Home › View all posts by Konjit Sitotaw
Blog Archives
ሰሞኑን ለየት ያለ አግዶ የመዘርፊያ ስልት መጥቷል። ከዚህ በፊት ሰው ታግቶ ወደ ዱር ተወስዶ ገንዘብ ይጠየቅ ነበር። አሁን ግን የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከመዲናዋ ሰውን አፍነው እዚያው ከተማዋ ውስጥ ይደብቃሉ። ወደ ፍርድ ቤት አይወስዱትም ፤ ለቤተሰቦቹም አያሳዩም።
ቤተሰብ በፍለጋ ሲጨነቅ ፣ የደህንነቶቹ ደላላዎች በመደወል ገንዘብ ከተሰጣቸው ያሉበትን ቦታ እንደሚነግሩ በስልክ ለቤተሰብ ያሳውቃሉ። ያ ገንዘቡ ከተከፈለ በኋላ ደግሞ ከቤተሰቡ ጋር ለማገናኘት ተጨማሪ ገንዘብ ይጠየቃል። ከዚያ በኋላም ለመልቀቅም በእጥፍ ገንዘብ ያስከፍላላኡ። ወዳጅ ዘመድ ሚስጥር ቢያወጣ ታፋኙ እንደሚገደል ያስፈራራሉ። ህዝባችን መንግስታዊ ካባ በለበሱ ሌባ ዱርዬዎች መጫወቻ ሆነ።
ለማንኛውም ዘመድ የታፈነባችሁ እስኪ ኮልፌ ፖሊስ ማሰልጠኛ አፈላልጉ። በመቶውች እዛ በድብቅ ታግተው ይገኛሉ። ( ጃዋር መሐመድ እንደፃፈው)
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለህዝብ አገልግሎት እንዲሰጡ መመሪያ ሰጠ!!
የሙሉ መግለጫው ዝርዝር https://www.facebook.com/photo?fbid=4219626751641829&set=a.1476263212644877
የኬንያው “ኬሲቢ” ባንክ፣ ከአንድ ስሙ ይፋ ካልሆነ የኢትዮጵያ የግል ባንክ የአክሲዮን ድርሻ ለመግዛት ንግግር መጀመሩን ዳይሊ ቢዝነስ ዘግቧል። ኬሲቢ፣ በ18 ወራት ውስጥ ከባንኩ ለመግዛት የወሰነው 40 በመቶ የአክሲዮን ድርሻ መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል።
ኬሲቢ አክሲዮን መግዛትን የመረጠው፣ በአገሪቱ የፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚው ሕዝብ 46 ነጥብ 5 በመቶ ብቻ በመሆኑና በዲጂታል ዘዴዎች አማካኝነት በቁጠባ ረገድ የሚገጥመውን ፉክክር ለማስቀረት ነው ተብሏል።
11 ክልል ዓቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ ለመተባበር ያስችለናል ያሉትን ጥምረት መስርተዋል።
በጥምረቱ ምስረታ ሂደት ከ20 በላይ ፓርቲዎች ቢሳተፉም፣ እስከፍጻሜው የዘለቁት ግን 11ዱ ብቻ ናቸው።
የጥምረቱ መስራቾች አናሳ ብሔረሰቦችን የሚወክሉ ሲሆኑ፣ ከእነዚህም መካከል የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአፋር ነጻ አውጭ ግንባር፣ የጋሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአገው ብሔራዊ ሸንጎ፣ የካፋ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና የጋምቤላ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ይገኙበታል።
ጤና ሚንስቴር፣ የውጭ ዜጎች በመንግሥት የጤና ተቋማት ለእያንዳንዱ አገልግሎት የወጣውን ተመን እጥፍ እንዲከፍሉ የሚያስገድድ መመሪያ ማውጣቱን ሪፖርተር ዘግቧል። መመሪያው፣ የዩኒቨርስቲ ሆስፒታሎች የአገልግሎት ተመኑን በየሦስት ዓመቱ እንዲከልሱ እንደሚያዝ ዘገባው ጠቅሷል።
በክልሎች የሚገኙ ሆስፒታሎች የሚያደርጉት ክለሳ ደሞ የሕዝቡን የመክፈል አቅም ታሳቢ እንዲያደርግ፣ የጤና ተቋማትን ደረጃና የሚገኙበትን ቦታ ከግምት እንዲያስገባ ያዛል ተብሏል።
የመድኃኒትና ሌሎች አላቂ የሕክምና ቁሳቁሶች ዋጋ ትመናም፣ መጓጓዣን ጨምሮ ከ25 እስከ 30 በመቶ ተጨማሪ እንደሚደረግበት ደንቡ ላይ እንደሠፈረ ዘገባው አመልክቷል።
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደገም ወረዳ ልዩ ስሙ “ኤግዱ” በተባላ ስፍራ ከአማራ ክልል ግንደወይን ከተማ ወደ አዲስ አበባ ሲያቀና ከነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ ታጣቂዎች ዛሬ ከ40 በላይ መንገደኞችን ማገታቸውንና ሹፌሩን መግደላቸውን ተሰምቷል።
ሹፌሩ ከእገታው ለማምለጥ ሲሞክር፣ አውቶብሱ ተገልብጦ በተወሰኑ ተሳፋሪዎች ላይ አካላዊ ጉዳት እንደደረሰ የዓይን እማኞች ተናግረዋል።
ከስራ መባረርን በመስጋት ከራሳቸው ኪስ እያወጡ አዲስ ቡክ የሚያስከፍቱ የባንክ ሰራተኞች ምሬታቸውን ገለፁ
“አሁን ላይ ባለው የአካውንት ክፈቱ ጥያቄ የተማረረው ማህበረሰብ አካውንት ቢከፍት እንኳን መነሻውን ብር ለመስጠት ፈቃደኛ አይደለም፣ ስለዚህ እኛ ሰራተኞች ስራችንን ከምናጣ ብለን ይህንን ብር ከኪሳችን ለመሙላት እንገደዳለን።”
መረጃ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/yp9drxtd
በተመደቡበት ሀገር በስራ ላይ እያሉ የተደባደቡት የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደሩ እና ምክትላቸው ከስራ ታገዱ
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://tinyurl.com/24sshv7d
” በህግ እንጂ በሀይል አንገዛም ! ” – የመኾኒ ከተማ ነዋሪዎች
➡️ ” ምርጫችን ሽፍቶች ህዝብ ይዘው እንዲጠፉ መፍቀድ ወይስ ለሞትና ስደት የዳረጉንን ማስወገድ ? ” አቶ ጌታቸው ረዳ
በትግራይ ደብባዊ ዞን ራያ ዓዘቦ ወረዳ መኾኒ ከተማ በታጣቂዎች መካከል በተከፈተ ቶክስ 8 ስቪሎች መቁሰላቸው ተከትሎ ቁጣ የተቀላቀለበት ስልፍ ዛሬ ተካሂደዋል።
በርካታ ወጣቶችና እናቶች የተተሳተፋበትና ፓሊስ ስርዓት ያስከበረበትን ሰልፍ የከተማው አስተዳደር እንደጠራው ነው የተሰማው።
ነዋሪዎቹ ዛሬ ከሰዓት በኃላ ባካሄዱት ቁጣ የተሞላበት ሰልፍ የትግራይ ኃይል (ቲዲኤፍ) ከከተማቸው እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ሰልፈኞቹ ፦
– በህግ እንጂ በሀይል አንገዛም !
– ሰላማዊ ሰዎች መጨፍጨፍ ይቁም !
– በሀይል የሚጫንብን አስተዳደር አንቀበልም !
– ራስን በራስ የማስተዳደር መብታችን አሳልፈን አንሰጥም !
– የሀይል አገዛዝ እንኮንናለን !
– አንድ ቡድን ስልጣን ላይ እንዲቆናጠጥ አልሞ የሚካሄድ ጭፍጨፋ አንኮንናለን !
የሚሉና ሌሎች መፈክሮች አስምተዋል።
ዛሬ ሰልፉ ተከትሎ የተፈጠረ ግጭት እንደሌለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ምንጮች አረጋግጠዋል።
ሰሞነኛውን ሁኔታ በተመለከተ የቀድሞ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ” በመኾኒ ሰላማውያን ሰዎች ላይ የተፈፀመ የአመፅ ተግባር በኔትወርክ የተደራጀው የወንጀለኞች ቡድን በትግራይ ህዝብ ላይ ሲፈፅመው የቆየውና በቀጣይ ሊያደርገው ያቀደው ተቀጥያ ነው ” ብለዋል።
” በጥቂት ለሚቆጠሩ ኃላቀሮች ተብሎ ህዝብ እንደ ህዝብ ቢያልቅ ግደ የሌለው ቡድን ዕድሜ በጨመረ ቁጥር የባሰ እልቂት ማስከተሉ አይቀሬ ነው ” ሲሉ ገልጸዋል።
” ምርጫችን ሽፍቶች ህዝብ ይዘው እንዲጠፉ
በኪንዶ ኮይሻ ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ3 ሰዎች ሕይወት አለፈ።
በወላይታ ዞን ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ በዛሬው ዕለት ቀኑን ሙሉ ከመጠን በላይ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሶስት ሰዎች ሕይወት አልፏል።
በአደጋው ሰለባ የሆኑ ሰዎች የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው የተባለ ሲሆን አደጋው ፍንጫዋ በተባለ ፏፏኔ አጠገብ ለሣር አጨዳ በሄዱበት መከሰቱ ተገልጿል።
በአደጋው ምክንያት ህይወታቸው ካለፉት መካከል የአንዲት ሴት ልጅ አስከሬን መገኘት ችሏል። ሆኖም የእናት እና የወንድ ልጅ አስክሬን ግን ባለመገኘቱ የአከባቢ ማኅበረሰብና የፀጥታ አካላት ፍለጋ ላይ ይገኛሉ።
በወረዳው በአደጋ ቀጠና ስር ያሉ ሰዎችን እንደዚህ ዓይነትና ሌሎች አደጋዎች እንዳይርስባቸው ወደ ሌላ ቦታ የማሸጋገር ሥራዎች እየተሱሩ ይገኛሉ ሲል የወረዳው ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የኢትዮጵያ መንግሥት አዲስ በተሻሻለው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ረቂቅ አዋጅ ያካተታቸውን ድንጋጌዎች ባስቸኳይ እንዲያነሳ ጠይቋል።
ተቋሙ፣ የኢትዮጵያ ፍትሕ ሚንስቴር አዋጁን የማሻሻል ሂደት በከፍተኛ ሚስጢር እንደያዘውና በማሻሻያው ዙሪያ የሚደረጉ ውይይቶች በጣም ውስን እንደኾኑ በመጥቀስም ተችቷል።
መንግሥት ማሻሻያውን እንዲተው የልማት አጋሮች ግፊት እንዲያደርጉ፣ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደራጀትና የመሰብሰብ መብት እንዲከበርና በመብት ተሟጋቾች፣ በጋዜጠኞችና በማኅበረሰብ አንቂዎች ላይ የሚወሰዱ ርምጃዎች እንዲቆሙ የጠየቀው ተቋሙ፣ የልማት አጋሮች በአገሪቱ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ የሚያደርጉትን ክትትል እንዲያጠብቁም ጥሪ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ጥያቄና የሥራ ማቆም አድማ አስተባባሪ ቡድን፣ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ከደመወዝ ጋር ብቻ የተያያዘ እንዳልኾነ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባስተላለፈው መልዕክት አስታውቋል።
የጤና ባለሙያዎች አጣዳፊ ጥያቄዎች የኾኑት የትርፍ ሰዓትና የጉዳት ክፍያና የመኖሪያ ቤት ድጎማ አኹንም ምላሽ እንደሚፈልጉ ቡድኑ ገልጧል። ቡድኑ፣ እነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ እስካላገኙ ድረስ የደመወዝ ማስተካከያው ምሉዕ ሊኾን አይችልም ብሏል።
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ለተከታታ ሶስት ቀናት ከአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ 101ኛ፣ 102ኛ፣ 103ኛ፣ 104ኛ ክ/ጦር አየር ወለድ ኮማንዶ፣ አድማ ብተና እና የሚኒሻ አባላት ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል።
በዚህ ከነሀሴ 8/2017 ዓ ም ጀምሮ እየተካሄደ ባለው አውደ ውጊያ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የአጼ ይኩኖ አምላክ፣ ሰባት ለሰባ እና ነጎድጓድ ክ/ጦር የተውጣጡ ሺ አለቃዎች በወሰዱት መብረቃዊ ጥቃት የጥላት ኃይል ሙትና ቁስለኛ ሁኗል።
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው እዝ ከነሀሴ 8 -9/2017 ዓ ም ከሌሊቱ 11:00 ጀምሮ በድንጋይ ወድማ ግንባር ስብር ሽ አለቃ ከሰባት ለሰባ፣ 4ኛ ሽ አለቃ ከአጼ ይኩኖ አምላክ ክ/ጦር፣ በጉሎ ግንባር ከሰባት ለሰባ ደመላሽ ሽ አለቃ፣ ከነጎድጓድ ክ/ጦር መብረቁ ብርገድ ጠላት ካምፕ ድረስ ዘልቀው ሲገቡ በከርካሜ ተረተር ግንባር ደግሞ የአጼ ይኩኖ አምላክ 5ኛ ሺ አለቃ ባካሄዱት ኦፕሬሽን የጥላት ሀይል ጭዳ ተደርጓል።
በእብሪት አማራን ለመጨፍጨፍ በሸዋ ክ/ሀገር መንዝ ግንባር የገባው የብረሃኑ ጁላ ቀይ ምንጣፍ ሰራዊት ከነሀሴ 8-10/2017 ዓ ም በተወሰደበት የተቀናጀ ጥቃት 2 ፓትሮል አስከሬ እና አንድ አይሱዚ ቁስለኛ ሲታቀፍ በጉሎ አካባቢ ደግሞ አንድ ፓትሮል ቁስለኛ፣ አንድ አይሱዚ ሙሉ አስከሬ ሲጭን ከ40 በላይ ቁስለኞች መሀል ሜዳ ሆስፒታል አስገብቷል።
በተጨማሪም በካራ ቆሬ ጤና ጣቢያና ትምህርት ቤት በሰፈረው የአብይ አህመድ ምስለኔ ሰራዊት ላይ የአጼ ይኩኖ አምላክ ክ/ጦር አስራት ወ/ጌስ
አብን፣ መንግሥት የውጭ አካላት በአገሪቱ ላይ በሚፈጥሩት ስጋት ዙሪያ ግልጽና ወቅታዊ መረጃ እንዲሰጥ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። አብን፣ መንግሥት ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ደኅንነት ሕዝቡ ያለውን ድጋፍ እንዲያስተባብር፣ የውስጥ ግጭቶችን በንግግር እንዲፈታና በሉዓላዊነት ላይ የሚቃጡ ስጋቶችን በጥብቅ እንዲከታተልና እንዲያጋልጥም አሳስቧል። ሕዝቡ ግድቡን ከወገንተኛ ፖለቲካ፣ ከውስጣዊ ልዩነቶች ወይም ከግጭቶች በላይ መሆኑን እንዲገነዘብም ፓርቲው አሳስቧል። አብን፣ የግብጹ ፕሬዝዳንት አል ሲሲ ግብጽ በናይል ወንዝ ላይ አለኝ የምትለውን የውሃ ድርሻ አሳልፋ እንደማትሰጥና በዓለማቀፍ ሕግ ያላትን መብት ተጠቅማ ማናቸውንም ርምጃ እንደምትወስድ ሰሞኑን የሰሙትን ማስጠንቀቂያም አውግዟል።
ኢትዮጵያ፣ ከጅቡቲ፣ ከኬንያና ሶማሌላንድ ጋር በተያዘው በጀት ዓመት በየብስ ትራንስፖርት ለመገናኘት ቁርጠኛ አቋም እንዳላት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚንስትር ደኤታ ባረኦ ሐሰን መናገራቸውን ሚንስቴሩ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።
ባረኦ ይህን ያስታወቁት፣ መቀመጫውን ናይሮቢ ያደረገው የ”አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች” የግል የትራንስፖርት ኩባንያ ባለቤቶችንና አመራሮችን ሰሞኑን በጽሕፈት ቤታቸው ባነጋገሩበት ወቅት እንደሆነ ተገልጧል።
በቅርቡ ከናይሮቢ-አዲስ አበባ የሙከራ የአውቶብስ ትራንስፖርት የጀመረው “አቢሲኒያ ላግዠሪ ኮች” ኩባንያም አስፈላጊውን ሂደት አሟልቶ እንዲቀርብ ከስምምነት ላይ እንደተተደረሰ ተገልጧል።
አብዲራህማን መሃዲ የሚመሩት የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) አንጃ፣ የሶማሌ ክልል ጸጥታ ኃይሎች ጅግጅጋ ውስጥ ሴቶችን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላቱን ሐሙስ፣ ነሃሴ 8፣ 2017 ዓ፣ም እየደበደቡ በመውሰድ አስረዋል በማለት ከሷል።
አንጃው፣ ጸጥታ ኃይሎች በበርካታ አካባቢዎች ቢሮዎቹን በኃይል ሰብረው መግባታቸውንም ገልጧል። አንጃው፣ የክልሉ ፕሬዝዳንት ሙስጠፋ ኡመር ሰላማዊ ፖለቲካ ለማካሄድ የሚያስችለውን የመጨረሻውን በር ጥርቅም አድርገው ዘግተውታል በማለት ከሷል።
ሙስጠፋን በሶማሌ ሕዝብ ላይ በመጫን የሰላም ስምምነት ከንቱ ሆኖ እንዲቀር ያደረጉት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ናቸው በማለትም አንጃው ወቅሷል።
ይሄው የኦብነግ) አንጃ፣ የሶማሌ ክልል የተወሰኑ የአገር ሽማግሌዎች ዛሬ ሙስጠፋ ስብሰባ ላይ በነበሩበት የአዲስ አበባው ስካይ ሆቴል ፊት ለፊት ተቃውሞ ማሠማታቸውንም ገልጧል።
እ.ኤ.አ. የ2024 የሀገር ውስጥ የሰብአዊ መብት ተግባራት ሪፖርቶች፡ ኢትዮጵያ
EXECUTIVE SUMMARY
Section 1. Life
a. Extrajudicial Killings
b. Coercion in Population Control
c. War Crimes, Crimes against Humanity, and Evidence of Acts that May Constitute Genocide, or Conflict-Related Abuses
Section 2. Liberty
a. Freedom of the Press
Physical Attacks, Imprisonment, and Pressure
Censorship by Governments, Military, Intelligence, or Police Forces, Criminal Groups, or Armed Extremist or Rebel Groups
b. Worker Rights
Freedom of Association and Collective Bargaining
Forced or Compulsory Labor
Acceptable Work Conditions
c. Disappearance and Abduction
Disappearance
Prolonged Detention without Charges
d. Violations in Religious Freedom
e. Trafficking in Persons
Section 3. Security of the Person
በፈረንሳይ ይገኛሉ የተባሉ ሁለት ጋዜጠኞች ለኢትዮጵያ ተላልፈው እንዲሰጡ በመንግስት ጥያቄ ቀርቦ እንደነበር ታወቀ
=================================
(መሠረት ሚድያ)- በቅርብ አመታት በርካታ ጋዜጠኞች ለደህንነታቸው በመስጋት በተለያየ መንገድ ወደተለያዩ ሀገራት ከሀገር መውጣታቸው ይታወቃል።
ይህን ተከትሎ መንግስት በቅርብ ሳምንታት እና ወራት እነዚህ ጋዜጠኞች ከተቻለ ተላልፈው እንዲሰጡት፣ ካልሆነም ያሉበት ሀገራት መንግስታት ዝም እንዲያስብሏቸው እንቅስቃሴ ጀምሮ እንደነበር ለመሠረት ሚድያ የደረሰ መረጃ ይጠቁማል።
ከነዚህ ጥረቶች መሀል በኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ጅቡቲ፣ ደቡብ አፍሪካ እና በአንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት የሚገኙ ጋዜጠኞች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር የመንግስት ምንጮቻችን ተናግረዋል።
ከዚህ መሀል በፈረንሳይ ሀገር ይገኛሉ የተባሉ ሁለት የኢትዮ ፎረም ጋዜጠኞች ላይ መንግስት ትኩረት አድርጎ እንደነበር ታውቋል።
በመንግስት ስራ ዙርያ ተከታታይ መረጃዎችን በማውጣት እና የሰላ ትችት በመስጠት የሚታወቀው የኢትዮ ፎረም ጋዜጠኞች ያየሰው ሽመልስ እና አበበ ባዩ የትኩረቱ ኢላማ እንደነበሩም ምንጫችን ተናግረዋል።
“ሁለቱ ጋዜጠኞች የሚሰሯቸው ዘገባዎች በመንግስት ዘንድ የራስ ምታት ሆነዋል፣ በዚህም ምክንያት በቅርቡ በጠ/ሚር አብይ አህመድ የተመራ የልዑክ ቡድን ፈረንሳይን በጎበኘበት ወቅት ሚድያው ትኩረት አግኝቶ ነበር” ያሉት እኚህ የመንግስት መረጃ ምንጫችን ናቸው።
በዚህ ግንቦት 14/2017 ዓ.ም በተደረገ ኦፊሴላዊ ጉብኝት ወቅት ከተቻለ ሁለቱ ጋዜጠኞች ተላልፈው እንዲሰጡ፣ ካልሆነም ዝም እንዲሉ እንዲደረጉ በልዑክ ቡድኑ ለፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን በቀጥታ ጥያቄ ቀርቦ የነበረ ቢሆንም ጥያቄው ተቀባይነት እንዳጣ ታውቋል።
“ተላልፎ መስጠት የሚለው እንደማይሆን ቀድሞ የታሰበበት ይመስላል፣ ነገር ግን ጋዜጠኞቹን በዚህ ንግግር መሀል ስራቸውን ማስቆም እንዲቻል ጥያቄ ቀርቦ ነበር። አልተሳካም” በማለት የነበረውን
የኤርትራው መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገብረመስቀል፣ የኢትዮጵያው ብልጽግና ፓርቲ ደጋፊችና ተሳዳቢዎች፣ በኤርትራ ላይ በየቀኑ “የስድብ መዓት በማውረድ” እና “የስም ማጥፋት ዘመቻ” በማካሄድ ተጠምደዋል በማለት ወቅሰዋል።
ኤርትራ የኢትዮጵያን ልማት ስታስተጓጉል ቆይታለች የሚል “የስም ማጥፋት” እየቀረበባት እንደሆነ የጠቀሱት የማነ፣ ሆኖም ኤርትራ የቀጠናው አገራት እድገትና ብልጽግና ቢያስመዘግቡ ለቀጠናው ሕዝቦች ጠቃሚ ይሆናል የሚል እምነት እንዳላት ገልጸዋል።
የማነ፣ የዜሮ ድምር ስሌት የኤርትራ የቀጠናዊ ፖሊሲና የልማት ስሌት አካል እንዳልኾነም ጠቅሰዋል።
“ድብቅ ዓላማን ለማራመድ” ሲባል፣ እነዚህን መሠረታዊ ሃቆች በሐሰት ትርክት ማጥፋት አይቻልም በማለትም የማነ መልዕክታቸውን ቋጭተዋል።
የአብይ ሠራዊት ሰሞኑን በምሥራቅ ወለጋ ዞን በጊዳ አያና እና ኪረሙ ወረዳዎች ከአማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊትና ከአማራ ክልል ድንበር ተሻግረው ከሚመጡ ታጣቂዎች ጋር ውጊያዎችን እያደረገ መኾኑን የአካባቢውተሰምቷል።
በተለይ በኪረሙ ወረዳ “በዴሳ”፣ “ሲሬ ዶሮ”፣ “ባጊን” እንዲሁም “ኦፍጪ” ከተባሉ ኦሮሚያ ክልል ከአማራ ክልል ጋር በሚዋሰንባቸው ቀበሌዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች ከአማራ ክልል ድንበር ተሻግረው የሚመጡ ታጣቂዎች በሚያደርስባቸው ተደጋጋሚ ጥቃት ሳቢያ ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው ታውቋል።
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ጊዳ ከተማ፣ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ዛሬ በፈጸመው ጥቃት ከ150 በላይ ታራሚዎችን ማስመለጡ ተሰምቷል ።
አብዛኞቹ ታራሚዎች፣ በአካባቢው ጥቃት ሲፈጽሙ የነበሩ ታጣቂዎች መኾናቸውን ምንጮች ነግረውናል።
ኹሉም ሊባል በሚችል ደረጃ ከእስር ቤቱ አምልጠዋል በማለት ነግረውናል።
ቡድኑ፣ በርካታ ክላሽንኮቭ ዘርፎ መውሰዱንም ምንጮች ገልጸዋል።
ይህንኑ ተከትሎ፣ ያመለጡ እስረኞችን ፍለጋ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች አሰሳ መጀመራቸውንና ባካባቢው ከፍተኛ ውጥረት መስፈኑን ምንጮች ጠቁመዋል።
የውጭ ምንዛሪ እጥረት ጉዳይ በኢትዮጵያ ለረዥም ጊዜ የኢኮኖሚ ችግር ሆኖ መቆየቱ ይነገራል፡፡ ‹‹ዶላር ናረ፣ ብላክ አሻቀበ፣ ባንክ ስንት ገባ?›› የሚሉ ሐረጎች ከብዙዎች አፍ የማይጠፉ የወሬ መጀመሪያ ርዕሶች ከሆኑ ከራርመዋል፡፡ ይህ ሁሉ የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እጅግ ሥር የሰደደ ችግር ሆኖ መዝለቁን የሚጠቁም ነው፡፡ የዶላር የመደበኛ/የባንኮች ዋጋና የጥቁር ገበያ ዋጋ ልዩነት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴና በገበያ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳዳሪ መሆኑም በሰፊው ሲነገር ቆይቷል፡፡
የውጭ ምንዛሪ አቅርቦትን ለማሳደግ በመንግሥት ብዙ የፖሊሲ ዕርምጃዎች ቢወሰዱም፣ ነገር ግን በዚህ ረገድ ችግሩ እስካሁንም የተቀረፈ አይመስልም፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በውጭ ምንዛሪ ድርቅ የሚጠቃው በብዙ መነሻ ምክንያቶች እንደሆነ ይነገራል፡፡ አንዳንድ ወገኖች የመንግሥትን የኢኮኖሚ ጣልቃ ገብነት በምክንያትነት ሲያነሱ፣ ሌሎች የፋይናንስ ገበያ ሥርዓቱን ለዚህ ተጠያቂ ያደርጋሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ዋና ምንጩ የወጪና ገቢ ንግድ ገቢ አለመመጣጠን መሆኑን ነው የሚናገሩት፡፡ ከዚህ የተለየ ሐሳብ የሚያቀርቡ ወገኖች ደግሞ የፋይናንስ ሥርዓቱ የተጋፈጣቸው የገበያ አሻጥሮችን፣ ኢመደበኛ፣ እንዲሁም ሕገወጥ ንግዶችን በመዘርዘር ችግሩ የዚህ ውጤት እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡ የሐዋላ ወይም ሬሚታንስ ገቢ፣ ዕርዳታና ብድር ግኝት መጨመር ጉዳዮች ጭምር ከዚሁ የምንዛሪ ድርቅ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ነጥቦች ሲሆኑም ይታያል፡፡
የውጭ ምንዛሪ እጥረት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ችግር ብቻ ነው ተብሎ አይታመንም፡፡ ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ ያለው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ለረዥም ዓመታት በመቆየቱና ሊፈታ ያልቻለ ችግር በመሆኑ ከሌሎች አገሮች እንደሚለይ ብዙዎች ይናገራሉ፡፡ ሌላው ቀርቶ ችግሩ ከቅርብ የጎረቤት አገሮች ጋርም ተነፃፃሪ አለመሆኑን ነው
ዩኒቨርሲቲዎች ብቁ ተማሪ ከማውጣት፣ ጥናት ከማካሄድ፣ የምርምር ሥራዎችን ከማድረግ ይልቅ የመንግሥት የፖለቲካ መሣሪያ ሆነው በማገልገል ላይ ናቸው ሲሉ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ገለጹ፡፡
ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ይህንን የተናገሩት ሐምሌ 28 እና 29 ቀን 2017 ዓ.ም. ‹‹ከፍተኛ ትምህርት ለላቀ ተፅዕኖ›› በሚል መሪ ሐሳብ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ጉባዔ ማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ ነው፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) እንደገለጹት፣ ‹‹ዩኒቨርሲቲዎች ብቃት ያላቸው መምህራንና ተማሪዎችን ከመፍጠርና ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የምርምር ሥራዎችን ከማከናወን ይልቅ የፖለቲካ መድረኮች ሆነዋል፤›› ብለዋል፡፡
‹‹ኅብረተሰቡ ጥሩ ፖለቲከኛ እንዲኖሩት እንደሚፈልግ ሁሉ፣ ለአገራቸው የሚቆረቆሩና አርቀው የሚያስቡ ምሁራንንም ይሻል፡፡ ከዩኒቨርሲቲዎች የምንጠብቀውም ይህንኑ ነው፤›› ያሉት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ ዩኒቨርሲቲዎች መጪውን ትውልድ ከመቅረፅና ከመፍጠር ባሻገር የሐሳብ መሪዎች መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ፖለቲከኞች ምሁራን የሚያነሷቸውን ሐሳቦች ተከትለው አገር መምራት ሲኖርባቸው፣ አሁን ግን ቦታው በመለዋወጥ በተቃራኒው በሐሳብ እየመሩ የሚገኙት ፖለቲከኞች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች የሰላም ቦታ መሆን አለባቸው፡፡ ምሁራኑም ያለ ምንም ፍርኃትና ጭንቀት እውነትን መያዝና ዕውቀትን በመደገፍ መሥራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ አገርም የምትሻው፣ እኛም የምንፈልገው ተቋማቱ የመንግሥት መሣሪያ ሆኖ ከማገልገል ነፃ እንዲሆኑ ነው ብለዋል፡፡
‹‹እዚህ አገር ዩኒቨርሲቲዎች ሙስና የሚሠራባቸውና ሙስና የሚነገርባቸው ሆነዋል፡፡ በሚዲያ አካባቢዎችና በኅብረተሰቡ ዘንድ ከኦዲት ሪፖርት ጋር በተያያዘ የዩኒቨርሲቲዎች ስም በስርቆት የሚነሳ ነው፤›› ያሉት ሚኒስትሩ፣ አሁን ላይ ዩኒቨርሲቲዎች እየታወቁና እየተለኩ የሚገኙት ከተልዕኳቸውና ከተቋቋሙለት ዓላማ ውጪ በሚሠሩት ሥራ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የዩኒቨርሲቲ አመራሮችንና ምሁራንን የሚጎዳ፣
የትግራይ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ በትግራይና አፋር ክልሎች አዋሳኝ የሚንቀሳቀሰው የትግራይ አፈንጋጭ ታጣቂ ቡድን ዛሬ በክልሉ ጸጥታ ኃይሎች ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት አድርሷል በማለት ባወጣው መግለጫ ከሷል።
ቢሮው፣ ታጣቂ ቡድኑ “ጠብጣብ” በተባለ ቦታ ላይ አደረሰው ባለው ጥቃት የአንድ የክልሉ ጸጥታ ኃይል አባል ሕይወት መጥፋቱን ገልጧል።
ይህ አጥፊ ተግባር ከቀጠለ ቡድኑን በሚመሩና በሚያስተባብሩ አካላት ላይ ርምጃ እወስዳለሁ በማለት ያስጠነቀቀው ቢሮው፣ ደም መፋሰሱ ባስቸኳይ ይቁም በማለት ጥሪ አድርጓል።