Home › View all posts by Konjit Sitotaw
Blog Archives
የፌዴራል ዋና ኦዲተር የተሟላ አስተዳደራዊና የፋይናንስ ነፃነት እንደሌለው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥናት አመለከተ
ኦዲተሩ በሚያጋልጣቸው የፋይናንስና የሕግ ጥሰቶች ላይ ተጠያቂነት አልተረጋገጠም ብሏል ኦዲተሩን የሚቆጣጠረው የፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ ገለልተኛ አለመሆኑ ተጠቅሷል የፌዴራል ዋና ኦዲተር በመንግሥት ጣልቃ ገብነት የተነሳ አስተዳደራዊ ነፃነቱ መገደቡንና የፋይናንስ ነፃነቱም የተጓደለ መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥናት አመለከተ። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ከ2001 እስከ 2015 ዓ.ም. ባካሄዳቸው የፋይናንስና የሥራ አፈጻጸም ኦዲትና ግኝቶቹን መነሻ… https://ethiopianreporter.com/147032/
“የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
የቅዱስነታቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ መልእክት ከዚህ እንደሚከተለው ይቀርባል።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
• ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
• ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ቅዱስ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፤
የጎደለብንን እየሞላ አገልግሎታችንን እያቃና ከዚህ ላደረሰን፣ ይህንን ዓመታዊና ሐዋርያዊ ጉባኤያችንን ለማካሄድም ለሰበሰበን ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቀርባለን፡፡
“ወእፌጽም ታሕጻጸ ሕማሙ ለክርስቶስ በሥጋየ በእንተ ሥጋሁ እንተ ይእቲ ቤተ ክርስቲያኑ፡- ስለ አካሉ ማለትም ስለ ቤተክርስቲያኑ ስል በሥጋዬ በክርስቶስ መከራ የጎደለውን እፈጽማለሁ” (ቈላ.፩÷፳፬)
ያለንበት ዓለም በሁሉም ነገር በጉድለቱ የሚታወቅ ነው፤ ጉድለት ባይኖርና ሁሉም የሞላለት ቢሆን ኖሮ ፍጥረት እርስ በርስ የሚተረማመስበት ሁኔታ አይኖርም ነበር ወይም አሁን ባለበት ደረጃ የከፋ አይሆንም ነበር፡፡
እግዚአብሔር ሁሉንም አሟልቶ መፍጠር ወይም መስጠት የሚችል ከሃሊ አምላክ ቢሆንም፣ እሱ ባወቀ ፍጥረትን ሁሉ ጉድለት ያለበት አድርጎ ፈጥሮታል፤ በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ጉድለቱን ለመሙላት በሚያደርገው ፍትጊያ እየተጋጨ እርስ በርስ ሲተረማመስ ማየቱ የተለመደ ነው፡፡ ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያንም በጐዶሎው ዓለም እስካለች ድረስ ከሚመጣው ፈተና አታመልጥም፤ ይህም በመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ ለቈላስይስ ሰዎች “የጎደለውን እፈጽማለሁ” በማለት ሲጽፍ እናስተውላለን፡፡
• ብፁዓን አበው
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ‘ፅንፈኛ’ የተባሉ ታጣቂዎች ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ንጹሃንን ገደሉ፡፡
DW : የንጹሃን ግድያ ተደጋግሞ በተሰማበት በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ እሁድ ምሽት በግምት ሁለት ሰዓት ግድም የታጠቁ አካላት ባደረሱት ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች ወዲያው መገደላቸውን ተጎጂዎች እና የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡
ጥቃቱ ከትናንት በስቲያ እሁድ ጥቅምት 09 ቀን 2018 ዓ.ም. ማምሻውን አገር ሰላም ብለው እንደወትሮው ወደ ቤታቸው በገቡ ንጹሃን የኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ ነው የተወሰደው ያሉት አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ አንድ የአከባቢው ነዋሪ፤ በአጎራባች የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ወረዳዎች የሚንቀሳቀሱ ያሏቸው ታጣቂዎቹ ወሰን ተሻግረው ባደረሱት ጥቃት የአከባቢው ሰላማዊ ዜጎች ላይ ዘግናኝ ያሉትን ግድያ መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡ “ጥቃቱን ያደረሱት በአከባቢው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ የተባሉ ታጣቂዎች ናቸው” ያሉት አስተያየት ሰጪው፤ በእሁድ ምሽቱ ድንገተኛ ጥቃት 22 ሰዎች ወዲያው መገደላቸውን አመልክተዋል፡፡ በኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዳርጌ በሚባል ስፍራ እሁድ ምሽት ከአንድ እስከ ሁለት ሰዓት ግድም በተወሰደው በዚህ ጥቃት ህጻናት እና ሴቶች በስፋት ተጠቂ መሆናቸውን አስረድተዋልም፡፡
ቤተሰቦቻቸው የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን የነገሩን ነገር ግን አለብን ባሉት የደህንነት ስጋት ስማቸውን ከመግለጽ የተቆጠቡት ሌላው የአከባቢው ነዋሪ፤ “ሰላማዊ ዜጎችን በጭለማ ገብተው ነው የፈጁዋቸው፡፡ አሁን በእሁድ ምሽቱ በዚህ ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 29 ደርሰዋል፡፡ 22 ሰዎች ወዲያው መገደላቸው ሲረጋገጥ ቀሪዎቹ አስከሬናቸው በየጥሻው የወደቁና በሆስፒታል ህይወታቸው ያለፉ ናቸው” ብለዋል፡፡ የተገደሉትን ለመለየት ትናንት እስከ
በአፋር ክልል ገዋኔ ወረዳ ትናንት ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለ 8 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ያሉና የመንግስት ሰራተኞች የመጠጥ ውኃ በአግባቡ እየቀረበ አይደለም የሚሉ የወረዳው ነዋሪዎች የኢትዮጵያ ጅቡቲን አውራ ጎዳና መንገድ ለሰዓታትበመዝጋት ተቃውሟቸውን ማሰማታቸው ተነገረ፡፡ ለተቃውሞወደ አደባባይ የወጡ የገዋኔ ነዋሪዎች እንደገለፁት በወረዳውየሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች በተገቢው መንገድ ደመወዝ እየደረሰን አይደለም ይላሉ፡፡ ‹‹ደመወዝ ከነጭማሪው ወደ 8 ወራት አልተከፈለንም፡፡ በ2017 ዓ.ም ግማሽ አለ፡፡ ከ2018 ዓ.ም ያልተከፈለ የደመወዝ ጉዳዩን ማን ይስማ፡፡›› ተጨማሪ https://www.dw.com/am/
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ (የኀዘን መግለጫ)
=====
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡።
++++
“አድኅነኒ እግዚኦ እስመ ኀልቀ ኄር። አቤቱ፥ አድነኝ፥ ደግ ሰው አልቋልና።” (መዝ. 11፥1)

እግዚአብሔር በየዘመናቱ አገርን ያለ መካሪ፣ ሕዝብን ያለዘካሪ አይተወውም! ለዚህም ምስክሩ ታላቅ አረጋዊ፣ የበሳል አእምሮ ባለቤት፣ አገርን የሚወዱ፣ ሕዝባቸውን የሚያከብሩ፣ የተጠቁት ወዳጅ፣ የትውልድ አባት የሆኑት የክብር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ነበሩ፡፡
ኢትዮጵያ በጣት ከሚቆጠሩ አረጋውያን፣ አፈ ማር ከሆኑ መካሪዎችዋ መካከል አንዱ የሆኑትን፣ ለመወደድ የታደሉትን የዘመናችን ጌጥ አጥታለች። ይህንን የድካም ዓለም መገላገል ለእርሳቸው ዕረፍት ቢሆንም ለአገር ግን ታላቅ ጉዳት ከመሆኑም በላይ ዕድሜን ከጥበብ ጋር ያዋሐዱ በሁሉ ዘመን አይገኙምና ኀዘናችን ጥልቅ ነው።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን እንመኛለን፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
አሜን።
የልጅ እያሱ ኮር አሃዶች በጥምረት በርካታ የጠላት ሃይል በመደምሰስ ከ30 በላይ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት እና 45 ክላሽ በመማረክ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::
የልጅ እያሱ ኮር ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 11:00 እስከ ቀኑ 5:00 ሰዓት በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ በውርጌሳ አካባቢ አምባሰል ወረዳ ውጫሌ ጨፌ አና ወርቃረያ እስከ ኩታ በር ወረዳ ተጋድሎ በማድረግ ታላቅ ድል አስመዘገበ::
በዚህ የውጊያ ግንባር በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ውርጌሳ እና አካባቢው በራስ አሊ ክፍለ ጦር ስር የምትገኘው አራተኛ ሻለቃ እና በራምቦ ክፍለ ጦር ስር የሚገኙት ሻለቃ አንድ እና ሻለቃ ሁለት በመሆን በውርጌሳ እና አካባቢው ያሉትን ተራሮች ተብትቦ ይዞ የነበረውን የ11ኛ እዝ አካላት ላይ በተደረገ የማጥቃት እርምጃ ገሚሱ ሲገደል ገሚሱ ደግሞ እጅ ሰጥቷል።
የአካባቢው ነዋሪ አንዳሉት በተደረገው ውጊያ መከላከያ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እንደደረሰበት የአይን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
በዚህ ግንባር ብቻ የሞተ የጥላት ወታደር በርካታ ሲሆን ምርኮኛ 30 የተማረከ ክላሽ ብዛት 45 የወገብ ትጥቅ 42 ቦንብ 74 የብሬን ተተኳሽ 1417 የክላሽ ተተኳሽ 3375 የመገናኛ ሬድዮ 1 የዝናብ ልብስ/Rain coat/ 27 በመማረክ ውጊያው ተቋጭቷል።
ሁለተኛው ግንባር ውጫሌ ከተማ ላይ የነበረ ሲሆን የአምባሰል ወረዳ ዋና መቀመጫ የሆነችው ውጫሌ ላይ ወፍ ሲበር ጭምር ሲደነብር ውሎ የሚያድረው እና ከተማውን ለመያዝ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ በልጅ እያሱ ኮር አመራሩን የተነጠቀው ዝክንትል ወታደር ነፍስ ግቢ ነፍስ ውጭ አይነት ውሎ እንደዋለ እና ብዙ የሰራዊቱ አባል በፋኖ
ለአገር ዕድገት የማይበጁ ተግዳሮቶች ይወገዱ!
October 19, 2025
ለአገር ልማትና ዕድገት አንዳችም አስተዋፅኦ ሳይኖራቸው ከፍተኛ መጠን ያለው ጥፋት የሚያደርሱ፣ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ የሚያስከትሉ፣ ከብሩህ ተስፋ ይልቅ ለጨለምተኝነት የሚዳርጉ፣ የሥራ ሞራልንና ተነሳሽነትን የሚያላሽቁ፣… https://ethiopianreporter.com/146939/
ኢትዮጵያ የዩሮ ቦንድ ዕዳዋን መልሶ ለማዋቀር ያደረገችው ድርድር መክሸፍና መዘዞቹ
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. 2014 ዓ.ም. ከዓለም አቀፍ ገበያ በዩሮ ቦንድ አንድ ቢሊየን ዩሮን ለመበደር የበቃችው የአገሮችን ብድር የመክፈል አቅም የሚለኩት እንደ ፊች፣ ፑር እና ሙዲ… https://ethiopianreporter.com/146906/
” የኑሮ ሁኔታ በጣም ከባድ ነው የሚከፈለን ብር 760 ነው፡፡ … እኛ ሴቶች እንጨት ለቅመን ነው የምንማረው ወንዶችም እንጨት እየለቀሙ እየጋገሩ ይማራሉ ” – የመምህራን ማሰልጠኛ ተማሪዎች
ከ40 አመት በላይ መምህራንን በማሰልጠን የሚታወቀዉ የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ በመምህርነት በዲግሪና ዲፕሎማ የሚሰለጥኑ ተማሪዎች በወር ለምግብ የሚሰጣቸዉ 760 ብር ለመኖር ስላላስቻላቸዉ ሰዉ ቤት ተቀጥረዉ በቤት ሰራተኝነት ከጫካ ጭራሮ እየለቀሙ የራሳቸውን ምግብ ለማብሰል መገደዳቸውን ገልጸዋል።
ከእነዚህ ተማሪዎች አንዱ በእንጨት ለቀማ ወቅት ሕይወቱ እንዳለፈም ሰልጣኞቹ ተናግረዋል።
በወር የሚከፈላቸው 760 ብር ነው ፤ አንድ እንጀራ ለመግዛት የዋጋውን ውድነት አልቻሉትም ከዚህ ኑሮ ውድነት በመነሳት ወንዶች ኩሽና ተፈቅዶላቸው እንጀራ እየጋገሩ እየኖሩ ናቸው።
ነገ ተማሪዎችን ለማስተማር የሚሰለጥኑ መምህራን የሚማሩትን ሳይሆን የሚበሉትን በማሰብ የማገዶ እንጨት በመልቀም፣ የቀን የጉልበት ሠራተኛ በመሆን፣ እንዲሁም ሊጥ አብኩተው ለምግባቸው የሚሆን እንጀራ በመጋገር ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ ነው የተባለው።
ሰልጣኝ መምህራኑ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ምን አሉ ?
በ760 ብር የምግብ ወርሃዊ ክፍያ የመኖሪያ ቤት ተሰጥቷቸው በኮሌጅ የሚማሩ ተማሪዎች ከትምህርት በኋላ የሚመገቡትን ምግብ ለማብሰል በደሴ ወደሚገኙት የጦሳ፣ አዘዋና ሌሎች እንጨት ለመልቀም ወደሚያስችላቸው ጫካዎች ሲያመሩ ከሞት ጋርም ተጋፍጠዋል፡፡
ለመማር በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ በጦሳ ተራራ እንደዚሁም በአዘዋ ተራራ ካለቀምን በስተቀር እንጨት አይገኝም ብለዋል።
በዚህም አንድ ሳሙኤል የተባለ የእንግሊዝኛ ክፍል የዲግሪ ተማሪ በጦሳ ተራራ እንጨት ሊለቅም ሄዶ ህዳር 28 ቀን ህይወቱ አልፏል፡፡
ችግሩ በተለይ ሴቶች ላይ የጎላ ነው የምትለው ሠልጣኝ ተማሪ
እናት ፓርቲ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣሪያና ግድግዳ ግብር መመሪያ ተግባራዊ እንዳይኾን የጣለውን እገዳ የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሠሚ ችሎት ትናንት እንደሻረው አስታውቋል። ይግባኝ ሠሚ ችሎቱ፣ ከሳሽ ተከራይ እንጂ ቤትም ኾነ ቦታ እንደሌለው፤ በጉዳዩ ላይ መብትም ኾነ ጥቅም እንዲኹም በፍርድ ቤት እንዲከራከር የወከለው አካል እንደሌለ ገልጦ፣ የሥር ፍርድ ቤት ኹለቱን ወገኖች ማከራከር አልነበረበትም በማለት መወሰኑን ፓርቲው ገልጧል። እናት ፓርቲ በ2015 ዓ፣ም የወጣው መመሪያ ሕገወጥ መኾኑን ጠቅሶ በአስተዳደሩ ላይ በመሠረተው ክስ መሠረት፣ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት መመሪያው ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም በማለት በጥር 2017 ዓ፣ም መወሠኑ ይታወሳል።
” ወጣቶቹ ያለ ፍርድቤት ትዕዛዝ ታስረዋል፤ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸውም ተደርጓል ” – ቤተሰቦችና ነዋሪዎች
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ኮቾሬ ወረዳ ፍሰሃ ገነት ተብሎ የሚጠራዉ አከባቢ ነዋሪዎች እና ” ልጆቻችን ያለ አግባብ ታስረዋል ” የሚሉት ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
በአከባቢዉ ማህበረሰብ በተደጋጋሚ ሲጠየቅ የቆየዉን የፍሰሃ ገነት የወረዳ መዋቅርነት ጥያቄ ” በማህበራዊ ሚዲያዎች አሰራጭታችኋል ” በሚል ወጣቶችን እያሰሱ እያሰሩ ነው ሲሉ ነው ቃላቸውን የሰጡት።
” ስድስት ወጣቶች ያለ ፍ/ቤት ትዕዛዝ ታስረዋል ” የሚሉት ነዋሪዎቹ የፍሰሃ ገነት ወረዳ በቀደመዉ ጊዜ የወረዳ መዋቅር የነበረዉ መሆኑንና የመዋቅር ጥያቄዉ የሕብረተሰቡ በመሆኑ እነዚህም ወጣቶች ይህንኑ ሃሳባቸዉን በማህበራዊ ሚዲያ በማሰራጨታቸው ብቻ ከስራና የትምህርት ገበታቸው እየታሰሱ መታሰራቸውንና ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸዉ መደረጉን ገልጸዋል።
” ፖሊስ ልጆቻችንን እንዳናገኝ ከማድረጉም በላይ ‘ በተባባሪነት አስራችኋለዉ ‘ እያለ እያስፈራራን ነዉ ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩት የአከባቢው ወጣቶች ” እኛም እየተፈለግን በመሆኑ አከባቢያችንን ለቀን ሸሽተናል ” ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጌዴኦ ዞንና የኮቾሬ ወረዳ ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ፈቃደኛ ባለመሆናቸዉ የኮቾሬ ወረዳ አዛዥ ደግሞ ስልካቸዉ ባለመስራቱ ለጊዜው አልተሳካም።
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረመስቀል፣ የኢትዮጵያው ብልጽግና ፓርቲ “አንቂዎች” እና “ተንታኞች”፣ የኤርትራ የነጻነት ትግል በውጭ ኃይሎች “ቀስቃሽነት” እና “ድጋፍ ሠጪነት” የተካሄደ እንደኾነ በመግለጽ ላይ ይገኛሉ በማለት ዛሬ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሠፈሩት መልዕክት ከሠዋል። “የትናንት ታሪክ በውሸት ብዛት ሊፋቅ አይችልም” ያሉት የማነ፣ ኤርትራ በልጆቿ መስዕዋትነት ነጻነቷን ያገኘችው በየተራ በአሜሪካ እና በሶቪዬት ኅብረት ይደገፍ ከነበረ መንግሥት ጋር ተዋግታ ነው ብለዋል። ሌላው ቢቀር፣ በኤርትራ ላይ አስከፊ ግፍ የፈጸሙ ኃይሎች “ለታሪካዊ ወንጀሎቻቸው ይቅርታ መጠየቅ እንጂ በኤርትራ ቁስል ላይ ጨው መነስነስ አልነበረባቸውም” በማለት የማነ ወቅሰዋል።
የ19 ዓመቷ ፋኒት በዓለም ዋሴ የግፍ ግድያ የጦር ወንጀል ነው፤
መንግስት መሆን ያቃተው ብልጽግና የአማጽነት ወግም እርቆታል፤ Yared Hailemariam
++++

በአለም አቀፍ የሰብአዊነት ህግ (International Humanitarian Law) ወይም the laws of armed conflict እና የGeneva Convention በመባል በሚታወቁት አለም አቀፍ ሕጎች የጦርነትን ሁኔታና በጦርነት ወቅት ቆስለው ወይም ሳይቆስሉ የሚማረኩ የተቀናቃኝ ጦር አባላትን አያያዝ የሚደነግጉ አንቀጾች አሉ፡፡ በእነዚህ ድንጋጌዎች መሠረት Hors de combat (out of the fight) የሚባሉት ከተፋላሚዎቹ ሃይሎች መካከል በጦርነቱ ጉዳት ደርሶባቸው የቆሰሉና የተማረኩ፣ በሕመም ላይ የሚገኙ ወይም እጅ ሰጥተው በተቀናቃኝ ጦር የተማረኩ ሰዎች እና Prisoners of war (POWs) የጦር እስረኞች ምን አይነት የሕግ ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባና ጥበቃ ማድረግ በሚገባቸው አካላት ላይ ስለተጣለው ሃላፊነት እነዚህ ህጎች በዝርዝር ይደነግጋሉ፡፡ በጉዳት ምክንያት ወይም በምርኮ የተያዘ ሰው ተገቢው ህክምና እና ጥበቃ ተደርጎላቸው ሰብአዊነት በተሞላው አያያዝ እንዲቆዩ መደረግ እንዳለበት ይደነግጋሉ፡፡ ይህን መጣስ እንደ ጦር ወንጀል እንደሚቆጠርም እነዚህ ሕጎች ይገልጻሉ፡፡
ከእነዚህ መሠረታዊና ቁልፍ ከሆኑ የጦርነት መርሆዎች በእንግሊዘኛው ፤
1ኛ/ IHL prohibits the use of unnecessary force and weapons that cause unnecessary suffering. This includes prohibiting torture, cruel treatment, and the use of excessive force. (የአለም አቀፉ የሰብአዊነት ሕግ አላስፈላጊ እና ያልተመጣጠነ ሃይል እና መሳሪያ በመጠቀም በተማረኩ፣ ቆስለው በተያዙና የጦር እስረኛ በሆኑ ሰዎች ላይ መጠቀም፣ የማሰቃየት ወይም ጭካኔ የተሞላው አያያዝ መፈጸም የተከለከለ መሆኑን ይደነግጋል)
2ኛ/
የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር በዓመት ውስጥ እስከ 15 ሺሕ ጨምሯል።
አማኑኤል የአዕምሮ ህሙማን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆስፒታሉ የሚስተናገዱ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር በዓመት ውስጥ እስከ 15 ሺሕ መጨመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ይህን ያሉን፣ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር እየጨመረ ወይስ እየቀነሰ ነው ? ግጭትና ጦርነት የህሙማኑን ቁጥር ለመጨመር ገፊ መንስኤ አልሆነም ? ስንል የጠየቅናቸው የአዕምሮ ሐኪምና የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ክብሮም ኃይሌ ናቸው።
ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?
” የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ግጭት፣ ድርቅ፣ ጦርነትና መፈናቀሎች በተደጋጋሚ አጋጥመዋል። እነዚህ ክስተቶች የአዕምሮ ጤና ችግርን እንደሚጨምሩ የሚያሻማ አይደለም።
ካለፈው ዓመት መጠነኛ ጭማሪ አለው፡፡ የ2017 እስከ ሰኔ ያለው ከ130 ሺሕ ትንሽ ከፍ ይላል፤ በዚያኛው ዓመት ካየነው 10 ሺሕ፣ 15 ሺሕ ጭማሪ አለው።
ስለዚህ የመጨመር ሁኔታዎች አሉ፤ እንደሚጨምርም ይታወቃል፡፡ ግን ሁሉም (ታማሚ) አይመጣም፡፡ ስለዚህ የሆስፒታሉ ዳታ ማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ላያሳይ ይችላል። ስለዚህ እኛ ጋር ያለው የታካሚ ቁጥር መጨመር አለመጨመሩ የችግሩን መኖር አለመኖሩን (ሙሉ በሙሉ) አያሳይም።
የአማኑኤል ሆስፒታል የህሙማን ፍሰትን የሚያግዱ የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። ለአብነትም በገንዘብ አቅም ማነስ፣ በሚያግዝ ሰው አለመኖር ህሙማን ላይመጡ ይችላሉ።
የመፍትሄ ሀሳብ ምን ሰጡ ?
” እኛ ነን ችግሩ ወዳጋጠመበት ቦታ መሄድ ያለብን፡፡ በአንድ ቦታ ግጭት ሲያጋጥም ‘ወገኖቼ ይሞታሉ’ በሚል መሸበር ይኖራል፡፡ በተለይ በዚያ ወቅት ስነ ልቦናዊ ድጋፍ ካልተገኘ ችግሩ ይብሳል።
ስለዚህ አዕምሮ ጤናም ጉዳይ ሌሎች እርዳታዎች ጋር አብሮ መሄድ አለበት፡፡ በግንዛቤ እጥረት በትራንስፖርትና
በሱዳን ጦርነት ለሚዋጉ የኮሎምቢያ ተዋጊዎች የቦሳሶ ወደብ መሸጋገሪያ መሆኑ ተነገረ።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የምታስተዳድረው በቦሳሶ የሚገኝ ወታደራዊ ማዘዣ ለተዋጊዎቹ መሸጋገሪያ መሆኑ ተገልጿል።
የቀድሞ የኮሎምቢያ ጦር አባላት ለግለሰባዊ ደህንነት ከተመለመሉ በኋላ ለሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል እንዲዋጉ ይደረጋሉ ተብሏል።
አንድ የኮሎምቢያ ተዋጊ 2600 ዶላር በወር የሚያስገኝለትን ኮንትራት መፈረሙን ገልፆ በኢትዮጵያ በኩል አድርጎ ወደ ፑንትላንድ ቦሳሶ ወደብ መወሰዱን በኋላም በዳርፉር መስፈሩን ገልጿል።
የቦሳሶ ወደብ መጀመሪያ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሲሰራ የፑንትላንድ የባህር ኃይልን ለማሰልጠን ነበር ሲባል አሁን ሙሉ ለሙሉ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የምትቆጣጠረው ማዘዣ ነው ተብሏል።
ምንም እንኳን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በሱዳን ጦርነት ያላትን ተሳተፎ ብትክድም ከሰሞኑ የቦሳሶ ወደብ እንዴት የኮሎምቢያ ተዋጊዎች መሸጋገሪያ እንደሆነና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እየተጠቀመች እንደሆነ የሚያሳይ የምርመራ ዘገባ ወጥቷል።
ዘ ጋርዲያንና La Silla Vacia የተሰኘ የኮሎምቢያ ጋዜጣ በጉዳዩ ላይ የሰሩትን የምርመራ ሪፖርት ከዚህ ማንበብ ( https://www.theguardian.com/world/2025/oct/08/colombian-mercenaries-sudan-war ) ይችላሉ።
‹‹ትክክለኛ የትምህርት ፖሊሲ አለ ከተባለ ተጠያቂነትም መኖር አለበት›› ጥሩሰው ተፈራ (ፕሮፌሰር)፣ የትምህርት ዘርፍ ባለሙያና…
October 12, 2025
ኢትዮጵያ ከትምህርት ሥርዓቱ የምትፈልገውን ብቁና በቂ የተማረ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ ውስንነት እንዳለበት በተደጋጋሚ ይነገራል፡፡ ለዚህ የሚሰጠው አመክንዮ አንድም መንግሥታት በተቀያየሩ ቁጥር የሚቀያየር መሆኑን፣… https://ethiopianreporter.com/146689/
በአማራ ክልል ካለው የፀጥታ መደፍረስ ጋር በተገናኘ የፋኖ ታጣቂዎችን ትደግፋላችሁ በሚል በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙ እስረኞች ከጠበቆቻቸው ጋር እንዳይገናኙ መከልከላቸውን ቤተሰቦቻቸው ለመሠረት ሚዲያ ተናግረዋል።
“እስረኞቹ ከጠበቃቸው ጋር እንዳይገናኙ ተከለከሉ የተባለው ምን ያህል እውነት ነው?” ስንል ከጠበቆቹ አንዱ የሆኑትን አቶ ሰለሞን ገዛኽኝን ጠይቀናቸው ነበር።
አቶ ሰለሞን ጉዳዩ እውነት መሆኑን አረጋግጠው “እስረኞቹን አግኝተህ የሕግ አገልግሎት መስጠት አትችልም በሚል የተከለከልኩት እኔ ነኝ” ሲሉ ገልፀዋል።
“ከእስረኞቹ ጋር እንዳይገናኙ የተከለከሉበት ምክንያት ምንድን ነው?” ተብለው ከመሠረት ሚዲያ ለተነሳላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ደግሞ “ካሳለፍነው ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ እስከ ጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም ድረስ በሽብር የተከሰሱ እስረኞቹን ለይተው ከጠበቆቻቸው ጋር እንዳይገናኙ በሚል በማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ተከልክለናል” ሲሉ አቶ ሰለሞን አክለዋል።
ጠበቃው ጨምረውም “እንኳን ጠበቆቻቸው ቤተሰቦቻቸው ገብተው እንዳይጠይቋቸው ከፍተኛ ጫና እየተደረገባቸው ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
በሽብር ወንጀል የተከሰሱ እስረኞቹ ከሌላው በተለየ ሁኔታ ሕክምና ሳይቀር እየተከለከሉ ነው ያሉት ጠበቃ ሰለሞን በጠና ታመው አልጋ ላይ የዋሉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል ዶክተር ካሳ ተሻገር ሕክምና እንዳያገኙ ከተከለከሉት እስረኞች ውስጥ አንዱ ናቸው ብለዋል።
ዶክተር ካሳ በጀርባ ዲስክ መንሸራተት ምክንያት መንቀሳቀስ እንዳልቻሉ የተናገሩት ጠበቃው ማረሚያ ቤቱ ለማሳከም ፍቃደኛ አልሆነም ብለዋል።
ይህንን በእስረኞቹ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ጫና አስመልክቶ አቤቱታ ለማቅረብ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የጥበቃ እና ደኅንነት ማስተባበሪያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ድሪባ ሰንበታን የጠየቁት አቶ ሰለሞን ተቋሙን የማይወክል እና ራሳቸውን የሥርዓቱ ተወካይ አድርገው
በኢትዮጵያ 800 ሺሕ ያህል ስደተኞች የረሃብ አደጋ እንደተጋረጠባቸው የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስታወቀ
በመጪዎቹ ስድስት ወራት 34 ቢሊዮን ብር ካላገኘ ሙሉ ለሙሉ ዕርዳታ ይቋረጣል ብሏል የዓለም የምግብ ፕሮግራም በገንዘብ እጥረት ምክንያት ወደ 800 ሺሕ የሚጠጉ ኢትዮጵያ ውስጥ ተጠልለው… https://ethiopianreporter.com/146711/
በኢትዮጵያ ያለው የድህነት ምጣኔ በ2025 ወደ 43 በመቶ ከፍ ሊል እንደሚችል የዓለም ባንክ አስታወቀ
የዓለም ባንክ ድህነትንና የሀብት ፍትሐዊነትን በተመለከተ ከሰሞኑ ባወጣው መረጃ በኢትዮጵያ በተያዘው እ.ኤ.አ. 2025 የድህነት ምጣኔ ወደ 43 በመቶ ከፍ ሊል እንደሚችል አስታወቀ፡፡ የዓለም ባንክ የድህነት… https://ethiopianreporter.com/146715/
ለሥራ ስምሪት ወደ ውጭ አገር ለሚጓዙ ሠራተኞች የበረራ ትኬት የሚቆረጥበት አሠራር ቅሬታ አስነሳ
ቪዛ የተመታላቸው 14 ሺሕ ሠራተኞች ወደ ሳዑዲ መጓዝ አልቻሉም ተብሏል በአዲሱ የውጭ አገር የሥራ ስምሪት አዋጅ መሠረት ሠራተኞችን ወደ ውጭ ለመላክ ፈቃድ ያገኙ ኤጀንሲዎች የትራንስፖርት… https://ethiopianreporter.com/146718/
የሕግ ትምህርት ቤቶች የመዘጋት አደጋ እንደተጋረጠባቸው ተገለጸ
‹‹ጉዳዩን የሚመለከት ቁርጠኛ የፖለቲካ አካል ሊኖር ይገባል›› የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በደመወዝ፣ በጥቅማ ጥቅም ማነስ፣ በሰው ኃይል እጥረትና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች የሕግ ትምህርት ቤቶች የመዘጋት አደጋ እንደተጋረጠባቸው በጥናት ተመላከተ፡፡ የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ሕግ ትምህርት ቤቶች ማኅበር ጋር በመተባበር፣ ‹‹በኢትዮጵያ የሕግ ትምህርት አዝማሚዎች፣ ፈተናዎችና ዕድሎች›› በሚል መሪቃል መስከረም 29 ቀን 2018… https://ethiopianreporter.com/146730/
እስከ ተመድ የዘለቀው የፌዴራል መንግሥትና የሕወሓት መካሰስ
መስከረም 22 ቀን 2018 ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬስ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የተጻፈው ደብዳቤ፣ ሕወሓትን በጠብ ጫሪነትና ሰላም… https://ethiopianreporter.com/146700/
ከስምምነት ያልተደረሰው የፕሪሚየር ሊጉ የስታዲየም ተመልካቾች ‹‹ይመዝገቡ›› ጥያቄ
October 12, 2025
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላለፉት አምስት ዓመታት በተለይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ሳይካሄድ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ዘንድሮ ውድድሩ በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚካሄድ በመገለጹ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር… https://ethiopianreporter.com/146668/
ከሻቢያ የተጠጋ ሁሉ መጨረሻው ክሽፈት፣ ውርደትና ውድመት ነው፤ ( ያሬድ ሃይለማርያም፡ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች)
+++++
በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ሻቢያን እጁን ይዘው እየጎተቱ ጣልቃ የሚያስገቡና አቅም ባነሳቸው ቁጥር ኢሳያስ እግር ስር የሚነጠፉ ፖለቲከኞች ሁሌም መጨረሻቸው ኢትዮጵያን እንዳዋረዷት፣ እንደጎዷትና እንዳከሰሯት ነው። ኢሳያስ የራሱን ሀገር ኤርትራን ያቆረቆዘ፣ የኤርትራን ወጣት በባህር ያሰደደና ለባህር አውሬ የዳረገ፣ ሕዝቡንም አፍኖ ይዞ ያደኸየ ክፉና በቀጠናው ውስጥ ከቀሩ አንጋፋ ጨካኝ አንባገነኖች አንዱ ነው። ኢሳያስ የነካው የኢትዮጵያ ጉዳይ ሁሉ ሁሌም ውድመትና ምን እንደነካው እንጨት መጨረሻው አስከፊ መሆኑን እንዴት ወደኋላ መለስ ብለው ማየት እንደሚቸገሩ ግራ ይገባኛል።
1ኛ/ ወያኔ ከጫካ ወደ ስልጣን ስትመጣ ሻቢያን ከፊት አስቀድማ ነበር። አዲስ አበባን ተቆጣጥራም ለተወሰኑ ጊዜያት ቤተመንግስቱ ጭምር ይጠበቅ የነበረው በሻቢ ጦር ነበር። ኤርትራም ስትገነጠል ህውሃት ዋነኛ ሂደቱን አቀላጣፊ በመሆን ኢትዮጵያን የሯሷን አገር ለማስገንጠል የእውቅና ደብዳቤ የጻፈች የመጀመሪያዋ አገር አረገቻት። መለስ ከሻቢያ የበለጠ አሰብንም ውሰዱልኝ ብሎ መሸኘቱን አደራዳሪዎቹ መስክረዋል። ሻቢያ ግን በዛም ሳያበቃ ኢትዮጵያን ለመዝረፍ እቅድና ስልት ነድፎ ጠላትነቱን አጠናክሮ ቀጠለ።
2ኛ/ ከዛም ባለፈ ወያሬ የአገሪቱን አንጡራ ሃብትና ከቡና እስከ ጦር መሣሪያ ጭምር በሻቢያ እንዲዘረፍ ሁኔታዎችን አመቻቸችለት። ውለታዋን ግን ሻቢያ ባድመንና ዛላንበሳን በመውረር በክህደትና በጭካኔ ሳይል ሳያድር መለሰ። ብዙ ሺዎች አለቁ። ትግራይ ዳግም በደም ጨቀየች። ሻቢያ ዋና የህውሃትና የኢትዮጵያ ጠላት ሆኖ ቀጠለ።
3ኛ/ ከወያኔ መማር ያልቻሉ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎች ወያኔ አስከፍታናለች ብለው ኢሳያስ እንዲያስጠልላቸው፣ እንዲያስታጥቃቸው፣ እንዲያሰለጥናቸውና