Blog Archives
ኢትዮጵያና ጾመ ነነዌ
በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ
[email protected]
“አንባቢ ይፈጥን ዘንድ ራእዩን ጻፈው፣ በጻላትም ግለጸው፣ ራእዩ በተወሰነለት ጊዜ ይገለጣል፡፡ ወደ ፍጻሜ ለመምጣት ይቸኩላል፣ ውሸት አይደለም፡፡ ቢዝገይም ይመጣል” (ዕንባቆም 2፡2-3)በሚለው ተንተርሰው የቀደሙ አባቶቻችን “የሚሰማም የሚያነብም ባይኖርም፣ ሰሚ ጆሮ ያላቸው አንብበው የሚረዱ ጥቂት ሰወች ስለሚኖሩ ይጻፍ ይነገር” ይላሉ፡፡
ለኢትዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን ያልተከሰተና ያልተነገረ እንግዳ ነገር የለም፡፡ በየዘመናቱ የሚታዩት ሁሉ እንግዳ የሚሆኑትን ላዲሱ ትውልድና ክስተቶችን ለሚያስተናግዱ መሪዎች ነው፡፡ በኢትዮጵያና በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስቲያኖች ላይ የሚከሰቱት መከራወች የአመጣጣቸው መንገድ ይቀያየራል እንጅ የተለመዱ ናቸው፡፡ ስለዚህ ለኢትዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን የሚያስፈልገው ያለፈውን ታሪክ መመርመርና ሊቃውንት አበው በዝክረ ሊቃውንት ቅኔዎቻቸው የተቀኟቸውን ቅኔዎች መፈተሽ እንጅ አዲስ ሕልምም ራእይም አያስፈልግም፡፡
ለሚከሰቱ ነገሮች አዲስ ራዕይ ምልክት የሚሻ ቢኖር “ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፡፡ከነቢዩ ከዮናስ በቀር ምልክት አይሰጠውም” (ማቴ 12፡39-42) እንዳለው፦ ከዚህ ቀደም የተከሰቱትን ከመመርመርና ቅኔዎችን በጥንቃቄ ከመመልከት ይልቅ ህልምና ራዕይ መሻት ክፉና አመንዝራ ትውልድ መሆን ነው፡፡ ለኛ ብዙ ምልክቶች ተሰጥቶናል፡፡ሊቃውንት አባቶች ነገረ መለኮቱን የተረጎሙበት አንድምታቸውና ዝክረ ነገር ብለው ቀምረው ያስቀመጡልን ቅኔዎቻቸው ዘመን እያሰገሩ የሚከሰቱትን ሁሉ በግልጽ የሚያሳዩ ናቸው፡፡
ከ 8 አመታት በፊት የነነዌን ጾሞ መነሻ በማድረግ ያቀረብኩት ያባቶች አንድምታ ያለፈውን ያስቃኛል፡፡ ባቀረብኩበት ዘመን ይካሄድ የነበረውን አሳይቷል። በዚህ አመት ነነዌ ጾማችን ላይም ካለፉት ዘመናት በተከታታይ ሲካሄድ የነበረው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞችና የአማራ ህዝብ ላይ የተከፈተው ጦርነት ተፋፍሞና ተባብሶ ህዝቡ ከሰማይ በድሮንና በጦር ጀት ከመሬት ደግሞ
የደቡብ ወሎ ዞን ኮማንድ ፖስት በንፁኋኖች ላይ ከወትሮው በተለየ መልኩ ጥቃቶች እንዲፈፀሙ ስለመወሰኑ መረጃው አፈትልኮ ወጣ!
የደቡብ ወሎ ዞን ኮማንድ ፖስት አመራሮች በመካነሰላም ከተማ ባካሄዱት ሚስጥራዊ ስብሰባ ከወትሮው በባሰና ተከታታይነት ባለው መልኩ በንፁኋኖች ላይ ጥቃት እንዲፈፀም ስለመወሰናቸው ለመረብ ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመላክታል።
ይህም፡ ሕዝቡ በሚፈፀምበት ጥቃት ተማሮ ጦርነቱን አስቁሙልኝ በሚል እንዲጠይቅና ፋኖንም በአደባባይ ወጥቶ እንዲያወግዝ ያስችልልናል በሚል ነው ውሳኔውን ያስተላለፉት ብለዋል ምንጮቻችን።
አገዛዙ ጦርነቱ የተራዘመብኝ ሕዝቡ ለፋኖ ደጀን በመሆኑ ነው ብሎ ያምናል።
በአንድም በሌላም መንገድ በሕዝቡ ላይ የሚፈፀመውን ጥቃት ተባብሶ እንዲቀጥል በማድረግ፡ ሕዝቡ በመሰላቸት ለፋኖ የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያቆምና ጦርነቱ እንዲቆም ተማፅኖ እንዲያቀርብ ለማድረግ አገዛዙ እንደ አማራጭ እየተጠቀመው የሚገኘው አካሄድ ነው።
ወዲህ ደግሞ ለአማራ ሕዝብ ያለውን ጥላቻ እና ቂም የሚወጣበት መንገድ ሆኖ አግኝቶታል።
ስለሆነም ከወደ ፋኖ የሚሰነዘርበትን ጥቃት መቋቋም ሲያቅተው የፈሪ በትሩን በንፁኋን ላይ በማንሳት ሰቅጣጭ ግፍ መፈፀሙን ቀጥሏል።
የደቡ ወሎ ዞን ኮማንድ ፖስት አመራሮች ጥር 20/2018 ዓ/ም በመካነሰላም ከተማ ባካሄዱት ዝግ ስብሰባ ሕዝቡ በሚፈፀምበት ጥቃት ተማሮ ከፋኖ ይርቃል፡ እንዲሁም ፋኖን ወደ አደባባይ ወጥቶ እንዲያወግዝ ያስደርግልናል ያሉትን ውሳኔ ስለመወሰናቸው ምንጮቻችን መረጃውን አድርሰውናል።
ውሳኔው ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በተጠናና ተከታታይነት ባለው መልኩ በንፁኋኖች ላይ ጥቃት እንዲፈፀም የማድረግ ሴራ ሲሆን፡ ይህም መካነሰላምን ጨምሮ በዞኑ ስር በምዕራብ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ እንዲሁም በሌሎች የዞኑ አከባቢዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል ነው ያሉት የመረብ ሚዲያ ምንጮች።
ሴትና
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ስማቸው በኤፕስታይን ኢሜይል ላይ የተጠቀሰበትን አግባብ በተመለከተ ለመሠረት ሚድያ ምላሽ ሰጡ
የአሜሪካ መንግስት ትናንት ይፋ ያረገው የወንጀለኛው የጄፍሪ ኤፕስታይን መረጃዎች ላይ የፕሮፌሰር ብርሀኑ ስም ለ ‘ግንቦት ሰባት’ የትጥቅ ትግል ድጋፍ በሚደረግበት ዙርያ የነበረ የኢሜይል ልውውጥን ይዞ ወጥቷል፣ ዝርዝሩን ይዘናል
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/f4b
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት ሊሸጥ ነው
ከፍተኛ የወርቅ ክምችት እንዳለበት በሚታመነውና ከአሶሳ እስከ ሱዳን ድንበር በተንሰራፋው የመቶ ኪሎሜትሮች የኩርሙክ ወርቅ ፕሮጀክትን እስካሁን ይዞ ያስተዳድር የነበረው አላይድ ጎልድ ኩባንያ ፕሮጀክቱን ለቻይናው ዝጅን ኩባንያ ለማስተላለፍ እየተዘጋጀ መሆኑን ሰምተናል።
ያለፉትን አመታት የግብፅ እጅ የነበረበትና የህዳሴው ግድብ አቅራቢያ በመገኘቱ ስጋት የፈጠረው ፕሮጀክት ወደ ቻይናው ኩባንያ መሸጋገሩ ለስጋቱ እልባት እንደሚሰጠው ይታመናል።
ዝርዝሩን ያንብቡት- https://cutt.ly/Jtc2WALH
የአሜሪካ ፍርድ ቤት የትራምፕ አስተዳደር የኢትዮጵያውያን ጊዜያዊ ከለላ እንዲያበቃ የሰጠውን ውሳኔ በጊዜያዊነት አገደ።
የአሜሪካ የፌደራል ዳኛ የትራምፕ አስተዳደር ለኢትዮጵያ ዜጎች የተሰጠው ከለላ በማብቃት ከሃገር እንዲወጡ ያዘዘውን ውሳኔ በጊዜያዊነት አግዶታል።
ዳኛው ጉዳዩ በህግ አግባብ በደንብ እስኪታይ ድረስ በየካቲት 13 የሚጀምረው የከለላ መቋረጥ እንዲዘገይ መወሰናቸውን ገልጸዋል።
የአሜሪካ የፍትህ ቢሮ ከኢትዮጵያውያኑ ስደተኞቹ ለቀረበበት ክስ መልስ ለመስጠት ተጨማሪ ጊዜ እንደሚፈልግ ቢገልጽም የፍርድ ቤቱን የማዘግየት ውሳኔ ተቃውሟል።
ዘገባው https://mereja.forum/content/viewtopic.php?f=2&t=374782 ነው።
የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አማካሪና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመሩት ስምረት ፓርቲ፣ “ኋላቀር” ሲል የጠራው የሕወሃት ቡድን ከባድ መሳሪያዎችን ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በማስጠጋት ተኩስ ከፍቷል በማለት ከሠሠ።
ስምረት፣ ሕወሃት አፋር ክልልን እና የጎንደር አካባቢን ያካለለ “መጠነ-ሰፊ” ጥቃት ለመፈጸም ዝግጅቱን ጨርሷል ሲል ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ከሷል። በቅርቡ በመንግሥት እና በሕወሃት ኃይሎች መካከል ጠለምት ላይ ግጭት መካሄዱን የጠቀሠው ፓርቲው፣ ቡድኑ ጦርነት የከፈተው የትግራይን “የግዛት አንድነት” እና “የተፈናቃዮችን መመለስ ጉዳይ” እንደ ሽፋን በመጠቀም ነው ብሏል።
ቡድኑ ቀድሞ የቀበራቸውንና የደበቃቸውን ከባድ መሣሪያዎች በማውጣት ግጭት ጀምሯል በማለት ጭምር ፓርቲው የከሠሠ ሲኾን፣ የቡድኑ እንቅስቃሴ የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት “ሙሉ በሙሉ” በማፍረስ የሚያካሂደው ነው ሲል በመግለጫው አካቷል። የሕወሃት ቡድን ይህን ጦርነት የጀመረው ከኤርትራ መንግሥት ጋር ተሰልፎ ነው በማለትም ፓርቲው ከሷል. ሳልሳይ ወያነ እና የትግራይ ነጻነት ፓርቲም፣ ዓለማቀፍ አጋሮች በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ኃይሎች መካከል መጠነ ሰፊ ግጭት እንዳይከሠት ፍጥጫው እንዲረግብ ጥረት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሃሙድ የሱፍ፣ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና ሕወሃት መተማመንን ከሚሸረሽሩ ድርጊቶች እንዲቆጠቡ እና እስካሁን ያልተፈቱ ጉዳዮችን በገንቢ ንግግር እንዲፈቱ ጠየቁ።
የሱፍ፣ በትግራይ ክልል ሰሞኑን የተከሠቱ ክስተቶች በጥልቅ እንዳሳሰቧቸው እኩለ ቀን ላይ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል። ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተሉ መሆኑን የጠቀሱት የሱፍ፣ የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ያስገኛቸውን እድሎች መጠበቅ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።
የአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪ ቡድን አሁንም በሁለቱ ወገኖች መካከል ንግግር እንዲካሄድ ለማመቻቸትና መተማመንና ትብብር እንዲጎለብት ለማስቻል ዝግጁ መሆኑንም የሱፍ አረጋግጠዋል።
ጥር 23 ጀምሮ በስስ ፌስታል እቃ መያዝ ሆነ መሸጥ በህግ ያስቀጣል !
” ህጉ ወጥቷል ፤ ማህበረሰቡ ማክበር አለበት ፤ ካላከበረ ህግ አስከባሪ ሁሉ እርምጃ የመውሰድ ግዴታ አለበት ” – ባለስልጣኑ
⚫️ ” አዋጁ ያስቀመጠው የጊዜ ገደብ ነገ ከመሆኑ፣ እሱም ጊዜ ከመድረሱ ውጭ ከየትኛውም አካል በኩል የተለየ የተሰጠን ማብራሪያ የለም ” – ማህበሩ
” ህብረተሰባችን፣ ሰፊው የንግድ ማህበረሰብም የተቀመጠለት መፍትሄ የለም። ዓይን ጨፍኖ እየተገባበት ነው። አሁንም ቆም ተብሎ ቢታሰብበት መልካም ነው ” – ማህበሩ
ከዛሬ ጀምሮ እቃን በፌስታል ይዞ መንቀሳቀስ ያስቀጣል።
የፕላስቲክ ኢንዱስትሪው ከስራው እንዲወጣ መደረጉ በ100 ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችንና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎችን የሚጎዳ በመሆኑ “በድጋሚ እንዲጤን” የኢትዮጵያ ፕላስቲክ እና ጎማ አምራቾች ማህበር አሳስቧል።
የማህበሩ አባል እና ጉዳዩን በሚደነግገው አዋጅ ምክንያት የተቋቋመው ኮሚቴ ጊዚያዊ ሰብሳቢ አቶ በረከት ገ/ህይወት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ” አሁንም ቆም ተብሎ ቢታሰብበት መልካም ነው ” ብለዋል።
አቶ በረከት በዝርዝር ምን አስተያየት ሰጡ ?
” የሚፈጠረውን አብረን እናያለን። ከዚህ በፊት በአጽንኦት ያሳሰብናቸው መሰረታዊ ጉዳዮች አሉ፤ የተኪ ምርቶች ሁኔታ በአግባቡ አልታየም።
ኢንዱስትሪዎች በቂ የሽግግር ጊዜ ያስፈልጋቸዋል። ካልሆነ ይከስማሉ፣ ሠራተኞች ይበተናሉ፤ ለሀገርም የምናበረክተው አስተዋጽኦ በዜሮ ይባዛል። ህብረተሰባችን ምቹና ተመጣጣኝ የሆነ ሸቀጦችን የሚሰበስብበት ግብዓትን እንዲያጣ ይደረጋል፤ በዚህ ምክንያት ላላስፈላጊ የኑሮ ውድነትም ይጋለጣል።
ተኪ የሚባል ነገር ቢገኝ እንኳ (አሁን ባለው ሁኔታ እሱን የሚያሳይ ነገር ባይኖርም) በዋጋ፣ በቅልጥፍና፣ በምቾት፣ ሁሉንም አይነት
በመድፍ፣ በቢ ኤም 107፣ ዙ23 እና ሞርተሮች ታግዞ ከባድ ውጊያ የከፈተው ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ዛሬ ጥር 22/2018 ዓ.ም ደቡብ ወሎ ዞን ተንታ እና መቅደላ ወረዳ እንዲሁም ማሻ ከተማ ዙሪያ ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ያስተናገደ ሲሆን ልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር የንጉስ ሚካኤል ኮር አሃድ ከሆነው ሸህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ጋር በመጣመር በመቶ የሚቆጠር የጠላት ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ እንዲሁም በርካታ ጦር መሳሪያና ተተኳሽ በመማረክ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::
ምኒልክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር በተጋድሎው ማሻ ከተማ ድረስ ዘልቀው በመግባት በርካታ ጥምር ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ከመደምሰስ ባሻገር አንድ ስናይፐር፣ አንድ ብሬን፣ 21 ክላሽ፣ እና የእጅ ቦምቦች እንዲሁም 3000 የክላሽ ተተኳሽ ማርከዋል:: በተጨማሪም ሸህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ማሻ ከተማ ድረስ ዘልቀው በመግባት ባንዳን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣትና በመማረክ ጭምር ታላቅ ጀብድ ፈፅመዋል::
ልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር ለሌላ ተጨማሪ ጦርነት እየተዘጋጀ ላለው ፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና ራስ ምታት የሆነ ታላቅ ድል ማሻ ከተማ ላይ ያስመዘገቡ ሲሆን በርካታ እግረኛ ሰራዊቱ የተመታበት ብሎም የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እንዲሁም ተተኳሽ የተማረከው አገዛዙ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገብቷል::
ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ያስተናገደውና የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው የብልፅግና ሰራዊት የበቀል አፈሙዙን ወደ ንፁሃን ጦር መሳርያ ያልታጠቁ አማራዎች በማዞር ተንታ አካባቢ አንዲት እናት በሞርተር የገደለ ሲሆን በዙ23 ዘጠኝ መኖሪያ ቤቶችን አቃጥሏል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት
ወደ ትግራይ በሚደረጉ የአየር በረራዎች መሰረዝ ዙርያ አዲስ መረጃ ወጥቷል፣ አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጦርነት እንዲያስቀር ‘የመጨረሻ’ የተባለለት ጥሪ ቀርቧል፣ ከራያ አላማጣ እና ኮረም አካባቢ አዲስ መረጃ ተሰምቷል፣ እንዲሁም መቀሌ ከተማ ውስጥ አሁን ስላለው ድባብ መረጃ ይዘናል።
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/bcf
Elias Meseret : የህግ አስከባሪ አካላት በቅርቡ በተደጋጋሚ እየፈፀሙት ያለ ትኩረት የሚሻ ነገር ቢኖር ግለሰቦችን በሙስና፣ የህብረተሰቡን እሴት በመበከል… ወዘተ ጠርጥረን በቁጥጥር ስር አዋልን ብለው ህብረተሰቡን ካስፈነጠዙ እና ሙገሳቸውን አፋቸው ላይ ካረጉ በኋላ ተጠርጣሪዎቹን ካለ አንድ ኮሽታ የሚለቁት ነገር ነው።
ለምሳሌ የዛሬ ሁለት ወር ገደማ አንዳንድ የመንግስት ሚድያዎች በሰበር ዜና ጭምር ሲያቀርቡት የነበረው “ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ” የሚለውን ዜና እንይ፣ ዛሬ ላይ አንድም ተጠርጣሪ ሳይቀር በምርመራ ምንም ሳይገኝበት ነፃ ሆኗል ተብሏል።
ፎቷቸው እንደ ሌባ በፌስቡክ ተለጥፎ ‘አጭበርባሪ፣ የታባቱ፣ ይሰቀል’ ሲባል የነበረው ሁሉ ዛሬ ላይ ነፃ ሲሆን አንድም የመንግስት ሚድያ አልዘገበውም (ለዝርዝሩ መሠረት ሚድያ ላይ: https://www.meseretmedia.org/p/100-24
በተመሳሳይ ታዋቂ የሚባሉ ቲክቶከሮች በቅርቡ ፎቷቸው እየተለቀቀ ታሰሩ ሲባል ነበር፣ ህዝብም ‘የታባቱ/የታባቷ’ ሲል ነበር፣ አሁን ግን እስራቸው እንጂ መፈታታቸው ለህዝብ ሳይነገር ሁሉም ተለቀው ስራቸውን ቀጥለዋል። ሌላም፣ ሌላም…
ይህ ምናልባት መታሰራቸው የመንግስትን ጥንካሬ፣ መፈታታቸው ደግሞ ድክመትን ያሳያል በሚል የተፈፀመ እንደሚሆን ልምምዶች አሉ። ነገር ግን ይህ የተጠያቂነት ግርግርን (performance of accountability) እንጂ ተጠያቂነትን ራሱን (accountability) አያመጣም።
ሰው ተጠርጥሮ አይያዝም አይባልም፣ ነገር ሁሉም ሊጠይቅ የሚገባው ነገር ቢኖር:
– ህዝቡ ግለሰቦች ሲታሰሩ ብቻ ሳይሆን ሲፈቱ የማወቅ መብት የለውም?
– እነዚህ ዜጎች በምን ጉዳይ ታሰሩ፣ ምን ክስ በየትኛው አንቀፅ ተመሰረተባቸው? ካልተመሰረተስ ለምን?
– ክስ ሲቋረጥ ወይም እንዲለቀቁ ሲደረግ ማን
ከቤቲንግ ጋር በተያያዘ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል ተጠርጥረው ታስረው የነበሩ 24 ግለሰቦች ሙሉ በሙሉ ከእስር መለቀዋቸው ታወቀ
በግለሰቦቹ መታሰር ዙርያ ተከታታይ ሰበር ዜና ሲሰሩ የነበሩት የመንግስት ሚድያዎች በመፈታታቸው ዙርያ እስካሁን ያሉት ነገር የለም።
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/100-24
Abebe Fentaw
አላማጣ ከተማ ራያ አላማጣ እና ኮረም ዙሪያ የነበረው የፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና መከላከያ ሰራዊት እና ፌደራል ፖሊስ ያለ ምንም የጥይት ተኩስ ጥር 21/2018 ዓ.ም አካባቢውን ለቆ ወጥቷል::
ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ሚያዚያ 2016 ዓ.ም ራያ ላይ የነበረውን መዋቅር በሴራ አፍርሶ አካባቢውን አሳልፎ በመስጠት በኋላም የተወሰነ ሃይሉን የተለያዩ ቦታዎች ላይ በማስፈር አካባቢውን ከትግራይ ሃይሎች ጋር ይዞ መቆየቱ የሚታወቅ ነው::
ፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና በተጠቀሱት የራያ አካባቢዎች ከሚያዚያ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከትግራይ ሃይሎች ጋር በጋራ ሰፍሮ ይኖር የነበረውን ሰራዊቱን ጥር 21/2018 ዓ.ም ያለ ምንም የጥይት ተኩስ ለቆ እንዲወጣ አድርጎ ቦታውን ሙሉ ለሙሉ ለትግራይ ሃይሎች አስረክቧል::
ከዚህ ጋር ተያይዞም አገዛዙ በዚህ መንገድ ለቆና አስረክቦ የወጣውን የራያ አካባቢዎች የሃሰት ፕሮፓጋንዳና ሴራ ሊሰራበት እንደተዘጋጀ መረጃው አለን:: ይህንን ካሁን በፊት እንዳደረገውና አሁንም እንደሚያደርግ ግን ለህዝብ የተደበቀ አይደለም::
ብልፅግና ይዞት የነበረውን የራያ መሬት በዚህ መንገድ ያስረከበ መሆኑ እየታወቀ ነገር ግን በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ህዝብ ላይ የተለመደ ፀረ ፋኖ የውሸት ፕሮፓጋንዳውን በመስራትና አዲስ የውጊያ አጀንዳ በመፍጠር ብሎም በፀረ-ህዝብና አገር አፍራሽ ሚዲያዎቹ በማስተጋባት ለአማራው ከእልቂት በስተቀር አንዳች መፍትሄ ወደሌለው ጦርነት በማስገባት እድሜውን ለማራዘም እየሰራ ይገኛል::
ከዚህ ጋር ተያይዞም ከደቡብ ወሎ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች በሚሊሻ ስም የሰበሰበውን የአማራ ገበሬ እና አድማ ብተና ቀድሞ ወልድያ እና ራያ ቆቦ ዙሪያ ያሰፈረ ሲሆን ከሰሜን ወሎ ሚሊሻ ጋር በማድረግ በቀጣይ ከትግራይ ሃይሎች ጋር ሊያደርገው ባሰበው
በምስራቅ ዐምሓራ ቀጠና በተሁለ ድሬ ወረዳ ከሐይቅ ከተማ በቅርብ ርቀት ልዩ ስሙ ቆሎ ባቄላ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ የሚገኘውና ከቦታ አቀማመጡ ጋር ተዳምሮ በመዘመናዊ መንገድ ተሰርቶ የነበረው የአገዛዙ ወታደራዊ ምሽግ በፋኖ ቦምብ ድርምስምሱ ወጥቷል።
በምሽጉ ውስጥ የነበሩ በርካታ ወታደሮች የእሳት እራት ሆነው ሲቀሩ፡ ሕይወታቸውን ለማትረፍ ሲሸሹ የነበሩ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካቶች ደግሞ ገደል ገብተው አልቀዋል።
በአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒሊክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ጥር 19 ለጥር 20/2018 ዓ/ም አጥቢያ ሌሊት በፈፀሙት ታአምራዊ ኦፕሬሽን የጠላትን አከርካሪ በመስበር ታላቅ ድል መጎናፀፋቸውን የመረብ ሚዲያ የምስራቅ ዐምሓራ ቀጠና ዘጋቢዎች ለማረጋገጥ ችለዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ ልዩ ቦታው ቆሎ ባቄላ ተብሎ በሚጠራው ቦታ በነበረው የአገዛዙ ወታደሮች ምሽግ ላይ ነው መብረቃዊው እርምጃ የተወሰደው።
ከቦታው መልካአ ምድራዊ አቀማመጥ ጋር ተዳምሮ በመዘመናዊ መንገድ ተሰርቶ የነበረው የአገዛዙ ወታደሮች የኮንክሪት ምሽግ ነው “ተናዳፊዎቹ” በሚል ቅፅል ስም የሚጠሩት በልጅ እያሱ ኮር ስር የ24 ክ/ጦር ፋኖዎች ትናንት አጥቢያ ለሊቱን የጥቃት ዶፍ አውርደውበት ድርምስምሱን ያወጡት።
የፋኖ አባላቱ የጥይት ካዝናቸውን እንዳነገቡና የብሬን ሸንሼናቸውን ልክ እንደመቀነት በወገባችው ደግድገው በደረታቸው እየተሳቡ በጠላት ምግሽ ተወርውረው በመግባት በቅድሚያ የምሽጉ ዋርድያዎችን በድምፅ አልባው ሳንጃ ካጋደሙ በኋላ በምሽጉ ውስጥ የነበሩ ወታደሮችን ጭዳ እንዳደረጓቸው የመረብ ሚዲያ የቀጠናው ዘጋቢ ጋዜጠኞች አረጋግጠዋል።
የሳንጃ ትንቅንቅን ጨምሮ የክላሽ ጨበጣ ውጊያው የተካሄደው በድቅድቅ ጨለማ በመሆኑ የተገደሉ የአገዛዙ ወታደሮች ቁጥር
ብልፅግና ወልቃይት ላይ የመዘዘው የመጨረሻ ካርዱ!
ከጥር 18/2018 ዓ/ም ጀምሮ በአማራ ክልል ወልቃይት ቀጠና በማይ-ዳጉሻ በኩል የተጀመረው ውጊያ አድማሱን አስፍቶ በምስራቅ ጠለምት እና በምዕራብ ጠለምት ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ይገኛል።
ሦስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው ውጊያ በሰላሬ፣ በመቃብር አንበሳ፣ ማይበረና ሰራር የተባሉ አከባቢዎችን ጨምሮ በምጫራ ግንባር በአጠቃላይ በሦስት ግንባሮች በከባድ መሣሪያዎች ታግዞ እየተካሄደ መሆኑን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
ብልፅግና፡ በባለቤቱ በአማራ ቁጥጥር ስር የሚገኘውን ወልቃይትን ከሕወሓት ታጣቂዎች የሚከላከል መስሎ ተኩስ ከጀመረ በኋላ፡ እንደለመደው በስልታዊ ማፈግፈግ ስም ወልቃይትን ሙሉ ለሙሉ ለሕወሓት በማስረከብ “ወልቃይትን ከወረራ እንዳልከላከል ፋኖ እንቅፋት ሆኖብኛል” የሚል ካርድ ለመምዘዝ መዘጋጀቱም ታውቋል።
ብልፅግናም ሆነ የብልፅግና ተላላኪው በአዴን የወልቃይት ጉዳይ ጉዳያቸው አይደለም። እነዚ ሁለት ፀረ አማራ ኃይሎች ወልቃይትን የሚፈልጉት ለፖለቲካዊ ትኩሳታቸው ማብረጃ ብቻ ነው።
ወዲህ ደግሞ በአዴን የወልቃይትን አጀንዳ የሚያነሳው ፋኖን እርስ በእርሱ ለመከፋፈልና ከሕዝቡ ጋር የመነጠል ስራ ለመስራት ነው።
እንጂማ በአዴን በየትኛው ጊዜና ሰዓት ነው የፌደራል መንግስቱ እግር አጣቢ ከመሆን ወጥቶ ለሕዝብ አስቦና ተቆርቁሮ የሚያውቀው።
የአማራን እርስት አሳልፈው የሰጡ በአዴኖች፣ ከክልሉ ውጭ ያለው አማራ ውክልና እንዳያገኝ በማድረግ ለዘር ፍጅት የዳረጉት በአዴኖች፣ ለመጣ ለሄደው የፌደራል መንግስት ዘዋሪ ቡድን ማጎብደድና መላላክ የማይሰለቻቸው በአዴኖች፣ የፌደራል መንግስቱ ከድሮንና ጄት ጀምሮ በአለም አቀፍ የጦር ሕግ የተከለከሉ መርዛማ መሳሪያዎችን ጭምር ታጥቆ የክልሉ ሕዝብ ላይ የዘር ጭፍጨፋ እንዲፈፅም የፈቀዱና አሁንም ይሄንን ዘግናኝ ድርጊት እየመሩና እያስተባበሩ የሚገኙት በአዴኖች፣ ሕዝቡ አማራዊ ስነልቦና
የደጋው መብረቅ ኮር አሃዶች በመቄትና ቋና በሁለት ግንባር በጥላት ሰራዊት ላይ መጠነ ሰፊ ማጥቃት በማድረግ ታላቅ ድል አስመዘገቡ::
የደጋው መብረቅ ኮር አሀድ የሆኑት አንሻ ክፍለ ጦርና ቀኝአዝማች ተበጀ ወርቁ ክፍለ ጦር በሁለቱ ግባሮች ላይ በርካታ የብርሀኑ ጁላን መከላከያ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ተደርገዋል!
አፋብን ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የደጋው መብረቅ ኮር አሀዶች ጥር 20/2018 ዓ/ም በሁለት ግባር ከሶስት ወረዳዎች ለከበባ በመጣ የብርሀኑ ጁላ መከላከያ ሰራዊት ላይ ከባድ ጥቃት ተፈፅሟል።
ከመቄት፣ከጋሸናና ከኮን በሶስት አቅጣጫ ለከበባ የመጣው የጥላት ሰራዊት የከበባ ጥቃት የከፈተ ቢሆንም ፤በፋኖዎቹ በተወሰደ አፀፋዊ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ በሁለቱም ግባር ከ15 በላይ የጥላት ሰራዊት ሲደመሰሱ፤ዘጠኙ ከባድ ቁስለኛ ተደርገዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ከባድ የሰብአዊና ቁሳዊ እንዲሁም ሞራላዊ ኪሳራ የተከናነበው የጥላት ሰራዊት ወደመጣበት ሲመለስ በንፁኋኖች ላይ የፈሪ በትሩን አሳርፎ አርሶ አደሮችን በገፍ ጨፍጭፏል። በፋኖዎቹ የመልሶ ማጥቃት ጥቃት ክፉኛ የተከፈተበት የፋሽስቱ ሰራዊት እግሬ አውጭኝ በማለት ወደየመጣበት ምሽጉ ተመልሷል።
©የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የደጋው መብረቅ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል
ሀገር አፍራሹ የብልፅግና ቡድን በአፋር ሓራ መሬት ብሎ በጠራው አከባቢ እያደራጀው በሚገኘው ታጣቂ ኃይል እና በአፋር ሕዝብ መካከል ከባድ ግጭት ተቀስቅሷል።
ሕዝቡ አፋር የጦርነት ቀጠና አይደለችም፡ በአስቸኳይ ክልላችንን ለቃችሁ ውጡ በሚል ወደ አደባባይ በመውጣት ቁጣውን የገለፀ ሲሆን፡ ታጣቂዎቹ ደግሞ በሕዝቡ ላይ የዘፈቀደ ተኩስ በመክፈት በርካታ ንፁኋንን ማቁሰላቸው ታውቋል።
በአፋር ሐራ መሬት ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በብልፅግና እገዛ እራሳቸውን እያደራጁ በሚገኙት በእነጌታቸው ረዳ እንዲሁም በእነፃድቃን ገብረተንሳይ ታጣቂዎች እና በአፋር ሕዝብ መካከል ሦስተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ከባድ ግጭት መቀስቀሱን ምንጮች ገልፀዋል።
በክልሉ ኪልበቲ ረሱ ዞን በርሃሌ ወረዳ ስር በምትገኘው ቡሬ ተብላ በምትጠራ ቀበሌ የተጀመረው ግጭቱ አሁን ላይ አድማሱን አስፍቶ ታጣቂዎቹ በሰፈሩባቸው በሁሉም አከባቢዎች ተዳርሷል ነው ያሉት ምንጮቻችን።
ብልፅግና ከአማራ ሕዝብ ጋር በሚያደርገው ውጊያ እንዲያግዙት ወዲህ ደግሞ ሕወሓትን ለሁለት ለመክፈል ሲል ስንቅም ትጥቅም ከቤተመንግስት እየሰፈረላቸው በአፋር ክልል ሓራ መሬት በተባለ አከባቢ እያሰለጠናቸው የሚገኙት የነጌታቸው ረዳ ታጣቂዎች ሴት ከመድፈርና የቀንድ ከብት ከመዝረፍ ጀምሮ በአፋር ሕዝብ ላይ ከባድ ሰብአዊ ግፍ እየፈፀሙ መክረማቸው ሲነገር ቆይቷል።
አገዛዙ ከወራት በፊት በዋግኽምራ ብሔረሰብ ዞን ጋዝጊብላ ወረዳ ላይ ከፋኖ ጋር ባደረገው ውጊያ የሓራ መሬት ታጣቂዎች ከመከላከያ ሰራዊት ጎን ተሰልፈው ወደ ውጊያ ገብተው የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ከወደ ፋኖ በተወሰደባቸው የፀረ መከላከልና የመልሶ ማጥቃት እርምጃ ከባድ የሆነ ሰብአዊና ቁሣዊ ኪሳራ መከናነባቸውን በወቅቱ መዘገቡ አይዘነጋም።
አገዛዙ በወቅቱ ለመከላከያ ሰራዊቱ እገዛ እንዲያደርጉለት ታጣቂዎቹን በጭፍራና በቆቦ
ኢትዮጵያ የሕጻናት የወንጀል ተጠያቂነት የእድሜ ገደብን ከ9 ዓመት ከፍ እንድታደርግ የተመድ የሕጻናት መብት ኮሚቴ ትናንት የኢትዮጵያን የሕጻናት መብት ይዞታ በገመገመበት ወቅት ጠየቀ። የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን፣ መንግሥት በጥናት በሚያገኘው ውጤት ላይ ተመስርቶ የእድሜ ገደቡን ለማሻሻል ዝግጁ መኾኑን በመድረኩ ላይ በሠጠው ምላሽ ገልጧል። አንድ የኮሚቴው ባለሙያ፣ ሕጻናት ጭምር ሰላማዊ ሰዎች በተሳተፉባቸውና ሕይወት በጠፋባቸው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፎች ላይ “ያልተመጣጠነ ኃይል” በተጠቀሙ የጸጥታ አካላት ላይ ምርመራ ተደርጓል ወይ? በማለት ጠይቀው ነበር። ልዑካን ቡድኑ፣ በሰላማዊ ሰልፎች ላይ ኃይል መጠቀምን ለመከላከል ረቂቅ ሕግ መዘጋጀቱን ጠቅሶ፣ ባንድ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ተይዘው ታስረዋል የተባሉትን ልጃገረድ ሕጻናት ጉዳይ ግን አጣራለሁ ብሏል። ከሕጻናት የጾታ ጥቃት አንጻር፣ በብሄራዊ ደረጃ “የጾታ ጥቃት ፈጻሚዎች መዝገብ” በቅርቡ ተግባር ላይ እንደሚውል ልዑካኑ ገልጧል። መንግሥት ምን ያህል በጀት ለሕጻናት ተኮር ሥራዎች እንደመደበ ለቀረበው ጥያቄም፣ ከአጠቃላይ አገራዊ ምርቱ ሦስት በመቶው ተመድቧል ሲል ልዑካኑ ምላሽ ሠጥቷል።
አብዱራህማን መሃዲ የሚመሩት የኦብነግ ክንፍ እና ሁለት የሶማሌ ክልል ተቃዋሚ ድርጅቶች በቅርቡ ያቋቋሙት ጥምረት፣ በክልሉ በአፍዴር፣ ሸበሌ እና ዳዋ ዞኖች የተከሠተው ድርቅ “ሰብዓዊ ቀውስ” አስከትሏል አለ። ሰብዓዊ ቀውሱ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ብቻ የተከሠተ አይደለም ያለው ጥምረቱ፣ የመንግሥት “የዝግጁነት ማነስ”፣ “የሰብዓዊ እርዳታ ብክነት” እና “የዘላቂ እቅድ አለመኖር” ጭምር የሰብዓዊ ቀውሱ ምክንያት ናቸው ሲል የክልሉን መንግሥት ወቅሷል። የሰብዓዊ ቀውሱ ሰለባዎች “አስቸኳይ” ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጥምረቱ የጠየቀ ሲኾን፣ የዕርዳታ አቅርቦቱም “በገለልተኛ” አካል ቁጥጥር ሊደረግበት ይገባል ብሏል። በሦስቱ ዞኖች ተከስቷል ላለው ሰብዓዊ ቀውስ በውጭ የሚኖሩ የክልሉ ተወላጅ ሶማሌዎች ዕርዳታ እንዲያሰባስቡ የጠየቀው ጥምረቱ፣ ኾኖም ዕርዳታው በመንግሥት በኩል ሳይኾን “በታማኝ” የረድኤት ድርጅቶችና “በማኅበረሰብ መዋቅሮች” በኩል ብቻ በቀጥታ ለተጎጂዎች እንዲደርስ ጥሪ አቅርቧል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አሥተዳደር,፣ በዋትሳፕ፣ በቴሌግራም እና በሌሎች የመልዕክት መላላኪያ መተግበሪያዎች ላይ የሚፈጸሙ የባይነ መረብ ጥቃት በእጅጉ ተስፋፍቷል በማለት አስጠነቀቀ። የበይነ መረብ ጥቃት ፈጻሚዎቹ በአገሪቱ የሚካሄዱ የተለያዩ ሲምፖዚየሞችን፣ ዓለማቀፍ መድረኮችንና የበይነ መረብ ስብሰባዎችን ለሐሰተኛ ድርጊቶቻቸው መጠቀሚያ እያደረጓቸው እንደሚገኙ ተቋሙ ገልጧል። ተቋሙ፣ ጥቃት ፈጻሚዎች የግለሰቦችንና ተቋማትን የባንክ ሂሳቦች ለመመዝበር፣ የግለሰቦችን የግል መረጃዎች ለመመንተፍ እና የዲጂታል ደኅንነትን ለማናጋት “በተቀናጀ” መልኩ እየሠሩ ስለመኾኑም በክትትልና ምርመራ አረጋግጫለሁ ብሏል። የበይነ መረብ ጥቃቶቹ የሚፈጸሙት በሕዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት የሚሠጣቸውን “ተፈላጊ” እና “ወቅታዊ” ጉዳዮች መነሻ በማድረግ በተዘረጋ “ስልታዊ የማታለያ ዘዴ” ነው ያለው ተቋሙ፣ የዲጂታል መገናኛ ዘዴዎች ተጠቃሚዎች ከማይታወቁ ወይም ካልተረጋገጡ አድራሻዎች በዋትሳፕ፣ ቴሌግራምና በሌሎች የዲጂታል የመገናኛ ዘዴዎች የሚላኩላቸውን የድረገጽ መረጃዎች እንዳይከፍቱና አጠራጣሪ መልዕክቶች ሲደርሷቸው ወዲያውኑ “ሪፖርት” እንዲያደርጉም አሳስቧል።
ዋግ ኽምራ ላይ በቅርቡ ‘በስህተት’ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ህይወታቸው ባለፈ ሚሊሻዎች ስም መንደር ሊገነባ መሆኑ ታወቀ
የሰሃላ ሰየምት ወረዳ ኮሚኒኬሽን ሟቾቹን ‘ሰላም ማስከበር ላይ እያሉ የተሰው የጸጥታ አባላት’ በማለት የገለፃቸው ሲሆን አንድ የወረዳው ሀላፊ ደግሞ “እውነት ነው፣ በድሮን የሞቱትን በተመለከተ ነው” የሚል የአጭር ፅሁፍ መልዕክት ምላሽ ለሚድያችን ሰጥተዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/f69
ቲክቶክ የአሜሪካ የጣምራ ድርጅቱን ይፋ ካደረገ በኋላ በአማካይ በየቀኑ መተግበሪያውን የሚያጠፉ የአሜሪካ ተጠቃሚዎች ቁጥር ከባለፉት ሶስት ወራት አንፃር በ150% መጨመሩ ተዘግቧል።
በርካታ የአሜሪካ ተጠቃሚዎች የቲክቶክ አዲሱ ፖሊሲ የሰዎች የዘር ማንነትና ምንጭን መረጃ እንደሚሰበስብ የገለጹ ሲሆን፣ በተጨማሪ ስደተኛና ዜጋ መሆናቸውን እንደዚሁም ወሲባዊ ህይወትን በተመለከተ መረጃ ይሰበስባል ብለዋል።
ይህም በርካታ ተጠቃሚዎች የአሜሪካው የቲክቶክ ተቋም ይፋ ከሆነ በኋላ መተግበሪያውን እንዲያጠፉ ምክንያት ሆኗል ተብሏል።
ሌሎች ተጠቃሚዎች ደግሞ ቪዲዮ በሚለቁበት ወቅት ችግር እንደገጠማቸው ሲገልጹ የአሜሪካው ተቋም ችግሩ በአሜሪካ የዳታ ማዕከል ላይ ባጋጠመ ችግር መከሰቱን ገልጿል።
የቲክቶክ መተግበሪያ መጥፋትን ተከትሎ የተፎካካሪዎቹ የአፕስክሮልድ መተግበሪያን የሚጭኑ ሰዎች በአስር እጥፍ ሲጨምር፣ የስካይላይት ሶሻል በ919% እንደዚሁም የሬድኖት ደግሞ በ53% በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ጨምሯል።
ዘገባው የሲኤንቢሲ ነው።
ስፔን በሃገሯ ያሉ በመቶ ሺህዎች ለሚቆጠሩ ስደተኞች የህጋዊ ፈቃድ ልትሰጥ እንደሆነ ገልፃለች።
የስፔን የስደተኞች ሚኒስትር ኤልማ ሳይዝ በስፔን ያለ ፈቃድ ያሉ ስደተኞች በስፔን እስከ አንድ አመት የሚቆይ የስራ ፈቃድና የመኖሪያ ፈቃድ እንዲያገኙ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
ፈቃዱ የሚሰጠው ከፈረንጆቹ ታህሳስ 31፣ 2025 በፊት ወደ ስፔን ለገቡ ስደተኞች መሆኑና በስፔን ከአምስት ወራት በላይ ስለመኖራቸው ማስረጃ ለሚያቀርቡ እንደዚሁም የወንጀል ታሪክ ለሌላቸው ነው ተብሏል።
በውሳኔው በስፔን የሚኖሩ ከ500 ሺህ እስከ 800 ሺህ ስደተኞች ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሚኒስትሩ ስደተኞቹ ፖሊሲው ወደ ስራ ከገባ በኋላ ከመጪው ሚያዝያ ወር ጀምሮ ማመልከት እንደሚችሉ ገልጿል።
ዘገባው የአፍሪካ ኒውስ ነው።
ወደ ትግራይ ክልል የሚደረጉ መደበኛ የአየር በረራዎች ከዛሬ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ መቋረጣቸው ታወቀ
ሚድያችን ማምሻውን እንዳረጋገጠው የመጨረሻው የትግራይ መደበኛ በረራ ዛሬ ምሽት 3:30 ላይ ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ የተደረገ ሲሆን ከነገ ጀምሮ ግን ሁሉም በረራዎች እንደተሰረዙ ታውቋል።
ተጨማሪ ያንብቡ: https://meseretmedia.org/p/acb
የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ከተስፋፋ፣ ሰብአዊና ስትራቴጂካዊ አደጋ ይሆናል።
የቀይ ባህር ፉክክር የአፍሪካ ቀንድን የሚያጋልጥ አደጋ።
ዋሽንግተን የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይዛመት መከላከል አለባት …… የRSF ዋና ደጋፊ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) በኢትዮጵያ በኩል አዲስ ግንባር ከፍቷል። እንዲህ ማድረግ ግጭቱን የበለጠ ክልላዊ ያደርገዋል፣ ይህም በሳውዲ አረቢያ እና በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መካከል ባለው የተፅዕኖ ጦርነት ውስጥ ሌላ ወሳኝ ነጥብ ይፈጥራል እንዲሁም ግብፅን እና ኤርትራን በቀጥታ ወደ ውስጥ ያስገባል። …… ዝርዝሩን እነሆ https://miniliksalsawi.substack.com/p/if-sudans-civil-war-spreads-to-ethiopia
በአማራ ሳይንት ወረዳ አጅባር ከተማ 01ቀበሌ የአስት ዮሃንስ ወልደ ነጎድጓድ ቤተክርስቲያን እና የፋሬታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን እድሜ ጠገብ ታሪካዊ ቅርሶች በአገዛዙ ወታደርች ዘረፋ ተፈፀመባቸው!
የአገዛዙ ወታደሮች ዛሬ ጥር 20/2018 ዓ/ም አዳራቸውን በሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የነበሩ ቅርሶችን መዝረፋቸውን ተከትሎ በአሁን ሰዓት በአከባቢው ከባድ ውጥረት ነግሷል።
የአከባቢው ማሕበረሰብ ቅርሶቻችንን መልሱ በሚል የአገዛዙ ወታደሮችን ተቃውሞ ወደ አደባባይ የወጣ ሲሆን፡ ወታደሮቹም ሕዝቡን ለመበተን ተኩስ መክፈታቸውን የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ዘረፋ የተፈፀመባቸው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቤተክርስቲያን እና ፋሬታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከ200 ዓመታ በላይ እድሜ ያስቆጠሩ ቅርሶች መገኛ ቅዱሳን ስፍራዎች ናቸው።
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ኢሕአፓንና መኢአድን ጨምሮ ስምንት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከእጩዎች የዲጂታል ምዝገባ ጋር በተያያዘ ሰሞኑን ያቀረቡትን ቅሬታ “አግባብነት የሌለው” እና “የእጩዎችን ምዝገባ ከማስተጓጎል” ያለፈ ምንም ጥቅም የሌለው ነው በማለት አጣጣለ።
ቦርዱ፣ ከብሄራዊ መታወቂያ ውጭ ለቀጣዩ ምርጫ የእጩዎች ምዝገባ የጠየቀው አዲስ “ሰነድ” ወይም “ማስረጃ” እንደሌለ ለፓርቲዎቹ ቅሬታ በሠጠው ምላሽ ገልጧል።
ከከተሞች ውጭ ያሉ እጩዎች ለምዝገባ የትውልድ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ካልቻሉ ሲወለዱ በአካል የነበረ የዓይን ምስክር ማቅረብ እንዳለባቸው ቦርዱ ግዴታ አስቀምጧል በማለት ፓርቲዎቹ ያቀረቡት ቅሬታ ስህተት አለበት ያለው ቦርዱ፣ የውልደት ምስክር ወረቀት ማቅረብ ያልቻለ እጩ በሚወዳደርበት የምርጫ ክልል መወለዱን በሚያውቁ የሰው ምስክሮች ማረጋገጥ እንደሚችል አማራጭ ማስቀመጡን አብራርቷል።
ቦርዱ፣ እጩዎች ከወከሏቸው ፓርቲዎች እውቅና ውጭ ራሳቸውን ከእጩነት ማግለል እንዲችሉ ተፈቅዷል የተባለው ቅሬታም ከአሠራሩ ውጭ የኾነ ቅሬታ ነው ሲል አስተባብሏል።
ተቀማጭነቱን በአዲስ አበባ ያደረገ እና ለውጪ ሚድያ የሚሰራ አንድ እንግሊዛዊ ጋዜጠኛ ከሀገር በግዳጅ እንዲወጣ መደረጉ ተሰማ
ጋዜጠኛውን ለአንድ ቀን እስር እና ከሀገር ለመባረር (deportation) የዳረገው ሁኔታ ምንድነው?
ዝርዝሩን ይዘናል ያንብቡ: https://meseretmedia.org/p/bc6
የሙጃ ማርያም ከተማ ኗሪው ወጣት ባለሐብት በአገዛዙ ሰራዊት በጭካኔ ተገደለ!
በሰሜን ወሎ አስተዳደር ዞን ግዳን ወረዳ መናገሻ ሙጃ ማርያም ኗሪ የሆኑት ወጣት ባለሐብት አራጋው ሲሳይ በአረመኔው ብልፅግና ሰራዊትና አመራሮች ጥር 17/2018 ዓ/ም አመሻሽ 2:00 ሰዓት ላይ በግፍና በአሰቃቂ ሁኔታ አንድያ ህይወቱ ልታልፍ ችላለች።
በግዳን ወረደ ብልፅግና አመራሮችና በብርሃኑ ጁላ ሰራዊት አዛዦች የጦስ ዶሮ የሆነው ወጣት ባለሐብት በተሸረበበት ሴራ 5ሚሊዮን ብር ለአብይ አህመድ ወንበር መፅናት ለሚታትሩ መከላከያ አመራሮች የሐብት ማከማቻ ግዛት እንዲከፍል፣ባይከፍል እንደሚገደል ውሳኔ ተወስኖ እንዲከፍል ሲነገረው እንደሚገድሉት ስላወቀ ካሶኒውን ሽጦ ቢከፍላቸውም የፋኖ ደጋፊ ስለሆነ መረሸን አለበት በሚል ውሳኔ በአረመኔዎቹ የጦስ ዶሮ ሊሆን ችሏል።
ይህንን ግድያ ያስተባበሩትና የውሳኔ አካል የሆኑት
1ኛ. እንዳለው አባተ:- የግዳን ወረዳ ሚሊሻ ፅህፈት ቤት ኃላፊ
2ኛ. አማኑኤል አያሌው:- የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ
3ኛ. ሰማኝ ባዮ:- ሰላምና ፀጥታ ኃላፊ እና
4ኛ. ሙጃ ከተማ የሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት አዛዥ ሲሆኑ በቀጥታ በጄኔራል አሰፋ ቸኮል ትዕዛዝ ከዚህ በፊት እያንዳንዳቸው 1.5ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉና ካልከፈሉ እንደሚረሸኑ ተነግሯቸው የተጠየቁትን ከከፈሉ በኋላ ወጣቱ ባለሐብት እንዲረሸንና አፈፃፀሙን እንዲያስተባብሩ የተሰየሙ ጥቁር አማራዎች መሆናቸውን የውስጥ መረጃዎች አሳውቀዋል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማኑኤል አያሌው በመሩት የመንግስት ሰራተኞች መድረክ ላይ መንግስት አገልጋዩን ሰብስቦ ሰሞኑን የሚረሸን ሰው አለ በማለት የተናገረ ሲሆን በተናገረ ሁለት ቀን ባልሞላው ውስጥ ወጣቱን ባለሐብት አምስት መከላከያዎች በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ደፈጣ ይዘው በአምስት ክላሽንኮፍ ጥይት በሳስተው ከገደሉት በኋላ ለሌሎች
በዲጂታል ዘመን የሚካሄድ ምርጫ እና ፈተናዎቹ!
/ኢትዮጵያ ቼክ/- መንግስት እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የሰዎችን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ለመገደብ ሲሰሩ አልፎ አልፎ ይታያሉ፣ በተለይ ደግሞ በምርጫ ወቅት።
ከነዚህም ውስጥ:
1. የኢንተርኔት መዘጋት
በርከት ያሉ መንግስታት ኢንተርኔትን በመዝጋት እና ቴሌኮሚኒኬሽን በማቋረጥ የፍትሃዊ የምርጫ ስርዓቱን ሲያስተጓጉሉ ይታያሉ። ኔትወርክን ማቋረጥ ሰዎች ማግኘት ያለባቸውን መረጃ ሆን ተብሎ በማቋረጥ የሰዎችን የሰብዓዊ መብትን መጋፋት ነው። ኔትወርክን ማቋረጥ የዓለም አቀፍ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ስምምነት
አንቀጽ 19(3) ጋር በግልፅ ይቃረናል።
የሰብዓዊ መብቶች ኮሚቴ እንዳስቀመጠው ከሆነ በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የኔትወርክ ማቋረጥ ተገቢ ሊሆን አይችልም ይላል። ለህብረተሰቡ ደህንነት በሚልም ሆነ ለብሄራዊ ደህንነት ሲባል የኔትወርክ መቋረጥን እንደተገቢ እርምጃ መውሰድ አይቻልም። የኔትወርክ መቋረጥ የተለያየ መልክ ሊይዝ ይችላል እነሱም ኢንተርኔትን መዘጋት፣ የስልክ ኔትወርክን ማቋረጥ፣ የአጭር የስልክ መልዕክትን መዘጋት፣ የማህበራዊ ትስስር ሚዲያዎች በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ መዘጋት ሊሆኑ ይችላል። በተለይ በምርጫ ወቅት የኔትወርክ መቋረጥ ከፍተኛ ጉዳትን ይዞ ይመጣል።
ስለምርጫው አጠቃላይ ስለሚወጡ መረጃዎች፣ ስለ እጩ ተወዳዳሪዎች አቋም፣ በምርጫው ቀን ደግሞ ስለምርጫ ጣቢያዎች እና የመሳሳሰሉትን መረጃዎች ሰዎች እንዳያገኙ ያደርጋቸዋል። ይህም ደግሞ በተዘዋዋሪ የዜጎችን በነፃ እና በግልፅ የፓለቲካ ምህዳር ውስጥ ተሳትፎ ያግዳል።
2. የሀሰተኛ መረጃን የመከላከል ስራ
በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስታት የሀሰተኛ መረጃን ስርጭት ለመቀነስ/ለመቆጣጠር ሲባል የተለያዩ ህጎችን እና መመሪያዎች ሲያፀድቁ አይተናል። የሀሰተኛ መረጃዎች መሰራጨት በመራጮች ላይ እንዲሁም በአጠቃላይ በዴሞክራሲ አውዱ ላይ ብዙ ተፅዕኖ
ብልፅግና የመጨረሻ ያለውን ካርዱን ወልቃይት ላይ መዟል!
በጠለምት ዋልድባ አካባቢ ማይ-ዳጉሻን ጨምሮ በአራት ግንባር ከትናንት ጥር 18/2018 ዓ/ም ጀምሮ ውጊያ ተቀስቅሷል።
ብልፅግና፡ በባለቤቱ በአማራ ቁጥጥር ስር የሚገኘውን ወልቃይትን ከሕወሓት ታጣቂዎች የሚከላከል መስሎ ተኩስ ከጀመረ በኋላ፡ እንደለመደው በማፈግፈግ ወልቃይትን ሙሉ ለሙሉ በሕወሓት ታጣቂዎች የማስወረር እቅድ እንዳለው ነው የተነገረው።
ስልታዊ ማፈግፈግ በሚል የአማራ ሕዝብ ላይ የነበረውን የጥላቻ ጥማት የተወጣው ብልፅግና ዛሬም በዚችው ማሊያ ለመጫዎት ካርዱን መምዘዙ ታውቋል።
አስወረርከን የሚል ጥያቄ ሲነሳበትም “የሕወሓት ታጣቂዎችን ከወልቃይት እንዳላስወጣ ፋኖ እንቅፋት ሆኖብኛል” የሚል ካርድ ለመምዘዝ መዘጋጀቱን የመረብ ሚዲያ ምንጮች ገልፀዋል።
ይህ ነውረኛና ፀረ አማራ ቡድን በአክቲቪስቶቹ በኩል የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወልቃይትን በሕወሓት አስወረረብን የሚል የለቅሶ ፖለቲካ ለመስራት ድንኳን ተከላ ጀምሯል።
የእኛ አምላክ ባርጆ ነው። የአንተ አምላክ ከባርጆ ከበለጠ ነገ ዝናብ እንዲያዘንብ ንገረው።…ሐመሮች ሊቀጳጳሱ የፈተኑበት ጥያቄ***

በአንድ ወቅት የቀድሞው የሰሜን ኦሞ [ደቡብ ኦሞ ፣ጋሞ ጎፋ፣ዳውሮ፣ወላይታ] ሀገረሰብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት እና አሁን በዕረፍት ሥጋ የተገቱት ሊቀ ጳጳስ ብፁዑ አቡነ ዕንባቆብ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ ደቡብ ኦሞ ዞን የአርብቶ አደሮች ምድር ወደ ሆነችው የሐመሮች መንደር ይሄዳሉ። ክላሽ ታጥቀው፤መፋቂያ ጥርሳቸው ላይ ሰክተው ለአፍረተ ስጋቸው ብቻ ብጣሽ ጨርቅ ገላቸው ላይ ጥለው በእዛ ሐሩር በሚያቀልጥበት በረሐ እራቁታቸውን የሚሄዱ የሐመር አርብቶ አደር ወጣቶቸው ጥቁር ቀሚስ ከጥቁር አስኬማ ጋር አድርገው ዱላ [በትረ ሙሴ] የያዙትን አረጋዊውን ሊቀ ጳጳስ እንደ ልዩ ፍጥረት በአግራሞት ያያሉ።በሐመሮች መንደር ” ለሐዋርያዊ አገልግሎት መጥቻለው” ተብሎ ዝም ብሎ በድፍረት ወንጌል መስበክ አይቻልም። ምን አልባትም በድፍረት አደርጋለው ከተባለ ህይወትን የሚያስገብር ታላቅ ሞት ጠሪ ድፍረት ይሆናል።ለምንም ዓይነት መንግስታዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ተግባር ቅድሚያ የሐመሮችን የማኅበረሰቡን መሪ የሆኑትን በዕድሜ የጎለመሱት አባትን ፍቃድና ይሁንታ ማግኘት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ቋሚ አሰራርም ጭምር ነው።ሊቀ ጳጳሱም ለወንጌል አገልግሎት ፍቃድ ለማግኘት የሐመሮችን ባለአባት ለማግኘት ወደ ሐመሮች የጎሣ መሪ እልፍኝ ውስጥ ከአስተርጓሚያቸው ጋር ገቡ።የሐመር ባለአባትም ጥቁር በጥቁር ሆነው የመጡትን ሊቀ ጳጳስ ተመለከቱ። ለተከበረ ሰው የሚቀርበውን የቁርበት ምንጣፍ አስወጥተው እንዲነጠፍላቸው አስደረጉ። በተነጠፈውም ቁርበት ላይ ሊቀ ጳጳሱ እንዲቀመጥ አዘዙ። ሊቀ ጳጳሱ የመጡበትን ጉዳይ ለሐመር ባለአባት አስረዱ፤”የሐመር አባላትን ጥምቀት አስጠምቀው ኦርቶዶክስ ለማድረግ እንደሚፈልጉ እና እግዚአብሔር የሚባል አምላክን እንዲቀበሉ” በግልጽ ተናገሩ።
ብልፅግና አየር ሃይሉን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ከሞተበት አስነሳሁት እንደሚለው ሳይሆን እነ ብርሃኑ ጁላና ይልማ መርዳሳ አየር ሃይሉን በባሰ ሁኔታ ምን ያክል መቀመቅ እንደከተቱትና በዘርና በፒለቲካ አድሏዊነት የአየር ሃይልን ፕሮፌሽን ምን ያክል እንደገደሉት የሚከተሉት በሰባት አመት ውስጥ የተከሰቱ ተጨባጭ መረጃዎች ያሳያሉ ከነዚህም ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል

1 – አየር ሃይሉን በፍፁም ዘረኝነትና ወገንተኝነት በማዋቀር በርካታ የተቋሙን የአማራና የትግራይ ተወላጅ አመራሮችንና ፓይለቶችን በማግለል በማሳደድና ከዛም አልፎ ለእስርና ስደት በመዳረግ ሃገሪቱ ከፍተኛ ሪሶርስ በማውጣት የአሰለጠነቻቸውን ከ መቶ በላይ ( ስማቸውን መዘርዘር ይቻላል ) ብርቅየ አብራሪዎች በዘርና በፒለቲካ አስተሳሰብ ሃገራቸውንና ተቋማቸውን እንዳይጠቅሙ ተደርገዋል የዚህም ውጤት ማሳያው ዛሬ በርካታ የበረራ ስኳድሮኖች ሲኔር ፓይለቶቻቸውንና አመራሮቻቸውን አጥተው ከፍተኛ ዶላር ወጭ ተደርጎ በውጭ መርሰነሪ ፓይለቶች ተተክተዋል ለምሳሌ አሁን ላይ ብልፅግና የሚኮፈስበትና ፕሮፓጋንዳ እየሰራበት ያለው ኤር ሾው ላይ የተሳተፉት በሙሉ በሚባል ደረጃ የውጭ መርሰነሪ ፓይለቶች ናቸው
ለምሳሌ su -27 – Russian retired pilots
Yak-130 Russian retired pilots
Grob -120 Paraguay & Argentina
L-39 – check Republic pilots
ሲሆኑ በተለይም L-39 አድቫንስድ ጀት ማሰልጠኛና su 27 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ በውጭ አስተማሪዎች ተተክተዋል ። ይሄም የብልፅግና ዘረኝነትና ብሔርተኝነት ምን ያክል ፕሮፌሽንኑን እየጎዳው እንዳለ ያሳያል ።
2- ከሰሞኑ በብልፅግና የሚዲያ ሰራዊት ብዙ ሲወራና በ ፋና በኢቢሲ ብዙ ሲነገርለት የነበረው አጠቃላይ ራሻን ጨምሮ አምስት ሃገራት በዚህ ኤርሾው ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ ቢጠበቅም በሃገሩና በጎረቤት ሃገራት

ዜና ዕረፍት፣ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። ቅዱስ ሲኖዶስም “ሥርዓተ ቀብራቸው በደብረ ሊባኖስ ገዳም ይፈጸማል” ሲል የጠቅላይ ቤተ ክህነት ቴሌቪዥን ዘግቧል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ለቤተ ክህነት ቴሌቪዥን እንደገለጸው ከሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ሥርዓተ ቀብር ነገ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም በተማሩበት በመነኮሱበት እና ለረጅም ዓመታት ባገለገሉበት በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ይፈጸማል።
=====
ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ማን ነበሩ?
=======
+ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም በቀድሞ ስማቸው ጸባቴ ተክለ ሐዋርያት ባሳዝነው ይባሉ ነበር።
+ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም (የቀድሞው ፀባቴ ተክለ ሐዋርያት ባሳዝነው) በደብረ ብርሃን አውራጃ በሚገኘው በእነዋሪ ወረዳ ልዩ ስሙ ከያዱር በዓለ ወልድ በሚባለው ቀበሌ ከአባታቸው ከአቶ ባሳዝነው ወንድም አገኘሁና ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለ ማርያም ማናየ ተወለዱ፡፡
+ ዕድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ በዚሁ አካባቢ ወደሚገኘው ወደ ደብረ ብሥራት ዜና ማርቆስ ገዳም በመሄድ ፊደል መቁጠር እንደጀመሩ ወደ ሰቃ መድኃኔ ዓለም ገዳም በመሄድ ቅኔና ትርጓሜ መጻሕፍት ከሚያስተምሩት ከታላቁ ምሁር አባት ከመምህር አባ ዘካርያስ ኃይለ ማርያም ዘንድ (ዛሬ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ) ከፊደል ጀምሮ ንባብ ከነቃል ትምህርቱ ተምረዋል፡፡ እንዲሁም በእሳቸው እየተወከሉ ከሚያስተምሩ ከመምህር አስበ ጸድቅ ወርቅነህና ከአባ ተክለ ሃይማኖት ሀብተ ጊዮርጊስ ዳዊት ተምረዋል፡፡ ከዚያም በመቀጠል በዚሁ ገዳም ቅዳሴ ያስተምሩ ከነበሩት
በበርካታ የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ በተከሰተው እጅግ ከባድ ቅዝቃዜ ያለበት የአየር ሁኔታ ምክንያት በተለያዩ ቦታዎች የሰዎች ሕይወት እየጠፋ ነው ተባለ።
ካለፈው ሳምንት ማብቂያ ቀናት አንስቶ በአሜሪካ ባጋጠመው የበረዶ ወጀብ ምንም እንኳን የአንዳንዶቹን ምክንያት በትክክል ለማረጋገጥ ገና ቢሆንም እስካሁን ቢያንስ 14 ሰዎች በተለያዩ ግዛቶች ውስጥ ሞተዋል።
➡️ የቴኒሲ ግዛት ባለሥልጣናት ከአየር ሁኔታው ጋር በተያያዘ ሦስት ሰዎች መሞታቸውን አረጋግጠዋል።
➡️ ከበረዶው ወጀብ ጋር በተያያዘ የሁለት ሰዎች ሞት በሉዊዚያና ግዛት ውስጥ ተመዝግቧል።
➡️ ቴክሳስ ውስጥ በአንድ ነዳጅ ማደያ ውስጥ ሞቶ የተገኘ ግለሰብ ምክንያቱ የጤና ወይም ከቅዝቃዜው ጋር የተገናኘ ሊሆን እንደሚችል ፖሊስ ገልጿል።
➡️ ቴክሳስ ውስጥ አንዲት የ16 ዓመት ታዳጊ በረዶ ላይ ስትንሸራተት በገጠማት አደጋ ሕይወቷ አልፏል።
➡️ ማሳቹሴትስ ውስጥ አንዲት ሴት በረዶ ተደርምሶባት ሞታለች።
➡️ ካንሳስ ውስጥ ደግሞ አንዲት ሴት በበረዶ ተሸፍና ሞታ ተገኝታለች።
የሞታቸው ምክንያት ገና ባይረጋገጥም ኒው ዮርክ ውስጥም አምስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በሌላ በኩል አሜሪካንን በመታት በሰሞነኛው ከባድ በረዶ በሜይን ዝጋት ስምንት ሰዎችን ያሳፈረ የግል ጄት ባንጎር ከተባለ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲነሳ ተከስክሷል። የተሳፋሪዎቹ ሁኔታ እና ማንነት ለጊዜ አልታወቀም።
በአሜሪካ ያለው ሁኔታ ለአየር ትራንስፖርትም ፈተና ሆኗል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ሌሎችም አየር መንገዶች በአሜሪካ ባለው መጥፎ የአየር ፀባይ የተነሳ በረራዎችን ሰርዘዋል። በሺዎች የሚቆጠሩ በረራዎች ነው የተሰረዙት።
መረጃው ከቢቢሲ ነው የተገኘው።
ኢትዮጵያ የፈረንሳይ ስሪት የሆኑ ‘ሚራዥ 2000’ የተባሉ ተዋጊ ጀቶችን በቅርቡ ልትረከብ መሆኑ ይፋ ሆነ
ጀቶቹ ከየት ሀገር ተገኙ? በምን ስምምነት? የጀቱ አቅም ከሌሎች አንፃር እንዴት ይለካል? በዚህ ዙርያ በቀጠናው የተሰጡ አስተያየቶች ምን ይመስላሉ? ዝርዝሩን ይዘናል ⤵️
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/2000
ባህር ዳር ውስጥ ለመጀመርያ ግዜ ሁለት አለም አቀፍ ስም እና ዝና ያላቸው ሆቴሎች ሊገነቡ መሆኑ ታወቀ
“እነዚህ ሆቴሎች ለባህር ዳር የመጀመርያ አለም አቀፍ ሆቴሎች ይሆናሉ፣ በክልሉ ያለውን የቱሪዝም አቅም አሟጦ ለመጠቀም ቁልፍ ኢንቨስትመንቶች ናቸው”
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/cb0
‘ሐራ መሬት’ በሚል ስም የተደራጁ የትግራይ ኃይሎች በአፋር ክልል በረሀሌ ወረዳ ውስጥ ከሕዝብ ጋር ዛሬ ቀትር ላይ መጋጨታቸው ታወቀ
በኢትዮጵያ የፌደራል መንግስት እንደሚደገፉ የሚነገርላቸው እነዚህ የታጠቁ የትግራይ ኃይሎች በአፋር ክልል ክልበቲ ረሱ፣ በረሀሌ ወረዳ ‘ቡሬ’ ተብላ በምትጠራ ቀበሌ ለመስፈር በዝግጅት ላይ እንዳሉ ከአካባቢው ህዝብ ጋር በዛሬው ዕለት ግጭት ውስጥ መግባታቸው ታውቋል።
https://www.meseretmedia.org/p/944
በምስራቅ ጎጃም ዞን ከታፈሱ 1330 ወጣቶች መካከል 850 የሚደርሱት ከደብረ ማርቆስ ማሰልጠኛ ካምፕ መጥፋታቸው ተረጋግጧል”
እነዚህ አራት ወጣቶች ደረጀ ጎሹ፣ ደሳለኝ ወርቁ፣ እንዳለ ይበልጣልና ዝጋለ ሰጤ ይባላሉ በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ከመርጡለ ማርያም ከተማ መሐል አደባባይ ታፍሰው ድቅድቅ ባለው ጨለማ ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ ከተጓዙ 110 ወጣቶች መካከል ይገኙ ነበር።
ደሳለኝ ወርቁ በመርጡለ ማርያም ከተማ ዙሪያ የሸዋት ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን ከአመታት በፊት በደረሰበት የአንጀት መታጠፍ በቀዶ ጥገና ህክምና ህይወቱ የተረፈች መሆኑን የሚመሰክር ለምጽ በሆዱ መሀል ተመልክተናል። ቀሪ ሶስት ወጣቶች ከተሰማሩበት የጉልበት ስራ በሚኒሻዎች ታፍሰው ከደሳለኝ ወርቁ ጋር በአንድ መኪና ተጭነው ደብረ ማርቆስ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እራሳቸውን ማግኘታቸውንም ከታፋሾች አንደበት ሰምተናል።
ሚኒሻዎች እየደበደቡ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ከወሰዱን በኋላ ስልካችንን ቀምተው ምሽት በአንድ መኪና አጭቀው የወሰዱን 60 የመርጡለ ማርያም ከተማ ወጣቶችና 50 የዙሪያ ቀበሌ ወጣቶች በድምራችን 110 ሁነን ደብረ ማርቆስ ከተማ ስንደርስ ከምስራቅ ጎጃም ዞን ወረዳዎች ታፍሰው ከመጡት ጋር 1330 እንሆን ነበር ያሉት ወጣቶቹ በወታደራዊ ካምፕ ለ10 ቀናት መቆየታቸውን ያስታውሳሉ ።
በደብረ ማርቆስ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ በገባን በሁለተኛው ቀን ለሁለት ከፍለው ወደ አዳራሽ ወስደው የሀይማኖት አባቶች፣ ሴቶች፣ ወጣቶችና ሽማግሌዎች የሚደበደቡበትን video እንድንመለከት ካደረጉን በኋላ ከዚህ ወጣችሁ ብትጠፉ ጥንፈኛው እንደዚህ ያሰቃያችኋል እያሉ ሲያሸማቅቁን እኛ እየሳቅን እንመለከታቸው ነበር እያሉ በፈገግታ የገጠማቸውን ነገር ሁሉ እያወጉን አረፈድን።
ለቀን ስራ ይሆናል ብለን በለበስነው ልብስ ስፖርት ሲያሰሩን የነበሩትም ከታፈሱት
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴውድሮስ (፭) ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አርበኛ ታድሎ ደሴ (ካስትሮ) ከየፈረንሳዩ የድረ ገጽ ጋዜጣ ሚዲያፓርት (Mediapart) ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ የሚከተለውን ተናግረዋል::
«የእኛ ተነሳሽነት ሕፃናትን ጨምሮ በግዳጅ ከተመለመሉት ወታደሮች ሠራዊት የላቀ ነው። ፋኖዎች ለነጻነታቸውና ለሕዝብ ነፃነት ነው የሚታገሉት»
ሙሉ የዜና ዘገባውን ከዚህ በታች ማግኘት ይቻላል:: https://miniliksalsawi.substack.com/p/they-burned-everything-in-northern
ከሁለት ዓመት ለተሻገረ ጊዜ በበርካታ የተለያዩ ዕዞች ስር ሆነው ከመንግሥት ጋር ሲዋጉ የቆዩት የፋኖ ኃይሎች፤ በመጨረሻም ወደ አንድ ድርጅት የመጡ ይመስላል።
በዘመነ ካሴ የሚመራው አማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) እና በእስክንድር ነጋ የሚመራው የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ራሳቸውን “አክስመው” አንድ ታጣቂ ድርጅት መፍጠራቸውን ይፋ አድርገዋል።
“የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)” የሚል ስያሜ የያዘው አዲሱ ድርጅት፤ “የመጨረሻዎቹ የፋኖ ኃይሎች ተዋህደው” የፈጠሩት እንደሆነ የድርጅቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ሆነው የተመደቡት አስረስ ማረ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
የፋኖ ኃይሎች አዲስ ድርጅት መመሥረታቸውን ይፋ ያደረጉት፤ ለበርካቶች ሞት እና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ሕጻናት ከትምህርት ውጪ መሆን ምክንያት የሆነው የአማራ ክልል ግጭት ወደ ሦስተኛ ዓመቱ እያመራ ባለበት ጊዜ ነው።
እንደ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ ኮሎኔል ፈንታው ሙሀባው እና እያሱ አባተ ያሉ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት አመራሮችም የትጥቅ ትግልን በመተው ከመንግሥት ጋር ስምምነት የፈጸሙትም በዚሁ ሰሞን ነው።
መንግሥት የሰላም ንግግርን በተመለከተ በተለይም ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አባላት በሚሰጣቸው ማብራሪያዎች ላይ የፋኖ ኃይሎች የተበታተነ ዕዝ ስር መሆንን እንደ አንድ እንቅፋት ሲጠቅስ ቆይቷል። አሁን የፋኖ ኃይሎች የአንድ ድርጅት ምሥረታ በመንግሥት በኩል ሲነሳ የቆየውን አንድ ተግዳሮት የሚያስወግድ ይመስላል።
በእርግጥ ግን የፋኖ ኃይሎች ወደ አንድ መምጣት የሰላም ንግግርን ያቀርባል? ወይስ የተገዳዳሪነት ስሜትን በማጠናከር ድርድር እንዲገፋ ያደርጋል?
ባልተማከለ ዕዝ የተመራ የትጥቅ እንቅስቃሴ
የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በሰላም እና ደኅንነት ላይ የሠሩት ዶ/ር ዳንኤል (ስማቸው የተቀየረ)፤ የፋኖ ኃይሎች እንቅስቃሴ
የጅቡቲ አየር ሀይል አፋር ክልል ውስጥ ዘልቆ በመግባት ተደጋጋሚ የድሮን እና የጄት ጥቃት እየፈፀመ መሆኑ ታወቀ
ጥቃቱ ማን ላይ አነጣጠረ? ምን ያህል ጉዳት አደረሰ? የትኞቹ ቦታዎች ጥቃቱን አስተናገዱ? በጅቡቲ እና ኢትዮጵያ መንግስታት በጥቃቱ ዙርያ የተባለው ነገር ምንድነው?
ዝርዝሩን ይዘናል
ተጨማሪ ያንብቡ: https://meseretmedia.org/p/30b