ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የኒው ዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቅርቡ በካሕናት አባቶች ላይ የደረሰውን ግድያ አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት …. አብይ አሕመድን አውግዘው ለሕዝቡ አስቸኳይ ጥሪ አስተላልፈዋል ። ….. #MerejaTv ….@mohammed_meaza… pic.twitter.com/CqoXi1PHL5
— Mereja TV (@merejatv) June 30, 2025
በአማራ ክልል ከጎንደር መተማ መንገድ ላይ “መቃ” በተባለች ሥፍራ የቅማንት ታጣቂዎች ሰኞ’ለት በፈጸሙት ጥቃት 16 አሽከርካሪዎች ተገድለው በርካቶች መቁሰላቸውን ታውቋል። በቅማንት ታጣቂዎች ከተገደሉት ሾፌሮች በተጨማሪ ተሳፋሪዎችና በርካታ አሽከርካሪዎች ታፍነው መወሰዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል። አብዛኞቹ አሽከርካሪዎች የተገደሉት፣ ከጥቃቱ ለማምለጥ ጥረት በማድረግ ላይ ሳሉ በእሩምታ ተኩስ እንደኾነ ተነግሯል። የፋኖ ታጣቂዎች በመተማ ወረዳ ከቅማንት ብሄረሰብ ታጣቂዎች ዘረፋ ለማስቆም የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ምንጮች ተናግረዋል። የቅማንት ታጣቂዎች በአብይ አሕመድ ድጋፍ እየተደረገላቸው በዘረፋ እና እገታ ላይ መሰማራታቸው የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
የኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ለውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች በይፋ መከፈቱን ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ
ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያውያን ባለሃብቶች ብቻ ሲካሄድ የቆየው የባንክ ስራ አገልግሎት፤ ከዛሬ ጀምሮ ለውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች በይፋ መከፈቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። በዘርፉ መሰማራት የሚፈልጉ የውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች ከዛሬ ጀምሮ ማመልከቻዎቻቸውን ለብሔራዊ ባንክ ማስገባት እንደሚችሉም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
አቶ ማሞ ምህረቱ በገዢነት የሚመሩት ብሔራዊ ባንክ ይህን ያስታወቀው፤ የውጭ ባለሃብቶች የባንክ ስራ ፈቃድ ለማግኘት እና ለማሳደስ የሚያስችላቸውን መመሪያ ይፋ ባደረገበት መግለጫ ነው። አዲሱ መመሪያ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የውክልና ጽህፈት ቤት ለመክፈት ማሟላት የሚያስፈልጋቸውን ቅድመ-ሁኔታዎችም ይዘረዝራል።
መመሪያው ብሔራዊ ባንክ ባለፈው ዓመት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ያደረገው “ሰፊ ምክክር” ውጤት እንደሆነ የመስሪያ ቤቱ መግለጫ አመልክቷል። የኢትዮጵያ መንግስት ለውጪ ባንኮች እና ለኢንቨስተሮች ተዘግቶ የቆየውን የባንክ ስራ ዘርፍ ለመክፈት ዝግጅት ሲያደርግ ከቆየ በኋላ ወደ ተግባር የገባው ከሶስት ዓመት በፊት ነበር።
🔴ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16188/
በኦሮሚያ ክልል አዋሽ ቢሾላ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ለሁለት ወራት የመሠረታዊ ውትድርናና ፖለቲካዊ ሥልጠና ሲወስዱ ለነበሩ የክልሉ የመንግሥት አመራሮች አቀባበል ለማድረግ ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ከ500 ብር ጀምሮ በግዳጅ መዋጮ እንደተሰበሰበ ዋዜማ ሠምታለች። አመራሮቹ፣ ሥልጠናውን አጠናቀው ትላንት ወደየመጡባቸው አካባቢዎች መመለሳቸውን ዋዜማ ተረድታለች። መዋጮውን ለማዋጣት ፈቃደኛ ባልኾኑ ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጫና ሰደረግባቸው እንደነበርም ምንጮች አስረድተዋል። ከ17 ሺሕ በላይ ሠልጣኝ አመራሮች መካከል ስድስቱ በሥልጠናው ክብደትና በአካባቢው ሞቃት የአየር ጠባይ ሳቢያ ስድስቱ ሕይወታቸው ማለፉንና 200 ያህሉ ከካምፑ መጥፋታቸውን ዋዜማ ቀደም ሲል መዘገቧ አይዘነጋም።
ከእስራኤል እና ከኢራን ጦርነት ባሻገር . . .
ከእስራኤል እና ኢራን ጦርነት ጋር ተያይዞ ከሚነሱ ስጋቶች ውስጥ አንዱ ኢራን ምናልባት የሆርሙዝ ሰርጥን ልትዘጋ ትችላለች የሚለው አንዱ ነው።
የሆርሙዝ ሰርጥ ምንድን ነው?
የሆርሙዝ ሰርጥ አለማችን ላይ ወሳኝ ከሚባሉ የንግድ መተላለፊያዎች ውስጥ ዋነኛው ሲሆን ኢራንን ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ከኦማን የሚለይ 167 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሰርጥ ነው።
ሰርጡ አስፈላጊ የሆነው የአለም ከ20-30 በመቶ የነዳጅ ሽያጭ የሚያልፍበት እና በቀን ከ20 ሚሊየን በርሜል ነዳጅ በላይ በየቀኑ የሚሸጋገርበት መስመር በመሆኑ ነው።
የኢራን እና እስራኤል ጦርነት መካረርን ጨምሮ ኢራን ሰርጡን ልትዘጋ ትችላለች የሚል ስጋት እየጨመረ መጥቷል።
ኢራን ሰርጡን ከዘጋች ምን ሊፈጠር ይችላል?
⛽️ የነዳጅ ዋጋ መናር
የዓለም ዋና ዋና የሚባሉ የነዳጅ ላኪ ሃገራት የነዳጅ ምርታቸውን ወደ ዓለም ገበያ ለማቅረብ ይህንን ሰርጥ ሲጠቀሙ የሰርጡ መዘጋት ለዓለም ገበያ የሚቀርበውን የነዳጅ መጠን በመቀነስ ዋጋው እንዲጨምር ያደርገዋል።
በጦርነቱ ጅማሬ ብቻ ከ7 በመቶ በላይ የዋጋ ጭማሪ ያሳየው ነዳጅ ሰርጡ ተዘግቶ ጦርነቱ ከቀጠለ ዋጋው በእጅጉ ሊጨምር እንደሚችል ተገምቷል።
በዘርፉ ያሉ ተመራማሪዎች ሰርጡ እንኳን ሳይዘጋ በኢራን የኃይል ማዕከላት ላይ የሚፈፀም ጥቃት በራሱ የነዳጅ ዋጋን እስከ 90 ዶላር በበርሜል ሊያደርሰው እንደሚችል ግምታቸውን ሲሰጡ፤ ሰርጡ ከተዘጋ የነዳጅ ዋጋ ታይቶ በማይታወቅ ዋጋ ሊንር ይችላል የሚል ስጋት አይሏል።
ከዚህ በፊት በእስራኤል የአረብ ጦርነት ወቅት የነዳጅ ዋጋ በ300 % ጨምሮ እንደነበር ይታወሳል።
የዋጋ ጭማሪው እና የአቅርቦት እጥረት