Home › View all posts by Meheret Setegn
Blog Archives
“አቡነ ፋኑኤል የጎረጎሩት ዓሣ ዘንዶ ሆኖ ወጣ!” በሚል ርዕስ ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ያቀርቡልን ጽሁፍ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንና በአጠቃላይ በአገሪቱ ላይ የተከፈተው የማፍረስና የማጥፋት ዘመቻ እጅግ እየተጧጧፈ በሚካሄድበት ወቅት ላይ ነው። በዚህም መሠረት የጥፋት ወጭቱ ውስጥ እጃቸውን ከከተቱት መካካል በዋናነት ዘንዘሪጡ ዳንኤል ክብረት፣ አባ ሰረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል፣ አቡነ ማትያስና አቡነ ፋኑኤል ይገኙበታል።
ከዚህ በታች የሰፈረችውን ጦማር የወቅቱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማንያን፣ ገዳማት፣ የቆሎ ት/ቤቶች፣ካህናትና አገራችን ኢትዮጵያ ላይ እየተደረገ ያለውን የጥፋት ዘመቻ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ባለፈው ሳምንት በዘረኝነትና ፖለቲካ ያበዱት አቡነ ማቲያስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሆነው በታላቁ ወንበር ላይ የተቀመጡ ቢሆንም “ድመት መንኩሳ ዐመሏን አትረሳ” ነውና ቤተ ክርስቲያኒቷን አውግዞ ላፈነገጠ በዘረኞችና ፖለቲከኞች የተፈጠረውን “መንበረ ሰላማ” መርቀው ከፍተዋል። ከዚህ መረዳት የሚቻለው አብይ አህመድና አቡነ ማቲያስ ሁለት አዲስ አገሮችን ማለትም ትግራይና ኦሮሚያን በማዋለድ ሂደት ውስጥ መሆናቸውንና ለዚህ እንቅፋት ይፈጥርብናል ያሉትን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን እየገነጣጠሉ መሆናቸውን ነው። በቅርቡም ብርሃኑ ጁላ ህወሃቶችን “በሰላም መገንጠል ትችላላችሁ እናሰናብታችኋለን” ብሎ የተናገረውን ማስታወስ ያስፈልጋል። ጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። አቡነ ፋኑኤል የጎረጎሩት ዓሣ ዘንዶ ሆኖ ወጣ!
ፍልሰታ “እኛም ማየት አለብን” በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ
በየዓመቱ ከነሀሴ 1 እስከ 15 ድረስ የምትጾመው ፍልሰታን በዘልማድ ነው የምንጾማት ወይንስ ሚስጢሩን ተረድተነውና አውቀነው ነው ሲሉ ቀሲስ አስተርአየ ይጠይቃሉ። “የፍልሰታ ጾም ትንሿ የጤፍ እንደ ጤፏ ቅንጣት እየወደቅን እየተነሳን አድገን፥ እኛነታችንን ለሚቀጥለው ዘሮቻችን ለማቀበል በዚህ ምድር ላይ መዘራታችንን የምንመረምርበትየጥሞና ወቅታችን ናት። መንፈሳችን ከሥጋዊ ስሜትና ፍላጎት ርቆ ያጣነውን ፈልጎ ለማግኘት የሚሰማራበት ወቅት ናት”። ቀሲስ አስተርአየ በጽሁፋቸው አፅንዖት በመስጠት በብሔራዊና በመንፈሳዊ ስሜታቸው የተመኙትን አይተው ያለፉ ኢትዮጵያዊያን አርበኛ በላይ ዘለቀ፣ አቡነ ቴዎፍሎስንና ጋሼ አበራ በቀለን ከፍልሰታ ጾም መንፈስ ጋር ያላቸውን መስተጋብር በዝርዝር አስረድተዋል።
በተለይ ምዕመናንና ቤተ ክርስቲያንን በአውሬ አላስበላም ብለው እራሳቸውን መስዋዕት ስላደረጉላት አቡነ ቴዎፍሎስ ስናነሳ በአሁን ጊዜ ፓትርያርኩ፣ ሲኖዶሱና ጳጳሳቱ በጎሰኝነት፣ በፖለቲካ፣ በስልጣን፣ በገንዘብ፣ በዝሙትና በተለያዩ ህጸጾች የተጨማለቁ መሆናቸውን ስንመለከት ምንኛ ያንገበግባል። ቤተክርስቲያኒቷና በአጠቃላይም አገሪቷ የወረዱበትን አዘቅትና መከራ እንዲሁም በአማራነታቸውና በተዋህዶ ዕምነት ተከታይነታቸው ብቻ በየዕለቱ ስለሚጨፈጨፉትና ሞታቸው ከዝንብ ሞት እኩል ስለተቆጠረባቸው ምዕመናን ስናጤን ጊዜው የምፅዓት ነው ወይ ያሰኛል። በሐዋርያት ስራ 20፡28 በግልፅና በማያሻማ ሁኔታ እንደተጻፈልን “በገዛ ገንዘቡ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከሄድኩ በኋላ ለመንጋው የማራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሱ እኔ አውቃለሁ” የሚለው የእግዚአብሔር ቃል በአሁን ጊዜ እንደተፈጸመብን አያጠራጥርም። በአቡነ ማቲያስ የሚመራው ሲኖዶስና
ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ለበርካታ ዘመናት በቤተክርስቲያን ላይ በአንዳንድ ካህናት፣ መነኮሳት፣ ጳጳሳት የሚፈጸሙ ወንጀሎችን እግር በእግር በማጋለጥና መወሰድ ስለሚገቡ እርምቶች የምድረ በዳ ጩኸት ሲያሰሙ ኖረዋል። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከውጭ የሚመጡባትን ወረራዎችንና ጥቃቶች እየመከተች በማሸነፍ ሉዓላዊነቷንና ክብሯን ጠብቃ ከሁለት ሽህ ዓመታት በላይ ቆይታለች። ሆኖም ከውስጥ ሆነው ዝሙት በመፈጸም፣ ሴቶችን በመድፈር እንዲሁም ጸያፍና አስነዋሪ ድርጊቶችን በማድረግ ህዝብ እንዲሸሻትና እንዲጠላት የሚያደርጓት ካህናት እጅግ ከፈተኛ ፈተና ሆነውባታል። ይህ ጉዳይ በግላዥጭ አደባባይ አይውጣ እንጅ ምዕመናን በየቤታደው የሚምከነከኑበትና የሚያዝኑበት ከሆነ ውሎ አድሯል። እንዲንከባከቧቸውና እንዲጠብቋቸው አደራ የተሰጣቸውን የምዕመናን አደራቸውን በልተውና ዕምነታቸው አጉድለው ዝሙት በመፈጸም ቤተክርስቲያንን እያደሙና እየገዘገዙ ያሉ ካህናትና መነኮሳት ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ከዛሬ 11 ዓመታት በፊት አሌክሳንደሪያ ቨርጂኒያ ውስጥ በመትገኘው ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዝሙት መፈጸሙ በማስረጃ የተረጋገጠበትን ታደሰ ሲሳይ የተባለ ግለሰብ ተወግዞ ስልጣነ ክህነቱ እንዲዘረዝ ማድረጋቸው ይታወሳል። ሆኖም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ፋኑኤል ከታደሰ ሲሳይ ጋር በመመሳጠር የተላለፈው ውግዘት እንዳይጸናና ግለሰቡም በዝሙት ተጨማልቆ ቤተክርስቲያንን ማርከሱንና ማቆሸሹን እንዲቀጥልነት አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በአሁኑ ጊዜ የሲኖዶስ አባል የሆነው “አቡነ” ኤውስጣጢዎስ የተባለው ግለሰብ ዋሽንግተን ሲያትል ውስጥ በሚገኘው Orthodox Church in America መንፈሳዊ ኮሌጅ ውስጥ ከዛሬ 12 ዓመታት በፊት ከሁለት ሴቶች ጋር ዝሙት መፈጸሙ በማስረጃ ተረጋግጦበት ከኮሌጅ መባረሩ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ቀሲስ አስተርአየ የግለሰቡን በዝሙት ምክንያት ከኮሌጅ መባረር አስተመልክቶ የተጻፈው ደብዳቤ ከኮሌጁ ተልኮላቸው ስለነበር ግለሰቡ ከክህነት አገልግሎት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ኩለንታዊት ቀዳማዊት ደኀራዊት፡ ዘመናዊት ናት ስትባል እም ኀበ አልቦ አይደለም፡፡ በብዙ እሴቶቿ ነው፡፡ ኩለንታዊት ከምታደርጋት ከብዙ እሴቶቿ መካከል የጽሑፌ መነሻ የሆኑት ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋራ የተሳሰሩት የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ ስንበቴ በቀጥታ ከእግዚአብሔር የታዘዘች ናት፡፡ የጽዋ ማኅበርም እንደ ሰንበቴው ቀጥታ ከግዚአብሔር ባይሆንም፡ በዮቶር በኩል ለሙሴ የደረሰው የግዚአብሔር ምሪት ናት፡፡ የጽዋ ማሕበርና ሰንበቴ የትርጉማቸው መነሻ፡ መድረሻና የመጨረሻ ዋና ዓላማቸው ሰባዊ ክብርና ነጻነት ነው፡፡
ኢትዮጵያ የተፈታተኗትን ሁሉ ቅኝ ገዥወች ከተከላከለችባቸው ከተዋጋችባቸውና ነጽነቷን ካስከበረችባቸው ዋናወቹ እሴቶቿ ውስጥ የጽዋ ማሕበራትና ሰንበቴወች ናቸው፡፡ በቅኝ ገዥወች ሲቀጠቀጡ ከኖሩት ካጎራባች አገሮች ልዩና የነጻነት ምሳሌ ያደርጓትም የጽዋ ማህበርና ሰንበቴ ናቸው፡፡ የጽዋ ማኅበራትና የሰንበቴ ድርጅቶች እንዴት ተመሰረቱ? ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሙ? ትሩፋታቸው ምንድነው? የደርግንና የወያኔን ዘመናት እንዴት ተሻገሩ? በብልጽግና ዘመንስ እንዴት ናቸው? እንዴት ይቀጥሉ ? የሚሉትን ጥያቄወች ለመመለስ ከጽዋ ማኅበር እንጀምር፡፡ ሙሉውን ጽሁፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. ያንብቡ።
የጽዋዕ ማህበራት በቀሲስ አስተርአየ ጽጌDownload
ዘንድሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስታና የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት አካላት በተለይም አማሮችና ተጋሩወች በመልካሙ ዘመን እንደሚያደርጉት ግብረ ሕማማት የሚባለውን መጽሐፍ ዘርግተው ለማንበብ ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ የሚያስፈልጋቸው አይደለም፡፡ ራሳቸው ግብረ ሕመም የሚባለውን መጽሐፍ ሆነዋል፡፡ ምድራቸውም ግብረ ሕማማቱ የሚነበበት ወደ ቤተ ክርስቲያንነት ተቀይሯል፡፡ እንዴት? የሚል ጥያቄ መከተሉ ስለማይቀር ተባብረን ለመመለስ የግብረ ሕማማቱን ሐተታ አብረን እንቃኘው፡፡ ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ።
ግብረ ሕማማትDownload
አባ ሠረቀ ከእግረኛው ጋራ ያደረጉትን ንግግር አዩት? ሰሙት? ብየ ቀሲስ አስተራየን ጠየኳቸው፡፡ “አዎ ሰማሁት” አሉኝ፡፡ ምን ተሰማዎት? ብየ ጠየኳቸው፡፡ በግረኛውና በአባ ሠረቀ መካከል የተካሄደው ንግግር “በሲኖዶሱ ጸሐፊ በአቡነ ጴጥሮስ እጅ የነበረው ስልጣን በአባ ሠረቀ እጅ ቢሆን ለወደዱት ትልቅ ጥቅም በጠሉት ላይ ትልቅ ጉዳት ያደርሱበት እንደነበርና አባ ሠረቀ ለአመኑለት ነገር እስከ ሞት ለመሄድ የወሰኑ መሆኑን ተረዳሁ። በአማራው ጎን ያሉት ጳጳሳት ለራሳቸው ጥቅምና ክብር ከመቆም በቀር ለምንም የምይጠቅሙ ደካሞች መሆናቸውን በዚህ ንግግር አየሁ። ዳዊት “ጽዋ በግዚአብሔር እጅ ነውና። ያልተቀላቀለ የወይን ጠጅ ሞላበት። ከዚህም ወደ ዚያ አገላበጠው። ነገር ግን አተላው አልፈሰሰም። የምድር ኅጢአተኞች ሁሉ ይጠጡታል (መዝ 74፡7_10) እንዳለው አባ ሠረቀ የጀመሩትን የኃጢአት ጽዋ ራሳቸውን ከነአተላው እግዚአብሔር ሲግታችሁ ተመለከትኩ” አሉኝ።
ቀሲስን እንድጠይቃቸው ያደረገኝ ከአመታት በፊት ምክር አዘል ደብዳቤ ለአባ ሠረቀ ጽፈውላቸው የነበረውን አንብቤ ስለነበር ነው። “ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይለቅም” እንደሚባለው አባ ሠረቀ በዲያብሎስ የተሰረሩ እርጉም ስለሆኑና ፖለቲካው ደማቸው ውስጥ ስለሚናኝ የሚሰሙና የሚታረሙ አይደሉም። አንድኛውን ከደፈሩ አይቀር ጭምብላቸውን አውልቀው ጥለው የትህነግ ታጋይ መሆናቸው ቢያውጁ ይሻላቸዋል። የትህነግ ታጋይና ቀንደኛ ካድሬ እንደነበሩ በጦርነትም ውስጥ ከፍተኛ ተሳትፎ እንዳላቸው ይታወቃል። እሳቸውስ አንዱ ይዘውታል “የዘሬን ብረሳ ይዘርዝረኝ” ብለዋል። እኔ የሚገርመኝ ከአማራው ወገን ያሉት ጳጳሳትና ቆሞሳት ይህ ሁሉ መርዝ በአባ ሠረቀ ሲረጭ የትግራዩ “መንበረ አሳማ” የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ቀለብ እየሰፈረች ሆዳቸው በምትሞላላቸው ቤተ ክርስቲያን ላይ ወንጀል ሲሰራባትና ስትቦረቦር እየተመለከቱ እጃቸውን አጣጥፈው መቀመጣቸው
የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማኅበር በሰሜን አሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የአሌክሳንደሪያ ቨርጂኒያ ከተማ ምክር ቤት የአድዋ ድል በዓልን አስመልክቶ አዋጅ እንዲያውጅ አስደርጓል። የአሌክሳንደሪያ ከተማ ምክር ቤት በከንቲባዋ ወ/ሮ አሊያ ጋስኪን ፊርማ ባወጣው አዋጅ 129ኛውን የአድዋ ድል አስመልክቶ ለኢትዮጵያዊያን “የእንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት አስተላልፏል። ከዚህም በተጨማሪ የአድዋ ድል የሚከበርበትን የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም. (ማርች 2 ቀን 2025) የአድዋ ድል በዓል ቀን ሆኖ እንዲታሰብ አዋጅ አውጇል። በአዋጁ ላይ የአድዋ ድል ለኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝብም ድል መሆኑንና በቅኝ ግዛት ተይዘው ለነበሩ በመላው ዓለም ለሚገኙ ህዝቦችም ለነጻነታቸው እንዲታገሉ መልካም ምሳሌና ማበረታቻ እንደሆናቸው ተመልክቷል። በአሌክሳንደሪያ ከተማ ውስጥ በርካታ ኢትዮጵያዊያን እንደሚኖሩ የሚታወቅ ሲሆን የወጣው አዋጅ ኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያን በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊያው፣ ባህላዊ መስኮች ያበረከቱትን ገንቢ አስተዋጽኦ ዕውቅና ሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማኅበር በሰሜን አሜሪካ የዘንድሮውን የአድዋ ድል በዓል ከአቡጊዳ የቋንቋና ባሕል ተቋም ጋር በትብብር ቅዳሜ፣ ማርች 1 ቀን 2025 እንደሚያከብር አስታውቋል። ዝርዝር መረጃዎችን ለማግኘት የኢትዮጵያ ውርስና ቅርስ ማኅበር በሰሜን አሜሪካ ድረ ገጽ ጎብኙ። www.ehsna.org
ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ስለ አቡነ ማትያስ መተኛትና ማንቀላፋት በተከታታይ አውስተው እንቀስቅሳቸው እንጎትጉታቸው በሚል ያቀረቡትን ዝርዝር ትንታኔ በቱምቢ መገናኛ አደመጥኩት፡፡ ሰውም እየተቀባበለ በሰፊው በመደመጥ ላይ ነው፡፡
ቀሲስ አስተርአየ ከዚህ ቀደም የጻፏቸውን እንደኔ ያነበባችሁ፡ የተናገሯቸውን እንደኔ ያዳመጣችሁ ስንት እንደሆናችሁ አላውቅም፡፡ ከደረግ ዘመን ጀምሮ ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናቸው ይጽፉትና ይናገሩት የነደነበረው ሁሉ በዘመኑ በነበሩት መገናኛ ድረ ገጾች በሰፊው እየቀረቡ ይነበቡና ይሰሙ እንደነበር አውቃለሁ፡፡ እስካሁን ድረስ የሚጽፏቸውና የሚናገሯቸው እርስበርስ ሳይጋጩ ወጥ ሆነው ሲቀጥሉ እየተመለከትኩና እየታዘብኩ ነኝ፡፡ በዚህ አቋማቸው በዘመናችን ካሉት መንፈሳዊያን ሰወች ሰባኪወች ጸሐፊወችና ተናጋሪወች ቀሲስን የተለዩ አድርጓቸውል፡፡
ቀሲስ አስተርአየ ሰሞኑን በቱምቢ መገናኛ እየቀረቡ የተናገሩት፡ ከ 12 አመት በፊት በ2005 በየካቲት ወር “ምቱር ፓትርያርክ” በሚል ርእስ ላቀረቡት ጽሑፍ መደምደሚያ መስሎ ስለተሰማኝ ከ archive ውስጥ መዝዠ ለማቅረብ ሳስብ ራሳቸው ደጋግመው የተጠቀሟትን ውጥንቅጥ የምትለውን ቃል መግቢያ እንዳደርጋት አስገደደኝ፡፡
ቀሲስ “የተኙትን ፓትርያርክ እንቀስቅሳቸው” ያሉትን ሲያብራሩ “በኔ በኩል ከመቀስቀስም አልፌ ጎትጉቻለሁ” ያሉትን መነሻ በማድረግ ዲያቆን ዮሴፍ “ፓትርያርኩ ተቀስቅሰውም ተጎትጉተውም ካልነቁ ቀጣዩ ምን ይሁን? ብሎ ላቀረበላቸው ጥያቄ በይቆየን አንተርሰውታል፡፡ ዛሬም የሚናገሩት ከዚህ ቀደም “ ምቱር ፓትርያርክ” በሚል ርእስ ላቀረቡት ጽሑፍ መደምደሚያ ስለመሰለኝ ውጥንቅጥ ብለው የተናገሯት ቃል ጎልታ ታየችኝ፡፡ ቀሲስ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሥራተ ትምህርትና አስተዳደግ ሲገልጹ ውጥንቅጥ የምትለውን ቃል ደጋግመው መጥቀሳቸውን ያነበበ የሚዘነጋ አይመሰኝም፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሥራተ ትምህርትና አስተዳደግ ሲገልጹ