Blog Archives
የሸገር ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጋዜጠኞች ትዕግስት ዘሪሁንና ምንታምር ጸጋው ላለፉት 17 ቀናት በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ ሸገር ዘግቧል።
ፖሊስ ጋዜጠኞቹን በቁጥጥር ስር ያዋላቸው፣ ለጤና ባለሞያዎች ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ጤና ሚንስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ ዙሪያ ባአንድ የሕክምና ባለሙያ አስተያየት ላይ ጣቢያው በሠራው ዘገባ ሳቢያ መኾኑን ለፍርድ ቤት አስረድቷል ተብሏል።
ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጋዜጠኞቹ በገንዘብ ዋስትና እንዲለቀቁ ወስኖ የነበረ ቢኾንም፣ ፖሊስ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ እንደጠየቀና ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ለመስከረም 12፣ ቀጠሮ እንደሠጠ ዘገባው አመልክቷል።
ኢሕአፓ፣ መኢአድ፣ እናት ፓርቲ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞከራሲያዊ ፓርቲና የአማራ ግዮናዊ ንቅናቄ ቅንጅት መስርተዋል።
ፓርቲዎቹ ቀድም የመሠረቱት፣ ኃይላቸውን ለማሰባሰብና በምርጫ ወቅት ትብብር ለማድረግ መኾኑን የኢሕአፓ ዋና ጸሐፊ ሚስጥረሥላሴ ታምራት ለዋዜማ ተናግረዋል፡፡
ኾኖም ፓርቲዎቹ በቀጣዩ ምርጫ ስለመሳተፍ ገና ያልወሰኑ ሲኾን፣ ቅንጅቱ ወደፊት አስቻይ ኹኔታ መኖር አለመኖሩን አጥንቶ ይወስናል ተብሏል።
ቅንጅቱ መስከረም 10 በይፋዊ ፊርማ እውን እንደሚሆን ሰምተናል፡፡
የኢትዮጵያ የእዳ ጫና አስተማማኝ ደረጃ ላይ አይደለም ሲል ዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም ባወጣው አዲስ ሪፖርት አስጠንቅቋል።
ተቋሙ፣ አገሪቱ ከፍተኛ እዳ እንደተጫናትና ከፍተኛ የጥሬ ገንዘብ እጥረትና የውጭ እዳ የመክፈል አቅም ውስንነት እንደገጠማት ገልጧል።
የአገሪቱ የውጭ እዳ ጫና ወሳኝ ደረጃዎችን ማለፉን፣ ከአጠቃላይ ዓመታዊ የአገሪቱ የወጪ ንግድ 206 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱንና አገሪቱ እዳዋን ለመክፈል የምታወጣው ወጪ በተያዘው ዓመት ከመንግሥት አጠቃላይ ገቢ 37 ነጥብ 7 በመቶውን እንደሚሸፍንም ተቋሙ ጠቅሷል።
ተቋሙ፣ የፖለቲካና ማኅበራዊ ተጽዕኖዎች የመንግሥትን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሊያዘገዩት ወይም ሊቀለብሱት ይችላሉ በማለትም አስጠንቅቋል።
የጠ/ሚሩን አዲስ መፅሀፍ በግዴታ ግዙ እየተባልን ነው በማለት የንግድ ባንክ ሰራተኞች አማረሩ
(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በሚድያዎች አበይት ክስተት ሆነው ከሰነበቱ ጉዳዮች አንዱ መስከረም 6 ቀን ለንባብ የበቃው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የተፃፈው ”የመደመር መንግሥት” የተባለው መፅሀፍ ነው።
በመደመር እሳቤ ላይ ተመርኩዞ ለአራተኛ ግዜ ለንባብ የበቃው መፅሀፍ በርካታ የመንግስት ባለሰልጣናት በተገኙ…
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/mvuudc7h
(መሠረት ሚድያ)- ሁለት የሸገር ኤፍ ኤም ጋዜጠኞች ከሁለት ሳምንት በፊት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እና ሜክሲኮ ታስረው እንደሚገኙ በወቅቱ መረጃ ማቅረባችን ይታወሳል።
ዋና አዘጋጁ ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ በወቅቱ ከታሰረ ከሰዓታት በኋላ መለቀቁ የሚታወስ ሲሆን አርታኢዋ ትግስት ዘሪሁን እና ሪፖርተሯ ምንተአምር ፀጋው ግን አሁንም ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ማቆያ እንደሚገኙ ሚድያችን አረጋግጧል።

በትናንትናው ዕለት ፍርድ ቤት እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ ቢፈቅድም ጋዜጠኞቹ እስካሁን አለመፈታታቸው ታውቋል።
ሸገር ኤፍ ኤም በበኩሉ በጉዳዩ ዙርያ ዝምታን የመረጠ ሲሆን በራሱ ጋዜጠኞች እስር ዙርያ የሰራውን የዜና ዘገባ ከገጾቹ አንስቷል።
“ትናንት ዋስትናቸው ከተፈቀደ በኋላ ይፈታሉ የሚል ተስፋ ነበረን፣ እስካሁኑ ሰዓት ግን ይህ አልሆነም” ያለው አንድ የመረጃ ምንጭ ሁለቱ ሴት ጋዜጠኞች በዓልን ጭምር በእስር ማሳለፋቸው ለቤተሰባቸው ከፍተኛ የስነ-ልቦና ጉዳት አምጥቷል ብሏል።
“ተቋሙ እንኳን ድምፅ ሊሆናቸው አልቻለም፤ እንደታሰሩ መታሰራቸውን ከዘገበ በኋላ አጥፉ ተብለው ነው አሉ አጠፉት” በማለት አስተያየት የሰጠ አንድ የሙያ አጋራቸው ሁለቱም ታሳሪዎች ታታሪ ጋዜጠኞች መሆናቸውን ገልጿል።
“ሁለቱም ሴት ጋዜጠኞች ናቸው፣ ይሁንንና የሙያ ማህበራትም ሆኑ ሚዲያዎችም እንዲሁም የሴት መብት ተቆርቋሪዎችም ሁሉም ጉዳዩን እያነሱት እንኳን አይደለም። ማንም ድምፅ እየሆናቸው አይደለም” በማለት የተሰማውን ለሚድያችን አጋርቷል።
ጋዜጠኞቹ የታሰሩት በጤና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ ዙርያ ከሁለት ሳምንት በፊት በነበረ ዜና ዙርያ መሆኑን የሚድያው ምንጮች ጠቁመው ዋና አዘጋጁ የተለቀቀው ዜናው ሲለቀቅ በስራ ላይ እንዳልነበር በመታወቁ ነው ብለዋል።
“ሸገር ኤፍኤም ለበርካታ አመታት እጅግ የበዙ
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ እንደቶ ቀበሌ ሰኞ’ለት ታጣቂዎች በፈጸሙት “ሐይማኖት ተኮር” ጥቃት ሁለት የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ተከታይ ምዕመናን መገደላቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል።
“ሐይማኖት ተኮር” ነው በተባለው ጥቃት፣ ከበደ ማሞ የተባሉ የ65 ዓመት አዛዉንትና የ6 ልጆች አባት እንዲሁም አበሬ ስዩም የተባሉ የሁለት ልጆች እናት በጥይት ተመትተው ሕይወታቸው ማለፉን የዜና ምንጩ ከነዋሪዎች መስማቱን ጠቅሶ አስነብቧል።
ከሳምንታት በፊት በዞኑ ሮቤ ወረዳ የመሰራንጄ ኦዳ ቅዱስ ጊዎርጊስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ መምሬ ንጉሤ ወልደ መድኅን ካህን በመኖሪያ ቤታቸው በታጣቂዎች በጥይት ተደብድበው መገደላቸው ይታወሳል።
ብሪታንያ፣ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር በገባችበት የባሕር በር ውጥረት ጋር በተያያዘ የተሳሳተ ስሌት እንዳትይዝ የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዴቪድ ላሚ ለኢትዮጵያ አቻቸው ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ባለፈው ነሃሴ ማስጠንቀቂያ አዘል ምክር ሰጥተው እንደነበር የብሪታኒያ ፓርላማ አባላት ማክሰኞ’ላት ባደረጉት አንድ ውይይት ተገልጧል።
ላሚ ኢትዮጵያ ይልቁንም ውጥረቱን ለማርገብ ድርድርን እንድትመርጥ መምከራቸውን፣ በብሪታንያ ፓርላማ የመንግሥት ተጠሪ ጀራርድ ሌሞስ ፓርላማው በሁለቱ አገሮች ውጥረት ዙሪያ ባደረገው ውይይት ላይ ተናግረዋል። የብሪታንያ መንግሥት ለኤርትራ ባለስልጣናትም ተመሳሳይ መልዕክት አስተላልፏል ተብሏል።
ሌሞስ፣ ማንም አገር ለንግድ አገልግሎት የባሕር በር ማግኘት ያለበት በሰላማዊ ድርድር ብቻ ነው የሚል አቋም እንዳላትና በሌላ አገር ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ላይ የሚቃጣ የኃይል ዛቻ እንደማትደግፍ ተናግረዋል።
ብሪታንያ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለችና አገራቱ ውጥረቱን ከሚያባብሱ ድርጊቶች እንዲቆጠቡ እያስጠነቀቀችና ድርድር እንዲጀምሩ ግፊት እያደረገች እንደሆነም ሌምስ ገልጸዋል።
የኬንያ ፓርላማ አባል የሆኑት ፋራህ መዓሊም፣ ኤርትራ፣ ሶማሊያ፣ ጅቡቲ እና ሱዳን የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይን ጨምሮ የኢትዮጵያ መንግሥታት በቀጠናው ያራምዱታል ያሉትን የማናለብኝነት ፖሊሲ ለመመከት፣ የጋራ ወታደራዊ ትብብር ስምምነት እንዲፈራረሙ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሠፈሩት መልዕክት ጥሪ አድርገዋል።
ኢትዮጵያን ከእስራኤል ጋር ያመሳሰሉት መዓሊም፣ ኢትዮጵያ ልክ እንደ እስራኤል “በሐሰት ታሪክ እና በምዕራባዊያን ያልተቆጠበ ድጋፍ አቅሏን ስታለች” በማለት ተችተዋል።
መዓሊም፣ ከሶማሊያ ጋር የምትዋሰነውን የኬንያዋን ጋሪሳ ግዛት የሚወክሉ የፓርላማ አባል ሲሆኑ፣ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በተደጋጋሚ የከረረ ትችትና ተቃውሞ በማቅረብ ይታወቃሉ።
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር፣ የኢትዮጵያው ገዥ ፓርቲ ባለስልጣናት፣ በባሕር በር ዙሪያ የሚያራምዱት ትርክት “ቢራቢሮ መቀመጫዋን መሸፈን ሳትችል፣ መሬት ትሸፈናለች” የሚለውን አገራዊ ብሂል የሚያስታውስ ነው በማለት ተሳልቋል።
ሚንስቴሩ፣ የብልጽግና ፓርቲ ባለስልጣናት ሕገወጡን የባሕር በር አጀንዳ ትክክለኛ ብሄራዊ አጀንዳ ለማስመሰል መጠነ ሰፊ ዘመቻ ያደርጋሉ ብሏል። ትርክቱ በኢትዮጵያና በጠቅላላው በቀጠናው ላይ አለመረጋጋት ያስከትላል ያለው ሚንስቴሩ፣ ኤርትራ ከጎረቤቶቿ ጋር ትብብር ማድረግ የምትችለው በመከባበር፣ በግልጽ ሕጋዊ መሠረትና ለቀጠናዊ መረጋጋት በጋራ በመስራት ብቻ ነው በማለት የመንግሥትን አቋም አስፍሯል።
ሚንስቴሩ፣ የብልጽግና ፓርቲ የባሕር በር አጀንዳ “ሃላፊነት የጎደለው”፣ “የማያዛልቅ”፣ ውድቅ ሊደረግና ሊመከት የሚገባው መኾኑንም ጠቅሷል።
አብዱራህማን መሃዲ የሚመሩት የኦብነግ አንጃ፣ ሰሞኑን ይፋ ከሆነው የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ97 በመቶው በላይ የሶማሌ ክልል ተማሪዎች መውደቃቸው “አስደንጋጭ ክልላዊ ውድቀት” ነው በማለት ቅሬታውን ገልጧል። ፈተናውን ከወሰዱት 16 ሺሕ 779 ተማሪዎች ያለፉት 462ቱ ብቻ መሆናቸውን አንጃው ጠቅሷል። አንጃው፣ የተማሪዎች ዝቅተኛ ውጤት፣ ገዥው ፓርቲ በሶማሌ ክልል ላይ የሚያራምደው አድሏዊ አሠራር እና የክልሉ ባለስልጣናት የተዘፈቁበት ሙስና ውጤት ነው በማለትም ከሷል።
በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ጭናቅሰን ወረዳና በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ዶባ ወረዳ የሶማሌ ክልል የጸጥታ ኃይል አባላት ናቸው የተባሉ አካላት በፈጸሙት ጥቃት የአምስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተሰምቷል።
በጥቃቱ ሕይወታቸው ያለፈው የጭናቅሰን ወረዳ ነዋሪዎች መሆናቸውን ያስረዱት ምንጮች፣ በሌሎች ስድስት ሰዎች ላይ ደሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል።
ጳጉሜን 5 ላይም፣ በዶባ ወረዳ “ኩርፋ መቱ” ቀበሌ የታጠቁ ኃይሎች ባደረሱት ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች አካላዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል።
በእስር ላይ የሚገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ በጠና መታመማቸውን ቤተሰቦቻቸው እና ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።
ሰኞ ዕለት ታስረውበት ወደ ሚገኙበት የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሄደው እንደጎበኋቸው የገለጹት ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ፣ አቶ ክርስቲያን በቅርቡ ቀዶ ሕክምና ከማድረጋቸው ጋር በተያያዘ ሕመማቸው እየተባባሰ መምጣቱን ገልጸዋል።
የአቶ ክርስቲያን ታደለ አንድ ቤተሰብ አባልም፣አቶ ክርስቲያን ከወራት በፊት በመቅረዝ ሆስፒታል ቀዶ ሕክምና ማድረጋቸውን እና በቂ ክትትል ሳይደረግላቸው ወደ ማረሚያ ቤት እንዲመለሱ መደረጋቸው አሁን ላሉበት ሁኔታ እንዳበቃቸው ተናግረዋል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) ወክለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እንዲሁም በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነበሩ።
በአማራ ክልል የተፈጠረውን የፀጥታ መደፍረስ ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከተደነገገ በኋላ በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ በእስር ላይ እያሉ ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ ላለፉት ሁለት ዓመታት በእስር ላይ ይገኛሉ።

ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የአቶ ክርስቲያን የቤተሰብ አባል ለአቶ ክርስቲያን በሕክምናም ሆነ በፍርድ ቤት የተፈቀደላቸውን ለሕመማቸው ተስማሚ የሆኑ ምግቦችን ማስገባት እንዳልተፈቀደላቸው እና ከአንድም ሁለቴ ምግብ መቅረብ ሳይችሉ መመለሳቸውን ገልጸዋል።
ከዚህም ባሻገር አቶ ክርስቲያንን ጨምሮ በሽብር ተከሰው ማረሚያ ቤት የሚገኙትን የምክር ቤት አባላት ለመጠየቅ ወደ ማረሚያ ቤቱ በሚያመሩበት ወቅት እንግልት እና መጉላላት ይደርስብናል ብለዋል።
አቶ ክርስቲያን ከወራት በፊት ቀዶ ሕክምና ተደርጎላቸው እንደነበር ቤተሰቦቻቸው እና ጠበቃቸው የገለጹ ሲሆን፣ በወቅቱ በተገቢው ሁኔታ ክትትል አግኝተው ሳያገግሙ ወደ እስር ቤት እንዲመለሱ ተደርገዋል
አውስትራሊያን ጨምሮ የምዕራብና የምሥራቅ አውሮፓ አገሮች ያሉበት የ42 አገሮች ቡድን፣ በኢትዮጵያ የተጀመረው የሽግግር ፍትሕ ሒደት ባለበት መቆሙና የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ እንዳሳሰባቸው ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) አስታወቁ፡፡
በጀኔቭ ስዊዘርላንድ እ.ኤ.አ. ከመስከረም 8 ቀን 2025 እስከ ጥቅምት 8 ቀን 2025 ድረስ እየተካሄደ ባለው 60ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት ጉባዔ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ አባል አገሮች እየተሳተፉበት ይገኛሉ፡፡
ከቀናት በፊት ኢትዮጵያን በተመለከተ የጋራ መግለጫ ካወጡ አገሮች መካከል ፈረንሣይ፣ ቼክ ሪፐብሊክ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ኖርዌይ፣ ዩክሬን፣ አውስትራሊያ፣ አየርላንድ፣ ቡልጋሪያ፣ ሞልዶቫ፣ ስዊድንና አውስትራሊያን ጨምሮ 42 የአውሮፓ ኅብረት አባል አገሮች ይገኙበታል፡፡
በዚህ ጉባዔ ኢትዮጵያን በተመለከተ የሰብዓዊ መብት ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን አገሮቹን ወክሎ ሪፖርት ያቀረበው የአውሮፓ ኅብረት፣ በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ሁኔታ እንዳሳሰበው ገልጿል፡፡ ‹‹ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ፣ ሰላማዊ ሠልፍ የማድረግና የመደራጀት መብት ከመጪው ምርጫ አስቀድሞ መገደባቸው ያሳስበናል፤›› ብሏል፡፡ ኢትዮጵያ መጪውን አገራዊ ምርጫ በተያዘው ዓመት አሥር ወራት ውስጥ ታካሂዳለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ … ዝርዝሩ እዚህ ያገኙታል https://ethiopianreporter.com/145830/
ኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ቁመናቸው ዝቅተኛ ከሆኑ አገሮች አንዷ መሆኗ ተገለጸ
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የዴሞክራሲ ቁመናቸው ዝቅተኛ ነው ከተባሉት ሞሪታኒያ፣ ምይንማር፣ ሊባኖስና ግሪክ ጋር መመደቧን ዓለም አቀፍ የዴሞክራሲና ምርጫ ድጋፍ ተቋም (አይዲያ) የተሰኘው ተቋም… https://ethiopianreporter.com/145825/
ሳንድፎርድ ትምህርት ቤት በዶላር የማይከፍሉ ተማሪዎች እንደማይቀጥሉ ማስታወቁ ጥያቄ አስነሳ
ትምህርት ቤት፣ ክፍያ፣ የውጭ ምንዛሪ፣ የትምህርት ሥልጠና ባለሥልጣን፣ ብሔራዊ ባንክ፣ ፍርድ ቤት Mhiret የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ማብራሪያ በመጠየቅ ትምህርታቸው እንዳይስተጓጎል… https://ethiopianreporter.com/145828/
…ብሔራዊ ባንክ ትልቁ ትምህርት ቤት ነው፣ ሁሉም ነገር እዚያ ነው ያለው፡፡ ዕድለኛ ነኝ ያልኩበት አንዱ ምክንያት ከአይኤምኤፍ ጋር በነበረው ድርድር ገና ጀማሪ ሆኜ ለአገሬ በጣም ከፍተኛ ተፎካካሪ ነበርኩ፡፡ ውጤትም አግኝቼበታለሁ፡፡ ብዙ ነገሮች አስቀይሬያለሁ፡፡ በድርድራችን ጊዜ አይኤምኤፍ አሸንፎን አያውቅም፡፡ …በልማት ባንክ ሥራ ስጀምርም የባንኩን ሠራተኛ ወደ አንድ የሚያመጣ ሥራ ሠርቻለሁ፡፡ አንድም ሠራተኛ አላባረርኩም፡፡ ሠራተኛው ሥራውን በፍቅር እንዲገባበት ተደረገ፣ ውጤት እያየ ሲመጣ ደግሞ አገልግሎቶች ከላይ እስከ ታች የተናበቡ ሆኑ፡፡ የባንኩ ፖሊሲ እስከተፈጸመ ድረስ ፕሬዚዳንት ስለሆንኩኝ ገደብ የለሽ ሥልጣን አልወሰድኩም፡፡ ዋናው ቁጥጥሬ ፖሊሲው በአግባቡ እየተተገበረ መሆን አለመሆኑ ላይ ነው፡፡ ችግር ካለና ከሠራተኞች አቅም በላይ የሆነ ነገር ካለ እሱን መፍታት ነው፡፡ የሚሰርቅና የሚያጭበረብረውን ደግሞ ቦታ እንዳይኖው ነው ያደረግኩት፡፡ እንዲህ በመሥራት ነው ለውጡና ዕድገቱ የመጣው፡፡ …በየቦታው የተበለሻሸ ነገር ነበር፡፡ ሁለተኛው የመንግሥት ከመጠን ያለፈ ጣልቃ ገብነት ነበር፡፡ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ይደወልና ለእከሌ ብድር ስጠው ይባል ነበር፡፡ ሰንሰለቱ በጣም የተንዛዛ ነበር፡፡ የተናበበ ሲስተም አልነበረውም፡፡ የአሠራር ፖሊሲ አልነበረም፡፡ ብዙ ችግር ነበር፡፡ የመንግሥትን ዓላማ አቅጣጫ ይዤ ባንኩ የተሰጠውን ተልዕኮ ማስፈጸም ሥራዬ ነው፡፡ ስለአገር አቅም መከራከር ሥራዬ ነው፡፡ ከውጭም ይምጣ እዚህ አገር ያለም ዜጋ ይሁን፣ ትልቅም ሆነ ትንሽ ኢንቨስተርም ይሁን የአገር ጥቅም መቅደም ስላለበት በዚያ አግባብ ነበር የምሠራው፡፡ …ዝርዝር ዘገባውን በዚህ ሊነክ ይመልከቱ፡፡
ኬንያ የ42 የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን ፈቃድ ልትሰርዝ ነው።
የኬንያ የኮሚዩኒኬሽን ባለስልጣን በ7 ቀናት ውስጥ የ42 የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን ፈቃድ ሊሰርዝ መሆኑ ተነግሯል።
ባለስልጣኑ ፈቃዳቸው ሊሰረዝ የሚችልን ጣቢያዎች ዝርዝር ይፋ ሲያደርግ ፈቃዳቸው ከተሰረዘ በኋላ ምንም ስራ ማከናወን እንደማይችሉ ገልጿል።
የኮሚዩኒኬሽን ባለስልጣኑ የኬንያን የመረጃ ህግ የሚጥሱ ተቋማት በጋዜጣ ከተነገረ በኋላ በ7 ቀናት ውስጥ ፈቃዳቸው ሊሰረዝ እንደሚችል ሲያነሳ በዋነኝነት ያልተገባ ይዘት ማሰራጨት፣ የማሰራጫ መሰረተ ልማት አለመኖርና የፈቃድ ክፍያ አለመክፈል ፈቃድ ሊያሰርዙ ይችላሉ።
ከወራት በፊት የቤቲንግ ቁጥጥር እና ፈቃድ ቦርድ 23 የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከስፖርታዊ ውርርድ ጋር በተያያዘ የወጣውን የማስታወቂያ መመሪያ በመጣሳቸው ሊዘጉ እንደነበር አስጠንቅቆ ነበር።
ጣቢያዎቹ የስፖርት ውርርድ ማስታወቂያ እንዳይተወወቅ ቢታገድም ማስታወቂያዎችን ማሳየት መቀጠላቸውን ቦርዱ ገልፆ ነበር።
42 የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ፈቃድ መሰረዝ በባለፈው የፈረንጆቹ መስከረም 12 በጋዜጣ የወጣ ሲሆን በመጪዎቹ 7 ቀናት ውስጥ ይፈፀማል ተብሎ ይጠበቃል።
ጎረቤት ሃገር ኬንያ በ2023 በአጠቃላይ 135 (https://youtu.be/vyCHx1WJfMg?si=zyPPwWoC-zawEPd-) የቴሌቪዥን ጣቢያዎችና 225 የሬዲዮ ጣቢያዎች የነበሯት ሲሆን በዋነኝነት መቀመጫቸውን በዋና ከተማዋ ናይሮቢ ያደረጉ ናቸው።
ዘገባው የKenyans ነው።
ሰበር!…..ከባድ ተኩስ በወልድያ ከተማ!
የሰሜን ወሎ ዞን መቀመጫ በሆነችው ወልድያ ከተማ ከምሽቱ 5:35 ጀምሮ ለደቂቃዎች የቆየ ከባድ የተኩስ ድምፅ መሰማቱን የከተማዋ ነዋሪዎች ለመረብ ሚዲያ ገልፀዋል።
የተኩስ ድምፁ የተሰማው በከተማዋ አዳጎ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በሚገኘው የአድማ ብተና ካምፕ ውስጥ ነው ተብሏል።
አሁን ላይ ተረጋግቷል የሚሉት የመረብ ምንጮች፡ ነገር ግን ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በከተማዋ አውራ ጎዳናዎች ላይ የአምቡላንስ እንቅስቃሴ ይታያል ብለዋል።
የዞኑ ካድሬዎች የሕዳሴ ግድብ መመረቁን ሰበብ በማድረግ በከተማዋ መንግስትን የሚደግፍ የግዳጅ ሰልፍ ለነገ መጥራታቸውን መረብ ሚዲያ ከሰዓታት በፊት መዘገቡ ይታወሳል።
የብልፅግናው ቡድን እራሱ ባደራጃቸው ሽብር ፈጣሪ አካላት በአማራ ክልል በተመረጡ ከተማዎች ለነገ በጠራው የግዳጅ ሰልፍ ላይ ቦምብ በማስወርወር “ፋኖ ጥቃት ፈፀመ” በሚል ሐሰተኛ መረጃ ለማሰራጨት ዝግጅት ስለማድረጉ ለጣቢያችን የደረሰው መረጃ ያመላክታል።
መረብ ሚዲያ አደጋው በደረሰ በደቂቃዎች ልዩነት የአይን እማኞችን አነጋግሮ በማህበራዊ ትስስር ገፆቹ መረጃውን ማስነበቡ አይዘነጋም።
ገዢው የብልፅግና ቡድን፡ የሕዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለዛሬ መስከረም 04/2018 ዓ/ም የድጋፍ ሰልፍ እንዲያካሂዱለት ባስተላለፈው መመሪያ መሠረት፡ በሰልፉ ላይ ልዩ ልዩ ትርኢቶችን እንዲያሳዩ ስልጠና ሲሰጣቸው የነበሩ ታዳጊዎች ተሰብስበውበት የነበረው መድረክ ተንዶ በበርካታ ታዳጊዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ማስከተሉን መረብ ሚዲያ ትናንት ምሽቱን የአይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ አደጋው በደረሰ በውስን ደቂቃዎች ልዩነት ዘግቦ ነበር።
አደጋው የደረሰው ትናንት መስከረም 03/2018 ዓ/ም ምሽት 2 ሰዓት ገደማ ላይ ሲሆን፡ አደጋው ከደረሰባቸው ታዳጊዎች መካከል ሕይወታቸው ያለፈ እንዳለ፡ ነገ ግን ብዛታቸውን በውል ማወቅ እንዳልተቻለ ምንጮቻችን በወቅቱ ገልፀው ነበረ።
መረብ ሚዲያ ያነጋገራቸው የአይን እማኞች፡ “እኛ በአከባቢው የነበርን ሰዎች ወደ ውስጥ ገብተን እንዳናግዝ ስለ ጉዳቱ መረጃ ታወጣላችሁ በሚል ተከልክለን፡ አከባቢው ከፍተኛ ቁጥር ባለው የፀጥታ ኃይል እየተጠበቀ ጥቂት የፖሊስ አባላት ብቻ ፍርስራሹን እንዲያነሱ ተደርጓል” ብለዋል።
ተጎጂዎቹን ከፍርስራሽ ውስጥ አውጥቶ ወደ ሕክምና ለመውሰድ ሰዓታትን ፈጅቷል ያሉት ምንጮቻችን፡ በዚህም መትረፍ የሚችሉ ታዳጊዎች አስቸኳይ እርዳታ ባለማገኘታቸው ሳይተርፉ ቀርተዋል ብለዋል።
በልጆቻቸው ላይ የደረሰውን አደጋ የሰሙ ወላጆች ተጎጂዎቹ ወደ ተወሰዱበት ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሄዱ ቢሆንም፡ ነገር ግን በሆስፒታሉ በር ላይ በቆሙ የፀጥታ ኃይሎች እንዳይገቡ ተከልክለዋል።
በዚህም በርካታ የተጎጂ ታዳጊዎች ቤተሰብ ለሊቱን ሙሉ በሆስፒታሉ በር ላይ ሆነው በለቅሶና ዋይታ ተሞልተው ማደራቸውን ጣቢያችን ለማረጋገጥ ችሏል።
የገዢው
ኢትዮጵያና አፍሪካ ታላቁን ልጃቸውን አጥተዋል!

የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ አገራቸውን ብሎም አሕጉራቸውን አፍሪካን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በአገር ፍቅር ስሜትና በልቀት ሲያገለገሉ የኖሩት ታላቁ የኢትዮጵያ አገልጋይ ዶክተር ምናሴ ኃይሌ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ዶክተር ምናሴ ኃይሌ ከአባታቸው ከባላምባራስ ኃይሌ ድብነህ ከእናታቸው ወይዘሮ ኢሌኒ ኃይሌ ታኅሣሥ 24 ቀን 1922 ዓ.ም. ሐረር ከተማ የተወለዱት ሲሆን ከማንም በላይ የለፋላትን አገራቸውን ከኀምሳ አመታት በላይ ሳያዩ በስደት እንዳሉ በአሜሪካን አገር በኒውጀርሲ ጠቅላይ ግዛት ሕይዎታቸው አልፏል።
ከአለሙ ንጥል ብለው ከሚኖሩት ከእኒህ ታላቅ ሰው ጋር ስለዘመናቸው የመወያየት እድል ከገጠማቸው ሰዎች አንዱ ነኝ ብዬ አስባለሁ። ስለ ሕይዎታቸው፣ ስለደከሙላት አገራቸውና ስለትዝብታቸው ያጫወቱኝ ብዙ ነው። ዶክተር ምናሴ ጨዋ፣ አገር ወዳድ፣ ሰው አክባሪና የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሕዝብ የደከመውን ድካም ከአረመኔዎቹ ከደርግና ወያኔ ጋር ፊት ለፊት እየተጋፈጡ ያለማመንታት ሳይታክቱ ባሳተሟቸው ጥናታዊ ጽሑፎችና መጽሐፍት ታሪካችንን እንድናውቅ አድርገናል።
ዶክተር ምናሴ ሆስፒታል ውስጥ ተኝተው ሕክምና በሚከታተሉበትም ወቅት ጤናቸው በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ በስልክ በጠየቅኋቸው ወቅት ከነበሩን ቆይታዎቻችን መካከል ከታች የተያያዘው አጭር የስልክ ቆይታችን አንዱ ነው። ወደፊት በሌላ ጽሑፍ ሕይዎታቸውን እንዘክረዋለን!
በሰው ላይ ሞትን የሚያህል እዳ አለና ዶክተር ምናሴ ኃይሌ የማንም ባለጌ የሚፈነጭባትን የፉላትን አገራቸውን ሳያዩ ማለፋቸው እጅግ ያሳዝናል። እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በገነት ያኑረው። ለወዳጆቻቸውና ለቤተሰባቸው በሙሉ ጽናትንና ብርታትን ፈጣሪ እንዲሰጣቸው ከልብ እመኛለሁ። የኢትዮጵያ አገልጋይ ሆነው ለአገርዎ
(መሠረት ሚድያ)- በመስቀል አደባባይ የተከናወነው ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ እና ትርዒት ለማቅረብ ሲለማመዱ የነበሩ ታዳጊዎች የመድረክ መደርመስ አደጋ እንዳጋጠማቸው ይታወሳል።
የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁን በማስመልከት የተካሄደው ሰልፍ ላይ ለመሳተፍ ልምምድ ሲያደርጉ የነበሩት ታዳጊዎች አደጋው ያጋጠማቸው ቅዳሜ ምሽት 3 ሰዓት ገደማ በመስቀል አደባባይ መሆኑ ታውቋል። በዚህ ዙርያ ዛሬ የደረሰን ተጨማሪ መረጃ እንደሚጠቁመው በአደጋው ተጎድተው ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከተወሰዱ ታዳጊዎች መሀል ቁጥራቸው በውል ያልታወቁት ህይወታቸው ያለፈ መሆኑን መሠረት ሚድያ ሰምቷል።
“ገና በለጋ እድሜያቸው ጎበዝ ጎበዝ ተማሪዎችን ከየትምህርት ቤታቸው በመምረጥ መንግስት ለጎበዝ ተማሪዎች ያዘጋጀው የጉብኝት ፕሮግራም አለ፣ ለሶስት ቀን ስለምትቆዩ ብርድ ልብስ እና አንሶላ ይዛችሁ ኑ ተብለው ስድስት ኪሎ ካምፓስ አስገብተዋቸው ነበር” ብለው ለሚድያችን ቃላቸውን የሰጡ አንድ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የመረጃ ምንጫችን ናቸው።
ምንጩ አክለውም “ከዛ አምስት ቀን ትቆያላችሁ፣ ቀጥሎ አስር ቀን ትቆያላችሁ፣ ብሎም በቃ ጳጉሜ ትሄዳላችሁ ካሏቸው በኋላ መውጣት አትችሉም በማለት ለአባይ ግድብ ምርቃት ትርዒት ታቀርባላችሁ ብለው ስልጠና አስጀምረዋቸው ነበር” ይላሉ።
ለአዲስ ዓመት በዓል ጭምር ታዳጊዎቹ ወደ ቤተሰቦቻቸው ሳይሄዱ ተነጥለው ማሳለፋቸው የታወቀ ሲሆን ላለፉት 15 ቀናት መስቀል አደባባይ ላይ በእንጨት እስከ 18 ደረጃ በተሰራ መድረክ ልምምድ ሲያደርጉ መቆየታቸው ታውቋል።
“ብዙዎቹን በአዲስ አበባ ባሉ ሆስፒታሎች ከፋፍለው ነው የላኳቸው። እኔ በምሰራበት ሆስፒታል 45 ልጆች ተጎድተው የመጡ ሲሆን ከመጡት ውስጥ 11 የሚሆኑት የጀርባ አጥንት ስብራት፣ የእጅ አጥንት ስብራት እና የእግር አጥንት ስብራት ያጋጠማቸው ሲሆን ሌሎች
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት የ”ሕወሓትን ህጋዊ ሠውነት መሻር ተቀባይነት የለውም” ሲሉ አስታወቁ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሠ ወረደ የ”ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕወሓትን ህጋዊ ሠውነት የመሻር ውሣኔ ተቀባይነት የለውም ብለው የገለፁ ሲሆን የፖለቲካ መፍትሔ እንዲሠጠውም” አሣስበዋል።
“ሕወሓት ሠርዤዋለሁ ተብሎ በቀላሉ ሊታለፍ የሚችል ተራ ፓርቲ አይደለም” ያሉት ፕሬዚዳንቱ ጉዳዩ ፖለቲካዊ መፍትሔ እንጂ በቢሮክራሲያዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንደማይችል አፅንኦት ሠጥተዋል።
አብዛኛው የትግራይ ምሁራን፣ ተቃዋሚዎችን ጨምሮ፣ ከሕወሓት ጋር ግንኙነት እንደነበራቸው የገለጹ ሲሆን፣ ድርጅቱን “ታሪካዊ ፓርቲ” ሲሉ ጠርተው መሻሩ “ተቀባይነት የለውም” ብለዋል።
የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት በምርጫ ቦርድ እና በሕወሓት መካከል ያለው አለመግባባት በድርድር መፈታት ያለበት መሆኑንም ተናግረዋል።
ፓርቲው “ከምርጫ ቦርድ ሰርተፍኬት ቢቀበልም ድርድር ብቸኛው ዘላቂ መፍትሄ ነው” ሲሉም ለክልሉ ሚዲያዎች ተናግረዋል።
የምርጫ ቦርድ ሕወሓት ደረጃውን ለማሟላት ቦርዱ ያዘዘውን “የማስተካከያ እርምጃዎች” በስድስት ወራት ውስጥ ጠቅላላ ጉባዔ ማካሄድን ጨምሮ ተግባራዊ ማድረግ ባለመቻሉ በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም የፓርቲውን ህጋዊ ሰውነት መሻሩ ይታወቃል።
በወቅቱ ሕወሓት ውሳኔውን ውድቅ ያደረገ ሲሆን፣ የፓርቲው ህጋዊነት የተረጋገጠው በፕሪቶሪያው የጦርነት ማቆም ስምምነት እንጂ በምርጫ ቦርድ ቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሰረተ ማዕቀፍ እንዳልሆነ ተናግሯል። ፓርቲው እገዳውን ተከትሎ ከዚያ በኋላ የተሰጠውን ስረዛ “በህግ ደረጃ ትርጉም የለሽ” ሲል ቀደም ሲል ውድቅ አድርጎ ነበር።
ሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ ድርድር እንዲደረግ በማሳሰብ፣ የሕወሓት መሰረዝ የፕሪቶሪያን ስምምነት ሂደት አደጋ ላይ ሊጥል እና ሰፊውን የትግራይ የፖለቲካ ክፍል ሊያገለል እንደሚችል
“ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ተሰርቷል፤ የሚቀሩ እባጮች ነበሩ አሁን እነርሱን ነው ቆርጠው ያወጡለት” – የአቶ ክርስቲያን ታደለ የቅርብ ሰው
ለሁለት ዓመት ከአንድ ወር በእስር የሚገኙት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ሰሞኑን ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ማድረጋቸውን ቤተሰባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ሰው በሰጡን ቃል፣ “ ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ተሰርቷል፤ የሚቀሩ እባጮች ነበሩ አሁን እነርሱን ነው ቆርጠው ያወጡለት ” ብለዋል፡፡
ከዚህ ቀደም የቀዶ ህክምና አድርጎ እንደነበር ያስታወሱት እኝሁ የአቶ ክርስቲያን ቤተሰብ፣ “እባጭ ነበረው፤ ያኔም ያን ነበር ቆርጠው ያወጡለት፤ ግን የሚቀር እባጭ ነበር ” ሲሉ የአሁኑን ቀዶ ህክምና ምክንያት አስረድተዋል፡፡
በእስር ቤት ቆይታቸው ” ለአንጀት ድርቀት ህመም በመዳረጋቸው ” ከዚህ ቀደም ቀዶ ጥገና ማድረጋቸውን ያስታወሱት እኝሁ አካል፣ ያኔ ሙሉ ለሙሉ ቀዶ ህክምናው ተደጎላቸው ቢሆን ኖሮ “ እዛው ተኝቶ ሊከታተል ስለማይችል ከፍተኛ ጉዳት ይደርስበት ስለነበር ጊዜያዊ ሰርጀሪ ነበር የተሰራለት ” ብለዋል።
“ የሰው ልጅ አይደለም ቀዶ ህክምና የማያክል ነገር ተሰርቶና ታሞ እስር ቤት ሆኖ እቤት ተኩኖም ያስቸግራል” ብለው፣ “ሰዎች፣ የሰባዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ሂደው ቢያዩአቸው፤ ጠያቂ ቤተሰብ የሚደርስበትን ግፍም ቢመለከቱ” ሲሉ አሳስበዋል፡፡
ሰሞኑን በመቅረዝ ሆስፒታል ለሁለተኛ ጊዜ ቀዶ ህክምና ከተደረገላቸው በኋላ ተቆርጦ የወጣው እባጭ ለካንስር ቅድመ ምርመራ እንደተላከና ውጤቱ ለቀጣይ ሳምንት እየተጠበቀ እንደሆነ ተመልክቷል፡፡
የፍርድ ቤት ሂደቱ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲጠይቃቸውም፣ “ ከፍተኛ ፍርድ
“ሊበርጢኖን”
“ሊበርጢኖን የተባለው ስብስብ የቅዱስ የአስጢፋኖስን ተግሳጽ ከመቀበል ይልቅ አሴረበት፡፡ ሴራውን ያልተረዳውን ህዝብ አንሳስቶ አዘመተበት ፡፡ በመጨረሻም ገደለው፡፡ ዛሬ የማቀርብላችሁ ምስክርነት እስጢፋኖስ የተገደለበትን ሴራ የሚያሳስብና እንዳይደገም የሚያስተምረው በአብነቱ ትምህርት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡
“ከአቡነ ማትያስ ጀምሮ በዚህ ዘመን ያለን ካህናትና እናንተ ሁላችሁ ከብልጽግና መንግሥት ጋራ ተቆራኝታችሁ ወደ ሰማእቱ ታዴወስ ሄዳችሁ እሳቸው የሚሰጧችሁን ንስሐ በመቀበል የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሚሰይመው ዳኛ እጃችሁን ብትሰጡና ፍትህ ቢፈጸም መሬት ትጽዳለች፡፡ አየሩም ይጸዳል ወንዞችም ይጠራሉ፡፡ ከዚህ የተሻለ ኢትዮጵያን የሚፈውስ ፍቱን
አብነት የሚገኛ አይመስለኝም፡፡”
ይህንን እጅግ ብስለት ያለውንና ወቅቱን የዋጀ ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። “ሊበርጢኖን”
ፀረ ህዝብ የሆነዉ ብልፅግና በእስቴ መካነየሱስ ከተማ አሰቃቂ ተግባር መፈፀሙ ተሰማ!!
የእስቴ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ማንተፋርዶ ሞላ የተባለ ሆድ አደር ባንዳ የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ የሜጀር ጀኔራል ዉባንተ አባተ ኮር አንድ ጉና ክፍለጦር አስቴ ዴንሳ ብርጌድ ሻለቃ ሁለት ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ታርቆ ታመነ ቤትን በቦንብ በመምታት በቤቱ ላይ ከባድ ጉዳት እንዲደርስ ተደርጓል።
በእስቴ መካነየሱስ ከተማ ቀበሌ01 የሚገኘውን መኖሪያ ቤት ከሌሊቱ 6 :00 ሰአት ቤቱ ውስጥ የሚገኙትን ሰወች እንደተኙ በስከውጭ እንዳይወጡ በመቆለፍ ቤቱን በጋዝ በማርከፍከፍ በቦንብ ጭምር ቤቱ እንዲቃጠል አድርገውታል።
6 ሰው የአርበኛ ቤተሰቦች እብረው እንዲቃጠሉ ከተፈረደባቸው የሞት ፍርድ በእሪታ አካባቢ ሰው ደርሶ አትርፏቸዋል።
በከተማዋ የሚፈፀሙ አሰቃቂ ድርጊቶች ተጠናክረው የቀጠሉ ሲሆን የሚፈፀሙ አሰቃቂ ግፎችን በበላይነት የሚፈፅመዉ የወረደው አስተዳዳሪ አቶ ማንተፋርዶ ሞላ ነዉ።
የፋኖ አመራሮችን ለማስገደል ተልዕኮ ተሰጥቶት የነበረው የደህንነት አባል እጅ ከፈንጅ ተያዘ!
የደህንነት አባሉ የፋኖ አመራሮች ያሉበትን ቦታ ጥቆማ በመስጠት በድሮን ለማስገደል እንዲሁም የፋኖ ሎጅስቲክ ማከማቻ ናቸው ብሎ የሚያስባቸው ቦታዎችን ለድሮን ተኳሾች ጥቆማ በመስጠት የማውደም ተልዕኮ ተሰጥቶት ነበር ተብሏል።
የደህንነት አባሉ፡ በአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና አርበኛ በላይ ዘለቀ ዕዝ 4ኛ ደጃች ኮር ስር የሚገኘው ዋዋ ጎቤ ክ/ጦር በሚንቀሳቀስበት ቀጠና ሲቪል ልብስ በመልበስ በአካባቢው ሲንቀሳቀስ ነው በቁጥጥር ስር የዋለው ሲሉ የክፍለ ጦሩ አመራሮች አስታውቀዋል።
የደህንነት አባሉ መሐመድ ዋዮ ዎቴ በሚል ስም የሚጠቀም መሆኑንና የመከላከያ ሰራዊት አባል እንደሆነ በኪሱ ከያዘው መታወቂያ ለማረጋገጥ ተችሏል።
አብዲራህማን መሃዲ የሚመሩት የኦብነግ አንጃ፣ የሶማሌ ክልል መንግሥት አንድ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባሉን ጨምሮ አራት ከፍተኛ አመራሮቹን ጅግጅጋ ውስጥ በተያዘው ሳምንት መጀመሪያ ላይ እንዳሠረ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።
በክልሉ መንግሥት ትንኮሳ ወደ ጦርነት ተገደን አንመለስም ያለው አንጃው፣ ቡድኑ በሰላማዊ ትግሉ እንደሚቀጥልም አረጋግጧል።
አንጃው አያይዞም፣ የሶማሌ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ ለመወሰን፣ ለፍትሕና ዲሞክራሲ የሚያደርገውን ትግል በኃይል መጨፍለቅ አይቻልም ብሏል።
የክልሉ መንግሥት የአሥመራውን የሰላም ስምምነት በመጣስ፣ በክልሉ በተለይም በኦጋዴን ዳግም የትጥቅ ግጭት እንዲቀሰቀስ በማድረግ ላይ ይገኛል በማለት አንጃው በተደጋጋሚ ሲከስ ቆይቷል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ኹኔታ በአሜሪካ “ብሄራዊ ደኅንነት” እና “የውጭ ፖሊሲ” ላይ “ያልተለመደ” እና “ልዩ የኾነ ስጋት” ደቅኗል በማለት ከአራት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ላይ ያሳለፉትን ፕሬዝዳንታዊ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ድንጋጌ ሰሞኑን ለአንድ ተጨማሪ ዓመት አራዝመውታል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፕሬዝዳንታዊውን የአስቸኳይ ጊዜ ኹኔታ ድንጋጌ ያራዘሙት፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ኹኔታ በአገሪቲ ሰላምና መረጋጋት እንዲኹም በቀጠናው ላይ የደቀነው ስጋት አኹንም ቀጥሏል በማለት ነው።
ፕሬዝዳንታዊ ድንጋጌው፣ በጦርነቱ ወቅት ተፈጽመዋል በተባሉ “የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች” እና “የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተጓጎል” ወንጀሎች በተጠረጠሩ ማንነታቸውና ቁጥራቸው ባልተጠቀሰ የተወሰኑ ግለሰቦች ላይ ማዕቀብ የጣለ ነው።
“ጅራፍ አጮህን አልሰማ አሉ፡ ነፍጥ አነሳን” በደቡብ ጎንደር የክምር ድንጋይና የአከባቢው ታጋይ አርሶ አደሮች!
“ጅራፍ እያጮህን የአፈር ማዳበሪያ ስጡን ብለን ጠየቅን፡ አልሰማን አሉ።እንደውም “የጅራፍ ፖለቲካ” እያሉ ተሳለቁብን። እቅዳቸው ከጦርነት የሚተርፈውን አማራ በረሃብ ለመጨረስ ነበር። እኛ ግን ቀድመን ስለነቃን ጅራፍ እያጮኽን በጠየቅንበት፡ አሁን አልቢንና ጓንዴያችንን አንስተን መብታችንን ለማስከበር መራር ትግል እያደረግን ነው።”
“እቅዳችን አማራን እንደ አማራ የሚያስከብር፣ አርሶ አደሩን ምን ጎደለባችሁ እያለ ዝቅ ብሎ የሚጠይቅ ከኛው ከአማራ አብራክ የወጣ መሪ ማስቀመጥ ነው”
በደቡብ ጎንደር የክምር ድንጋይና የአከባቢው ታጋይ አርሶ አደሮች ከመረብ
የህዳሴ ግድብ የፈጠረው ሀይቅ የሚይዘው የውሀ መጠን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ያሏት ሀይቆች ከሚይዙት ውሀ መጠን ይበልጣል በሚል የቀረበው መረጃ የተሳሳተ ነው
/ኢትዮጵያ ቼክ/- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በተሰራጨ ንግግራቸው ላይ የህዳሴ ግድብ የፈጠረው ሀይቅ የሚይዘው የውሀ መጠን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ያሏት ሀይቆች ከሚይዙት ውሀ መጠን ይበልጣል የሚል መረጃ ተናግረዋል (ሊንክ: https://www.facebook.com/share/r/19wghsZ58y/)
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በዚህ ንግግራቸው ላይ “ኢትዮጵያ ውስጥ በተፈጥሮ ጣና፣ አብያታ፣ ሻላ፣ ላንጋኖ የሚባሉ ሁሉም ሀይቆች ተደምረው አሁን ያላቸው አቅም 70 ቢልየን ሜትር ኪዩብ ነው” ብለዋል።
አክለውም “ህዳሴ በሚሞላበት ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሀይቆቹን በሙሉ የሚበልጥ አቅም አለው ማለት ነው። አንድ ሰው ሰራሽ ግድብ በተፈጥሮ እስካሁን ኢትዮጵያ ያላትን ሀይቆች በሙሉ የሚበልጥ መጠን (size) የውሀ ክምችት ያለው ሆኖ ይታያል” ሲሉ ተደምጠዋል።
ኢትዮጵያ ቼክ በዚህ ንግግር ዙርያ ማጣራት ያደረገ ሲሆን ‘ንጋት’ የሚል ስያሜ የተሰጠው የህዳሴ ግድብ በሚይዘው የውሀ መጠን ከኢትዮጵያ ቀዳሚው ሰው ሰራሽ ሀይቅ ቢሆንም ሁሉም ሀይቆች ተደምረው ግን ከህዳሴ ግድብ ሀይቅ በላይ ይይዛሉ እንጂ አያንሱም።
የተለያዩ በመንግስት ጭምር የተለቀቁ መረጃዎች እንደሚያሳዩት እና ጠቅላይ ሚኒስትሩም እንዳሉት የህዳሴ ግድብ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ውሀ የመያዝ አቅም 74 ቢልዮን ኪዩቢክ ሜትር ገደማ ነው።
ይሁንና በኢትዮጵያ ያሉ ሁሉም ሀይቆች ውሀ የመያዝ አቅም ከ87 እስከ 97 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር እንደሆነ የተለያዩ ሳይንሳዊ ጥናቶች ያሳያሉ።
ለምሳሌ ‘International Journal of Applied Earth Observation and Geoinformation’ የተባለው የምርምር ተቋም
ዙ23ና ዲሽቃ በታጠቀ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ሰራዊት ታጅበው ከማክሰኝት ወደ አዘዞ ሲጓዙ በነበሩ የአገዛዙ ወታደራዊ አዛዦች ላይ ከባድ የደፈጣ ጥቃት መፈፀሙ ተሰማ!
ወታደራዊ አመራሮቹ ከፍተኛ ቁጥር ባለውና ከዙ23 ጀምሮ እስከ ዲሽቃ መሣሪያ በታጠቀ ሰራዊት ታጅበውም ከፋኖ ጥቃት ባለመትረፋቸው “የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም” በሚል የተተረቡ ሲሆን፡ በተጨማሪም የትኛውም ሰራዊትና ከባድ መሣሪያ ከፋኖ እንደማያድናቸው በግልፅ ያሳየ ነው ተብሏል።
በማዕከላዊ ጎንደር መነሻቸውን ከማክሰኝት ከተማ አድርገው ዙ23ና ዲሽቃ መሣሪያ በታጠቀ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ሰራዊት ታጅበው ወደ አዘዞ ወታደራዊ ካምፕ ሲጓዙ የነበሩ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች፡ ልዩ ስሙ ምንዝሮ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ ከባድ የሆነ ደፈጣ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው መረብ ሚዲያ ከአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለማረጋገጥ ችሏል።
ይሄንን የተመለከቱ የአከባቢው ነዋሪዎች፦
“ወይ መድፍ ብላሽ ወይ ድሮን ብላሽ፡
ወይ ሞርተር ብላሽ ወይ ታንክ ብላሽ፡
አፈር አስጋጠው ፋኖ በክላሽ”
በሚል ሲተርቡ አርፍደዋል።
ደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመው ዛሬ ጳጉሜ 03/2017 ዓ/ም ማርፈጃውን ሲሆን፡ እርምጃውን የወሰዱት በአፋብኃ በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ከ/ጦር ስር የሚገኙት “ፀያይሞቹ አናብስቶች”የሚል ቅፅል ስም የተሰጣቸው የሻለቃ ዋሴ ተኮላ ብርጌድ አባላት መሆናቸው ታውቋል።
በዚህ ደፈጣ ጥቃት፡ ታጅበው ሲጓዙ በነበሩ ወታደራዊ አዛዦች ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ በግልፅ ባይታወቅም፡ ነገር ግን አዛዦቹን አጅበው ከነበሩ ወታደሮች መካከል በርካቶች ሙትና ቁስለኛ መደረጋቸውን ዕዙ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል ባወጣው መረጃ ገልጿል።
ወታደራዊ አመራሮቹ ከፍተኛ
በአርማጭሆ ቀጠና ልዩ ስሙ ኩርቢ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ከባድ ተጋድሎ ሲደረግ መዋሉ ታውቋል።
የአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ደጃዝማች ኮር በሻለቃ እሸቴ አሸብር የሚመራው ደጀን አሸብር ክፍለጦር በአርማጭሆ ቀጠና ልዩ ስሙ ኩርቢ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ ዛሬ ጳጉሜ 03/2017 ዓ/ም ከንጋት ጀምሮ ከባድ ትንቅንቅ ሲያደርግ መዋሉን መረብ ሚዲያ ማረጋገጥ ችሏል።
በዚህ ውጊያ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የጠላት ብልፅግና ቡድን ወታደሮች የተገደሉ ሲሆን፡ እገዛ ለማድረግ ከወደ ሳንጃ ከተማ ተነስቶ ወደ ክርቢ ለመግባት ሲገሰግስ የነበረው ኃይልም የደፈጣ ጥቃት ተፈፅሞበት ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊና ቁሳዊ ውድመት አስተናግዶ ወደ መጣበት መፈርጠጡ ታውቋል።
ስለውጊያው ዝርዝር ውጤት የዕዙ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃ ሲያወጣ ጠብቀን ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።
ታሪካዊው ዲማማ ዲክላሬሽን በተፈፀመባት ታሪካዊቷ ዲማማ ቀበሌ ላይ በርካታ የአገዛዙ ወታደሮች መገደላቸው ተሰማ!
በምዕራብ አማራ ቀጠና ፋግታ ለኮማ ወረዳ ስር በምትገኘው ድማማ ቀበሌ ማዘዣ ጣቢያቸውን አድርገው በነበሩ የአገዛዙ ወታደርች ላይ ዛሬ ጳጉሜ 03/2017 ከንጋት ጀምሮ በተወሰደ እርምጃ በርካታ ወታደሮች ሲገደሉ በርካቶች መቁሰላቸውን መረብ ሚዲያ ከዕዙ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለማረጋገጥ ችሏል።
በአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና አፄ ቴዎድሮስ ዕዝ ጎጃም አገው ምድር ክ/ጦር ስር የሚገኙት የአሥር አለቃ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ እና ራስ ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ አባላት ዛሬ ከንጋት ጀምሮ በወሰዱት እርምጃ ዘጠኝ ወታደሮች ሲገደሉ ከ12 በላይ የሚሆኑት ደግሞ መቁሰላቸው ተረጋግጧል።
በጥቃቱ በተለይ በዲማማ ቀበሌ ልዩ ስሙ ማንጉዳት ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ የነበረው የጠላት ማዘዣ ካምፕ የወደመ ሲሆን በርካታ የጦር መሣሪያዎችም በፋኖ እጅ መግባታቸው ታውቋል።
የፋግታ ለኮማ ወረዳዋ ዲማማ ቀበሌ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ኃይል እና የአማራ ፋኖ ጎጃም ዕዝ ውህደት የፈፀሙባት፣ የጎጃም ፋኖ አንድነት ማሰሪያ ገመድ የተቋጠረበት ዲማማ ዲክላሬሽን የተፈፀመባት ታሪካዊት ቦታ ናት።
የጎጃም ፋኖ አንድነት ፅንስ ተፀንሶ በተወለደባት በዚች ታሪካዊት ስፍራ ሰፍረው በነበሩ የፀረ አማራው አገዛዝ ተላላኪ ወታደሮች ላይ እርምጃው የተወሰደው።
ዲማማ ለሚገኘው ኃይል እገዛ ለማድረግ መነሻቸውን ከእንጅባራ፣ ከአዲስ ቅዳም፣ ከጎመጅ ተራራ እና ከጊሳ ከተማ ያደረጉ ዙ23ና ሌሎች ከባባድ የጦር መሣሪያዎችን የታጠቁ የአገዛዙ ኃይሎች ካሰቡበት ሳይደርሱ ከወደ ፋኖ በተሰነዘረባቸው ጥቃት ብትንትናቸው ወጥቶ እርስ በእርሳቸው ሲታኮሱ መዋላቸው ታውቋል።
መንግስት የሚልከውን ነዳጅ በአካባቢው በሚመረት ወርቅ ቀይረው የሚቀበሉት ባለስልጣናት
“የኮፖሬሽኑ አመራሮች ኮርፖሬሽኑ የመንግስት ተቋም እንደመሆኑ መጠን ድርጊቱን ተከታትሎ ማስቆም ሲገባው ከዚህ ፍፁም ተቃራኒ በሆነ ሁኔታ በአካባቢው በሚከናወናው ነዳጅን በወርቅ የመቀየር ስራ ላይ ተጠምደዋል”
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/pppxe93h
የባህል ስብጥር ባለበት አገር culture apartheid ያዛልቃል? ( ያሬድ ኃይለማርያም)
+++

የአገዛዝ ሥርዓቱ አይን ባወጣ መንገድ እየፈጸመ ያለው Cultural Apartheid ከወዲሁ እልባት ሊበጅለት ካልቻለ በማህበረሰቦች መካከል ቁርሾን፣ መቃቃርና ጤናማ ያልሆነ ግንኙነት እንዲስፋፋ ያደርጋል። እንደ ኢትዮጵያ ባለ እጅግ የተሰባጠረ ባህልና የማንነት መገለጫዎች ያሉትን ሕዝብ የሚያስተዳድር መንግስት ሁሉንም በዓላት በእኩልነትና በአገር የባህል ቅርስነት ቆጥሮ እኩል ማስተናገድ ሲገባ የተወሰኑ ማህበረሰቦችንና በአላትን በውክቢያ፣ በክልከላ፣ በእስርና እንግልት ዜጎች ባህላቸውን በነጻነትና በደስታ ያለ ፍርሃት እንዳያከብሩ እየከለከለ ሹመኞች የእኔ የሚሉትን በዓል ደሞ ከፍተኛ የመንግስት በጀት መድቦና ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ መንግስታዊ ክብረ በዓል ማስመሰል የአፍሪካ መዲና በምትባል ከተማ ውስጥ Cultural Apartheid ማካሄድ ነው።

የአሸንዳ፣ አሸንድዬና ሻዳይ በዓልን ከአመታት በፊት በዪኔስኮ ጭምር እንዲመዘገብ እሰራለሁ ያለ መንግስት በአሉ በአደባባይም ሆነ በአዳራሾች እንዳይካሄድ ከልክሏል። ያም አልበቃ ብሎ በራሳቸው ገንዘብ ባዕሉን ማክበር የሚፈልጉ ወጣቶች በአዲስ አበባ በተለያዩ ሆቴሎች ተሰባስበው ሊያከብሩ ያደረጉት ጥረት ለዚሁ በተመደቡ ፖሊሶችና የደህንነት ሃይሎች እየተዋከቡና እየተገፈተሩ ተባረዋል። በወቅቱ የታሰሩም አስተባባሪዎች ነበሩ። ይህ አስነዋሪ ድርጊት በተፈጸመ በሳምንቱ ደግሞ በአዲስ አበባ በፊት ተከብሮ የማያውቅና ለሁለተኛ ጊዜ የተከበረውን ተመሳሳይ የኦሮሞ ወጣት ሴትች በአል መንግስት እጅግ ከፍተኛ በጀት መድቦ፣ ለወጣቶቹ አንድ አይነት ልብስ አልብሶ፣ ከየመጡበት የሚያመላልሱ አውቶቢሶችን መድቦ፣ አበል ከፍሎ፣ ደግሶ፣ አውራ ጎዳናዎችን ዘግቶና ከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ መድቦ በአሉን መንግስታዊ ቬስቲቫል በሚመስል መልኩ አክብሯል።
የኦሮሞ ወጣት ሴቶች በአል በዚህ ደረጃ መተዋወቁና መከበሩ እሰየው