Home › View all posts by Konjit Sitotaw
Blog Archives
በአስገዳጅ ሁኔታዎች ከሥራ ኃላፊነት መልቀቄን አስመልከቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ!
እኔ ያሬድ ኃይለማርያም ከተመሰረተ አራት አመት ተኩል ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከልን (Ethiopian Human Rights Defenders Center) በዋና ዳይሬከተርነት ሳገለግል ቆይቼ ባጋጠሙኝ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከአገስት 1 ቀን 2025 (ሐምሌ 25 2017) ጀምሮ ከሃላፊነቴ እና ከድርጅቱ ለመልቀቅ መገደዴን ለማሳወቅ እወዳለሁ፡፡
ይህ ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲቋቋምና በሌሎች አፍሪካ አገሮች ከሚገኙ አቻ ድርጅቶች ጎን ቆሞ ለሰብአዊ መብት ተሟጋቶች መብት መከበርና አቅማቸውንም ለማጎልበት በርካታ ሥራዎችን እንዲሰራ ምሪት በመስጠትና በአጭር ጊዜም ውስጥ ድርጅቱ በአገር ውስጥና ከአገር ውጭም እውቅና እና ተቀባይነት እንዲያገኝ ከፍተኛ ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ፡፡
ድርጅቱ ከተመሰረተ አጭር እድሜ ያለው ቢሆንም ሲያከናውን የቆያቸው ሥራዎች እና አገሪቱ ውስጥ ለሚፈጽሙ የመብት ጥሰቶች፤ በተለይም በጋዜጠኞች፣ በሲቪል ማህበረሰብ አባላት እና በመብት ተሟጋቾ ላይ የሚፈጸሙ የመበት ጥሰቶችን በማጋለጥና መብታቸው እንዲከበርበአደባባይ በመሟገት ግንባር ቀደም ተቋም ሆኖ እንዲቀጥል ከድርጅቱ ጠንካራ ሠራተኞችና የቦርድ አባላት ጋርበመሆን ቁልፍ ሚና ስጫወት ቆይቻለሁ፡፡
ይሁንና ከአንድ አመት ወዲህ በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ በሚገኙ ሚዲያዎች ላይ እየቀረብኩ አገሪቱ ውስጥ ስላለው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የምሰጠቸው መገልጫዎችና ማብራሪያዎች፣ በማህበረ ድህረ ገጾች ላይ ዜጎችን ስለ መብታቸው እንዲያውቁና በአገሪቱ ውስጥ ስላለው የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በማስመልከት የማካፍላቸው ሃሳቦችና የምሰነዝራቸው የሰሉ ትችቶች በአገዛዝ ሥርአቱ ዘንድ በጥሩ ሁኔታ እየታ ባለመምጣታቸው የተነሳ በተለያዩ አቅጣጫዎች የተለያዩ አይነት ጫናዎችን ሳስተናግድ ቆይቻለሁ፡፡
የተለያዩ ዛቻዎች፣ ማስፈራሪያዎችና ትንኮሳዎችን በጸጥታ አካላት በኩል ሲፈጸሙ
አፍራሽ ይዞታ ያላቸው የባለሥልጣናት_ንግግሮች_ሊገሩ_ይገባል!
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከመኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ እናት ፓርቲ እና ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ)
ከባለሥልጣናት አንደበት የሚወጡ የማይጠበቁ ቃላት አንድ ጊዜ ሲሆን የአፍ ወለምታ ተብሎ ሊወሰድ ይችላል። በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተለያዩ ጊዜያት የሚነገሩ ተመሳሳይ ንግግሮች ሥርዓታዊ የአመለካከት አቅጣጫን የሚያመላክቱ መሆናቸው ግን ጥርጥር የለውም። በዚህ ረገድ የሰሜኑ ጦርነት በሚካሄድበት ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ሕወሓትና የትግራይ ክልልን አስመልክቶ “በሕዝብ አገር መሆን እንፈልጋለን ከኢትዮጵያ ተገንጥለን ካሉ እኮ ራሳቸው የቀረጹት ሕገ መንግሥት ላይ የተቀመጠ እኮ አንቀጽ አለ። በዚያ መሠረት መሄድ ነው!” ብለው መናገራቸው የአንድ ወቅት መነጋገሪያ የነበረ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም በቅርቡ ባደረጉት ንግግር “ለመገንጠል ደግሞ ጉልበት አያስፈልግም። አሠራር ሕገ መንግስት አለ። በዚያ ሂዱ።” ሲሉ ተደምጠዋል።
እነዚኽ በይፋ የተነገሩትን ለአብነት ጠቀስን እንጂ ከቅርብ ጊዜያት ወዲኽ ለብልጽግና ሹማምንት ቅርበት የነበራቸው ግለሰቦች እያወጧቸው ያሉና ማስተባበያም ማስተማመኛም ያልተሰጠባቸው ተመሳሳይ ይዘት ያላቸው የከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ንግግሮች ጆሮን ጭው የሚያደርጉ ናቸው። የኾነው ኾኖ በይፋም ከመጋረጃ ጀርባም የተነገሩና የተባሉ አደገኛ ንግግሮች በስሕተት የተነገሩ እንዳልኾኑ ከድግግሞሹና ከተናገሩት ባልሥልጣናት ደረጃ ማየት የሚቻል ሲኾን ይኽም ሥርዓታዊ አቋም ነው ወይ?! ለማለት ያስገድዳል፡፡
በሌላ በኩል በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አገር የምትገኝበት መጠነ ሰፊ የርስ በርስ ጦርነት አልበቃ ብሎ ባለፈው ያደናቀፈንና ሚሊዮን ዜጎቻችንን ጭዳ ያደረገው የጦርነት እንቅፋት ዳግም ሊመታን ከቋፍ መድረሱን እያየን ነው፤ ከላይ የተጠቀሱ ንግግሮችም
ከፍተኛ የክልል ባለስልጣናት የሚሳተፉበት እና አንድ ሊትር ናፍጣ ማደያ ውስጥ እስከ 280 ብር የሚሸጥበት የጋምቤላ ክልል ( የምርመራ ዘገባ )
“… ደላሎች ይመጡና ነዳጅ አለ፣ ሌሊት ይቀዳልሃል በ280 ብር ትገዛለህ ወይ? ትባላለህ። እሺ ብለህ ከተደራደርክ በኋላ ገንዘቡን ወደ ባለማደያ አካውንት ውስጥ እንድታስገባ ካደረጉህ በኋላ ሌሊት ይቀዳልሃል”
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/280
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ነባራዊ ኹኔታ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማከናወን “ተስፋ ሰጪ ነገሮች የማይታዩበት” ነው ሲል የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓረቲዎቸ ስብስብ – ኮክሰ ሥጋቱን ገለፀ። በቅድሚያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “የአሰራርና ተቋማዊ” ያላቸው ችግሮች እንዲፈቱ የጠየቀው ኮከስ በተቋሙ “እውነተኛ ሪፎርም ከሌለ ተዓማኒ፣ አካታች፣ ነጻና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሊኖር አይቸልም” ብሏል። በዋናነት 8 የፓለቲካ ድርጅቶች ንቁ ተሳትፎ ያደርጉበታል የተባለው ኮከስ ስለ ምርጫ ከመታሰቡ በፊት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ጦርነት እና ግጭቶች እንዲቆሙ፣ ሰላም እንዲሰፍን እና በተለይ ከኤርትራ ጋር እየተስተዋለ ያለው ውጥረት እንዲፈታ ጠይቋል።
የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓረቲዎቸ ስብስብ – ኮክሰ ዛሬ ሐምሌ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ግጭጦች እንዲቆሙ ደጋግሞ ቢጠይቅም አሁንም ለሀገር ደኅንነት ሥጋት ሆነው መቀጠላቸውን ገልጿል። የዚህ ስብስብ አባል ፓርቲ የሆነው የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል ሞጊሶ “ጦርነት ይብቃ” የሚለው አሁንም ዋና የጥሪያቸው ጭብጥ መሆኑን ገልፀዋል።
“ዘላቂ ሠላም እንዲመጣ ከተፈለገ ጦርነት መቆም አለበት። ይሄ ነገር እየሰፋ በሄደ ቁጥር ይቺ ሀገር እያየን ልትፈርስ ትችላለች”።
ኮከስ ቀጣዩን ምርጫ ለማከናወን አስቻይ ኹኔታ የለም ብሏል
ኮከስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከጅምሩ “የነጻነት እና የገለልተኝነት” ጥያቄዎች እንደሚነሱበት በመጥቀስ አሁንም አሉበት ያላቸው “የአሰራርና ተቋማዊ ችግሮች” እስካልተፈቱ ድረስ “ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም” ብሏል፡፡ “እውነተኛ ሪፎርም ከሌለ ተዓማኒ፣ አካታች፣ነጻና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ” ሊኖር እንደማይችልም አቋሙን ይፋ አድርጓል።
“ሕዝብ ሰላማዊ ባልሆነበት ኹኔታ ዲሞክራሲን አይደለም የሚመርጠው። ሕዝብ
” ተፈናቃዮቹ ቤተክርስቲያን እና ሆቴል በር ላይ እየለመኑ ነው ” – የተፈናቃይ ተወካይ
➡️ ” እነሱ በሚሉት ልክ አይደለም የተቋረጠባቸው ” – የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት
በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር በደባርቅ ከተማ ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚገኙ የትግራይ ተፈናቃዮች የእርዳታ እህል ካገኙ ከ8 ወር በላይ እንደሆናቸው ተናግረዋል።
በማኅበር የተደራጅተው ችግራቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩት ተፈናቃዮቹ የሚበሉት ከማጣታቸው የተነሳ ለልመና መውጣታቸውን የመሀበሩ ጸሐፊ መርጌታ ጠበቃው ወልደ ገብርኤል ተናግረዋል።
መርጌታ ጠበቃው እንደሚሉት ወትሮም አልፎ አልፎ ይሰጥ የነበረው እርዳታ ከቆመ 8 ወር ሆኖታል።
ከሰሜኑ የኢትዮጵያው ጦርነት ጋር በተያያዘ ተፈናቅለው በደባርቅ ከተማ መጀመሪያ በመጠለያ ጣቢያ በኃላም ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው መቆየታቸውን የሚናገሩት መርጌታ ጠበቃው ካለፈው ህዳር ወር ጀምሮ እርዳታ እንደተቋረጠባቸው ተናግረዋል።
ምክንያቱ ደግሞ የአካባቢው ባለስልጣናት የወረዳና የከተማ ብለው ተፈናቃዮችን መከፋፈላቸው ነው ይላሉ።
” በከተማ ነዋሪነት የተመዘገቡ ተፈናቃዮች በየጊዜው እርዳታ ያገኛሉ በወረዳ ተፈናቃይነት የተመዘገቡት ግን እያገኙ አይደለም ሁለቱም በአንድ ሰፈር የሚኖሩ ናቸው ” ብለዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የሰሜን ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰላም ይሁን ሙላትን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገረ ሲሆን ” ተፈናቃዮቹ ለ8 ወራት ያህል እርዳታ ተቋረጠብን የሚሉት ስህተት ነው ” ባይ ናቸው።
ከህዳር ወር በኃላ ወሩን በትክክል ባያስታውሱትም ለእያንዳንዱ ተፈናቃይ የሁለት ወር እርዳታ እንደተሰጣቸው አስረድተዋል።
ከዛም አመልድ ኢትዮጵያ 4 ሚልየን ብር በመመደብ ለ200 በጣም ችግር ውስጥ ላሉና ለአቅመ ደካማ ተፈናቃዮች
በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል አዋሳኝ የሚገኙ 14 ወረዳዎች ወደ ሶማሌ ክልል እንዲካለሉ የተወሰነውን ውሳኔ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና እና ቦረና ዞኖች ሕዝባዊ ተቃዉሞ መቀስቀሱን ዋዜማ ሰምታለች።
ይህ ውሳኔ የተወሰነው የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደው ዓመታዊ ጉባኤው ላይ መሆኑን ያስረዱት ምንጮች፣ ይህንኑ ተከትሎ በቅርቡ እንደ አዲስ በተዋቀረው የምስራቅ ቦረና ዞን መቀመጫ ነጌሌ ቦረና ከተማ እና የቦረና ዞን መቀመጫ በሆነችው ያቤሎ ከተማ፣ እንዲሁም በሌሎች ወረዳዎች ከዛሬ ማለዳ አንስቶ የተቃውሞ ሰልፎች እየተካሄዱ መሆኑን ዋዜማ የደረሳት መረጃ ያመልክታል።
ወደ ሶማሌ ክልል እንዲካለሉ በምክር ቤቱ የተወሰኑት 14ቱ ወረዳዎች በሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ በሚገኙት ቦረና፣ ባሌ፣ ሐረርጌ እንዲሁም ከድሬደዋ አካባቢዎች ወደ ሶማሌ ክልል እንዲካለሉ ውሳኔ የተሰጠባቸው እንደሆኑ ምንጮች ነግረውናል።
ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 21፣ 2017 ዓ፣ም እኩለ ቀን ድረስ በፌዴራልም ሆነ በኦሮሚያ ክልል መንግሥት በኩል በጉዳዩ ላይ የተባለ ነገር የለም። [ዋዜማ]
የኬንያው ፕረዚዳንት 14 ሚሊየን የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ሰዓት አድርገው መታየታቸው ግርምትን ፈጥሯል።
ፕሬዚዳንት ሩቶ ሮሌክስ ደይቶና የተባለውን ቅንጡ ሰዓት አድርገው የታዩት በአፍሪካ ከሚገኙት ትላልቅ ፓርኮች መካከል አንዱ በሆነው በማሳይ ማራ ብሔራዊ ፓርክ ጉብኝት ባረጉበት ወቅት ነው።
ሮሌክስ ደይቶና ለገበያ የቀረበው በፈረንጆቹ 1963 ሲሆን የተሰራው በዋነኝነት ለመኪና ውድድር ሹፌሮች ነው።
ሰዓቱ እስከ 72 ሰዓት ኃይል ማቆየት እንደሚችል ሲነገር እስከ 400 ማይልስ በሰዓት ድረስ አማካይ ፍጥነትንም ያሰላል ተብሏል።
በ2024 ዊሊያም ሩቶ እንደዚሁ 425,000 የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ቀበቶ አድርገው መታየታቸው የሚታወስ ነው።
በቅርቡ ዊሊያም ሩቶ 8000 ሰዎችን መያዝ የሚችል ቤተክርስቲያን በቤተመንግስታቸው ውስጥ ለመገንባት ማቀዳቸውን ተናግረው የነበረ ሲሆን አጠቃላይ የግንባታ ወጪውም 1.2 ቢሊየን የኬንያ ሽልንግ ተገምቷል።
ፕሬዚዳንቱ ቤተክርስቲያኑን ለመገንባት ከህዝብ የሚሰበሰብ ገንዘብ እንደሌለና በራሳቸው ወጪ እንደሚገነቡት ቢናገሩም ከትችት አልተረፉም።
የኬንያ ባለስልጣናት ቅንጦት በማዘውተር ሲወቀሱ በቅርቡ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩ በቅርቡ 900,000 የኬንያ ሽልንግ የሚያወጣ ሰዓት፣ 80,000 ሽልንግ የሚያወጣ ጫማ እና የ20,000 ሽልንግ ከረቫት አለኝ ብለው መናገራቸው ቁጣን ቀስቅሶ ነበር።
በአፍሪካ መሪዎች የሚኖሩት ኑሮ ከህዝቡ በተቃራኒ እንደሆነና የቅንጦት ኑሮን የሚያዘወትሩ እንደሆነ በተደጋጋሚ የሚነገር ቢሆንም ባለስልጣናት አሁንም ቢሆን የቅንጦት ኑሮን ከማዘውተር አልቦዘኑም።
Source: The Kenya Times, Tuko News, Standard Media
ሳይንቲስቶች ሰዎች ህፃን አያሉ ወደፊት ከመጠን በላይ ይወፍራሉ ወይ የሚለውን መለየት የሚያስችል ሞዴል መስራታቸው ተነገረ።
የኮፐንሃገን እና ብሪስቶል ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ከ5 ሚሊየን ሰዎች በተሰበሰበ መረጃ በተሰራ ትንተና ሰዎች ከመጠን በላይ ሊወፍሩ ይችላሉ የሚለውን ገና በልጅነታቸው መገመት እንደሚቻል እና ይህም ውፍረቱን ለማስቀረት በጊዜ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚረዳ ገልፀዋል።
በ2035 ከአለም ህዝብ ውስጥ ግማሽ ያህሉ ከመጠን በላይ ይወፍራል ተብሎ ሲጠበቅ ሳይንቲስቶቹ የሰሩት ሞዴል ህፃናት እና ወጣቶች ከመጠን በላይ ለመወፈር ዘራቸው ያለውን ተጋላጭነት በአግባቡ በመገመት መፍትሄ እንዲኖር ያደርጋል ተብሏል።
አዲሱ ሞዴልም በሰዎች ላይ የሚኖርን 17 በመቶ የሰውነት መጠን መለኪያ(BMI) ልዩነት ያስረዳል ተብሏል።
ከመጠን በላይ ውፍረት በአሁኑ ጊዜ አሳሳቢ የማህበረሰብ የጤና ችግር ሲሆን ከአካባቢ፣ አኗኗር እና ከዘር ጋር በተያያዘ ይመጣል።
በተጨማሪ ሳይንቲስቶቹ ከዘር ጋር በተያያዘ ከመጠን በላይ የወፈሩ ሰዎች ክትትል አድርገው እንዲቀንሱ ሲደረግ በቶሎ እንደሚቀንሱ እንደዚሁም ሲያቆሙ በቶሎ ክብደታቸው እንደሚጨምር ገልፀዋል።
በአለም አቀፍ ደረጃ ከመጠን በላይ ውፍረት አሳሳቢ ደረጃ ሲደርስ ከመጠን በላይ የሚወፍሩ ጎልማሶች ቁጥር በ2010 ከነበረበት 524 ሚሊየን በ2030 1.13 ቢሊየን ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
በተጨማሪ በ2050 ነገሮች ካልተቀየሩ 3.8 ቢሊየን ጎልማሶች እና 746 ሚሊየን ህፃናት ከመጠን በላይ ውፍረት ያጋጥማቸዋል ተብሎ ተገምቷል።
በ2021 በአሜሪካ 42 በመቶ ወንዶች እና 46 በመቶ ሴቶች ከመጠን በላይ ወፍረው እንደነበር ተዘግቧል።
ከሰሃራ በታች ባሉ ሃገራት ከመጠን በላይ የሚወፍሩ ሰዎች ቁጥር በ2050 በ250 በመቶ በመጨመር 522 ሚሊየን እንደሚደርስ ይጠበቃል።
ከመጠን በላይ
አልሸባብ ከሞቃዲሾ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ያለችን ከተማ ዳግም መያዙን ገለፀ።
አልሸባብ ባለፉት ቀናት ከሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለችው ሳቢድ ከተማ ከባድ ውጊያ ማድረጉን ገልፆ በኡጋንዳ እና ሶማሊያ ጦር ላይ ከፍተኛ ጥቃት ሰንዝሮ ከተማዋን ዳግም መቆጣጠሩን ገልጿል።
በተጨማሪ አልሸባብ በከተማዋ ያለን የሶማሊያ ጦር እና የኡጋንዳ ሰላም አስከባሪ ጦር ማዘዣዎችን እንደዚሁም መኪኖችን እና መሳሪያዎችን መያዙን ገልጿል።
የሳቢድ ከተማን ከወር በፊት የሶማሊያና የኡጋንዳ ጦር ከአልሸባብ ነፃ አውጥተውት የነበረ ሲሆን ከተማዋ በአልሸባብ እጅ ዳግም በመወደቋ ላይ የሶማሊያ ጦርም ሆኑ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ያሉት ነገር የለም።
አልሸባብ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ኃይሉን እያጠናከረ በርካታ ከተሞችን መያዝ ሲጀምር በሶማሊያ ያለው የህብረቱ ተልዕኮ ከበጀት ድጋፍ ጋር በተገናኘ የሚፈልገውን ያህል እየተንቀሳቀሰ እንዳልሆነ ሲዘገብ መቆየቱ ይታወሳል።
Source: Somali Guardian
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ለግብፅ የ4.7 ቢሊየን ዶላር የመሳሪያ ሽያጭን አፅድቋል።
በመሳሪያ ሽያጩ መሰረት ግብፅ ራዳር፣ ሚሳኤሎች እና የሎጅስቲክስ እንደዚሁም የኢንጂነሪንግ ድጋፎችን ከአሜሪካ ታገኛለች።
አሜሪካ ለግብፅ የምትሰጠው የአየር ስርዓት መሳሪያ ሂሊኮፕተሮችን፣ ድሮኖችን እንደዚሁም ክሩዝ ሚሳኤሎችን ለመመከት ያስችላል።
አሜሪካ ይህንን ሽያጭ የኔቶ አባል ሃገር ካልሆኑት ዋነኛ አጋሮቿ ውስጥ የሆነችው የግብፅን ደህንነት ለማሻሻል መሆኑን ገልፃ ይህም በመካከለኛው ምስራቅ ሰላም እና የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲኖር ያስችላል ብሏል።
በተጨማሪ ለግብፅ ጦር ስልጠና እና የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ 26 የአሜሪካ መንግስት ሰራተኞች እና 34 ኮንትራክተሮች ወደ ግብፅ ያመራሉ ተብሏል።
የመሳሪያ ሽያጩን የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ያፀደቀው ሲሆን በቀጣይ የኮንግረሱ ውሳኔ ይቀረዋል።
ከ1979 ጀምሮ ግብፅ ከእስራኤል ጋር የሰላም ስምምነት በመፈራረሟ ከአሜሪካ የመሳሪያ ሽያጭ እና ድጋፍ በገፍ እያገኘች እንደሆነች ይታወቃል።
ግብፅ በተመሳሳይ በ2024 የ5 ቢሊየን ዶላር የመሳሪያ ግዢን ከአሜሪካ ፈፅማለች።
ሃገረ ግብፅ ከእስራኤል በመቀጠል ከአሜሪካ ሁለተኛዋ ከፍተኛ የወታደራዊ ድጋፍ የሚደረግላት ሃገር ስትሆን ከ1979 ጀምሮ በየአመቱ የ1.3 ቢሊየን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ ከአሜሪካ ታገኛለች።
Source: Al Jazeera, Madamasr, Defensepost
የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ፣ የኢትዮጵያ መሪዎች ከጠብ አጫሪ ንግግር ተቆጥበው በአገሪቱ የውስጥ ችግሮች ላይ እንዲያተኩሩ በሁለተኛው ክፍል ቃለ ምልልሳቸው መክረዋል። ፕሬዝዳንቱ፣ ኤርትራን መወንጀል ሌላ ጣጣ ማምጣት እንደሚሆንና የከፋ ውጤት ከመጣ ማቆም እንደማይቻል አጠንቅቀዋል። ኢሳያስ፣ በሱዳኑ ጦርነት ጀርባ ዋነኛዋ ተዋናይ ኢምሬቶች ናት በማለትም ከሰዋል።
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ከበላይ አካላት በደረሰበት ጫና የአመቱን ሪፖርት በተመለከተ ሊሰጠው የነበረውን ጋዜጣዊ መግለጫ መሰረዙ ታወቀ
ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ መንግስታዊ ተቋማት በአንፃራዊነት ነፃነት እንዳለው በስፋት ይነገርለት የነበረው የፌደራል ዋና ኦዲተር ቢሮ ከቅርብ አመታት ወዲህ፣ በተለይ ደግሞ ባለፈው አንድ አመት ‘ከበላይ አካላት’ ከፍተኛ ተፅእኖ እየደረሰበት መሆኑ ታውቋል።
የፕሪሚየም አባል ከሆኑ ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/bde9y4sm
የአለም ጤና ድርጅች የቺኩንጉንያ ቫይረስ በፍጥነት እየተዛመተ ነው ሲል አስጠነቀቀ።
በአለም ላይ ከ20 አመት በፊት ተከስቶ የነበረውና በወባ ትንኝ ዝርያ የሚከሰተው የቺኩንጉንያ ቫይረስ በህንድ ውቅያኖስ አካባቢ በሚገኙ ሃገራት ዳግም ተቀስቅሶ እየተስፋፋ ነው ተብሏል።
በ119 ሃገራት የሚኖሩ 5.6 ቢሊየን ሰዎች የቫይረሱ ስጋት ውስጥ መሆናቸውም ተገልጿል።
በላ ሪዩኒየን ደሴት ከሚገኘው ህዝብ አንድ ሶስተኛው በቫይረሱ ተይዟል ያለው የአለም ጤና ድርጅት ቫይረሱ በአሁኑ ጊዜ ወደ ማዳጋስካር ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ ተስፋፍቷል ብሏል።
በሽታው ወደ አውሮፓ ተስፋፍቶ 800 ሰዎች በፈረንሳይ በቫይረሱ ተይዘዋል ሲባል በጣሊያንም የተያዙ ሰዎች ተገኝተዋል።
ቫይረሱ ምንም አይነት ህክምና የሌለው ሲሆን የሚተላለፈው በወባ ትንኝ ዝርያ እንደሆነ ሲገለፅ እንደ ድካም፣ ትኩሳት እና የራስ ምታት ያሉ ምልክቶችም አሉት ተብሏል።
የአለም ጤና ድርጅት ሰዎች ራሳቸውን በልብስ በመሸፈን እና እንደ አጎበር ባሉ ነገሮች በመጠቀም እንዲጠብቁም መክሯል።
በ2005 በተከተሰው ወረርሽን ወቅት በሚሊየኖች በበሽታው ሲያዙ በመቶዎቾ የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወትም አልፏል።
ቫይረሱ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ በ2008 ዓ.ም ተከስቶ የነበረ ሲሆን ከተከሰተባቸው አከባቢዎች አንዱ ኢትዮጵያ ከኬንያ ጋር በምትዋሰንበት ዶሎ አዶ አካባቢ ሲሆን በድሬዳዋም በተመሳሳይ ተከስቶ ነበር።
በቫይረሱ ዙሪያ በቅርብ በተደረገ ጥናት (https://www.frontiersin.org/journals/public-health/articles/10.3389/fpubh.2025.1538911/full) ኢትዮጵያ ለቫይረሱ ተጋላጭነት አድሏ 24 በመቶ መሆኑን ይጠቁማል። በዚህም ቫይረሱ የህብረተሰብ ጤና ስጋት መሆኑን ያነሳል።
Source: USA TODAY
በIMF የተማረሩ ሀገራት! በመጨረሻ IMF ኢትዮጲያ ደርሷል!
በ IMF ድጋፍ ዙሪያ ክርክር አለ! ለሀገራት ይጠቅማል እና ይጎዳል!
ከ IMF ድጋፍ ተከትለው ስለሚመጡ የጉዳት ማስረጃዎች ከጥቅሙ ይበዛሉ!
ከ IMF ጋር ሪፎርም በማድረግ ከፍተኛ መማረር ውስጥ ስለገቡ ሀገራት እና ምክንያት በምሳሌ እመለከታለን!
ኢትዮጲያ ከIMF ጋር የቅርብ ሪፎርም አካል ነች! የአንድ ዓመቱን ምልክት ከሌሎች ሀገራት ጋር እያነጻጸርን እመለከታለን! https://youtu.be/T631z06d49g
መቀጣጫው ለእኔ ሳይሆን ለእናንተ ነው! ( ልደቱ አያሌው )በቅርቡ- “መኖሪያ ቤትህን በ10 ቀን ውስጥ የማህበረሰብ ፖሊስ ጣቢያ ላደርገው ነው” ብሎ የዛተው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አገዛዝ ዛቻውን ለመፈጸም 10 ቀንም መታገስ አልቻለም። ከሁለት ቀን በፊት ያለምንም የፍርድ ቤት ውሳኔ የቤተሰቤ ንብረት የሆነውን መኖሪያ ቤቴን ከነ ሙሉ እቃው በመቀማት (መውረስ አይደለም) ፖሊሶች ገብተውበታል። ቀደም ሲል እንዳሉት የማህበረሰብ ፖሊስ ጣቢያ ያድርጉትወይም የባለስልጣን መኖሪያ እስካሁን በግልፅ አላዎቅነም። ይህንን ማድረግ አልበቃቸው ብሎም የቤቴን ጠባቂያለምንም ምክኒያት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደው አስረውታል።ይህ አገዛዝ አይፈጽመውም ብዬ የምገምተው ምንም ዓይነት ነውርና ወንጀል ባይኖርም፣ ይህ የጠቅላይሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዐይን ያዎጣ የወንጀል ድርጊት የፖለቲካ አንደምታው ምን እንደሆነ እይታየንለህዝብ ማካፈል ስለፈለግሁ ይህችን አጭር መጣጥፍ ላስነብባችሁ ወደድኩ።በኢትዮዽያ ፖለቲካ ተሳታፊ ከሆንኩ 33 ዓመት ሆኖኛል። በ27 ዓመቱ የኢህአዴግ አገዛዝ 5 ጊዜ ታስሬ ተፈትቻለሁ። ለ18 ቀናት የቤትና የቢሮ ውስጥ እገታ፣ ለ120 ተከታታይ ቀናት የደህንነት ክትትልና ማዋከብ፣ቢያንስ ለ20 ተከታታይ ዓመታት የስም ማጥፋት ዘመቻ ተካሂዶብኛል። አጸያፊ ስድብና መለስተኛ ድብደባ የደረሰብኝ ወቅትም ነበር። በእነዚህ ሁሉ ተጽዕኖዎች ምክኒያት ለተለያዩ የማህበራዊ፣ የኢኮኖሚና የጤና ችግሮች ተጋላጭ ሆኛለሁ።ይህ ሁሉ በደል ሲደርስብኝ ግን በወቅቱ በስልጣን ላይ የነበረው የኢህአዴግ አገዛዝ በእኔ ላይ ለሚፈጽማቸውህገ-ወጥ ድርጊቶች ቢያንስ ህጋዊ ሽፋን ለመስጠትና ለማስመሰል በተቻለው አቅም ይሞክር ነበር። በእኔየፖለቲካ ተሳትፎ ምክኒያትም በቤተሰቦቸና በጓደኞቸ ላይ አንድም ጊዜ ችግር ለመፍጠርና የግል ንብረቴን ለመውረስ ሞክሮ አያውቅም። አባል የነበርኩበትን ፓርቲም ለመከፋፈልና ለማዳከም እንጂ

በደምቢዶሎ ከተማ በሁለተኛ ዲግሪ (ማስተርስ) ተመርቃ መንገድ ላይ አትክልት እና ፍራፍሬ በመቸርቸር የምትተዳደረው መምህርት ፎቶ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ተጋርቶ በርካቶች ዘንድ አነጋጋሪ ሆኗል።
አባይነሽ ሐምቢሳ የተባለችው ይህች መምህርት ከደምቢደሎ ዩኒቨርስቲ በሒሳብ የትምህርት ዘርፍ የማስተርስ ዲግሪዋን ያገኘችው በማዕረግ ነው።
ይህች መምህርት ላለፉት ዓመታት ትምህርት በሚዘጋበት በክረምት ወቅት እንዲሁም በእረፍት ቀኗ ቅዳሜዎችን መንገድ ላይ በመቸርቸር ነው ኑሮዋን የምትደግፈው።
ለ13 ዓመታት በመምህርነት ያገለገለችው አባይነሽ በየወሩ የምታገኛት 7,500 ብር ደመወዝ ካለው የዋጋ ግሽበት ጋር ተያይዞ ኑሮዋን መደጎም ስላዳገታት ነው ወደ ጉሊት የወጣችው።
“የማገኘው ደሞዝ ልጆቼን ለማስተዳደር፣ ማኅበራዊ ሕይወቴን ለመደገፍ፣ ለትምህርት፤ ለአጠቃላይ ለኑሮዬ በቂ አይደለም። በአሁኑ ሰዓት ለመንግሥት ሠራተኞች የሚከፈለው ደመወዝ በቂ አይደለም፤ ያለውን የኑሮ ውድነትን ያገናዘበ አይደለም” ትላለች።
ከማስተማር ሥራዋ ጎን ለጎን ትምህርቷን በከፍተኛ ደረጃ መቀጠሉ አስፈላጊ ሆና ያገኘችው አባይነሽ፣ የማስተርስ ትምህርቷን ለመደጎምም ሌላኛው አማራጩ ጉሊት ነበር።
“በወር ደሞዜ የትምህርቴን ከፍዬ፣ ኑሮዬን ደግፌ፣ ለልጆቼ አውጥቼ አይሆንም” ስትል የአራት ልጆች እናት የሆነችው አባይነሽ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ገልጻለች።
በምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ዩብዶ ወረዳ የተወለደችው አባይነሽ የጉሊት ችርቻሮዋን የጀመረችው ከሁለት ዓመታት በፊት ነው።
ሙዝ፣ ብርቱካን፣ ሎሚ እና አቮካዶ የመሳሰሉ ፍራፍሬዎችን ከደምቢዶሎ ከ20 አስከ 25 ደቂቃ በእግር የሚያስኬድ መንገድ ከሚጠይቀው ስፍራ ተሸክማ አምጥታ በከተማዋ ትችረችራለች።
ገበያ በደራበትም ቀንም ከ200 አስከ 500 ብር ታገኛለች።
“ከማገኘው ትርፍ 100 ወይም 200 ብር አስቀምጬ ቀሪውን ደግሞ ለቤተሰቤ የሚያስፈልጉ እንደ ሳሙና፣ ስኳር ወይም
በዘንድሮው የ6ኛ እና የ8ኛ ፈተና ወቅት በአንዳንድ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ መምህራን ለተማሪዎች መልስ እንዲሞሉ ሲደረግ እንደነበር ታወቀ
– “በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል ያለዉን የውጤት ልዩነት እጅግ እየተቀራረበ መጥቷል”- የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
– “ሚሽኑ የተሰጣቸው መምህራን ድርጊቱን ባያምኑበት እንኳን አማራጭ አልነበራቸውም”- መምህራን
ከሆኑ ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/y4a2fhnw
በአዲስ አበባ ከተማ ከትናንት ጀምሮ ተመልሶ የመጣው መጠነ-ሰፊ የወጣቶች አፈሳ
“ሲቪል ፖሊስ በየመንገዱ እወስድሀለው እያለ ይደራደራል፣ ሌብነቱ ሀላል ወጥቷል። በየቀኑ ከመዝናኛ ቦታ እየወሰዱ በብር ተደራድረው ይለቋቸዋል።”
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/6mcu6xfd
የእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ የምስክር አሰማም ሂደት ለጊዜው ታግዶ እንዲቆይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ
የተከሳሽ ጠበቆች በይግባኙ አቤቱታ ላይ እንደገለፁት አቃቤ ሕግ 15 ምስክሮችን ካሰማ በኋላ ቀድሞ በስም ዝርዝሩ ውስጥ ያልተካተተን ምስክር በመጋረጃ ጀርባ እንዲመሰክር ብሎ ማቅረቡ የተከሳሾችን መብት በእጅጉ የሚጎዳ በመሆኑ ይሄው የስር ፍርድ ቤቱ ብይን ሊነሳ ይገባል የሚል ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/65f?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
የጠላት 78ኛ ክ/ጦር ተደመሰሰች።
በአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ እዝ 4ተኛ ደጅ አዝማች ኮር የጎቤ ክፍለ ጦር ዛሬ ሐምሌ 15/2017 ዓ.ም
በቁጥር አንድ እና በኪኒቸሩ መካከል ባደረገው ውጊያ የተገኘ ከፊል ምርኮ:-
1.አስር/10 ተሺከርካሪ
2.አንድ ሞርታር ከ6 ቅንቡላ ጋር
3.አንድ ዲሽቃ ከ18 ሳጥን /አስቃጥላ ተተኳሺ ጋር
4.ከ 117 በላይ ነፍስ ወከፍ
5.ቁጥሩ ያልታወቀ ብሬን እና ስናይፐር
6.ብዙ የክላሺ እና ብሬን ተተኳሺ
7.ቁጥሩ ያልታወቀ ምርኮኛ
👉የጠላት ኃይል 78ኛ ክፍለ ጦር(የቅጥረኛው ግርማ ኃይል ነው )
💉2 ሬጅመንት የጠላት ኃይል ተደምስሷል::
💉ሻለቃ አስረስ የተባለው የጠላት ጦር መሪም ተገሏል::
👉ኦፕሬሺኑን በበላይነት የመሩት የጎቤ ክፍለ ጦር አመራሮች
1ኛ. አርበኛ ኢሳያስ ሰጠኝ=ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
2ኛ. አርበኛ መንገሻ አስራት=ም/ዋ/አዛዥ
3ኛ.አርበኛ እሸቱ ምስጋናው=ኦርዲናንስ ኃላፊ
4ኛ.አርበኛ እርታው ታገለ=ሕዝብ አደረጃጀት ኃላፊ ናቸው::
ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ
“ለቅቄ ወጥቻለሁ”
<<እኔን የወከለ አስተዳዳሪ የለም ፤ ህጋዊ የዞኑ አስተዳዳሪ እኔ ነኝ ፤ አላስፈላጊ ግጭትና ደም መፋሰስ ለማስቀረት በማሰብ ፅህፈት ቤቴን ለቅቄ ወጥቻለሁ። በዞኑ የሚደረግ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ቀይ መስመር ነው ፤ ወታደር ስለአሰማራህ አስተዳድረሀል ማለት አይደለም ከትናንት ሀምሌ 14 ከምሽቱ 3፡30 ጀምሮ የአድማ ብተና ፖሊስና ታጣቂ ሰራዊት ወደ ዞኑ ተሰማርቷል።ለረጅም ጊዚያት እቅድና ዝግጅት ሲደረግበት የቆየ የዞኑ አስተዳደር የማፍረስ ተግባር እየተፈፀመ ነው። ጀኔራል ታደሰ እርስበራሱ የሚጋጭ አዲስ ቀውሰ አዋላጅ ነው። ህውሃት ኃላቀርና ቆሞ ቀር ቡድን ነው።>>
አቶ ሃፍቱ ኪሮስ
የትግራይ ደቡባዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
አሜሪካ ከተመድ የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ተቋም (UNESCO) ልትወጣ ነው።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዳግም ወደ ነጩ ቤተመንግስት ከተመለሱ በኋላ አሜሪካ ከአለም አቀፍ ተቋማት እንድትወጣ እየሰሩ ሲሆን አሁን ከዩኔስኮ እንድትወጣ መወሰናቸውን የነጩ ቤተመንግሥት ምክትል ቃለ አቀባይ አና ኬሊ ተናግረዋል።
አና ኬሊ የዩኔስኮ የባህል እና ማህበራዊ ፖሊሲ አሜሪካውያን ድምፃቸውን ከሰጡበት ፖሊሲ ጋር ስለሚቃረን ፕሬዚደንቱ አሜሪካ እንድትወጣ መወሰናቸውን ገልፀዋል።
በተጨማሪ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ቃለ አቀባይ ታሚ ብሩስ የአሜሪካ በዩኔስኮ መቀጠል ከብሔራዊ ጥቅሟ በተቃራኒ መሆኑን ገልፀዋል።
ታሚ ብሩስ ተቋሙ ውስጥ ፀረ ሴማዊነት አለ ያሉ ሲሆን ተቋሙ ፍልስጤምን እንደ አባል ሃገር መቀበሉ ከአሜሪካ ጥቅም በተቃራኒ ነው ብለዋል።
የዩኔስኮ ዳይሬክተር ኦድሪ አዙላይ ተቋማቸውን ይህንን ውሳኔ ሲጠብቅ እንደነበር ገልፀው ሲዘጋጁበት እንደነበርም ገልፀዋል።
አሜሪካ ከተመድ የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ተቋምም በፈረንጆቹ ታህሳስ 31፥2026 ትወጣለች ተብሏል።
አሜሪካ በ1945 ዩኔስኮን ከመሰረቱ ሃገራት አንዷ ስትሆን በ1984 ከፋይናንስ አያያዝ እና ከአሜሪካ በተቃራኒ ቆሟል በሚል ከወጣች በኋላ ተቋሙን በ2003 ዳግም ተቀላቅላለች።
በተመሳሳይ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፕሬዚዳንት ሆነው በተመረጡ ጊዜ አሜሪካን ከተቋሙ አስወጥተው የነበረ ቢሆንም ጆ ባይደን ዳግም መልሰዋት እንደነበር የቅርብ ጊዜ ሁነት መሆኑ ይታወሳል።
Source: CNN
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ
ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ
ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒሊክ ዕዝ ስር የተከወኑ የሀምሌ 15/2017 ዓ.ም የዕለቱ ሁነቶች !
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
🔸ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ክፍለ ጦር በመቄት ወረዳ ከ18 በላይ የብልፅግና አድማ ብተና አባላት በመደምሰስ ከ16 በላይ በማቁሰልና 15 ፈቅዶ እንዲቀላቀል በማድረግ አንፀባራቂ ተጋድሎ ፈፅመዋል።
🔸የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ አሳምነው ኮር የሜጀር ጄኔራል ውባንተ አባተ ክፍለ ጦር በመቄት ወረዳ የሚገኘው የብልፅግና ወንበር አስከባሪ አድማ ብተና አባላት ላይ ጥቃት በመፈፀም 18ቱ ሲደመሰሱ 16ቱ ቆስለዋል።
በዚህ አውደ ውጊያ የውባንተ አባተ ክፍለ ጦር አራት ሻለቃዎች መቶ አለቃ ዳንዔል መለሰ፣ኮሎኔል ሰሎሞን አሻግሬ፣አይሻ ሙሀመድ እና ዋግሹም አድማሱ ሻለቃዎች ላይ የተውጣጡ ፋኖዎች የተሳተፉበት ሲሆን ደብረ ዘቢጥ፣ኮኪት፣አግሪት፣ጫት ውኃ፣ፍላቂትና ገረገራ መሽጎ በነበረው የአገዛዙ ሎሌ በሆነው አድማ ብተናና ፖሊስ አባላት ላይ ሐምሌ 14 / 2017 ዓ.ም ጥቃት አድርሰውበታል።
በዚህ ኦፕሬሽን 18 የተሰዋ፣16 የቆሰለ፣ 18 ክላሽ፣አምስት የወገብ ትጥቅ፣450 ተተኳሽ የተማረከ ሲሆን 11 ሚሊሻዎች እና አራት አድማ ብተና አባላትም የአገዛዙን ግፍና መከራ በመቃወም ወደ አድማ ብተና አባላት አፈሙዝ አዙረው እየተኮሱ የውባንተ አባተ ክፍለ ጦር ፋኖዎችን ተቀላቅለዋል።
🔸ተጠናክሮ በቀጠለው የምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለጦር የራያ ቆቦ ዞብልና ቀዩ ጋሪያ ተጋድሎ ትናንት ሐምሌ 14/2017
አፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና
በላይ ዘለቀ ዕዝ
ጀግናው ሰራዊታችን ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም የአገዛዙን ሰራዊት የሚደመስስ የረቀቀ ወታደራዊ ዕቅድ በማቀድ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በመተማ ወረዳ ሽመለ ጋራ፣ደለሎ ቁጥር አንድና ቁጥር አምስት በከፈተው ወታደራዊ ማጥቃት ከ170 በላይ የተደመሰሰ፣ከ40 ጠላት እጅ ሰቶ ተማርኳል፣ከ100 በላይ የነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያ ሲማረክ 06 የቡድን የጦር መሳሪያ ብሬንና ስናይፐር ተማረኳል።
አንድ ዲሽቃ ሞተራይዝድ የተማረከ ሲሆን 05 አይኮም ወታደራዊ ሬድዮን ጨምሮ 01 ሽጉጥ የተማረከበት ስኬታማው ኦፕሬሽን ነው።
ዘግይቶ በደረሰን መረጃ መሰረት ደጃዝማች 4ኛ ኮርና ከመይሳው ካሳ 2ኛ ኮር አጣናው ዋሴ ክ/ጦር በቅንጅት የብርሃኑ ጁላ ታጣቂን በበርሃማው ጠረፋማ ቀጠና አንጀቱን በጎተቱበት ውጊያ የጠላት 78ኛ ክ/ጦር 1ኛ ሬጅመንት ሙሉ በሙሉ ሲደመሰስ 2ኛ ሬጅመንትም በከፊል ተደምስሳለች።
የዓብይ አህመድ 78ኛ ክ/ጦር 1ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሻለቃ ኤፍሬምም በደለሎ ቁጥር አንድ ከተደመሰሱት መካከል እንደሚገኝበት ማረጋገጥ ተችሏል።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ በላይ ዘለቀ ዕዝ
ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ
Amhara Fano National Force
@AmharaFanoNF
·
39m

አሁን ያለው የኑሮ ውድነት በምን ኹኔታ የሚገለጽ ነው?
አሁን ያለው የኑሮ ውድነት በምን ኹኔታ የሚገለጽ ነው?