Home › Archive for VIDEO ቪዲዮ
Blog Archives
” ቤቴና መሶቤ ሙሉ ነበር ከቀዬ ከተፈናቀለኩ በኃላ ግን ሁሉ ባዶ ታሪክ ሆኗል ፤ እኔና 6 ቤተሰቦቼ ከምንበላው ጦማችን የምናድርበት ጊዜ ይበዛል ድረሱልን ” – በመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃይ
➡️ ” ጊዚያዊ አስተዳደሩና የመንግስት መዋቅሩ ረሀቡ መከሰቱ በማህበራዊ የትስስር ገፃች ከመነገሩ በኃላ መንቃቱ የአመራር ክፍተት ዋነኛ ማሳያ ነው ” – አስተያየየት ሰጪዎች
በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አስገደ ወረዳ ከእንዳስላሰ-ሽረ ከተማ አቅራቢያ የምትገኘው #ሕፃፅ ከደም አፈሳሹ የትግራይ ጦርነት በፊት የኤርትራ ስደተኞች ማቆያ በመሆን ትታወቃለች።
በሕፃፅ የስደተኞችና የተፈናቃዮች የመጠለያ ጣብያ የዛሬውን ያህል በእህል፤ ውሃና ህክምና እጦት የገረጡ ፊቶች ታይተው አያውቁም።
ሕፃፅ በዙሪያዋ ከሚገኘው የወርቅ ማዕድን ሀብት በሚሊዮን የሚገመት ብር የሚዛቅበት ሆና ሳለ በጉያዋ ግን በሀይለኛ ረሀብና ውሃ ጥም ተፈናቃዮች ወደ መቃብር ይሸኙባታል።
አርሶ አደር ጉዕሽ በትግራዩ ጦርነት ምክንያት ከምዕራባዊ ዞን አደባይ ከተባለ ሰፊ እርሻ ያለበት ቦታ ተፈናቅለው በሕፃፅ የመጠለያ ጣብያ በአሮጌ ፕላስቲክ በተሰራ ቤት መኖር ከጀመሩ 5 ዓመታት ተቆጥረዋል።
አርሶ አደሩ በመጠለያ ጣብያዋ ከሚገኙ 16 ሺህ ተፈናቃዮች መካከል ሲሆኑ ‘ አስቸኳይ እርዳታ ካላገኙ ለቀናት እንኳን በህይወት መቆየት ይከብዳቸዋል ‘ ተብለው በዞኑ ከተጠኑ 1,700 በላይ የተቸገሩ ወገኖች አንዱ ናቸው።
በድስት ያረረ ወጥ እያሳዩ ” ቤቴና መሶቤ ሙሉ ነበር ከቀዬ ከተፈናቀለኩ በኃላ ግን ሁሉ ባዶ ታሪክ ሆኗል ፤ እኔና 6 ቤተሰቦቼ ከምንበላው እራት ጦማችን የምናድርበት ጊዜ ይበዛል ድረሱልን ” ሲሉ ተማፅነዋል።
ሌላኛዋ ራሷና
ላልተገራ ሥልጣን መታዘዝ እና ከአንባገነናዊ ባህሪ ጋር መዋሃድ፤ (ያሬድ ኃይለ ማርያም )
Obedience to authoritarian and internalization of authoritarian attitudes
+++++
“Blind obedience to authority is the greatest enemy of truth”
Albert Einstein
እንደምን ከረማችሁ የመልዕክተ ቅዳሜ ታዳሚዎች? አሰልሳ ብቅ ባለችው የዛሬዋ መልዕክተ ቅዳሜ ዋነኛ የትኩረት ነጥብ አንድ ማህበረሰብ ከአምባገነናዊ ሥርዓቶች ሳይላቀቅ ለረዥም ጊዜ በአፈና ውስጥ ሲቆይ እና በግፍ፣ ጭካኔ እና ሰቆቃ ውስጥ ሲኖር ከገዢዎቹ ከሚወርሳቸው ነገሮች አንዱ በሆነው ግፍን የመላመድና አንባገነናዊ ባህሪን የመላበስ ዝንባሌ ላይ የሚያተኩር ይሆናል፡፡
በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ልጽፍ ያሰብኩት ያለፈው ሳምንት ቅዳሜ ነበር፡፡ ምክንያቱም ሃሳቡ የመነጨው የብልጽግና አገዛዝ በአለባበሳችሁ ባህልን እና ልማድን አጉድፋችኋል በሚል ለተወሰኑ ቀናት ወይም ከሳምንት በላይ ለቆየ ጊዜ ያሰራቸውን ቲክቶከሮች ተከትሎ በማህበረሰባችን በጉል የነበረው ግብረ ምላሽ ያጫረብኝ ነገር ነበር፡፡ ቲክቶከሮቹ የአገሪቱን ባህል፣ ወግ እና ልማድ በሚጥስ መልኩ ለብሰው በአደባባይ በመታየታቸው በወንጀል ጠርጥሬ አስሬያቸዋለሁ ብሎ የፌደራል ፖሊስ መግለጫ ሲሰጥ በደቦ እልል እያለ ድጋፉን የሰጠው አብላጫው የማህበረሰባችን ክፍል ልጆቹ ሲፈቱ እና መንግስት ለምን እና እንዴት ሊፈታቸው እንደቻለ ምንም መግለጫ ሳይሰጥ ሲቀር ደግሞ ያሁሉ የባህል ተቆርቋሪ እና ተሟጋች እንዴት ተፈቱ? የወንጀሉሱ ጉዳይ? ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎችን አለማንሳቱ አግራሞት ስለጫረብኝ ነው ርዕሱን ሰፋ ባለ መንገድ ከማህበረሰብ ባህሪ ጋር በማያያዝ ልመለስበት የወደድኩት፡፡
የልጆቹን ጉዳይ ላቆየውና ከላይ በርዕሱ ላይ እንደገለጽኩት አንድ ማህበረሰብ ወይም የአንድ አገር ሕዝብ ምን ሁኔታዎች ሲገጥሙት
ካሜራ የተገጠመላቸው ገቢ ሰብሳቢዎች 11 ሰዓት ላይ ካሜራ ለቢሯቸው ካስረከቡ በኋላ ድጋሜ በመውጣት ዘረፋ ላይ እየተሰማሩ መሆኑ ታወቀ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ካሜራው ‘ሙሉ ለሙሉ ችግሩን ይቀርፋል’ ቢልም ገና ካሁኑ አንዳንድ ሰራተኞች የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ገንዘብ ዘረፋ መጀመራቸውን መሠረት ሚድያ አረጋግጧል።
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/11
ኢትዮጵያ በጋዛ የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ እንድትሳተፍ ከአሜሪካ ጥሪ እንደቀረበላት ተገለጸ።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከቀናት በፊት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ጋር በስልክ መነጋገራቸው መገለጹ ይታወሳል።
በወቅቱ በውይይቱ ሁለቱ ሀገራት ለቀጠናዊ መረጋጋት እና በአፍሪካ ቀንድ ሰላምን ለመገንባት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት የገለጹበት እንደነበር ስቴት ዲፖርትምንት በወቅቱ ገልጾ ነበር።
ዛሬ ታይምስ ኦፍ እስራኤል ይዞ በወጣው ዘገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በዚህ ውይይት ወቅት ኢትዮጵያ በጋዛ ሰርጥ በሚቋቋመው ዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይል ተሳታፊ እንድትሆን መጠየቃቸውን አንስቷል። ይሁን እንጂ ዘገባው የኢትዮጵያን ምላሽም ሆነ ዝርዝር ጉዳዮችን አላካተተም።
ማርኮ ሩቢዮ በአንድ ጋዜጣዊ መግለጫቸው “ያነጋገርናቸው ሀገራት ሁሉም በሚባል ደረጃ ወታደሮቻቸውን ለመላክ ምን ዓይነት ግዳጅ ውስጥ እንደሚገቡ እና የፋይናንስ አቅርቦቱ ምን እንደሚመስል ማወቅ እንደሚፈልጉ ጠቁመዋል።
ማርክ ሮቢዮ ይህንን የተናገሩት ፓኪስታን ወታደሮቿን ለማሰማራት ፈቃደኝነቷን መግለጿን ተከትሎ በቀረበላቸው ጥያቄ ውቅት ሲሆን የፓኪስታንን ጥያቄ “እያጤነው ነው” ሲሉም መልሰዋል።
አብዛኞቹ የአረብ ሀገራት ወታደሮቻቸውን ለመላክ “የፍልስጤም መንግስት ምስረታ የጊዜ ሰሌዳ በግልጽ እንዲቀመጥ” የሚል ጥብቅ ቅድመ ሁኔታ ሲያስቀምጡ አንዳንዶቹ የሰላም አስከባሪ ኃይሉ የእስራኤልን ወታደራዊ ፍላጎት ብቻ የሚያስፈጽም እንዳይሆን እና በሕዝባቸው ዘንድ “ተቃውሞ” እንዳያስነሳ ስጋት ገብቷቸዋል።
ማርኮ ሩቢዮ ሀገራት ወታደሮቻቸው ምን ዓይነት ግዳጅ ውስጥ እንደሚገቡ ሳያውቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ አንጠብቅም ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የጋዛ ዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪ ኃይል (ISF) በዋናነት ሰብዓዊ እርዳታዎች ለተጎጂዎች እንዲደርሱ ጥበቃ ማድረግን፣ የሲቪል አስተዳደሩን መደገፍ እና አካባቢው ዳግም
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት በታጣቂዎች ታግተው መሰዳቸውን፣ ሁለቱ ቢመለሱም ሦስቱ ባለመለቀቃቸው የአካባቢው አመራሮች ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ነዋሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ጠየቁ።
እገታው የተፈጸመው ከአርሲ ሮቤ 6 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ “አኪያ” በሚባል ቦታ መሆኑን ገልጸው፣ “አምስት የአንድ ቤተሰብ ወንዶች አዝመራ በውቂያ ሳሉ በአካባቢው ባሉ የሸኔ ታጣቂዎች ተወስደዋል” ሲሉ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የታጋቾች አባትና አያት የሆኑ የ90 አመት የእድሜ ባለጸጋ ደግሞ፣ ሦስት ልጆቻቸው እና ሁለት የልጅ ልጆቻቸውን በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
” ይህን ሊያሰማኝ አቆየኝ ” በማለት ሳግ የሚተናነቃቸው እኚሁ የእድሜ ባለጸጋ በገለጹት መሰረት፣ ልጆችና የልጅ ልጆቻቸው እህል ለመውቃት ነዶ ወደአውድማ እያስገቡ ባለበት ነው ” ከጫካ በወጡ የሸኔ ታጣቂዎች ” ታግተው የተወሰዱት።
እኝሁ አባት፣ ” ሐሙስ ታህሳስ 9 ቀን 2018 ዓ/ም ጠዋት 2 ሰዓት ተኩል ነው የእህል ነዶ እያጋዙ ባለበት የተወሰዱት። ነዶውን አውድማ አስገብተው ሊወቁ ነበር ” ነው ያሉት።
ምን ያክል ሰዎች እንደተወሰዱ ሲያስረዱም፣ “መጀመሪያ የተወሰዱት አምስት ናቸው፤ መጀመሪያ የተወሰዱት ሁለቱ የልጅ ልጆቼ ነበሩ ለቀቋቸው። ሦስቱን እንደወሰዷቸው ቀሩ ሦስቱ ልጆቼ ናቸው። ወደ ቄርቄር ውስጥ ከረዩ ስር ነው የወሰዷቸው” ብለዋል።
“አቆሙንና ‘የማናችሁ? አሉን’፣ ‘የአምዴ ነን አልናቸው’፤ ‘በሉ እናንተ ተመለሱ አሉን'” ሲሉ ከእገታ ተመላሾች መግለጻቸውን አስረድተው፣ “የተለቀቁት አባት አብሮ የታገተ ነው፤ የወሰዷቸው ከጫካ የወጡ ባለትጥቅ ናቸው” ብለዋል።
“እዚህ ነው ያሉት እንኳ አልተባልንም፤ ዝም ብለን ቁጭ ብለናል፤
” በሁለት ቀናት እስከ 20 ሰዎች ተገድለዋል፣ በአንድ ወረዳ ብቻ። በሌሎችም አሉ። ከሁለት ቀናት በፊትም በአቦል ወረዳ ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቁ በርካቶች ሞተዋል ” – የጋምቤላ ነዋሪዎች
➡️ ” በርካታ ቁስለኞች ወደ ህክምና ይላካሉ። በኛ ሆስፒታሉ የመጡት ብቻ ወደ 8 ይደርሳሉ። ጉዳት የደረሰባቸው ሦስት ሰዎች ወደ ጅማ ሪፈር ተደርገዋል” – በክልሉ በሚገኝ ሆስፒታል የሚሰሩ ሀኪም
በጋምቤላ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች በተለይ ከህዳር 30 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በተፈጠረው የሰላም መደፍረስ የበርካታ ንጹሐን ህይወት እየተቀጠፈ መሆኑን የሟች ቤተሰብ፣ ነዋሪዎችና በሆስፒታል የሚሰሩ ሀኪም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
አንዳንዶቹ የሟቾችንና ቁስለኞችን ቁጥር “ከ50 እስከ 60” ያደረሱት ሲሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ “ከዚያም የበለጠ ነው” ይላሉ። ከቀናት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ አንድ የክልሉ ባለስልጣን “የሟቾች ቁጥር ከ10 በላይ ሊሆን ይችላል” ብለው ነበር።
የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ማበር ኮር ደግሞ፣ ሰዎች መሞታቸውን አምነው፣ ብዛታቸው ግን “10 እንደማይሆን” ሰሞኑን ነግረውን የነበረ ሲሆን፣ ነዋሪዎችና ጤና ባለሙያዎች ዛሬ እንደነገሩን ከሆነ ደግሞ ጥቃቱ ባለመቆሙ የሟቾና ተጎጅዎች ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ ነው።
በሆስፒታል የሚሰሩ ሀኪምና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
ነዋሪዎቹ በሰጡን ቃል፣ “በሁለት ቀናት እስከ 20 ሰዎች ተገድለዋል በአንድ ወረዳ ብቻ። በሌሎችም አሉ። ከሁለት ቀናት በፊትም በአቦል ወረዳ ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቁ በርካቶች ሞተዋል” ብለዋል።
የ27 አመት ወጣት በጸጥታው ችግር የተገደለባቸው ነዋሪ፣ “በጥይት ተመትቶ ነው ያረፈው። ብዙ መንገዶች ዝግ ስለሆኑ በጥይት የተመቱ ሰዎች
ብፁዕ አቡነ ያሬድ ከምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ተነሱ። ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ሀገረ ስብከቱን እንዲመሩ ተመድበዋል።
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የምሥራቅ አርሲ ሀገረስብከትን እስከ ግንቦት የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ ድረስ ደርበው እንዲመሩ በቋሚ ሲኖዶስ ተመደቡ።
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ከሚመሩት ሀገረ ስብከት በተጨማሪ የምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከትን እስከ ግንቦት 2018 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ ድረስ ደርበው እየመሩ እንዲቆዩ በቋሚ ሲኖዶስ ተወስኖ በቅዱስ ፓትርያርኩ በተጻፈ ደብዳቤ ተመድበዋል።
ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከሚገኙ ካህናት፣ አባ ገዳዎች፣ሀደ ሲንቄዎች፣ ወጣቶችና ምዕመናን የቀረበለትን ተደጋጋሚ አቤቱታ ሲቀርብለት ነበር።
ይህን መነሻ በማድረግ አጣሪ ልዑክ መድቦ ችግሩ በዝርዝር ተጠንቶ እንዲቀርብለት ካደረገ በኋላ ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ብፁዕ አቡነ ያሬድ ከምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ተነስተው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሰቲያን የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስነት ሥራቸውን እያከናወኑ እስከ ግንቦት የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ እንዲቆዩ ውሳኔ አስተላልፏል።
የቅዱስ ሲኖስ ምልዐተ ጉባኤ ጥቅምት 2018 ዓ.ም ባደረገደው ጉባኤ ቋሚ ሲኖዶስ የተከሰተውን ችግር በመመርመር መፍትሔ እንዲሰጥ ውሳኔ ማሰተላለፉ ይታወሳል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው
ፓርላማ ውስጥ ያሉ አንዳንድ የመንግስት ተጠሪዎችና የፅህፈት ቤት ሀላፊዎች በውጭ ጉዞ ስም የሚቀበሉት የአየር ትኬት ላይ ማጭበርበር እንደሚፈፅሙ ታወቀ
“ከጉዞ ከቀሩ ለመንግስት ተመላሽ ይደረጋል እንጂ እንዴት ይሰረቃል?”
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/ba0
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ የአሜሪካን ግሪን ካርድ ሎተሪን (ዲቪ) አገደ። የዲቪ ሎተሪ ፕሮግራም የታገደው፣ ከቀናት በፊት አንድ በዲቪ ሎተሪ ወደ አሜሪካ የገባ የፖርቹጋል ተወላጅ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በኹለት ሰዎች ላይ ከፈጸመው ግድያ ጋር በተያያዘ እንደኾነ ተገልጧል።
የአሜሪካ ባለሥልጣናት፣ በዲቪ ፕሮግራም ወደ አገሪቱ በሚገቡ ሰዎች ምክንያት በአሜሪካዊያን ላይ ከእንግዲህ ጉዳት እንዳይደርስ ለማረጋገጥ እገዳውን መጣል እንዳስፈለገ ተናግረዋል።
ፕሮግራሙ ለተለያዩ አገራት ዜጎች በየዓመቱ 50 ሺሕ የመኖሪያና ዜግነት ማግኛ ቪዛዎችን ሲሠጥ የቆየ ሲኾን፣ ባለፉት 30 ዓመታት ከ3 ሺሕ 600 በላይ ኢትዮጵያዊያን የእድሉ ተጠቃሚ ኾነዋል።
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረመስቀል፣ የኢትዮጵያው ብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች ኤርትራ ከኢጋድ መውጣቷ “የመነጠል አጀንዳዋ” እና “ለበይነ መንግሥታታት መድረኮች ያላት ጥላቻ” ማሳያ ነው በማለት ላይ ይገኛሉ ሲሉ ተቹ። የማነ፣ ኾኖም ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ስትፈራረም እና ከዚያም ኢትዮጵያ ራሷ የምትቆጣጠረው የባሕር በር አጀንዳ ስታራምድ ኢጋድ ዝምታን መምረጡ፣ ለኤርትራ እና ሌሎች ተጎጂ አገራት እዳ እንዲሆን አድርጎታል በማለት ወቅሠዋል። የብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች ባኹኑ ወቅት በኤርትራ ላይ የማጥላላት ዘመቻ የሚያካሂዱት፣ የፓርቲውን “የራስ የባሕር በር አጀንዳ አቅጣጫ በማስቀየር የተጎጂነትና ራስን የመከላከል ዘመቻ አድርጎ ለማቅረብ ነው” በማለትም የማነ አጣጥለዋል። ለዚህ ግብ አንዱ ስልት ኤርትራን የኢትዮጵያ እና የቀጠናው “በጥባጭ” አድርጎ ማቅረብ ነው ያሉት የማነ፣ ይህ ተቀባይነት እንዲኖረው ማድረግ ግን እጅግ ይከብዳቸዋል ብለዋል።
ለጥይት መግዣ እና ለብልፅግና ፓርቲ ህንፃ ግንባታ የሚል አዲስ አስገዳጅ የህዝብ መዋጮ በበርካታ ቦታዎች መጀመሩ ታወቀ
“ለአስተዳደር ህንጻ ግንባታ ከደሞዛችን ስንቆርጥ ከርመን የጨረስነው ከወር በፊት ነው፣ አሁን ደግሞ ለፓርቲ ተባልን”- የካፋ ዞን ጎባ ወረዳ የመንግስት ሠራተኞች
– “ለጥይት መግዣ ብር አምጡ ብለው እያስፈራሩን ነው። በዚህ ስራ በሌለበት ወቅት ከየት አምጥተን ነው ምንከፍለው?”- የምዕራብ ሸዋ ዞን አደአ በርጋ ወረዳ ነዋሪዎች
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/0af
የአማራ ማሕበር በሎሳንጀለስ አንዳንድ አካላት በሕገወጥ መንገድ የማህበራችንን ስምና አርማ እየተጠቀሙ ነው ሲል ከሰሰ

https://x.com/Amharas_Of_LA/status/2002243576424772088
በደብረወርቅ ከተማ በተደረገ ውጊያ ከተገደሉ የወረዳ አመራሮችና የአድማ ብተና እንዲሁም የሚኒሻ አባላት መካከል የጥቂቶቹ ስም ዝርዝር ይፋ ሆኗል!
በደብረወርቅ ከተማ ትናንት ታህሳስ 07/2018 ዓ/ም በተደረገ ውጊያ ከ50 በላይ የበአዴን ወታደሮች ሲገደሉ 27 ክላሽንኮቭ መሣሪያ መማረኩን መረብ ሚዲያ የቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያን ዋቢ አድርጎ መዘገቡ አይዘነጋም።
በከተማዋ በተካሄደው ውጊያ በወቅታዊ ጉዳይ ማለትም ፋኖን ትደግፋላችሁ፣ የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ በሚል ታስረው የነበሩ ከ100 በላይ የግፍ እስረኞች ፋኖ እንዳስለቀቃቸው ታውቋል።
በዚህም በውጊያው ከተገደሉት መካከል፦
1ኛ ደመላሽ ካሳ የወረዳ አስተዳደር መረጃ ሀላፊ
2ኛ ሳጅን ምትኩ ሞላ ፖሊስ
3ኛ ሳጅን እንዳወቀ አማረ ፖሊስ
4ኛ አልኸኝ አያል ሚኒሻ
5ኛ ይሔነው እንዳላመው ሚኒሻ
6ኛ ጌታየ ቢረሰው ሚኒሻ
7ኛ ባየ አልሀኝ ሚኒሻ
8ኛ ያለው ታረቀኝ ሚኒሻ
9ኛ ተዋቸው አፍኔ ሚኒሻ
10ኛ ጌታሠው እስካሁን ሚኒሻ
11ኛ ካሰው አቻም ሚኒሻ
12ኛ አሰፋ ማርኬ ሚኒሻ
13ኛ ጌታሰው ቢረሰው ሚኒሻ
እነዚህ በስም የታወቁት ሲሆኑ በስም ያልተጠቀሱ በርካታ የጠላት አባላት ተገድለዋል።
ጥብቅና የሚቆም በሌለበትና ገዳይ “በማይታወቅበት” የቀጠለው የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮችን የማጽዳት ተልዕኮ አኹንም ቀጥሏል!
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)
በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች በኦርቶዶክስ እምነትና ንጹሓን ዜጎች ላይ የተጀመረው የማጽዳት ዘመቻ ከአርሲ ወደ ወለጋ ፊቱን በማቅናት የሆሮ ጉድሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ኡፋ እና ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ በዓል ለማክበር በወጡበት ከኅዳር 21 ጀምረው ሻምቡ መግቢያ አካባቢ ታግተው ቅዳሜ ታኅሣስ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአጋቾች መገደላቸውንና በአባትነት በተመላለሱበት ምድር የቀብር አፈር ተነፍገው አስከሬናቸውም እንዳልተገኘ እንዳልተቀበሩ ከቦታው ለማረጋገጥ ችለናል። አኹንም ገዳዮቹ ለላፉት 7 ዓመታት በሚገድሉብት የዳቦ ስም “ታጣቂዎች” ናቸው በሚል መሸፈኑ ነገሩን አስገራሚም ግራ አጋቢም አድርጎታል። ከቦታው በደረሰን መረጃ መሠረት ግድያውን የፈጸሙት አስከሬንም የከለከሉት በሻምቡ አካባቢ ይንቀሳቀሳል የሚባለው ኦነግ ሸኔ(ራሱን ኦነሰ ብሎ የሚጠራው) ኃይል መኾኑን ደርሰንበታል፤ በከተማ የሚኖሩ በተባባሪነትና በጥቆማም የተሳተፉ ሊኖሩ እንደሚችሉ ፍንጮች አሉ፡፡
የቤተ ክርስቲያን አባቶችንና ምዕመናን ግድያ ስልታዊ በኾነ የሚፈጸም የዘር ማጽዳት ዘመቻ አካል እንጂ ድንገቴ እንዳልኾነ በጽኑ እናምናለን። እንደ ቀደሙት ግድያዎች ኹሉ በዚኽም ላይ ገዳዮችን አድኖ ፍትሕ እንዲሰፍን የሚወሰድ እርምጃ አይደለም ለሞቱ እውቅና እንኳን ያለመስጠት ብሎም ለወትሮው እንደሚደረገው የማስተባበል አዝማሚያ ነገሩ ምን ያኽል የተቀናጀና በጥንቃቄ የሚፈጸም ስለመኾኑ ማሳያ አድርጎ መውሰድ ይቻላል። ቀሲስ ዱጉማ የ6 ልጆች አባት ሲኾኑ ቀሲስ ደሳለኝ የመንግሥት ሠራተኛና የኹለት ልጆች አባት ናቸው፡፡
በአንጻሩ ለእነዚህ በእምነታቸውና በሃይማኖታዊ ተልዕኮዋቸው ምክንያት ለተገደሉ ወገኖቻችን

የፎቶው ባለመብት,Getty Images
የምስሉ መግለጫ,ባለፈው ዓመት ሐምሌ ላይ የአሜሪካ የፀጥታ ሠራተኞች አንድ ስደተኛን የስደተኞች ጉዳይ ከሚታይበት ችሎት ይዘው ሲወጡ
16 ታህሳስ 2025
የአሜሪካ መንግሥት ከሦስት ዓመት በፊት ኢትዮጵያውያን በጊዜያዊ የሕግ ከለላ በአገሪቱ ውስጥ እንዲኖሩ እንዲሠሩ የፈቀደበትን አሠራር እንዲያከትም ወስኗል።
በትግራይ ጦርነት ምክንያት በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ለኢትዮጵያውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ሲሰጥ የነበረው ጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ መነሳቱን ተከትሎ፤ ከለላው ተሰጥቷቸው የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከአሜሪካ ለመውጣት የ60 ቀናት ጊዜ ተሰጥቷቸዋል።
የአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖም “የአገሪቱን ሁኔታ በመመርመር እና ከሚመለከታቸው የአሜሪካ መንግሥት አካላት ጋር በመመካከር” ኢትዮጵያ ለጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎችን “የማታሟላ አገር ናት” የሚል ውሳኔ መተላለፉን አስታውቀዋል።
በ60 ቀናት አሜሪካን ለቅቀው እንዲወጡ የተነገራቸው ኢትዮጵያዊያን ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይችላል? ጊዜያዊ የሕግ ጥበቃ የሚሰጥባቸው ሁኔታዎችስ የትኞቹ ናቸው? የሚለውን በተመለከተ በአሜሪካ ከአሥር ዓመት በላይ የሠሩትን የሕግ ባለሙያ ሙሉዓለም ጌታቸው አድገህ አነጋግረናል።
ጊዜያዊ ከለላ ምንድን ነው? በምን ዓይነት ሁኔታስ ይሰጣል?
የአሜሪካ መንግሥት ጊዜያዊ ጥበቃ ወይም ከለላ መስጠት የጀመረው በአውሮፓውያኑ 1991 ሲሆን፤ ይህ መብት የሚሰጠው በአገራቸው ግጭት፣ ጦርነት፣ የተፈጥሮ አደጋ ወይም ሌላ ለደኅንነታቸው አስጊ የሆነ ክስተት ለገጠማቸው ስደተኞች ነው።
Temporary Protected Status ወይም TPS ከተሰጣቸው አገራት መካከል ሶማሊያ እና ሶሪያ (ከጦርነት ጋር በተያያዘ) እንዲሁም ኤል ሳልቫዶር (ከርዕደ መሬት ጋር በተያያዘ) ይጠቀሳሉ።
ለአንዳንድ አገራት እስከ 20 ዓመት የዘለቀ ከለላ ተሰጥቷል። ለምሳሌ የሶማሊያ ጊዜያዊ ጥበቃ

የፎቶው ባለመብት,EOTC
የምስሉ መግለጫ,በታጣቂዎች ከተገደሉት መካከል መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ
16 ታህሳስ 2025
በኦሮሚያ ክልል፣ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሁለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች በታጣቂዎች ከተገደሉ ቀናት ቢቆጠርም አስከሬናቸው እንዳልተገኘ ተገለጸ።
ኅዳር 21 ቀን 2016 ዓ. ም. ቀሳውስቱ በሀራቶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ ክብረ በዓል ታድመው ወደ ሻምቡ ከተማ እየተመለሱ ሳለ ነበር መኪናቸው በታጣቂዎች እንዲቆም ከተደረገ በኋላ ወደ ጫካ ተወስደው የተገደሉት።
በጉዞው ላይ አብረዋቸው ከነበሩት ቀሳውስት አንደኛው “በጅማ ገነቲ አካባቢ የቅድስት ማርያም ክብረ በዓል ነበር። ከሥነ ሥርዓቱ ስንመለስ 9 ሰዓት አካባቢ ታጣቂዎች አስቆሙን” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
እኝህ የዐይን እማኝ በመኪናው ተሳፍረው የነበሩት “20 ሰዎች” እንደሆኑ ገልጸው፤ “ከ20ዎቹ መካከል አስሩን አስወርደው ወደ ጫካ ወሰዷቸው። የተቀሩት በበቆሎ ማሳ ውስጥ ተበታትነው በመሮጥ አመለጡ” ብለዋል።
ቄሱ እንደገለጹት፤ ታጣቂዎቹ በሻምቡ ከተማ መግቢያ ላይ መንገድ ዘግተው እና ስናይፐር መሣሪያ ይዘው ነበር።
ወደ ጫካ አካባቢ ከተወሰዱት ቀሳውስት መካከል የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ አገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ ሕጻናት እና መዘምራን እንደሚገኙበትም ተናግረዋል።
“ጫካው ውስጥ ወስደው በስም ጠሯቸው። አንድ በአንድ በስም ከጠሯቸው በኋላ ልጆቹ ታጣቂዎቹ ከያዙት የስም ዝርዝር ውስጥ ስላልነበሩ ለቀቋቸው” ብለዋል።
“አራቱ ሰዎች የሆሮ ጉዱሩ አገረ ስብከት ዋና ኃላፊ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ፣ ቄስ ቀናሳ ጊዲሳ፣ ቄስ ደሳለኝ ነሞምሳ እና ቄስ ባቡሽን ጠሩ ናቸው” ሲሉም በስም ጠቅሰዋል።
ታጣቂዎቹ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባላት ናቸው ሲሉም
ከኦፌኮ በመውጣት አዲስ መንገድ በማማተር ላይ ያሉ ፖለቲከኛ
በኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) በከፍተኛ አመራርነት ለዓመታት ያገለገሉ ፖለቲከኛ ደስታ ዲንቃ ከፓርቲው መውጣታቸውን አረጋገጡ፡፡
ፖለቲከኛው ከሌሎች የትግል አጋሮቻቸው ጋር በመሆን በሌላ የፖለቲካ ድርጅት ለመምጣት መንገድ ስለመጀመራቸውም ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡
የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት..
ከአንጋፋውየኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረንስ (ኦፌኮ)የመውጣት ውሳኔያቸው እራሳቸውን ከፖለቲካው ዓለም የማራቅ ፍላጎት ተደርጎ እንዳይወሰድ የገለጹት ፖለቲከኛ ደስታ ዲንቃ፤ ለዓመታት በትላልቅ ኃላፊነቶች ካገለገሉት የፖለቲካ ድርጅት ለመውጣት የገፋቸው ዋናው ምክንያት በእርሳቸው እና በኦፌኮ መካከል ያለው የፖለቲካ አመለካከት አለመግባባት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
“የእኔ የፖለቲካ አመለካከትና የፖለቲካ አስተዳደር ከሌሎች የተለየ እንደሆነ እረዳለሁ” ያሉት ፖለቲከኛ ደስታ ባሁን ወቅት በአገሪቱ “ከጫፍ ጫፍ የሚስተዋሉ አለመረጋጋቶች” እንቅልፍ እንደሚነሱአቸው በመግለጽ ከሳቸው ጋር ተመሳሳይ ሃሳብ ካላቸው ዜጎች ጋር በመሆን በተለየ አቀራረብና አያያዝ በአዲስ የፖለቲካ ድርጅት ለመምጣት ማቀዳቸውንም አስረድተዋል፡፡
የፖለቲካው ውጣ ውረድ
በኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረንስ ውስጥ ከሌሎች ጓዶቻቸው ጋር በመሆን በርካታ የፖለቲካ ስራዎችን መስራታቸውን የሚያምኑት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ምሩቅና የቀድሞ ጠበቃና የህግ ባለሙያ የአሁኑ ፖለቲከኛ አቶ ደስታ ዲንቃ፤ በፖለቲካው ህይወታቸው ከአካላዊ ጥቃት እስከ ቤተሰብ ስቃይ ያደረሳቸው አባጣ ጎባጣ መንገድ ላይ ማለፋቸውንም ያስታውሳሉ፡፡

ከፖለቲከኛ ደስታ ዲንቃ ጋር ኦፌኮን የለቀቁ ስለመኖራቸው ይነገራልምስል፦ Desta Dinka via Seyoum Getu DW
ፖለቲከኛው ከምስረታው ጀምሮ አባልና አመራር ከነበሩበት ኦፌኮ በተለየ መንገድ ላይ እንዲቆሙ ካደረጉአቸው ጉዳዮች ከ2013 ዓ.ም. ስድስተኛው ብሔራዊ ምርጫ የመገለል ውሳኔ እና ሌሎችም መኖራቸውን ጠቃቅሰዋል፡፡ “መድረክ ውስጥ
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ አቅራቢያ ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቤተክርስቲያን አገልግሎት በሚመለሱበት ወቅት በታጠቁ አካላት ተይዘው ከተወሰዱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን አገልጋዮች መካከል ሁለት ካህናት ተገደሉ፡፡
ከታገቱ ከሁለት ሳምንታት ግድም በኋላ ከትናንት በስቲያ ቅዳሜ ታህሳስ 04 ቀን 2018 ዓ.ም. መገደላቸው ይፋ የሆነው የአገረስብከቱ ስራአስከያጅ እና አንድ ሌላ አገልጋይ የታገቱት በዞኑ በጅማ ገነቲ ወረዳ የምትገኝ ቀዲዳ ማሪያም ቤተክርስቲያን አገልግሎት ውለው ወደ ሻምቡ ከተማ በምመለሱበት ወቅት በመንገድ ላይ ባደፈጡ ታጣቂዎች እንደሆነ የአይን እማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡
በእለቱ ህዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ወደ ጅማ-ገነቲ ወረዳ ሀራቶ ከተማ ቀዲዳ ማሪያም ለአገልግሎት ተጉዘው የነበሩት የሀገረስብከቱ አገልጋዮች ላይ እገታው የተፈጸመው ጬካ-አባጀና በሚባል ደናማ ስፍራ ነው ተብሏል፡፡ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር በምትገኘው ሐረቶ ማርያም በዓሉን አክብረው ሲመለሱ ከነበሩት የቤተክርስቲያን አገልጋዮች መካከል የሀሮሮጉዱሩ ሀገረስብከት ስራአስከያጅ መልአከ ኤዶም ቀሲስ ዱጉማ ዱፋ እና ሌላው የቤተክስቲያን አገልጋይ ቀሲስ ደሳለኝ ነሞምሳ ቅዳሜ ዕለት መገደላቸው ተረጋግጧልም ተብሏል::
እገታው እንዴት ተፈጸመ?
በእለቱ በታጣቂዎች ተገድለዋል ከተባሉት ሁለቱ ካህናት ጋር ከአገልግሎት ስመለሱ የነበሩና በታጣቂዎች እገታ ወቅት በዚያው የነበሩ አንድ ለደህንነታቸው ስባል ግን ስማቸውን ከመግለጽ የተቆጠቡት የአይን እማኝ ለዶይቼ ቬለ እንደነገሩት፤ እገታው የተፈጸመባቸው በአገረስብከቱ ተሽከርካሪ ወደ ሻምቡ ከተማ በመጓዝ ላይ ሳሉ ነበር፡፡ “በእለቱ ከታገቱት መካከል እኔ አንዱ ነበርኩ” ያሉን የአይን እማኙ በርካቶች ያመለጥነው ታጣቂዎች ወደ ሚፈልጉት አቅጣጫ ከመጓዝ ይልቅ
በኢትዮጵያ እዳ እና ሀብት ዙርያ በፓርላማ ሊደረግ የነበረ ወሳኝ ውይይት አነጋጋሪ በሆነ ምክንያት ለሌላ ግዜ መተላለፉ ተሰማ፣ ዝርዝሩን ይዘናል
“የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ‘ይህ ሁሉ ሚዲያ ምንድን ነው? ብለው ከአዳራሹ ወጥተው ስልክ ካወሩ በኋላ ውሳኔውን አሳውቀዋል”
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/7f9
በደቡብ ኦሞ ዞን እንደ አዲስ እየተስፋፋ በመጣው የማርበርግ ቫይረስ ሁለት ወንድማማቾች በቀናት ልዩነት ህይወታቸው ማለፉ ታወቀ
“ወጣቱ በታመመ ሰዓት ሊጠይቁት የሄዱ በርካታ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ስለነበሩ እነሱም በሙሉ ተለይተው ወደ ለይቶ ማቆያ ገብተዋል”
ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/da4
ነውረኛው ብልፅግና ቡድን በጉልበት ስራ የተሰማሩ ወጣቶችን አፍኖ “የሰላም አማራጭ የተቀበሉ ታጣቂዎች” በሚል ሐሰተኛ መረጃ እያሰራጨ መሆኑ ታውቋል።
ከጉልበት ሰራተኞች በተጨማሪ የባጃጅ አስከርካሪዎችንና የሊስትሮ ባለሙያዎችን በማፈን ነው የሐሰተኛ ፕሮፖጋንዳው ሰለባ ያደረጋቸው።
አገዛዙ እስረኞችን ሰብስቦ “የሰላም አማራጭ የተቀበሉ ታጣቂዎች” በሚል በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች ሰልፍ ሊያካሂድ መሆኑን ነው የመረብ ሚዲያ ምንጮች የገለፁት።
አገዛዙ በተለይ በደብረማርቆስ ከተማ በርካታ ቁጥር ያላቸው በጉልበት ስራና በሌሎች የስራ መስኮች ተሰማርተው የነበሩ ወጣቶች አፍኖ ወደ ባህርዳር የወሰዳቸው ሲሆን፡ በተመሣሣይ በሌሎች ከተሞችም ወጣቶችን እያፈነ ሊያካሂድ ላሰበው የሰልፍ ትርኢት እያዘጋጃቸው መሆኑ ታውቋል።
በየከተማው በገፍ እየታፈሱ ከሚገኙ ወጣቶች መካከል ተከታታይነት ያለው መድሀኒት የሚወስዱና የአዕምሮ ሕሙማን ጭምር እንደሚገኙበት ነው ጣቢያችን መረብ ሚዲያ ካሰባሰበው መረጃ ለማረጋገጥ የቻለው።
የብሔራዊ ተሐድሶ ኮሚሽን “እጅ የሚሰጡ የፋኖ አመራሮችንና አባሎችን በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች የሰልፍ ትርኢት በማድረግ ለማሳየት እቅድ መያዙን ጣቢያችን ከሰሞኑ መዘገቡ አይዘነጋም።
የተሐድሶ ኮሚሽኑ፡ እጅ የሰጡ ታጣቂዎች በሚል ሰልፍ ለማካሄድ እቅድ ይዞ የነበረው ሰሞኑን እነማስረሻ ሰጤ እጃቸውን መስጠታቸውን ተከትሎ ብዙ ኃይል እናመጣለን ያሉትን ተማምኖ ነው ተብሏል።
ነገር ግን እነማስረሻ እናመጣለን ያሉትን ኃይል ማምጣት ባለመቻላቸው “እጅ ይሰጣሉ ያላችኋቸው የፋኖ አመራሮች እስካሁን ለምን አልሰጡም?” በሚል ኮሚሽኑ እነማስረሻ ሰጤን በደብዳቤ ጠይቋል።
የተሐድሶ ኮሚሽኑ፡ እነ ማስረሻ “አባሎቻችን ይመጣሉ” ባሉበት ቀን ባለማምጣታቸው የሰልፍ ፕሮግራሙ እንደተጓተተበት ገልፆ፡ “በአጭር ቀናት ውስጥ እንዲመጡ አስደርጉ” ሲል በምክትል ኮሚሽነሩ ብርጋዲየር ጄነራል ደርቤ መኩሪያ የተፈረመበት የማስጠንቀቂያ
ደቡብ አፍሪካ 14 ኢትዮጵያውያን ዜጎች ወደ ሃገሯ ሊገቡ ሲሉ በኤርፖርት መያዟን አስታውቃለች።
የደቡብ አፍሪካ የድንበር አስተዳደር ባለስልጣን 5 ወንድና 9 ሴት ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ወደ “OR Tambo” አለም አቀፍ ኤርፖርት ቢደርሱም የመጡበት መንገድ አጠራጣሪ ሆኖ ስላገኘው ለተጨማሪ ምርመራ እንደያዛቸው ገልጿል።
አስተዳደሩ የኢትዮጵያውያኑ ጉዞ ከሰዎች ዝውውር ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል ያለ ሲሆን በተደረገ የመጀመሪያ ምርመራ ሰዎቹ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተመልሰው በህገወጥ መንገድ ከመግባታቸው በፊት ወደ ሌሎች ጎረቤት ሃገራት ለመሻገር የተደረገ ጥረት እንደሆነ ገልጿል።
አስተዳደሩ በመንገደኞቹ የጉዞ መረጃ ላይ አጠራጣሪ የሆኑ ነገሮችን ስላገኘ በኤርፖርት ተለይተው ለምርመራ መወሰዳቸውን አንስቷል።
የደቡብ አፍሪካ የድንበር አስተዳደር በሌላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ወደ ሃገሩ በተጭበረበረ ቪዛ ሊገቡ የነበሩ 16 የባንግላዴሽ ዜጎችንም ይዣለሁ ብሏል። ደቡብ አፍሪካ በእነዚህ 30 ሰዎች ላይ ተጨማሪ ምርመራ መጀመሯን የገለፀች ሲሆን የሰዎችን ዝውውር ለመቆጣጠር የደህንነት እርምጃዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልፃለች።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእያንዳንዱ መንገደኛ የ890 ዶላር ቅጣት ተጥሎበታል።
ደቡብ አፍሪካ በሁለት በረራዎች ወደ ሃገሯ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተጓጓዙ 14 ኢትዮጵያውያንን እና 16 የባንግላዴሽ ዜጎችን ከሰዎች ዝውውርና የተሳሳተ ቪዛ ጋር በተያያዘ ከያዘች በኋላ መንገደኞቹን ባጓጓዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ ቅጣት መጣሏን የሃገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞቹን ሰነድ በተገቢ መልከ ሳያጣራ ወይም በአጠራጣሪ ሁኔታ ስር በማጓጓዙ በእያንዳንዱ መንገደኛ 890 ዶላር ወይም 15,000 የደቡብ አፍሪካ ራንድ እንዲከፍል ተቀጥቷል።
ደቡብ አፍሪካ የያዘቻቸው 30 ሰዎች
አሜሪካ ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ሰጥታ የነበረውን የጊዜያዊ ከለላ መብት አንስታለች።
የአሜሪካ የሃገር ውስጥ ደህንነት ቢሮ ኃላፊ ክርስቲ ኖዬም ለኢትዮጵያ ተሰጥቶ የነበረው የጊዜያዊ ከለላ መብት መነሳቱን አስታውቀዋል።
አሜሪካ በጦርነት፣ በተፈጥሮ አደጋ ወይም በሌሎች ምክንያቶች ወደ ሃገራቸው መመለስ ለማይችሉ ዜጎች ጊዜያዊ ከለላ (Temporary protected status) ትሰጥ የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያም ይኸው መብት ነበራት።
አሜሪካ ከ1990ዎቹ ጀምሮ በሃገሯ የሚኖሩ የሌሎች ሃገራት ዜጎች ጦርነትን ጨምሮ በአንዳንድ ምክንያቶች ወደመጡበት ሃገር መመለስ ለማይችሉ ሰዎች ይህንን ከለላ መስጠት ጀምራ ነበር።
ይህ ከለላ የሚሰጣቸው ዜጎችም የሃገራቸው ሁኔታ እስኪሻሻል በአሜሪካ የመኖርና የመስራት መብት ሲሰጣቸው ከአሜሪካ ከመባረር ይጠበቁ ነበር።
አሜሪካ” በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሱ ግለሰቦች ደህንነት ላይ ስጋት አይፈጥርም” ያለች ሲሆን በዚህም የተነሳ ይኸው ከለላ መነሳቱን አስታውቃለች።
አሜሪካ ሌሎች በአሜሪካ ለመቆየት ህጋዊ መሰረት ካላቸው ኢትዮጵያውያን ውጪ የኢትዮጵያ ዜጎች በ60 ቀናት ከሃገሯ እንዲወጡ አሳስባለች።
ቀድመው ከአሜሪካ ለሚወጡ የትኬት ወጪያቸው እንደሚሸፈን፣ የ1000 ዶላር ጉርሻ እንደሚሰጥና ለወደፊቱ ህጋዊ የኢሚግሬሽን እድል እንደሚኖራቸው ገልፃለች።
ከፈረንጆቹ የካቲት 13 በኋላ ከለላው እንደሚያበቃ ገልፃ ያለ ከለላው በአሜሪካ የሚኖር ኢትዮጵያዊ ዜጋ እንደምታስር እና ከሃገሯ እንደምታባርር አስጠንቅቃለች።
አሜሪካ ከሳምንታት በፊት ተመሳሳይ ከለላ የነበራቸውን የደቡብ ሱዳን ዜጎችን መብት አስንታለች።
አብዱራህማን መሃዲ የሚመሩት የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) አንጃ፣ አዲሱ የአሜሪካ ብሄራዊ የደኅንነት ስትራቴጂ በቀጠናው ውስጥ መንግሥታዊ ያልሆኑ ቡድኖችን ያገለለ በመሆኑ ግጭቶችን ፈጽሞ አይፈታም በማለት ተቸ። ቡድኑ፣ አሜሪካና አጋሮች በቀጠናው ሰላም ማስፈን ከፈለጉ፣ የሰላም ስምምነቶች በተመረጠ ሁኔታ ተፈጻሚ ሊሆኑ እንደማይችሉ፣ የሶማሌ ሕዝብን የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት የኢትዮጵያ መንግሥት እንደጨፈለቀው እና ኢትዮጵያ ለኤርትራ፣ ለሱዳን፣ ለሶማሊያ እና ለግብጽ የምታሳየው የጠቅላይነት አካሄድ ለቀጠናዊ ሰላም ጠንቅ መሆኑን ማወቅ አለባቸው ብሏል። ቡድኑ አያይዞም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በአፍሪካ ቀንድ የአለመረጋጋት ምንጭ ሆኗል ብሏል። ኦብነግ፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ፌደራል መንግሥቱ የሚያካሂደውን አፈና እና ጦርነት ችላ ብሏል በማለት የወቀሠው ቡድኑ፣ መንግሥት በሶማሌ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ እና ሌሎች ክልሎች የሚፈጽማቸው ድርጊቶች ሁሉ ሆነ ብሎ ተቃውሞንና ብዝሃነትን ለማጥፋትና የብሄሮችን መብቶች ለመጨፍለቅ ያለመ ነው በማለት ከሷል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፣ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ለአልጀርሱ ስምምነት መከበር ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ እንዲያሳዩ ጥሪ አደረጉ። ጉተሬዝ ይህን ጥሪ ያደረጉት፣ የአልጀርሱ ስምምነት የተፈረመበትን 25ኛ ዓመት አስመልክተው በቃል አቀባያቸው ስቲፋኒ ዱጃሪክ በኩል ትናንት ባወጡት መግለጫ ነው። ጉተሬዝ፣ በሁለቱ አገራት መካከል ባሁኑ ወቅት የተፈጠረው አዲስ ውጥረት ቀጠናዊ ሰላምን ሊያውክ ይችላል በማለት አስጠንቅቀዋል። የአልጀርሱ ስምምነት የሁለቱን አገራት ድንበር ለማካለል ማዕቀፍ ያስቀመጠና ለአገራቱ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት መከበር መሠረታዊ መርሆዎችን በድጋሚ ያረጋገጠ መሆኑንም ጉተሬዝ ጠቅሠዋል። ተመድ ለአልጀርሱ ስምምነት ጠንካራ ድጋፍ እንዳለው የገለጡት ጉተሬዝ፣ የሁለቱ አገራት መሪዎችም ከሰባት ዓመታት በፊት ለሰላም ያላቸውን ቁርጠኝነት በስምምነት ማረጋገጣቸውን አስታውሰዋል። ጉተሬዝ አያይዘውም፣ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከቀጠናዊ እና ዓለማቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ የልማት ትብብር እንዲያካሂዱ ጠይቀዋል።
የመርካቶ ነጋዴዎች ተነሱ የተባሉበትን ቦታ ለማልማት አቅም አለን ቢሉም ወረዳው “ህይወት መቅደምና መቀደም ነው፣ ተቀድማችኋል” የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናገሩ
2,500 ካሬ ስፋት ያለው ቦታው ለአንድ ባለሀብት እንደተሰጠ የታወቀ ሲሆን የተሸጠበትን ርካሽ ዋጋም ‘አስቂኝ’ በማለት ነጋዴዎቹ ገልፀውታል፣
ዝርዝሩን ይዘናል ፤ተጨማሪ ያንብቡ: https://www.meseretmedia.org/p/6db
በአዲስ አበባ ከተማ የኢ-ካርታ አገልግሎት የተቋረጠው አገልግሎቱን የሰራው ባለሙያ በገንዘብ አለመስማማት ሲስተሙን ዘግቶ በመሰወሩ መሆኑ ታወቀ
ይህ የኢ-ካርታ ስርዐት የብዙ ሚሊዮኖችን የቤት እና የመሬት መረጃ እንደያዘ መቋረጡ ስጋትን ፈጥሯል፣ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተሰራው አዲስ ሲስተም ደግሞ ከድሮው ጋር መናበብ እንዳልቻለ የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/7f2
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶንዮ ጉተረዥ ኢትዮጵያና ኤርትራ በአልጀርሱ ስምምነት መሰረት አንዱ የሌላኛው የግዛት አንድነት ለማክበር ቁርጠኝነታቸውን ዳግም እንዲያረጋግጡ አሳሰቡ። የዋና ጸሐፊው ቃል አቀባይ ስቲፋን ዱጃሪክ የስምምነቱን 25ኛ ዓመት አስመልክተው ባስተላለፉት የዋና ጸሐፊው መልዕክት ሁለቱም ሐገራት ዘላቂ ሰላምን በማምጣት ላይ ተግተው እንዲሰሩ ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያና የኤርትራ መሪዎች ከ7 አመታት በፊት ያደሱት ሰላማዊ ግንኙት ያወደሰው የጉተረዥ መልዕክት ይህም የውይይትና የትብብር ዋጋ የሚያሳይ ነው ብሏል። አያይዘውም በአልጀርስ ስምምነት ላይ የተካተተውን የዘላቂ ሰላም፣ ሉአላዊነት እና የግዛት አንድነትን ለማክበር ቁርጠኝነታቸውን ዳግም እንዲያረጋግጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የትራምፕ አስተዳደር በዩናይትድ ስቴትስ፣ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ዜጎች ህጋዊ መኖርያ ፈቃድን በግዚያዊነት ማገዱን አስታወቀ። “የአገሮችን ሁኔታ ከገመገሙ በኋላ እና
አግባብነት ካላቸው የአሜሪካ መንግስት ተቋሞች ምክክር ካደረጉ በኋላ፤ የደኅንነት ዘርፍ ቢሮ ኢትዮጵያ ከዚህ በኋላ ለጊዜያዊ ጥበቃ ሁኔታ ስያሜ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት እንደማትቀጥል፤ ፣ “የሃገር ውስጥ ደህንነት ጸሐፊው ክሪስቲ ኖኤም በፌዴራል ውስጥ በተለጠፈ ማስታወቂያ ላይ መናገራቸዉን ሮይተርስ ዘግቧል።
የፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያን ጊዜያዊ የሕግ ከለላ (TPS) ጥቅም አይገባቸውም ሲል ይህን እፎይታ ያነሳው ዛሬ አርብ ነ ው ። ጊዜያዊ ከለላው በሰሜኑ በተለይም በትግራይ ጦርነት ወቅት በዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት የተሰጠ ነበር ። በዚህ እድል ሲጠቀሙ የነበሩ በግምት ወደ 26 ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ላይ ምን ሊከተል ይችል ይሆን? ታምራት ዲንሳ የአትላንታ ዘጋቢኢችን ታሪኩ ኃይሉን በስልክ አነጋግሮታል ። https://www.dw.com/am