Blog Archives

የሕወሓቱ ጄኔራል ሳሞራ የኑስ በሕወሓቱ ጄኔራል ሠአረ መኮንን ተተኩ

በጠቅላይ ሚንስትር አብይ አሕመድ የታጩት የሕወሓት ጄነራል ሰዓረ መኮንን ዛሬ ከኢሕአዴግ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ ሹመታቸውን ተቀብለዋል። በመሆኑም የሕወሓቱን ጀነራል ሳሞራ የኑስን ተክተው የመከላከያ ሰራዊትን በጠቅላይ ኤታማዦር ሹምነት ይመራሉ። መተካካቱ ይቀጥላል ። #MinilikSalsawi
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሳሞራ የኑስ ማነው?

በብዙ ሞቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን ኢትዮጵያውያንን ደም ያፈሰሰው ቫምፓየር ጄነራል ሳሞራ የኑስ ከስልጣን መነሳቱ ቢነገርም ውሳኔው ገና ይፋ አልሆነም። ማን እንደተካውም አልተገለጸም። ይህ እጁ በኢትዮጵያውያን ደም የተጨማለቀው እርኩስ ግለሰብ ማነው? ይህን ቪዲዮ ይመልከቱ። VIDEO 1 VIDEO 2
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኮማንድ ፖስቱ ለጠቅላይ ሚኒስተሩና ለፖለቲካው አመራር ሪፖርት አላቀርብም ማለቱ ተሰማ።

  ኮማንድ ፖስቱ ለጠቅላይ ሚኒስተሩና ለፖለቲካው አመራር ሪፖርት አላቀርብም ማለቱ ተሰማ።   በፓርላማ ውድቅ የተደረገው ነገር ግን ህወሃት በጉልበት ያጸደቀው የአስቸኳ ጊዜ አዋጅ ከተደነገገበት የካቲት 9/2010 ዓ.ም ጀምሮ አገራችን ሙሉ በሙሉ በወታደራዊ አገዛዝ ስር ወድቃ እየማቀቀች እንደሚገኝ ይታወቃል። በመሆኑም ይህን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በበላይነት የሚያስፈጽሙትና የሚቆጣጠሩት ጠቅላይ ሚኒስተሩ፣የመረጃና ደህንነት መስሪያ ቤቱ፣ የመከላከያ ሚኒስተሩ፣ የመከላከያ ኢታማዦር ሹም እንዲሁም የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽነር ናቸው። በዚህም መሰረት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተገኙ ውጤቶች፣ የጠፉ ጥፋቶች፣በአጠቃላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፈጻጸም እንዲገመገሙ በየቀጠናው የተሰበሰቡ መረጃዎች ተጠቃለው ለጠቅላይ ሚኒስተሩ ዝርዝር ሪፖርት እንዲደረግ ያዛል። ይሁን እንጂ ኮማንድ ፖስቱን በበላይነት የሚቆጣጠሩት የመከላከያ ሰራዊቱ አዛዦች የሆኑት የህወሃት ወታደራዊ አዛዦች ስለ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ዝርዝር መረጃ እንዲሁም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ምክንያት በመላ አገሪቱ ስለታሰሩት ዜጎች ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስተር ለዶ/ር አቢይ አህመድ እንዲሁም ለፖለቲካው አመራር ሪፖርት አናደርግም ማለታቸውን የመረጃ ምንጮቻችን ጠቁመዋል። የመረጃ ምንጮቻችን አክለው የህወሃት ሰዎች ለዶክተር አቢይ ሪፖርት ብናቀርብ ነገሮችን ያበላሽብናል ብለው መስጋታቸውን አብራርተዋል። በተለይ ጄነራል ሳሞራ የኑስ <<ትላንት ለእኔ በተጠንቀቅ ሰላምታ ይሰጠኝ ለነበረ ለአንድ ተራ ወታደር ዛሬ ገና ለገና ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ ብየ ሪፖርት አላቀርብም >> ሲል መናገሩ ተከትሎ ሁኔታው ዶ/ር አቢይ አህመድ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፈጻጸም ያበላሽብናል ከሚል የመነጨ ብቻ ሳይሆን ከነሳሞራ አንሸነፍም ባይነት እንዲሁም የመታብይና የበታችነት ስሜት የተቀዳ መሆኑን መረጃዎች አመላክተዋል። በዚህም ምክንያት በእነሳሞራ በአጠቃላይ በህወሃት ሰዎች ጥርስ ውስጥ
Tagged with: , , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News