Home › Archive for VIDEO ቪዲዮ
Blog Archives
የምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ላይ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::
የምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ላይ ዛሬ ህዳር 23/2018 ዓ.ም ማለዳ 3:00 ጀምሮ እስከ ቀን 6:00 ከፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ጋር በመፋለም ታላቅ ድል አስመዝግበዋል::
ጠላት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ከተማን ለመቆጣጠር ከኮንና ጋሼና አንድ ክፍለጦር ዙ23ን ጨምሮ እንዲሁም ከወገል ጤና አንድ ክፍለ ጦር ዙ 23 ጋር ወደ ዳውንትና ፀሃይ መውጫ ማጥቃት ያደረገ ሲሆን ከምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለ ጦር እና ከደጋው መብረቅ ኮር ከፅናት መክትና ሰንጥቅ ክፍለ ጦር የተውጣጡ ሻለቆች እንዲሁም ሌሎች በመደራጀት ላይ ያሉ አሃዶች በጥምረት የጠላትን ሰራዊት ለጊዜው በስም ያልታወቁ አመራሮችን ጨምሮ በመደምሰስና በማቁሰል ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ ብሎም ቀጠናውንና ከተሞቹን በማስከበር ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::
በዚህ በድንቅ መናበብ በተመዘገበ ታላቅ ፍልሚያና ድል የጠላት ሰራዊት በሁሉም አቅጣጫ የተመታ ሲሆን አስከሬንና ቁስለኛውንም እያነሳ ወደመጣበት አቅጣጫ ሽሽቷል:: በተጋድሎው በመደራጀት ላይ ያለ የልዩ ዘመቻ አሃድም የተሳተፈ ሲሆን ከልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር አንድ ጓድ በውጊያ መሃል ደፈጣ ጥቃት በመፈፀም ታላቅ ጀብድ ሰርተዋል::
በዚህ ታላቅ ተጋድሎ ከባድ ምት የተመታው አገዛዙ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገባ ሲሆን የደላንታና የወገል ጤና የብልፅግና ካድሬዎችና አመራሮች ተከበናል መላም የለን እያሉ ወደ ደሴ ከተማ መሸሽ ጀምረዋል:: ውጊያው አሁንም ሌሎች አሃዶች ተጨምረውበት ተጠናክሮ ቀጥሏል::
አፋብኃ ምስራቅ አማራ
ወልዲያ ከተማ ውስጥ የሚገኙ በርካታ የዓብነት ተማሪዎች ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ታፍሰው መወሰዳቸው ታወቀ –
“ቤተ ክርስቲያኒቱ ተማሪዎቹ እንዲለቀቁ በደብዳቤ ብትጠይቅም እስካሁን ምላሽ አልተገኝም። አፍነው የወሰዱት የሚሊሻ አባላት በወሰዱት በእያንዳንዱ ተማሪ 7 ሺህ ብር እየጠየቁ ይገኛሉ”
– ከተያዙት ተማሪዎች መካከል አንደኛው ባሳለፍነው አርብ ለማምለጥ ሲሞክር ከሚሊሻ በተተኮሰበት ጥይት ተመትቶ ከፒያሳ ወደ ቲንፋዝ በሚወስደው መንገድ ላይ ህይወቱ ማለፉ ታውቋል ተጨማሪ ያንብቡ: https://meseretmedia.org/p/2b4
Op<በአረጋ ከበደ ላይ በጎጃም የሞርታር ጥቃት ተፈፀመባቸው …… የፋኖ ኃይሎች የተሳኩ የደፈጣ ጥቃቶችን አድርገዋል ……. በወሎና በጎጃም በርካታ የአብይ ወታደሮች በቡድን እጅ እየሰጡ ነው። …… እነዚህን እና ሌሎች በርካታ የግንባር መረጃዎችን ይዘናል ያድምጡን …….. https://x.com/merejatv/status/1995716216443248895?s=20
ከአገዛዙ በተሰጣቸው ተልዕኮ መሠረት በእገታና ዝርፊያ ድርጊት ላይ ተሰማርተው የነበሩ የአድማ ብተና አባላት በፋኖ ቁጥጥር ስር ዋሉ!
በፋኖ ቁጥጥር ስር የዋሉት የአድማ ብተና አባላቱ፡ በፋኖ ስም ዝርፊያና እገታ፣ እንዲሁም አስገድዶ መድፈርና ሌሎች ወንጀሎችን እንዲፈፅሙ ከአገዛዙ ተልዕኮ ተቀብለው በየአከባቢው መሰራጨታቸውን ገልፀዋል።
ፋኖ፡ የትግሉን ገፅታ ለማበላሸት እንዲሁም በፋኖና በሕዝቡ መካከል ቅሬታና ጥርጣሬን ለመፍጠር ከብልፅግና ተልዕኮ ተቀብለው በእንደዚህ አይነት እኩይ ድርጊት ተሰማርተው በሚገኙ ወንጀለኞች ላይ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ጥብቅ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
ዝርዝር ዜናውን አድምጡ👉 https://x.com/i/status/1995002606674972836
የትግራይ ክልል ወቅታዊ የፖለቲካ አሠላለፍና የጦርነት ሥጋት
የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ የፌዴራል መንግሥት ሌላ ዙር ጦርነት በትግራይ ላይ ለመክፈት እየጣረ ነው ሲል ወንጅሏል፡፡ ማዕከላዊ ኮሚቴው ለተከታታይ ቀናት ስብሰባ በማድረግ… https://ethiopianreporter.com/148268/
የጥንቶቹ ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ከወራሪዎችና ከተስፋፊዎች በመከላከል ብዙውን የዕድሜያቸውን ክፍል አሳልፈው በክብር ሲያልፉ፣ በተነፃፃሪ የተሻለ ዘመን ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያን እርስ በርስ ሲናቆሩ አገራቸውን ለድህነት መዳረጋቸው ብዙዎችን የሚያስቆጭ ነው፡፡ ለአገራቸው በሁሉም መስኮች ትልልቅ አስተዋጽኦዎች ማበርከት የሚችሉ ወጣቶች በየቦታው ሲታኮሱና ሲጋደሉ ኖረው ያተረፉት ሞትና ጉስቅልና ነው፡፡ ጥራት ያለው ትምህርት አግኝተው ከራሳቸውና ከቤተሰቦቻቸው አልፈው ለአገራቸው የሚተርፍ ሀብት ማፍራት የሚችሉ ወጣቶች፣ በማይረቡ ምክንያቶች ጎራ በለዩ ፖለቲከኞች ሳቢያ በተቀሰቀሱ ግጭቶች ሕይወታቸውን ገብረዋል፡፡ በስክነት ተነጋግረው ልዩነቶቻቸውን ፈር ማስያዝ ባልቻሉ ፖለቲከኞች ምክንያት አገር ተበድላለች፡፡ ለኢትዮጵያ ልማትና ዕድገት ሊውል የሚገባው የወጣት ኃይልና የተፈጥሮ ሀብት፣ በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ ጦርነቶች በመማገዱ ድህነት መታወቂያ ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያ ምንም ሳታጣ የነጣች ደሃ የሆነችው በምን ምክንያት እንደሆነ በርካታ ምሳሌዎችን ማቅረብ ይቻላል፡፡
ፖለቲከኞች ከበፊት ጀምሮ ችግሮቻቸውን በሠለጠነ መንገድ መፍታት ቢችሉ ኖሮ፣ አገርን ከማንኛውም ዓይነት ወረራ የመጠበቅ አኩሪ ታሪካዊ እሴት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ተዓምር መፍጠር እንደሚችሉ ማንም አይስተውም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሠርቶ የሚያሠራው ቢያገኝ እንኳን ለአፍሪካ ለዓለም የሚተርፉ ምርቶችን ማምረት ይችል ነበረ፡፡ በቀን ሦስቴ መመገብ የሰማይ ያህል ሊርቀው ቀርቶ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም ኤክስፖርተር መሆን አያቅተውም፡፡ ልዩነቶቻቸውን በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ማስተናገድ ባቃታቸው ፖለቲከኞች ምክንያት ግን፣ እንኳንስ የተመጣጠነ ምግብ ሊመገብ ቀርቶ በቀን አንዴ በልቶ ለማደር ሰማይ ጠቀስ ተራራ የመውጣት ያህል በእጅጉ እየከበደው ነው፡፡ በአፍሪካ በተፈጥሮ ሀብቶች ተጠቃሽ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ሕዝቧ የተመጣጠኑ ምግቦች ማግኘት ሁሌም ብርቁ ናቸው፡፡ የአፍሪካ የውኃ ቋት
በምዕራብ ሐረርጌ የታፈነው ጩኸት እና በአርሲ የቀጠለው ዘር ፍጅት
በምዕራብ ሐረርጌ ዞን፣ ጭሮ ወረዳ፣ ላሎ ጉዶ ቀበሌ፣ ኢፈ ባስ(ifabaas) በምትባል የገጠር መንደር ውስጥ በኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 እልፌ ተስፋ ወሌ የሚባሉ እናት በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል። በዚኹ ቀበሌና በአጎራባች ቀበሌዎች ያብዶ ሸንበቆ፣ ረብሱ፣ ሼክ አደም፣ ሉጎ በርካታ ሃይማኖትና ማንነትን ማዕከል ያደረጉ ጭፍጨፋዎች የሚካሄዱባቸው ናቸው። ብንናገርም ሰሚ የለም። ሕዝቡና ሚዲያውም እኛን ረስቶናል ይላሉ የአካባቢው ነዋሪዎች በምሬትና በፍርኃት ተውጠው።
በወረዳው በቅርቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት የኾኑ ተፈሪ መንገሻ ከነ ባለቤቱ ቀለሟ በለጠ ጋር፣ ባለው መንገሻ፣ አሳምነው አባይነህ የተባሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በአሰቃቂ ኹኔታ በስለትና በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል። ግድያውን የሚፈጽመው በአካባቢው ሰዎች አጠራር ኦነግ ሸኔ(ራሱን ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል) ነው።
ይኽን መረጃ እያጣራን ባለንበት አፍታ በአርሲ ዞን በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ፣ በቀቅሳ ቀበሌ በአጨዳ ላይ የነበሩ ከ19 በላይ ገበሬዎች ኅዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም ታፍነው መወሰዳቸውን ከቦታው ለማረጋገጥ ችለናል። በዚኹ አካባቢ በቅርቡ ወንድማማቾችን ጨምሮ ሦስት ንጹሓን እንደተገደሉ ይታወሳል።
እናት ፓርቲ በምዕራብ ሐረርጌ ባሉ በርካታ ቀብሌዎች በጥንቃቄ ተደብቆ የሚካሄድውን ጭፍጨፋና እገታ፤ እንዲኹም በአርሲ እየተካሄደ ያለውን ዘር ፍጅት በጽኑ እናወግዛለን፤ የታገቱትም ያለምንም ቅድመ ኹኔታ እንዲፈቱ እንጠይቃለን።
እናት ፓርቲ
በመቐለ ከተማ ትናንት ኅዳር 18 ምሽት 4 ሰዓት ተኩል ገደማ ልዩ ስሙ “ዓዲ ሓቂ” በሚባል አካባቢ የቦንብ ፍንዳታ መድረሱን የከተማዋ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የከተማዋ ሰላምና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ረድሀኝ ፍስሃ፣ “ሕዝብን ለማሸበር ተልዕኮ የተሰጣቸው የጥፋት ኃይሎች” ሲል የጠራቸው አካላት የቦንብ ጥቃቱን መፈጸማቸውን እና ሆኖም የቦንብ ፍንዳታው በሰው ወይም በንብረት ላይ ጉዳት እንዳላደረሠ መናገራቸውን የመቐለ ኤፍኤም ሬድዮ ዘግቧል። በቦንብ ጥቃቱ የከተማዋ ነዋሪዎች መሸበራቸውን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ፤ የጥቃቱ ዓላማ “ሁከት እና ብጥብጥ ለመፍጠር ሆን ተብሎ እና ታስቦበት የተፈጸመ ነው” ብሏል። ጽሕፈት ቤቱ፣ የጸጥታ አካላት የቦንብ ጥቃቱን ፈጻሚዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል በጋራ እየሠሩ መሆኑንም ገልጧል። መሰል ጥቃቶችን በማቀነባበር ተግባር ላይ የተጠመዱ ግለሰቦች፤ በከተማዋ ውስጥ ከፍተኛ ችግር እንደተፈጠረ በማስመስል ሃሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ ነው በማለት የከሠሠው ጽሕፈት ቤቱ፣ ሆኖም ከቦንብ ጥቃቱ ውጪ ሌላ አንዳችም ችግር አልተፈጠረም ብሏል።
የታደሰ ወረደ አመራር ውድቀት ገጥሞታል፤ አዲስ መንግስት መቋቋም አለበት ሲል የትግራይ አለማቀፍ ምሁራን ስብስብ ጥሪ አቀረበ
ዋዜማ የተመለከተችው ሪፖርቱ በአቶ ጌታቸው ረዳ አመራር ወቅት ምክክር ተደርጎባቸው ትግራይ ከቀውስ ለማውጣትና የክልሉን ዘላቂ ጥቅሞች ለማስከበር የተለዩ አስር ጉዳዮች ላይ አሁን በሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ አመራር ፍፁም ተዘንግተው ክልሉን ለበለጠ አደጋና የጦርነት ስጋት ዳርገውታል ብሎ ያምናል።
ዝርዝሩን ያንብቡት-https://cutt.ly/4tymlVmv
” በማርበርግ ቫይረስ ምክንያት ከዛሬ ህዳር 20/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ1 ሣምንት ትራንስፖርት ዝግ ይሆናል” – የዞኑ መንግስት
በጂንካ ተከስቶ ለሰዎች ሞት ምክንያት እየሆነ ያለዉን የማርበርግ ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር ያስችል ዘንድ ወደ በሽታዉ መነሻ የአሪ ዞን የሚገባም ሆነ የሚወጣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ለ1 ሣምንት ዝግ እንዲሆን በአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብር ሃይል መወሰኑን የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ደምመላሽ አቦነህ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የቫይረሱ ስርጭት ከዕለት እለት አስከፊ እየሆነ በመምጣቱ የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር በአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብረሀይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኃላፊዉ እስካሁን በነበረው ሂደት ትምህርት ቤቶች የተዘጉና ፣ ሕዝብ የሚሰበሰብባቸዉ ጉዳዮች ላይ እቀባ የተጣለ ቢሆንም ስርጭቱን በሚፈለገዉ ልክ መግታት ባለመቻሉ የትራንስፖርት ዘርፉን ለ1 ሳምንት መዝጋት አስፈላጊ በመሆኑ ከዛሬ ህዳር 20/2018ዓም ጀምሮ ለ1 ሳምንት ዝግ እንዲሆን ግብረሀይሉ መወሰኑን ተናግረዋል።
ጂንካ ከተማን ጨምሮ ለሁሉም መዋቅር የትራፊክ ፍሰት እና የፀጥታ ዘርፍ አስተባባሪዎች ይህ መልዕክት መተላለፉንም አቶ ደምመላሽ አስታዉቀዋል።
በዚህ መሰረት ከክልል በወረደው አቅጣጫ መሰረት አገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ለ1 ሳምንት የታገደ ሲሆን በከተማ የሁለት እግር ተሽከርካሪዎችና የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ብሎም በዞኑ ውስጥ የሚኖሩ የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች በቀጣይ ቀናት ውስጥ ውሳኔ እንደሚሰጥባቸው ገልፀዋል።
ኃላፊው አያይዘውም በአሁኑ ወቅት የማርበርግ በሽታ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ የተከሰተ ቢሆንም ጂንካ ለቅሶ መጥቶ የተመለሰ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ በበሽታዉ መሞቱን መስማታቸዉንና የስርጭት
Posted in
Amharic News,
Ethiopia News,
News,
NRS-Import,
VIDEO ቪዲዮ,
አዉሮጳ,
አፍሪቃ,
ኢትዮጵያ,
ኤኮኖሚ,
ጀርመን,
ፖለቲካ
11 ክርስቲያኖች በምሥ/ አርሲ ተገደሉ
በምሥራቅ አርሲ እንቆሎ ዋቤ ወረዳ በመጭቱ በቀቅሳ ቀበሌ ነዋሪዎች የነበሩ አሥራ አንድ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች መገደላቸውን ምንጮች ለአደባባይ ሚዲያ ተናግረዋል።
ሕዳር 18 ቀን 2018 ዓ.ም መገደላቸው የተረጋገጠው ክርስቲያኖች በነፍሰ ገዳዮቹ ታግተው ተወስደው እንደነበር ምንጮቻችን ገልጸውልናል።
በርካታ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የሚኖሩበት ቤት ‘መሬት ባንክ ገብቷል’ እየተባሉ የቤት ሽያጭ፣ እድሳት እና ስም ማዞር መከልከላቸው ተሰማ
ከ16 ሺህ በላይ ቤቶች መሬት ባንክ መግባታቸው የታወቀ ሲሆን ጉዳዩ ያጋጠማቸው ነዋሪዎች ህዝቡ በየክፍለ ከተማው እየሄደ ቼክ እንዲያስደርግ መክረዋል
ተጨማሪ ያንብቡ:
https://www.meseretmedia.org/p/be1
ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ኡጋንዳ የአፍሪካ ቀንድ አገራት ከሆኑት ከኢትዮጵያ፣ ከኤርትራ እና ከሶማሊያ ለሚመጡ ሰዎች የስደተኝነት ምዝገባ ማቆሟን አስታወቀች።
የኡጋንዳ እርዳታ፣ የአደጋ ዝግጁነት እና የስደተኞች ሚኒስትር ሂላሪ ኦኔክ እንደተናገሩት ሠራተኞቻቸው ከሦስቱ አገራት የሚመጡ ስደተኞችን እንዳይመዘገቡ ማዘዛቸውን እና ለዚህም ምክንያቱ “በአገራቱ ውስጥ ድጋፍ ስለሌለ” መሆኑን ጠቅሰዋል።
ይህ የሚኒስቴሩ ውሳኔ የተሰማው ወደ ኡጋንዳ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበት እና ከለጋሾች ለስደተኞች ተብሎ የሚመጣው ድጋፍ በመቀነሱ እንደሆነ የኡጋንዳ ዘ ዴይሊ ሞኒተር ዘግቧል።
ቀደም ባሉት ዓመታት ከሦስቱ አገራት የሚወጡ ስደተኞች መዳረሻ ኬንያ የነበረች ሲሆን፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ኡጋንዳን የተሻለች አድርገው በመምረጣቸው በርካታ ስደተኞች ከኢትዮጵያ፣ ከኤርትራ እና ከሶማሊያ ወደ አገሪቱ እየገቡ ነው።
የአሁኑ የእገዳ ወሳኔ አዲስ የሚመጡ ሰደተኞችን የሚመለከት እንጂ ቀደም ሲል ወደ ኡጋንዳ በመግባት የተመዘገቡትን የሦስቱን አገራት ሴጎች የሚመለከት እንዳዳልሆነ ተገልጿል።
ሚኒስትሩ እስካሁን ወደ ኡጋንዳ የገቡት ስደተኞች ቁጥር ወደ ሁለት ሚሊዮን እየደረሰ አና በየዕለቱ እየጨመረ መሆኑን አመልክተው፤ በየቀኑ “በአንድ መቶ እና በ200 መካከል የሚቆጠሩ ሰደተኞች ከዲሞክራቲክ ኮንጎ ብቻ” ወደ ኡጋንዳ ይገባሉ” ብለዋል።
ኡጋንዳን በበርካታ ስደተኞች ተመራጭ የሆነችው ስደተኞች በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ፣ በሥራ እና በንግድ አንዲሰማሩ ከመፍቀዷ በተጨማሪ ለዜጎች የተፈቀዱ አገልግሎቶች መጠቀም ስለሚችሉ ነው።
ሚኒስትሩ እንዳሉት ኡጋንዳ ስደተኞችን ለመደገፍ በየዓመቱ ሁለት ቢሊዮን ሽልንግ (የኡጋንዳ ገንዘብ) ታወጣለች።
አሁን ኡጋንዳ እንዳይመዘገቡ እገዳ የጣለችባቸው የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ እና የሶማሊያ ስደተኞች በዋናነት በፖለቲካዊ ምክንያቶች፣ በጦርነት እና የአገራቸውን መንግሥታት
የፌደራሉ ዓቃቤ ሕግ በቀድሞው የሠላም ሚንስትር ዴኤታ ታዬ ደንደአ ላይ ሦስት አዲስ ክሶች መመስረቱ ተሰማ ። ዓቃቤ ሕግ በታዬ ላይ አዲስ ከመሠረታቸው ክሶች መካከል አንዱ፣ የሕወሃት ኃይሎች በ2013 ዓ፣ም በመከላከያ ሠራዊት ሰሜን እዝ ላይ በፈጸሙት ጥቃት ዙሪያ ተከሳሹ ሃሰተኛ መረጃ እና ፕሮፓጋንዳ አሰራጭተዋል የሚል እንደሆነ የታዬ ጠበቃ አበራ ንጉሥ ተናግረዋል። ሌሎቹ ሁለት ክሶች ደሞ፣ ከጸረ ሠላም ኃይሎች ጋር በማበር መንግስታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ ማሴር እና ድጋሚ ከመታሠራቸው በፊት “ሆርን ኮንቨርሴሽን” ለተሰኘ የበይነ መረብ ጣቢያ በሰጡት እና እስር ላይ ሳሉ በሦስት ክፍሎች በተላለፈው ቃለ ምልልሳቸው “የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ የሚጥል የተሳሳተ መረጃ አሰራጭተዋል” የሚሉ መሆናቸውን ጠበቃቸው ነግረውናል። ፍርድ ቤቱ፣ በአዲሶቹ ክሶች ላይ የተከሳሹን መልስ ለመስማት ለኅዳር 23፣ 2018 ዓ፣ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን አስረድተዋል።
የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ በባሕር በር ዙሪያ መግለጫዎችን በማውጣት ኢትዮጵያን የቀይ ባሕር ቁልፍ ባለድርሻ እንድትሆን የሚያደርገው ሙከራ “የማይሳካ”ነው ሲል አጣጥሏል። ሚንስቴሩ፣ ለኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሚቀርቡት “የኢኮኖሚ አስገዳጅነት”፣ “የደኅነት” እና “የታሪክ” መከራከሪያዎች የማያዛልቁ ናቸው ብሏል። ሚንስቴሩ፣ ኢትዮጵያ የአፋርን ሕዝብ ማንነት በመጥቀስ፣ በኤርትራ ሉዓላዊ የባሕር ዳርቻ ላይ የተፈጥሮ መብት አለኝ ለማለት ትፈልጋለች በማለት ተችቷል። የሁለት አገር ሕዝቦች ዝምድና የባሕር በር ለመቆጣጠር በማስረጃነት ቢወሠድ ኖሮ ኦጋዴንም ወደ ሶማሊያ ሊጠቃለል ይችላል ያለው ሚንስቴሩ፣ የኢትዮጵያ የቆዳ ስፋትም የባሕር በር ባለቤትነት ሊያጎናጽፋት አይችልም በማለት ሞግቷል። ሚንስቴሩ፣ ኤርትራ ነጻ አገር የኾነችው ኢትዮጵያን የባሕር በር ለማሳጣት አልባ ለማድረግ ነው የሚለው መከራከሪያም፣ ሐሰተኛ እና ትርጉም አልባ ነው በማለት ተችቷል።
የግብጽ የውሃና መስኖ ሚንስቴር፣ ኢትዮጵያ ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ በተናጥል እና ባልተቀናጀ ሁኔታ ከፍተኛ ውሃ በመልቀቅ ችግር እየፈጠረች ትገኛለች በማለት ሰሞኑን አዲስ ክስ አቅርቧል። የግድቡ የውሃ አለቃቅ ተለዋዋጭነት በግድቡ ላይ ቴክኒካዊ እና ሳይንሳዊ አስተዳደር እንደሌለ ያሳያል በማለት የተቸው ሚንስቴሩ፣ ግብጽ በዚሁ ሳቢያ ከአስዋን ግድብ የቶሽካ ማስተንፈሻን ለመክፈት ተገዳለች ብሏል። ሚንስቴሩ “ያልተቀናጀ” እና “ሳይንሳዊ ያልሆነ” ያለው የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ የውሃ አለቃቀቅ፣ በታችኛው ተፋሰስ አገራት ግድቦች ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል በማለትም ወቅሷል። በተያዘው ኅዳር ወር ሦስት ሳምንታት ውስጥ ከሕዳሴ ግድብ በቀን የተለቀቀው ውሃ 180 ሚሊዮን ሜትር ኪውብ መሆኑንና ይህም በዚህ ወቅት ቀደም ባሉት ዓመታት ይለቀቅ ከነበረው የውሃ መጠን በ80 በመቶ እንደሚበልጥ ሚንስቴሩ ጠቅሷል።
በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ አማራዎች አገዛዙ በህዝባቸው ላይ የሚፈፅመውን ግፍና ሰ’ቆቃ በማውገዝ አደባባይ ወጥተዋል …. የቡድን 20 አባል ሀገራት ስብሰባ በሚደረግበት አዳራሽ ፊለፊት በተካሄደው በዚህ ተቃውሞ ላይ ” Stop Amhara Genocide, Stop the hidden Amhara Genocide in Ethiopia , We demand Immediately Intervene & Stop Military Aggression into Amhara Region, …etc ” የመሳሰሉት መልዕክቶች ተስተጋብተዋል……… ይህ ከአማራ ህዝብ አብራክ የተገኙና በመላው አለም የሚገኙ ወገኖቻችን በሙሉ ፣ በህዝባቸው ላይ ለ7 አመታት ያለእረፍት የሚፈፀመውን ግፍና ሰቆቃ ለአለምአቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ በየጊዜው ሊያከናውኑት የሚገባውና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት የትግላችን አንዱ ፈርጅ መሆኑ ሊሠመርበት ይገባል! ……… … https://x.com/i/status/1992873321801605627
Alarm Bells Go Off on Ethiopia
Concerned Governments Should Act to Prevent Further Abuses
The fragile truce largely insulating civilians in northern Ethiopia from war crimes and other abuses may be unraveling. With many countries focused elsewhere, it is increasingly important that influential governments mobilize swiftly to prevent a resurgence of atrocities in the northern Tigray region that could spread further.
In recent weeks, Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed accused the Tigray region’s ruling party, the Tigray People’s Liberation Front (TPLF), of using its budget for military activities. The Ethiopian army chief called the party a “criminal clique” that needs to be eliminated. Tensions have risen since Ethiopian authorities and the TPLF repeatedly appealed—without success—for international mediation.
There have also been mounting tensions between Ethiopia and neighboring Eritrea, which Ethiopia’s foreign minister alleged was colluding with the TPLF to wage war. For months, diplomats and analysts have been warning that provocations between the two countries could lead to renewed conflict in areas that have not had a chance to recover from previous fighting.
The 2020-2022 conflict in northern Ethiopia, which spread from Tigray to the Afar and Amhara regions, was marked by serious atrocities, claimed the lives of several hundred