Blog Archives
ታላቁ የሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጋር “ተጨማሪ ውይይት” እንደማይደረግ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዲላቲ ለቢቢሲ ተናገሩ።

ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ ላለፉት 13 ዓመታት የተደረጉ ውይይቶች “አንዳችም መፍትሔ” አላመጡም ብለዋል።
የሕዳሴ ግድቡ ከተመረቀ በኋላ በኢትዮጵያ እና በግብፅ መካከል ያለው ግንኙነት “የበለጠ መሻከሩን” ጠቅሰው፤ በዚህ መካረር ምክንያት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ “ስጋት ሊሰማው” እንደሚገባም ተናግረዋል።
ባለፉት 13 ዓመታት በአገራቱ መካከል የተደረገው ውይይት ውጤት ባለማስገኘቱ፤ ግብፅ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት “የውሃ ደኅንነቷን እንደምታስከብር” አክለዋል።
ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ ጋር የተደረጉ ውይይቶች ምንም ውጤት ባለማስገኘታቸው “በቀጣይም ንግግር ማድረግ አስፈላጊ አይደለም” ብለዋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ።
የግድቡ ጉዳይ “ከኢትዮጵያጋር ካለን የሁለትዮች ግንኙነት ጋር የሚያያዝ ነው” ያሉት ሚኒስትሩ፤ ግድቡን “እንደተናጠል እርምጃ ነው የምንቆጥረው” ብለዋል። አክለውም “ሕገ ወጥ ነው” ሲሉ የመንግሥታቸውን አቋም አንጸባርቀዋል።
ግድቡን “ከዓለም አቀፍ ሕግ ጋር የሚጣጣም አይደለም” ሲሉ የገለጹት የውጭ ጉዳይ ሚኒሰትሩ “ዓለም አቀፍ ሕግ በግልጽ እንደሚለው ማንኛውም ድንበር ተሻጋሪ ወንዝ በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች መመራት አለበት። ይህም ማለት ማሳወቅን እና ጉዳት አለማስከተሉን ማረጋገጥ ያስፈልጋል” በማለት አብራርተዋል።
ከአንድ ወር በፊት ግብፅ ብሔራዊ ጥቅሟን እና የውሃ ደኅንነቷን ለማስጠበቅ “አስፈላጊ የሆኑ ሁሉንም እርምጃዎች እንደምትወስድ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ አል-ሲሲ መናገራቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያ በሰጠችው ምላሽ፤ ግብፅ “ሕገ ወጥነት እና የበላይነት በተሞላው መንገድ” የዓባይ ወንዝን ለመቆጣጠር መሞከሯን ቀጥላለች ብላለች።
አል ሲሲ፤ ግብፅ በዲፕሎማሲ እና
ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብን ሰውራዋል የተባሉ በርካታ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች ባለቤቶች እና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ።
ተቋሙ እንዳለው ግለሰቦቹ ለመንግሥት ገቢ መሆን የነበረበትን ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል ተጠርጥረው ነወ የተያዙት።
በተወሰደው እርምጃ በደኅንነት አገለግሎቱ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የ24 የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶች እና ተባባሪዎቻቸው መሆናቸው ተገለጿል።
የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር ተብለው ከሚጠሩ የፋይናንስ ሥርዓቶችን ከሚያካሂዱላቸው የአገር ውስጥ የክፍያ ሥርዓት አቅራቢ ተቋማት ጋር በመመሳጠር የገንዘብ ስወራውን ፈጽመዋል ተብሏል።
ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር የሚባሉት የአገር ውስጥ የገንዘብ ክፍያ ሥርዓት አቅራቢ ተቋማቱ ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በመውሰድ የሚንቀሳቀሱ ናቸው።
እነዚህ ድርጅቶች የደንበኛን ምሥጢር መጠበቅ የሚል ሙያዊ አሠራርን “እንደ ሽፋን ተጠቅመው” የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች የሚያንቀሳቅሱትን ገንዘብ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት ደብቀዋል ወይንም አሳንሰው አቅርበዋል ተብሏል።
የብሔራዊ መረጃ እና የደኅንነት አገልግሎት በዚህ የተነሳ የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች “በግብር ስወራ እንዲሁም ከፍተኛ የአገር ሀብትን ወደ ውጭ በማሸሽ ወንጀል ላይ ተሳትፎ እንዳላቸው” አመልክቷል።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል በጋራ መሥራታቸውም ተገልጿል።

የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ፈቃድ ኖሯቸው ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በገቡት ውል መሠረት የማይሠሩ፣ በሕገ ወጥ ድርጊት ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው የተሰረዘባቸው መሆኑን ጠቅሷል።
እንዲሁም ምንም ዓይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው በስፖርት አወራራጅነት ተሰማርተው የነበሩ
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን፣ ጅማ አርጆ ወረዳ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት አንድ ዐቃቤ ሕግ ሲገደል፣ ሦስት የሕግ ባለሙያዎች ደግሞ ታግተው መወሰዳቸውን የኦሮሚያ ዐቃቢያን ሕግ ማኅበር አስታወቀ።
ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ቢሮ አንድ ባልደረባ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ድርጊቱ የተፈጸመው ረቡዕ ኅዳር 17/2018 ዓ.ም. ከሰዓት ጅማ አርጆ ወረዳ፣ ሐራ ቀበሌ ውስጥ ነው።
ታግተው ከተወሰዱት መካከል አንድ ሾፌር እንደሚገኝበት ግለሰቡ ጨምረው ገልጸዋል።
ዐቃቢያን ሕጎቹ ላይ በታጣቂዎቹ ጥቃት የተፈጸመባቸው ለሥራ ወደ ጅማ ያቀኑ በነበረበት ወቅት ነው።
“ሥራቸውን አጠናቀው በበደሌ አልፈው ረቡዕ ወደ 9 ሰዓት አካባቢ ወደ ነቀምት ሲመለሱ ታጣቂዎች መኪናቸውን አስቁመው አግተው እንደወሰዷቸው ነው የሰማነው። የታገቱት አሽከርካሪውን ጨምሮ 5 ሰዎች ናቸው።”
ግለሰቡ አክለውም ከታገቱት ግለሰቦች ጋር አብረው የነበሩትን አቶ ነገሰ ከበደ የተባሉትን ዐቃቤ ሕግ ታጣቂዎቹ መገደላቸውን ተናግረዋል።
የሕግ ባለሙያዎቹ ላይ ጥቃት አድርሰው ግድያውን እና ያገታውን የፈጸሙት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ መንግሥት ሸኔ የሚለው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች መሆናችውን ግለሰቡ አክለው ገልፀዋል።
በኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ቢሮ የሕግ አርቃቂ የነበሩት አቶ ነገሰ በታጣቂዎቹ ከዋናው መንገድ ረዥም ርቀት ለሁለት ሰዓታት በእግር ከወሰዷቸው በኋላ እንደተገደሉ ግለሰቡ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ግለሰቦቹ ለሕግ ጥናት ወደ ጅማ መሄዳቸውን የተናገሩት ግለሰቡ “የክልል፣ የአገርም ሆነ የዓለም አቀፍ ሕጎች እንደሚመሰክሩት ዐቃቢያን ሕግ የፓርቲ አባል መሆን አይችሉም። ለሕገ መንግሥቱ ነው ተገዢ የሚሆኑት። አጋቾቹ ይህን ሊገነዘቡ ይገባል። ነገር ግን እነዚህ የሕግ ባለሙያዎች ባልተገባ ሁኔታ
በሐረርጌ እና በዙሪያዋ ላሉ አርሶ አደሮች ጫት ዋነኛ የገቢ ምንጭ ነው። ጫትን ከማምረት አንስቶ ወደ ውጭ አገራት እስከመላክ ባለው ሒደት ውስጥ የሚሳተፉ በርካቶች ናቸው።
በአካባቢው ጫት የውጭ ምንዛሬ ምንጭም ነው።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ፍተሻ የሚደረግባቸው ጣቢያዎች ቁጥር እንዲሁም እነዚህን የፍተሻ ጣቢያዎች ለማለፍ የሚጠየቀው የክፍያ መጠን ጨምሯል በሚል የጫት አምራቾች እያማረሩ ነው።
ጃፋር በአወዳይ የጫት አምራች ነው። ለዓመታት አርሶ አደሮችን ሲያማርሩ የቆዩ ችግሮች አሁንም ድረስ እንዳልተቀረፉ ይናገራል።
“ከዚህ ቀደም አርሶ አደሮችን ያማረረው ጫትን በሌላ ሰብል የመተካት ጉዳይ ነበር። ገበያው ላይ ያለው የጫት መጠን ከፍ ሲል ዋጋው ይቀንሳል” በማለት ያለውን ሁኔታ ይገልጻል።
አሁን ላይ ግን “በአገራችን የጫት ዋጋ ጨምሯል” ይላል ጃፋር።
“በአገራችን የጫት ዋጋ ጨምሯል። ለዚህ ምክንያቱ አሁን ጫት የሚበቅልበት ወቅት መሆኑ ነው። አርሶ አደሩ ጫት እየተከለ ነው። ምርቱ ሲጨምር ዋጋው ይቀንሳል።”
የጫት አርሶ አደሮች በዋነኛነት ቅሬታ ያቀርቡ የነበረው በተለያዩ ከተማዎች እና የፍተሻ ጣቢያዎች ‘የኮቴ’ ክፍያ በመጠየቃቸው ነው።

ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት፤ በሶማሊያ ገበያ የኬንያ ጫት አቅርቦት በ17 በመቶ ቀንሷል። ስለዚህም ለኢትዮጵያ ጫት ያለው ፍላጎት ከፍ ብሏል።
ከዚህ ቀደም በሶማሊያ ውስጥ የኬንያ ጫት ተቆጣጥሮት በነበረውን ገበያ አሁን ላይ የኢትዮጵያ ጫት ቀዳሚ ሆኖ ይዞታል።
በሶማሊያ ገበያ የኢትዮጵያ ጫት ተፈላጊነቱ መጨመሩን ተከትሎ፤ ኬንያ ከሶማሊያ ውጭ ያሉ የገበያ አማራጮችን እየፈለገች እንደሆነ የአገሪቱ የግብርና እና ምግብ ባለሥልጣን አስታውቋል።
አወዳይ ከተማ የተወለደው የጫት ነጋዴ አብዱልጀባር ኢብራሒም እንደሚለው፤ ኬላ ላይ
በአርበኛ ምሬ ወዳጆ የሚመራው ምኒልክ ዕዝ እና በአርበኛ መከታው ማሞ የሚመራው ሸዋጠቅላይ ግዛት ዕዝ በጋራ በካሄዱት ውጊያ ታላቅ ድል መጎናፀፋቸው ተሰምቷል።
በአይነቱ ለየት ያለ ወንድማማችነትና አንድነት የታየበት ጥምረት ተፈጥሮ፡ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ጠንካራ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ታውቋል።
ሁለቱ ኃያል ዕዞች ዛሬ ህዳር 23/2018 ዓ/ም ከረፋድ ጀምሮ እስከ ምሽት ድረስ በደቡብ ወሎ ዞን ስር በደገርና አከባቢው ላይ ከባድ ትንቅንቅ ሲያካሂዱ ውለው አምሽተዋል።
በተመሳሳይ መረጃ ስትራቴጂክ የጦር ስፍራ እንደሆነ በሚነገርለት በደላንታ ወረዳ ስር በሚገኘው ፀሐይ መውጫ አከባቢ ላይ በተደረገ ተጋድሎ ፋኖ ድል መቀዳጀቱ ታወቀ!
በተመሣሣይ በዳውንት ወረዳ በተካሄደ አውደ ውጊያ ፋኖ አዳዲስ የጦር ስልቶችን በመጠቀም ኃያልነቱን ያስመሰከረበትን ተጋድሎ ማካሄዱ ታውቋል።
በዚህ ታላቅ ተጋድሎ ከባድ ጥቃት የተሰነዘረበት አገዛዙ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገባ ሲሆን፡ የደላንታና የወገል ጤና የብልፅግና ካድሬዎች ተከበናል በሚል በዚህ ምሽት ወደ ደሴ ከተማ መሸሻቸውት ተሰምቷል። እንዲሁም በሌላ መረጃ ትናንት በሉማሜ ወረዳ ከተፈፀመበት ጥቃት ለጥቂት ተርፎ ሸሽቶ የነበረው የኦህዴድ ተላላኪው አቶ አረጋ ከበደና ቡድኑ፡ በደብረ ማርቆስ ከተማ ባካሄዱት ስብሰባ ከማሕበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ የሆነ ነቀፋና ውርደትን መከናነባቸው ተሰምቷል!
የልዩ ኃይሉ መፍረስ፣ በአገዛዙ የሚፈጸመው እገታ፣ ዘረፋ፣ ጅምላ ጭፍጨፋ፣ የንጹሐን ሞት፣ የገዳማት ውድመት፣ የመነኮሳት የቆሎ ተማሪዎች የካሕናት ጭፍጨፋ፣ ጡት ቆረጣ መሰል በአገዛዙ የሚፈፀሙ ግፎችን የጠቀሰው ማሕበረሰቡ፡ የዚህ ሁሉ አስፈፃሚዎች እናንተ ናችሁ በሚል ጣቱን ቀስሮባቸው እንደዋለ ታውቋል።
ነገሩ በጠበቁ ልክ ያልሆነላቸው እነአረጋ ከበደና ስብስቡ፡ በሕዝቡ አቋም
የምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ላይ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::
የምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ላይ ዛሬ ህዳር 23/2018 ዓ.ም ማለዳ 3:00 ጀምሮ እስከ ቀን 6:00 ከፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ጋር በመፋለም ታላቅ ድል አስመዝግበዋል::
ጠላት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ከተማን ለመቆጣጠር ከኮንና ጋሼና አንድ ክፍለጦር ዙ23ን ጨምሮ እንዲሁም ከወገል ጤና አንድ ክፍለ ጦር ዙ 23 ጋር ወደ ዳውንትና ፀሃይ መውጫ ማጥቃት ያደረገ ሲሆን ከምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለ ጦር እና ከደጋው መብረቅ ኮር ከፅናት መክትና ሰንጥቅ ክፍለ ጦር የተውጣጡ ሻለቆች እንዲሁም ሌሎች በመደራጀት ላይ ያሉ አሃዶች በጥምረት የጠላትን ሰራዊት ለጊዜው በስም ያልታወቁ አመራሮችን ጨምሮ በመደምሰስና በማቁሰል ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ ብሎም ቀጠናውንና ከተሞቹን በማስከበር ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::
በዚህ በድንቅ መናበብ በተመዘገበ ታላቅ ፍልሚያና ድል የጠላት ሰራዊት በሁሉም አቅጣጫ የተመታ ሲሆን አስከሬንና ቁስለኛውንም እያነሳ ወደመጣበት አቅጣጫ ሽሽቷል:: በተጋድሎው በመደራጀት ላይ ያለ የልዩ ዘመቻ አሃድም የተሳተፈ ሲሆን ከልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር አንድ ጓድ በውጊያ መሃል ደፈጣ ጥቃት በመፈፀም ታላቅ ጀብድ ሰርተዋል::
በዚህ ታላቅ ተጋድሎ ከባድ ምት የተመታው አገዛዙ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገባ ሲሆን የደላንታና የወገል ጤና የብልፅግና ካድሬዎችና አመራሮች ተከበናል መላም የለን እያሉ ወደ ደሴ ከተማ መሸሽ ጀምረዋል:: ውጊያው አሁንም ሌሎች አሃዶች ተጨምረውበት ተጠናክሮ ቀጥሏል::
አፋብኃ ምስራቅ አማራ
ሐረርጌ ዞን፣ ጭሮ ወረዳ፣ ላሎ ጉዶ ቀበሌ፣ ኢፈ ባስ(ifabaas) በምትባል የገጠር መንደር ውስጥ በኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 እልፌ ተስፋ ወሌ የሚባሉ እናት በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል። በዚኹ ቀበሌና በአጎራባች ቀበሌዎች ያብዶ ሸንበቆ፣ ረብሱ፣ ሼክ አደም፣ ሉጎ በርካታ ሃይማኖትና ማንነትን ማዕከል ያደረጉ ጭፍጨፋዎች የሚካሄዱባቸው ናቸው። ብንናገርም ሰሚ የለም። ሕዝቡና ሚዲያውም እኛን ረስቶናል ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች በምሬትና በፍርኃት ተውጠው።
በወረዳው በቅርቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት የኾኑ ተፈሪ መንገሻ ከነ ባለቤቱ ቀለሟ በለጠ ጋር፣ ባለው መንገሻ፣ አሳምነው አባይነህ የተባሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በአሰቃቂ ኹኔታ በስለትና በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል። ግድያውን የሚፈጽመው በአካባቢው ሰዎች አጠራር ኦነግ ሸኔ(ራሱን ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል) ነው።
ይኽን መረጃ እያጣራን ባለንበት አፍታ በአርሲ ዞን በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፣ በቀቅሳ ቀበሌ በአጨዳ ላይ የነበሩ ከ19 በላይ ገበሬዎች ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ታፍነው መወሰዳቸውን ከቦታው ለማረጋገጥ ችለናል። በዚኹ አካባቢ በቅርቡ ወንድማማቾችን ጨምሮ ሦስት ንጹሓን እንደተገደሉ ይታወሳል።
እናት ፓርቲ በምዕራብ ሐረርጌ ባሉ በርካታ ቀብሌዎች በጥንቃቄ ተደብቆ የሚካሄድውን ጭፍጨፋና እገታ፤ እንዲኹም በአርሲ እየተካሄደ ያለውን ዘር ፍጅት በጽኑ እናወግዛለን፤ የታገቱትም ያለምንም ቅድመ ኹኔታ እንዲፈቱ እንጠይቃለን።
ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!
እናት ፓርቲ
ኅዳር ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወልዲያ ከተማ ውስጥ የሚገኙ በርካታ የዓብነት ተማሪዎች ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ታፍሰው መወሰዳቸው ታወቀ –
“ቤተ ክርስቲያኒቱ ተማሪዎቹ እንዲለቀቁ በደብዳቤ ብትጠይቅም እስካሁን ምላሽ አልተገኝም። አፍነው የወሰዱት የሚሊሻ አባላት በወሰዱት በእያንዳንዱ ተማሪ 7 ሺህ ብር እየጠየቁ ይገኛሉ”
– ከተያዙት ተማሪዎች መካከል አንደኛው ባሳለፍነው አርብ ለማምለጥ ሲሞክር ከሚሊሻ በተተኮሰበት ጥይት ተመትቶ ከፒያሳ ወደ ቲንፋዝ በሚወስደው መንገድ ላይ ህይወቱ ማለፉ ታውቋል ተጨማሪ ያንብቡ: https://meseretmedia.org/p/2b4
የእንግሊዙ ዘጋርዲያን ጋዜጣ “ኢትዮጵያ ዳግም ወደ ግጭት አፋፍ ላይ ባለችበት በዚህ ወቅት፣ ‘ፋኖ’ የተሰኘው ብሔርተኛ ሚሊሻ፣ ከዓለም በተቆረጡት የሰሜን-ምዕራብ ተራራማ አካባቢዎች ከመንግስት ጦር ጋር ከባድ ውጊያ ገጥሟል።’ በሚል የፎቶግራፍ ዘገባ፣ ሀገሪቱን እየበጣጠሰው ያለውን ውጥረት የሚያሳይ እይታን ይዞ ወጥቷል።
“የትግራይ ጦርነት ካበቃ ከሶስት ዓመታት በኋላ፣ ኢትዮጵያ በሰሜን-ምዕራብ ክፍሏ በተቀሰቀሰ ከባድ የትጥቅ አመጽ እየተናጠች ነው።” የሚለው ዘገባው፣ በአብዛኛው በቀድሞው የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት የተዋቀረው “ፋኖ”፣ በአሁኑ ወቅት ሰፊውን የአማራ ክልል ገጠራማ አካባቢዎች (80% ገደማ) መቆጣጠሩን ሪፖርቱ ያሳያል።
ዘገባው እንዳመለከተው፣ የፌደራል ኃይሎች አመጹን ለማፈን በሚያደርጉት ጥረት “ሰፊ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን” እየፈጸሙ ነው። ከእነዚህም መካከል አፈና፣ የጅምላ ጭፍጨፋ፣ ጾታዊ ጥቃቶች እና በሰብአዊ እርዳታ ሰራተኞች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች ይገኙበታል።
“ሁኔታው ከቁጥጥር ውጪ ነው” ያለው ዘገባው፣ በክልሉ ከሱዳን ጦርነት የሸሹ ስደተኞችን ጨምሮ ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ህዝብ አፋጣኝ ሰብአዊ እርዳታ እንደሚያስፈልገው አስታውቋል
በተለይም መንግስት የክልል ልዩ ኃይሎችን “ለመበተን” መወሰኑ፣ በአማራ ተዋጊዎች ዘንድ እንደ ቀጥተኛ የጸጥታ ስጋት ተወስዷል። ዘገባው ይህንን “ጥልቅ የክህደት ስሜት” ሲል ይገልጸዋል። በሺዎች የሚቆጠሩ የቀድሞ የልዩ ኃይል አባላትም የፋኖን ጦር በመቀላቀል፣ ወታደራዊ ልምዳቸውንና ትጥቃቸውን ይዘው የ20,000 ተዋጊዎችን ኃይል እንደፈጠሩ ተገልጿል።
ፋኖ እራሱን “የአማራ ህዝብ ተከላካይ” አድርጎ የሚቆጥር ሲሆን፣ ግቡም ከክልሉ ሙሉ ቁጥጥር አንስቶ የዐቢይ አሕመድን መንግስት እስከመጣል ይደርሳል።
ሪፖርቱ እንዳነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ንጹሃን ዜጎች በግጭቱ መሃል ሆነው ከባድ ዋጋ እየከፈሉ ነው።
የ23 ዓመቷ ወ/ሮ
አስደማሚው የጎንደሩ ተጋድሎ እና የተገኘው ድል!
በማዕከላዊ ጎንደር ቡርኳስን፣ ዳዋ ዳሞትና ምንዝሮ ላይ በተደረገ ውጊያ 12 የአገዛዙ ወታደሮች ሲገደሉ ከ17 በላይ የሚሆኑት መቁሰላቸው ተሰምቷል!
በአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ኮር ስር የሚገኘው ግዙፉ የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ትናንት ህዳር 22/2018 ዓ/ም በጠላት ላይ ከባድ እርምጃ በመውሰድ ታላቅ ድል መቀዳጀቱን ከክፍለጦሩ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለማረጋገጥ ችሏል።
ከማዕከላዊ ጎንደር ጠዳ፣ ከማክሰኝት እና ከደጎማ ከተሞች ተሰባስቦ በዞኑ ስር ዳዋ ዳሞት፣ ምንዝሮ እና ቡርቧክስ በተባሉ አከባቢ ላይ በከባድ መሣሪያ ታግዞ ጥቃት ከፍቶ የነበረው የፀረ አማራው አገዛዝ ኃይል፡ ከወደ ፋኖ የተከፈተበትን የፀረ ማጥቃት መቋቋም አቅቶት ሙትና ቁስለኛውን ማንሳት እስኪያቅጠው ድረስ መፈርጠጡ ታውቋል።
ትናንት ከንጋት ጀምሮ እስከ ቀኑ 9:00 ሰዓት በተደረገው አውደ ውጊያው በጎንደሬ በጋሻው ክፍለጦር ስር ፋሲለደስ ፣ቃኘው እና ጎንደር ብርጌድ የተሳተፉ ሲሆን በኦፕሬሽኑ ከ12 በላይ ጠላት ሲገደል፡ ከ17 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ክፋኛ ቆስለዋል።
Op<በአረጋ ከበደ ላይ በጎጃም የሞርታር ጥቃት ተፈፀመባቸው …… የፋኖ ኃይሎች የተሳኩ የደፈጣ ጥቃቶችን አድርገዋል ……. በወሎና በጎጃም በርካታ የአብይ ወታደሮች በቡድን እጅ እየሰጡ ነው። …… እነዚህን እና ሌሎች በርካታ የግንባር መረጃዎችን ይዘናል ያድምጡን …….. https://x.com/merejatv/status/1995716216443248895?s=20
ከአገዛዙ በተሰጣቸው ተልዕኮ መሠረት በእገታና ዝርፊያ ድርጊት ላይ ተሰማርተው የነበሩ የአድማ ብተና አባላት በፋኖ ቁጥጥር ስር ዋሉ!
በፋኖ ቁጥጥር ስር የዋሉት የአድማ ብተና አባላቱ፡ በፋኖ ስም ዝርፊያና እገታ፣ እንዲሁም አስገድዶ መድፈርና ሌሎች ወንጀሎችን እንዲፈፅሙ ከአገዛዙ ተልዕኮ ተቀብለው በየአከባቢው መሰራጨታቸውን ገልፀዋል።
ፋኖ፡ የትግሉን ገፅታ ለማበላሸት እንዲሁም በፋኖና በሕዝቡ መካከል ቅሬታና ጥርጣሬን ለመፍጠር ከብልፅግና ተልዕኮ ተቀብለው በእንደዚህ አይነት እኩይ ድርጊት ተሰማርተው በሚገኙ ወንጀለኞች ላይ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ጥብቅ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
ዝርዝር ዜናውን አድምጡ👉 https://x.com/i/status/1995002606674972836
የትግራይ ክልል ወቅታዊ የፖለቲካ አሠላለፍና የጦርነት ሥጋት
የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ የፌዴራል መንግሥት ሌላ ዙር ጦርነት በትግራይ ላይ ለመክፈት እየጣረ ነው ሲል ወንጅሏል፡፡ ማዕከላዊ ኮሚቴው ለተከታታይ ቀናት ስብሰባ በማድረግ… https://ethiopianreporter.com/148268/
የጥንቶቹ ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ከወራሪዎችና ከተስፋፊዎች በመከላከል ብዙውን የዕድሜያቸውን ክፍል አሳልፈው በክብር ሲያልፉ፣ በተነፃፃሪ የተሻለ ዘመን ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያን እርስ በርስ ሲናቆሩ አገራቸውን ለድህነት መዳረጋቸው ብዙዎችን የሚያስቆጭ ነው፡፡ ለአገራቸው በሁሉም መስኮች ትልልቅ አስተዋጽኦዎች ማበርከት የሚችሉ ወጣቶች በየቦታው ሲታኮሱና ሲጋደሉ ኖረው ያተረፉት ሞትና ጉስቅልና ነው፡፡ ጥራት ያለው ትምህርት አግኝተው ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው ለአገራቸው የሚተርፍ ሀብት ማፍራት የሚችሉ ወጣቶች፣ በማይረቡ ምክንያቶች ጎራ በለዩ ፖለቲከኞች ሳቢያ በተቀሰቀሱ ግጭቶች ሕይወታቸውን ገብረዋል፡፡ በስክነት ተነጋግረው ልዩነቶቻቸውን ፈር ማስያዝ ባልቻሉ ፖለቲከኞች ምክንያት አገር ተበድላለች፡፡ ለኢትዮጵያ ልማትና ዕድገት ሊውል የሚገባው የወጣት ኃይልና የተፈጥሮ ሀብት፣ በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ ጦርነቶች በመማገዱ ድህነት መታወቂያ ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያ ምንም ሳታጣ የነጣች ደሃ የሆነችው በምን ምክንያት እንደሆነ በርካታ ምሳሌዎችን ማቅረብ ይቻላል፡፡
ፖለቲከኞች ከበፊት ጀምሮ ችግሮቻቸውን በሠለጠነ መንገድ መፍታት ቢችሉ ኖሮ፣ አገርን ከማንኛውም ዓይነት ወረራ የመጠበቅ አኩሪ ታሪካዊ እሴት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ተዓምር መፍጠር እንደሚችሉ ማንም አይስተውም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሠርቶ የሚያሠራው ቢያገኝ እንኳን ለአፍሪካ ለዓለም የሚተርፉ ምርቶችን ማምረት ይችል ነበረ፡፡ በቀን ሦስቴ መመገብ የሰማይ ያህል ሊርቀው ቀርቶ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም ኤክስፖርተር መሆን አያቅተውም፡፡ ልዩነቶቻቸውን በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ማስተናገድ ባቃታቸው ፖለቲከኞች ምክንያት ግን፣ እንኳንስ የተመጣጠነ ምግብ ሊመገብ ቀርቶ በቀን አንዴ በልቶ ለማደር ሰማይ ጠቀስ ተራራ የመውጣት ያህል በእጅጉ እየከበደው ነው፡፡ በአፍሪካ በተፈጥሮ ሀብቶች ተጠቃሽ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ሕዝቧ የተመጣጠኑ ምግቦች ማግኘት ሁሌም ብርቁ ናቸው፡፡ የአፍሪካ የውኃ ቋት
በምዕራብ ሐረርጌ የታፈነው ጩኸት እና በአርሲ የቀጠለው ዘር ፍጅት
በምዕራብ ሐረርጌ ዞን፣ ጭሮ ወረዳ፣ ላሎ ጉዶ ቀበሌ፣ ኢፈ ባስ(ifabaas) በምትባል የገጠር መንደር ውስጥ በኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 እልፌ ተስፋ ወሌ የሚባሉ እናት በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል። በዚኹ ቀበሌና በአጎራባች ቀበሌዎች ያብዶ ሸንበቆ፣ ረብሱ፣ ሼክ አደም፣ ሉጎ በርካታ ሃይማኖትና ማንነትን ማዕከል ያደረጉ ጭፍጨፋዎች የሚካሄዱባቸው ናቸው። ብንናገርም ሰሚ የለም። ሕዝቡና ሚዲያውም እኛን ረስቶናል ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች በምሬትና በፍርኃት ተውጠው።
በወረዳው በቅርቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት የኾኑ ተፈሪ መንገሻ ከነ ባለቤቱ ቀለሟ በለጠ ጋር፣ ባለው መንገሻ፣ አሳምነው አባይነህ የተባሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በአሰቃቂ ኹኔታ በስለትና በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል። ግድያውን የሚፈጽመው በአካባቢው ሰዎች አጠራር ኦነግ ሸኔ(ራሱን ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል) ነው።
ይኽን መረጃ እያጣራን ባለንበት አፍታ በአርሲ ዞን በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፣ በቀቅሳ ቀበሌ በአጨዳ ላይ የነበሩ ከ19 በላይ ገበሬዎች ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ታፍነው መወሰዳቸውን ከቦታው ለማረጋገጥ ችለናል። በዚኹ አካባቢ በቅርቡ ወንድማማቾችን ጨምሮ ሦስት ንጹሓን እንደተገደሉ ይታወሳል።
እናት ፓርቲ በምዕራብ ሐረርጌ ባሉ በርካታ ቀብሌዎች በጥንቃቄ ተደብቆ የሚካሄድውን ጭፍጨፋና እገታ፤ እንዲኹም በአርሲ እየተካሄደ ያለውን ዘር ፍጅት በጽኑ እናወግዛለን፤ የታገቱትም ያለምንም ቅድመ ኹኔታ እንዲፈቱ እንጠይቃለን።
እናት ፓርቲ
በመቐለ ከተማ ትናንት ኅዳር 18 ምሽት 4 ሰዓት ተኩል ገደማ ልዩ ስሙ “ዓዲ ሓቂ” በሚባል አካባቢ የቦንብ ፍንዳታ መድረሱን የከተማዋ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የከተማዋ ሰላምና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ረድሀኝ ፍስሃ፣ “ሕዝብን ለማሸበር ተልዕኮ የተሰጣቸው የጥፋት ኃይሎች” ሲል የጠራቸው አካላት የቦንብ ጥቃቱን መፈጸማቸውን እና ሆኖም የቦንብ ፍንዳታው በሰው ወይም በንብረት ላይ ጉዳት እንዳላደረሠ መናገራቸውን የመቐለ ኤፍኤም ሬድዮ ዘግቧል። በቦንብ ጥቃቱ የከተማዋ ነዋሪዎች መሸበራቸውን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ፤ የጥቃቱ ዓላማ “ሁከት እና ብጥብጥ ለመፍጠር ሆን ተብሎ እና ታስቦበት የተፈጸመ ነው” ብሏል። ጽሕፈት ቤቱ፣ የጸጥታ አካላት የቦንብ ጥቃቱን ፈጻሚዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል በጋራ እየሠሩ መሆኑንም ገልጧል። መሰል ጥቃቶችን በማቀነባበር ተግባር ላይ የተጠመዱ ግለሰቦች፤ በከተማዋ ውስጥ ከፍተኛ ችግር እንደተፈጠረ በማስመስል ሃሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ ነው በማለት የከሠሠው ጽሕፈት ቤቱ፣ ሆኖም ከቦንብ ጥቃቱ ውጪ ሌላ አንዳችም ችግር አልተፈጠረም ብሏል።
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ የሦስተኛው ዓለም አገራት ዜጎች በዘላቂነት ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ለማገድ መወሰናቸውን ትናንት አስታውቀዋል። የፕሬዝዳንቱ አስተዳደር፣ ኤርትራ፣ ሶማሊያ እና ሱዳንን ጨምሮ አሜሪካ ለ19 አገራት የውጭ ዜጎች የሠጠቻቸውን የመኖሪያ እና የሥራ ፍቃዶች በድጋሚ ሊመረምር መሆኑንም ገልጧል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ አሜሪካ ውስጥ የሚኖሩ የእነዚህ አገራት ዜጎች የያዙት የመኖሪያ እና የሥራ ፍቃድ በድጋሚ እንዲመረመር ትዕዛዝ ያስተላለፉት፣ አንድ አፍጋኒስታናዊ ስደተኛ ረቡዕ’ለት ዋይትሃውስ አቅራቢያ ሁለት የአሜሪካ ብሄራዊ ዘብ አባላትን ተኩሶ ማቁሰሉን ተከትሎ ነው። የፕሬዝዳንቱ አስተዳደር ባለስልጣናት የቀድሞው ፕሬዝዳንት የጆ ባይደን አስተዳደር ያጸደቃቸውን ሁሉንም የጥገኝነት ጥያቄዎች በድጋሚ እንደሚመረምሩም ተገልጧል። በቀድሞው ፕሬዝዳንት ባይደን አስተዳደር ወቅት የገቡ ሁሉም ስደተኞች የቋሚ መኖሪያ ፍቃድ ጥያቄዎችም ለጊዜው እንዲቆሙ ተደርጓል።
የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ፍላጎቱ “የደኅንነት አመክንዮም” ሆነ “የደኅንነት ትሩፋት” የለውም ሲሉ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረመስቀል አጣጣሉ። የጉዳዩ ዋና ውዝግብ የባሕር በር አይደለም ያሉት የማነ፣ ኢትዮጵያ ለንግድ አገልግሎት አዋጭ የሆኑ ስምምነቶች ላይ ለመድረስ በርካታ አማራጮች አሏት ብለዋል። የማነ፣ “የራስን የባሕር በር ማግኘት” የሚባለው አጀንዳ ግን “አደገኛ” እና “የኢትዮጵያ ጎረቤቶችን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሚጥስ” መሆኑን ገልጸዋል። የማነ፣ ሌላኛው የብልጽግና ፓርቲ አስገራሚ የራስን የባሕር በር ጥያቄ፣ ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ ለማቋቋም ፍላጎት ያለው መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጡ ነው በማለት ተችተዋል። የንግድ ልውውጡን በቀይ ባሕር በኩል የሚያደርግ ማንኛውም አገር ቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የባሕር ኃይል ጣቢያ የማቋቋም ሕጋዊ መብት ይኖረዋል ማለት እንዳልሆነም የማነ ጠቁመዋል። ብልጽግና ፓርቲ የውጭ ወታደራዊ አዛዦች በአዲስ አበባ አንዳንድ ጊዜ የሚያደርጓቸውን “ተራ” ጉብኝቶች አጣሞ የማቅረብ አሰልቺ አካሄድ ጀምሯል በማለት የማነ አያይዘው የተቹ ሲሆን፣ ፓርቲው የአሜሪካው የአፍሪካ ወታደራዊ ዕዝ እንዲሁም የጣሊያን ባሕር ኃይል እና የፈረንሳይ ጦር ኃይል አዛዦች በኢትዮጵያ ያደረጓቸው ጉብኝቶች የባሕር በር የማግኘት ፍላጎቱን የሚደግፉ አስመስሎ አቅርቧቸዋል ብለዋል።
የታደሰ ወረደ አመራር ውድቀት ገጥሞታል፤ አዲስ መንግስት መቋቋም አለበት ሲል የትግራይ አለማቀፍ ምሁራን ስብስብ ጥሪ አቀረበ
ዋዜማ የተመለከተችው ሪፖርቱ በአቶ ጌታቸው ረዳ አመራር ወቅት ምክክር ተደርጎባቸው ትግራይ ከቀውስ ለማውጣትና የክልሉን ዘላቂ ጥቅሞች ለማስከበር የተለዩ አስር ጉዳዮች ላይ አሁን በሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ አመራር ፍፁም ተዘንግተው ክልሉን ለበለጠ አደጋና የጦርነት ስጋት ዳርገውታል ብሎ ያምናል።
ዝርዝሩን ያንብቡት-https://cutt.ly/4tymlVmv
” በማርበርግ ቫይረስ ምክንያት ከዛሬ ህዳር 20/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ1 ሣምንት ትራንስፖርት ዝግ ይሆናል” – የዞኑ መንግስት
በጂንካ ተከስቶ ለሰዎች ሞት ምክንያት እየሆነ ያለዉን የማርበርግ ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር ያስችል ዘንድ ወደ በሽታዉ መነሻ የአሪ ዞን የሚገባም ሆነ የሚወጣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ለ1 ሣምንት ዝግ እንዲሆን በአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብር ሃይል መወሰኑን የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ደምመላሽ አቦነህ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የቫይረሱ ስርጭት ከዕለት እለት አስከፊ እየሆነ በመምጣቱ የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር በአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብረሀይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኃላፊዉ እስካሁን በነበረው ሂደት ትምህርት ቤቶች የተዘጉና ፣ ሕዝብ የሚሰበሰብባቸዉ ጉዳዮች ላይ እቀባ የተጣለ ቢሆንም ስርጭቱን በሚፈለገዉ ልክ መግታት ባለመቻሉ የትራንስፖርት ዘርፉን ለ1 ሳምንት መዝጋት አስፈላጊ በመሆኑ ከዛሬ ህዳር 20/2018ዓም ጀምሮ ለ1 ሳምንት ዝግ እንዲሆን ግብረሀይሉ መወሰኑን ተናግረዋል።
ጂንካ ከተማን ጨምሮ ለሁሉም መዋቅር የትራፊክ ፍሰት እና የፀጥታ ዘርፍ አስተባባሪዎች ይህ መልዕክት መተላለፉንም አቶ ደምመላሽ አስታዉቀዋል።
በዚህ መሰረት ከክልል በወረደው አቅጣጫ መሰረት አገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ለ1 ሳምንት የታገደ ሲሆን በከተማ የሁለት እግር ተሽከርካሪዎችና የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ብሎም በዞኑ ውስጥ የሚኖሩ የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች በቀጣይ ቀናት ውስጥ ውሳኔ እንደሚሰጥባቸው ገልፀዋል።
ኃላፊው አያይዘውም በአሁኑ ወቅት የማርበርግ በሽታ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ የተከሰተ ቢሆንም ጂንካ ለቅሶ መጥቶ የተመለሰ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ በበሽታዉ መሞቱን መስማታቸዉንና የስርጭት
Posted in
Amharic News,
Ethiopia News,
News,
NRS-Import,
VIDEO ቪዲዮ,
አዉሮጳ,
አፍሪቃ,
ኢትዮጵያ,
ኤኮኖሚ,
ጀርመን,
ፖለቲካ
(መሠረት ሚድያ)- ለሁለት ዓመታት ያህል በቂሊንጦ እስር ቤት ውስጥ የቆዩት የቀድሞው የተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ አብዱረሕማን አሕመዲን፣ አቶ ግዛቸው ታምር እና አቶ መኮንን ደሳለኝ የተባሉ ተጠርጣሪዎች የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ የፀረ-ሽብር ወንጀል ምድብ ችሎት እያንዳንዳችው በሁለት መቶ ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ ትናንት ሕዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ብይን ሰጥቶ ነበረ።
ለፋኖ ድጋፍ መስጠት በሚል የተጠረጠሩት ግለሰቦቹ የተጠየቁትን የሁለት መቶ ሺህ ብር ዋስ አስይዘው ዛሬ ሕዳር 19 ቀን 2018 ዓ.ም እኩለ ቀን ሲሆን ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሲወጡ የፌደራል ፖሊሶች እና ሲቪል የለበሱ ግለሰቦች በኃይል በማስገደድ አምቡላንስ ውስጥ አስገብተው ይዘዋቸው እንደሄዱ የዐይን እማኞች ለመሠረት ሚዲያ ተናግረዋል።
አቶ አብዱረሕማን አሕመዲን
የዐይን ምስክሮቹ እንደገለፁት ሦስቱም እስረኞች እድሜያቸው የገፋ ሲሆን አንደኛው እስረኛ በሰዎች ተደግፎ ከእስር ቤት ሲወጣ እንደተመለከቱ ገልፀዋል።
የእስረኛ ቤተሰቦች ደግሞ ለሚድያችን እንደገለፁት አዲስ አበባ ሜክስኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ድረስ በመሄድ ቢጠይቁም “አየሁ የሚል የለም” ሲሉ ተናግረዋል።
የቀድሞው የኢዴፓ እና የተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ አብዱረሕማን አሕመዲን በቅርቡ ከባድ ቀዶ ሕክምና የተደረገላቸው መሆኑን እና ይህንኑ የጤና ሁኔታቸውን ምክንያት ማድረግ የከፍተኛው ፍርድ ቤት በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ በዋስ እንደለቀቃቸው የገለፁት ምንጮቻችን ዛሬ ከማረሚያ ቤት ሲወጡ ታፍነው መወሰዳቸውን አስረድተዋል።
ቀደም ሲል በተመሳሳይ መልኩ ተጠርጥረው የከፍተኛው ፍርድ ቤት በሁለት መቶ ሺህ ብር ዋስ የለቀቃቸውን አቶ ሚካኤል መላክ የተባሉ ተጠርጣሪ ፖሊስ በር ላይ
ሕዳር 17 ቀን 2018 በቀሲስ አስተርአየ ስለ ክቡር አባታችን ሐጂ ሙፍቲ ዑመር ዘለቀ የቀረበው ጦማር አምስት በተለያዩ ወቅቶች ቀሲስ አስተርአየ ያቀረቧቸውን ጦማሮች አሰናስሎ ይዟል። የሙፍቲው መልዕክቶች የተንጸባረቁበት ጦማር ከአንድ እስከ አምስት ተዘርዝረው ቀርበዋል። ጦማሮች በየተጻፉባቸው ወቅቶች የነበሩትና አሁንም ያሉት ሰዎች አቋማቸውን እየቀያየሩ እንዴት እንደሚዋሹና ሕዝብ እንደሚያሳስቱ የሚገልጹ ናቸው።
የተሰናሰሉት ጦማሮች በተዘጋጁባቸው ወቅቶች የነበሩት አሁንም አቶ ጌታቸው ረዳን ጭምር አቅጣጭቸውን እየቀየሩ ያሉትን የሰዎችን ተገለባባጭነት ባጭር ባጭሩ የሚያሳዩ ናቸው። ሙፍቲው “ሰው ሁኑ! ሰው መሆን ይቀድማል” እያሉ ያሰሙት ንግግር በአምስቱም ጦማሮች ላይ የተጠቀሱትን ሰዎች ሁሉ ሰዎች አለመሆናቸውን የሚመሰክሩ ናቸው፡፡ ስለ ሙፍቲው የቀረበችውን ጦማር ካነበባችሁ በኋላ ከ 1 እስከ 5 የተደረደሩትን ሊንኮችን በማንበብ የራስችሁን ግንዛቤ አዳብራችሁ ፖለቲካው ቤተ ክህነቱን እንዴት መጠቀሚያ እንዳደረገው ትረዳላችሁ።
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ የጊራራው ንጉሥ
11 ክርስቲያኖች በምሥ/ አርሲ ተገደሉ
በምሥራቅ አርሲ እንቆሎ ዋቤ ወረዳ በመጭቱ በቀቅሳ ቀበሌ ነዋሪዎች የነበሩ አሥራ አንድ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች መገደላቸውን ምንጮች ለአደባባይ ሚዲያ ተናግረዋል።
ሕዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም መገደላቸው የተረጋገጠው ክርስቲያኖች በነፍሰ ገዳዮቹ ታግተው ተወስደው እንደነበር ምንጮቻችን ገልጸውልናል።
በርካታ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የሚኖሩበት ቤት ‘መሬት ባንክ ገብቷል’ እየተባሉ የቤት ሽያጭ፣ እድሳት እና ስም ማዞር መከልከላቸው ተሰማ
ከ16 ሺህ በላይ ቤቶች መሬት ባንክ መግባታቸው የታወቀ ሲሆን ጉዳዩ ያጋጠማቸው ነዋሪዎች ህዝቡ በየክፍለ ከተማው እየሄደ ቼክ እንዲያስደርግ መክረዋል
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/be1
ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ኡጋንዳ የአፍሪካ ቀንድ አገራት ከሆኑት ከኢትዮጵያ፣ ከኤርትራ እና ከሶማሊያ ለሚመጡ ሰዎች የስደተኝነት ምዝገባ ማቆሟን አስታወቀች።
የኡጋንዳ እርዳታ፣ የአደጋ ዝግጁነት እና የስደተኞች ሚኒስትር ሂላሪ ኦኔክ እንደተናገሩት ሠራተኞቻቸው ከሦስቱ አገራት የሚመጡ ስደተኞችን እንዳይመዘገቡ ማዘዛቸውን እና ለዚህም ምክንያቱ “በአገራቱ ውስጥ ድጋፍ ስለሌለ” መሆኑን ጠቅሰዋል።
ይህ የሚኒስቴሩ ውሳኔ የተሰማው ወደ ኡጋንዳ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበት እና ከለጋሾች ለስደተኞች ተብሎ የሚመጣው ድጋፍ በመቀነሱ እንደሆነ የኡጋንዳ ዘ ዴይሊ ሞኒተር ዘግቧል።
ቀደም ባሉት ዓመታት ከሦስቱ አገራት የሚወጡ ስደተኞች መዳረሻ ኬንያ የነበረች ሲሆን፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ኡጋንዳን የተሻለች አድርገው በመምረጣቸው በርካታ ስደተኞች ከኢትዮጵያ፣ ከኤርትራ እና ከሶማሊያ ወደ አገሪቱ እየገቡ ነው።
የአሁኑ የእገዳ ወሳኔ አዲስ የሚመጡ ሰደተኞችን የሚመለከት እንጂ ቀደም ሲል ወደ ኡጋንዳ በመግባት የተመዘገቡትን የሦስቱን አገራት ሴጎች የሚመለከት እንዳዳልሆነ ተገልጿል።
ሚኒስትሩ እስካሁን ወደ ኡጋንዳ የገቡት ስደተኞች ቁጥር ወደ ሁለት ሚሊዮን እየደረሰ አና በየዕለቱ እየጨመረ መሆኑን አመልክተው፤ በየቀኑ “በአንድ መቶ እና በ200 መካከል የሚቆጠሩ ሰደተኞች ከዲሞክራቲክ ኮንጎ ብቻ” ወደ ኡጋንዳ ይገባሉ” ብለዋል።
ኡጋንዳን በበርካታ ስደተኞች ተመራጭ የሆነችው ስደተኞች በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ፣ በሥራ እና በንግድ አንዲሰማሩ ከመፍቀዷ በተጨማሪ ለዜጎች የተፈቀዱ አገልግሎቶች መጠቀም ስለሚችሉ ነው።
ሚኒስትሩ እንዳሉት ኡጋንዳ ስደተኞችን ለመደገፍ በየዓመቱ ሁለት ቢሊዮን ሽልንግ (የኡጋንዳ ገንዘብ) ታወጣለች።
አሁን ኡጋንዳ እንዳይመዘገቡ እገዳ የጣለችባቸው የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ እና የሶማሊያ ስደተኞች በዋናነት በፖለቲካዊ ምክንያቶች፣ በጦርነት እና የአገራቸውን መንግሥታት
የፌደራሉ ዓቃቤ ሕግ በቀድሞው የሠላም ሚንስትር ዴኤታ ታዬ ደንደአ ላይ ሦስት አዲስ ክሶች መመስረቱ ተሰማ ። ዓቃቤ ሕግ በታዬ ላይ አዲስ ከመሠረታቸው ክሶች መካከል አንዱ፣ የሕወሃት ኃይሎች በ2013 ዓ፣ም በመከላከያ ሠራዊት ሰሜን እዝ ላይ በፈጸሙት ጥቃት ዙሪያ ተከሳሹ ሃሰተኛ መረጃ እና ፕሮፓጋንዳ አሰራጭተዋል የሚል እንደሆነ የታዬ ጠበቃ አበራ ንጉሥ ተናግረዋል። ሌሎቹ ሁለት ክሶች ደሞ፣ ከጸረ ሠላም ኃይሎች ጋር በማበር መንግስታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ ማሴር እና ድጋሚ ከመታሠራቸው በፊት “ሆርን ኮንቨርሴሽን” ለተሰኘ የበይነ መረብ ጣቢያ በሰጡት እና እስር ላይ ሳሉ በሦስት ክፍሎች በተላለፈው ቃለ ምልልሳቸው “የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ የሚጥል የተሳሳተ መረጃ አሰራጭተዋል” የሚሉ መሆናቸውን ጠበቃቸው ነግረውናል። ፍርድ ቤቱ፣ በአዲሶቹ ክሶች ላይ የተከሳሹን መልስ ለመስማት ለኅዳር 23፣ 2018 ዓ፣ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን አስረድተዋል።
በምርጫ ቦርድ ሕጋዊነቱ የተሰረዘበት ሕወሃት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አደራዳሪ አካል የስምምነቱን አተገባበር እና የሌላ ዙር ጦርነት ስጋትን ለመገምገም በአስቸኳይ እንዲሰበሰብ ጥሪ አቀረበ። የሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ከኅዳር 8 እስከ 13 ያካሄደውን ስብሰባ ማጠናቀቁን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፣ አፍሪካ ኅብረት እና ስምምነቱ እንዲፈረም አስተዋጽኦ ያደረጉ አገራት እና ዓለማቀፍ ድርጅቶች ስምምነቱ ከምንጊዜውም በበለጠ አደጋ ላይ መውደቁን እንዲገነዘቡ አሳስቧል። ፌደራል መንግስቱ የታጠቁ ቡድኖችን በማደራጀት እና በማስታጠቅ የግጭት ማቆም ስምምነቱን ጥሷል በማለት የከሰሰው የሕወሃት መግለጫ፣ መንግሥት ተጨማሪ ጥፋት ከሚያስከትል ሌላ ዙር ጦርነት እንዲቆጠብ፣ በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሰረት ግዴታውን ለመወጣት ከሕወሃት እና ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በመተባበር እንዲሰራ እና የትግራይን ሕዝብ በርሃብ ለማጥቃት እና ወደ አመጽ ለመግፋት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ ሕወሃት ማሳሰብ ይፈልጋል ብሏል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት በትግራይ ኃይሎች ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት “በከፍተኛ የፖለቲካ ውሳኔ” የተፈጸመ መሆኑን ያመለክታል በማለትም ሕወሃት መንግሥትን ከሷል።
የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ በባሕር በር ዙሪያ መግለጫዎችን በማውጣት ኢትዮጵያን የቀይ ባሕር ቁልፍ ባለድርሻ እንድትሆን የሚያደርገው ሙከራ “የማይሳካ”ነው ሲል አጣጥሏል። ሚንስቴሩ፣ ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሚቀርቡት “የኢኮኖሚ አስገዳጅነት”፣ “የደኅነት” እና “የታሪክ” መከራከሪያዎች የማያዛልቁ ናቸው ብሏል። ሚንስቴሩ፣ ኢትዮጵያ የአፋርን ሕዝብ ማንነት በመጥቀስ፣ በኤርትራ ሉዓላዊ የባሕር ዳርቻ ላይ የተፈጥሮ መብት አለኝ ለማለት ትፈልጋለች በማለት ተችቷል። የሁለት አገር ሕዝቦች ዝምድና የባሕር በር ለመቆጣጠር በማስረጃነት ቢወሠድ ኖሮ ኦጋዴንም ወደ ሶማሊያ ሊጠቃለል ይችላል ያለው ሚንስቴሩ፣ የኢትዮጵያ የቆዳ ስፋትም የባሕር በር ባለቤትነት ሊያጎናጽፋት አይችልም በማለት ሞግቷል። ሚንስቴሩ፣ ኤርትራ ነጻ አገር የኾነችው ኢትዮጵያን የባሕር በር ለማሳጣት አልባ ለማድረግ ነው የሚለው መከራከሪያም፣ ሐሰተኛ እና ትርጉም አልባ ነው በማለት ተችቷል።
የግብጽ የውሃና መስኖ ሚንስቴር፣ ኢትዮጵያ ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ በተናጥል እና ባልተቀናጀ ሁኔታ ከፍተኛ ውሃ በመልቀቅ ችግር እየፈጠረች ትገኛለች በማለት ሰሞኑን አዲስ ክስ አቅርቧል። የግድቡ የውሃ አለቃቅ ተለዋዋጭነት በግድቡ ላይ ቴክኒካዊ እና ሳይንሳዊ አስተዳደር እንደሌለ ያሳያል በማለት የተቸው ሚንስቴሩ፣ ግብጽ በዚሁ ሳቢያ ከአስዋን ግድብ የቶሽካ ማስተንፈሻን ለመክፈት ተገዳለች ብሏል። ሚንስቴሩ “ያልተቀናጀ” እና “ሳይንሳዊ ያልሆነ” ያለው የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ የውሃ አለቃቀቅ፣ በታችኛው ተፋሰስ አገራት ግድቦች ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል በማለትም ወቅሷል። በተያዘው ኅዳር ወር ሦስት ሳምንታት ውስጥ ከሕዳሴ ግድብ በቀን የተለቀቀው ውሃ 180 ሚሊዮን ሜትር ኪውብ መሆኑንና ይህም በዚህ ወቅት ቀደም ባሉት ዓመታት ይለቀቅ ከነበረው የውሃ መጠን በ80 በመቶ እንደሚበልጥ ሚንስቴሩ ጠቅሷል።
በሞያሌ ፖሊስ ጣቢያ (OB No. 32/22/11/2025) በቀረበው ይፋዊ ሪፖርት መሠረት፣ የኬንያ ፖሊስ፣ የአስተዳደር ፖሊስ አገልግሎት እና የድንበር ፓትሮል ክፍል መኮንኖች ወደ ውስጥ የገቡትን የአብይ አሕመድ ኃይሎች ለሁለት ሰዓታት ያህል በዘለቀ ግጭት ተዋግተዋል።
የኬንያ መከላከያ ሰራዊት በኋላ ላይ ወደ ዘመቻው ተቀላቅሎ፣ ቡድኖቹም አብረው የአብይን ወታደሮች ወደ ድንበር መስመር መልሰው ማስወጣት ችለዋል። የአብይ አሕመድ መከላከያ ሰራዊት (ENDF) ሕገ-ወጥ በሆነው ድርጊት ለምን እንደተሳተፈ ግልጽ አይደለም።
በልውውጡ ወቅት በርካታ ዙሮች ተተኩሰዋል፣ ነገር ግን በኬንያ መኮንኖች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም።
ይሁን እንጂ፣ ያልተረጋገጡ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት ቀደም ሲል በድንበር ላይ የኬንያ ቡድንን ያካተተ ነው ተብሎ የተነገረው በኢትዮጵያ በኩል የተፈፀመ ገዳይ የተኩስ ልውውጥ ወረራውን አስከትሎ ሊሆን ይችላል፣ ይህም በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ግንኙነት ሊጎዳ ይችላል።
ሁኔታው አሁንም ውጥረት የነገሠ ሲሆን የኬንያ ዲኤፍ ዋና አዛዥ ጄኔራል ቻርለስ ካሃሪሪ ከኢትዮጵያ አቻው ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር የመከላከያ ትብብር ስምምነት በአዲስ አበባ ከተፈራረሙ ከጥቂት ወራት በኋላ ነው። ኬንያ እና ኢትዮጵያ በደህንነት ጉዳዮች ላይ የቅርብ አጋር ናቸው። GAROWE ONLINE
በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ አማራዎች አገዛዙ በህዝባቸው ላይ የሚፈፅመውን ግፍና ሰ’ቆቃ በማውገዝ አደባባይ ወጥተዋል …. የቡድን 20 አባል ሀገራት ስብሰባ በሚደረግበት አዳራሽ ፊለፊት በተካሄደው በዚህ ተቃውሞ ላይ ” Stop Amhara Genocide, Stop the hidden Amhara Genocide in Ethiopia , We demand Immediately Intervene & Stop Military Aggression into Amhara Region, …etc ” የመሳሰሉት መልዕክቶች ተስተጋብተዋል……… ይህ ከአማራ ህዝብ አብራክ የተገኙና በመላው አለም የሚገኙ ወገኖቻችን በሙሉ ፣ በህዝባቸው ላይ ለ7 አመታት ያለእረፍት የሚፈፀመውን ግፍና ሰቆቃ ለአለምአቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ በየጊዜው ሊያከናውኑት የሚገባውና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት የትግላችን አንዱ ፈርጅ መሆኑ ሊሠመርበት ይገባል! ……… … https://x.com/i/status/1992873321801605627