Home › Archive for VIDEO ቪዲዮ
Blog Archives
በፌዴራል ደረጃ ከተመዘገቡት 470ሺ የንግድ አና አገልግሎት ሰጪ የግል ድርጅቶች ውስጥ 370ሺ ስራ አቁመዋል ….. አስደንጋጩን ሪፖርት እነሆ
https://miniliksalsawi.substack.com/p/ethiopia-out-of-470000-federally
… የድርጅቶች በዚህ ደረጃ መዘጋት የመንግስት ገቢን በመቀነሱ ምክንያትም በቀሩት ጥቂት ድርጅቶች ላይ የሚያሳድረው የግብር ጫና በሂደት ቀሪዎችንም ከገበያ ሊያሰወጣ የሚችል ክስተት መሆኑ ግንዛቤ ሊወሰድበት የሚገባ ነው። ……..በሥራና ክህሎት ሚኒስትር ኤክስፐርቶች ተጠንቶ የቀረበን ሪፖርት በመንተራስ ቅዳሜ የወጣው የእንግሊዘኛ ሪፖርተር ሳምንታዊ ጋዜጣ በፌደራል ደረጃ ተመዝግበው ከሚገኙና በተለያየ ሙያና ዘርፍ ከተሰማሩ የንግድ ድርጅቶች መካከል 80% የሚሆኑት እንደተዘጉና በአሁኑ ጊዜ በአገልግሎት ላይ የሚገኙት የንግድና አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ቁጥር ከ100 ሺህ እንደማይበልጡ ዘግቧል።…… ለረጅም ዓመታት ፈጣን እድገት በማሳያት 470 ሺህ ደረሰው ከነበሩት በፌደራል ደረጃ የተመዘገቡ የንግድና አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች መካከል 370 ሺዎቹ በ2025 መዘጋታቸውን በዘገባው ላይ አክሏል። ….. ሪፓርተር መሰረት ባደረገው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ኤክስፐርቶች ጥናት መሰረት በ2025 ከ370 ሺህ በላይ ድርጅቶች ከፌደራል መዝገብ ተሰርዘዋል ማለት ምን ያህል የስራ እድል፣ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ የመንግስት ገቢዎችን እንደሚቀንስና ከአገልግሎት አሰጣጥና ከአቅርቦት አኳያም በምን ያህል ደረጃ የምርት አቅርቦትና ስርጭት ሚዛንን እንደሚያዛባ መረዳት ይቻላል። #MinilikSalsawi
https://miniliksalsawi.substack.com/p/ethiopia-out-of-470000-federally
::
ምኒልክ ዕዝ የልዩ ዘመቻ መምሪያ አሃድ ከሆኑት መካከል ለወራት የሰለጠኑ ልዩ ኮማንዶ ፋኖዎች የዕዝ የኮርና የክፍለጦሩ አመራሮች በተገኙበትና መልክት ባስተላለፉበት ሁኔታ ተመርቀዋል::
ከፍተኛ የዕዙ አመራሮችም የተጀመረውን የፖለቲካ ትጥቅ ትግል ከግብ ለማድረስና የአማራን ህዝብ ህልውና ለማረጋገጥ ብሎም ቀጣይነት ያለው ነፃነት ለመጎናፀፍና የሃገራችን ባለቤት ለመሆን በፅናትና ቁርጠኝነት መታገል ብቻኛ አማራጭ መሆኑን ለተመራቂዎች አስገንዝበዋል::
ልዩ ኮማንዶ ፋኖዎችን ያስመረቁት በልዩ ዘመቻ መምሪያው ስር የሆነው አሃድ ወታደራዊ አዛዥና ምክትል ወታደራዊ አዛዥ የሆኑት አርበኞችም ለተመራቂዎች መልክታቸውን አስተላልፈዋል::
የልዩ ዘመቻ ሰልጣኝ ተመራቂዎች ዛሬ የተመረቃችሁ ምኒልክ ዕዝ የልዩ ዘመቻ እንደስማችሁ ልዩ ሰልጣኝ ተመራቂዎች ለበርካታ ወራት ፀሀዩን:ብርዱን:ቁሩን በርካታ ውጣውረዱ ሳይበግራችሁ ባልተመቻቸ ሁኔታ ተቋቁማችሁ ለዚህች ልዩ ቀን በመብቃታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩ የናንተ ስልጠና ለየት የሚያደርገው ያኔ በጣት በምንቆጠረበት ጊዜ ሳይሆን አሁን በሺዎች ብሎም በሚልዮኖች በትጥቅም ይሁን በሰው ኃይል አቅማችን እንዲሁም የማድረግ አቅማችን ትልቅ የስኬት ጫፍ ላይ ባለንበት ጊዜ መቀላቀላችሁ በተጨማሪም የዚህን አንባገነን ስርዓት ግፍ በደል እና ሰቆቃ አድራሽነት ማንም ሳይጎተጉታችሁ እያንዳንዳችሁ ቤት አንኳኩቶ የገባ በመሆኑ ያለማንም ቀስቃሽ በቃኝ አሻፈረኝ ብላችሁ ይህን ትልቅ የትጥቅ ትግል የተቀላቀላችሁ መሆኑ ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ለየት ያደርገዋል።
እንሰባሰባለን እንደራጃለን እንሰለጥናለን እንታጠቃለን ተዋግተን ይህን አንባገነን ፀረ_አማራ ስርዓት ከትክሻችን ላይ አሽቀንጥረን እንጥላለን።
የአማራ ተጋድሎ አካሄድ እና መስመር⚡️:-
👉 የተጋድሏችን
መነሻ:-የአማራ ህልውና አደጋ ነው።
መዳረሻው:- አደጋውን ቀልብሶ ህዝቡን ከባርነት አውጥቶ ከሁሉም ኢትዮጵያዊያን ጋር በመተባበር የሃገሪቱን በትረ ስልጣን
ኢሰመኮ፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት መያዝ ከሚችለው የተጠርጣሪዎች ቁጥር በላይ በመያዙ ከፍተኛ መጨናነቅ ተፈጥሯል አለ። ኢሰመኮ፣ ማረሚያ ቤቱ ለአካለ መጠን ያልደረሱ ተጠርጣሪዎችን ከሌሎች ተጠርጣሪዎች ለይቶ አለመያዙ “አሳሳቢ” እንደሆነ ገልጧል። በማረሚያ ቤቱ የተወሠኑ ዞኖች ለተጠርጣሪዎች በቂ የመንቀሳቀሻ ቦታ እንደሌለና ተጠርጣሪዎች እንዲይዙት የሚፈቀድላቸው ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን 200 ብር ብቻ መሆኑ አስፈላጊ ሸቀጦችን ለመግዛት በቂ እንዳልሆነ የጠቀሠው ኢሰመኮ፣ ማረሚያ ቤቱ ላንድ ተጠርጣሪ የእለት ቀለብ የመደበው 35 ብርም ምግብ ለማቅረብ በቂ አይደለም ብሏል። ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ፣ የተጠርጣሪዎችን መጨናነቅ ለመቀነስ፣ ፍርድ የተሠጣቸው እስረኞች በአፋጣኝ ወደ ቃሊቲ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ቤት እንዲዛወሩ ቀደም ሲል የተላለፈው ውሳኔ በፍጥነት ይተግበር በማለት አሳስበዋል።
በምስራቅ በለሳ ግንባር ፋኖ የአገዛዙን አከርካሪ የሰበረበት ትንቅንቅ!
በአፋብኃ ሰሜን ዐምሓራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ኮር ስር ከሚገኙት ከኮሩ ተወርዋሪ ኃይል፣ ከአፄ እያሱ ክ/ጦር፣ ከዞዝ አምባ ክ/ጦርና ከንስር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክ/ጦር እንዲሁም ከጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር የተወጣጡ የፋኖ አሃዶች በጋራ በመሆን ትናንት ጥር 01/2018 ዓ/ም ከንጋት ጀምሮ በወሰዱት እርምጃ የጠላትን አከርካሪ በመስበር ታላቅ ድል ተቀዳጅተው መዋላቸውን መረብ ሚዲያ ከኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለማረጋገጥ ችሏል።
ውጊያው የተደረገው በምስራቅ በለሳ ጣይመን ከተማ ሲሆን፡ በዚህም የፋኖ አባላቱ በከተማ ውስጥ የሚገኘውን የአገዛዙ ወታደራዊ ካምፕን ጥሰው ገብተው በሦስት አቅጣጫ ተኩስ በመክፈትና ሁለት ትላልቅ ምሽጎችን በመስበር ነው በጠላት ላይ ከባድ የሆነ የሰብአዊና ቁሣዊ እንዲሁም ሞራላዊ ኪሳራ ማድረስ የቻሉት።
በውጊያው 37 የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት አባላት ሲገደሉ 35 የአገዛዙ ወታደሮች ደግሞ ቆስለዋል ያለው ኮሩ፡ በለስ የቀናቸው 25 ወታደሮች ደግሞ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መማረካቸውን አሳውቋል።
ከንጋት ጀምሮ እስከ እኩለ ቀን በዘለቀው አማራዊ ጀግንነትን ከጦር ሣይንስ እውቀት ጋር ያጣመረ ነው በተባለው በዚህ ከባድ ተጋድሎ ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ ከተደረጉት በተጨማሪ፡ ሦስት ብሬን፣ 55 ክላሽንኮቭ መሣሪያ፣ 1ሺ የብሬን ተተኳሽ፣ 2ሺ የክላሽ ተተኳሽ፣ 100 የእጅ ቦምብ እና ሁለት ወታደራዊ መገናኛ ራዲዮ በፋኖ መማረኩን መረብ ሚዲያ ከዳግማዊ ቴዎድሮስ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለማረጋገጥ ችሏል።
ቁስለኛ ወታደሮች ለሕክምና ወደ ጓህላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና ወደ አርባያ ሆስፒታል ተወስደዋል ነው ያለው ኮሩ ባወጣው
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመት ምሕረት፤
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ አሜን!
+ በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
+ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
+ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
+ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
+ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣
እኛ በሕይወት እንኖር ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም የላከ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓስራ ስምንት ዓመተ ምሕረት በዓለ ልደቱ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
“ወበዝንቱ ተዓውቀ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር ላዕሌነ እስመ ለወልዱ ዋሕድ ፈነዎ ውስተ ዓለም ከመ ንሕየው በእንቲኣሁ፤ ወዝንቱ ውእቱ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር፡- የእግዚአብሔር ፍቅሩ በእኛ ዘንድ ተገለጠ፤ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነው፤ (፩ዮሓ. ፬፥፱)
በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቀው እኛ ምሥራቃውያን ክርስቲያኖች በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓል፣ የጌታችን የኣምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ነው፤ በዓለ ልደት የእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅር ለሰው ልጆች ሁሉ የታወጀበት ዕለት ነው፤ በዚህ ዕለት የሆነው የእግዚአብሔር ፍቅርና ሰላም ቃላዊ ወይም ተምኔታዊ ኣልነበረም፤ ወይም ደግሞ በርቀት በመልእክት የተላለፈ ኣልነበረም፤
ከዚህ ይልቅ ሰብእናችንን በመዋሐድ፣ በተግባር ሆኖ በመገኘት፣ እንዲሁም ለመሰጠት ዝግጁ በመሆን የተገለጠና የታየ ሰላምና ፍቅር
ለገና በዓል ቤተሰብ ጥየቃ ለመሄድ እየተዘጋጁ የነበሩ 16 ላብ አደሮች መረሸናቸው ተሰማ
ወጣቶቹ ቅዳሜ ምሽት ጎጃም ውስጥ በመንግስት ሀይሎች መረሸናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ጠቁመዋል፣
የሚድሮክ አካል በሆነው በአየሁ እርሻ ልማት መስሪያ ቤት ውስጥ ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውም ታውቋል
ተጨማሪ ያንብቡ: https://meseretmedia.org/p/16
በምስራቅ አማራ ቀጠና እየተገባደደ በሚገኘው ታህሳስ ወር ብቻ አንድ ጄነራል መድፍን ጨምሮ ሦስት የአየር መቃዎሚያ በፋኖ ወድሟል!
በቀጠናው የቀረው የጠላት ሜካናይዝድ መሣሪያም “ይዘገያል እንጂ አህያ የጅብ ናት” ነው እጣፈንታው ተብሏል።
በምስራቅ አማራ ቀጠና በክቡር ሰማዕቱ አርበኛ አደም አሊ(አባናደው) ስም በተሰየመው ወታደራዊ ዘመቻ 3ሺ ሦስት(3003) ወታደሮቹ በፋኖ የተገደሉበት እና 679 ወታደሮቹ ደግሞ የተማረኩበት በአሰፋ ቸኮል የሚመራው የሰሜን ምስራቅ ዕዝ፡ አሁን ደግሞ የዕዙ ሜካናይዝድ ክፍል አለኝ ከሚለው ከባባድ የጦር መሣሪያ መካከል አንዱና አዲሱ የአየር መቃዎሚያ በፋኖ በላውንቸር ተመቶ ሙሉ በሙሉ ወድሟል።
ሰሞኑን የክልሉ ፖሊስ አባላትን ባህርዳር ላይ ሰብስቦ “ፋኖን ያጀገነው እኛ ባለመተባበራችን እንጂ፡ ፋኖ አቅመቢስ ነው” በሚል ሲፎክር በነበረው፡ ከወራት ወዲህ ደግሞ የቅርብ ጓዶቹ “የባዶ ዕዝ አዛዡ” በሚል ስላቅ በሚጠሩት በአሰፋ ቸኮል የሚመራው ሰሜን ምስራቅ ዕዝ፡ “ዘመቻ አባናደው” ከመስከረም 14/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 16 ቀናት ከመካሄዱ በፊት ማለትም ነሐሴ 03/2017 ዓ/ም አንድ ዙ 23(የአየር መቃዎሚያ) ራያ ቆቦ ሮቢት ላይ በፋኖ እንደተማረከበት በእለቱ መረብ ሚዲያ በምስል አስደግፎ መዘገቡ አይዘነጋም።
ይኸው ሰሜን ምስራቅ ዕዝ ከዘመቻ አባናደው በኋላ በአዲስ መልክ ተደራጅቶ የነበረ ሲሆን፡ ከመማረክና ከመደምሰስ የተረፉ የዕዙ ሰራዊት አባላትን በቡርቃ ማሰልጠኛ ጣቢያ የአካልና የስነ ልቦና ተሀዲሶ ስልጠና ለወራት በመስጠት ታህሳስ 19/2018 ዓ/ም አስመርቆ ነበረ።
ለወራት የተሀድሶ ስልጠናው የተሰጣቸው የዕዙ ሰራዊት አባላት፡ ከነ አዛዦቻቸው ሲጠሉት የነበረውን ልሙጡን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራን በምረቃ ስነስርዓታቸው ላይ ከላይ እስከታች
በከተማዋ ቦርቸሌ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የሚገኘው ትልቁ የአየር ወለድ ኮማንዶ ካምፕ የተሰበረ ሲሆን፡ የፋኖ አባላቱ ከምሽግ ምሽግ እየተወረወሩ “የባለምጡቅ አዕምሮ ባለቤቶች” ሲል አገዛዙ የሚያሞካሻቸው ህፃን ደፋሪ፡ ሀብት ንብረት አውዳሚ ፀረ አማራ ኮማንዶዎችን ባፈሙዝ አለንጋ ሲገርፏቸው እንደዋሉ የመረብ ሚዲያ የግንባር ዘጋቢዎች ለማረጋገጥ ችለዋል።
ዝርዝር መረጃውን አድምጡ👉https://www.youtube.com/watch?v=uoJpt2xZmdY
Yared Hailemariam
ታዬን ለመበቀል፣ ቀነኒን ፍትህ በመንፈግ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአማራ ብሔር ተወላጅ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞችን በማንነታቸው ላይ ያነጣጠረ ጥቃት በመፈጸም የዘቀጠው የፍትህ ሥርዓት።
የፍትህ ሥርዓቱን ለበቀል፣ ለፖለቲካ እና የወገኑለትን ከተጠያቂነት ለማስመለጥ በመንግስት ደረጃ ታስቦበት ሲተገበር ማየት እጅግ ያማል። ሰዎች በማንነታቸውና በሃሳባቸው ብቻ ተፈርጀው፣ ታስረው እና በሃሰት ሽብርተኛ ተብለው ተከሰው በሚጉላሉበት አገር ብዙ ጥፋትና ወንጀል የፈጸሙና ያስፈጸሙ ሰዎች ደግሞ ያለጠያቂት በነጻነት ይንቀሳቀሳሉ።
ታዮ ደንድአን በሰንሰለት አስሬ ፍርድ ቤት ካላቀረብኩ ማለት ከፖለቲካ በቀል ውጪ ሌላ ትርጉም የለውም። አንድ እስረኛ በሰንሰለት ታስሮ ፍርድ ቤት የሚቀርበው እስረኛው አንድም ሊያመልጥ ይችላል ወይም ጉልበተኛ ሆኖ ፖሊሶቹን ወይም ዳኞችን ሊተናኮስ ይችላል ተብሎ ሲታሰብ ነው። ታዬን ማሰር ግን አላማው ማዋረድ፣ ማሸማቀቀ እና ፍትህን መበቀያ ማድረግ ነው። የታዮ ሁኔታ ሲገርመኝ ባለቤቱን ቀነኒን በመግደል ፖሊስ ጠርጥሮና ማስረጃ አሰባስቦ ለአቃቤ ሕግ ክስ እንዲመሰርትበት የተላለፈውን ፋይል በመዝጋትና ተጠርጣሪውን በመልቀቅ የወንጀሉን ጉዳይ አባገዳዎች በሽምግልና እና በካሳ እንዲጨርሱት ማድረግ ከነውርም አልፎ የፍትህ ሥርዓቱ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ማሳያ ነው። ( Yared Hailemariam )
ከወረታ ደብረታቦር ባለው አውራ ጎዳና በአገዛዙ ተደራጅተው በፋኖ ስም ሲዘርፉ የነበሩ ባንዳዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ መወሰዱ ተነገረ!
በአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ኮር ስር ከነበልባሉ ፎገራ ክ/ጦር የተወጣጡ የፋኖ አሃዶች በወረታ እና በደብረታቦር መካከል ሀገረ ሰላም፣ አርባ አምባ፣ በቆሽ በርና ውር ተብለው በሚጠሩ አከባቢዎች ላይ በወሰዱት እርምጃ በርካታ ባንዳዎችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ቀጠናውን ማፅዳታቸውን መረብ ሚዲያ ከክፍለጦሩ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለማረጋገጥ ችሏል።
ፋኖ፡ አገዛዙ የአማራ ሕዝብን በማሕበራዊና በኢኮንሚያዊ ሕይወቱ እረፍት እንዲነሱለት አደራጅቶ ያሰማራቸው ዘራፊ ወንበዴዎች ላይ የሚወስደውን ጥብቅ እርምጃ አጠናክሮ ቀጥሏል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ለክፍለ ጦር አመራሮችና ለሰራዊት አባሎች ፖለቲካዊ ስልጠና ሰጠ!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ ኮር ለተከታታይ ሶስት ቀናት አጠቃላይ ለክፍለጦር፣ለሻለሻለቃ አመራሮችና አጠቃላይ ለሰራዊቱ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። እንደሚታወቀው የአብይ አህመድ አገዛዝ ወሮበላው የኦሮምማው ስብስብ አማራን ለማጥፋት በተለያዩ የአማራ ግዛቶችና ከአማራ ግዛቶች ውጭ ባሉ የአማራ ተወላጆች ላይ የዘር ፍጅት እያደርገ መሆኑን አለም የሚያቀው ሀቅ ነው።
ሆኖም ይህን የብልፅግና ፋሽስታዊ ስርዐት የአማራ ልጆች በነበልባል ክንዳቸው እየተፋለሙትና እየመከቱ የበላይነታቸው እየወሰዱ ይገኛል። ስለሆነም የአሳምነው አናብስቶች ከትግሉ ጎን ለጎን በተለያዩ ለሰራዊት ፖለቲካዊ ስልጠና ማለትም፦
*የሰራዊት ስነምግባር እና ስነስረዓት መወሰኛ ደንብ
*ጓዳዊ ዝምደና
*ባህል እና ጨዋነት
*ድርጅትና የድርጅት ምንነት
*የአማራ ህዝብ ምንነት እና *የገጠሙት ፈተናወች እና ያደረጋቸው ተጋድሎወች
*ፋኖነት እና መገለጫ ባህሪያት በሚሉ
አርዕስቶች ላይ ለተከታታይ ሶስት ቀናት በአሳምነው ዕዝ ምክትል ድርጅት ጉዳይ አርበኛ ኢያሱ ሙሉጌታ ፣የአሳምነው ዕዝ ህግ ክፍል ሀላፊ አርበኛ ተስፋዬ ገስጥ እና የአሳምነው ዕዝ ሎጀስቲክ ኃላፊ ሻለቃ ሞገስ ለማ በመሆን ከትምህርት እና ስልጠና መምሪያ በተሰጠው ዕቅድ መሰረት የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ክር አፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለጦር የሻለቃ አመራሮች እና ለሰራዊት አባላት በበቂ ሁኔታ ስልጠና በመስጠት አመርቂ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።
በስልጠናውም የተገኙት የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ ኮር ዓፄ ይኩኖአምላክ ክፍለ ጦር አመራሮችና የሻለቃ አመራር
የህዝቡን አንድነት በማፅናት አስተማማኝ የህዝብ ደጀንነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ የደብረ ኤልያስ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት አስታወቀ።
በአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ በመልሶ ማደራጀት ትግበራው የህዝብን አስተዳደር የፀጥታና የፍትህ ጥያቄዎችን በመመለስ አስተማማኝ የህዝብ ደጀንነትን እንዲያረጋግጥ ታስቦ በአዲስ የተዋቀረው ጊዚያዊ መንግስት በ206ኛ ኮር ባሉ ወረዳዎችና ቀበሌዎች አገልግሎት በመጀመር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
በ206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር ስር የሚገኘው የደብረ ኤልያስ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት ከጠላት ነፃ በወጡ ሁሉም ቀበሌዎች የአስተዳደር መዋቅር በመዘርጋት የፍትህና ህግ አገልግሎት፣ ፀጥታ፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በማከናወን ከህዝቡ የሚነሱ ጥያቄዎችን በፍጥነት ምላሽ በመስጠት አመርቂ ለውጥ እያስመዘገበ መሆኑን የወረዳው ጊዚያዊ መንግስት ገልጿል።
የህዝብን አስተማማኝ ደጀንነት በማረጋገጥ ሰፊ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኘው ጊዚያዊ መንግስቱ የግል ታጣቂዎችን በማደራጀት የአካባቢያቸውን ሰላም በማረጋገጥ እንደቻሉ በማውሳት የሚሰጣቸውን ማንኛውንም ድርጅታዊ ግዳጅ ከመደበኛ ሰራዊቱ ጎን ተሰልፈው እንደሚወጡም አረጋግጧል።
በመልሶ ማደራጀት ትግበራው ባንዳዎችን በማፅዳት የሰራዊቱን የህዝቡንና የትግሉን ደህንነት በማስጠበቅ የጠላትን እረጅም እጅ እየቆረጠ የሚገኘው 206ኛ ኮር ለደብረ ኤልያስ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት አመራሮች፣ በህግና እና ስነ-ስርዓት እንዲሁም በጊዚአዊ መንግስት መመሪያዎች ላይ ከ14ኛ ክ/ጦር አመራሮች ጋር በመተባበር ስልጠና ሰጧል።
የድርጅቱን ህግ እና ደንብ ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የፀደቁ መመሪያዎች ላይ ስልጠና የተሰጣቸው የወረዳ ጊዚያዊ መንግስት አመራሮች ህዝቡን ለማስተዳደርና የድርጅታችንን ህግና ደንብ ለማስፈፀም በቂ ግንዛቤ ማግኘታቸውንም ተናግረዋል ።
የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል
ዛሬ ከንጋት ጀምሮ በደቡብ አማራ ሸዋ ቀጠና ደብረሲና ከተማን ጨምሮ በሾላ ሜዳ፣ በአርማኒያና ጭራ ሜዳ ላይ በተደረገ ትንቅንቅ ፋኖ በጠላት ላይ ከባድ ኪሳራ በማድረስ አንፀባራቂ ድል ማስመዝገቡ ታወቀ!
ወደ ደብረሲና ከተማ ዘልቀው የገቡት የፋኖ አባላቱ፡ በከተማዋ የአየር ወለድ ኮማንዶዎች የሰፈሩበትን ካምፕ በማፈራረስ በርካታ ኮማንዶዎችን ሙትና ቁስለኛ ማድረጋቸውን የመረብ ሚዲያ የግንባር ዘጋቢዎች ለማረጋገጥ ችለዋል።
ፀረ አማራው የብልፅግና ቡድን የፋኖን ጥቃት ለመመከት ከአየር ኃይልና ባሕር ኃይል ጀምሮ የአየር ወለድ ኮማንዶዎቹን፣ መሠረታዊ ወታደሮቹንና ሌሎች ታጣቂዎቹን ያሰለፈ ቢሆንም ነገር ግን ይህ ሁሉ ግብስብስ ኃይል የፋኖን ግስጋሴ ሊያስቆም እንዳልቻለ ነው የተነገረው።
“እየዘፈኑ ድህነት እያለቀሱ ክብረት”
በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ከንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር የተሰጠ መግለጫ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር በሚንቀሳቀስባቸው ከደሴ ከተማ በስተምዕራብ በሚገኙ 11 ወረዳዎች ውስጥ የሰርግ ጥሎሽ አምስት ሺህ ብር ብቻ እንድሆን መወሰኑና በያዝነው ዓመት መባቻ ላይ መመሪያ ማውጣቱ ይታወቃል:: የመመሪያውን ተፈፃሚነት ይከታተል ዘንድ ኮሩ በየወረዳዎች የመደበው ግብረኃይል የሰበሰበው መረጃ እንደሚያስረዳው ህዝባችን ራሱ ያፀደቀውን መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግ ያልቻለበት ሁኔታ ተፈጥሯል:: ወይ መቶ ወይ መተው እየተባለ እስከ መቶ ሺህ ብር ድረስ ጥሎሽ በመጣል ገደብ የለሽ እና ድሀን አግላይ ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑን ደርሰንበታል:: ሰርግ ምስለት እየዘፈኑ ክስረት ሆኗል:: አላማውንም እየሳተ ነው!
በምድር በሰማይ እሳት እየነደደበት ያለው ህዝባችን በጦርነቱ ከደረሰበት የኢኮኖሚ ድቀት እና የማህበራዊ እረፍት እጦት በተጨማሪ በእንቅርት ላይ ጆሮ ገድፍ የሆኑ ባህላዊ ክዋኔዎች አሉ:: ከእነዚህ ባህላዊ አሰራሮች አንዱ የሆነው በተጋነነ ድግስ የሚከወን የሰርግ ስነ ስርዓት ነው:: ለሰርግ ብቻ ሳይሆን ለተዝካር እና ሰደቃ ያለ የሌለን ጥሪት አሟጦ የመደገስ ውሳኔ ከሀይማኖት ባሻገር ባህላዊ እየሆነ ነው:: ሐይማኖቶች በሚፈቅዱት መሰረት ተብቃቅቶ ህይወትን መምራትና አላስፈላጊ ወጭዎችን መቀነስ ተገቢ ስለሆነ ይህን ለማድረግ ይቻል ዘንድ የንጉሥ ሚካኤል አሊ ኮር በሰርግ ዙሪያ መመሪያ አውጥቷል:: ይህ መመሪያ የሚደነግገው የሰርግ ጥሎሽ ከ 5 ሺህ ብር መብለጥ እንደሌለበት ነው::
መመሪያውን ተላልፎ የሚገኝ አካል 10 ሺህ ብር የሚቀጣ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ከ5 ሺህ በላይ
ከሶማሊያ በተናጥል ውሳኔ የተገነጠለችው ሶማሊላንድ ከ30 ዓመታት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በኋላ የመጀመሪያውን የአገርነት ዕውቅና ታኅሣሥ 17/2018 ዓ.ም. እስራኤል ሰጥታለች። ሶማሊላንድ እውቅናውን ያገኘችው፣ እስራኤል እና ሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአረብ አገራት ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲፈጥሩ በነደፉት “የአብርሃም ስምምነት” ማዕቀፍ አንዳቸው ለሌላኛቸው እውቅና ለመስጠት እና ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለመጀመር መስማማታቸውን ተከትሎ ነው።
ዕውቅናው የሶማሊላንድን ሕዝብ በደስታ ሲያስፈነድቅ፣ ከአፍሪካ እስከ መካከለኛው ምሥራቅ የዘለቀ ብርቱ ተቃውሞም ቀስቅሷል።
የሶማሊላንድ የዕውቅና ጥያቄ አነሳስና ጉዞ
የሶማሊላንድ የሉዓላዊ አገርነት የዕውቅና ጥያቄ በአውሮፓውኑ 1960 ከብሪታንያ እንዲሁም ደቡባዊቷ ሶማሊያ ከጣሊያን ቅኝ አገዛዝ ነጻ በወጡ ማግስት የሚጀምር ነው። ሶማሊላንድ ከብሪታንያ ነጻ በወጣች በአጭር ጊዜ ውስጥ በፍቃዷ ከሶማሊያ ጋር ተዋሃዳ ነበር። በእነዚያ አጭር ቀናት ውስጥ እንደ ሉዓላዊ አገር ካወቋት ከ30 በላይ አገራት መካከል አንዷ እስራኤል ነበረች።
ሆኖም በአውሮፓውያኑ 1980ዎቹ በግዛቲቷ አብላጫ ቁጥር ያለው የኢሳቅ ጎሳ አማጺ ቡድን የማዕከላዊውን የፕሬዝዳንት ዚያድ ባሬ ወታደራዊ መንግሥት አፈና እና መድልዖ በመቃወም የትጥቅ ትግል ማካሄድ ጀመረ። ሶማሊያም በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገባች። ቡድኑ ከሌሎች ታጣቂ ቡድኖች ጋር በመተባበር የዚያድ ባሬን መንግሥት በአውሮፓውያኑ 1991 ከጣለ በኋላ፣ ብዙም ሳይቆይ ነበር ሶማሊላንድ ነጻ አገር መኾኗን ያወጀችው።
ከዚያም ሶማሊላንድ በ2001 (እአአ በመጀመሪያው ፕሬዝዳንቷ መሐመድ ኢጋል አመራር በ97 በመቶ ድምጽ የግዛቲቱን ነጻነት የሚያውጀውን ሕገመንግሥት በሕዝበ ውሳኔ አጽድቃለች። በዓለም አቀፍ ሕግ ይፋዊ የነጻ አገርነት ጥያቄዋ የሚጀምረው ያኔ ነው።
ግዛቲቱ በዚሁ ሕገመንግሥቷ የመድበለ ፓርቲ
የአብይ አህመድ የጥገት ላም የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም ለደንበኞቹ የአገልግሎት ታሪፍ ጭማሪ ማድረጉን አስታወቀ
የሳፋሪ ኮምን ብስጭት፣ የሩቶን ቁጣ፣ የሰሞኑን የቴሌኮም ገበያን ንትርኮችን የአይ ኤም ኤፍ ግፊት ተከትሎ ኩባንያው በተለያዩ አገልግሎቶች ላይ ያደረገው አማካይ የ ዋጋ ጭማሪ የ23% በመቶ እንደሆነ ሰምተናል።
ኢትዮ ቴሌኮም ይህን የታሪፍ አገልግሎት ጭማሪ ያደረኩት፤ ተለዋዋጭ የ ማክሮ ኢኮኖሚ ፤ የካፒታል እና የስራ ማስኬጃ ወጭዎች ከፍ በማለቱ ነው ሲል ችግሮቹን ለመደባበቅ ጥሯል።
ከዚህም ባለፈ ኩባንያው፤ የአገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ የታሪፍ ጭማሪ አድርጌያለሁ ብሏል።
በዚህም መሰረት የ ዋጋ ጭማሪ ከተደረገባቸው አማካይ 23 በመቶ ውስጥ የቴሌብር ልዩ ስጦታ ጥቅል የ10% ቅናሽ ወደ 20% ከፍ ብሏል።
ኩባንያው ካሉት አብዛኛው ጥቅሎች ላይ 38 የተለያዩ ጥቅሎች ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አላደረኩም ሲል ዋሽቷል።
ከዚህ ውስጥም በውስጥ አሰራር በደቂቃዎች ላይ ሽፍጥ የተሰራባቸው የ1 ብር፣ የ2 ብር፣ የ5 ብር እና የ1 ሰዓት ጥቅሎች ባሉበት እንዲቀጥሉ ወስኛለሁ ማለቱ አነጋጋሪ ሆኗል።
በተመሳሳይ የኢትዮዽያን የቴሌኮም ኢንዱስትሪ ሁለተኛ አቅራቢ ሆኖ የተቀላቀለው ሳፋሪኮም ኢትዮዽያ የታሪፍ ጭማሪ ማድረጉ ይታወቃል።
ሳፋሪኮም ኢትዮዽያ ይህንን ጭማሪ ያደረገው በተመሳሳይ የኢንቨስትመንት እና የኦፕሬሽናል ወጪዎች ከፍ ማለታቸውን ተከትሎ እንደሆነ ሰምተናል።
ሳፋሪኮም ኢትዮዽያ በበኩሉ በአገልግሎቶቹ ላይ ከ 20 በመቶ ጀምሮ እንደየደረጃው እስከ 80 በመቶ ጭማሪ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
የነ አሰፋ ቸኮለ ሰሜን ምስራቅ ዕዝ ዛሬም በድጋሚ አከርካሪው ተሰብሯል!
በዕዙ ስር በዘመቻ አባናደው ከባድ ጉዳት ደርሶባት ዳግም የተደራጀችው 61ኛ ክ/ጦር ትናንት በስቲያ በተደረገ ውጊያ የሰው ኃይሏን ጨምሮ 197 ወታደሮቿ ሲገደሉ ከ85 በላይ የሚሆኑት ቁስለኛ ተደርገውባታል።
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ላስታ ጄኔራል አሳምነዉ ፅጌ ኮር በአርበኛ አምሳ አለቃ ጌታየ ተፈሪ የሚመራው ጄኔራል ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦርና ዋግሹም ብርጌድ እንዲሁም ከአፋብኃ ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሜጀር ጄኔራል ውባንተ አባተ ኮር የተውጣጡ የፋኖ ኃይሎች በጥምረት ባደረጉት አውደ ውጊያ የጠላት አከርካሪን በመስበር ታላቅ ድል መቀዳጀታቸውን ምኒልክ ዕዝ ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል።
ታህሳስ 19/2018 ዓ/ም ከንጋቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በሰሜን ምስራቅ ዕዝ 803ኛ ኮር ስር በሻምበል ጫላ የሚመራው 61ኛ ክ/ጦር ከዕዙ ሜካናይዝድ ጋር በመሆን መነሻውን ከአይና ቡግና ከተማ አድርጎ ወደ ብርኮ በአራት አቅጣጫ ማለትም በብርኮ ገብርኤል አቅጣጫ፣በጤና ጣቢያው አቅጣጫ፣በጭቃው አቅጣጫ እና በብርኮ ኪዳነ ምህረት አቅጣጫ ለማጥቃት አስቦ ተኩስ የጀመረ ቢሆንም፡ ነገር ግን ከወደ ፋኖ የተሰነዘረበትን የፀረ ማጥቃት እርምጃን መከላከል ሳይችል ቀርቶ ከባድ የሆነ የሰብአዊ፣ ቁሣዊና ሞራላዊ ኪሳራን ተከናንቧል።
በዙ-23፣ በሁለት ሞርታር በበርካታ ዲሽቃና በሌሎች የቡድንና ከባባድ ሜካናይዝድ ታግዞ ተሰልፎ የነበረው የጠላት ኃይል፡ ልብ እና እውነት ከሌለው መሣሪያ ብቻውን ዋጋቢስ መሆኑን አስመስክሮበታል ተብሏል።
የ61ኛ ክፍለ ጦር የሰው ኃይል ኃላፊና ሌሎች የክፍለጦሩ አመራሮችን ጨምሮ 197 የአገዛዙ ወታደሮች ሲገደሉ፡ ከ85
ቀናቶችን በወሰደው ተጋድሎ ባለሽርጡ ክፍለጦር በመደበኛ ውጊያ እና ደፈጣ ጥቃት አመርቂ ድሎችን አስመዘገበ::
ምኒልክ ዕዝ ምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለጦር በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ፋጂ በተባለ ቦታ ማዕረጉ በውል ያልታወቀ የስራዐቱ ወታደር ከፍተኛ አመራር ከጊራና ወደ ፋጂ ሲንቀሳቀስ በተያዘ የተጠና ደፈጣ ጥቃት ከነ ፖትሮሉ እና ከአጀቢዎቹ ጋር በመደምሰስ ድል ተጎናፀፈ።
በእብሪትና ትቢት ተሞልቶ የመጣውን የአብይ አህመድ ጭራቅ ሰራዊት በሀብሩ ወረዳ ፋጂ በተባለ ቦታ በተወሰደ የደፈጣ ጥቃት አንድ ጓድ የስርዐቱ ሀይሎችን በመደምሰስ እና ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ባንዳ የስርዐቱን ወንበር ጠባቂ ሀይሎችን ማቁሰልና መበተን ተችሏል።
ዛሬ ታህሳስ 18/2018 አ.ም ከቀኑ 11:30 በተወሰደ የደፈጣ ጥቃት አመራሩን ከነተሽከርካሪው በመደምሰስና በማውደም አመራሩን ለማሳለፍ ግራና ቀኝ ቦታ ይዘው የነበሩትን የስርዐቱን ወታደር ጭምር በመደምሰሰና በማቁሰል የጥላትን ቅጥረኛ ሰራዊት ወደ መሬት በግስላዎቹ ነፍጥ እየተፈለፈለ የረገፈ ሲሆን፤ ከፊቱ የሚነጠፈውን ጓዱን የተመለከተ ጥላት ለተዎሰነ ሰዓት ባለበት ቁሞ መሸሻውን ቢያማትርም ግስላው ፋኖ ወደ ፊት በማጥቃት”አንድ ጥይት ለአንድ ጥላት” በሚል የአማራ ብሂል ለአንድ ጥላት በአንድ ጥይት ግንባር ግባሩን ተመቷል።
በርካታ ሙት እና ቁስለኛ ያስተናገደው የአብይ አህመድ ሰራዊት የሞራል ውድቀት፤የቁስ ክስረትን በማስተናገድ፣እና የደረሰበትን ብትር መቋቋም ሲያቅተው ሁለት ንፁሀኖችን በዘፈቀደ ተኩስ በመግደል የዘወትር ግብሩንና አቅዶት የመጣውን የጥፋት ተልዕኮ ሳያሳካ ወደ መጣበት ወደ ጊራና ከተማ መመለስ ተችሏል።አገዛዙ ክፉኛ የቆሰለውን ሰራዊቱን በአንቡላንሶች ወደ ጊራና ጤና ጣቢያ ሲያጓጊዝ አምሽቷል።
ከዚህ ጋር ተያይዞም ቀናቶችን በወሰደው የመርሳ
ፋኖ በአምባሰል ግንባር በፈፀመው ስኬታማ የሞርተር ጥቃት አንድ የአገዛዙ መድፍ ሲወድም አራት ተኳሾች መገደላቸው ታውቋል።
አገዛዙ በአምባሰል ግንባር በታሪካዊቷ ውጫሌ ከተማ ዙሪያ ልዩ ቦታው ደንካ ሚካኤል ላይ መድፍ አጥምዶ የዘፈቀደ ድብደባ በመፈፀም የበርካታ ንፅኋንን ሕይወት ሲቀጥፍ፣ አያሌ ሀብት ንብረት ሲያወድም መቆየቱን መረብ ሚዲያ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ መዘገቡ አይዘነጋም።
ፋኖ ትናንት ታህሳስ 17/2018 ዓ/ም በፈፀመው ስኬታማ የሞርተር ጥቃት፡ ንፁኋንን ለእልቂት ሲዳርግ የነበረው የአገዛዙ መድፍ ከነ ተተኳሹ ዶግ አመድ ተደርጓል። በተጨማሪም አራት የመድፍ ተኳሾች በሞርተር ቅንቡላ ፍንጣሪ ተመተው ሕይወታቸው ማለፉን ምኒልክ ዕዝ ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል።
በምኒልክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር ስር በሞርተር ተኩስ ኢላማ “የሞርተር ቅምቡላን ከጥላት ኪስ ውስጥ መክተት ይችላሉ” የሚባልላቸው የ24ኛ ክ/ጦር ሜካናይዝድ ክፍል ምድብተኞች፡ በፈፀሙት ስኬታማ የሞርተር ጥቃት ነው የጠላት መድፍ ከነ ተተኳሹና ተኳሾቹ የወደመው።
በተያያዘ ዜና!
በዚኽው በአምባሰል ቀጠና ከታህሳስ 16/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በተደረገ የጨበጣ ውጊያ በርካታ የፀረ አማራው ብልፅግና ቡድን ተላላኪ ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ መደረጋቸው ተሰምቷል።
መነሻቸውን ከውጫሌ ከተማና ከጎልቮ እንዲሁም ጭሳ አባዲማ ቀበሌዎች ያደረጉ ራሳቸውን “መከላከያ ሰራዊት” ብለው የሚጠሩ የፀረ አማራው አገዛዝ አገልጋዮች በሚኒሻና አድማ ብተና መሪነት በወረዳው አበት ቀበሌ ላይ ማጥቃት ከፍተው የነበረ ቢሆንም፡ ነገር ግን ከወደ ፋኖ የተሰነዘረባቸውን የፀረ ማጥቃት እርምጃን መቋቋም አቅቷቸው ከባድ የሆነ የሰብአዊና ቁሣዊ እንዲሁም ሞራላዊ ኪሳራ መከናነባቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
በዚህ ውጊያ በርካታ ቁጥር ያላቸው
በአርሲ ዞን አቦምሳ ከተማ በቅርብ እርቀት ላይ በሚገኘው ልዩ ስሙ “ሞፈር ግቢ” በተሰኘ ስፍራ ላይ 6 አማራ ኦርቶዶክሳውያን (ንፁሃን ዜጎች) ታግተው ወደ አልታወቀ ቦታ ተወስደዋል ።
በአርሲ ዞን አቦምሳ ከተማ በቅርብ እርቀት በሚገኘው “ሞፈር ግቢ” ተብሎ በሚጠራው ስፍራ፤ በቀን 16/04/2018 ዓ.ም ከአሰኮ ወረዳ ሰንጎ ቀበሌ ለቅሶ ደርሰው ፒካፕ መኪና እያሽከረከሩ ወደ ናዝሪት ከተማ ሲጓዙ የነበሩ 6 ንፁሃን ዜጎች – አማራ ኦርቶዶክሳውያን ታግተው ወደ አልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውን የታጋች ቤተሰቦች መረጃውን አድርሰውናል ።
ይህ አማራ ኦርቶዶክሱን ማረደና በአሰቃቂ ሁኔታ መግደል እንዲሁም ከፍተኛ ገንዘብ በመጠየቅ…ግፈኛው፣ ዘራፊው፣ ገዳዩ የጥምር ቡድን እነኝህንም ንፁሃን ዜጎች አግቶ ከወሰደ በኋላ ለያንዳንዳቸው #አንድ_አንድ_ሚሊዮን_ብር ጠይቋል ። መረጃውን ያደረሱን የታጋች ቤተሰቦች እንዲህ ሲሉም ተደምጠዋል “ይህ መፍትሄ የታጣለት የማንነት ተኮር ግድያ፣ ዘረፋና እገታ…ዛሬም እንደቀጠለ ነው፤ ይሄው ቤተሰቦቻችን አግተው ከወሰዱ በኋላ ስልክ በመደወል እስከ 1 ሚለዮን ብር ክፍሉ አልበለዚያው እንገድላቸዋለን በማለት እያስፈራሩን ይገኛሉ ፥ ገንዘቡን ብንከፍልም ስለመለቀቃቸው ምንም አይነት ዋስትና የለንም፤ ምክንያቱም ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ ገንዘብ እየተቀበሉ ብዙ አማራ ኦርቶዶክሳውያንን ገድለዋል” በማለት ለጣቢያችን ተናግረዋል ።