በጎንደር ጠንካራ ውጊያ እየተደረገ ነው
ግንቦት 27/2017 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ጎንደር ቀጠና አዲስ የተደራጀው ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር በጎንደር ኮማንዶ በላይ የተሰኘ ንዑስ ልዩ ኦፕሬሽን ጀመረ።
የዘመቻ ቋራ ቃል ኪዳን አካል የሆነ ንዑስ ልዩ ኦፕሬሽን እየተደረገባቸው የሚገኘው …

፩ኛ የአፋብኃ ጎንደር ቀጠና ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር የጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር የጎንደር ብርጌድ፣የቃኘው ብርጌድና የዓፄ ፋሲለደስ ብርጌዶች በጥምረት ጎንደር ከተማ ምስራቃዊ አቅጣጫ ዘልቀው በመግባት ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ብርቱ ውጊያ በማድረግ የጠላትን ምሽግ እየሰበሩ እየገሰገሱ ነው።
መረጃው እስከደረሰበት ሰዓት ጠላት ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ የደረሰበት ሲሆን በከተማው በጥብቅ ጥበቃ ስር የሚገኘው የአገዛዙ ሹመኛ እየራደ ይገኛል።

፪ኛ በጎንደር ከተማ ደቡባዊ አቅጣጫ የዓፄ ቴዎድሮስ አይሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ ብርኃላ የተባለ የጠላት ምሽግን በማፈራረስ በጥልቀት ለመግባት እየተዋጋ የሚገኘው የአፋብኃ ጎንደር ቀጠና ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር የታድሎ ብርሃን አካል ብርጌዶች ናቸው።በዚህ የጎንደር ከተማ አስ/ር ጠዳ ክ/ከተማ እየተደረገ በሚገኘው ተጋድሎ የኦህዴድ ብልፅግና ጨፍጫፊ ታጣቂ በጀግናው ሰራዊታችን ብርቱ ክንድ እየተደቆሰ ይገኛል።

፫ኛ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ አዳሩን ማክሰኝት ከተማን ጠላትን ደምስሶ ሰብሮ በመቆጣጠር የወረዳውን ፖ/ጣቢያ በመስበር ከ70 በላይ የግፍ እስረኞችን ማስለቀቅ የቻለው የአፋብኃ ጎንደር ቀጠና የዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር የጥቁር አንበሳ ክ/ጦር ነው።አሁንም ከተማውን በመቆጣጠር ቀሪ ተልዕኮዎቹን በመፈፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን ከጎንደር ከተማ 40 ኪ.ሜ ርቀት የተወሰደ ስኬታማ ኦፕሬሽን ነው።የንስር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክ/ጦር አሃድም ተሳታፊ ነው።

፬ኛ የዳ/ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር የመብረቅና የሻለቃ