I’ve co-produced an episode of Al Jazeera English’s The Listening Post and it airs tomorrow. We investigated the Israeli government’s flying out of journalists and influencers from African countries to Israel, where they produce content that polishes Israel’s reputation and downplays genocide in Gaza. Ethiopian journalists were among the most effective of those commissioned. Tune in from 19h30 GMT (time edited).
ላለፉት 5 ወራት ከአል ጀዚራ ጋር በመስራት ያዘጋጀሁትን ስራ ነገ በአል ጀዚራ ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከምሽቱ 4:30 ጀምሮ ይተላለፋል። ከዛ በኋላ አልጀዚራ በዩቱብ ቻነሉ ያስቀምጧል።
የእስራኤል መንግስት በጋዛ ግዛት በሆኑት ፍልስጤማውያን ላይ ከፈረንጆቹ 2023 ዓመት ጀምሮ የዘር ፍጅት ወንጀል በመፈጸሙንና በግምት እስከ 70ሺህ ሰዎችን መግደሉ በሰፊው ተዘግቧል። ከተጨፈጨፉት መካከል አብዛኛዎቹ ሴቶች እና ህጻናት ናቸው። አምኔስቲ፤ ሂውማን ራይትስ ዋች እና በተመድ የተመደቡት የሰብዓዊ መብት ተመራማሪዎች ሁሉ በጋዛ የተፈጸመው ጭፍጨፋ የዘር ፍጅት መሆኑን ሶሥቱ ተቋማት በመሩት ምርመራዎች አረጋግጠዋል።
እስራኤል ወታደሮቿን ወደ ጋዛ መላክ ሲጀምር ከምዕራብ ዓለም ከባድ ተቃውሞ ግጥሞታል። ምንም እንኳን በበርካታ ምዕራብ አለም መንግስታት የቁሳቁስና የመሳሪያ ድጋፍ እያገኘ ቢሆንም በህዝብና በተለይ በወጣቱ ትውልድ እስራኤል እየተጸየፈ መጥቷል። በተለይ በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የገጠመው ተቃውሞ ካምፐሶች እና የታላላቅ ከተማ መንገዶች በየ ሳምንቱ በፍልስጤም ባንዲራ እንዲጥለቀለቁ ተደርገዋል።
የእስራኤል መንግስት በአሜሪካና በአውሮጳ ባሉት ወጣቶች ተስፋ የቆረጠ ይመስላል።
ትኩረቱን ወደ አፍሪካ አዙሯል።

ከ2024 ጀምሮ የእስራኤል መንግስት ከተለያዩ