደ ለሰላም በመምጣት መፍትሄዎችን እንዲያመቻች ጥሪ አቅርበዋል። አምባሳደሩ በመልዕክታቸው ማጠናቀቂያ ” ሰላምና መረጋጋት የምንመርጥበት ጊዜ አሁን ነው ” ብለዋል።
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

ከሀዲዎች በጊዜ መራገፋቸው ጥሩ እድል ነው ( አርበኛ ሀብቴ ወልዴ የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድ አባል )

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ, ፖለቲካ

አመራርና አዛዦች በፋኖ ተመተዋል ፤ የፋኖ ሀይሎች ከባድ ጥቃት ከፍተዋል

Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, VIDEO ቪዲዮ, ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ የነብስ ወከፍ ገቢ እየቀነሰ መምጣቱንና በአንጻሩ የዋጋ ግሽበት እየጨመረ መሄዱ ተገለጠ

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር እንደ ጎርጎሮሳዊያኑ ከ2001 እስከ 2023 የኢትዮጵያ ጠቅላላ አገራዊ ምርትና ምርቱ ለዜጎች የሚያስገኘው የነብስ ወከፍ ገቢ እየቀነሰ እንደሄደ በጥናት ማረጋገጡን መግለጡን ሸገር ዘግቧል። ማኅበሩ በተለይ ከአውሮፓዊያኑ ከአውሮፓዊያኑ 2016 ጀምሮ የነብስ ወከፍ ገቢ እየቀነሰ መምጣቱንና በአንጻሩ የዋጋ ግሽበት እየጨመረ መሄዱንና እንደገለጠ ዘገባው ጠቅሷል። የማዳበሪያ አጠቃቀም ከዓለማቀፍ መስፈርት አንጻር ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ የግብርናው ዘርፍ ያገኘው ብድር 7 ነጥብ 8 ከመቶ ብቻ መኾኑንም ተቋሙ ገልጧል ተብሏል። የጥሬ እቃ እጥረት፣ የኤሌክትሪክ ኃይልና የውሃ አቅርቦት እጥረትም ለአምራቹ ዘርፍ ፈተና እንደኾነ ተገልጧል። ግጭቶችም ኦኮኖሚው እንዲቀዛቀዝና ኢንቨስትመንት እንዲዳከም ምክንያት ሆነዋል ተብሏል።
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, ኢትዮጵያ, ኤኮኖሚ

ቤንሻንጉል ጉሙዝ : የተገደሉት ሰዎች ብዛት 17 ነው; ከሟቾች መካከል 12 ህፃናት ናቸው

“ የተገደሉት ሰዎች ብዛት 17 ነው። ከሟቾች መካከል 12 ህፃናት ናቸው ” – የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አባል በካማሺ ዞን ምዥጋ ወረዳ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ንጹሐን ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የክልሉ ምክር ቤት አባል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ። ነዋሪዎቹ፣ “የሸኔ ታጣቂዎች ጥቃት ፈጽመዋል” ብለው፤ ከ10 በላይ ንጹሐን እንደተገደሉ፣ አብዛኛዎቹ ሟቾች ህፃናት እንደሆኑ ተናግረዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለ ጥቃቱ የጠየቃቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ም/ቤት አባልና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ለሜሳ ኔኖ፣ “ ትክክል ነው። ንጹሐን ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ግድያ ነው የተፈጸመው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። የክልሉ ምክር ቤት አባል በሰጡን ቃል በዝርዝር ምን አሉ ? “ በካማሽ ዞን ምዥጋ ወረዳ አንገር ሜጢ የሚባል ታዳጊ ማዘጋጃ ቀበሌ ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ/ም ንጋት 12 ሰዓት ጅምሮ የሸኔ ቡድን ጥቃት ፈጽሟል። በዚሁ ጥቃት 16 ሰዎች እዛው ነው የሞቱት። አንደኛው ሰው ደግሞ ለህክምና ከሄደ በኋላ ነው የሞተው። የተገደሉት ሰዎች ብዛት 17 ነው። ከሟቾች መካከል 12 ህፃናት ናቸው። ቀሪዎቹ አዋቂ ናቸው። ቡድኑ በተለያዩ ጊዚያቶች ጥቃት ሰንዝሯል። እስካሁን በተፈጸሙ ሦስት ጥቃቶች 27 ሰዎች ናቸው የተገደሉት። የትላንቱ ጥቃት የተፈጸመበት ቦታ ለኦሮሚያ ክልል አንድ ቀበሌ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ነው የሚገኘው። ጥቃቱ በወረዳው ከሚያዚያ ወዲህ ለሦስተኛ ጊዜ የተፈጸመ ነው ” ብለዋል። ምክንያቱና መፍትሄው ምንድን ነው ? የታጣቂዎቹ ፍላጎታቸው ምንድን ነው ? መፍትሄውስ ? በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, ኢትዮጵያ

በደብረብርሃን ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች ላልተፈለገ እርግዝና እና በአባላዘር በሽታ እየተጠቁ ነው

” በደብረብርሃን ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች ላልተፈለገ እርግዝና እና በአባላዘር በሽታ እየተጠቁ ነው ” የተፈናቃይ ሴት ወጣት ተወካዮች ⚫ ” የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት ይሰጡ የነበሩ ድርጅቶች አሁን ላይ ሁሉም ወጥተዋል ” የቻይና ካምፕ ተፈናቃይ አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ በደብረብርሃን መጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚሰጠው የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት ጥራቱን ያልጠበቀ በመሆኑ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን የተፈናቃዮቾ ሴት ወጣት ተወካዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል። በህክምና ባለሙያዎች ዘንድም ሚስጥር ጠባቂ አለመሆን አገልግሎት ለማግኘት በምንሄድበት ወቅት የማሸማቀቂያ ቃላቶችን የሚጠቀሙ በመሆኑ አገልግሎቱን ማግኘት ከብዶናል ብለዋል። “የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት እየሰጠ ያለው ዩኒሴፍ ብቻ ነው፣ አገልግሎት የሚሰጠውም ግቢ ውስጥ ቢሆንም ሴት ልጅ ስትገባ የእንትና ልጅ የወሊድ መቆጣጠሪያ ልትጠቀም ገበች ይላሉ፣ ስንወጣ ደግሞ ወጣት ወንዶች ይጠብቁና ያሸማቅቁናል” ሲሉ ችግራቸውን ይገልጻሉ። በተጨማሪም ” የህክምና ባለሙያው ወንድ ነው፣ ይህ ደግሞ ሴቶች በነፃነት የሚፈልጉት እንዳይናገሩ አድርጓል፣ በከተማው ጤና ጣቢያዎች ስንሄድም በነፃ ስለሆነ የሚሰጠው ምን ልታደርጊ ትመጫለሽ ውጪ ይላሉ። እነሱ የሚፈልጉት ብር የሚከፍለውን ሰው ብቻ ነው” ሲሉ አክለዋል። ወጣት ሴቶችም በየፋርማሲው መድሀኒት እየገዙ ይውጣሉ፣ አብዛኞቹም ለህመም እየተዳረጉ ነው ብለዋል። በስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት እጥረት በርካታ ወጣቶች ላልተፈለገ እርግዝና፣ ለአባላዘር እና ለመሳሰሉ ተላላፊ በሽታዎች መጋለጣቸውንም አስረድተዋል። “በተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ ውስጥ ያሉ ወጣት ወንዶች ተስፋ እየቆረጡ አልኮል እየጠጡ ሴት ልጆችንን አስገድደው እየደፈሩን ነው፣ ስንጠይቅም በቸልተኝነት ሁሉም ይስተካከላል ይላሉ” ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርቧል። በዚህ ጉዳይ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቻይና ካምፕ የተፈናቃይ ኮሚቴ
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, አፍሪቃ, ኢትዮጵያ

ከሚሰራበት ባንክ ውስጥ በፀጥታ አካላት የተወሰደው ወጣት ያለበት ሳይታወቅ አራት ወር ሞላው

ከሚሰራበት ባንክ ውስጥ በፀጥታ አካላት የተወሰደው ወጣት ያለበት ሳይታወቅ አራት ወር እንደሞላው ታወቀ (መሠረት ሚድያ)- ጥር 9/2017 ዓ/ም ከሚሰራበት ባንክ ውስጥ በፀጥታ አካላት ታፍኖ ተወሰደው ወጣት ያለበት ቦታ ሳይታወቅ አራት ወር እንዳለፈው ታወቀ። https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/954?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
Posted in Amharic News, Ethiopia News, News, ኢትዮጵያ