Blog Archives

በፊልድ ማርሻሉ እና በዕዝ አዛዦች መካከል ከባድ ፍጥጫ …. በቅርቡ የገዛነው መሣሪያ እንዴት በፋኖ እጅ ገባ? ሲል ፊልድ ማርሻሉ ጄኔራሎቹን አፋጧል !

Posted in News

ተመስገን ጥሩነህና እስክንድር ነጋ …… በአብኖች የቀረበው የወሎ ክልልነት ጥያቄ

Posted in News

በጎጃም አዲስ ትንቅንቅ! ……የአዲስ አበባው ሰልፍና ባለስልጣናቱ!

Posted in News

የደሴ፣ የደብረ ብርሃንና የወልዲያው አድማ! ብልፅግና የውጭ ጀነራሎችን ቀጠረ!

Posted in News

40 በመቶ ተወረናል ! ጄኔራሉ

Posted in News

ዋናው ጄኔራል ድንበር አቋርጠው ተሻግረዋል (ዘመቻ አንድነት)

Posted in News

መግደልን ያስተማረን አብይ ነው፡……. በተጨከነብን ልክ ጨክነናል! ,…… አርሶ አደሩ ሞፈሩን ጥሎ ወደ ግምባር ጎረፈ!

Posted in News

የፕሬስ ነፃነትና አደገኛ አዝማሚያዎች

ዮናስ አማረ Reporter Amharic ለ20 ዓመታት በተለያዩ የኅትመትና የዲጂታል መገናኛ ብዙኃን ውስጥ ሲሠራ የቆየው ጋዜጠኛ ፋኑኤል ክንፉ ሚያዚያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም. ሌሊት 11 ሰዓት ግድም የፌዴራል ፖሊስ የተካተተበት የፀጥታ ኃይሎች ወደ መኖሪያ ቤቱ እንደመጡ ይናገራል፡፡ እርሱም፣ ባለቤቱም ሆነ ልጆቹ በር ሲንኳኳ በሌሊት ‹‹የማን መርዶ ነጋሪ መጣ›› ብለው ተደናግጠው ከእንቅልፋቸው መንቃታቸውንም ይገልጻል፡፡ በሩን ሲከፍትላቸው ወደ ቤቱ የዘለቁት የፀጥታ ኃይሎች እንደሚፈለግና ይዘውት እንደሚሄዱ ነግረው፣ የእጅ ስልኩን ተቀብለው መታወቂያውን እንዲይዝ በማስታወስ አካልበው እንደወሰዱት ያስረዳል፡፡ ‹‹ከሁሉ በላይ በልጆቼ ፊት ይህ መደረጉ ያሳዝነኛል፡፡ በአንድ መጥሪያ ና ቢሉኝ ካልፈለጉም በአንድ የስልክ ጥሪ ቢጠሩኝ የፈለጉበት ቦታ መገኘት የምችል ሰው  ነበርኩ፤›› ሲል ስሜቱን ይገልጻል፡፡ ተደናግጠው ከእንቅልፍ የተነሱት ልጆቹ እሱ ሲወሰድ እያለቀሱ እንደነበር በመጥቀስ፣ ወደ መኪና ሲያስገቡትም በመስኮት እየተመለከቱ ሲያለቅሱ መመልከቱን ነው የተናገረው፡፡ በቀጥታ ሜክሲኮ የሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ማቆያ እንደወሰዱት የተናገረው ጋዜጠኛ ፋኑኤል፣ በመጨረሻ ግን በስም ማጥፋት ወንጀል መከሰሱን እንደነገሩት ይገልጻል፡፡ ‹‹ታዘን ነው፣ እኛ የምናውቀው የለም፣ ወንጀሉ ከባድ ነው እያሉ ሲመልሱልኝ ቆይተው በመጨረሻ ግን የአንድ ግለሰብ ስም ጠርተው ስሜን አጥፍቷል የሚል ክስ እንደመሠረቱብኝ ነገሩኝ፡፡ አሁን በምሠራበት ፈንታሌ ሚዲያ በተባለ የራሴ የዩቲዩብ ሚዲያ ከአንድ ዓመት ከሁለት ወራት በፊት በተላለፈ ዝግጅት የተነሳ በስም ማጥፋት መከሰሴንም ነው የነገሩኝ፤›› ሲልም ያስረዳል፡፡ የፕሬስ ነፃነትና አደገኛ አዝማሚያዎች | Ethiopian Reporter | ሪፖርተር ጉዳዩ በአዲስ አበባ ፖሊስ ለምን አይታይም ብሎ መጠየቁን ጋዜጠኛው ይናገራል፡፡ እንዲሁም ዋስትና ከማያስከለክሉ ከሁለት እስከ ስድስት ወር ከሚያስቀጡ ቀለል
Posted in News

አምነስቲ መንግሥት በሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶች ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ፍላጎት የለውም አለ

በኢትዮጵያ ከፍርድ ቤት ትዕዛዝና ከሕግ ውጪ የሚፈጸሙ ግድያዎችን መንግሥት እንደሚክድ፣ በሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶች ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ያለው ፍላጎት ዝቅተኛ ነው ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ፡፡ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የአገሮችን የሰብዓዊ መብት ቁመና በተመለከተ ከቀናት በፊት ይፋ ባደረገው ሪፖርት፣ ኢትዮጵያን በትጥቅ የታገዘ ግጭት ከሚካሄድባቸውና በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሰዎች ሕይወት ከተቃወሰባቸው ኢራቅ፣ ሱዳን፣ ምያንማር፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶሪያና ዩክሬን የመሳሰሉ አገሮች ተርታ መድቧታል፡፡ አምነስቲ ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው ባለ410 ገጽ ሪፖርት፣ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና መንግሥታቸው፣ በአማራ ክልል በመከላከያ ሠራዊት እየተፈጸሙ ያሉ ከሕግና ከፍርድ ቤት ውጪ የሚፈጸሙ ግድያዎችን እየካዱ ነው ብሏል፡፡ ፍትሕ ለማስፈን ተፈጸሙ የሚባሉ ወንጀሎችን ከመካድ ባለፈ መንግሥት ትርጉም ያለው ዕርምጃ አለመውሰዱን አስታውቋል፡፡ የመንግሥት ባለሥልጣነት ወንጀል የፈጸሙ አካላት በሕግ መሠረት ተጠያቂ እንዲሆኑ ለማድረግ ምንም ዓይነት ዕርምጃ እንደማይወስዱ፣ ተጎጂዎች እውነትና ፍትሕ የማግኘት መብታቸውን መነፈጋቸውን ገልጿል፡፡ በሴቶችና በልጃገረዶች ላይ ከሚፈጸም ፆታዊ ጥቃት በተጨማሪ፣ ከግጭት ጋር የተገናኙ ፆታዊ ጥቃቶች እየጨመሩ መሆናቸውን የገለጸው ሪፖርቱ፣ በጅምላ የማሰር ድርጊት መኖሩን፣ ነገር ግን የመንግሥት አካላት በቁጥጥር ሥር የዋሉ ዜጎችን በ48 ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ የሚደነግገውን የኢትዮጵያን ሕግ መፈጸም እንደማይችሉ አብራርቷል፡፡ በአማራ ክልል ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶችና የሰብዓዊ አገልግሎቶች ሕጎች እየተጣሱ መሆናቸውንም ድርጅቱ ገልጿል፡፡ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ከሌሎች ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ጋር ለመገናኘት ወደ ውጭ ከሄዱ በኋላ ሲመለሱ ማስፈራሪያና ዛቻ ይገጥማቸዋል ብሏል፡፡ የመብት ተሟጋቾ በተጓዙባቸው አገሮች የሚገኙ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትና ዲፕሎማቶች ዛቻና
Posted in News

ክልል ጠቋሚ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች በአዲስ ሊተኩ መሆኑ ተጠቆመ

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሥርዓቱን ለመቀየር ጥናት እያካሄድኩ ነው ብሏል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ክልል ጠቋሚ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎችን በአገራዊ (ኢት – ET) ለመተካት ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ታወቀ። ይህ የተገለጸው ሚኒስቴሩ ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም. የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች ከተጠሪ ተቋማት አመራርና ሠራተኞች ጋር፣ “የመሀሉ ዘመን” በሚል ርዕስ በተዘጋጀ አገራዊ ሰነድ ላይ ውይይት ሲደረግ ነው። የሪፖርተር ምንጮች በውይይቱ ወቅት የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች ክልል ጠቋሚ የሆኑ የተሽከርካሪ ሰሌዳዎች ሊቀየሩ መሆናቸውን፣ አገራዊ በሆነ ወጥ መለያ እንደሚተኩ መግለጻቸውን ጠቁመዋል። የሰሌዳ አሰጣጥ ሥርዓቱን መቀየር አስፈላጊ ያደረገውም፣ የመጡበትን ክልል የሚጠቁም ሰሌዳ ያላቸው ተሽከርካሪዎች፣ ለሽብርና ለወገንተናዊ አሠራር ተጋላጭ እያደረገ መሆኑን በመሆኑ እንደሆነ በውይይቱ ላይ ገልጸዋል። ከፍተኛ አመራሮቹ ክልሎች በራሳቸው መጠሪያ ሰሌዳ መሰየም መብታቸው መሆኑን ገልጸው፣ ይሁንና ይህንን እንደ መብት ማረጋገጫ ማሳያ አድርጎ ከመውሰድ ይልቅ፣ ጥቅምና ጉዳቱን ማመዛዘን እንደሚያስፈልግ ማብራራታቸውን ጠቅሰዋል። ጉዳዮን በተመለከተ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዋና ኃላፊ አቶ አብዲሳ ያደታ፣ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ባይጀመርም፣ የሰሌዳ አሰጣጥ ሥርዓቱን መቀየር በተመለከተ ጥናት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፣ የጥናቱን ዝርዝር የትኩረት አቅጣጫዎችን ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል። ‹‹በጥናት ሒደት ላይ ነው ያለነው፣ ጉዳዩን በተመለከተ በሕግ ኃላፊነት የተሰጠው ለሚኒስቴሩ ስለሆነ፣ የሰሌዳ አሰጣጥ ሥርዓታችንን ፈትሸን ጊዜው በሚፈልገው ደረጃ ጥቅም ላይ ለማዋል መሥሪያ ቤቱ ጥናት እያካሄደ ነው፤›› ብለዋል። በሌላ በኩል ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በተደረገው ውይይት የተገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ደኤታ አቶ ዴንጌ ቦሩ በበኩላቸው፣
Posted in News

በኢትዮጵያ ሺሻን በግል መጠቀምን የሚከለክል ህግ የለም፣ ለንግድ አላማ ማስጠቀም ግን ህጉ ይከለክላል

ሺሻ (ሁካ)ማጨስ በህግ ያስቀጣ ይሆን? ⚫ “በኢትዮጵያ ሺሻን በግል መጠቀምን የሚከለክል ህግ የለም፣ ለንግድ አላማ ማስጠቀም ግን ህጉ ይከለክላል ” የህግ ባለሙያ በኢትዮጵያ ምግብና የመድኃኒት ባለስልጣን አስተዳደር የወጣው አዋጅ ቁጥር 1112/2011ዓ.ም #ሺሻን በግል ማጨስ ወይም መጠቀምን #አይከለክልም። ሆኖም የኢትዮጵያ ምግብና የመድኃኒት ባለስልጣን አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1112/2011 በወጣው የሺሻ ምርት ማስመጣት፣ ማጨስና መጠቀም ከ3 ወር እስከ 3 አመት ቅጣት እንደሚጣልበት ይደነግጋል። አዋጁ ከወጣ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል። የህግ ባለሙያው ሳሙኤል ግርማ በምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2011 ዓ.ም የፀደቀው አዋጅ ቁጥር 1112 ሺሻን ማስመጣት፣ ማስጠቀም፣ ለንግድ ስራ ማዋል እና ለ3ኛ ወገን አሳልፎ መስጠት ብቻ በህግ እንደሚያስጠይቅ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቃለመጠይቅ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ” በግል መጠቀምን የሚከለክል ህግ አለመውጣቱ በሀገር ኢኮኖሚ እና በማህበረሰቡ ጤና ላይ ትልቅ ተፅዖኖ እየፈጠረ ነው” የሚል ሀሳብ ያነሳሉ። አክለውም ፥ ” ብዙ ሰዎች ሺሻ መጠቀምን የሚከለክል ህግ የለንም ይላሉ ነገር ግን በግል መጠቀምን አይከልክል እንጅ ሁለት ሶስት ሆኖ በመኖሪያ ቤት ውስጥ እና በንግድ ቤት ማጨስ አይቻልም። ሁለት እና ከዚያ በላይ ሆኖ ሲጠቀም የተገኘ ግን በህጉ ያስጠይቀዋል ” ብለዋል። የቅጣት እርከኑ በምንድን ነው የሚለያየው? የህግ ባለሙያው ሳሙኤል ” የወንጀል ቅጣት ሥነ-ስርዓት የራሱ የሆነ መጥሪያ ፍርድ ቤት ያወጣው እርከኖች አሉ። ቅጣት ማቅለያ ተብሎ የሚያዝላቸው ቤተሰብ አስተዳዳሪ እና ጥፋቱን ያመነ ከሆነ ዝቅተኛ ቅጣት ነው የሚጣልበት ” ብለዋል። አያይዘውም ፥ ወንጀሉን
Posted in News

ወጣቱ የት ገባ? ከሚሰራበት የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ባልታወቁ ሰዎች ታግቶ የተወሰደው ወጣት ጉዳይ

ወጣቱ የት ገባ? ከሚሰራበት የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ባልታወቁ ሰዎች ታግቶ የተወሰደው ወጣት ጉዳይ (መሠረት ሚድያ)- ወጣት አማኑኤል የማነብርሃን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ልደታ ቅርንጫፍን በምክትል ስራ አስኪያጅነት ያገለግል ነበር። https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/6b3?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
Posted in News

ጠቅላዩ ያስጠነቀቋቸው የአብንና ኢዜማ መሪዎች …… በጉጉት የሚጠበቀው የፋኖ ጉባዔ

Posted in News

ፋኖ አንድነቱን ሊያበስር እየተጠበቀ ነው! ፋኖ ወታደራዊ ማሰልጠኛውን ተቆጣጥሯል!

Posted in News

ተጠባቂው ብስራት! የፋኖ አንድነት!

Posted in News

“ህወሓት ጦርነት ሊጀመር ነው” አምበሳደሩ/ የቀጠለው የፋኖና የአገዛዙ ከባድ ውጊያ/ የብልፅግናው ሹም በኤርትራ የትጥቅ ትግል ጀመሩ

Posted in News

የወልቃይት ጠገዴ አማራ ድጋሚ ወረራ ያሰጋው ይሆን? …. እባብ ለመደ ተብሎ በኪስ ይያዛል? …. ሕወሓት እና አማራ፣ ትግራይ እና ሕወሓት!

Posted in News

“አስደናቂ ወታደራዊ ድል ተቀዳጅተናል!” ፋኖበወቅታዊ ጉዳይ የተላላፈው የአቋም መግለጫ!ስለፋኖ አንድነት አዳዲስ መረጃዎችና ዘገባዎች!

Posted in News

እንኳን ለሚያዚያ 27 የድል ቀን አደረሳችሁ ! አሁን በነፃነት ለቆምንባት ምድር አያት ቅድመ አያቶቻችን መስእዋትነት ከፍለውበታል።

አሁን በነፃነት ለቆምንባት ምድር አያት ቅድመ አያቶቻችን መስእዋትነት ከፍለውበታል። ክብር ይህን ድል በደም አጥንታቸው ላመጡልን ጀግኖች አያት ቅድመ አያቶቻችን ይሁን ! እንኳን ለሚያዚያ 27 የድል ቀን አደረሳችሁ ። ==== ደጃዝማች ዑመር ሰመተር ! ! ….. የኦጋዴኑ የበረሀው መብረቅ ===== ተገዳይ እወልወል እጠረፉ ዳር፤ የመትረየሱ ሼክ የለበን መምህር ሞት ጠራህ አንተንም ዑመር ስመጥር!!! — ጣልያንን ከአፈር የደባለቀ ጀግና ! ደጃዝማች ዑመር ሰመተር በኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክ ለአገራቸው ነጻነት ሲሉ በፍጹም አገራዊ ፍቅር መተኪያ የሌለው ህይወታቸውን የከፈሉ አካላቸውን ያጎደሉ በርካቶች ናቸው፡፡ የቀደሙትን የእነዚሕን አባቶች ውለታ አቅም በፈቀደ በምናስታውስበት በዚ ገጽ ዛሬ ዕድል ቀናንና ታለቁን ኢትዮጵያዊ ጀግና ደጃዝማች ዑመር ሰመትረን ልንዘክር ተገናኘን….. እነሆ ሰውየው!!! አዲስ አበባ ከተማ ከሚገኘው ከታላቁ አንዋር መስኪድ አጠገብ ‘’ዑመር ሰመትረ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት’’ የሚል መጠሪያ የተሰጠውን ት/ቤት ( አሁን ፈርሶ ፓርኪንግ ሆኗል ) ሲያስቡ ከታሪኩ በስተጀርባ መታሰቢያ የቆመላቸው እኝህ ሰው ማን ናቸው ብለው መጠየቅዎ ወይም በሌላ ሰው መጠየቅዎ አይቀርም የዛሬው ባለታሪካችን የተወለዱት በኦጋዴን አካባቢ ካልካዩ በተባለ ሥፍራ ሲሆን ዓመቱም 1871 ዓ.ም ነው፡፡ በልጅነታቸው የተለያዩ ሀይማኖታዊ ትምህርቶችን ባህላዊ ሥርዓቶችን እየተማሩ ያደጉት እኝህ ሰው የአስተዳደር ሰው ለመሆን በነበራቸው ፍላጎት የመሪነት ክህሎታቸውን ሊያሳኩ የሚችሉ የተለያዩ ጥረቶችን እየመኮሩና ከአካባቢው የጎሳ መሪዎች አሰራርና ተሞክሮን እየቀሰሙ ማደጋቸው ይነገራል፡፡ ለአካለ መጠን ሲደርሱም በአካባቢ አስተዳደር ስራ በመሰማራት አገራቸውን ያገለገሉ ሲሆን በቅድሚያ በባላባትነት ማዕረግ በመቀጠልም የሱልጣን ዓሊ የሱፍ
Posted in News

ፋኖ በባሕር ዳር ታሪክ ሰራ !

Posted in News

ሞትና ሰርግ በአዲስ አበባ

Posted in News

ለታላቅ ውጊያ እየተዘጋጀን ነው ( ጀኔራሉ ) …. የፋኖ ውጊያና የኮሎኔል ክህደት

Posted in News

አዲስ አበባ ልዩ ጥበቃ ታዘዘ!

Posted in News

ጄኔራሉ ስለቀጣዩ ጦርነትና ፋኖ በከተሞች

Posted in News

አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ጥቃት ተፈፀመባቸው

አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ጥቃት ተፈፀመባቸው (መሠረት ሚድያ)- ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እስረኞች ወደ ማደሪያቸው ከገቡ በኋላ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ላይ ቀይ ቦኔት የጫኑ የፌደራል ፖሊሶች ቁልፍ ሰብረው ገብተው አቶ ክርስቲያን ታደለን እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌውን ከእስር ቤታቸው እንዳስወጧቸው እና እስከ ሌሊቱ 7:00 ሰዓት ድረስ ሜዳ ላይ አስተኝተው እንዳሳደሯቸው ምንጮቻችን ለመሠረት ሚዲያ ገልፀዋል። በተመሳሳይ ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ፣ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፣ ፕሮፌሰር መዓረጉ ቢያበይን እና ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው ይሄው ድርጊት የተፈፀመባቸው መሆኑን አርብ ሚያዚያ 24 ቀን 2017 ዓ/ም ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርበዋል። “ቀይ ቦኔት የጫኑ የፌደራል ፖሊሶች ምሽት 12:00 ሰዓት በሩን በኃይል ከፍተው ከገቡ በኋላ ሁላችንንም እጃችንን ወደ ላይ እንድናደርግ አዘው ሜዳ ላይ በሰልፍ አቁመውን በመሳሪያ ሲያስፈራሩን ነው ያደሩት” ሲሉ ነው ለፍርድ ቤቱ የገለፁት። “ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ድብደባ የፈፀሙብን የመንግስት ሹማምንት ከሁለት ዓመት በኋላ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤትን አጥር ጥሰው፣ የተኛንበትን ቤት በር በኃይል ሰብረው እስከ ሌሊት 7:00 ሰዓት ድረስ ሜዳ ላይ አሰልፈውን አሳድረውናል። ሕይዎታችን አደጋ ላይ መሆኑን ሕዝባችን እንዲያውቅልን” ሲሉ አሳስበዋል። አቶ ዮሐንስ ቧያሌው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ከአንድ አመት በፊት በአዋሽ አርባ ወታደራዊ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት የከፋ የጤና መታወክ ገጥሟቸው እንደ ነበር ይታወቃል። በመሆኑም ጤናቸው ገና ሳያገግም በድጋሜ ሜዳ ላይ ተሰልፈው እንዲያድሩ መደረጉ ለባሰ የጤና
Posted in News

ህፃናት በግዳጅ ከደርግ በከፋ አፈሳ እየተወሰዱ ነው።

ጌታቸው ሽፈራው ፡ በደርግ ወቅት ወጣቶች በግድ እየታፈኑ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ይወሰዱ ነበር። በዚህ መጠን ህፃናትን ግን አልነበረም። የዞን ኮሙኒኬሽን ገፅ ሳይቀር በይፋ የሚለጥፈውን ተመልከቱ። ህፃናት በግዳጅ ከደርግ በከፋ አፈሳ እየተወሰዱ ነው። እንዲህ ነው የሚያደርጉት! 1) በችግር ጎዳና የወጡ ህፃናትን ይይዟቸዋል። አንድ ሰሞን ትምህርት ቤት ወይንም ሌላ ቦታ ያሰነብቷቸዋል። 2) የቆሎ ተማሪዎችን በቡድንም ሆነ በተናጠል ሲሄዱ ይይዟቸዋል። 3) እረኞችን፣ ተማሪዎችን ይይዟቸዋል። 4) በቤተሰቦቻቸው ችግር ምክንያት ገና በለጋ እድሜያቸው በመኪና ረዳትነትም በሌላም ስራ የተሰማሩትን ይይዟቸዋል። በሌላም ሁኔታ ያሉትን እድሜያቸው ለውትድርና ያልደረሱትን በግድ አፍነው አንድ ማዕከል ያሰነብቷቸዋል። ከዛም ኮታዬን አሟልቻለሁ ብለው ያስረክባሉ። ይህ ከደርግ የባሰ ህፃናትን ለውትድርና መመልመል ስልጣናቸውን የሚታደግ መስሏቸዋል። ህዝብ አገር ለመከላከል ሲሆን ልጁን መርቆ ይሰጣል። ህፃን ልጁን ወደ ግድያ ሜዳ የሚወስደውን እንደሚታገለው ግን አላሰቡበትም። አሁን ህፃን ልጁ እንደሞተ ነው የሚቆጥረው። ደመኛው ደግሞ አገዛዙ። ይህ ልጁ የተወሰደበት አባት ብቻ ምሬትና እርምጃ አይሆንም። የሞራል ልኬትን፣ የልጅን ሁኔታ የሚያውቀው ሁሉ የሚጋራው ስሜት ይሆናል። ከብቶቹን በሰላም አውሎ ይመጣል ብሎ የሚጠብቀውን ልጁን፣ ተምሮ ይመለሳል ብሎ የሚጠብቀውን ልጁን፣ ሱቅ ተልኮ ይመለሳል የተባለውን ልጁን፣ ከተማ ሄዶ ይመለሳል ብሎ የሚናፍቀውን ልጁን…በዚህ መንገድ በጥጋብ ተነጥቆ “ይሁና” ብሎ የሚተው አባትም ሆነ ህዝብ የሚኖር ይመስላቸዋል። ይህ የአገዛዙ አረመኔነት የነበሩትን እሳቶች ያቀጣጠላል እንጅ እድሜያቸውን የሚያራዝም ከመሰላቸው የምርም ስተዋል ማለት ነው።
Posted in News

ዘመቻ አንድነት 45ኛ ቀን…. የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች መግለጫ ….. ” አብይ እና በለጠ ሞላ ወንጀላቸው እኩል ነው”

Posted in News

አዲስ አበባ ውጥረት ነግሷል…. ጥሶ የገባው ጦርና የቆሰሉት ባለስልጣን!

Posted in News

የቀጠለው ውጊያና የቦሌ ኤርፖርቱ ውጥረት! እነ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ሃገር እንዲገቡ ተፈቀደ!

Posted in News

ደርግና ብልፅግና ምንና ምን? … በመከላከያ ሰራዊት ታፈነ ልጇን ለማስለቀቅ 70ሺ ብር.. የዘመናችን መላኩ ተፈራዎች!

Posted in News

ዋና አዛዡ ተመታ…..ሆስፒታል ገብቷል … ወጣቶችን ሲያፍን የነበረው የጸጥታ አካል ላይ እርምጃ ተወሰደ

ዋና አዛዡ ተመታ…..ሆስፒታል ገብቷል … ወጣቶችን ሲያፍን የነበረው የጸጥታ አካል ላይ እርምጃ ተወሰደ
Posted in News

ስለወልቃይቱ ውጊያ እነ ኮ/ል ደመቀና ፋኖ!ተከዜን ተሻግሯል!

Posted in News

ስለወልቃይቱ ውጊያ እነ ኮ/ል ደመቀና ፋኖ! ተከዜን ተሻግሯል!

Posted in News

በወልቃይት የተጀመረው ጦርነት! የህወሃቶችና የዐቢይ ቁማር ተጀመረ!

Posted in News

ቁጥሩ ያሽቆለቆለው የዋሊያ አይቤክስ ጉዳይ እያሳሰበ ነው

በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የመጥፋት አደጋ በተጋረጠበት ብርቅዬው ዋሊያ አይቤክስ ላይ በግንቦት ወር ቆጠራ እንደሚደረግ የፓርኩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ማሩ ቢያድግልኝ ለዋዜማ ተናግረዋል። የዋሊያ ቁጥር መመናመን የጀመረው፣ ከፓርኩ ገቢ የሚያገኙ የፓርኩ አጋዥ ጠባቂ ሚሊሻዊች በኮሮና ወረርሽኝ ወቅት ሥራ ማቆማቸውን ተከትሎ ዋሊያ ለአደን በመጋለጡ እንደነበር የጠቀሱት ማሩ፣ የሰሜኑ ጦርነትም ለቁጥሩ መቀነስ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል። በ2015 እና በ2016 ዓ፣ም በተደረገ ቆጠራ፣ የዋሊያ ቁጥር ከ865 ወደ 306 ወርዶ መገኘቱን ዋዜማ ተረድታለች። በእርጥብና በደረቅ ወቅት በሚል በሁለት ዙር ቆጠራ የሚካሄድ ሲኾን፣ የግንቦቱ የእርጥብ ወቅት ቆጠራ ነው። በዓመት በአማካይ 30 ሺሕ የነበረው የፓርኩ ጎብኝዎች ቁጥር፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ወደ 3 ሺሕ ማሽቆልቆሉን ዋዜማ ተረድታለች።
Posted in News

የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ የታገቱ ኢትዮጵያውያንን አስለቀቀ

የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ፣ 17 ታዳጊዎችን ጨምሮ 44 ሕጋዊ ሰነድ የሌላቸው ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን ጁሃንስበርግ ከተማ ውስጥ ከፍቃዳቸው ውጭ ከተያዙበት ቤት ዛሬ መታደጉን የአገሪቱ ጋዜጦች ዘግበዋል። ባለፈው ወር፣ በሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ባንድ ቤት ውስጥ ተደብቀው የነበሩና ሕጻናትን ጨምሮ ከአሰሳ ያመለጡ 32 ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን ፖሊስ እያፈላለገ መኾኑን ገልጦ ነበር። ፖሊስ ዛሬ የታደጋቸው ፍልሰተኞች ጉዳይ፣ በመጋቢት ከተሠወሩት ጋር ይገናኝ ወይም አይገናኝ ለጊዜው አልተረጋገጠም ተብሏል። ባለፈው ጥር ወር በተመሳሳይ፣ ፖሊስ 26 ሕጋዊ ሰነድ ያልያዙ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች እርቃናቸውን ቤት ተዘግቶባቸው ማግኘቱ አይዘነጋም።
Posted in News

የኢትዮጵያ ፖለቲከኞችና ቡድኖች አካሄድ፣ “ከፍተኛ ፖለቲካዊ ስድብ ነው” ( የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ )

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገብረመስቀል፣ አንዳንድ የኢትዮጵያ ፖለቲከኞችና የፖለቲካ ቡድኖች የሚያራምዱት የሉዓላዊ ጎረቤት አገርን ግዛት የመቆጣጠር ፍላጎት፣ “ሊታሰብ ወይም ሊታለፍ የማይችል ቀይ መስመር ነው” በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ጽፈዋል። የኢትዮጵያ ፖለቲከኞችና የፖለቲካ ቡድኖች የጎረቤት አገርን ግዛት የመቆጣጠር አጀንዳቸውን የሚያንጸባርቁት፣ ሲያሻቸው “በወታደራዊ ኃይል በማስፈራራት” እና ሌላ ጊዜ ደሞ “ታሪካዊ” ወይም “ሕጋዊ” የሚሏቸውን ምክንያቶች በመደርደር ነው በማለት የማነ ተችተዋል። የማነ አያይዘውም፣ ይኼ ዓይነቱ የኢትዮጵያ ፖለቲከኞችና ቡድኖች አካሄድ፣ “ከፍተኛ ፖለቲካዊ ስድብ ነው” በማለት ወቅሰዋል።
Posted in News

በምሽግ ውስጥ የተቀረፀ … ለአማራ ሕዝብ የተከፈለ እዳ …. ሁለት ዶክተሮች ቁስለኛውን ይዘው….

Posted in News

አፈትላኪ የልዩ አፕሬሽን መረጃዎች ከጄኔራሉ ማስታወሻ

Posted in News

የታቀደው “ዘመቻ የፋኖ አመራሮችን መግደል”

Posted in News

ዘመቻ አንድነት 43ኛ ቀን …. የህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች መግለጫ ከግንባር

Posted in News

የወሎና ጎንደር ከባድ ተጋድሎ! እየመጣ ያለው አዲስ ጦርነት! የዐቢይና የህወሃቶች ቀይ መስመር!

Posted in News

ግዙፉ የኮማንዶ ሃይልና የፋኖ ተጋድሎ!ባለልስጣኖቹ ወደ ወታደራዊ ካምፕ ሊጋዙ ነው!

Posted in News

ወጣቶች ድንገት ከታፈስን በሚል ስጋት ለጉቦ ገንዘብ ይዘው ይንቀሳቀሳሉ

በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ፣ ወጣቶች በጸጥታ ኃይሎች ድንገት ከታፈስን በሚል ስጋት ለጉቦ ገንዘብ ይዘው እንደሚንቀሳቀሱ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። ጸጥታ ኃይሎች ምን ያህል ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋል እንዳለባቸው ከወረዳ አመራሮች ተተምኖ እንደሚሠጣቸው ምንጮች መግለጣቸውን ዘገባው አመልክቷል። ኢሰመኮ ኅዳር ላይ ባወጣው መግለጫ፣ የክልሉ ጸጥታ ኃይሎች ከመከላከያ ሚንስቴር የምልመላ መስፈርቶች ውጪ በግዳጅ ለተያዙ ሰዎች ማስለቀቂያ ቤተሰቦቻቸው ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚከፍሉ በምርመራ ማረጋገጡን አስታውቆ ነበር።
Posted in News

በኢንዱስትሪ ፖርኮች ውስጥ የሚሰሩ ሴት ሰራተኞች ደመወዛቸው አነስተኛ በመሆኑ ወደ ወሲብ ንግድ ተሰማርተዋል

” በኢንዱስትሪ ፖርኮች ውስጥ የሚሰሩ ሴት ሰራተኞች ደመወዛቸው አነስተኛ በመሆኑ ወደ ወሲብ ንግድ ተሰማርተዋል ” የጨርቃጨርቅ ፌዴሬሽን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚሰሩ ሴት ሰራተኞች የሚከፈላቸው ደመወዝ አነስተኛ በመሆኑ ኑሮን ለማሸነፍ አስቸጋሪ ስለሆነባቸው ወደ ወሲብ ንግድ እየተሰማሩ መሆኑ የጨርቃጨርቅ ፌዴሬሽን ገልጿል። የጨርቃ ጨርቅ ፌዴሬሽን ተወካይ የሆኑት አቶ ተስፋዬ አብዲሳ ሰራተኞቹ ከወሲብ ንግድ በተጨማሪ ትርፍራፊ ምግቦችን ከየሆቴሉ በመሰብብ ወደ ቤታቸው የሚወስዱ መኖራቸውን ተናግረዋል። አምራች ስራተኛ፣ ምቹ ስራ ለወጣቶች እና ሴቶች በጨርቃ ጨርቅ አምራች ኢንዱስትሪዎች ውስጥ መፍጠር በሚል ርዕስ የፖሊሲ አቅጣጫ ተቋማዊ ጥናት ለማድረግ የማህበራት ጥናት መድረክ (Forum For Social Studies) ውይይት ተካሂዷል። ውይይቱ ላይ የተገኙት የጨርቃ ጨርቅ ፌዴሬሽን ተወካይ አቶ ተስፋዬ አብዲሳ ” በሰራተኞች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥናት አረጋግጠናል ” ብለዋል። በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ስራተኞች ገቢያቸው እንዲሻሻል ለማድረግ  ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ማፅደቅ አንዱ መፍትሄ ነው ያሉት ተወካዩ ‘’በተለይ ለሴቶች ክፍያው ዝቅተኛ ስለሆነ በወሲብ ንግድ ላይ የተሰማሩ መኖራቸውን በጥናት አረጋግጠናል ነው ያሉት። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ አሰሪዎች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን ፈቃደኞች እንዲሆኑ ቢያረጋግጢም በመንግስት በኩል ግን እግሩን የሚጎትትበት ምክንያት ግልፅ እንዳልሆነ አስረድተዋል። በውይይቱ ላይ የተሳተፉት አካላት በኢንዲስትሪ ፓርኮች በጨርቃ ጨርቅ እና ጋርመንት ላይ ተሰማርተው የሚሰሩ ሴት ሰራተኞች የሚከፈላቸው ክፍያ ዝቅተኛ በመሆኑ ትዳር የሚመሰርቱት ስለፈለጉ ሳይሆን ወጪ ለመጋራት እንደሆነ እና በትዳር ሕይወታቸው ላይ እንኳን የመወሰን መብት እንዳይኖራቸው አድርጓል ነው ያሉት። ተወካዩ አቶ
Posted in News

አቡነ ገብርኤል በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ ተወሰነ

አቡነ ገብርኤል ያስተማሩት ሕጸጽ ተጣርቶ እስኪወሰን ድረስ “በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ” ተወሰነ+++++++++++++++++++++++++++++++ ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል። ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል። በዚህም መሰረት ቋሚ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማኅበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማኅበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ
Posted in News

ወንድማማች ታጋዮችን ለማጋደል የሚያሴሩ ተነቅቶብቸዋል” … የጎጃሙ ከፍተኛ አመራር ነጭ ነጯን ተናገረ!

Posted in News

የፋኖ ትግል የገጠሙት ፈተናዎች፥ የአብይ አሀመድ መርዛማ ፕሮጀክቶች

Posted in News

ኢትዮጵያ ውስጥ በድብቅ እየተተከለ ያለው ድርጅት በሌሎች ሀገራት የተከለከለ

Posted in News

ለሰሜን ምስራቅ እና ለደቡብ ዕዞች አዲስ ስምሪት!

Posted in News

ጥብቅ መረጃ እና የግንባር ዜናዎች

Posted in News

ስዩም ተሾመ የተባለውን ግለሰብ የፌደራል ፖሊስ ማቅረብ ካልቻለ እና ስማችንን ማጉደፍ የሚቀጥል ከሆነ ስራችንን ልናቆም እንገደዳለን”- የከፍተኛ የፍርድ ቤት ዳኞች

ፌደራል ፖሊስ ለሶስተኛ ግዜ አክቲቪስቱን ማግኘት አልቻልኩም ብሏል፣ ዳኞች በበከላቸው ለፍትህ ስርዐቱ ያለውን ንቀት ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል  (መሠረት ሚድያ)- ስዩም ተሾመ የተባለው አክቲቪስት የአቶ ዮሐንስ ቧያሌው እና የአቶ ክርስቲያን ታደለን የክስ ሂደት አስመልክቶ በችሎቱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እየፈጠረ ነው በሚል ፍርድ ቤቱ ግለሰቡን ሥነ-ሥርዓት እንዲያሲዘው መጠየቃቸውን አስመልክቶ በቅርቡ መዘገባችን ይታወሳል። ጉዳዩን እየተመለከተው የሚገኘው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የሽብር ወንጀል ችሎት አክቲቪስቱ ቀርቦ መልስ እንዲሰጥ ለፌደራል ፖሊስ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። ይሁን እንጂ ስዩም ተሾመ የተባለውን ግለሰብ በዛሬው እለትም ለሦስተኛ ጊዜ የፌደራል ፖሊስ ግለሰቡን አላገኘሁትም በሚል ምላሽ ሰጥቷል። የችሎቱ ዳኞች በበኩላቸው “የፌደራል ፖሊስ ግለሰቡን ለደህንነቱ ሲባል እጀባ እያደረገለት እንደሆነ ይታወቃል።ነገር ግን ፍርድ ቤቱ እንዲያቀርበው ትዕዛዝ  ሲደርሰው አላገኘሁትም የሚል ምላሽ መስጠቱ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ያለውን ንቀት የሚያሳይ ነው” ብለዋል። አክለውም “ግለሰቡ መሀል አዲስ አበባ ተቀምጦ የፍርድ ቤቶችን ዳኞች ስም ሲያጎድፍ እየዋለ ነው። ከችሎቱ አቅም በላይ ሆኗል። ስለዚህ የፍርድ ቤቱ የበላይ አመራሮች  ጉዳዩን ለማስቆም አለመሞከራቸው ያሳዝናል” ብለው በዛሬው ችሎት ላይ እንደተናገሩ የመሠረት ሚድያ ምንጮች ጠቁመዋል። “አሁንም ግለሰቡ በፖሊስ ተይዞ ካልቀረበ እና የዳኞችን ስም የሚያጎድፍ ከሆነ ስራችንን ለማቆም እንገደዳለን” ሲሉ ተናግረዋል። አቤቱታውን ያቀረቡት አቶ ዮሐንስ ቧያሌው በበኩላቸው “የዓቃቢ ሕግ ምስክሮች ለደኅንነታቸው ሲባል የስም ዝርዝራቸው እንዳይደርሰን ተከልክለን እያለ በዓቃቢ ሕግ አቶ ኢዮሲያድ አበጀ በኩል ለአቶ ስዩም ተሾመ ተሰጥቶት በማሕበራዊ ሚዲያ ማን እንደ ሚመሰክርብን ነግሮናል።
Posted in News

በኦሮሚያ ወደ አዳማ/ናዝሬት የሚጓዙ ተሳፋሪዎች ታገቱ

በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በአርሲ ስሬ ወረዳ ዛሬ ረፋዱ ላይ ታጣቂዎች አንድ ቅጥቅጥ አይሱዙ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ አስቁመው ከ50 በላይ ተሳፋሪዎችን አግተው መወሰዳቸውን ታውቋል። ታጣቂዎቹ እገታውን የፈጸሙት፣ ተሽከርካሪው ከአርሲ ስሬ ወረዳ ወደ አዳማ ከተማ በመጓዝ ላይ ሳለ እንደሆነ የአካባቢው የዓይን እማኞች ተናግረዋል። እገታው የተፈጸመበት ሥፍራ ከዚህ ቀደም በጸጥታ ኃይሎች ጥበቃ ይደረግለት እንደነበር የገለጹት ምንጮች፣ በዛሬው ዕለት ግን የጸጥታ ኃይሎች ከአካባቢው ተነስተው እንደነበር ገልጸዋል። ታጣቂዎች፣ በዞኑ በአቦምሳ ወረዳ ልዩ ስሙ ከሬቸር በተባለ ሥፍራ ባለፈው እሁድ በተመሳሳይ ወደ አዳማ/ናዝሬት ከተማ ሲጓዝ ከነበረ ተሽከርካሪ ላይ በርካታ ተሳፋሪዎች እንዳገቱም ምንጮች አስረድተዋል።
Posted in News

በኦሮሚያ ክልል የመንግሥት መዋቅር አመራሮች የመሠረታዊ ውትድርናና ፖለቲካ ሥልጠና ሊወስዱ ነው

በኦሮሚያ ክልል የወረዳና የቀበሌ የመንግሥት መዋቅር አመራሮች ከመጭው ሐሙስ ጀምሮ ለ40 ቀናት የመሠረታዊ ውትድርናና ፖለቲካ ሥልጠና ሊወስዱ እንደኾነ ዋዜማ ሠምታለች። ሥልጠናውን የሚወስዱት አመራሮች የወረዳና ቀበሌ ዋና አሥተዳዳሪዎችና የሠላምና ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊዎች መኾናቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ለ40 ቀናት ይቆያል የተባለው ሥልጠና የሚሠጠው፣ በአዋሽ ቢሾላ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ካምፕ ውስጥ መኾኑንም ምንጮች አስረድተዋል። የሥልጠናው ዓላማ በሁለቱ የመንግሥት መዋቅሮች ውስጥ የሚሠሩ አመራሮችን የመሠረታዊ ውትድርና ክህሎትና ፖለቲካዊ አቅም ማሳደግ እንደኾነ ዋዜማ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገረቻቸው ምንጮች ገልጸዋል።
Posted in News

አሜሪካ በየመን ቦምብ ጥቃት ኢትዮጵያዊ ገላለች ተባለ

አሜሪካ በየመን በአፍሪካዊያን ፍልሰተኞች ማዕከል ላይ በፈጸመችው የአየር ጥቃት በትንሹ 68 ሰዎች መገደላቸውን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች የሁቲዎችን ቴሌቪዥን ጠቅሰው ዘግበዋል። በጥቃቱ ሌሎች 47 ሰዎች መቁሰላቸውን የጠቀሱት ዘገባዎቹ፣ አንዱ ኢትዮጵያዊ እንደኾነ አመልክተዋል። ፔንታጎን ፍልሰተኞች የጥቃቱ ሰለባ በመኾናቸው ዙሪያ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ያለው ነገር የለም። በየመን ጊዜያዊ የፍልሰተኞች ማቆያ ማዕከላት ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ መሻገር የሚፈልጉ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ፍልሰተኞች ይገኛሉ።
Posted in News

በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ‘ትግራይ ሊብራል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ’ የሚባል አዲስ ፓርቲ ሊያቋቁም ነው

በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ‘ትግራይ ሊብራል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ’ የሚባል አዲስ ፓርቲ ሊያቋቁም ነው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ከህወሓት የተከፈለው ቡድን አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ለማቋቋም በሂደት ላይ መሆኑን ከአመራሮቹ መካከል አንዱ ለቢቢሲ ገለፁ። ይህ አዲስ በምዝገባ ሂደት ላይ የሚገኘው የፖለቲካ ፓርቲ በሊብራል ዴሞክራሲ ጽንሰ ሃሳብ የሚከተል መሆኑን የተናገሩት አመራሩ “ትግራይ ሊብራል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ” በማለት ለመጠራት መወሰኑን ተናግረዋል። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁት እኚህ የቀድሞ የህወሓት አመራር “ይህ ስም የፖለቲካ ፓርቲውን ለመመሥረት በእንቅስቃሴ ላይ ባሉ ሰዎች የተመረጠ እንጂ ከምርጫ ቦርድ እውቅና ስላላገኘ ጉባዔ ሲካሄድ ሊቀየር ወይንም ሊሻሻል ይችላል” ብለዋል። በሁለት ተከፍሎ እርስ በእርሱ ሲካሰስ የቆየው ህወሓት የኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው ቀነ ገደብ ጉባዔ ማካሄድ ባለመቻሉ ከፓርቲነት ሊሰረዝ እንደሚችል ቦርዱ ማስታወቁ ይታወሳል። የመሰረዝ አደጋ የገጠመው በደብረፂዮን (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ተደራድሮ የፕሪቶሪያ ስምምነትን እንደፈረመ ድርጅት እንደ አዲስ በቦርዱ መመዝገቡ ተገቢ አለመሆኑን ሲገልጽ ቆይቷል። የህወሓት መሰረዝ ስጋት የፈጠረባቸው በአቶ ጌታቸው የሚመራው የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ከሳምንታት በፊት ባወጡት መግለጫ በደብረፂዮን (ዶ/ር) ለሚመራው ቡድን በጋራ ጉባዔ ለማካሄድ ጥሪ አቅርበው የነበረ ቢሆንም በጎ ምላሽ አለማግኘታቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም ይላሉ የቢቢሲ ምንጭ “የህወሓት ሕጋዊነት ስለሚያበቃ የህወሓት የፖለቲካ ዓላማዎችን ለማሳካት የሚያስችለን አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ለመመሥረት ተገድደናል” ያሉ ሲሆን የፓርቲው ሕገ ደንብ እና ፕሮግራሞቻችን አርቅቀው መጨረሳቸውን ተናግረዋል። ምንጩ አክለውም የደጋፊዎቻቸውን ፊርማ በማሰባሰብ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ይኹን አንጂ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ
Posted in News

ብር ሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ዙሪያ ልዩ መረጃ

Posted in News

”የአብይ ብልጽግና ንቅናቄ”-አብን ፤ ‘ጦርነቱ ቶሎ ይጀመርልን’

Posted in News

በፋኖ ሀይሎች ከባድ ውጊያ የተዘጋው ቀጠና

Posted in News

የቀጠለው ውጊያ ! ብልጽግና ተከቧል!

Posted in News

ዘመቻ አንድነት 41ኛ ቀን | ፋኖ ታሪካዊ ቅርስ ዛሬ አስመልሷል

Posted in News

ሴቷ ፋኖ በምሽግ ውስጥ ሆና ያስተላለፈችው መልዕክት! “አንፈራም፣ አናፈገፍግም፣ አንሸነፍም”

Posted in News

የፋኖ ከባድ ውጊያና የአገዛዙ ወጣት አፈሳ፤ …. ወደ አማራ የገባው ሜካናይዝድ ጦር

Posted in News

የስለላ እና የመረጀ ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!

Posted in News

የጠረፉና የኮሪደሩ ልዩ ዘመቻ የውሎ መረጃዎች!ባለስልጣናት ተይዘው ተወሰዱ! 80 ምልምሎች ተያዙ!

Posted in News

81 ወታደሮች የአርበኛ ዘመነ ካሴን ጦር ተቀላቀሉ! ….. ግዳጅ ላይ የነበረው ጦር ፈራረሰ፤ ካምፑ ባዶውን ቀረ!

Posted in News

ለአማራ ክልል ዳኞች የተወሰነው የደመወዝ ጭማሪ በመዘግየቱ “ከፍተኛ ቅሬታ” ማስነሳቱ ተገለጸ

ለአማራ ክልል ዳኞች የተወሰነው የደመወዝ ጭማሪ በመዘግየቱ “ከፍተኛ ቅሬታ” ማስነሳቱ ተገለጸ የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር በክልሉ ለሚገኙ ዳኞች እና የጉባኤ ተሿሚዎች የደመወዝና የጥቅማ ጥቅም ጭማሪ ተፈጻሚ ሳይሆን በመዘግየቱ  “ከፍተኛ ቅሬታ” ማስነሳቱን ገለጸ። ለደመወዝ ጭማሪው የሚያስፈልገውን በጀት የአማራ ክልል መንግስት እንዲመድብ ለማድረግ፤ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት “የቅርብ ክትትል እና ጥረት” እያደረገ መሆኑን ማህበሩ አስታውቋል።  የዳኞች ማህበሩ ይህን ያስታወቀው ትላንት እሁድ ሚያዝያ 19፤ 2017 ለአባላቱ ባስተላለፈው መልዕክት ነው። ማህበሩ በዚሁ መልዕክቱ፤ ፍርድ ቤቶችን ከማጠናከር እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የጀመረውን የለውጥ ስራ የተሟላ ከማድረግ አኳያ የዳኞችን እና የጉባኤ ተሿሚዎችን ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም ማሻሻሉ “የማይተካ ሚና ያለው” “መሰረታዊ ነጥብ” እንደሆነ አስገንዝቧል። የዳኞች ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄን ለመመለስ፤ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኮሚቴ አዋቅሮ ጥናት ካደረገ በኋላ በክልሉ ዳኞች አስተዳደር ዐብይ ጉባኤ አማካኝነት ዝርዝር መመሪያ ማጽደቁን ማህበሩ አስታውሷል። ዐብይ ጉባኤው ካጸደቀው የደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም በተጨማሪ ሀገር አቀፍ የኑሮ ውድነት ማሻሻያ የደመወዝ ጭማሪ ለሁሉም ሰራተኛ የተደረገ መሆኑን በትላንቱ መልዕክቱ የጠቀሰው ማህበሩ፤ ሁለቱም “እስካሁን ተፈጻሚ ባለመሆናቸው” በዳኞች ዘንድ “ከፍተኛ ቅሬታ” እያስነሳ መሆኑን ገልጿል። 🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15741/
Posted in News

እነ እስክንድር ከብልፅግና ጋር በይፋ ሰለተሰለፉ ራሳችንን ወደ መከላከል ገብተናል ! …. (የፋኖ አደረጃጀቶች የቀጥታ መግለጫ )

Posted in News

ለአማራ ህልውና ከማን ጋር መስራት እንዳለብን እናውቃለን! …. ( አበበ ፈንታው ፡ የአማራ ፋኖ በወሎ ቤተ አምሓራ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ )

Posted in News

ጎንደር የምትሞሸረው ማን ሊያገባት ነው?

Posted in News

የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ዋና ጸሃፊ የአብይ አገዛዝ በአማራ ንፁሃን ላይ የሚፈፅመው የድሮን ጥቃት በማውገዝ እንዳሳሰባቸው ገለፁ

የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ዋና ጸሃፊ ቄስ ዶ/ር ጄሪ ፒሌይ፣ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸው እጅግ እንዳሳዘናቸው መግለጣቸውን ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ጥቃቱ እጅግ እንዳሳሰባቸው የጠቀሱት ዋና ጸሃፊው፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ንጹሃን በብዛት በሚኖሩባቸው አካባቢዎች የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶችን በእጅጉ ይኮንናል ማለታቸውን መግለጫው ጠቅሷል። ዋና ጸሃፊው፣ በግጭት ውስጥ ተዋጊ ያልኾኑ ሰዎችን ከጥቃት በማያስጠብቅና ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብት ሕግጋትን ባልተከተለ መልኩ የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች አሳሳቢ እንደኾኑ ተናግረዋል ተብሏል። አገር ዓቀፍና ዓለማቀፍ ባለድርሻ አካላትም፣ ለግጭቶች ሁሉን ዓቀፍ ውይይትና ሰላማዊ መፍትሄን እንደ ብቸኛ መፍትሄ እንዲከተሉ ዋና ጸሃፊው መማጸናቸውን መግለጫው አውስቷል። https://www.oikoumene.org/news/wcc-condemns-drone-attack-in-ethiopia
Posted in News

ዘመቻ አንድነት በመላው አማራ ( የፋኖ አመራሮች ማብራሪያ )

Posted in News

አፋር ላይ የሞቱት ባለስልጣን

Posted in News

ባለስልጣኑን የደፋው የህዝብ እንባ! …. አራት ኪሎን የናጠው ውጥረትና መዲናዋ!

Posted in News

”እድሜና ጤንነት ካገኘሁ እንገናኛለን” መንግሥቱ ኃ/ማርያም ከዚምባቡዌ ፤ ”አባቴ ለውሻ ነፍስ ይጨነቃል” የመንግሥቱ ልጅ

Posted in News

የእቴጌ ጣይቱን ሀውልት ማቆም እፈልጋለሁ ( አለምፀሃይ ወዳጆ)

Posted in News

አባት አርበኞቹ የመከላከያ ሰራዊት አዛዡን አጋደሙት! …… አስፈሪውና የመጨረሻው ክተት ታወጀ!

Posted in News

በኢትዮጵያ ያሉ 28 ባንኮች በቢሊዮን የሚቆጠር ብር ተጭበረበሩ

ከ31 ባንኮች መካከል 28ቱ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መጭበርበራቸው ተገልጿል! በዚህ ዓመት ባንኮች ያጡት ገንዘብ ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ300 ሚሊዮን ብር ጭማሪ አለው! የማጭበርበር ድርጊቶቹ የተፈጸሙት በሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች፣ በተሰረቁ የATM ማሽኖች፣ በሐሰተኛ ቼኮች፣ በሐሰተኛ የስልክ መልዕክት እና ተያያዥ መንገዶች አማካኝነት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የገንዘብ ደህንነት ሪፖርትን ጠቅሶ የፌደራል የሥነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሞሽን ነው ይፋ ያደረገው፡፡
Posted in News

አሜሪካ ልጅ ለሚወልዱ እናቶች ማበረታቻ መስጠት ልትጀምር ነው።

ኋይት ሃውስ ሰዎች ተጋብተው ልጅ እንዲወልዱ የሚገፋፋ ፖሊሲ በተግባር ላይ ለማዋል እያሰበ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ ልጅ ለሚወልዱ እናቶች የሚሰጠው ማበረታቻ ነው ተብሏል። በቀረበው ሃሳብ መሰረት እናቶች ልጅ ከወለዱ በኋላ የ5000 ዶላር ቦነስ የሚሰጣቸው መሆኑ ሲዘገብ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ስለ ጉዳዩ ተጠይቀው ለእኔ ጥሩ ሃሳብ ነው ብለው መልሰዋል። የኋይት ሃውስ ፕሬስ ሴክሪታሪያት ስለ ጉዳዩ ተጠይቀው ሃሳቡ የቀረበው የአሜሪካ ቤተሰቦችን ለመደገፍ መሆኑን አንስተው ፕሬዚዳንቱም ሁሉም የሚወለዱ ህፃናት አድገው የአሜሪካን ህልም እንዲያሳኩ ይፈልጋሉ ብለዋል። የትራምፕ አስተዳደር ቤተሰባዊነትን የሚያበረታታ እና ብዙ ህፃናት በአሜሪካ መወለድ አለባቸው ብሎ የሚያምን ስለመሆኑ ሲገለፅ ቆይቷል። ጉዳዩ በሃሳብ ደረጃ ላይ ያለ ሲሆን የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ውሳኔ ካገኘ እንደሚተገበር ይጠበቃል። Source: ABC NEWS
Posted in News

ጅቡቲ ድህነት አንሸከምም በሚል ኢትዮጵያዊያንን የማባረር እቅዷን ገፍታ ቀጥላበታለች

ጅቡቲ፣ ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሕጋዊ ሰነድ ሳይዙ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች እስከተያዘው ወር መጨረሻ በፍቃዳቸው እንዲወጡ ያዘዘችው፣ “በጸጥታ” እና “ጤና” ስጋት ሳቢያ እንደኾነ ተሠምቷል። የፕሬዝዳንት ኦማር ጌሌ አማካሪ አሌክሲስ ሞሐመድ፣ ጅቡቲ የዓለምን ድኅነት ልትሸከም አትችልም በማለት፣ የውሳኔውን ምክንያት መናገራቸው የፈረንሳይ የዜና ወኪል ዘግቧል። በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ኢትዮጵያዊያን በፍቃዳቸው ከአገሪቱ ለመውጣት ሦስት ተጨማሪ ወራት እንዲሠጣላቸው ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንዳላገኘ ከቀናት በፊት መግለጡ አይዘነጋም።
Posted in News

የጌታቸው ረዳ ቡድን የትግራይን ሕዝብ አንድነት ለመከፋፈል እየሠራ ይገኛል ( ደብረጺዮን )

በደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የሕወሓት ክንፍ፣ የጌታቸው ረዳ ቡድን አሁንም የትግራይን ሕዝብ አንድነት ለመከፋፈል እየሠራ ይገኛል በማለት አዲስ ባወጣው መግለጫ ከሷል። የደብረጺዮን ቡድን፣ የጌታቸው ቡድን በመገናኛ ብዙኀን አማካኝነት በሕወሓት ላይ የስም ማጥፋት ድርጊቶችን የሚያሠራጨው በጫና ወደ ሥልጣን ለመመለስ በማሰብ ነው በማለት ወቅሷል። የጌታቸው ቡድን፣ “የዘር ማጥፋት ወንጀል” ፈጻሚዎችን ነጻ ለማስደረግና ባንጻሩ ሕወሓትን ተጠያቂ ለማድረግ ያለመታከት እየሠራ ይገኛል በማለት የደብረጺዮን የሕወሓት ክንፍ ክሱን አሰምቷል።
Posted in News

አማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ኮር ወቅታዊ መግለጫ!

Posted in News

የጎንደሩ ከባድ ተጋድሎ! የባለስልጣኑ ሞት፣ አሜሪካ “በኢትዮጵያ ከባድ ነገር ሊፈጠር ነው አለች!”ጀነራሉ ድንገት ተገደሉ!

Posted in News

ፋኖ ለምን አንድ መሆን ተሳነው? | የፋኖ ሠራዊት ተስፋ እና ስጋት | የአገዛዙ ጥንካሬ ወይስ የፋኖ ድክመት…

Posted in News

የአማራ ብልጽግና ሃላፊው ግድያና ምስክሮቹ!የባህርዳር ዙሪያው ውጊያ! የመርሃቤቴው የህጻናት ጭፍጨፋ!

Posted in News

ወታደራዊ አዛዡ ከነ ሙሉ ጦሩ ፋኖን ተቀላቀለ!

Posted in News

ወጣቱ ዶክተር በሰሜን ሸዋ መራቢቴ ተገደለ !

“ በሙያው ጠቅላላ ሀኪም ነው ቤተሰብ ለመጠየቅ እየሄደ ነው በጥይት ተመትቶ የተገደለው ” – የሟች ጓደኛ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መራቢቴ ወረዳ በእናት ሆስፒታል የጠቅላላ ህክምና ሀኪሙ “በተተኮሰበት ጥይት” መገደሉን የቅርብ ሰዎቹ ገለጹ። ዶክተር ገብረሚካኤል ወልደ መላክ ተገደለ የተባለው ቤተሰቦቹን ለመጠየቅ በመኪና እየተጓዘ መራቢቴ አካባቢ መሆኑን ገልጸዋል። ቃላቸውን የሰጡን የሟች ጓደኛ፣ “ ቤተሰብ ለመጠየቅ እየሄደ ባለበት ነው በጥይት ተመትቶ የተገደለው። ትላንት ጠዋት 3 ሰዓት ነው የተገደለው ” ሲሉ ተናግረዋል። ሌሎች የቅርብ ሰዎቹ በበኩላቸው፣ “ እናት ሆስፒታል ነበር ተቀጥሮ የሚሰራው። መንገድ ላይ መኪና ውስጥ ሆኖ ነው የተተኮሰበት ሰው ሲደርስ ሞቶ ነው ተገኘ ” ብለዋል። የሙያ አጋሮቹ፣ “ ሕይወት የሚያድን ሀኪም ለዚያውም በጥይት እንዴት ሕይወቱ ባጭር እንዲቀጭ ይፈረድበታል ? እኛም ከፍተኛ ስጋት አለብን ” ሲሉ ሀዘነንና ስጋታቸውን ገልጸዋል። የገዳዮቹ ማንነት እስካሁን እንዳልታወቀ፣ የቀብር ሥርዓቱ የሚፈጸመው ዛሬ እንደሆነ ተመልክቷል። ዶክተር ገብረ ሚካኤል በ2015 ዓ/ም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀና ገና ወጣት ሀኪም ነው።
Posted in News

“አስደናቂ ድል ተቀዳጅተናል! አዛዡ ተደምስሷል”ፋኖሰባት ኮሎኔሎች ተቀላቅለዋል!ጉዳዩ አስደንጋጭ ነው!

Posted in News

ወታደራዊ አዛዡ ከመገናኛ ሬዲዮ ጋር በፋኖ እጅ ገባ!በመራቤቴ አውራጃ የሆነው ምንድነው?!

Posted in News

አፈና እና ግድያውን የሚያዘጋጀው በኦሮሞ ብልጽግና አባላት የሚመራው የደህንነት መስሪያ ቤት አመራሮች ስም ዝርዝር

Posted in News

ወታደሩ መገደል ሰለቸኝ፡ በቃኝ አልዋጋም አለ! መከላከያ ሰራዊቱ አፈሙዙን አዞረ/ ጄነራሉ ተሸበረ!

Posted in News

የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ችግር ስለሚከሰት ዜጎቹን አስጠነቀቀ

አሜሪካ ” ነገር አለ ! ” ብላለች ! ባልታሰበ ሰዓት የሚከሰት የተቃውሞ እንቅስቃሴ ስላለ …… አሜሪካ U.S. Embassy Addis Ababa በአዲስ አበባ ችግሮች ስለሚከሰቱ ራሳችሁን ጠብቁ ብላ ዜጎቿን አስጠንቅቃለች ……. ወንጀል በየትኛውም ቦታ እና በማንኛውም ጊዜ ሊከሰት ይችላል; ንቃት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ቁልፍ ነው። ስለዚህ በኢትዮጵያ ያላችሁ ዜጎቼ ተጠንቀቁ ፤ ነገር አለ ብላለች ! ………. ሰልፎችን፣ ስብሰባዎችን እና ሌሎች ትላልቅ የህዝብ ስብስቦች ባሉበት ቦታ እንዳትገኙ ስትል ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ለዜጎቿ ሰታለች ……… ፖሊሶች እና ሁከትን አጣምራ ችግሮች ቅርብ ናቸው ያለችው አሜሪካ በኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣይነት ምን ሊከሰት እንደሚችል የፖለቲካ መልዕክት ያለው እድምታዋን ተንፍሳለች ……. ሁሉም ሰው እንዲነቃ እናበረታታለን ብላለች …….. ሁላችንም አብረን የምናየው ይሆናል። #MinilikSalsawi
Posted in News

ዘመቻ አንድነት ፡ ጎንደር …. የአድማ ብተና ከፍተኛ አዛዥ ተማረከ/ ምሽጉ ተደረመሰ …. የተረፈው ሰራዊት ገደል ገብቶ አለቀ!

Posted in News

ዘመቻ አንድነት – ወቅታዊ መረጃ

Posted in News

የብልፅግናው አቃቢ ሕግ በቢሯቸው አስረው ሲያሰቃዩት የነበረው ግለሰብ ጉዳይ እያነጋገረ ነው

ተከሳሹ ወጣት በአቃቤ ህጉ በደረሰበት ድብደባ የጀርባ አጥንቱ መሰበሩን ገልፆ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲላክ ተማፀነ  ፍርድ ቤት ተከሳሹ ዛሬውኑ ወደ ቂሊንጦ የእስረኞች ማቆያ እንዲላክ እና ህክምና እንዲያገኝ አዟል  (መሠረት ሚድያ)- ታሪኩ ተፈራ የተባለ የ24 ዓመት ወጣት በአዲስ አበባ ከተማ ከግብረ-አበሮቹ ጋር በመሆን የሽብር ወንጀል ሊፈፅም ሲል በቁጥጥር ስር መዋሉን ክሱ ያስረዳል። ይሁን እንጂ ተጠርጣሪው በዛሬው ዕለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ የሽብር ወንጀል ችሎት ቀርቦ ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዳው “ለምርመራ በሚል ፖሊስ ለዓቃቢ ሕግ አሳልፎ በመስጠት ከአራት ወራት በላይ ናትናኤል ስንታየሁ በተባለ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ቢሮ ውስጥ ተዘግቶብኝ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሲፈፀምብኝ ነው የቆየው” ሲል ዛሬ ለችሎቱ አስረድቷል። ታሪኩ አክሎም “አሰቃቂ ድርጊት ሲፈፅምብኝ የነበረውም እዚህ በግራ በኩል የቆመው ዓቃቢ ሕግ ናትናኤል ስንታየሁ ነው። በድብደባ ብዛት የጀርባ አጥንቴ ተሰብሯል፣ እንደምትመለከቱኝ ሰው ካልደገፈኝ መቆም አልችልም፣ ሽንቴን እንኳ መቆጣጠር አቅቶኝ ሰውነቴ ተበላሽቷል። እባካችሁ ከእገታ አስለቅቁኝ። ምርመራው አልቆ ክስ መስርቶብኛል። ከዚህ በኋላ ለምንድን ነው በቢሮው የሚያስቀምጠኝ። ዛሬውኑ ወደ ማረሚያ ቤት ላኩኝና ከሰው ጋር ልቀላቀል” ሲል ተናግሯል። ችሎቱ በበኩሉ ግብረ አበሮቹ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩት ክስ ተመስርቶባቸው ቂሊንጦ የእስረኞች  ማቆያ ሲወርዱ ለምን ታሪኩ ተፈራን ነጥለው እንዳስቀሩት እና ሌሎቹ ተከሳሾች ከአራት ጊዜ በላይ በዚህ ችሎት ሲቀርቡ ለምን እሱን አላቀረባችሁትም የሚል ጥያቄ ያነሳ ቢሆንም “የጀርባ አጥንቱ ስለተጎዳ ሕክምና ለመውሰድ ነው ያቆየነው” ሲሉ ዓቃቢ ሕጉ አቶ ናትናኤል ስንታየሁ መመለሳቸውን የመሠረት ሚድያ
Posted in News

ከባዱ ጦርነት በመተማና ቋራ መስመር

Posted in News

የህክምና ባለሙያዎችን ድምፅ ያስተጋቡ አንድ ዶክተር ውሳኔ ተላለፈባቸው

የህክምና ባለሙያዎችን ድምፅ ያስተጋቡ አንድ ዶክተር ከድሬዳዋ ከተማ ተሰናብተው ገጠር ሄደው እንዲሰሩ ተወሰነባቸው የድሬዳዋ ጤና ባለሞያዎች ድርጊቱን ተቃውመው ፊርማ ማሰባሰብ ጀምረዋል (መሠረት ሚድያ)- በድሬዳዋ ከተማ በሚገኘው ሳቢያን አጠቃላይ ሆስፒታል ሰራተኛ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት እና ከሰሞኑ የጤና ባለሙያዎች ያሰሙትን ድምፅ ያስተጋቡ አንድ ጠቅላላ ሐኪም የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸው ገጠር ሄደው እንዲሰሩ እንደተወሰነባቸው ታወቀ። መሠረት ሚድያ የተመለከተው እና ሚያዝያ 9/2017 ዓ/ም በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ የተፃፈው ደብዳቤ ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ የተባሉት እኚህ የጤና ባለሙያ ‘የሙያ ስነምግባርን የተፃረረ ድርጊት’ መፈፀማቸውን ጠቅሶ ጉዳዩ ባለመታረሙ አሁን ከሚሰሩበት የድሬዳዋው ሳቢያን ሆስፒታል ወደ ለገኦዳ ጉዱንፈታ ጤና ጣብያ እንዲዛወሩ መደረጋቸውን ይገልፃል። “የዛሬ ወር ገደማ ቋሚ ቅጥር ከሳቢያን ሆስፒታል ጋር ፈፅሜያለሁ። ይህ ሆኖ እያለ ከሰሞኑ እኛ የኢትዮጵያ የጤና ተቋማት ሰራተኞች ድምፅ እያሰማን መሆኑን ተከትሎ እኔም አንዳንድ ፅሁፎችን ስላወጣሁ ኢላማ ተደርጌያለሁ” ያሉት ዶ/ር ሀብታሙ ውሳኔው ከመተላለፉ በፊት ባሉት ቀናት ስልክ እየተደወለ በጤና ባለሙያዎች እንቅስቃሴ ዙርያ አስተያየት እንዳይሰጡ ማስፈራርያ ሲደርሳቸው እንደነበር ጠቅሰዋል። “እኔ በበኩሌ ጉዳዩ የመኖር እና አለመኖር መሆኑን ጠቅሼ እንደማላቆም ነገሬያቸዋለሁ። የከተማው ጤና ቢሮ ሀላፊ የሆኑትን ዶ/ር ፅጌረዳን ለማናገር ብሞክርም ያልተገባ ነገር ተናግረውኝ ስልክ ዘግተውብኛል” የሚሉት የጤና ባለሙያው ከዚያም እኚህ ሀላፊ ዶ/ር ሀብታሙ ወደሚሰሩበት ሆስፒታል በመደወል ከስራቸው እንዲታገዱ ማድረጋቸውን መስማታቸውን ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል። ዶ/ር ሀብታሙ በቅርቡ ‘Hakim’ የተባለ የፌስቡክ ገፅ ላይ በርካቶች የተመለከቱት አንድ ፅሁፍ አጋርተው የነበረ
Posted in News

ኢትዮጵያዊው ካርዲናል የሚሳተፉበት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ምርጫ

በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አዲስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የሚመረጡት በመንበር ላይ ያሉት ጳጳስ ሲሞቱ ወይም ከፖፕ ፍራንሲስ በፊት የነበሩት ቤኔዲክት 16ኛ እንዳደረጉት በፈቃዳቸው መንበራቸውን ሲለቁ ነው። ተተኪው ጳጳስም በዓለም ዙሪያ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ተከታይ ያላት የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ በመሆን የመሪነቱን መንበር ይረከባሉ። በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከጳጳሱ በታች ከፍተኛ ሥልጣን ያላቸው ካርዲናሎች ከመካከላቸው የቤተ ክርስቲያኗ መሪ ሊሆኑ የሚችሉትን አዲሱን ጳጳስ ይመርጣሉ። በዓለም ዙሪያ 252 የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ካርዲናሎች ያሉ ሲሆን፣ ከመካከላቸው በአዲሱ የጳጳስ ምርጫ ላይ የሚሳተፉት ከ80 ዓመት በታች የሆኑት ብቻ ናቸው። የእነዚህ በጳጳስ ምርጫ ላይ የሚሳተፉት ካርዲናሎች ቁጥር አብዛኛውን ጊዜ በ120 የተገደበ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ግን ቁጥራቸው 135 ይደርሳል። በኢትዮጵያ “ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለረሃብ” መጋለጣቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስታወቀ የእርግዝና መከላከያ ክኒን በእርግጥ ሴቶችን የበለጠ እንዲጨነቁ ሊያደርግ ይችላል? ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ፑቲን ጠቆሙ https://flo.uri.sh/visualisation/22782656/embed?auto=1 ኢትዮጵያዊው ካርዲናል ማን ናቸው? የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ካርዲናል የሆኑት ብርሃነየሱስ ሱራፌል ሟቹን ፖፕ ፍራንሲስን በመተካት በዓለም ዙሪያ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ተከታዮች ያሏትን ቤተክርስቲያን የሚመሩትን አዲስ ጳጳስ በመምረጥ ከሚሳተፉት መካከል ናቸው። የአዲስ አበባ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ካርዲናል ብርሃነየሱስ 76 ዓመታቸው ሲሆን፣ በአገር ውስጥ እና በውጪ በከፍተኛ ደረጃ መንፈሳዊ ትምህርትን ተከታትለዋል። በአውሮፓውያኑ 1976 በኢትዮጵያ ውስጥ የቅስና ማዕረግን ተቀብለው ከሦስት ዓመት በኋላ ለአንድ ዓመት በወታደራዊው መንግሥት ታስረው ቆይተዋል። ከእስር ከወጡ በኋላ ወደ
Posted in News

በምሥራቅ ጎጃም በተፈጸመ የድሮን ጥቃት “ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን” የዓይን እማኞች ተናገሩ

በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሐሙስ ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም. በትምህርት ቤት ዙሪያ በደረሰ የድሮን ጥቃት ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ። በዞኑ እናርጅ እናውጋ ወረዳ ገደብ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ የትምህርት ቤት አጥር ለማጠር እና ቤት ለመሥራት ‘ለልማት ሥራ’ የወጡ “ሰላማዊ ሰዎች” በጥቃቱ መገደላቸውን ገልፀዋል። የአካባቢው አስተዳደር ግን ጥቃቱ በአካባቢው ተሰብስበው በነበሩ የፋኖ ታጣቂዎች ላይ እንጂ በንፁሃን ነዋሪዎች ላይ አለመፈጸሙን ለቢቢሲ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተፈጸመ ስለተባለው ጥቃት ክትትል እያደረገ መሆኑን አመልክቷል። ነዋሪዎች ለቢቢሲ እንደተናገሩት “ተሰብስበው” በከተማዋ ያለው ገደብ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አጥርን እያጠሩ በነበሩ የሰዎች ላይ ነው ጥቃቱ የተፈፀመው። MORE : https://www.bbc.com/amharic/articles/cq80gz2wv4wo
Posted in News

ቋሚ ሲኖዶስ በአቡነ ገብርኤል የኑፋ*ቄ ትምህርት ጉዳይ ላይ ተወያየ

(ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም/ April 23/2025):- ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን በማስመልከት ባስተላለፉት ትምህርት ዙሪያ ተወያየ። ቋሚ ሲኖዶስ ዛሬ ማለዳ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ባለፈው አርብ በስቅለት ዕለት በፎኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በቅድስት ድንግል ማእያም ዙሪያ ያስተላለፉትን ትምህርት በተመለከተ ውይይት አድርጓል። ብፁዕነታቸው የተላለፈውን ትምህርት ዝርዝር ሁኔታን በመመርመርም ውሳኔ ለማስተላለፍ ይቻል ዘንድ ሁሉም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት በተገኙበት ለሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ ማለትም ሚያዝያ ፳፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም (April 30/2025) ቀጠሮ ተይዟል።
Posted in News