የ19 ዓመቷ ፋኒት በዓለም ዋሴ የግፍ ግድያ የጦር ወንጀል ነው፤
መንግስት መሆን ያቃተው ብልጽግና የአማጽነት ወግም እርቆታል፤ Yared Hailemariam
++++

በአለም አቀፍ የሰብአዊነት ህግ (International Humanitarian Law) ወይም the laws of armed conflict እና የGeneva Convention በመባል በሚታወቁት አለም አቀፍ ሕጎች የጦርነትን ሁኔታና በጦርነት ወቅት ቆስለው ወይም ሳይቆስሉ የሚማረኩ የተቀናቃኝ ጦር አባላትን አያያዝ የሚደነግጉ አንቀጾች አሉ፡፡ በእነዚህ ድንጋጌዎች መሠረት Hors de combat (out of the fight) የሚባሉት ከተፋላሚዎቹ ሃይሎች መካከል በጦርነቱ ጉዳት ደርሶባቸው የቆሰሉና የተማረኩ፣ በሕመም ላይ የሚገኙ ወይም እጅ ሰጥተው በተቀናቃኝ ጦር የተማረኩ ሰዎች እና Prisoners of war (POWs) የጦር እስረኞች ምን አይነት የሕግ ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባና ጥበቃ ማድረግ በሚገባቸው አካላት ላይ ስለተጣለው ሃላፊነት እነዚህ ህጎች በዝርዝር ይደነግጋሉ፡፡ በጉዳት ምክንያት ወይም በምርኮ የተያዘ ሰው ተገቢው ህክምና እና ጥበቃ ተደርጎላቸው ሰብአዊነት በተሞላው አያያዝ እንዲቆዩ መደረግ እንዳለበት ይደነግጋሉ፡፡ ይህን መጣስ እንደ ጦር ወንጀል እንደሚቆጠርም እነዚህ ሕጎች ይገልጻሉ፡፡
ከእነዚህ መሠረታዊና ቁልፍ ከሆኑ የጦርነት መርሆዎች በእንግሊዘኛው ፤
1ኛ/ IHL prohibits the use of unnecessary force and weapons that cause unnecessary suffering. This includes prohibiting torture, cruel treatment, and the use of excessive force. (የአለም አቀፉ የሰብአዊነት ሕግ አላስፈላጊ እና ያልተመጣጠነ ሃይል እና መሳሪያ በመጠቀም በተማረኩ፣ ቆስለው በተያዙና የጦር እስረኛ በሆኑ ሰዎች ላይ መጠቀም፣ የማሰቃየት ወይም ጭካኔ የተሞላው አያያዝ መፈጸም የተከለከለ መሆኑን ይደነግጋል)
2ኛ/