Blog Archives
የህክምና ባለሙያዎችን ድምፅ ያስተጋቡ አንድ ዶክተር ከድሬዳዋ ከተማ ተሰናብተው ገጠር ሄደው እንዲሰሩ ተወሰነባቸው
የድሬዳዋ ጤና ባለሞያዎች ድርጊቱን ተቃውመው ፊርማ ማሰባሰብ ጀምረዋል
(መሠረት ሚድያ)- በድሬዳዋ ከተማ በሚገኘው ሳቢያን አጠቃላይ ሆስፒታል ሰራተኛ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት እና ከሰሞኑ የጤና ባለሙያዎች ያሰሙትን ድምፅ ያስተጋቡ አንድ ጠቅላላ ሐኪም የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸው ገጠር ሄደው እንዲሰሩ እንደተወሰነባቸው ታወቀ።
መሠረት ሚድያ የተመለከተው እና ሚያዝያ 9/2017 ዓ/ም በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ የተፃፈው ደብዳቤ ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ የተባሉት እኚህ የጤና ባለሙያ ‘የሙያ ስነምግባርን የተፃረረ ድርጊት’ መፈፀማቸውን ጠቅሶ ጉዳዩ ባለመታረሙ አሁን ከሚሰሩበት የድሬዳዋው ሳቢያን ሆስፒታል ወደ ለገኦዳ ጉዱንፈታ ጤና ጣብያ እንዲዛወሩ መደረጋቸውን ይገልፃል።
“የዛሬ ወር ገደማ ቋሚ ቅጥር ከሳቢያን ሆስፒታል ጋር ፈፅሜያለሁ። ይህ ሆኖ እያለ ከሰሞኑ እኛ የኢትዮጵያ የጤና ተቋማት ሰራተኞች ድምፅ እያሰማን መሆኑን ተከትሎ እኔም አንዳንድ ፅሁፎችን ስላወጣሁ ኢላማ ተደርጌያለሁ” ያሉት ዶ/ር ሀብታሙ ውሳኔው ከመተላለፉ በፊት ባሉት ቀናት ስልክ እየተደወለ በጤና ባለሙያዎች እንቅስቃሴ ዙርያ አስተያየት እንዳይሰጡ ማስፈራርያ ሲደርሳቸው እንደነበር ጠቅሰዋል።
“እኔ በበኩሌ ጉዳዩ የመኖር እና አለመኖር መሆኑን ጠቅሼ እንደማላቆም ነገሬያቸዋለሁ። የከተማው ጤና ቢሮ ሀላፊ የሆኑትን ዶ/ር ፅጌረዳን ለማናገር ብሞክርም ያልተገባ ነገር ተናግረውኝ ስልክ ዘግተውብኛል” የሚሉት የጤና ባለሙያው ከዚያም እኚህ ሀላፊ ዶ/ር ሀብታሙ ወደሚሰሩበት ሆስፒታል በመደወል ከስራቸው እንዲታገዱ ማድረጋቸውን መስማታቸውን ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
ዶ/ር ሀብታሙ በቅርቡ ‘Hakim’ የተባለ የፌስቡክ ገፅ ላይ በርካቶች የተመለከቱት አንድ ፅሁፍ አጋርተው የነበረ
በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አዲስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የሚመረጡት በመንበር ላይ ያሉት ጳጳስ ሲሞቱ ወይም ከፖፕ ፍራንሲስ በፊት የነበሩት ቤኔዲክት 16ኛ እንዳደረጉት በፈቃዳቸው መንበራቸውን ሲለቁ ነው።
ተተኪው ጳጳስም በዓለም ዙሪያ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ተከታይ ያላት የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ በመሆን የመሪነቱን መንበር ይረከባሉ።
በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከጳጳሱ በታች ከፍተኛ ሥልጣን ያላቸው ካርዲናሎች ከመካከላቸው የቤተ ክርስቲያኗ መሪ ሊሆኑ የሚችሉትን አዲሱን ጳጳስ ይመርጣሉ።
በዓለም ዙሪያ 252 የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ካርዲናሎች ያሉ ሲሆን፣ ከመካከላቸው በአዲሱ የጳጳስ ምርጫ ላይ የሚሳተፉት ከ80 ዓመት በታች የሆኑት ብቻ ናቸው።
የእነዚህ በጳጳስ ምርጫ ላይ የሚሳተፉት ካርዲናሎች ቁጥር አብዛኛውን ጊዜ በ120 የተገደበ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ግን ቁጥራቸው 135 ይደርሳል።
በኢትዮጵያ “ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለረሃብ” መጋለጣቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስታወቀ
የእርግዝና መከላከያ ክኒን በእርግጥ ሴቶችን የበለጠ እንዲጨነቁ ሊያደርግ ይችላል?
ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ፑቲን ጠቆሙ
https://flo.uri.sh/visualisation/22782656/embed?auto=1
ኢትዮጵያዊው ካርዲናል ማን ናቸው?
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ካርዲናል የሆኑት ብርሃነየሱስ ሱራፌል ሟቹን ፖፕ ፍራንሲስን በመተካት በዓለም ዙሪያ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ተከታዮች ያሏትን ቤተክርስቲያን የሚመሩትን አዲስ ጳጳስ በመምረጥ ከሚሳተፉት መካከል ናቸው።
የአዲስ አበባ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ካርዲናል ብርሃነየሱስ 76 ዓመታቸው ሲሆን፣ በአገር ውስጥ እና በውጪ በከፍተኛ ደረጃ መንፈሳዊ ትምህርትን ተከታትለዋል።
በአውሮፓውያኑ 1976 በኢትዮጵያ ውስጥ የቅስና ማዕረግን ተቀብለው ከሦስት ዓመት በኋላ ለአንድ ዓመት በወታደራዊው መንግሥት ታስረው ቆይተዋል።
ከእስር ከወጡ በኋላ ወደ
በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሐሙስ ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም. በትምህርት ቤት ዙሪያ በደረሰ የድሮን ጥቃት ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።
በዞኑ እናርጅ እናውጋ ወረዳ ገደብ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ የትምህርት ቤት አጥር ለማጠር እና ቤት ለመሥራት ‘ለልማት ሥራ’ የወጡ “ሰላማዊ ሰዎች” በጥቃቱ መገደላቸውን ገልፀዋል።
የአካባቢው አስተዳደር ግን ጥቃቱ በአካባቢው ተሰብስበው በነበሩ የፋኖ ታጣቂዎች ላይ እንጂ በንፁሃን ነዋሪዎች ላይ አለመፈጸሙን ለቢቢሲ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተፈጸመ ስለተባለው ጥቃት ክትትል እያደረገ መሆኑን አመልክቷል።
ነዋሪዎች ለቢቢሲ እንደተናገሩት “ተሰብስበው” በከተማዋ ያለው ገደብ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አጥርን እያጠሩ በነበሩ የሰዎች ላይ ነው ጥቃቱ የተፈፀመው።
MORE : https://www.bbc.com/amharic/articles/cq80gz2wv4wo

(ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም/ April 23/2025):- ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን በማስመልከት ባስተላለፉት ትምህርት ዙሪያ ተወያየ።
ቋሚ ሲኖዶስ ዛሬ ማለዳ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ባለፈው አርብ በስቅለት ዕለት በፎኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በቅድስት ድንግል ማእያም ዙሪያ ያስተላለፉትን ትምህርት በተመለከተ ውይይት አድርጓል።
ብፁዕነታቸው የተላለፈውን ትምህርት ዝርዝር ሁኔታን በመመርመርም ውሳኔ ለማስተላለፍ ይቻል ዘንድ ሁሉም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት በተገኙበት ለሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ ማለትም ሚያዝያ ፳፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም (April 30/2025) ቀጠሮ ተይዟል።
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ በኢትዮጵያ እና ኬንያ ሊያደርጉት የነበረውን ጉብኝት መሰረዛቸው ተዘግቧል።
ጉብኝታቸውን መሰረዛቸውን ያሳወቁት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ወደ ቤጂንግ ለጉብኝት ማምራታቸው ከተዘገበ በኋላ መሆኑ ተነግሯል።
ማርክ ሩቢዮ የአፍሪካ የመጀመሪያ ጉብኝታቸውን በሁለቱ ሃገራት እንደሚጀምሩ አቅደው የነበረ ሲሆን ዕቅዳቸውን ማራዘማቸው ተዘግቧል።
Source: Africa intelligence
ለ650 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሲደርስ የነበረ የምግብ እርዳታ ሊቆም መሆኑ ተሰማ
(መሠረት ሚድያ)- የአለም ምግብ ፕሮግራም (World Food Programme) 10 ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ርሀብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ችግር አጋጥሟቸው እንደሚኝ ገልፆ ይህ እየሆነ ባለበት ወቅት በገንዘብ እጥረት ምክንያት ለ650 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሲያደርስ የነበረውን የምግብ እርዳታ ሊያቆም መሆኑን ዛሬ አስታውቋል።
ከእነዚህ መሀል 3 ሚልዮን የሚሆኑት በጦርነት እና በከባቢ አየር ጠባይ መቀየር ምክንያት ተሰደው የሚገኙ መሆናቸውን የጠቆመው ይህ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አካል የሆነ ተቋም 4.4 ሚልዮን የሚሆኑ እርጉዝ እና አጥቢ እናቶች እንዲሁም ህፃናት በከፍተኛ ደረጃ ለረሀብ ተጋልጠው ይገኛሉ ብሏል።
“በኦሮሚያ፣ ሶማሌ፣ ትግራይ እና አፋር የህፃናት በምግብ እጥረት መዳከም ተከስቷል” ያለው የአለም ምግብ ድርጅት በኢትዮጵያ እና በቀጠናው ባሉ ሀገራት ያሉ ግጭቶች ችግሩን እያባባሱ እንደሚገኙ ይፋ አድርጓል።
ይህም አልበቃ ብሎ በመጪዎቺ ወራት በደቡብ-ምስራቅ ኢትዮጵያ ዝቅተኛ የዝናብ መጠን የተተነበየ ሲሆን ይህም በሶማሌ ክልል ድርቅ እንዳያስከትል እንደተፈራ ጨምሮ ገልጿል።
በአማራ ክልል የቀጠለው ግጭት፣ የእርዳታ እህል የጫኑ ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈፀም ዝርፊያ መሬት ላይ ያሉ ችግሮች ተብለው በዛሬው መግለጫ ላይ የተነሱ ሲሆን የአለም አቀፍ እርዳታ መቀነስ በዋናነት ተጠቅሷል።
“አዲስ እርዳታ ካልተገኘ በቀር ለ3.6 ሚልዮን ኢትዮጵያውያን የምናቀርበውን እርዳታ በመጪዎቹ ሳምንታት ለማቋረጥ እንገደዳለን፣ አሁን ላይ ለ650 ሺህ ሰዎች ስናደርስ የነበረውን የነፍስ አድን እርዳታ እያቆምን ነው” ብሏል በመግለጫው።
ይህ አሳሳቢ ክስተት እንደ ቢቢሲ እና አልጀዚራ ባሉ አለም አቀፍ የሚድያ ተቋማት ሽፋን ቢያገኝም
በአባ ገብርኤል የስሕተት ‘ስብከት’ ላይ የቀረበ ሙሉ ትችት
(መምህር Arega Abate (ዶ/ር) እንደጻፈው)አባ ገብርኤል ከውጭ ወደ ውስጥ ያስተጋቡትን ትችት አዘል፣ በስሕተት የተሞላውን ስብከታቸውን በተመለከተ ትናንት ማታ ከመምህር በረከት ጋር በነበረን የቲክቶክ መርሐ ግብር በሰፊው ዳስሰነዋል፡፡

በዚህ ጽሑፍ በጥልቀት የዳሰስንባቸውን ነጥቦችና ዋና ዋና ትችታቸውን በቲክቶክ ላይ በነበረው ውይይታችን ያነሣነው ቢሆንም ያንን ላልተከታተሉትም ጭምር ይሆን ዘንድ አሰናድቸዋለሁና ተጋበዙ፡፡
በነገራችን ላይ ለሊቀ ጳጳሱ የተሰጡ መልሶች ላይ እስከአሁን ባደረኩት ዳሰሰ፣ ‘እመቤታችን ቤዛዊተ ዐለም አይደለችም’ ከሚለው ትችታቸው ውጭ ጠቅላላ ስብከታቸውን ተመልክተው በዚያ ስብከት በኩል ከውጭ ወደ ቤተ ክርስቲያን የተጮኹ የሌላ አካል ድምጾችን በተመለከተ ትችትና አስተያየት ሲሰጥ አላየሁም፡፡
ርብርቡንና የሁሉንም ጥረት ባደንቅም ሁሉም የተረባረበው አንድ ጉዳይ ላይ ብቻ መሆኑ ጉዳዩን ሙሉዕ እንዳይሆን አድርጎታል ባይ ነኝ፡፡ ለዚያ ነው ይኸንን ጽሑፍ ጨርሶ ማንበብ ጉዳዩን በጥልቀት ለመረዳትና የሊቀ ጳጳሱን መልእክት በጠቅላላው ለመረዳት ሊያግዝ ይችላል የምለው፡፡
ሙሉ ቪዲዮውን ተመልክቼ ስጨርስ አባ ገብርኤል ያቀረቧቸው ነቀፋዎች አንድ ቤተ ክርስቲያንን ‘ቤቴ፣ መጠጊያ፣ አካሌ’ ከሚል አባት ወይም መምህር ሳይሆን፣ ቤተ ክርስቲያንን፣ ‘ጠላት፣ ሌላ፣ ውጭ’ አድርገው ከሚያዩት፣ ተሐዲሶና ፕሮቴስታንት በተደጋጋሚ የሚጮኹትን ጩኸትና እነሱን ተክተው፣ መስለውና አህለው የጮኹት ነው የሚል መደምደሚያ ላይ ነው ያደረሰኝ፡፡
መግቢያ
ስብከቱን የሰበኩት አባ ገብርኤል የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሲሆኑ፣ የሰበኩበት ቦታ ደግሞ ባለሃብቱ አቶ ጸጋየ ለስቅለት ባዘጋጀው የአዳራሽ መርሐ ግብር ላይ ነው፡፡ እኔ የተመለከትኩት ስብከት የ51 ደቂቃ ቪዲዮ ነው፡፡
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ ማርክ ሩቢዮ በአፍሪካ የመጀመሪያ ጉብኝታቸውን ለማድረግ ዝግጅት ላይ መሆናቸው ተዘገበ።
ኃላፊው በመጀመሪያ ጉብኝታቸው ኬንያን እና ኢትዮጵያን እንደሚጎበኙ ተነግሯል።
ማርክ ሩቢዮ መጀመሪያ ወደ ናይሮቢ ካመሩ በኋላ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተነግሯል።
በጉብኝታቸው ወቅትም ማርክ ሩቢዮ ከሁለቱ ሃገራት መሪዎች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ተዘግቧል።
የውጪ ጉዳይ ኃላፊው ከወራት በፊት ከኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በስልክ መወያየታቸው ይታወሳል።
Source: Africa Intelligence
ናይጀሪያ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የፍርደኛ እስረኞች ልውውጥ የመግባቢያ ስምምነትን ባስቸኳይ እንዲፈርም መጠየቁን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
የናይጀሪያ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደኤታ ቢያንካ ኦጁኩ፣ በአቡጃ ከኢትዮጵያ አምባሳደር ለገሠ ገረመው ጋር ሰሞኑን በተወያዩበት ወቅት፣ ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ያላቸውን ጨምሮ በአዲስ አበባ ወህኒ ቤቶች የሚገኙ ናይጀሪያዊያን የተያዙበት ሁኔታ መንግሥታቸውን እንዳሳዘነ መናገራቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱን ለመፈረም ለመፈረም ዳተኝነት ማሳየቱንም ኦጁኩ ተችተዋል ተብሏል።
በቅርቡ አንድ ናይጀሪያዊ እስረኛ በአዲስ አበባ ወህኒ ቤት ውስጥ ሕይወቱ ማለፉንም ሚንስትር ደኤታዋ ለአምባሳደሩን ማንሳታቸውን የዜና ምንጮቹ ዘግበዋል።
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ፣ ጀኔራል ታደሠ ወረደ እንደገና ያዋቀሩት ካቢኔ ሌሎችን ያገለለ፣ አቃፊ ያልኾነና ተቀባይነት የሌለው ነው በማለት ተቃውሟል።
ካቢኔው የተዋቀረው፣ የአንድን ቡድንና የወታደራዊ አዛዦችን ፍላጎት ብቻ በመስማት ነው ያለው ቡድኑ፣ የካቢኔው አወቃቀር ባስቸኳይ እንዲስተካከል ጠይቋል።
በጊዜያዊ አስተዳደሩ አወቃቀር ላይ ማስተካከያ ካልተደረገ ግን፣ የትግራይን ሕዝብ ከ”ኋላቀሩ ገዢ” ቡድን ለማላቀቅ ማናቸውንም የትግል ስልት ለመከተል እንገደዳለን በማለት አስጠንቅቋል።
ጀኔሬል ታደሠ የአዲሱን ካቢኔ ዝርዝር ይፋ ባያደርጉም፣ በደብረጺዮን የሚመራው የሕወሓት ክንፍ ምክትል ሊቀመንበር አማኑዔል አሠፋን ምክትል ፕሬዝዳንት ኾነው እንደተሾሙ ተሠምቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የታክሲ ተራ አስከባሪ ማኅበራት ከገቢያቸው 20 በመቶውን ለመንግሥት እንዲሰጡ የሚያስገድድ ደንብ አጽድቋል።
ደንቡ ማኅበራቱ “ዝግ እና መደበኛ የባንክ አካውንት” እንዲከፍቱና ከሁለት ዓመት በኋላ “ወደ ሌላ የሥራ ዘርፍ እንዲሸጋገሩ” ግዴታ ይጥላል።
“የተርሚናል አገልግሎት አሠራርና ቁጥጥር” የተሰኘው ደንብ፣ ኢንተርፕራይዝ በማለት የሠየማቸው ማኅበራት የሚደራጁት በከተማዋ የሥራና ክህሎት ቢሮ መስፈርት መኾኑን ዋዜማ ተረድታለች።
ኢንተርፕራይዞቹ 30 በመቶ “የግዴታ ቁጠባ” መቆጠብ፣ 50 በመቶውን በተንቀሳቃሽ የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥና ያንድ ዓመት ውል መፈረም እንዳለባቸውም ይደነግጋል።
በሱማሊያዋ ፑንትላንድ ራስ ገዝ የኢትዮጵያ ቆንስላ ውስጥ ተመድበው ይሠሩ የነበሩት ኢትዮጵያዊው ዲፕሎማት ፋራህ አይዲድ ጃማ ከሱማሌላንድ ራስ ገዝ በቅርቡ በተነጠለችው “ኤስ ኤስ ካቱሜ” ግዛት ላስ አኖድ ከተማ ውስጥ በጥይት ተመትተው ሕይወታቸው ማለፉን የሱማሊያ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
የግዛቲቷ ባለሥልጣናት፣ ግድያውን የፈጸሙት የአልሸባብ አባላት ሳይኾኑ አይቀርም የሚል ጥርጣሬ እንዳላቸው ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።
በዲፕሎማቱ ሕልፈት ዙሪያ የግዛቲቱ ባለሥልጣናት ምርመራ እያደረጉ እንደኾነ ተገልጧል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ በዲፕሎማቱ ሕልፈት ዙሪያ በይፋ ያለው ነገር የለም።
የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት፣ ከሶማሌላንድ መገንጠል እንፈልጋለን ያሉ የጎሳ ሚሊሻዎች ከደም አፋሳሽ ውጊያ በኋላ የመሠረቷትን “ኤስ ኤስ ካቱሜ” ግዛት፣ ባለፈው ሳምንት የፌደሬሽኑ አባል ግዛት አድርጎ መቀበሉን ማወጁ ይታወሳል።
“ ራሳችንን ለአዲሱ የታሪፍ ስርዓት በሚገባ ለማዘጋጀት፣ የ90 ቀናት የእፎይታ ጊዜው እንደሚራዘም ተስፋ እናደርጋለን” – ማሕሙድ ዓሊ ዩሱፍ
የአፍሪካ ሕብረት በአሜሪካ በተጣለው አዲስ ቀረጥ ላይ ስጋቱን ገለፀ።
የአፍሪካ ህብረት፣ የፕረዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በአፍሪካ ሀገራት ላይ የጣለው አዲስ ቀረጥ እንዳሳሰበው አስታወቀ፡፡
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሕሙድ ዓሊ ዩሱፍ፣ ፕረዝደንት ትራምፕ ያኖሩት አዲስ ታሪፍ/ቀረጥ፣ በአፍሪካ ሀገራት ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ስጋታቸውን ገልፀዋል፡፡
“ አሜሪካ በአፍሪካ ምርቶች ላይ የጣለችው አዲስ ቀረጥ፣ የአባል ሀገራቱን ኢኮኖሚ ያዳክማል ” በማለትም አክለዋል፡፡
ፕረዝደንት ትራምፕ ያሳለፉት አዲስ የቀረጥ ውሳኔ፣ ከቻይና በስተቀር፣ በሌሎች ሀገራት ዘንድ ከሶስት ወራት በፊት እንዳይተገበር፣ ወይም ለ90 ቀናት ሳይተገበር እንዲቆይ አዘዋል፡፡
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበሩ ማሕሙድ ዓሊ ዩሱፍም ፤ የአፍሪካ ሀገራት ውሳኔውን ለመተግበር በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ፣ ለ90 ቀናት እንዳይተገበር የተላለፈው ውሳኔ፣ ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ እንዲራዘም ጠይቀዋል፡፡
“ ራሳችንን ለአዲሱ የታሪፍ ስርዓት በሚገባ ለማዘጋጀት፣ የ90 ቀናት የእፎይታ ጊዜው እንደሚራዘም ተስፋ እናደርጋለን ” ሲሉም ገልፀዋል ሊቀመንበሩ፡፡
የፕረዝደንት ትራምፕ አዲስ የቀረጥ ፖሊሲ፣ በተለይም እ.ኤ.አ ከ 2000 ዓ.ም ጀምሮ የአገዋ ዕድል ተጠቃሚዎች የሆኑ 32 የአፍሪካ ሀገራትን ይበልጥ ሊጎዳ እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡
የአፍሪካ ሀገራት፣ እንዲህ ዓይነት ችግሮችን ለመቋቋም እንዲችሉ፣ የታሪፍ ከለላዎችን የማስወገደውን የአፍሪካ አህጉራዊ የነፃ ንግድ ስምምነትን (AfCFTA) ትግበራ እንዲያፋጥኑም ሊቀመንበሩ በአፅንኦት ጠይቀዋል፡፡
የአህጉራዊው የነፃ ንግድ ስምምነት መተግበር፣ ከሌላው ክፍለአለም የሚመጡ መሰል ተግዳሮቶችን ለመቋቋም ያስችላል ሲሉም ገልፀዋል፡፡
የቀድሞው ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም አውሮፕላን ነበራቸው?
ኢትዮጵያ ቼክ- የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ኮ/ል መንግስቱ ኀይለ ማርያም ይጠቀሙበት የነበረ ዳሽ ፋይፍ (ቡፋሎ) አውሮፕላን በአየር ኃይል የጥገና ሰራተኞች የጥገና ሥራ ተሰርቶለት ከ37 ዓመት በኋላ ለበረራ መብቃት መቻሉ በዛሬው እለት በመንግስት ሚድያዎች በስፋት ተዘግቦ ነበር።
እነዚህ ሚድያዎች በዘገባቸው ላይ “የቀድሞው ፕሬዝደንት መንግስቱ ኀይለ ማርያም አውሮፕላን” የሚል መረጃ ደጋግመው ሲጠቀሙ ታይተዋል፣ ይህም በበርካታ ህዝብ ዘንድ “ኮ/ል መንግስቱ ራሳቸው ብቻ የሚበሩበት (Presidential) አውሮፕላን ነበራቸው ማለት ነው?” የሚል ጥያቄን ጭሯል።
ኢትዮጵያ ቼክ በዚህ ዙርያ አንድ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የታሪክ ምሁርን እና የኢትዮጵያ አየር መንገድን መረጃ ጠይቋል።
“እርግጥ ነው፣ የመንግስት ሚድያዎቹ ሲፅፉት ‘የቀድሞው ፕሬዝደንት መንግስቱ ኀይለ ማርያም አውሮፕላን’ የሚል ሀረግ ተጠቅመዋል፣ ይህም አሳሳች ነው ምክንያቱም ኮ/ል መንግስቱ ለግላቸው ይጠቀሙበት የነበረ አውሮፕላን አልነበራቸውም። እንደ አሁኖቹ መሪዎች የውጭ በረራ ሲኖራቸው ይጠቀሙ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖችን ነበር” ብለው የታሪክ ምሁሩ ተናግረዋል።
አንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀላፊ በአጭር የፅሁፍ መልዕክት ለመሠረት ሚድያ በላኩት ማብራርያ ይህንኑ ሀሳብ ተጋርተው “ይህ DHC 5 አውሮፕላን በመንግስቱ ግዜ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አርማ (livery) የተቀባ እና በአየር መንገዳችን ስር ይበር የነበረ ነው። ወዲያው ግን ከአገልግሎት ውጪ ተደርገው ነበር” በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በዚህም መሰረት የመንግስት ሚድያዎች በዚህ ዙርያ ባሰራጩት ዘገባ ላይ “የቀድሞው ፕሬዝደንት መንግስቱ ኀይለ ማርያም አውሮፕላን” በሚል ያቀረቡት መረጃ አሳሳች ሆኖ ተገኝቷል።
“ከዚህ አቀራረብ ይልቅ የቀድሞው
ዘንድሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስታና የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት አካላት በተለይም አማሮችና ተጋሩወች በመልካሙ ዘመን እንደሚያደርጉት ግብረ ሕማማት የሚባለውን መጽሐፍ ዘርግተው ለማንበብ ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ የሚያስፈልጋቸው አይደለም፡፡ ራሳቸው ግብረ ሕመም የሚባለውን መጽሐፍ ሆነዋል፡፡ ምድራቸውም ግብረ ሕማማቱ የሚነበበት ወደ ቤተ ክርስቲያንነት ተቀይሯል፡፡ እንዴት? የሚል ጥያቄ መከተሉ ስለማይቀር ተባብረን ለመመለስ የግብረ ሕማማቱን ሐተታ አብረን እንቃኘው፡፡ ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ።
ግብረ ሕማማትDownload
የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ ከፍተኛ ቡድን በፍጥነት በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ እንዲወያይ መጠየቃቸውን የትግራይ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ደብረጺዮን ይህን የጠየቁት፣ የአፍሪካ ኅብረት የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ተከታታይ፣ አረጋጋጭና ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ከፍተኛ ሃላፊ ኾነው አዲስ ከተሾሙት ሜጀር ጀኔራል ሳማድ አላዴ አሶዴ ጋር ዛሬ መቀሌ ውስጥ በተወያዩበት ወቅት ነው። ሕወሓት እና መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት እስካሁን የፖለቲካ ውይይት እንዳልጀመሩና የፓርቲው ሕጋዊ እውቅና እንዳልተመለሰለት ደብረጺዮን መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። አፍሪካ ኅብረት ጀኔራል ሳማድን የሾመው፣ የሥራ ጊዜያቸውን ባጠናቀቁት ጀኔራል እስጢፋኖስ ራዲናን ምትክ ነው። ሕወሓት ከኮሚቴው ጋር በትብብር እንደሚሠራ ያረጋገጡት ደብረጺዮን፣ ኮሚቴው መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ኹኔታ በግልጽ በመለየት ሪፖርት እንዲያቀርብ ጠይቀዋል ተብሏል።
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ ልዩ ስም “ፍልቅልቅ” በተባለ ሥፍራ ለጂፕሰም የፋብሪካ ምርት ጥሬ ዕቃ በማውጣት ላይ የነበሩ የማሽን ሠራተኞች ጨምሮ አስር ያህል ሰዎች ትናንት በታጣቂዎች እንደታገቱ ዋዜማ ሰምታለች። አጋቾቹ ከአማራ ክልል ተሻግረው የገቡ መሆናቸውን ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። ታፍነው ከተወሰዱት ሰዎች በተጨማሪ፣ ከታጣቂዎቹ ጥቃት ለማምለጥ ሲሞክሩ የነበሩ ሌሎች ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች በተከፈተባቸው ተኩስ አካላዊ ጉዳት እንደደረሰባቸው ምንጮች ጨምረው ገልጸዋል። አጋቾቹ ሰዎቹን ወደየት እንደወሰዷቸው ምንም ፍንጭ እንዳልተገኘም ተናግረዋል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚያካሂደው የከተሞች የመንገድ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በሰብዓዊ መብት ላይ የሚያስከትለው ተጽዕኖ እስኪጠና፣ ነዋሪዎችን ማፈናቀሉን እንዲያቆም ጠይቋል።
አምነስቲ፣ መንግሥት “ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ” በከተማ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶቹ ነዋሪዎችን እያፈናቀለ ይገኛል ሲል ከሷል። አምነስቲ፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት በኮሪደር ልማቱ ተጎጅ የኾኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በበቂ ሁኔታ እንዳላማከሩ፣ በቂ ማስጠንቀቂያ እንዳልሠጡና ካሳ እንዳልከፈሉ ጠቅሷል።
ዓለማቀፍ አጋሮች ዜጎችን በግዳጅ ከመኖሪያ አካባቢያቸው ማፈናቀላቸውን እንዲያቆሙ በፍጥነት ማግባባት እንዳለባቸው አምነስቲ አሳስቧል።
“የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አመራር የነበረው የሾዴ መገደልን ተከትሎ ከቡድኑ ከድተው መንግስትን የተቀላቀሉ የቀድሞ ተዋጊዎች ቤተሰቦች ኢላማ ተደርገናል”- የቤተሰብ አባላት ለመሠረት ሚድያ
(መሠረት ሚድያ)- ሾዴ እየተባለ የሚጠራው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (በመንግስት አጠራር ኦነግ ሸኔ) የቀድሞ ከፍተኛ አመራር በመከላከያ ሰራዊት መጋቢት 26, 2017 ዓ/ም መገደሉን ተከትሎ ቀደም ብለው ከቡድኑ ከድተው መንግስትን የተቀላቀሉ የቡድኑ ተዋጊዎች ቤተሰቦች እየተገደሉ እና እየተሰደዱ መሆናቸውን ለሚድያችን ተናግረዋል።
መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ “የጃል መሮ ዋና ሰው የነበረው እንዲሁም በታንዛኒያው ድርድር ከጫካ ወጥቶ ታንዛኒያ ዳሬሰላም ድረስ ከመሮ ጋር ተጉዞ የሸኔ ሽብር ቡድን ተደራዳሪ የነበረው ሾዴ በተወሰደበት እርምጃ ተገድሏል” ማለቱ ይታወሳል።
ሾዴ ከታንዛኒያ መልስ የአጠቃላይ የወለጋ ዞኖች አዛዥ ተደርጎ በመሮ ተሹሞ የነበረ መሆኑንም መከላከያ አስታውቆ ነበር።
ይሁንና አመራሩ በምስራቅ ወለጋ ዞን ሃሮ ሊሙ ወረዳ ገንጂ አካባቢ ከኮርማ ወንዝ ወደ ሱጊ በሚወሰደው መንገድ ላይ በሞተር ሳይክል ተደብቆ ሲጓዝ የፀጥታ ኃይሎች ባገኙት መረጃ መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ ላይ እርምጃ እንደተወሰደበት መንግስት አስታውቆ ነበር።
ይህን ተከትሎ ግን በምስራቅ ወለጋ ዞን ሃሮ ሊሙ ወረዳ ጎርባ ጉዲና እና ሱጌ ቀበሌዎች የሚኖሩ እና ከወራት በፊት ከቡድኑ ከድተው መንግስትን የተቀላቀሉ የቀድሞ ተዋጊዎች ቤተሰቦች ኢላማ መደረጋቸውን ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
“ከሾዴ ግድያ በሗላ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ተጠያቂ ያደረገው የራሱን የቀድሞ ታጣቂዎች ነበር፣ እነዚህ ደግሞ ከድተው መንግስትን የተቀላቀሉት ናቸው” ያሉን አንድ የአካባቢው ነዋሪ የእነዚህ
ሰሙነ ሕማማት !
ከሆሳዕና በዓል (እሁድ) ስድስት ሰዓት እስከ አርብ (ስቅለት) ማታ ድረስ ያሉት ቀናት ሰሙነ ሕማማት ናቸው።
ሳምንቱ ” ዘመነ ፍዳ ” የሚታሰብበት ጊዜ ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰሙነ ሕማማት ወቅት ” የፈጣሪን ህመም ” ታሳቢ ያደረግ ልዩ ህግና ስርዓት አለ።
ቤተክርስቲያን ወትሮ የምታከናውናቸው ስርዓቶች በሕማማት ቀናት አይከናወኑም።
ህዝበ ክርስቲያኑ በሰሙነ ሕማማት የፈጣሪውን መከራ በማሰብ በተለየ ስርዓት ነው ቀናቱን የሚያሳልፈው።
በሰሞነ ሕማማት የትኞቹ የቤተ ክርስቲያን ስርዓቶች አይተገበሩም ?
በሰሙነ ሕማማት በቤተ ክርስቲያን ” ግብረ ህማማት ” የሚባል መጽሀፍ ይነበባል ፤ ለሳምንቱ የተዘጋጀ ልዩ ጸሎት ይደረጋል።
የሌሎች ስርዓቶች ክዋኔ ይገታል።
በሰሙነ ሕማማት ፦
ቅዳሴ አይቀደስም (ከጸሎተ ሀሙስ ውጭ)
ማህሌት አይቆምም
ጸሎተ ፍትሀት አይደረግም
መስቀል አይሳለምም
ክርስትና አይነሳም
ኑዛዜ አይሰጥም አይቀበልም
እነዚህ ስርዓቶች በሆሳዕና ዕለት አስቀድመው የሚከናዎኑ ናቸው።
ምዕመናን ሰሙነ ሕማማትን በምን ስርዓት ይከውናሉ ?
በቤተ-ክርስቲያኗ ” የመከራ ዘመን ” የሚባለውን 5500 ዓመትን በመወከል አምስት ቀናት ተኩል የሆነው ሰሙነ ሕማማት በምመናን ዘንድ በተለያዩ ድርጊቶች ይታሰባል።
የሚተገበሩት ድርጊቶች ሀዘንን ለመግለጽ እንዲሁም ከአስተምሮ ጋር መልዕክ ያላቸው ናቸው።
ምእመናን በሰሙነ ሕማማት ፦
ከመጨባበጥና መሳሳም በመራው
በባዶ እግር በመቆም
በስግደት
በጸሎት
ራስን ዝቅ ማድረግ ያስባሉ።
አባቶች በሕማማት ሳምንት ምዕመኑ ፦° ወደ ራሱ ጠልቆ በመግባት መጸለይ እንዳለበት° ሰው ስለ ኃጢያቱ ማሰብ እንዳለበት° ስለ ሀገሩ ማዘን እንዳለበት° ለሰላም መጸለይ እንዳለበት° የሰው ልጅ ሰላም እንዲያገኝ ሰላም ያጣው
በነዳጅ የሚሠሩ ባለሁለት እግር (ሞተር ሳይክል) እና ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጅ) ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መወሰኑን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለጦር ሽፈራው ገርባው ብርጌድ 2ኛ ዙር የምረቃ ዝግጅት – ክፍል 2 #MerejaTV #merejamedia #fano #amhara #gojjam pic.twitter.com/lif64hiMlK— Mereja TV (@merejatv) April 12, 2025
የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለጦር ሽፈራው ገርባው ብርጌድ 2ኛ ዙር የምረቃ ዝግጅት – ክፍል 1 #MerejaTV #merejamedia #fano #amhara #gojjam pic.twitter.com/5iSSNABl2C— Mereja TV (@merejatv) April 12, 2025
በአቶ ልደቱ አያሌው ለመሠረት ሚድያ የተላከ
የፕሪቶሪያው ስምምነት በተፈረመ ማግስት “የፕሪቶሪያው ስምምነት ያሳዝናል፣ ያስደስታል፣ ያሳስባል!” በሚል ርዕስ አንድ መጣጥፍ አስነብቤ ነበር። “ያሳዝናል” ያልሁት- ጦርነቱ ለጊዜውም ቢሆን እንዲህ በሰላማዊ ድርድር ሊቋጭ በሚሊዬን የሚገመቱ ወገኖቻችንን ህይዎት ባልተገባ የዕርስ-በርስ ጦርነት ማጣታችን እጅግ አሳዛኝ ስለነበር ነው።
“ማናችሁም በዘላቂነት ላታሸንፉ በቀላሉ የማይዎጣበት ጦርነት ውስጥ አታስገቡን” የሚለውን የአንዳንዶቻችንን ምክር “ጀሮ-ዳባ ልበስ” ብለው ወደዚያ ህዝብ ጨራሽና አውዳሚ ጦርነት ያስገቡን ግብዞች ከዚያ ሁሉ ዕልቂትና ውድመት በኋላ የተደረሰበትን ያን የፕሪቶሪያ ስምምነት እንደ ልዩ ስኬትና ድል ቆጥረው እንደ ሰላም አርበኛ ለመመስገንና ለመወደስ ሲፈልጉ እንደማየት ልብ የሚሰብር ክስተት አልነበረም።
“ያስደስታል” ያልሁት- ለጊዜውም ቢሆን የሰላም ስምምነት መፈረም በመቻሉና የህዝብ ዕልቂት በመቆሙ ነበር። የወደፊት ውጤቱ ምንም ይሁን ምንም ያ ህዝብ ጨራሽና አውዳሚ የሆነው ጦርነት ሲቆምና ህዝቡ ለጊዜውም ቢሆን የሰላም አየር ሲተነፍስ እንደማየት በርግጥም የሚያስደስት ክስተት አልነበረም።
“ያሳስባል” ለማለት የተገደድኩት- ስምምነቱ ጦርነቱን በዘላቂነት የሚያስቆምና ዘላቂ ሰላም ሊያመጣ የሚችል እንዳልሆነ አስቀድሞ ግልፅ ስለ ነበር ነው። በርግጥም ስምምነቱ በቂ ዝግጅትና ድርድር ያልተደረገበት፣ በውጫዊ ጫናና ግፊት እንጂ በራስ ልባዊ ፍላጐት ያልተፈረመ፣ ዘላቂ መፍትሄን ለማምጣት ሳይሆን ለሌላ ዙር ጦርነት ጊዜ ለመግዛት ታስቦ የተካሄድ፣ ለጦርነቱ ምክኒያት የሆኑትን ቅራኔዎች በቅጡ ያላገናዘበና ዘላቂ መፍትሄዎችን በአግባቡ ያልዋጀ ስምምነት ስለነበር መሬት ላይ በተግባር ሊፈፀም እንደማይችል አስቀድሞ የታወቀ ነበር።
የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ ሁለት ዓመት ከመንፈቅ ሆኖታል። ስምምነቱን ወደ ተግባር ለመለወጥ የስምምነቱ ተፈራራሚና ባለቤት በሆኑት
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ የክልሉ ጸጥታ ሃላፊና የቀድሞው ምክትል ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ ተሠጥተዋቸው የነበሩትን የሥራ ዝርዝሮች መፈጸም አልቻሉም ነበር በማለት ከቢቢሲ ፎከስ ኦፍ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተችተዋል።
የጀኔራል ታደሠ የሥራ ዝርዝር በውድቀት የተሞላ ነበር ያሉት ጌታቸው፣ እርሳቸውን በወቅቱ ከሃላፊነት ማንሳት አለመቻላቸው ውድቀታቸው እንደኾነ ገልጸዋል። ሥልጣኑን ጠቅልሎ ለመያዝ ከሚፈልገው ደብረጺዮን ከሚመሩት የሕወሓት አንጃ የሚመጣው ከቁጥጥር ውጪ የኾነ የሥልጣን ጥማት፣ ለአዲሱ ፕሬዝዳንት ተግዳሮት ኾኖ ሊቀጥል እንደሚችልም ጌታቸው ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ ሥልጣን ከሚጎመዡት የሕወሓት ሰዎች ሁሉ የተሻሉት ጀኔራል ታደሠ ናቸው በማለት ሊያሳምኗቸው እንደሞከሩና የታደሠ ሹመት የጠቅላይ ሚንስትሩ ውሳኔ እንደኾነ ጠቅሰዋል።
የትግራይን ፖለቲካ ይበልጥ አስቸጋሪ ካደረጉት ጉዳዮች መካከል፣ በመንግሥት ሥር መኾን የነበረበት ሠራዊት እስካኹን ራሱን የቻለ አካል አድርጎ መቆጠሩ ተጠቃሽ እንደኾነም ጌታቸው አውስተዋል። ኤርትራን በተመለከተ፣ በእሳቸው አስተዳደር ውስጥ የተወሰኑ ሰዎች በሕገወጥ መንገድ ከኤርትራ መንግሥት ጋር ለመገናኘት ሲሞክሩ እንደነበር ጌታቸው ተናግረዋል።