Home › View all posts by Konjit Sitotaw
Blog Archives
የደቡብ ሱዳን የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በፈጸሙት “የደፈጣ ተኩስ ጥቃት” ስድስት ሰዎች ተገደሉ
ከደቡብ ሱዳን የመጡ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች፤ በጋምቤላ ክልል፣ በአኙዋሃ ዞን፣ ዲማ ወረዳ በሚገኝ ቦታ ላይ በከፈቱት “የደፈጣ ተኩስ ጥቃት” ስድስት ሰዎች መገደላቸውን የወረዳው የአስተዳደር እና የፖሊስ ኃላፊዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በትላንትናው ዕለት ጠዋት በተፈጸመው በዚህ ጥቃት፤ በዘጠኝ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን መመልከታቸውን በአካባቢው የሚገኙ የህክምና ባለሙያ ገልጸዋል።
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ጥቃቱን የሰነዘሩት፤ ከዲማ ወረዳ 39 ሰዎች አሳፍሮ ወደ ጎግ ወረዳ ሲጓዝ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ላይ እንደሆነ የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር ኡታክ ሜዶ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሱ የደፈጣ ጥቃት የተሰነዘረበት፤ ከዲማ ከተማ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ተጉዞ አቻኛ እና 45 በተባሉ ቀበሌዎች መካከል በደረሰበት ወቅት እንደሆነ የፖሊስ አዛዡ አስረድተዋል።
ታጣቂዎቹ በአውቶብሱ ላይ ተኩስ በከፈቱበት ወቅት “መሳሪያ የያዘ ተሳፋሪ” መልሶ በመተኮስ አጸፋውን መመለሱን ረዳት ኢንስፔክተር ኡታክ አመልክተዋል። በተኩስ ልውውጡ አንድ ታጣቂ መገደሉንም የፖሊስ አዛዡ ጠቁመዋል። በታጣቂዎቹ የደፈጣ ጥቃት የአውቶብሱን ሹፌር ጨምሮ የስድስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በስድስት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱንም ጨምረው ገልጸዋል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16005/
ኢትዮጵያ ውስጥ በዝንጀሮ ፈንጣጣ (Mpox) የተያዘ ሰው ተገኘ።
በMpox የተያዘ ሰው የተገኘው ሞያሌ ከተማ ነው።
ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት Mpoxን አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም ኢኒስቲትዩቱ በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ በህመሙ መያዛቸው ከተጠረጠሩ ታማሚዎች በወሰደው ናሙና በMpox ቫይረስ የተያዘ ሰው ማግኘቱን እንዳረጋገጠ ይፋ ተደርጓል።
ቫይረሱ እንደተገኘበት የተረጋገጠው የ21 ቀን እድሜ ያለው ህፃን ልጅ ሲሆን እናቱም በተደረገው ቀጣይ ምርመራ ለቫይረሱ እንደተጋለጠች ለማረጋገጥ መቻሉ ተገልጿል።
የህፃኑ አባትም ወደ ጎረቤት ሀገር ሄዶ የነበረ መሆኑ መታወቁና የሄደባቸውን አካባቢዎች እንዲሁም ከግለሰቡ ጋር የቅርብ ንክኪ የነበራቸው ግለሰቦችን የመለየትና ክትትል የማድረግ ስራ እንደተጀመረ ይፍ ተደርጓል።
ታማሚው ህፃን እና እናቱ፣ አስቀድሞ በተዘጋጀው የለይቶ ማከሚያ፣ ተገቢው የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን፣ እስካሁን ባለው ሁኔታ የከፋ የጤና እክል አልገጠማቸውም ተብሏል።
የMpox በሽታ ቫይረሱ ካለባቸው ግለሰቦች ጋር ንክኪ ያለው ሰው የሚከተሉት ምልክቶች በሚታዩበት ወቅት ማለትም ፦
– ሽፍታ
– ሳል
– ትኩሳት
– የራስ ምታት
– ድካም እና የጀርባ ህመም ሲያስተውል በአፋጣኝ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ተገቢውን የምርመራና ህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ጥሪ ቀርቧል።
እንዲሁም የግል እና የእጅ ንፅህና በመጠበቅና ከላይ የተገለፁት ምልክቶች ባሉባቸው ታማሚዎች አካባቢ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛዎችን በመጠቀም ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ተብሏል።
በአሁኑ ወቅት ይህ በሽታ በተወሰነ ቦታ ብቻ የታየ በመሆኑ ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ የተለመደውን አኗኗር መቀጠል ይችላል ያሉት ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
በአማራ ክልል በመቶዎች የሚቆጠሩ የባንክ ጥበቃዎች እየታሰሩ ነው፣ ምክንያቱ ምን ይሆን?
(መሠረት ሚድያ)- በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ አንዳንድ ከተሞች ውስጥ የባንክ ጥበቃ በመሆን እያገለገሉ ያሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች ከባለፈው ሁለት ሳምንት ወዲህ አፈሳ በሚመስል መልኩ እየታሰሩ ይገኛሉ።
መሠረት ሚድያ ‘ጉዳዩ ምን ይሆን?’ በሚል ማጣራት አድርጓል።
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/9de?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
የኤርትራው ፕሬዝደንት በትናንት ምሽት ብዙዎችን ባስደመመ ንግግራቸው ስለ ኢትዮጵያ ምን አሉ?
– “የውጭ ሀይሎች በብልፅግና ወኪላቸው አማካኝነት የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ላለፉት አምስት አመታት ያወጁት ጦርነት ምን ያህል ተስፋ እንደቆረጡ ያሳያል”
– “ሊያቀርቡ የሚፈልጓቸው ምክንያቶች; ናይል እና ቀይ ባህር፣ የባህር በር ማግኘት፣ የኦሮሞ ህዝብን የማይወክል የኦሮሙማ አስተሳሰብ፣ የኩሽ እና የሴም ግጭት… ናቸው”
– “የኢትዮጵያ ህዝብ የራሱን ምርጫ መርጧል፣ ተቃውሞውን ለማጠንከር እየተዘጋጀ ነው”
ሙሉ ዜናውን ያንብቡ፣ የሚድያችን ቤተሰብ ይሁኑ ⤵️
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/3bf?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
የአሜሪካ ኢምባሲ፣ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መንግሥት የድሮን ጥቃቶችን “በራሱ ሕዝብ ላይ” መፈጸምን “በአፋጣኝ እንዲያቆም” በጠየቁበት የዛሬው መልዕክታቸው ላይ ማሻሻያ አድርጓል። በተሻሻለው መልዕክት፣ ይህ መልዕክት ተነስቶ በምትኩ መንግሥት ለግጭቶች “ከኃይል ውጪ ያሉ ሰላማዊ አማራጮችን” መፈለግ እንዲቀጥልና “የዜጎቹን ደኅንነት እንዲያስቀድም” አምባሳደሩ መጠየቃቸው ብቻ ተጠቅሷል። የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የኦሮሚያው ግጭት እንዲያበቃ የሰላም ድርድሩን እንዲቀጥል፣ የፋኖ ቡድንም “ተጨባጭ” እና “ሰላማዊ የኾኑ” ግቦችን እንዲይዝና “በትጥቅ ትግል ስም የሚካሄድ ሕገወጥነት እንዲያበቃ” አምባሳደሩ በቀደመውም ኾነ በተሻሻለው መልዕክታቸው ጠይቀዋል። ኢምባሲው፣ የአምባሳደሩ መልዕክት በምን ምክንያት እንደተሻሻለ አላብራራም። https://www.facebook.com/profile.php?id=100007836377373
አንዳንድ ምግባረ ብልሹ የፀጥታ አካላት በመዲናዋ ነዋሪዎች ላይ በግልፅ ዝርፊያ መፈፀም እንደጀመሩ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- የፀጥታ አካላት በአቅራቢያችን ሲገኙ ደህንነት ይሰማናል፣ ከሌላው ግዜ በተለየ ህግ አስከባሪ እንዳለ ተሰምቶን ሰላም ይታየናል። ይህ የተለመደ ስሜት ግን በቅርብ ግዜያት በተለይ በመዲናዋ አዲስ አበባ እየጠፋ ይገኛል፣ ለዚህ ደግሞ እየበዙ የመጡት ምግባረ ብልሹ የፀጥታ አካላት ናቸው።
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/0be?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
አሜሪካ ምን አለች ?
➡️ ” ፋኖ ተጨባጭ እና ሰላማዊ የሆነ ዓላማ ይዞ ይምጣ። ”
➡️ ” የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) በኦሮሚያ ያለውን ግጭት ለማስቆም ድርድሩን ይቀጥል። ”
➡️ ” የፌዴራል መንግሥት በራሱ ዜጎች ላይ የሚያደርገውን የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ ያቁም። ”

አሜሪካ ዛሬ አዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ በኩል ለፌዴራል መንግሥት እና ለታጣቂዎች መልዕክት አስተላልፋለች።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ዛሬ ባስተላለፉት መልዕክት በመላው ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለጉዳት የዳረጉ ግጭቶች ሰላማዊና ትክክለኛ መፍትሔ እንዲፈለግላቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
አምባሳደሩ፥ ለታጣቂ ኃይሎች እና ለፌደራል መንግስት ባስተላለፉት መልዕክት ህዝብን እንዲያስቀድሙ ጥሪ አቅርበዋል።
” ጦርነቱን ማቆም፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ መርዳት እና ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ እና የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ ነው ” ሲሉ አስገንዝበዋል።
” በትጥቅ ትግል ስም የሚፈጸሙ ህገወጥ እና የኃይል እርምጃዎች ሊቆሙ ይገባል ” ብለዋል።
አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በመልዕክታቸው ለፋኖ ፣ ለኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) እና ለፌደራል መንግስት የተናጠል መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዚህም ፥
– ፋኖ ተጨባጭ የሆነ እና ሰላማዊ የሆነ ዓላማ/ግብ ይዞ እንዲመጣ፤
– የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) ደግሞ በኦሮሚያ ያለውን ግጭት ለማስቆም ድርድሩን እንዲቀጥል፡
– የፌደራል መንግስት በራሱ ዜጎች ላይ የሚያደርገውን የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ እንዲያቆምና ረጅም እርምጃ ወደ ለሰላም በመምጣት መፍትሄዎችን እንዲያመቻች ጥሪ አቅርበዋል።
አምባሳደሩ በመልዕክታቸው ማጠናቀቂያ ” ሰላምና መረጋጋት የምንመርጥበት ጊዜ አሁን ነው ” ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር እንደ ጎርጎሮሳዊያኑ ከ2001 እስከ 2023 የኢትዮጵያ ጠቅላላ አገራዊ ምርትና ምርቱ ለዜጎች የሚያስገኘው የነብስ ወከፍ ገቢ እየቀነሰ እንደሄደ በጥናት ማረጋገጡን መግለጡን ሸገር ዘግቧል። ማኅበሩ በተለይ ከአውሮፓዊያኑ ከአውሮፓዊያኑ 2016 ጀምሮ የነብስ ወከፍ ገቢ እየቀነሰ መምጣቱንና በአንጻሩ የዋጋ ግሽበት እየጨመረ መሄዱንና እንደገለጠ ዘገባው ጠቅሷል። የማዳበሪያ አጠቃቀም ከዓለማቀፍ መስፈርት አንጻር ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ የግብርናው ዘርፍ ያገኘው ብድር 7 ነጥብ 8 ከመቶ ብቻ መኾኑንም ተቋሙ ገልጧል ተብሏል። የጥሬ እቃ እጥረት፣ የኤሌክትሪክ ኃይልና የውሃ አቅርቦት እጥረትም ለአምራቹ ዘርፍ ፈተና እንደኾነ ተገልጧል። ግጭቶችም ኦኮኖሚው እንዲቀዛቀዝና ኢንቨስትመንት እንዲዳከም ምክንያት ሆነዋል ተብሏል።
“ የተገደሉት ሰዎች ብዛት 17 ነው። ከሟቾች መካከል 12 ህፃናት ናቸው ” – የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አባል
በካማሺ ዞን ምዥጋ ወረዳ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ንጹሐን ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የክልሉ ምክር ቤት አባል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ነዋሪዎቹ፣ “የሸኔ ታጣቂዎች ጥቃት ፈጽመዋል” ብለው፤ ከ10 በላይ ንጹሐን እንደተገደሉ፣ አብዛኛዎቹ ሟቾች ህፃናት እንደሆኑ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለ ጥቃቱ የጠየቃቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ም/ቤት አባልና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ለሜሳ ኔኖ፣ “ ትክክል ነው። ንጹሐን ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ግድያ ነው የተፈጸመው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የክልሉ ምክር ቤት አባል በሰጡን ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
“ በካማሽ ዞን ምዥጋ ወረዳ አንገር ሜጢ የሚባል ታዳጊ ማዘጋጃ ቀበሌ ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ/ም ንጋት 12 ሰዓት ጅምሮ የሸኔ ቡድን ጥቃት ፈጽሟል።
በዚሁ ጥቃት 16 ሰዎች እዛው ነው የሞቱት። አንደኛው ሰው ደግሞ ለህክምና ከሄደ በኋላ ነው የሞተው። የተገደሉት ሰዎች ብዛት 17 ነው። ከሟቾች መካከል 12 ህፃናት ናቸው። ቀሪዎቹ አዋቂ ናቸው።
ቡድኑ በተለያዩ ጊዚያቶች ጥቃት ሰንዝሯል። እስካሁን በተፈጸሙ ሦስት ጥቃቶች 27 ሰዎች ናቸው የተገደሉት።
የትላንቱ ጥቃት የተፈጸመበት ቦታ ለኦሮሚያ ክልል አንድ ቀበሌ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ነው የሚገኘው። ጥቃቱ በወረዳው ከሚያዚያ ወዲህ ለሦስተኛ ጊዜ የተፈጸመ ነው ” ብለዋል።
ምክንያቱና መፍትሄው ምንድን ነው ?
የታጣቂዎቹ ፍላጎታቸው ምንድን ነው ? መፍትሄውስ ? በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ
” በደብረብርሃን ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች ላልተፈለገ እርግዝና እና በአባላዘር በሽታ እየተጠቁ ነው ” የተፈናቃይ ሴት ወጣት ተወካዮች
⚫ ” የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት ይሰጡ የነበሩ ድርጅቶች አሁን ላይ ሁሉም ወጥተዋል ” የቻይና ካምፕ ተፈናቃይ አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ
በደብረብርሃን መጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚሰጠው የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት ጥራቱን ያልጠበቀ በመሆኑ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን የተፈናቃዮቾ ሴት ወጣት ተወካዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
በህክምና ባለሙያዎች ዘንድም ሚስጥር ጠባቂ አለመሆን አገልግሎት ለማግኘት በምንሄድበት ወቅት የማሸማቀቂያ ቃላቶችን የሚጠቀሙ በመሆኑ አገልግሎቱን ማግኘት ከብዶናል ብለዋል።
“የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት እየሰጠ ያለው ዩኒሴፍ ብቻ ነው፣ አገልግሎት የሚሰጠውም ግቢ ውስጥ ቢሆንም ሴት ልጅ ስትገባ የእንትና ልጅ የወሊድ መቆጣጠሪያ ልትጠቀም ገበች ይላሉ፣ ስንወጣ ደግሞ ወጣት ወንዶች ይጠብቁና ያሸማቅቁናል” ሲሉ ችግራቸውን ይገልጻሉ።
በተጨማሪም ” የህክምና ባለሙያው ወንድ ነው፣ ይህ ደግሞ ሴቶች በነፃነት የሚፈልጉት እንዳይናገሩ አድርጓል፣ በከተማው ጤና ጣቢያዎች ስንሄድም በነፃ ስለሆነ የሚሰጠው ምን ልታደርጊ ትመጫለሽ ውጪ ይላሉ። እነሱ የሚፈልጉት ብር የሚከፍለውን ሰው ብቻ ነው” ሲሉ አክለዋል።
ወጣት ሴቶችም በየፋርማሲው መድሀኒት እየገዙ ይውጣሉ፣ አብዛኞቹም ለህመም እየተዳረጉ ነው ብለዋል።
በስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት እጥረት በርካታ ወጣቶች ላልተፈለገ እርግዝና፣ ለአባላዘር እና ለመሳሰሉ ተላላፊ በሽታዎች መጋለጣቸውንም አስረድተዋል።
“በተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ ውስጥ ያሉ ወጣት ወንዶች ተስፋ እየቆረጡ አልኮል እየጠጡ ሴት ልጆችንን አስገድደው እየደፈሩን ነው፣ ስንጠይቅም በቸልተኝነት ሁሉም ይስተካከላል ይላሉ” ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርቧል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቻይና ካምፕ የተፈናቃይ ኮሚቴ
ከሚሰራበት ባንክ ውስጥ በፀጥታ አካላት የተወሰደው ወጣት ያለበት ሳይታወቅ አራት ወር እንደሞላው ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- ጥር 9/2017 ዓ/ም ከሚሰራበት ባንክ ውስጥ በፀጥታ አካላት ታፍኖ ተወሰደው ወጣት ያለበት ቦታ ሳይታወቅ አራት ወር እንዳለፈው ታወቀ።
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/954?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
በመቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች፤ ከደህንነት ስጋት ጋር በተያያዘ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ካልተመለሱ የጀመሩትን የስራ ማቆም እንደሚቀጥሉ ገለጹ
በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች በትላንትናው ዕለት የጀመሩትን የስራ ማቆም ዛሬም በመቀጠላቸው በከተማይቱ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች ተዘግተው ዋሉ። ዳኞቹ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ያቀረቧቸው ጥያቄዎች እስኪፈቱ ድረስ የስራ ማቆማቸውን እንደሚቀጥሉ የትግራይ ዳኞች ማህበር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጿል።
በመቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች ስራቸውን ለማቆማቸው በዋነኛነት የጠቀሱት ምክንያት “የደህንነት ችግር አለብን” የሚል ነው። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትላንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫም፤ በመቐለ ሰባት ክፍለ ከተሞች ባሉ ፍርድ ቤቶች እና በከተማይቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚሰሩ ዳኞች “በደህንነት ስጋት” ምክንያት ስራ እንዳቆሙ ማሳወቃቸውን አረጋግጧል።
የትግራይ ዳኞች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ዳዊት ሃይለስላሴ፤ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ያቀረቧቸው አምስት ጥያቄዎች ከዳኞች ደህንነት ጋር የተያያዙ መሆናቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የዳኞቹ የመጀመሪያ ጥያቄ በችሎት የሚመደቡ የጸጥታ አስከባሪዎችን የሚመለከት ነው።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15997/
የሕክምና ማስተማሪያ ሆስፒታሎች ያሏቸው በርካታ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አዲስ የጤና ባለሙያዎችን ለመቅጠር ማስታወቂያ በማውጣት ላይ እንደኾኑ የጤና ባለሙያዎች የሥራ ማቆም አድማ አስተባባሪዎች ገልጸዋል። አለርት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ 50 ጠቅላላ ሐኪሞችን፣ 120 ነርሶችንና 100 ሚድዋይፈሮችን ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣቱን አስተባባሪዎቹ ያጋሩት መረጃ ያሳያል። የካቲት 12 ሆስፒታል ሬዚደንት ሐኪሞች እስከ ዓርብ ግንቦት 15 ወደ ሥራና የትምህርት ገበታቸው ካልተመለሱ አካዳሚያዊ ርምጃ እንደሚወስድ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሲያወጣ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በበኩሉ እስከ ነገ እኩለ ቀን ወደ ሥራቸውና ትምህርታቸው ያልተመለሱ ረዚደንት ሐኪሞች ጥቁር ከዩኒቨርስቲው እንዲለቁ አሳስቧል።
የጤና ሚንስትር ደኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ፣ የሥራ ማቆም አድማ ያደረጉ የጤና ባለሙያዎች ባስቸኳይ ወደ ሥራቸው ካልተመለሱ የሙያ ፍቃዳቸውን ሊነጠቁ እንደሚችሉ ለመንግሥታዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል አስጠንቅቀዋል። በአድማው ሳቢያ የተወሰነ የሆስፒታሎች አገልግሎት መስተጓጎል መኖሩን ያመኑት ሚንስትር ደኤታው፣ ከድንገተኛ እና ከእናቶችና ሕጻናት ሕክምና ክፍሎች ጥለው የወጡ የሕክምና ባለሙያዎች መኖራቸውን እናውቃለን ብለዋል። የአድማው ዋነኛ ተሳታፊዎች፣ ሬዚደንት ሐኪሞች እንደኾኑም ዶ/ር ደረጀ ጠቅሰዋል። የጤና ባለሙያዎች ሙሉ የሥራ ማቆም አድማ ዛሬ ሦስተኛ ቀኑን ይዟል።
(መሠረት ሚድያ)- በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር (space) የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ ከቅርብ አመታት ግን ጥቂት ሰዎች ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል የዝቅተኛው ንፍቀ ክበብ የጠፈር ጉብኝት አድርገዋል።
መሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበርካታ ቀናት ሲያሰባስበው የነበረው መረጃ እንደሚጠቁመው በአለም ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የአንድ የሀገር መሪ ወደ ጠፈር ሊጓዝ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፣ መንገደኛውም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ናቸው።
በኤምሬቶች የሚገኙ ምንጮቻችን እንዳረጋገጡልን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የመጓዛቸው አላማ በርካታ ግቦችን አካቷል፣ ከእነዚህም መሀል የሰላም እና የአንድነት መልዕክት ለአለም ብሎም ለኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ እንዲሁም ወጣቶች ወደ ቴክኖሎጂው ዘርፍ እንዲሳቡ እና እንዲነሳሱ ለማድሩግ ታስቧል።
“ውይይቱ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተባበሩት ኤምሬቶች በኩል በስፋት ንግግር እየተደረገበት ነው” ያሉት አንዱ በዱባይ የሚገኝ የመረጃ ምንጭ በተለይ ከጠፈር ላይ ሆኖ ለአለም ህዝብ መልዕክት ማስተላለፍ የእቅዱ ዋና ግብ ነው ብለዋል።
‘Project X’ የሚል ስም ተሰጥቶት እየተሰራበት እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጠፈር ጉዞ ወጪው በተባበሩት ኤምሬቶች የሚሸፈን መሆኑን አንድ ሌላ እዛው ዱባይ የሚገኝ ምንጭ ለሚድያችን ተናግሯል።
ለመዳሰስ የሞከርናቸው ፅሁፎች እንደሚጠቁሙት ወደ ጠፈር የሚደረግ ጉዞ ለአንድ ሰው ከትንሹ 250 ሺህ ዶላር እስከ ከፍተኛው 55 ሚልዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ይጠቁማሉ።
ለምሳሌ ‘Blue Origin’ እና ‘Virgin Galactic’ የተባሉት መንኩራኩሮች ከንፍቀ ክበብ በታች ለሚደረግ እና ርካሽ የተባለ ጉዞ ከ200 ሺህ ዶላር
ኢሰመኮ፣ በርካታ የጤና ባለሙያዎች ከሥራ ማቆም አድማው ጋር በተያያዘ እየታሠሩ፣ ማስፈራሪያ እየደረሰባቸውና ከማስተማሪያ ሆስፒታሎች በግዳጅ እንዲወጡ እየተደረጉ መኾኑን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ኢሰመኮ፣ በአዲስ አበባ፣ ጂማ፣ ባሕርዳር፣ ሀዋሳ እና ጎንደር በርካታ ሬዚደንትና ተለማማጅ ሐኪሞችን ጨምሮ በርካታ የጤና ባለሙያዎች እንደታሠሩና በግዳጅ ከማስተማሪያና የሥራ ቦታቸው ከኾኑ ሆስፒታሎች እንዲወጡ እንደተደረጉ ገልጧል። ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ፣ በጤና ባለሙያዎች ላይ የሚወሰዱ ሕጋዊና አስተዳደራዊ ርምጃዎች የሰብዓዊ መብቶች መርኾዎችን የተከተሉ መኾን እንዳለባቸው አሳስበዋል። ችግሩን ለመፍታት ውይይት እንዲደረግና ተጠያቂነት እንዲሠፍን የጠየቀው ኢሰመኮ፣ አፈና አዋጭ መንገድ አይደለም ብሏል።
የተቀደሰው ቀጠሮ – የፋኖዎችን ጉዞ የሚያስቃኘው ዶክመንታሪ ፊልም ተለቀቀ – ጸሃፊ – ፋኖ ባየ ደስታው
የአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ፣ ዛሬ ወደ ትግራይ አቅንተው ከሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አማኑኤል አሠፋና ከጸጥታ ኃይሎች ከፍተኛ አዛዦች ጋር በጸጥታ፣ ፖለቲካዊ፣ በሰብዓዊ ጉዳዮች፣ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አተገባበርና በቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል። አምባሳደሩ የሽሬውን የተፈናቃዮች መጠለያ የጎበኙ ሲኾን፣ ለተፈናቃዮች ዕርዳታ መስጠት ዘላቂ መፍትሄ ሊሆን እንደማይችልና መፍትሄው ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው መመለስ እንደኾነ መናገራቸውን የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። አምባሳደሩ፣ ተፈናቃዮቹ ወደ ቀያቸው ተመልሰው ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ከተፈናቃዮቹ ጋር ካደረጉት ውይይት ተረድቻለሁ ተብሏል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ተማሪዎች አንድነት፣ የዘንድሮው የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፣ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ላይ በሚስተዋሉ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ አላተኮረም በማለት ተችቷል። ማኅበሩ፣ በትግራይ የሚገኙ አሕጉረ ስብከቶች ከሲኖዶሱ ከተለዩ በኋላ በተስተዋሉ ጥፋቶች ዙሪያ ያዘጋጀውን ሰነድ ለቋሚ ሲኖዶስና ለፓትርያርኩ ማቅረቦ ምላሽ አለማግኘቱን ጠቅሷል። መምሪያው፣ በኦሮሚያ ክልል በአስተዳደራዊ ችግሮች ቤተክርስቲያናት እየተዘጉ፣ ካህናትና ተከታይ ምዕመናንም እየፈለሱ መሆኑን ገልጧል። የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅነትና የአሕጉረ ስብከት ጽሕፈት ቤቶች የአስተዳደር ዘርፍ ከሊቃነ ጳጳሳት ውጪ በብቁ ባለሙያዎች እንዲመሩ የጠየቀው መምሪያው፣ የቤተክርስቲያኗ ተቋማት ለምዝበራ ተጋልጠዋል ብሏል።
” መንግስታት ውጤት አልባ ከሆነ የIMF የበጀት መቀነስና ዕዳ መክፈል ፖሊሲ ወጥተው ትኩረታቸውን ዜጎቻቸው ላይ ማድረግ አለባቸው ” – አክሽን ኤድ
በአፍሪካ ስድስት ሃገራት በጤና እና ትምህርት ዘርፉ በጀት በመቀነሱ ሰራተኞች የከፋ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን አዲስ ጥናት (https://actionaid.org/sites/default/files/publications/The%20Human%20Cost%20of%20Public%20Cuts%20May%202025.pdf) አመላከተ።
ጥናቱን አክሽን ኤድ የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት የሰራው ሲሆን ፦
– በኢትዮጵያ
– በጋና
– በኬንያ
– በላይቤሪያ
– በማላዊ
– በናይጄሪያ 600 የጤና ባለሙያዎች፣ መምህራንና የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ ነው ተብሏል።
በጥናቱ ከተሳተፉት መሃል 97 በመቶ የሚሆኑት የጤና ባለሙያዎች የሚያገኙት ደመወዝ መሰረታዊ የሚባለውን ወጪያቸውን ለመሸፈን እንደማያስችላቸው ተናግረዋል።
97 በመቶ የሚሆኑት የጤና ባለሙያዎች በደመወዛቸው የቤት ኪራይ መክፈል፣ የምግብ እና ሌሎች ወጪዎችን መሸፈን እንዳልቻሉ አንስተዋል።
በጥናቱ በ6ቱ ሀገራት የሚገኙ የጤና ተቋማት ተገልጋዮች በሃኪሞች እጥረት እና በዋጋ መጨመር ደስተኛ አይደሉም ሲል ያስቀመጠ ሲሆን መንግስታት ውጤት አልባ ከሆነ የIMF የበጀት መቀነስና ዕዳ መክፈል ፖሊሲ ወጥተው ትኩረታቸውን ዜጎቻቸው ላይ ማድረግ አለባቸው ብሏል።
ህመምተኞች ወደ ጤና ተቋማት ለመሄድ ረጅም መንገዶችን እንደሚጓዙ፤ የወባ መድኃኒትም በ10 እጥፍ ዋጋው መጨመሩ በጥናቱ የተካተተ ነው።
ለአብነትም በኢትዮጵያ ሙያከላ ቀበሌ የምትኖር ሴትን በመጥቀስ ከ5 አመት በፊት የወባ መድሃኒት በ50 ብር ትገዛ እንደነበር እና አሁን ግን ከግል ተቋማት በ500 ብር እንደሚገዛ መናገሯን ገልጿል።
በሌላ በኩል ፥ በጥናቱ ከተሳተፉት 87 በመቶ የሚሆኑት መምህራን የክፍል ውስጥ ቁሳቁሶች /የማስተማሪያ ቁሳቁሶች እንዳልተሟሉላቸው ሲገልፁ ፤ 73 በመቶ ያህሉ የትምህርት ማስተማሪያ
Posted in
News,
አፍሪቃ,
ኢትዮጵያ
የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችላቸው አዋጅ “ጊዜውን የጠበቀ አይደለም” በሚል ተተቸ
የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቅስ ንብረት ባለቤት እና ባለይዞታ እንዲሆኑ የሚያስችላቸው አዋጅ “ጊዜውን የጠበቀ አይደለም” በሚል በፓርላማ አባላት ተተቸ። ትችቱ የቀረበው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 12፤ 2017 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው።
በአራት ክፍሎች እና በ20 አንቀጾች የተከፋፈለው የአዋጅ ረቂቅ፤ የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ለመሆን ማሟላት ስለሚጠበቅባቸው ቅድመ ሁኔታዎች፣ የፈቃድ አሰራሮች፣ ገደቦች፣ መብቶች እና ግዴታዎች አካትቶ ይዟል። የህግ ረቂቁ በዝርዝር እንዲታይ ለተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ከመመራቱ አስቀድሞ በተደረገ ውይይት ላይ፤ ሁለት የፓርላማ አባላት ትችት አዘል ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል።
የአዋጁ ዋና ዓላማ “የውጭ ካፒታል ወደ ሀገር ውስጥ ማምጫ” እና “የውጭ ምንዛሬ ማግኛ እንደሆነ” መገንዘባቸውን የገለጹት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካዩ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፤ በህግ ረቂቁ ላይ ያላቸውን ስጋቶች እና አስተያየቶች በዝርዝር አቅርበዋል። የፓርላማ አባሉ ለስጋታቸው በምክንያትነት ካስቀመጧቸው ጉዳዮች አንዱ የሀገሪቱ የነፍስ ወከፍ ገቢ እና ደመወዝ በአለም አቀፍ ደረጃ ካለው ሲነጻጸር ያለውን ልዩነት ነው።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15990/
🔴 የፓርላማ አባላቱን አስተያየት ለማድመጥ ➡️ https://youtu.be/0WW5cfnTOJc

ልክ የዛሬ አመት በዚህ ወር በምርመራ ክፍል ውስጥ በአሰቃቂ ሁኔታ ስለተገደለው ኢሳያስ በላይ የተሰራ የምርመራ ዘገባ!ለስድስት አመታት ያህል በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) ውስጥ ከፍተኛ የሳይበር ደኅንነት ባለሙያ ሆኖ አገልግሏል።በ2014 ዓ/ም የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የክልሉ ሰላምና ደኅንነት የሚጠቀምበት ወታደራዊ ሬዲዮ የመለያ ኮዱ በቀላሉ ተጋላጭ ሆኖ ተገኘ። ይህንን የሬዲዮ ትስስር እንደ አዲስ ማስተሳሰር ግድም ሆነ።ኢሳያስ በላይ የወታደራዊ ሬዲዮ ትስስሮች እንዲሁ በቀላሉ የሚከወኑ አይደለም። በዘርፉ ልምድ ያላቸው አለም አቀፍ ተቋማት ተወዳድረው በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሚጠይቁበት ስራ ነው።አገርን ለከፍተኛ ወጪ የዳረገ የሬዲዮ ግንኙነት መረብ እንዲሁ በቀላሉ የይለፍ ቃሉ ተሰብሮ ሚስጥሮች የሚባክኑ ከሆነ ደግሞ ሌላ የአገራዊ ደኅንነት ስጋት ነው። ይህ ስጋት በ2014 ዓ/ም በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የሰላም እና ደኅንነት የሬዲዮ መገናኛ ላይ በግልፅ ታየ።ችግሩ እንዴት ይቀረፍ? በሚል ኢንሳ መፍትሄ ሲያፈላልግ ኢሳያስ በላይ በተቋሙ ውስጥ ያገኘውን አለም አቀፍ ልምድ በመውሰድ የክልሉን የሬዲዮ አውታር እንደ አዲስ ለማቀናጀት ሀሳቡን አቀረበ። ኢንሳ ሰባት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን አዋቅሮ ኢሳያስን የቡድኑ መሪ አድርጎ ወደ አማራ ክልል ሸኘው።ቡድኑን በማስተባበር የአማራ ክልልን ከወረዳ ጀምሮ እስከ ዋናው ቢሮ ድረስ ያለውን የሬዲዮ ትስስር በዘመናዊ መልኩ አቀናጅቶ ለክልሉ መንግስት በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ አስረክቧል። ኢሳያስ ዛሬ በሕይወት ባይኖርም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እና የሰላምና ደኅንነት ቢሮ እስከ ወረዳ ድረስ የሚጠቀሙበት የሬዲዮ መገናኛ መረብ በዚህ ድንቅ ወጣት የተሳሰረ ነው።ኢሳያስ በላይ ለምን ተገደለ?የአማራ
ሕወሓት፣ ፌደራል መንግሥቱ የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት በመጣስ በትግራይ ሕዝብ፣ በፖለቲካ ድርጅቱ፣ በባለሥልጣናቱ፣ በጸጥታ ኃይል አዛዦቹና በተቋማቱ ላይ “ከፍተኛ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በማካሄድ ላይ ይገኛል” በማለት ዛሬ ባስተላለፈው አጭር መልዕክት ከሷል። ሕወሓት፣ መንግሥት በተለይ በቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ አማካኝነት የከፈተው የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በትግራይ ሕዝብና በዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ላይ “ከፍተኛ ስጋት” ፈጥሯል ብሏል። የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አንቀጽ 3 ሕወሓትና የፌደራል መንግሥቱ ከማናቸውም የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ እንዲቆጠቡ ይደነግጋል ያለው ሕወሓት፣ ፌደራል መንግሥቱ ከፕሮፓጋንዳ ድርጊቶቹ ይቆጠብ ሲል ጠይቋል።
የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጥቁር አንበሳ የአጥንት ሕክምና ሐኪሞች በዶ/ር ነብዩ ኤርሚያስ፣ ዶ/ር ሐብታሙ መንክር እና ሌሎች 9 ሐኪሞች ላይ ትናንት የ12 ቀናት የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን የጤና ባለሙያዎች የሥራ ማቆም አድማ አስተባባሪዎች አስታውቀዋል። ፖሊስ በጤና ባለሙያዎቹ ላይ ያቀረበው ክስ፣ ተጠርጣሪዎቹ በሥራ ገበታቸው ላይ ባለመገኘታቸው የታካሚዎች ሕይወት እንዳለፈና ተጠርጣሪዎቹ ከአመጸኛ ኃይሎች ጋር ግንኙነት በማድረግ ሽብር ለመፍጠር እንደሞከሩ የሚገልጹ እንደኾኑ አስተባባሪዎቹ ጠቅሰዋል። ክሶቹ “የፈጠሬ ክሶች” ናቸው ያሉት አስተባባሪዎቹ፣ ሁሉም ታሳሪዎች ያለምንም ቅድመ ኹኔታ እስኪፈቱና መንግሥት ለጤና ባለሙያዎች ጥያቄዎች “ተጨባጭ” እና “በጊዜ የተገደበ” መልስ እስኪሠጥ።የሥራ ማቆም አድማው እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በጋዜጠኞች ላይ ስለሚፈጸመው ተደጋጋሚ እስር ሲፒጄ ምን አለ?
በኢትዮጵያ ከመጋቢት ወር አጋማሽ እስከ ሚያዝያ ወር አጋማሽ ባለው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ 14 ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ሰራተኞች ለእስር ተዳርገው እንደነበር ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (ሲፒጄ) አስታወቀ። ከታሰሩት ጋዜጠኞች እና ሰራተኞች ውስጥ ሁለቱ አሁንም በእስር ላይ እንደሚገኙ ሲፒጄ ገልጿል።
ሲፔጄ ይህን የገለጸው፤ በየሀገራቱ ያሉ ጋዜጠኞችን የተመለከቱ ሰሞነኛ ጉዳዮችን አጠናቅሮ ይፋ በሚያደርግበት ዘገባ ላይ ነው። ድርጅቱ ትላንት አርብ ግንቦት 8፤ 2017 ባወጣው ዘገባ፤ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደተቀመጠች አስታውሷል።
በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞችን በተመለከተ ድርጅቱ በየዓመቱ በሚያወጣው ዓመታዊ ሪፖርት፤ ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት ከኢትዮጵያ በላቀ ጋዜጠኞች የታሰሩባት ሀገር ኤርትራ መሆኗ ተመልክቷል። ዓመታዊ ሪፖርቱ እስከተጠናቀረበት እስካለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ድረስ በኢትዮጵያ የታሰሩ ጋዜጠኞች ስድስት እንደነበሩ ሲፒጄ በትላንቱ ሪፖርቱ ጠቅሷል።
ይህ ቁጥር ባለፈው መጋቢት እና ሚያዝያ ወር በተፈጸሙ እስራቶች በከፍተኛ ሁኔታ አሻቅቦ ነበር። በመጋቢት ወር ከተፈጸሙ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እስሮች ከፍተኛው ቁጥር የተመዘገበው በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች ላይ ነው።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15939/
በሀገራዊ ምክክር ሂደት የሚታየው የምሁራን ተሳትፎ ከሚጠበቀው አንጻር “አነስተኛ ነው” ተባለ
በኢትዮጵያ ያሉ ምሁራን በሀገራዊ የምክክር ሂደት ላይ ያላቸው ተሳትፎ፤ ሊኖራቸው ከሚገባው “አስተዋጽኦ” አንጻር ሲታይ “አነስተኛ ነው” ሲሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ ተናገሩ። አብዛኞቹ ምሁራን ከሂደቱ “ራሳቸውን የማግለል” አሊያም ሁኔታውን “በዝምታ የመመልከት” አካሄዶችን የመከተል “አዝማሚያዎች” እንደሚታይባቸውም ገልጸዋል።
ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ይህን የገለጹት፤ በሀገራዊ የምክክር ሂደት ምሁራን የሚኖራቸውን ሚና በተመለከተ ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 9፤ 2017 በተካሄደ የውይይት መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። በአዲስ አበባው ሃይሌ ግራንድ ሪዞርት በተካሄደው በዚህ መርሃ ግብር ላይ ከአማራ፣ ኦሮሚያ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች የተመረጡ 90 ምሁራን ተሳትፈዋል።
ይህን መርሃ ግብር በንግግር የከፈቱት ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ፤ በሌሎች ሀገራት የተከናወኑ ሀገራዊ ምክክሮች “ውጤታማ እንዲሆኑ” ካደረጓቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ “የምሁራኖቻቸው አስተዋጽኦ” እንደሆነ አስገንዝበዋል። ምሁራን ሀገራዊ ምክክርን “በተለየ መልኩ ማየት አለባቸው” የሚል አቋም ኮሚሽኑ እንዳለው የጠቀሱት ሂሩት፤ ጉዳዩ “በአመለካከት ልዩነቶች ሳይጋረዱ” “ያለስስት አስተዋጽኦ ሊያበረክቱለት የሚገባ” እንደሆነም አሳስበዋል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15933/
ከኢግል ሂልስ ‘ላጋር ዋን’ ሳይት ቤት የገዙ ደንበኞች ገጠመን ያሉት አነጋጋሪ ክስተት
– “ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ቅድሚያ የከፈልነው ገንዘብ እና ቤቱ ራሱ እንደሚወሰድብን ማስጠንቀቂያ ደርሶናል”
– “አጥብቀን ስንጠይቅ ‘ይህ እኮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግላቸው የሚከታተሉት ፕሮጀክት ነው’ የሚል ማስፈራርያ አዘል ማሳሰቢያ ይሰጠናል”
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/fda?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
” ጥያቄ እየጠየቀ ያለን ባለሙያ ለማሸማቀቅ በሚመስል መልኩ እንደማስፈራሪያ መጠቀሙ ከአንድ ትልቅ ኃላፊነት ካለበት ተቋም አይጠበቅም ” – የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር
ከሰሞኑን የጤና ባለሙያዎች እንቅስቃሴ እና እያካሄዱ ካሉት ከፊል የሥራ ማቆም ጋር በተያያዘ 78 የሚሆኑ ባለሙያዎች በእስር ላይ እንደሚገኙ ባለሙያዎቹና የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ጤና ባለሙያዎቹ በሰጡት ቃል፣ ” ቀደሞ ከተፈቱት ውጪ አሁን በእስር ላይ የሚገኙት 78 ጤና ባለሙያዎች ናቸው ” ብለዋል።
” ይሄ ማለት እስከ ትላንት የደረሰን ዳታ ነው፤ የዛሬውን አልጨመርንበትም። የተፈቱትን ሳይጨሞር እንቅስቃሴው ከተጀመረበት ጊዜ ወዲህ ታስረው በእስር የሚገኙ ናቸው ” ብለዋል።
ዳታው በምን መልኩ ተሰበሰበ ? ትክክለኛነቱን በምን አረጋገጣችሁ ? ለሚለው ጥያቄ ” ዳታው ትክክለኛ ዳታ ነው። ከቤተሰቦቻቸው፣ ከጓደኞቻቸው፣ አብረዋቸው ከሚሰሩ የሆስፒታል ባለሙያዎች የተበሰቡ፣ ያሉበት እስር ቤት ጭምር የምናውቃቸው ናቸው ” ብለዋል።
የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኀበር በበኩሉ ፥ በእስር ላይ ይገኛሉ የተባሉት 78 ባለሙያዎች ዝርዝር እንደደረሰው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
” የታሰሩ ባለሙያዎች ዳታ በውስጥ ከመረጃ መሰብሰቢያ ቋት የደረሰን መረጃ ነው ” ብሏል።
” እስራቱና ድብደባው ቆሞ መንግስት ነገሩን ቆም ብሎ በማሰብ ጥያቄ እየነሳው ካለው ባለሙያው ጋር እልህ በመጋባት ታች ያለው ህብረተሰብ እንዳይጎዳ መጠንቀቅ ያስፈልጋል ” ሲልም አሳስቧል።
ማኅበሩ የትላንቱን የጤና ሚኒስቴር መግለጫ በተመለከተ በሰጠው አስተያየት ፥ ” ጤና ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ ከእውነታው የራቀና ትክክለኛ ጥያቄ እያቀረቡ ያሉ ጤና ባለሙያዎችን ‘በሃሰተኛ መረጃ የተወናበዱ’፣ ‘ምንም
Posted in
News,
ኢትዮጵያ,
ኤኮኖሚ
የኢትዮጵያ የሕክምና ባለሙያዎች ማኅበር፣ ከሥራ ማቆም አድማ ጋር በተያያዘ ከ78 በላይ የጤና ባለሙያዎች መታሠራቸውን ገልጸዋል። የሥራ ማቆም አድማው አስተባባሪዎችም፣ የጤና ሚንስቴር በአድማ ላይ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ባስቸኳይ ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ ያወጣውን ማስጠንቀቂያ አጣጥለዋል። ሚንስቴሩ ሁሉም ሆስፒታሎች አገልግሎት እየሠጡ እንደሆነ መግለጡን ያስተባበሉት አስተባባሪዎቹ፣ በርካታ ሆስፒታሎች ከፊል አገልግሎት እየሠጡ እንዳልኾነ ገልጸዋል። ሚንስቴሩ በዚህ አካሄዱ ከቀጠለ፣ ሁሉም ጥያቄዎች ምላሽ እስኪያገኙ፣ በእስር ላይ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ እስኪፈቱና በጥያቄዎቹ ላይ ድርድር እስኪደረግ ድረድ፣ የጤና ባለሙያዎች ከቀጣዩ ሰኞ ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ሙሉ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉም አስተባባሪዎቹ አስጠንቅቀዋል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ሃይል ጎጃም ቀጣና ጃዊ መተከል 4ኛ ክ/ጦር መተከል ጣና በለስ ብርጌድ እና መብረቁ ብርጌድ በጥምረት በሰሩት አስደናቂ ኦፕሬሽን በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረስ ችለዋል። በቀን 08/09/2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 12:30 ሰዓት ወደ ፓዊ ወረዳ መንደር 26 ቀበሌ ሰርገዉ በመግባት በመከላከያ ካምፕ ላይ በተፈፀመ ጥቃት 10 የጠላት ሀይል ሲደመሰስ 15 ከባድ እና ቀላል ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል።
ሌላዉ 2 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከእነ ሙሉ ትጥቃቸዉ የመተከል ጣና በለስ ብርጌድን ተቀላቅለዋል። “ድል ለተገፋዉ ለሰፊው የአማራ ህዝብ” !!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ጎጃም ቀጠና ጃዊ መተከል 4ኛ ክፍለ ጦር ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ያዕቆብ ጌታሁን
ከህወሓት መሰረዝ በኋላ የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት እጣፈንታ ምንድነው ?
“ የህወሓት ሙሉ በሙሉ ህጋዊ ሰውነት ማጣት የፕሪቶሪያውን ስምምነት አይሽረውም፡፡ በህወሓት የተፈረመውን የፕሪቶርያ ስምምነት የሚፈፅም አካል በዛው ስምምነት ተወልዷል እሱም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ነው ” – አቶ ያሬድ ኃይለማርያም
የህወሓት ከፓርቲነት መሰረዝና የህግ ባለሙያ አስተያየት !
የህወሓት ጉዳይ ፖለቲካዊ መፍትሔ ነበር የሚያስፈልገው ?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ህወሓትን ከፖለቲካ ፓርቲነት ሰርዞታል።
ይህን አስመልክቶ አንድ የህግ ባለሙያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሙያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ሙያዊ ማብራሪያ የሰጡት የህግ ባለሙያውና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች አቶ ያሬድ ኃይለማርያም ሲሆኑ የህወሓት ጉዳይ በደረቅ ህግ ሳይሆን በፖለቲካዊ መንገድ መታየት ነበረበት ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተለያየ ዕድሜ፣ የአመሰራረት ታሪክና ቁመና እንዳላቸው የገለፁት ባለሙያው፣ እነዚህን ፓርቲዎች በአንድ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጦ በአንድ ህግ ብቻ ማየት ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡
የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት በራሱ የሕወሓትን እጣፈንታ መበየን ሲገባው፣ ይህን ጉዳይ ጨምሮ ስምምነቱ ያላያቸውና ያልተብራሩ በርካታ ጉዳዮች አሉ ያሉት ባለሙያው፣ ስምምነቱ ጥቅል ጉዳዮችን በቻ የያዘ ስለሆነ፣ በሌሎች ሰነዶች መብራራት ነበረበት በማለት ገልፀዋል፡፡
የህግ ባለሙያው በዝርዝር ምን አሉ ?
” ምርጫ ቦርድ በህወሓት ላይ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች ህጉን የተከተሉ ሲሆኑ፣ በህወሓት የሚነሱት ጉዳዮች ደግሞ ፖለቲካዊ ናቸው፡፡
‘ እንደ አዲስ ፓርቲ መመዝገብ የለብኝም፣ ለረዥም ጊዜ የነበረ ፓርቲ ነው፣ እንደነባር ፓርቲ ነው የምንቀጥለው እንጂ ዛሬ እንደሚመሰረት አዲስ ፓርቲ አዲስ ምዝገባ ማድረግ
በ2024 ምን ያህል ሰዎች ተፈናቀሉ ?
ዓለም አቀፉ የተፈናቃዮች ክትትል ማዕከል (IDMC) ያለፈው የፈረንጆቹ ዓመት 2024 በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች (IDP) ቁጥር የተመዘገበበት ሆኗል ሲል በዓመቱ 83.4 ሚሊዮን ሰዎች መፈናቀላቸውን ገልጿል ።
በተለያዩ አከባቢዎች የተነሱ ግጭቶችና አመጾች መበራከት የተፈናቃዮች ቁጥር ከፍተኛ ጭማሪ ለማሳየቱ ምክንያት ነው ሲባል በዚህ ብቻ ለ73.5 ሚሊዮን ሰዎችን ተፈናቅለዋል።
በዓመቱ በተከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎች በአንጻሩ ለ 9.8 ሚሊዮን ሰዎች በምክንያትነት ተቀምጧል።
ሱዳን በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር ከፍተኛውን ድርሻ በዓመቱ የያዘች ሲሆን 11.6 ሚሊየን ሱዳናዊያን ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል። ሶሪያ፣ ጋዛ እና ዩክሬን በከፍተኛ ሁኔታ ዜጎቻቸው የተፈናቀሉባቸው ሀገራት ናቸው።
29 ሃገራት በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ምክንያት ዜጎቻቸው እንደተፈናቀሉ መግለፃቸውን የጠቀሰው ድርጅቱ በ2024 የተመዘገበው የውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥርም ከፍተኛው እንደሆነ አንስቷል
ድርጅቱ ኢትዮጵያን በተመለከተ በሪፖርቱ ውስጥ ያካተተ ሲሆን በ 2024 2.4 ሚሊየን በላይ ዜጎች በሀገር ውስጥ መፈናቀላቸውን ሲገልጽ ከ80 በመቶ በላዩ የተፈናቀሉት ከግጭት ጋር በተያያዘ መሆኑን አስታውቋል።
በ2023 በአለም አቀፍ ደረጃ የውስጥ ተፈናቃይ የነበሩ ሰዎች ቁጥር 75.9 ሚሊየን ነበር። https://www.internal-displacement.org/countries/ethiopia/