Blog Archives
አዲስ አበባ-የኢትዮጵያ አየር መንግድ ለሩሲያ አዉሮፕላን ማከራየት አይፈልግም-ዋና ሥራ አስፈፃሚ
DW : የኢትዮጵያ አየር መንግግድ ለሩሲያ አየር መንገዶች አዉሮፕላን ለማከራየት ተስማምቷል የሚለዉን ዘገባ አየር መንገዱ አስተባበለ።ዩክሬንን በመዉረሯ ምክንያት ዩናይትድ ስቴትስ፣ የአዉሮጳ ሕብረትና ተባባሪዎቻቸዉ ተደጋጋሚ ማዕቀብ የጣሉባት የሩሲያ አየር መንገዶች አዉሮፕላንና የመለዋወጫ እጥረት ገጥሟቸዋል ይባላል።ችግሩን ለማቃለል ከኢትዮጵያና ከሌሎች ሐገራት አየር መንገዶች አዉሮፕላኖችን ለመከራየትና መለዋወጫዎችን ለመግዛት መስማማቷ ተዘግቧል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቡድን (ግሩፕ) ዋና ሥራ አሥፈፃሚ መስፍን ጣሰዉ ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ግን አየር መንገዳቸዉ አዉሮፕላኖቹን ለሩሲያ አየር መንገዶች ለማከራየት «ሐሳቡም የለዉም፤ ብንጠየቅም አናደርግዉም» ብለዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሩሲያ አዉሮፕላን የማያከራይበት ምክንያት
የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ሰለሞን ሙጬ እንደጠቀሰዉ አየር መንገዱ ለዉሳኔዉ ሁለት ምክንያቶች እንዳሉት ዋና ሥራ አሥፈፃሚዉ አስታዉቀዋል።«አንደኛ እኛ ራሳችን አዉሮፕላን ተጨማሪ የምንፈልግበት እንጂ ለሌላ አካል የምናከራይበት ወቅት አይደለም።» አቶ መስፍን እንደ ሁለተኛ ምክንያት የጠቀሱት አየር መንገዳቸዉ ከዩናይትድ ስቴትስ አዉሮፕላን አምራች ኩባንያ ቦይንግ አዉሮፕላን ሲገዛና በተለያዩ ሐገራት ሲበር የየሐገሩን ሕግ አክብሮ የሚሰራ መሆኑን ነዉ።«አሜሪካ ራሺያ ላይ ማዕቀብ እንደጣሉ እናዉቃለን፣ እኛ ደግሞ ከአሜሪካ ጋር በጣም ብዙ ቁርኝት አለን።ሥለዚሕ የአሜሪካን ሕግ አክብረን ነዉ (የምንሰራዉ)፣ ያን ሕግ ካላከበርን የሚከተለዉን ችግር እንረዳለን።»
የሩሲያና የምዕራባዉያን ጠብ ያስከተለዉ ጣጣ
ኢትዮጵያ በተለይ በትምሕርት፣በሥልጠናና በጦር መሳሪያ ግዢ ከሩሲያ ጋር የረጅም ጊዜ ግንኙነት አላት።የሩሲያና የምዕራባዉያን መንግሥታት ጠብ ከናረ ወዲሕ ደግሞ BRICS በሚል ምሕፃረ ቃል በሚጠራዉ ምጣኔ ሐብታዊ ማሕበር አማካይነት ከሩሲያ ጋር ያላት
በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ አርሲ ዞን ኮኮሳ እና ነንሰቦ ወረዳዎችና የሲዳማ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች በተቀሰቀሰ የድንበር ግጭት፣ ሁለት ሰላማዊ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉንና በ7ቱ ላይ አካላዊ ጉዳት መድረሱን ቢቢሲ ዘግቧል።
ጥቃቱን ያደረሱት ከሲዳማው ጉራ ወረዳ የተሻገሩ ታጣቂዎች መኾናቸውንና ጥቃቱን ተከትሎ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ዜና ምንጩ ጠቅሷል።
ታጣቂዎቹ ነዋሪዎቹን ባፈናቀሉበት ቦታ ላይ ለመስፈር አስበው እንደነበርም ምንጮች ተናግረዋል ተብሏል።
ካሁን ቀደም ከምዕራብ አርሲ ዞን ተሻግረው በአካባቢው ሠፍረው የነበሩ ሰዎች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲመለሱ ተደርጎ እንደነበርም ተገልጧል።
በተመድ የኤርትራ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ሶፊያ ተስፋማርያም፣ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በቅርቡ ስለ ኢትዮጵያና ኤርትራ ትብብርና ውህደት ያቀረቡትን ፍኖተ ካርታ “ቅንነት የጎደለው” እና “ኤርትራን ለኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎት ተገዢ ለማድረግ ያለመ ነው” በማለት አጣጥለውታል። አምባሳደር ሶፊያ፣ የዲና ሃተታ “በኤርትራ ትክሻ ላይ ኢትዮጵያ በውስጣዊና ቀጠናዊ ደረጃ የተበላሸባትን ምስል ለማደስ የተቀነባበረ ነው” ብለዋል። በሁለት ሉዓላዊ አገሮች መካከል ቀጠናዊ ትብብር ወይም ውህደት እንዲፈጠር የሚቀርብ ሃሳብ የቱንም ያህል ማራኪ ቢሆን፣ በመጀመሪያ መነሻውን “ታሪካዊ እውነታ” ላይ ማድረግ ይገባዋል- ብለዋል አምባሳደሯ። ድንበሮችና ሉዓላዊነት የማይገሠሱ መሆናቸው በማያሻማ ሁኔታ ሳይረጋገጥ፣ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ቀጠናዊ ትብብር ለመመስረት የምትችልበት ሁኔታ እንደማይኖርም አምባሳደር ሶፊያ ገልጸዋል።

አብይና ሹመኞቹን ማመን ቀብሮ ነው ! …… Ethiopian Human Rights Commission ኢሰመኮ ” በዚህ ኮሚሽን ተገዶ የሚኖር፣ ተገፍቶ የሚወጣ ኮሚሽነር መኖር የለበትም እኔን ጨምሮ ” – ይህንን ያለው ትላንት የሕወሓት አሽከርና ተላላኪ የነበረው ዛሬ ለኦሕዴድ እና ለአብይ አሕመድ በአሽከርነት የሚላላከው ብርሃኑ አዴሎ ነው ። …….. ተጣርቶ በኮሚሽኑ ሰራተኞች ከቀረበው 280 ገፅ ገደማ ሪፖርት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቀናንሶ በወዲ አዴሎ እንዲቀርብ የተደረገው 152 ገፅ ነው። ……. በተላላኪነት የተሾመው ብርሃኑ አዴሎ የተሰጠውን ተልዕኮ ይዞ ሲሾም በዋናነት ስራው ኮሚሽነሮቹ ስራ እንዲለቁ እየጠራ የእጅ አዙር ጫና ማድረግ ነበር ……. ሪፖርቶችን ማጣጣል እና አቅጣጫ ማስቀየር ዋና ግቡ ሆኖ አድርጎታል አሁንም እያደረገው ነው…. ለዚህ ደግሞ በቂ ማስረጃ አለ ….. የነጮች ተላላኪ በሚል ሽፋን በኮሚሽኑ ሰራተኞች ላይ የሚደረገው የደሕንነት መስሪያ ቤቱ ማስፈራሪያ እና ከኮሚሽኑ እንዲለቁ የሚደረግ ጫና አሁንም እንደቀጠለ ማስረጃዎች አሉ……. የአብይ አገዛዝ በሕዝብ ላይ የሚያደርሰውን ሰቆቃ እና ስቃይ ለመደበቅ ኮሚሽኑን በብልፅግና አማሳኞች እና ጀሌዎች ለመሙላት የሚደረገው ስራ እንደቀጠለ ነው። ……. ሙሉ ሪፖርቱ ይፋ ካልተደረገ በስተቀር የ152 ገፁ ሪፖርት ተቀባይነት የለውም። #MinilikSalsawi
” የቢዝነስ እና የቱሪስት ቪዛ አመልካቾች እስከ 15 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በማስያዣነት ይጠየቃሉ ” – አሜሪካ
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ወደ አገሪቱ ለመግባት የቢዝነስ እና የቱሪስት ቪዛ አመልካቾች እስከ 15 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በማስያዣነት ሊጠየቁ እንደሚችሉ አስታውቋል።
ይህ በሁለት ሳምንት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የሙከራ ፕሮግራም ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የሚቆዩ ጎብኚዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ያወጣው ይህ ማስታወቂያ በርካታ ሰዎች ወደ አገሪቱ ለመግባት የሚያደርጉትን ሂደት አስቸጋሪ ያደርግባቸዋል ተብሏል።
እንደ የፌደራል መንግሥቱ የምዝገባ ማስታወቂያ ከሆነ ይህ አሠራር በቀጣዮቹ 12 ወራት ውስጥ በሙከራነት በተወሰኑ አገራት ላይ ተግባራዊ ይሆናል።
የሙከራ መርሃ ግብሩ አሜሪካ ውስጥ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ዜጎች ባሏቸው አገራት እና የአገር ውስጥ ሰነዶች ላይ የላላ ቁጥጥር በሚያደርጉ አገራት ላይ ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል ተብሏል።
የእነዚህ አገራት ዜጎች ለቪዛ ሲያመለክቱ 5,000, 10,000 ወይም 15,000 ዶላሮችን በማስያዣነት እንዲያቀርቡ ሊጠየቁ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ሰነድ አልባ ስደተኞችን ከአገር ማስወጣት እንዲሁም የድንበር ቁጥጥሩን ለማጠናከር በጀት ከፍ የማድረግ እና ወደ አገሪቱ በሕገወጥ የገቡ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር የማዋል እርምጃዎችን ሲወስዱ ቆይተዋል።
በሰኔ ወር ከ19 አገራት ወደ አሜሪካ ለመግባት የሚያመለክቱ ግለሰቦች ላይ ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በተያያዙ ምክንያቶች የጉዞ እገዳ ጥለዋል።
በትራምፕ የስደተኞች ፖሊሲ ምክንያት የተወሰኑ ጎብኚዎች ወደ አሜሪካ የሚያደርጉትን ጉብኝት እየሰረዙ መሆኑ ይሰማል።
ከነሐሴ 20
” ወንድሜ ተርፏል መነሻው ከራያ ነው ሳምንት አልፏል ከቤት ከወጣ እና ከእሱ ጋር የነበሩት አብዛኛዎቹ ሞተዋል ” – ወንድም
🕯” ራያ አላማጣ አካባቢ ለሟች ቤተሰቦች መርዶ ተነግሯል ! ”
154 ኢትዮጵያውያንን ጭና መዳረሻዋን ወደ ሳኡዲ አረቢያ ያደረገች ጀልባ በመስጠሟ እስካሁን የ68 ኢትዮጵያውያን ህይወት አልፎ አስክሬናቸው ወዳድቆ መገኘቱ 12 ሰዎች በህይወት መትረፋቸው ሌሎቹ ግን የገቡበት እንደማይታወቅ አስክሬናቸውም እየተፈለገ እንደሆነ መነገሩ ይታወሳል።
በአሰቃቂው አደጋ ህይወታቸው ያለፉ ኢትዮጵያዊያን ወንድም እና እህቶቻችንን አስክሬን የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተለቀቁ ይገኛል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአደጋው ወንድሙ በህይወት ከተረፈለት እና ወንድሙን በስልክ ማነጋገር የቻለን ሰው ከሳኡዲ አረቢያ አነጋግሯል።
ምን አለ ?
” እኔ ሳኡዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ ነው የምኖረው ወንድሜ ተነስቻለሁ ብሎ ከነገረኝ ሳምንት ይሞላዋል።
ከእሱ ጋር የአንድ አካባቢ ልጆች የሆኑ ጎረቤቶቻችን አብረው ተነስተዋል ከራያ መሆኒ አካባቢ።
ከእኛ ሰፈር ብቻ አራት ልጆች ሆነው ነው የተነሱት ከአላማጣ ደግሞ 3 ልጆች ተጨምረው በአጠቃላይ በአንድ ደላላ ሰባት ሆነው ወጥተዋል።
እንደ እድል ሆኖ የእኔ ወንድም እና አንድ ልጅ ተረፉ ከሞቱት ውስጥ ሁለቱ የአጎት ልጆች ናቸው ትላንት ማታ መርዶ ተነግሯቸዋል።
አብዛኞቹ የራያ ልጆች ናቸው በአደጋው የሞቱት።
ራያ አላማጣ አካባቢ ለሟች ቤተሰቦች መርዶ ተነግሯል።
ወንድሜ ሊደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው ጀልባዋ መገልበጧን ነግሮኛል እጅግ ተደናግጦ ስለነበር ብዙ ነገር ሊነግረኝ አልቻለም።
በህገ ወጥ ጉዞ ላይ ጀልባ የሚያሽከረክሩ ደላላዎች የባህር ጠባቂዎችን ሲያዩ ይደናበራሉ ምናልባትም ይህ አደጋም
ፍልሰታ “እኛም ማየት አለብን” በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ
በየዓመቱ ከነሀሴ 1 እስከ 15 ድረስ የምትጾመው ፍልሰታን በዘልማድ ነው የምንጾማት ወይንስ ሚስጢሩን ተረድተነውና አውቀነው ነው ሲሉ ቀሲስ አስተርአየ ይጠይቃሉ። “የፍልሰታ ጾም ትንሿ የጤፍ እንደ ጤፏ ቅንጣት እየወደቅን እየተነሳን አድገን፥ እኛነታችንን ለሚቀጥለው ዘሮቻችን ለማቀበል በዚህ ምድር ላይ መዘራታችንን የምንመረምርበትየጥሞና ወቅታችን ናት። መንፈሳችን ከሥጋዊ ስሜትና ፍላጎት ርቆ ያጣነውን ፈልጎ ለማግኘት የሚሰማራበት ወቅት ናት”። ቀሲስ አስተርአየ በጽሁፋቸው አፅንዖት በመስጠት በብሔራዊና በመንፈሳዊ ስሜታቸው የተመኙትን አይተው ያለፉ ኢትዮጵያዊያን አርበኛ በላይ ዘለቀ፣ አቡነ ቴዎፍሎስንና ጋሼ አበራ በቀለን ከፍልሰታ ጾም መንፈስ ጋር ያላቸውን መስተጋብር በዝርዝር አስረድተዋል።
በተለይ ምዕመናንና ቤተ ክርስቲያንን በአውሬ አላስበላም ብለው እራሳቸውን መስዋዕት ስላደረጉላት አቡነ ቴዎፍሎስ ስናነሳ በአሁን ጊዜ ፓትርያርኩ፣ ሲኖዶሱና ጳጳሳቱ በጎሰኝነት፣ በፖለቲካ፣ በስልጣን፣ በገንዘብ፣ በዝሙትና በተለያዩ ህጸጾች የተጨማለቁ መሆናቸውን ስንመለከት ምንኛ ያንገበግባል። ቤተክርስቲያኒቷና በአጠቃላይም አገሪቷ የወረዱበትን አዘቅትና መከራ እንዲሁም በአማራነታቸውና በተዋህዶ ዕምነት ተከታይነታቸው ብቻ በየዕለቱ ስለሚጨፈጨፉትና ሞታቸው ከዝንብ ሞት እኩል ስለተቆጠረባቸው ምዕመናን ስናጤን ጊዜው የምፅዓት ነው ወይ ያሰኛል። በሐዋርያት ስራ 20፡28 በግልፅና በማያሻማ ሁኔታ እንደተጻፈልን “በገዛ ገንዘቡ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከሄድኩ በኋላ ለመንጋው የማራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሱ እኔ አውቃለሁ” የሚለው የእግዚአብሔር ቃል በአሁን ጊዜ እንደተፈጸመብን አያጠራጥርም። በአቡነ ማቲያስ የሚመራው ሲኖዶስና
714 ሚልዮን ዛፍ በአንድ ቀን… ቁጥሮቹ ሲፈተሹ! ( ኤሊያስ መሰረት እንደፃፈው )
በመጀመርያ፣ በቅርቡ በሌላ አንድ ፅሁፌ ላይም እንዳነሳሁት ሰባም ይሁን ሰባት መቶ ሚልዮን ችግኝ መትከል በጎ ስራ ነው፣ መንግስት ከሚያከናውናቸው ተግባራት መሀል የማደንቀው አንዱ ነው።
ይሁንና እንደ አንድ ተራ ዜጋም ሆነ የሚድያ ባለሙያ ቁጥሮች ላይ ፍተሻ ማድረግ ይጠቅማል ብዬ አስባለሁ፣ ቁጥሮቹ ዞረው ዞረው የደን ፖሊሲ የሚዘጋጅባቸው ግብዐቶች ስለሆኑ።
1ኛ: በዛፍ ተከላው ላይ 30 ሚልዮን ገደማ ኢትዮጵያዊ (ከኢትዮጵያ ህዝብ 25 ፐርሰንት ገደማው) ተሳትፏል ተብሏል። በዚህ ዙርያ ያነጋገርኳቸው እና በፕሮግራሙ ዙርያ የሰሩ ሰዎች ይህ ፍፁም ሊሆን እንደማይችል፣ በተለይ ዘንድሮ የመንግስት ሰራተኞች እና በአንዳንድ ስፍራዎች አርሶ አደሮችን ማሳተፍ ተቻለ እንጂ ከቀድሞ አመታት ያነሰ የሰው ቁጥር እንደነበር ተናግረዋል። በእለቱ ህፃናትን፣ አዛውንቶችን፣ ታማሚዎችን ጨምሮ ከአራት ኢትዮጵያዊ አንዱ ችግኝ ተክሏል? የሚለውን እጅግ ገራሚ ቀጥር እንያዝ
2ኛ: በእለቱ 714 ሚልዮን ችግኝ ተተክሏል የተባለው አንድ ሰው 24 ችግኝ ሲተክል ነበር ተብሎ ነበር። በድጋሚ በዚህ ዙርያ ያሉኝ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ብዙ ቦታ የችግኝ እጥረት እንደነበር፣ ምናልባት አንድ ሰው በአማካኝ በዛ ከተባለ አምስት እና ስድስት ሲተክል እንደነበር ይጠቁማሉ። ገፋ እናርገው እና 10 ችግኝ ተከለ ብንል 714 ሚልዮን ችግኝ ለመትከል 71.4 ሚልዮን ኢትዮጵያዊ (ማለትም ከኢትዮጵያ ህዝብ ከግማሽ በላይ) ችግኝ ሲተክል ነበር ማለት ነው። ይህንንም እንያዝ።
3ኛ: የግብርና ሚኒስቴር ዳታዎች እንደሚያሳዩት አንድ ችግኝ ለመትከል 4*4 የሆነ መሬት ጥቅም ላይ ይውላል፣ 16 ሜትር
በአስገዳጅ ሁኔታዎች ከሥራ ኃላፊነት መልቀቄን አስመልከቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ!
እኔ ያሬድ ኃይለማርያም ከተመሰረተ አራት አመት ተኩል ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከልን (Ethiopian Human Rights Defenders Center) በዋና ዳይሬከተርነት ሳገለግል ቆይቼ ባጋጠሙኝ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከአገስት 1 ቀን 2025 (ሐምሌ 25 2017) ጀምሮ ከሃላፊነቴ እና ከድርጅቱ ለመልቀቅ መገደዴን ለማሳወቅ እወዳለሁ፡፡
ይህ ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲቋቋምና በሌሎች አፍሪካ አገሮች ከሚገኙ አቻ ድርጅቶች ጎን ቆሞ ለሰብአዊ መብት ተሟጋቶች መብት መከበርና አቅማቸውንም ለማጎልበት በርካታ ሥራዎችን እንዲሰራ ምሪት በመስጠትና በአጭር ጊዜም ውስጥ ድርጅቱ በአገር ውስጥና ከአገር ውጭም እውቅና እና ተቀባይነት እንዲያገኝ ከፍተኛ ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ፡፡
ድርጅቱ ከተመሰረተ አጭር እድሜ ያለው ቢሆንም ሲያከናውን የቆያቸው ሥራዎች እና አገሪቱ ውስጥ ለሚፈጽሙ የመብት ጥሰቶች፤ በተለይም በጋዜጠኞች፣ በሲቪል ማህበረሰብ አባላት እና በመብት ተሟጋቾ ላይ የሚፈጸሙ የመበት ጥሰቶችን በማጋለጥና መብታቸው እንዲከበርበአደባባይ በመሟገት ግንባር ቀደም ተቋም ሆኖ እንዲቀጥል ከድርጅቱ ጠንካራ ሠራተኞችና የቦርድ አባላት ጋርበመሆን ቁልፍ ሚና ስጫወት ቆይቻለሁ፡፡
ይሁንና ከአንድ አመት ወዲህ በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ በሚገኙ ሚዲያዎች ላይ እየቀረብኩ አገሪቱ ውስጥ ስላለው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የምሰጠቸው መገልጫዎችና ማብራሪያዎች፣ በማህበረ ድህረ ገጾች ላይ ዜጎችን ስለ መብታቸው እንዲያውቁና በአገሪቱ ውስጥ ስላለው የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በማስመልከት የማካፍላቸው ሃሳቦችና የምሰነዝራቸው የሰሉ ትችቶች በአገዛዝ ሥርአቱ ዘንድ በጥሩ ሁኔታ እየታ ባለመምጣታቸው የተነሳ በተለያዩ አቅጣጫዎች የተለያዩ አይነት ጫናዎችን ሳስተናግድ ቆይቻለሁ፡፡
የተለያዩ ዛቻዎች፣ ማስፈራሪያዎችና ትንኮሳዎችን በጸጥታ አካላት በኩል ሲፈጸሙ
አፍራሽ ይዞታ ያላቸው የባለሥልጣናት_ንግግሮች_ሊገሩ_ይገባል!
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከመኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ እናት ፓርቲ እና ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ)
ከባለሥልጣናት አንደበት የሚወጡ የማይጠበቁ ቃላት አንድ ጊዜ ሲሆን የአፍ ወለምታ ተብሎ ሊወሰድ ይችላል። በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተለያዩ ጊዜያት የሚነገሩ ተመሳሳይ ንግግሮች ሥርዓታዊ የአመለካከት አቅጣጫን የሚያመላክቱ መሆናቸው ግን ጥርጥር የለውም። በዚህ ረገድ የሰሜኑ ጦርነት በሚካሄድበት ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ሕወሓትና የትግራይ ክልልን አስመልክቶ “በሕዝብ አገር መሆን እንፈልጋለን ከኢትዮጵያ ተገንጥለን ካሉ እኮ ራሳቸው የቀረጹት ሕገ መንግሥት ላይ የተቀመጠ እኮ አንቀጽ አለ። በዚያ መሠረት መሄድ ነው!” ብለው መናገራቸው የአንድ ወቅት መነጋገሪያ የነበረ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም በቅርቡ ባደረጉት ንግግር “ለመገንጠል ደግሞ ጉልበት አያስፈልግም። አሠራር ሕገ መንግስት አለ። በዚያ ሂዱ።” ሲሉ ተደምጠዋል።
እነዚኽ በይፋ የተነገሩትን ለአብነት ጠቀስን እንጂ ከቅርብ ጊዜያት ወዲኽ ለብልጽግና ሹማምንት ቅርበት የነበራቸው ግለሰቦች እያወጧቸው ያሉና ማስተባበያም ማስተማመኛም ያልተሰጠባቸው ተመሳሳይ ይዘት ያላቸው የከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ንግግሮች ጆሮን ጭው የሚያደርጉ ናቸው። የኾነው ኾኖ በይፋም ከመጋረጃ ጀርባም የተነገሩና የተባሉ አደገኛ ንግግሮች በስሕተት የተነገሩ እንዳልኾኑ ከድግግሞሹና ከተናገሩት ባልሥልጣናት ደረጃ ማየት የሚቻል ሲኾን ይኽም ሥርዓታዊ አቋም ነው ወይ?! ለማለት ያስገድዳል፡፡
በሌላ በኩል በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አገር የምትገኝበት መጠነ ሰፊ የርስ በርስ ጦርነት አልበቃ ብሎ ባለፈው ያደናቀፈንና ሚሊዮን ዜጎቻችንን ጭዳ ያደረገው የጦርነት እንቅፋት ዳግም ሊመታን ከቋፍ መድረሱን እያየን ነው፤ ከላይ የተጠቀሱ ንግግሮችም
ከፍተኛ የክልል ባለስልጣናት የሚሳተፉበት እና አንድ ሊትር ናፍጣ ማደያ ውስጥ እስከ 280 ብር የሚሸጥበት የጋምቤላ ክልል ( የምርመራ ዘገባ )
“… ደላሎች ይመጡና ነዳጅ አለ፣ ሌሊት ይቀዳልሃል በ280 ብር ትገዛለህ ወይ? ትባላለህ። እሺ ብለህ ከተደራደርክ በኋላ ገንዘቡን ወደ ባለማደያ አካውንት ውስጥ እንድታስገባ ካደረጉህ በኋላ ሌሊት ይቀዳልሃል”
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/280
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ነባራዊ ኹኔታ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማከናወን “ተስፋ ሰጪ ነገሮች የማይታዩበት” ነው ሲል የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓረቲዎቸ ስብስብ – ኮክሰ ሥጋቱን ገለፀ። በቅድሚያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “የአሰራርና ተቋማዊ” ያላቸው ችግሮች እንዲፈቱ የጠየቀው ኮከስ በተቋሙ “እውነተኛ ሪፎርም ከሌለ ተዓማኒ፣ አካታች፣ ነጻና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሊኖር አይቸልም” ብሏል። በዋናነት 8 የፓለቲካ ድርጅቶች ንቁ ተሳትፎ ያደርጉበታል የተባለው ኮከስ ስለ ምርጫ ከመታሰቡ በፊት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ጦርነት እና ግጭቶች እንዲቆሙ፣ ሰላም እንዲሰፍን እና በተለይ ከኤርትራ ጋር እየተስተዋለ ያለው ውጥረት እንዲፈታ ጠይቋል።
የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓረቲዎቸ ስብስብ – ኮክሰ ዛሬ ሐምሌ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ግጭጦች እንዲቆሙ ደጋግሞ ቢጠይቅም አሁንም ለሀገር ደኅንነት ሥጋት ሆነው መቀጠላቸውን ገልጿል። የዚህ ስብስብ አባል ፓርቲ የሆነው የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል ሞጊሶ “ጦርነት ይብቃ” የሚለው አሁንም ዋና የጥሪያቸው ጭብጥ መሆኑን ገልፀዋል።
“ዘላቂ ሠላም እንዲመጣ ከተፈለገ ጦርነት መቆም አለበት። ይሄ ነገር እየሰፋ በሄደ ቁጥር ይቺ ሀገር እያየን ልትፈርስ ትችላለች”።
ኮከስ ቀጣዩን ምርጫ ለማከናወን አስቻይ ኹኔታ የለም ብሏል
ኮከስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከጅምሩ “የነጻነት እና የገለልተኝነት” ጥያቄዎች እንደሚነሱበት በመጥቀስ አሁንም አሉበት ያላቸው “የአሰራርና ተቋማዊ ችግሮች” እስካልተፈቱ ድረስ “ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም” ብሏል፡፡ “እውነተኛ ሪፎርም ከሌለ ተዓማኒ፣ አካታች፣ነጻና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ” ሊኖር እንደማይችልም አቋሙን ይፋ አድርጓል።
“ሕዝብ ሰላማዊ ባልሆነበት ኹኔታ ዲሞክራሲን አይደለም የሚመርጠው። ሕዝብ
” ተፈናቃዮቹ ቤተክርስቲያን እና ሆቴል በር ላይ እየለመኑ ነው ” – የተፈናቃይ ተወካይ
➡️ ” እነሱ በሚሉት ልክ አይደለም የተቋረጠባቸው ” – የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት
በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር በደባርቅ ከተማ ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚገኙ የትግራይ ተፈናቃዮች የእርዳታ እህል ካገኙ ከ8 ወር በላይ እንደሆናቸው ተናግረዋል።
በማኅበር የተደራጅተው ችግራቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩት ተፈናቃዮቹ የሚበሉት ከማጣታቸው የተነሳ ለልመና መውጣታቸውን የመሀበሩ ጸሐፊ መርጌታ ጠበቃው ወልደ ገብርኤል ተናግረዋል።
መርጌታ ጠበቃው እንደሚሉት ወትሮም አልፎ አልፎ ይሰጥ የነበረው እርዳታ ከቆመ 8 ወር ሆኖታል።
ከሰሜኑ የኢትዮጵያው ጦርነት ጋር በተያያዘ ተፈናቅለው በደባርቅ ከተማ መጀመሪያ በመጠለያ ጣቢያ በኃላም ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው መቆየታቸውን የሚናገሩት መርጌታ ጠበቃው ካለፈው ህዳር ወር ጀምሮ እርዳታ እንደተቋረጠባቸው ተናግረዋል።
ምክንያቱ ደግሞ የአካባቢው ባለስልጣናት የወረዳና የከተማ ብለው ተፈናቃዮችን መከፋፈላቸው ነው ይላሉ።
” በከተማ ነዋሪነት የተመዘገቡ ተፈናቃዮች በየጊዜው እርዳታ ያገኛሉ በወረዳ ተፈናቃይነት የተመዘገቡት ግን እያገኙ አይደለም ሁለቱም በአንድ ሰፈር የሚኖሩ ናቸው ” ብለዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የሰሜን ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰላም ይሁን ሙላትን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገረ ሲሆን ” ተፈናቃዮቹ ለ8 ወራት ያህል እርዳታ ተቋረጠብን የሚሉት ስህተት ነው ” ባይ ናቸው።
ከህዳር ወር በኃላ ወሩን በትክክል ባያስታውሱትም ለእያንዳንዱ ተፈናቃይ የሁለት ወር እርዳታ እንደተሰጣቸው አስረድተዋል።
ከዛም አመልድ ኢትዮጵያ 4 ሚልየን ብር በመመደብ ለ200 በጣም ችግር ውስጥ ላሉና ለአቅመ ደካማ ተፈናቃዮች
በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል አዋሳኝ የሚገኙ 14 ወረዳዎች ወደ ሶማሌ ክልል እንዲካለሉ የተወሰነውን ውሳኔ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና እና ቦረና ዞኖች ሕዝባዊ ተቃዉሞ መቀስቀሱን ዋዜማ ሰምታለች።
ይህ ውሳኔ የተወሰነው የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደው ዓመታዊ ጉባኤው ላይ መሆኑን ያስረዱት ምንጮች፣ ይህንኑ ተከትሎ በቅርቡ እንደ አዲስ በተዋቀረው የምስራቅ ቦረና ዞን መቀመጫ ነጌሌ ቦረና ከተማ እና የቦረና ዞን መቀመጫ በሆነችው ያቤሎ ከተማ፣ እንዲሁም በሌሎች ወረዳዎች ከዛሬ ማለዳ አንስቶ የተቃውሞ ሰልፎች እየተካሄዱ መሆኑን ዋዜማ የደረሳት መረጃ ያመልክታል።
ወደ ሶማሌ ክልል እንዲካለሉ በምክር ቤቱ የተወሰኑት 14ቱ ወረዳዎች በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ በሚገኙት ቦረና፣ ባሌ፣ ሐረርጌ እንዲሁም ከድሬደዋ አካባቢዎች ወደ ሶማሌ ክልል እንዲካለሉ ውሳኔ የተሰጠባቸው እንደሆኑ ምንጮች ነግረውናል።
ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 21፣ 2017 ዓ፣ም እኩለ ቀን ድረስ በፌዴራልም ሆነ በኦሮሚያ ክልል መንግሥት በኩል በጉዳዩ ላይ የተባለ ነገር የለም። [ዋዜማ]
የኬንያው ፕረዚዳንት 14 ሚሊየን የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ሰዓት አድርገው መታየታቸው ግርምትን ፈጥሯል።
ፕሬዚዳንት ሩቶ ሮሌክስ ደይቶና የተባለውን ቅንጡ ሰዓት አድርገው የታዩት በአፍሪካ ከሚገኙት ትላልቅ ፓርኮች መካከል አንዱ በሆነው በማሳይ ማራ ብሔራዊ ፓርክ ጉብኝት ባረጉበት ወቅት ነው።
ሮሌክስ ደይቶና ለገበያ የቀረበው በፈረንጆቹ 1963 ሲሆን የተሰራው በዋነኝነት ለመኪና ውድድር ሹፌሮች ነው።
ሰዓቱ እስከ 72 ሰዓት ኃይል ማቆየት እንደሚችል ሲነገር እስከ 400 ማይልስ በሰዓት ድረስ አማካይ ፍጥነትንም ያሰላል ተብሏል።
በ2024 ዊሊያም ሩቶ እንደዚሁ 425,000 የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ቀበቶ አድርገው መታየታቸው የሚታወስ ነው።
በቅርቡ ዊሊያም ሩቶ 8000 ሰዎችን መያዝ የሚችል ቤተክርስቲያን በቤተመንግስታቸው ውስጥ ለመገንባት ማቀዳቸውን ተናግረው የነበረ ሲሆን አጠቃላይ የግንባታ ወጪውም 1.2 ቢሊየን የኬንያ ሽልንግ ተገምቷል።
ፕሬዚዳንቱ ቤተክርስቲያኑን ለመገንባት ከህዝብ የሚሰበሰብ ገንዘብ እንደሌለና በራሳቸው ወጪ እንደሚገነቡት ቢናገሩም ከትችት አልተረፉም።
የኬንያ ባለስልጣናት ቅንጦት በማዘውተር ሲወቀሱ በቅርቡ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 900,000 የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ሰዓት፣ 80,000 ሽልንግ የሚያወጣ ጫማ እና የ20,000 ሽልንግ ከረቫት አለኝ ብለው መናገራቸው ቁጣን ቀስቅሶ ነበር።
በአፍሪካ መሪዎች የሚኖሩት ኑሮ ከህዝቡ በተቃራኒ እንደሆነና የቅንጦት ኑሮን የሚያዘወትሩ እንደሆነ በተደጋጋሚ የሚነገር ቢሆንም ባለስልጣናት አሁንም ቢሆን የቅንጦት ኑሮን ከማዘውተር አልቦዘኑም።
Source: The Kenya Times, Tuko News, Standard Media
ሳይንቲስቶች ሰዎች ህፃን አያሉ ወደፊት ከመጠን በላይ ይወፍራሉ ወይ የሚለውን መለየት የሚያስችል ሞዴል መስራታቸው ተነገረ።
የኮፐንሃገን እና ብሪስቶል ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ከ5 ሚሊየን ሰዎች በተሰበሰበ መረጃ በተሰራ ትንተና ሰዎች ከመጠን በላይ ሊወፍሩ ይችላሉ የሚለውን ገና በልጅነታቸው መገመት እንደሚቻል እና ይህም ውፍረቱን ለማስቀረት በጊዜ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚረዳ ገልፀዋል።
በ2035 ከአለም ህዝብ ውስጥ ግማሽ ያህሉ ከመጠን በላይ ይወፍራል ተብሎ ሲጠበቅ ሳይንቲስቶቹ የሰሩት ሞዴል ህፃናት እና ወጣቶች ከመጠን በላይ ለመወፈር ዘራቸው ያለውን ተጋላጭነት በአግባቡ በመገመት መፍትሄ እንዲኖር ያደርጋል ተብሏል።
አዲሱ ሞዴልም በሰዎች ላይ የሚኖርን 17 በመቶ የሰውነት መጠን መለኪያ(BMI) ልዩነት ያስረዳል ተብሏል።
ከመጠን በላይ ውፍረት በአሁኑ ጊዜ አሳሳቢ የማህበረሰብ የጤና ችግር ሲሆን ከአካባቢ፣ አኗኗር እና ከዘር ጋር በተያያዘ ይመጣል።
በተጨማሪ ሳይንቲስቶቹ ከዘር ጋር በተያያዘ ከመጠን በላይ የወፈሩ ሰዎች ክትትል አድርገው እንዲቀንሱ ሲደረግ በቶሎ እንደሚቀንሱ እንደዚሁም ሲያቆሙ በቶሎ ክብደታቸው እንደሚጨምር ገልፀዋል።
በአለም አቀፍ ደረጃ ከመጠን በላይ ውፍረት አሳሳቢ ደረጃ ሲደርስ ከመጠን በላይ የሚወፍሩ ጎልማሶች ቁጥር በ2010 ከነበረበት 524 ሚሊየን በ2030 1.13 ቢሊየን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
በተጨማሪ በ2050 ነገሮች ካልተቀየሩ 3.8 ቢሊየን ጎልማሶች እና 746 ሚሊየን ህፃናት ከመጠን በላይ ውፍረት ያጋጥማቸዋል ተብሎ ተገምቷል።
በ2021 በአሜሪካ 42 በመቶ ወንዶች እና 46 በመቶ ሴቶች ከመጠን በላይ ወፍረው እንደነበር ተዘግቧል።
ከሰሃራ በታች ባሉ ሃገራት ከመጠን በላይ የሚወፍሩ ሰዎች ቁጥር በ2050 በ250 በመቶ በመጨመር 522 ሚሊየን እንደሚደርስ ይጠበቃል።
ከመጠን በላይ
አልሸባብ ከሞቃዲሾ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ያለችን ከተማ ዳግም መያዙን ገለፀ።
አልሸባብ ባለፉት ቀናት ከሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለችው ሳቢድ ከተማ ከባድ ውጊያ ማድረጉን ገልፆ በኡጋንዳ እና ሶማሊያ ጦር ላይ ከፍተኛ ጥቃት ሰንዝሮ ከተማዋን ዳግም መቆጣጠሩን ገልጿል።
በተጨማሪ አልሸባብ በከተማዋ ያለን የሶማሊያ ጦር እና የኡጋንዳ ሰላም አስከባሪ ጦር ማዘዣዎችን እንደዚሁም መኪኖችን እና መሳሪያዎችን መያዙን ገልጿል።
የሳቢድ ከተማን ከወር በፊት የሶማሊያና የኡጋንዳ ጦር ከአልሸባብ ነፃ አውጥተውት የነበረ ሲሆን ከተማዋ በአልሸባብ እጅ ዳግም በመወደቋ ላይ የሶማሊያ ጦርም ሆኑ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ያሉት ነገር የለም።
አልሸባብ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ኃይሉን እያጠናከረ በርካታ ከተሞችን መያዝ ሲጀምር በሶማሊያ ያለው የህብረቱ ተልዕኮ ከበጀት ድጋፍ ጋር በተገናኘ የሚፈልገውን ያህል እየተንቀሳቀሰ እንዳልሆነ ሲዘገብ መቆየቱ ይታወሳል።
Source: Somali Guardian
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ለግብፅ የ4.7 ቢሊየን ዶላር የመሳሪያ ሽያጭን አፅድቋል።
በመሳሪያ ሽያጩ መሰረት ግብፅ ራዳር፣ ሚሳኤሎች እና የሎጅስቲክስ እንደዚሁም የኢንጂነሪንግ ድጋፎችን ከአሜሪካ ታገኛለች።
አሜሪካ ለግብፅ የምትሰጠው የአየር ስርዓት መሳሪያ ሂሊኮፕተሮችን፣ ድሮኖችን እንደዚሁም ክሩዝ ሚሳኤሎችን ለመመከት ያስችላል።
አሜሪካ ይህንን ሽያጭ የኔቶ አባል ሃገር ካልሆኑት ዋነኛ አጋሮቿ ውስጥ የሆነችው የግብፅን ደህንነት ለማሻሻል መሆኑን ገልፃ ይህም በመካከለኛው ምስራቅ ሰላም እና የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲኖር ያስችላል ብሏል።
በተጨማሪ ለግብፅ ጦር ስልጠና እና የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ 26 የአሜሪካ መንግስት ሰራተኞች እና 34 ኮንትራክተሮች ወደ ግብፅ ያመራሉ ተብሏል።
የመሳሪያ ሽያጩን የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ያፀደቀው ሲሆን በቀጣይ የኮንግረሱ ውሳኔ ይቀረዋል።
ከ1979 ጀምሮ ግብፅ ከእስራኤል ጋር የሰላም ስምምነት በመፈራረሟ ከአሜሪካ የመሳሪያ ሽያጭ እና ድጋፍ በገፍ እያገኘች እንደሆነች ይታወቃል።
ግብፅ በተመሳሳይ በ2024 የ5 ቢሊየን ዶላር የመሳሪያ ግዢን ከአሜሪካ ፈፅማለች።
ሃገረ ግብፅ ከእስራኤል በመቀጠል ከአሜሪካ ሁለተኛዋ ከፍተኛ የወታደራዊ ድጋፍ የሚደረግላት ሃገር ስትሆን ከ1979 ጀምሮ በየአመቱ የ1.3 ቢሊየን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ ከአሜሪካ ታገኛለች።
Source: Al Jazeera, Madamasr, Defensepost
የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ፣ የኢትዮጵያ መሪዎች ከጠብ አጫሪ ንግግር ተቆጥበው በአገሪቱ የውስጥ ችግሮች ላይ እንዲያተኩሩ በሁለተኛው ክፍል ቃለ ምልልሳቸው መክረዋል። ፕሬዝዳንቱ፣ ኤርትራን መወንጀል ሌላ ጣጣ ማምጣት እንደሚሆንና የከፋ ውጤት ከመጣ ማቆም እንደማይቻል አጠንቅቀዋል። ኢሳያስ፣ በሱዳኑ ጦርነት ጀርባ ዋነኛዋ ተዋናይ ኢምሬቶች ናት በማለትም ከሰዋል።
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከበላይ አካላት በደረሰበት ጫና የአመቱን ሪፖርት በተመለከተ ሊሰጠው የነበረውን ጋዜጣዊ መግለጫ መሰረዙ ታወቀ
ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ መንግስታዊ ተቋማት በአንፃራዊነት ነፃነት እንዳለው በስፋት ይነገርለት የነበረው የፌደራል ዋና ኦዲተር ቢሮ ከቅርብ አመታት ወዲህ፣ በተለይ ደግሞ ባለፈው አንድ አመት ‘ከበላይ አካላት’ ከፍተኛ ተፅእኖ እየደረሰበት መሆኑ ታውቋል።
የፕሪሚየም አባል ከሆኑ ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/bde9y4sm
የአለም ጤና ድርጅች የቺኩንጉንያ ቫይረስ በፍጥነት እየተዛመተ ነው ሲል አስጠነቀቀ።
በአለም ላይ ከ20 አመት በፊት ተከስቶ የነበረውና በወባ ትንኝ ዝርያ የሚከሰተው የቺኩንጉንያ ቫይረስ በህንድ ውቅያኖስ አካባቢ በሚገኙ ሃገራት ዳግም ተቀስቅሶ እየተስፋፋ ነው ተብሏል።
በ119 ሃገራት የሚኖሩ 5.6 ቢሊየን ሰዎች የቫይረሱ ስጋት ውስጥ መሆናቸውም ተገልጿል።
በላ ሪዩኒየን ደሴት ከሚገኘው ህዝብ አንድ ሶስተኛው በቫይረሱ ተይዟል ያለው የአለም ጤና ድርጅት ቫይረሱ በአሁኑ ጊዜ ወደ ማዳጋስካር ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ ተስፋፍቷል ብሏል።
በሽታው ወደ አውሮፓ ተስፋፍቶ 800 ሰዎች በፈረንሳይ በቫይረሱ ተይዘዋል ሲባል በጣሊያንም የተያዙ ሰዎች ተገኝተዋል።
ቫይረሱ ምንም አይነት ህክምና የሌለው ሲሆን የሚተላለፈው በወባ ትንኝ ዝርያ እንደሆነ ሲገለፅ እንደ ድካም፣ ትኩሳት እና የራስ ምታት ያሉ ምልክቶችም አሉት ተብሏል።
የአለም ጤና ድርጅት ሰዎች ራሳቸውን በልብስ በመሸፈን እና እንደ አጎበር ባሉ ነገሮች በመጠቀም እንዲጠብቁም መክሯል።
በ2005 በተከተሰው ወረርሽን ወቅት በሚሊየኖች በበሽታው ሲያዙ በመቶዎቾ የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወትም አልፏል።
ቫይረሱ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ በ2008 ዓ.ም ተከስቶ የነበረ ሲሆን ከተከሰተባቸው አከባቢዎች አንዱ ኢትዮጵያ ከኬንያ ጋር በምትዋሰንበት ዶሎ አዶ አካባቢ ሲሆን በድሬዳዋም በተመሳሳይ ተከስቶ ነበር።
በቫይረሱ ዙሪያ በቅርብ በተደረገ ጥናት (https://www.frontiersin.org/journals/public-health/articles/10.3389/fpubh.2025.1538911/full) ኢትዮጵያ ለቫይረሱ ተጋላጭነት አድሏ 24 በመቶ መሆኑን ይጠቁማል። በዚህም ቫይረሱ የህብረተሰብ ጤና ስጋት መሆኑን ያነሳል።
Source: USA TODAY
በIMF የተማረሩ ሀገራት! በመጨረሻ IMF ኢትዮጲያ ደርሷል!
በ IMF ድጋፍ ዙሪያ ክርክር አለ! ለሀገራት ይጠቅማል እና ይጎዳል!
ከ IMF ድጋፍ ተከትለው ስለሚመጡ የጉዳት ማስረጃዎች ከጥቅሙ ይበዛሉ!
ከ IMF ጋር ሪፎርም በማድረግ ከፍተኛ መማረር ውስጥ ስለገቡ ሀገራት እና ምክንያት በምሳሌ እመለከታለን!
ኢትዮጲያ ከIMF ጋር የቅርብ ሪፎርም አካል ነች! የአንድ ዓመቱን ምልክት ከሌሎች ሀገራት ጋር እያነጻጸርን እመለከታለን! https://youtu.be/T631z06d49g
መቀጣጫው ለእኔ ሳይሆን ለእናንተ ነው! ( ልደቱ አያሌው )በቅርቡ- “መኖሪያ ቤትህን በ10 ቀን ውስጥ የማህበረሰብ ፖሊስ ጣቢያ ላደርገው ነው” ብሎ የዛተው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አገዛዝ ዛቻውን ለመፈጸም 10 ቀንም መታገስ አልቻለም። ከሁለት ቀን በፊት ያለምንም የፍርድ ቤት ውሳኔ የቤተሰቤ ንብረት የሆነውን መኖሪያ ቤቴን ከነ ሙሉ እቃው በመቀማት (መውረስ አይደለም) ፖሊሶች ገብተውበታል። ቀደም ሲል እንዳሉት የማህበረሰብ ፖሊስ ጣቢያ ያድርጉትወይም የባለስልጣን መኖሪያ እስካሁን በግልፅ አላዎቅነም። ይህንን ማድረግ አልበቃቸው ብሎም የቤቴን ጠባቂያለምንም ምክኒያት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደው አስረውታል።ይህ አገዛዝ አይፈጽመውም ብዬ የምገምተው ምንም ዓይነት ነውርና ወንጀል ባይኖርም፣ ይህ የጠቅላይሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዐይን ያዎጣ የወንጀል ድርጊት የፖለቲካ አንደምታው ምን እንደሆነ እይታየንለህዝብ ማካፈል ስለፈለግሁ ይህችን አጭር መጣጥፍ ላስነብባችሁ ወደድኩ።በኢትዮዽያ ፖለቲካ ተሳታፊ ከሆንኩ 33 ዓመት ሆኖኛል። በ27 ዓመቱ የኢህአዴግ አገዛዝ 5 ጊዜ ታስሬ ተፈትቻለሁ። ለ18 ቀናት የቤትና የቢሮ ውስጥ እገታ፣ ለ120 ተከታታይ ቀናት የደህንነት ክትትልና ማዋከብ፣ቢያንስ ለ20 ተከታታይ ዓመታት የስም ማጥፋት ዘመቻ ተካሂዶብኛል። አጸያፊ ስድብና መለስተኛ ድብደባ የደረሰብኝ ወቅትም ነበር። በእነዚህ ሁሉ ተጽዕኖዎች ምክኒያት ለተለያዩ የማህበራዊ፣ የኢኮኖሚና የጤና ችግሮች ተጋላጭ ሆኛለሁ።ይህ ሁሉ በደል ሲደርስብኝ ግን በወቅቱ በስልጣን ላይ የነበረው የኢህአዴግ አገዛዝ በእኔ ላይ ለሚፈጽማቸውህገ-ወጥ ድርጊቶች ቢያንስ ህጋዊ ሽፋን ለመስጠትና ለማስመሰል በተቻለው አቅም ይሞክር ነበር። በእኔየፖለቲካ ተሳትፎ ምክኒያትም በቤተሰቦቸና በጓደኞቸ ላይ አንድም ጊዜ ችግር ለመፍጠርና የግል ንብረቴን ለመውረስ ሞክሮ አያውቅም። አባል የነበርኩበትን ፓርቲም ለመከፋፈልና ለማዳከም እንጂ