Blog Archives
አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ በአዲስ መዋቅር ስር ሆኖ እንደሚቀጥል አስታወቀች
የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (USAID) ቢዘጋም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈጸሙ “የሁለትዮሽ የእርዳታ ስምምነቶች” በሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ስር በተዘረጋው አዲስ መዋር እንደሚቀጥሉ የአሜሪካ ኤምባሲ አስታወቀ። ኤምባሲው ዋነኛ ናቸው ያላቸው የሰብአዊ እርዳታ፣ ዓለም አቀፍ ጤና እና የምግብ ዋስትና መርሃ ግብሮች በአዲሱ መዋቅር እንደሚቀጥሉ ዛሬው ባወጣው መግለጫ አረጋግጧል።
አሜሪካ በእነዚህ ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ እንደሚቀጥል ኤምባሲው ማረጋገጫ የሰጠው፤ የሀገሪቱ ተራድኦ ደርጅት የሆነው USAID ባለፈው ምንት በይፋ መዘጋቱን ተከትሎ ነው። ላለፉት 64 ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሰብአዊ እና የልማት እርዳታ ሲያቀርብ የቆየው ይህ ተቋም የተዘጋው፤ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ድርጅቱን ቀስ በቀስ ሲያዳክመው ከቆየ በኋላ ነው።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት፤ ድርጅቱ የነበሩትን ኃላፊነቶች ካለፈው ሰኞ ሰኔ 24፤ 2017 ጀምሮ በይፋ ተረክቧል። ሽግግሩ “ድግግሞሽን ለመቀነስ”፣ “ተጠያቂነትን ለማጠናከር” እና የእርዳታ መርሃ ግብሮችን ከዩናይትድ ስቴትስ “የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ እና የብሔራዊ ደህንነት ዓላማዎች ጋር ለማጣጣም የሚያስችል” ሆኖ እንደተቀረጸ የአሜሪካ ኤምባሲ በዛሬው መግለጫ ጠቁሟል።
በሽፋን ምርመራ ወቅት “ከግድያ በስተቀር” የሚፈጸም ወንጀልን ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርገው አወዛጋቢ ድንጋጌ ተሰረዘ
በወንጀል የተገኘ ንብረትን ህጋዊ ማስመሰል እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን “በሽፋን ስር” ሆኖ የመመርመር ኃላፊነት የተሰጠው ሰው፤ “ከግድያ በስተቀር” የሚፈጽማቸውን የወንጀል ድርጊቶች ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርገው ድንጋጌ ተሰረዘ። ድንጋጌው የተሰረዘው አዋጁ “በሰፊው እንዲተረጎም ስለሚያደርግ” እና በአተገባበሩም ላይ “አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያስከትል ስለሆነ ነው” ተብሏል።
አወዛጋቢው ድንጋጌ ተካትቶ የነበረው፤ በወንጀል የተገኘ ንብረትን ህጋዊ ማስመሰል እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በወጣ አዋጅ ላይ ነበር። እነዚህን ወንጀሎች ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ከ12 ዓመት በፊት የወጣውን ህግ ያሻሻለው አዲሱ አዋጅ በፓርላማ የጸደቀው ሰኔ 10፤ 2017 ነበር።
በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራን በተመለከተ በአዋጁ የተካተተ ድንጋጌ፤ በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እና በሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ትችት ቀስቅሶ ሰንብቷል። ድንጋጌው “በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ ወይም በቁጥጥር ስር የሚደረግ ማስተላለፍን እንዲያስፈጽም የተመደበ ሰው፤ በግዴታው ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት እና ከፈቃዱ ውጭ ሆኖ ከግድያ ወንጀል በስተቀር ለሚፈጽመው የወንጀል ድርጊት የወንጀል ክስ አይቀርብበትም” ይላል።
አዋጁ በጸደቀበት ዕለት የውሳኔ ሃሳብ ለፓርላማ ያቀረበው የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚቴ፤ ድንጋጌው እንዲካተት የተደረገው “ልዩ የምርመራ ስራን” “ውጤታማ የሚያደርግ በመሆኑ” ምክንያት እንደሆነ ገልጾ ነበር።
🔴ዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16248/
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን፣ ወገራ ወረዳ ገደብጌ ከተማ ውስጥ 11 ንፁሀን ዜጎች ትናንት በመንግስት ሀይሎች በተወሰደባቸው የበቀል እርምጃ ህይወታቸው አልፏል።
የከተማው ነዋሪዎች ትናንት የድረሱልን ጥሪ ሲልኩ አንድ ዜና መሠረት ሚድያ ላይ ወጥቶ ነበር (https://tinyurl.com/yz6r7yvr) ከሆስፒታል ምንጮች እና ከገደብጌ ከተማ ነዋሪዎች የደረሰኝ መረጃ እንደሚጠቁመው አብዛኞቹ እድሜያቸው ከ50 ዓመት በላይ የሆኑ 11 ሰዎች ናቸው ከቤታቸው እንዲወጡ እየተደረገ የተገደሉት። ( ኤሊያስ መሰረት እንደፃፈው)
አል-ፋሽጋ ዳግም በኢትዮጵያውያን እጅ ገባ
ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል።
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት በትግራይ ክልል የህግ ማስከበር ዘመቻ ላይ በነበረበት ወቅት የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም፣በሱዳን ጦር ተወርሮ የነበረው ሰፊና ለም መሬት፣ አሁን በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ገበሬዎችና ሚሊሻዎች ቁጥጥር ስር ውሏል።
የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን የውስጥ ችግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር፣ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የመተማና የቋራ ወረዳ ለም መሬቶችን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር።
በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ሁኔታውን በትዕግስት ሲከታተል የነበረ ሲሆን፣ መንግሥትም ችግሩን በዲፕሎማሲና በውይይት ለመፍታት ያለውን ፍላጎት በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል፡፡
በዚህ የሱዳን ወረራ ወቅት ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ከእርሻቸው ከመፈናቀላቸውም በላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብልና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው አይዘነጋም፡፡
የሱዳን ባለሥልጣናት ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት በመታገዝ የአማራ ክልል አዋሳኝ ወደኾኑ የሱዳን ለም መሬቶች በመስፋፋት ላይ ናቸው ሲሉ መክሰሳቸው ተዘግቦ ነበር፡፡
andafta
ዘንድሮ 23 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ከሴፍቲኔት ተረጂነት ወጥተዋል በሚል ትናንት በጠ/ሚሩ የቀረበው መረጃ የተሳሳተ መሆኑ ተጠቆመ
“ባለፈው አመትም ይሁን ዘንድሮ፣ ወይም ከዛ በቀደሙት አመታት የሴፍቲ ኔት ፕሮግራም ውስጥ 23 ሚልዮን ወይም 27 ሚልዮን ሰዎች አልነበሩም። ፕሮግራሙ በ1997 ዓ/ም ከጀመረ ወዲህ ከፍተኛው የሴፍቲ ኔት ተጠቃሚ ቁጥር በአመት ከ8 ሚልዮን በልጦ አያውቅም”- የሴፍቲ ኔት ፕሮግራም አስተባባሪ………….. https://meseretmedia.substack.com/p/23
” ለምሳሌ የካ ክፍለ ከተማ ወደ 100 የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን በማስረጃዎች አረጋግጠናል፤ ወደ ቦሌ ወደ 200 የሚሆኑ አሉ ” – ድርጅቱ
” ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ ” የመብት ተሟጋች የተሰኘው ድርጅት፣ ” የትግራይ ተወላጆች በአዲስ አበባ በዘፈቀደ እየታሰሩ ነው ” ሲል ለቲካቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ስለእስሩ በተጨባጭ ያላችሁ መረጃ ምንድን ነው ? ብለን የጠየቅናቸው የድርጅቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ መብሪሂ ብርሃነ፣ ” በባለፉት ሁለት፣ ሦስት ሳምንታት ያለየፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ ያለበቂ ጥርጣሬ ሰዎች በማንነታቸው ብቻ እየታሰሩ ስለሆነ ይህን መሠረት አድረገን ክትትል ስናደርግ ቆይተናል ” ብለዋል።
” ከክትትል ባለፈ ደግሞ ተጨባጭ ማስረጃ ካገኘን በኋላ እና ታስረው የወጡት፣ የታሳሪ ቤተሰቦችና ጓደኞችን ከጠየቅን በኋላ ሪፖርት አውጥተናል ” ብለው፣ ” ሰዎች ከሕግ ውጪ ሲታሰሩ ብቻ ሳይሆን ያለበቂ ጥርጣሬ ታስረው ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ሲቀር ይሄ የዘፈቀደ እስር ነው ” ሲሉ ወንጅለዋል።
” ሰዎች ሊታሰሩ ይችላሉ። ግን ሕግ ቢተላለፉ እንኳ ወደ ፍርድ ቤት ነው እንጂ የሚቀርቡት ከ48 ሰዓታት በላይ ፓሊስ አስሮ ማቆየት አይችልም በወንጀል እንኳ የተጠረጠረውን። እነዚህ ግን የወንጀል ጥርጣሬም የላቸውም፣ ለምን እንደታሰሩም አይነገራቸውም ” ነው ያሉት።
እስራቱ ከምን ጋር የተያያዘ እንደሆነ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ” እስሮች በየጊዜው ይፈጸማሉ አሁን በትግራይ ተወላጆች ትኩረቱን አደረገ እንጂ፤ ከዚህ በፊትም ማንነት ተኮር እስሮች አሉ። ምክንያቱን አሳሪዎቹ ናቸው የሚያውቁት ” ብለዋል።
” አንድ ሰው ከታሰረ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት እንጂ
በአርሲ ሮቤ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ
========
በሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
በምሥራቅ አርሲ ሮቤ ወረዳ ቤተ ክህነት የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ካህን ቀሲስ ተስፋዬ ረታ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡30 አካባቢ በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ተገልጿል።
ለማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ በደረሰን መረጃ ባለቤታቸው በተመሳሳይ ሁኔታ መገደላቸው የተገለጸ ሲሆን አካባቢው ካህኑ የተወለዱበት እና ከዲቁና ጀምሮ በአሁኑ ወቅትም በቤተ ክርስቲያኑ በቅስና ማእረግ እያገለገሉ ነበር ተብሏል፡፡
የካህኑ የቀብር ሥነ ሥርዓት በትናንትናው ዕለት ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት በሮቤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መፈጸሙን የደረሰን መረጃ ያመላክታል፡፡
በአሁኑ ሰዓት በወረዳው እየተባባሰ የሚገኘውን አፈና እና ግድያን በመፍራት እና በመስጋት በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናን ከተማውን ለቀው እየተሰደዱ መሆኑ ታውቋል፡፡
ቀሲስ ተስፋዬ ረታ የሰባት ልጆች አባት ሲሆኑ ልጆቻቸውም ምንም አይነት ሥራ መሥራት የማይችሉ እና ሕጻናት በመሆናቸው ለመጠለያ ይሆናቸው ዘንድ የወረዳው አስተዳደር 200 ካሬ ሜትር መስጠቱን የተናገሩት መረጃ ሰጪያችን የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ በጋራ ሆነው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
ጣቢያችን ጉዳዩ ከተከሰተበት ሰዓት አንስቶ ስለጉዳዩ ተጨማሪ መረጃዎችን ለመሰብሰብ የወረዳው የፀጥታ ኃይል ኀላፊን ለማግኘት በተደጋጋሚ በእጅ ስልካቸው ላይ ብንደውልም መልስ ማግኘት ሳንችል ቀርተናል፡፡
ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ለበርካታ ዘመናት በቤተክርስቲያን ላይ በአንዳንድ ካህናት፣ መነኮሳት፣ ጳጳሳት የሚፈጸሙ ወንጀሎችን እግር በእግር በማጋለጥና መወሰድ ስለሚገቡ እርምቶች የምድረ በዳ ጩኸት ሲያሰሙ ኖረዋል። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከውጭ የሚመጡባትን ወረራዎችንና ጥቃቶች እየመከተች በማሸነፍ ሉዓላዊነቷንና ክብሯን ጠብቃ ከሁለት ሽህ ዓመታት በላይ ቆይታለች። ሆኖም ከውስጥ ሆነው ዝሙት በመፈጸም፣ ሴቶችን በመድፈር እንዲሁም ጸያፍና አስነዋሪ ድርጊቶችን በማድረግ ህዝብ እንዲሸሻትና እንዲጠላት የሚያደርጓት ካህናት እጅግ ከፈተኛ ፈተና ሆነውባታል። ይህ ጉዳይ በግላዥጭ አደባባይ አይውጣ እንጅ ምዕመናን በየቤታደው የሚምከነከኑበትና የሚያዝኑበት ከሆነ ውሎ አድሯል። እንዲንከባከቧቸውና እንዲጠብቋቸው አደራ የተሰጣቸውን የምዕመናን አደራቸውን በልተውና ዕምነታቸው አጉድለው ዝሙት በመፈጸም ቤተክርስቲያንን እያደሙና እየገዘገዙ ያሉ ካህናትና መነኮሳት ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ከዛሬ 11 ዓመታት በፊት አሌክሳንደሪያ ቨርጂኒያ ውስጥ በመትገኘው ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዝሙት መፈጸሙ በማስረጃ የተረጋገጠበትን ታደሰ ሲሳይ የተባለ ግለሰብ ተወግዞ ስልጣነ ክህነቱ እንዲዘረዝ ማድረጋቸው ይታወሳል። ሆኖም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ፋኑኤል ከታደሰ ሲሳይ ጋር በመመሳጠር የተላለፈው ውግዘት እንዳይጸናና ግለሰቡም በዝሙት ተጨማልቆ ቤተክርስቲያንን ማርከሱንና ማቆሸሹን እንዲቀጥልነት አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በአሁኑ ጊዜ የሲኖዶስ አባል የሆነው “አቡነ” ኤውስጣጢዎስ የተባለው ግለሰብ ዋሽንግተን ሲያትል ውስጥ በሚገኘው Orthodox Church in America መንፈሳዊ ኮሌጅ ውስጥ ከዛሬ 12 ዓመታት በፊት ከሁለት ሴቶች ጋር ዝሙት መፈጸሙ በማስረጃ ተረጋግጦበት ከኮሌጅ መባረሩ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ቀሲስ አስተርአየ የግለሰቡን በዝሙት ምክንያት ከኮሌጅ መባረር አስተመልክቶ የተጻፈው ደብዳቤ ከኮሌጁ ተልኮላቸው ስለነበር ግለሰቡ ከክህነት አገልግሎት
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የኒው ዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቅርቡ በካሕናት አባቶች ላይ የደረሰውን ግድያ አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት …. አብይ አሕመድን አውግዘው ለሕዝቡ አስቸኳይ ጥሪ አስተላልፈዋል ። ….. #MerejaTv ….@mohammed_meaza… pic.twitter.com/CqoXi1PHL5
— Mereja TV (@merejatv) June 30, 2025

የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶር)፣ ባለፈው ሳምንት እሑድ ከደረሰባቸው ከባድ የመኪና አደጋ ጋራ በተያያዘ ላለፉት 6 ቀኖች በኢትዮ-ጠቢብ ሆስፒታል በጽኑ ሕሙማን ክፍል (አይሲዩ) የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ዋዜማ ስምታለች። ምንጮቻችን ሚኒስትሩ በወቅቱ በአልኮል መጠጥ ተጽዕኖ ስር ሳይሆኑ እንዳልቀሩ መታመኑን ጠቁመዋል።
ሚኒስትሩ አደጋው የደረሰባቸው፣ ባለፈው ሳምንት እሑድ፣ ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ለሰኞ አጥቢያ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ገደማ ወደ ቤታቸው በማምራት ላይ ሳሉ፣ ራሳቸው ሲያሽከረክሩት የነበረው መኪና በካርል አደባባይ ከቆመ ኤክስካቫተር ጋራ በመላተሙ እንደኾነ ምንጮች ለዋዜማ ገልጸዋል።።
በግጭቱ፣ ሚኒስትሩ ካሳሁን በእጃቸው፣ በእግራቸው እና በደረት አጥንቶቻቸው ላይ ከባድ ጉዳት እንዳገኛቸው ተመልክቷል።
ሚኒስትሩን ከአደጋው ሥፍራ ወደ ሆስፒታሉ ያደረሷቸው ሰዎች፣ በግጭቱ ከተጎዳው ተሽከርካሪያቸው ውስጥ ሲያወጧቸውም ሆነ የተሻለ ሕክምና ያገኙባቸዋል ወዳሏቸው የተለያዩ ሆስፒታሎች ሲያዘዋውሯቸው፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣን መኾናቸውን ባይገነዘቡም በአልኮል መጠጥ ተጽዕኖ ውስጥ እንደነበሩ ግን ማወቃቸውን ምንጮቻችን ተረድተዋል።
የመኪና አደጋውን ጠቅላይ ሚኒስትሩና ሌሎች አካላት እንዳይሰሙት ለመደበቅና ለተሻለ ህክምና ከአገር ወጥተው እንዲታከሙ ታስቦ እንደነበር የመረጃው ምንጮች አውስተዋል። ይሁንና ከነዳጅ ጉዳይ ጋራ ለተያያዘ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈለጓቸው ወቅት ስለ አደጋው በመስማታቸው ምክትላቸውን አደም ፋራህን ልከው አስጠይቀዋቸዋል ተብሏል። ከዚህ በኋላ እንደታሰበው ለህክምና ወደሌላ አገር ይላኩ እንደሆነ ለማረጋገጥ አልቻልንም ። [ዋዜማ]
የኤርትራ መንግስት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ግጭት ለመፍጠር ሰበቦችን እየፈለገች መሆኑን ጠቅሶ ባለፉት ጥቂት ቀናት ለተባበሩት መንግስታትና ለበርካታ አገራት ‹‹ኤርትራ ሉአላዊ ግዛቴን ጥሳለች›› የሚል ስሞታ ማስገባቷን አስታውቋል፡፡
ሲቀጥልም ‹‹ይህ ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሀል›› የሚል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ እንደሆነ አስረድቷል፡፡ የኢትዮጵያ ገዥው ፓርቲ ባለፉት ሁለት አመታት የኤርትራ ወደቦችን ‹‹በውዴታም ሆነ በግዴታ›› ለመውሰድ ቅስቀሳ ሲያደርግ መቆየቱን ያወሳው መግለጫው ጨምሮም ‹‹ከቃላትም ባለፈ የኢትዮጵያ መንግስት የጦር መሳሪያ ሲገዛ ቆይቷል›› በሚል ክስ አቅርቧል፡፡
እነዚህን ቀስቃሽ ድርጊቶች በትእግስት ማሳለፉን ገልፆም ኤርትራ በአልጀርስ በተላለፈው የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ መሰረት በግዛቷ ውስጥ እንዳለችና ምንም የወረረችው የኢትዮጵያ መሬት እንደሌለ አስረድቷል፡፡ በመግለጫው መጨረሻም ‹‹ኢትዮጵያ የጎረቤቷን ሉአላዊ መሬትና ባህር በር ለመውሰድ የምታደርገው ህገ ወጥ ጥረት ምኞት ነው›› ብሏል፡፡
መንግሥት፣ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ላይ አገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ለፖለቲካ ቅስቀሳ’፣ ለመራጮች ትምህርትና ለምርጫ ታዛቢነት ሥራዎች ከውጭ ምንጮች የገንዘብ ድጋፍ እንዳይቀበሉ የሚከልክል ድንጋጌ በማካተት የማሻሻያ ሃሳብ ማቅረቡን ቢቢሲ ዘግቧል።
ማሻሻያው፣ በውጭ ድርጅቶችና ኢትዮጵያ ውስጥ በሚኖሩ የውጭ አገር ዜጎች የተመሠረቱ አገር በቀል ድርጅቶች፣ በኢትዮጵያዊያን ለተቋቋሙ አገር በቀል ድርጅቶች የገንዘብ ወይም የቴክኒክ ድጋፍ እንደማይሠጡ እንደሚያግድም ዘገባው ጠቅሷል።
በሥራ ላይ ባለው አዋጅ በተጣለበት ዕገዳ ቅር የተሠኘ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ቅሬታውን ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማቅርብ ይችላል ተብሎ የተደነገገው መብት፣ የመጨረሻው ውሳኔ ሠጭ የባለሥልጣኑ የሥራ አመራር ቦርድ ነው በሚል አንቀጽ መተካቱንም ዘገባው አመልክቷል።
ብሔራዊ ባንክ በፈረንጆቹ 2024 10 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደገጠመው በገለልተኛ ኦዲት መረጋገጡን ሪፖርተር አስነብቧል፡፡ ባንኩ ኦዲት የተደረገው፣ መንግሥትና ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት በደረሱበት ስምምነት መሠረት ነው። ባንኩ ወርቅ የገዛበትና የሸጠበት ዋጋ ልዩነት መስፋቱ፣ ባንኩ ለመንግሥት አበድሮ ያልተመለሰለት ገንዘብ፣ የብር የመግዛት እቅም መዳከምና ከዓለማቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ያለበት ዕዳ በውጭ ምንዛሬ የሚከፈል መኾኑ ለኪሳራው አስተዋጽኦ አድርገዋል ተብሏል። ባንኩ ለመንግሥት ባንኮች 134 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር፣ ለግል ባንኮች 13 ቢሊዮን ብር እና ለመንግሥት 687 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር አበድሮ ገና አልተመለሰለትም ተብሏል
በአማራ ክልል ከጎንደር መተማ መንገድ ላይ “መቃ” በተባለች ሥፍራ የቅማንት ታጣቂዎች ሰኞ’ለት በፈጸሙት ጥቃት 16 አሽከርካሪዎች ተገድለው በርካቶች መቁሰላቸውን ታውቋል። በቅማንት ታጣቂዎች ከተገደሉት ሾፌሮች በተጨማሪ ተሳፋሪዎችና በርካታ አሽከርካሪዎች ታፍነው መወሰዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል። አብዛኞቹ አሽከርካሪዎች የተገደሉት፣ ከጥቃቱ ለማምለጥ ጥረት በማድረግ ላይ ሳሉ በእሩምታ ተኩስ እንደኾነ ተነግሯል። የፋኖ ታጣቂዎች በመተማ ወረዳ ከቅማንት ብሄረሰብ ታጣቂዎች ዘረፋ ለማስቆም የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ምንጮች ተናግረዋል። የቅማንት ታጣቂዎች በአብይ አሕመድ ድጋፍ እየተደረገላቸው በዘረፋ እና እገታ ላይ መሰማራታቸው የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
የኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ለውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች በይፋ መከፈቱን ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ
ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያውያን ባለሃብቶች ብቻ ሲካሄድ የቆየው የባንክ ስራ አገልግሎት፤ ከዛሬ ጀምሮ ለውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች በይፋ መከፈቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። በዘርፉ መሰማራት የሚፈልጉ የውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች ከዛሬ ጀምሮ ማመልከቻዎቻቸውን ለብሔራዊ ባንክ ማስገባት እንደሚችሉም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
አቶ ማሞ ምህረቱ በገዢነት የሚመሩት ብሔራዊ ባንክ ይህን ያስታወቀው፤ የውጭ ባለሃብቶች የባንክ ስራ ፈቃድ ለማግኘት እና ለማሳደስ የሚያስችላቸውን መመሪያ ይፋ ባደረገበት መግለጫ ነው። አዲሱ መመሪያ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የውክልና ጽህፈት ቤት ለመክፈት ማሟላት የሚያስፈልጋቸውን ቅድመ-ሁኔታዎችም ይዘረዝራል።
መመሪያው ብሔራዊ ባንክ ባለፈው ዓመት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ያደረገው “ሰፊ ምክክር” ውጤት እንደሆነ የመስሪያ ቤቱ መግለጫ አመልክቷል። የኢትዮጵያ መንግስት ለውጪ ባንኮች እና ለኢንቨስተሮች ተዘግቶ የቆየውን የባንክ ስራ ዘርፍ ለመክፈት ዝግጅት ሲያደርግ ከቆየ በኋላ ወደ ተግባር የገባው ከሶስት ዓመት በፊት ነበር።
🔴ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16188/
የአፋብኃ ማዕከላዊ ኮማንድ መግለጫ
“ የተገደሉት አባት ለ12 ዓመት በብትውና የኖሩ ነበሩ። ቀብራቸው ተፈጽሟል። ጥቃት በተከፈተበት ዋሻ አካባቢ የነበሩ ሰባት አባቶችን ወደ ገዳሙ አምጥተናል ” – ደብረ ከዋክብት ዝቋላ ገዳም
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎም፤ “ ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ ግን በርካታ አባቶች ተገደሉ፤ ታግተው ተወሰዱ ” የሚል መረጃ በማህበራዊ ሚዲያው በሰፊው የተዘዋወረ ሲሆን በርካቶችን አሳዝኗል አስቆጥቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ በሰሞንኛው የታጣቂዎች ጥቃት የተገደሉት ምን ያህል አባቶች ናቸው ? ታግተው የተወሰዱስ አሉ እንዴ ? “ ይገደሉ ይኖሩ ገና አልታወቀም ” የተባለላቸው አባቶች ጉዳይስ ከምን ደረሰ ? ሲል ዛሬ ገደሙን ጠይቋል።
” ‘ሁለት አባቶች ተገድለዋል’ የሚል መረጃ ተሰራጭቶ ነበር፤ ይህን ያሉን አባቶች አንዱን አባት ከዋሻው ሲገድላቸው ሲያዩ ተደብቀው ቆይተው ሸኔዎቹ ሲሄዱላቸው ተኩስ ወደ ከተከፈተበት ዋሻ ሲመለሱ አንዱን አባት ሞተው አገኟቸው፤ ወደ ሁለተኛው አባት ዋሻ ሲሄዱ ግን አጧቸውና በተከታታይ ጥይት ተተኩሶ ስለነበር እሳቸውንም ገድለዋቸዋል በሚል ‘ሁለት አባቶች ሞተዋል’ ብለው ነገሩን ” ሲል መልሷል።
” ነገር ግን ትላንት ዋሻው ድረስ ሂደን አይተን ስናረጋግጥ የሞቱት አንድ አባት ብቻ ናቸው። ሌላኛው ‘ተገደሉ ተብለው የነበሩት አባት ደግሞ ሸኔዎቹን ሲያዩ ከዋሻቸው ወጥተው ተሰውረው ስለነበር በፍለጋ አግኝተናቸዋል” ሲል ገዳሙ ገልጷል።
የጥቃት ቀጠና በነበሩት የገዳሙ ዋሻዎች የነበሩ ሌሎች ሰባት አባቶችን ወደ ዋናው ገዳም
ከኢትዮጵያ መንግስት ለአፍሪካ ልማት ባንክ ሊከፈል ሂደት ላይ እያለ የተዘረፈን 4.8 ሚልዮን ዩሮ ለማስመለስ ኢንተርፖል ጣልቃ መግባቱ ታወቀ
በሜክሲኮ ያሉ አጭበርባሪዎች ገንዘቡን እንደዘረፉ የሚጠቁመው የአፍሪካ ኢንተሊጀንስ ዘገባ ኢንተርፖል ድምፁን አጥፍቶ ላለፉት በርካታ ወራት በዝርፊያው ዙርያ ምርመራ እያረገ እንደሚገኝ ጠቁሟል።
ዝርዝሩን ያንብቡ: https://tinyurl.com/2rep3pfx