Blog Archives

የቤተ መንግስቱ ሚስጢር! “አማራ ከእንግዲህ ኢትዮጵያን አይመራም። Not in a million years!” አብይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምሬትና ቁጣ በገነፈለ ህዝባዊ ማዕበል እየተገፉ የስልጣን ኮርቻ ከተፈናጠጡ አምስት አመታት ተቆጠሩ። ነጻነት፣ ፍትትህና እኩልነት በማወጅ ስልጣን የጨበጡት አብይ አህመድ ከቃላት የዘለለ ፋይዳ ያለው ለውጥ ሳያመጡ ኢትዮጵያ በጦርነት፣ እልቂት፣ በጅምላ መፈናቀልና ግድያ ሳቢያ በደም ጎርፍ ታጥባለች፣ በዋታና ለቅሶ ተናውጣላች። በእነዚህ ጥቂት አመታት ውስጥ ከብልጽግና ይልቅ ከፍተኛ ውድመትና ጥፋት ደርሷል። አሁን ደግሞ በአማራ ህዝብ ላይ ጦርነት ታውጆ እልቂቱና ውድመቱ፣ የጅምላ እስርና ድቀቱ ሞትና መፈናቀሉ ተባብሶ ቀጥሏል። ከዚህ ሁሉ ጀርባ ያለው እሳቤና ድብቅ አጀንዳ ምንድ ነው? ጋዘጤኛ አበበ ገላው የገጠመውን አስደንጋጭ ክስተት ተንተርሶ አይን ገላጭ የሆን ሚስጥር ያካፍለናል። ይህን ልዩ ዝግጅት እስከመጨረሻው ተከታተሉ። ብዙ ከዚህ በፊት ያለተሰሙ በርካታ ቁም ነገሮችን ታገኙበታለችሁ። የቤተመንግስቱ ሚስጥር!?
Posted in Amharic News, Video

ምጥ ማቅ ልደት ትንሣኤ

ተሰጠ ከተወልደ መድኅን ዘብሔረ አግዓዚ ግንቦት ፳፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም የሚያነብ ይረዳው፡ የተረዳው ያስረዳ። ይህ መጽሐፍ ሸቀጥ አይደለም። አቅሙ ኖሮት አባዝቶ በነጻ ሊያከፋፍለው የሚሻ ቢኖር ይህ ነጻ ነው ብሎ አትሞበት አባዝቶ በነጻ እንዲያሰራጨው ፍቃድ አለው። የሚያሳትመውም የዚህ መጽሐፍ ባለቤት አይደለም፡ ቃላቱም መልእክቶቹም የእሱ አይደሉም፤ እኔ መጭውን ለሕዝብ እንድገልጥ እንዲሁ እሱ ደግሞ እንዲያስተላልፍ ትእዛዝ ፈጻሚ እንጂ። በዚህ መልእክት የጌታ መንግሥት ይክበርበት። ኢትዮጵያም ትዳንበት። ነገሩ እንዲህ ነው፡- ሙሉ ጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ
Posted in Articles

በአዲስ አበባ እና በደብረ ኤሊያስ የተፈፀሙትን ጥቃቶች በጥብቅ እናወግዛለን – የአማራ ሕዝባዊ ግንባር

(ግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም.) በአማራ ጥላቻ እና ጥቃት ላይ የበቀለው ዘረኛው ስርዓት ፣ በአማራው ሕዝብ ላይ ላለፉት 30 ዓመታት ሲያደርሰው የኖረው ሁለንተናዊ ጥቃት ወደለየለት የዘር ጭፍጨፋ እና የኃይማኖት ተቋማት ጥቃት ተሸጋግሯል። ለዚህ በወለጋ ካለው ሁኔታ በተጨማሪ፣ ግንቦት 18 እና 19 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሙስሊም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ፣ በደብረ ኤሊያስ (ጎጃም) ደግሞ፣ በስላሴ እና በተክለ ኃይማኖት ገዳማት ላይ በከባድ የጦር መሣሪያዎች የተፈፀሙት “መንግስታዊ” ጥቃቶች ዓይነተኛ ማሳያዎች ናቸው። ግንቦት 18 እና 19 2015 ዓ.ም በሁለት አቅጣጫ ወደ ደብረ ኤሊያስ የገባው የመከላኪያ ኃይል፣ “ለፋኖ እርዳታ ታደርጋላችሁ” በሚል መነሻ፣ ላለፉት ወራት በ”መንግስት” ታጣቂዎች ተከቦ በቆየው የስላሴ አንድነት ገዳም ላይ የከባድ መሣሪያ ተኩስ በመክፈት የጦር ወንጀል ፈፅሟል። በዚህም መሠረት፣ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጭምር ይህንን ጉዳይ በአንክሮ እንዲመለከተው እንጠይቃለን። እንዲሁም፣ በዛሬው ዕለት “ፋኖን ይደግፋል” ወደ ተባለው ተክለኃይማኖት ገዳምም ወታደራዊ ኃይል በማስገባት እና መንገድ በመዝጋት መንግሥት ተብዬው ወረራ ፈፅሟል። ይህ መግለጫ እስከወጣበት ግዜ ድረስ፣ የደረሰው ጉዳት በትክክል አልታወቀም። ይህን ፈርጀ ብዙ የህልውና ጥቃት ተቀምጠን የምናመልጠው፣ ከሌሎች በመጠበቅ የምናስቀረው፣ በአጥቂዎቻችን በጎ ፈቃድ የሚቆም አይደለም። ዛሬ በአማራ፣ በወለጋ፣ በአዲስ አበባ እና በሌሎችም አካባቢዎች የሚካሄዱት የዘር እና የኃይማኖት ጥቃቶች፣ ኢትዮጵያን እንደ ሀገር የማጥፋት ግብ የሰነቁ ናቸው። ስለሆነም፣ ይህንን ጥፋት መመከት የዘር ጥቃት እየተፈፀመበት የሚገኘው የአማራ ግዴታ ብቻ ሳይሆን፣ ኃይማኖታቸውን እና ሀገራቸውን የሚወዱ የመላ ኢትዮጰያዊያንም ግዴታ ጭምር ነው። ይህንን
Posted in Amharic News

ፖሊሶች ሳላስበው እጆቼን ከያዙ በኋላ በምላጭ ያንገቴን ማህተብ በጠሱት – ናትናኤል ያለምዘውድ

ከታሰርኩባቸው እስሮች ትንሹ የሚባለው ይሄኛው እስር ቢሆንም ከፍተኛ ግፍና ማስጠንቀቂያ ያዘለ እስር ነው፡፡ ዝርዝሩን በሰፊው እመለስበታለሁ። ከመጀመሪያ ጀምሮ ማህተቤን እንድበጥስ ግፊት ቢደረግብኝም ያንን ማደረግ እንደማልችል እና ለእኔ ሞት እንደሆነ ነግሬ አልበጥስም አልኩ:: ከአንድ ቀን ጭቅጭቅ በኋላ አራት ፖሊሶች ብቻዬን በማስጠራት ሳላስበው እጆቼን ከያዙ በኋላ በምላጭ ያንገቴን ማህተብ በጠሱት:: እቅም የማጣት ስሜት ተሰማኝ:: እንዲደበድቡኝ ተሳደብኩ፡፡ እነሱ ከዱላ በላይ የሆነ ነገር እንዳደረሱብኝ ስለገባቸው ዝም አሉኝ። መብላት መጠጣት አቃተኝ፡፡ በአይሲስ ሊቢያ ውስጥ ማህተባችንን አልበጥስም ብለው የተሰው ወንድሞቼ አይነት አቅም እንደሌለኝ ሲሰማኝ ልቤ ክፉኛ ተሰበረ፡፡ ኡፍፍ ይህን ክፉ ቀን መቼም አልረሳውም፡፡ ይህ እንዲህ እንዳለ፣ ሁሌም ከግፉዓን ጎን የሚቆመው ወንድማችን ጠበቃ ቤተማርያም አለማየሁ በዚህ ፈተና ወቅት ሙያዊ ግዴታው እንዳለ ሆኖ እንደወትሮ አሁንም፣ ስለፍትህ፣ ስለ እውነት በማለት ከእኔ ከተበዳይ ጎን በመቆምህ ወንድሜ ቤተማርያም እግዚአብሔር እድሜና ጤና ይስጥህ፣ አመሰግናለሁ። ሁሌም ቢሆን የግፉዓን ዓይንና ጆሮ በመሆን የተበዳዬች ድምጽ የምታሰሙ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች ክብር ለእናንተ ይሁን፡፡ ብቻ ፈተውኛል፡፡ ለሁላቹም እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡
Posted in Ethiopian News

የአሜሪካን ኢትዮጵያዉያን ሕዝብ ጉዳይ ኮሚቴ (ኤፓክ) መግለጫ

Posted in Amharic News

ፈራሁ አሁንስ ፈራሁ – ብርሃነ መዋ

ብርሃነ መዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ማቅ ለበሰች፣ ጩኸት ጮኸች። አባቶችን ከመካከላቸው ጭምብላቸውን የገፈፉ የፖለቲካ ካባ የለበሱ አተራመሱአቸው። አስደነገጡአቸው። አስለቀሱአቸው። ቀኖናው ተጣሰ። በህግ አምላክ እያለች ህግ ራቃት። በሰሜኑ ጦርንት ተጨፋጭፈን። እፎይ ስንል በወለጋ ዘር እየለየን መጨፍጨፉ፣ መታረዱ፣ መሰደዱ የተነጣጠረበት ምስኪን አማራ በኦሮሞ በትግሬ በጉራጌ በደቡቡ በሁሉም ብሄር ዜጋ ወንድሞቹ ታጅቦ ሃይማኖቱንና እምነቱን ሲነኩበት በፖለቲካ ሲለውሱበት፣ ተስፋው ሁሉ ይጨልማል ህይወቱ ባዶ ይሆናል። የመንግስት ጥበቃን ሲያጣ በተስፋ የሚጸልይበት መንበር ቤተ-እምንቱ ብቻ ነበር። የሰይጣን ጆሮ ሰማና የማይነካ ነገር ነካ። ኦርቶዶክስን ነቀነቃት። ቤተክርስቲያን አነባች፣ ተጣራች። ለኢትዮጵያ መኩሪያ ከመሆንዋ አንጻር ከጎንዋ ለመቆም የለበሰችውን ጥቁር ለመልበስ፣ ለእውነት ለመቆም ኦርቶዶክስ መሆንን ብቻ አይጠይቅም። የምንም እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊነትን እንጅ። እናም ጥቁር ለበሰች፣ እኛም ጥቁር ለበስን። ኦርቶዶክስ በመሆኔ ጥቁር ለበስኩ። ቤተክርስቲያንና አማኝ ዜጎች ስለተናቁ ጥቁር ለበስኩ። የህግ የበላይነት ስላልተከበረ ጥቁር ለበስኩ። በዘር መከፋፈልን ስለምጸየፍ ጥቁር ለበስኩ። የፖለቲካ ሴራ መሆኑን በማመኔ ጥቁር ለበስኩ። ቀኖናውን ያፈረሱትን ትቶ የሲኖዶስ አባላትን ሲያዋክቡአቸው በማየቴ ጥቁር ለበስኩ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትናን አስፋፍታ፡ በስነምግባር አርቃ፡ ዘር ቋንቋ ሳትለይ አቀራርባና አፋቅራ፡ ታሪክ ጠብቃ አገር አስከብራ። ኢትዮጵያውያንን ሽርባና አጋምዳ ሁሉን አቅፋ ያንድነት ተምሳሌት ሆና ያለችውን የመጨረሻዋን ገመድ ሊቆርጡ ሲገዘግዙ ሳይ ፈራሁ በጣም ፈራሁ። ለሃግሬ ፈራሁ። ላንድነታችን ፈራሁ። ለዜጎች መብት ፈራሁ። ለዘረኝነት መስፋፋት ፈራሁ። በነጻነት መዘዋወር ስላለምኖሩ ሳስብ ፈራሁ። በጣም ፈራሁ። አምላክ ሆይ ህዝብህን ታደግ፡ ቤተ ክርስቲያንን አስከብር። መንግስት ሆይ
Posted in Ethiopian News

የወደቁትን አንሱ ልዩ ዝግጅት – ቪዲዮ

Posted in Amharic News

ዶፍ ዝናብ ላይ ያገኘናቸው ምስኪን አባት

Posted in Amharic News

“ባለቤቴ የልጃችንን ህመም ሲያውቅ ቤቱን ጥሎ ወጣ” – በልጃቸው ህመም እየተሰቃዩ ያሉ እናት ታሪክ

Posted in Amharic News

ሸፍጥ ከፕሪቶሪያ እስከ ፓርላመንት

ከአማራ ጀግኖች አደራ (አጀአ)፣ ዩኬ የተሰጠ መግለጫ PDF ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) በወታደራዊ ኃይል ወደ ስልጣን ለመመለስ ካለው ከፍተኛ ፍላጎት በመነሳት ወደ ስልጣን ለመመለስ ሲል በጥቅምት 24 የሰሜን እዝ ላይ ታሪክ ይቅር የማይለዉ ኢ-ሰበዓዊ ግድያ እና እንግልት ማድረሱ የአጭር ጊዜ ትዉስታ ነዉ። ይህንን ወረራም ለመፈፀም በቅራቅር ቆርጦ ወደ ጎንደርና ባህርዳር ለማለፍ የተሰማራውን የሕወሓት ኃይል በጀግንነት በመቀልበስ ቀዳሚ ሚና የነበረዉ የአማራ ሕዝብ፤ የአማራ ልዩ ኃይል፤ ፋኖ እና ሚሊሻ መሆኑ ይታወቃል። የብልፅግና መንግስትም በሜዲያ እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ብልፅግናን በስልጣኑ እንዲቆይ ያደረጉትን የአማራ ጥምር ኃይሎች በግልፅ አመስግኗል። ነገር ግን ወረራዉ ከተቀለበሰ በኋላ በተንኮልና ሴራ ጥርሱን የነቀለዉ የኦሮሙማዉ መሪ አብይ አህመድ እነዚህን ኃይሎች ለመወንጀል የቀደመዉ አልነበረም። አሁንም የህወሃት ግብዓተ መሬት ሊፈፀም በተቃረበበት አስራ አንደኛዉ ሰዓት ላይ በድርድር ስም ህወሃትን የማዳንና አማራን ደግሞ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተባብሮ ለመበታተን እና ለማጥፋት በሂደት ላይ ይገኛል። የፕሪቶሪያና የናይሮቢ የኦነግና ህወሃት ስምምነቶች ተከትሎ የአማራ አፅመ ርስቶችን ወልቃይትና ራያን በተኩላው የብልፅግና መንግስት አማካኝነት ለህወሃት አሳልፎ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቱ እየተከናወነ እንደሆነ በተለያዩ መንገዶች መረዳት ይቻላል። ከሰሞኑ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት በሰጠዉ አጭር ማብራሪያ የአሜሪካ ከፍተኛ የሴኔት አባላት ለዓለም ጋዜጠኞች ሲያብራሩ በፕሪቶሪያዉ እና በናይሮቢዉ የድርድር ስምምነት መሰረት የአማራ ልዩ ኃይል፤ ፋኖ እና ሚሊሻ ከአማራ አፅመ ርስቶች ወልቃይትና ራያ መልቀቅ እንዳለባቸው የብልፅግና መንግስት ቃል እንደገባና እንዴውም ለማስፈፀም ዝግጅት መጀመሩንም ይገልፃሉ።
Posted in Amharic News

ሲሪላንካዎች ግን ሲያስቀኑ – መ/ር ዘመድኩን በቀለ

ፕሬዘዳንቱ ህዝቡ ላይ ተኩሱ ይላል። ልክ እንደ ብርሃኑ ጁላና አበባው ታደሰ የመሰሉ የወታደሩን ሹመኞች። ወታደሩ ግን የህዝብ ማዕበሉን ካየ በኋላ፦ አላደርገውም። ህዝብ ላይማ አይተኮስም ይላል። ልብ በሉ ይሄ ሲሪላንካ ነው። ከእኛዎቹ ሰው በላ የአገዛዝ አሽከር ከሆኑት (የደርግ፣ ህወሓት፣ ኦህዴድ፣ ኦነግ እና ብአዴን ወታደሮች ጋር እያነፃፀራችሁ አትበሳጩ)። በሲሪላንካ ወታደሩ እንደ ኦሮሚያና እንደ ዐማራ፣ እንደ ትግሬም ልዩ ኃይል አይደለም። ወደ ገዛ ህዝቡ አይተኩስም። አያርድም፣ አይጨፈጭፍም። ወታደሩ ህዝቡ ማሸነፉን ሲያውቅ መሳሪያውን ጣለ። ዩኒፎርሙንም አወለቀ። ከዚያም ከህዝቡ እንደ አንዱ ሆነ። አለቀ። ብርሃኑ ጁላ፣ አበባው ታደሰ፣ ተመስገን ጥሩነህ፣ ደህና ናችሁ? በየሱስ በጌታ ስም ሲሪላንካዎች ግን ሲያስቀኑ! @merejatv ሲሪላንካዎች ግን ሲያስቀኑ #Sri ♬ original sound – Mereja TV
Posted in Amharic News

እንዴት አንድ ዶ/ር ደሳለኝ ብቻ በፓርላማ የወገኑ ጠበቃ ሆነ? – መ/ር ዘመድኩን በቀለ

በዛሬው የፓርላማ ውሎ ብቸኛው የተመዘገበው የተቃውሞ ድምፅ የዐብኑ ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ብቻ ነው። “…በፌስቡክ ላይ ዘራፍ የሚለው ወንድማችን ክርስቲያን ታደለ ለምን ጮጋ አለ…? አልገባኝም። ማብራሪያ ባገኝ ደስስ ይለኛል። ባለፈው ጊዜም እነ ዶክተር ደሳለኝ ፓርላማውን ረግጠው ሲወጡ “ሪፖርት ማቅረብ ስላለብኝ ነው ወንድሞቼን ተለይቼ የቀረሁት” ያለን እሱ ራሱ ነው። እና ዛሬስ ምን አግኝቶ፣ ምንስ ሆኖ ነው ያ የፌስቡክ ላይ አንበሳ የምወደው ክርስቲያን ለ5 ተጨፍጫፊ ዐማራ የ ደቂቃ የኅሊና ጸሎት የሰጠን፣ ታራጆቹን በስማቸው ዐማሮች ብሎ መጥራት ተፀይፎ ንፁሃን እያለ የሚያላግጥን የታገሰ ጫፎን ፓርላማ በስምምነት ደግፎ ጮጋ ያለው? …ስላልገባኝ ነው። ትናንት 14 ሺ ሰው በፌስቡክ እያየው ዋይ ዋይ ሲል ያመሸውና የአዲስ አበባ ልጅ “የሴተኛ አዳሪ”ና “የኮንዶም ትራፊ” ነው በሚለው ዝነኛ ስድቡ የምናውቀው የጭናቅሰኑ የሀረርጌው መራታ ሃንጋሳ ኢብራሂም ዛሬ በፓርላማ ምንም ሳይተነፍስ፣ በአብላጫ ድምጽ አጽድቆ መውጣቱስ ምንን ያመለክታል። የሃንጋሳ አይገርምም። ድሮም ከሃዲ ነው። የገዳይ ወገን ነው። ከብአዴንና ከዐብን እንዴት አንድ ዶር ደሳለኝ ብቻ የወገኑ ጠበቃ ሆነ? • በወለጋ ንፁሐን አልሞቱም • በወለጋ ዜጎች አልሞቱም • በወለጋ ኢትዮጵያውን አልተገደሉም • በወለጋ የተጨፈጨፉት ዐማሮች ናቸው። የዐማሮች ዘር ነው የጠፋው። አከተመ።
Posted in Amharic News

የባልደራስ አመራሮች በጦር ሜዳ የጀግንነት ሜዳሊያ ከተሸለሙት የቀድሞ ወታደር አሊ ያሲን ጋር አፈጠሩ

በዛሬው የጁመዓ ዕለት፣ የባልደራስ አመራሮች በጦር ሜዳ የጀግንነት ሜዳሊያ ከተሸለሙት የቀድሞ ወታደር አሊ ያሲን እና ቤተሰቦቻቸው ጋር አፍጥረዋል። አቶ አሊ ያሲን በደርግ ግዜ በጦር ሜዳ ለፈፀሙት ጀብድ ከኮለኔል መንግሥቱ እጅ ሜዳሊያ የተቀበሉ ሲሆን፣ በህወሓት ግዜ ደግሞ በሽብርተኝነት ተከሰው ለእስር የተዳረጉ ናቸው።በምርጫ 97ም የቅንጅት አባል ሆነው ጉልህ ነበራቸው። በአሁኑ ግዜ ላያቸው ላይ ልትፈርስ እያስፈራራች በምትገኝ አንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ ይኖራሉ። ታሪካቸው አስደማሚ ነው። በራሳቸው አንደበት ለባልደራስ አመራሮች ሲተርኩ በቪዲዮ ተቀርፀዋል። ነገ በአዲስ አበባ ሰዓት አቆጣጠር ከ10 ሰዓት ቦኃላ በዚህ ገፅ ይለቀቃል።
Posted in Ethiopian News

ተሾመ ምትኩ – ምነው ወዳጄ

Posted in Music

ታፕታፕ ሴንድ በኢትዮጵያ ስራ መጀመሩን አስታወቀ

ያለምንም ክፍያ የገንዘብ ዝውውር አገልግሎት የሚሰጠው እና በፍጥነት በማደግ ላይ ያለው ታፕታፕ ሴንድ በኢትዮጵያ አገልግሎቱን መጀመሩን አስታውቋል። ኢትዮጵያ በፋይናንሺያል ዘርፍ ግብይት የሚያደርጉ ጎልማሶችን በመቶኛ በመጨመር የፋይናንስ አካታችነትን ለማሻሻል ለብዙ አመታት ጠንክራ ሰርታለች። ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ትልቅ ለውጥ በማስመዝገብ በአህጉሪቱ ፈጣን ኢኮኖሚ እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት አንዷ ሆናለች። የድህነት ቅነሳ፣ የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እድገት እና የፋይናንስ አካታችነት መጨመር እንዲሁም የኢኮኖሚ ግስጋሴዎች ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀሱ ናቸው። ቀጣይነት ያለው እና በኃላፊነት የሚሰራ የፋይናንስ አካታችነት ለገንዘብ እና ለገንዘብ መረጋጋት አስተዋፅዖ ያደርጋል፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር አደጋን ለመዋጋትም ይረዳል፣ የተፋጠነ የኢኮኖሚ እድገትን፣ የላቀ ብልጽግናን እና ማህበራዊ ልማትንም ይደግፋል። የጥሬ ገንዘብ ማበረታቻ ከመደበኛው የፋይናንስ ሥርዓት ውጭ የገንዘብ መጠን እንዲሰራጭ አስችሏል። ይህ ገንዘብ ለወንጀል ድርጊቶች መስፋፋት፣ ለሙስና እና ለህገወጥ የገንዘብ ፍሰት በከፊል ተጠያቂ ነው። እነዚህን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ለመፍታት ታፕታፕ ሴንድ ጉልህ ሚና ለመጫወት እየሰራ ይገኛል። ሄለን አመልጋ US -Ethiopia, launcher at taptap send አዲስ የተጀመረውን የሞባይል ገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት በተለይ ከዲያስፖራ ወደ ሀገር ቤት የሚልኩ ሰዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ የመጀመሪያው መተግበሪያ እንደሆነ ገልጻለች። ታፕታፕ ሴንድ ከአውሮፓ እና ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የገንዘብ ልውውጥ ለማድረግ አገልግሎቱን በመጀመር የፋይናንሺያል አካታችነት ጥረቶችን ለማሳደግ ተዘጋጅቷል። እንደ ታፕታፕ ሴንድ ያሉ ህጋዊ የገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶችን መጠቀም መደበኛ ያልሆነውን ሴክተር አጠቃቀምን እና ወደ ኢትዮጵያ የሚገባውን ህገወጥ የገንዘብ ፍሰት ይቀንሳል። የኢትዮጵያ
Posted in Ethiopian News

በሃብት የተትረፈረፈው የአማራ ክልል በሶማሌና በኦሮሚያ ክልል በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች ድጋፍ አደረገ – የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

(ኢፕድ) – የአማራ ክልል በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚሆን 31 ተሽከርካሪ የእንስሳት መኖ ድጋፍ አድርጓል። የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ለአንድነታችን በጋራ መሥራት ይገባናል ያሉት ዶክተር ይልቃል የሶማሌ ወንድሞቻችን የድርቅ አደጋ የሁላችንም ቁስል በመሆኑ አይዟችሁ ልንላቸዉ መጥተናል። በጋራ መቆም በሚያስፈልገበት ወቅት በጋራ ቆመናል፤ በዚህም ድጋፍ የአንድነት ተምሳሌትነታችንን አሳይተናል ብለዋል። በሶማሌ ክልል የተከሰተውን የድርቅ ችግር በጋራ ለመፍታት ጥረት እንደሚያደርጉ ገልጸወ፣ ለተደረገላቸው አቀባበል ምሥጋና አቅርበዋል፡፡ የአማራ ክልል በኦሮሚያ ክልል በጉጂ፣ ቦረና እና ባሌ አካባቢ በድርቅ ለተጎዱ አርብቶ አደሮች የእንስሳት መኖ ድጋፍ አደረገ። በድጋፍ ርክክቡ ስነስርዓቱ ላይ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለ እና የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር ሽመልስ አብዲሳ ተገኝተዋል። የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር ሽመልስ አብዲሳ፣ ኢትዮጵያ የገጠማትን ችግሮች መቀልበስ የሚቻለው ክልሎች እርስ በእርስ መደጋገፍ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የአማራ ክልል ላደረገው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን ከኦሮሚያ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
Posted in Ethiopian News

ዝክረ ዘእሸቴ ሞገስ ወይታገስ – እስክንድር ነጋ

እስክንድር ነጋ፣ የህሊና እስረኛ፣ ቂልንጦ፣ አዲስ አበባ ቁምነገሩ ከቶ ይህ ጥያቄ መጥቶልኝ አያውቅም፡፡ ሆኖም፣ ይህችን እስክሪብቶ ብድግ አድርጌ ስለ አባትና ልጅ ልፅፍ ስከጅል፣ ድንገት ብልጭ ብሎብኛል፡፡ ግን ወደዚያ ከመግበቴ በፊት፣ የሚቀድም ነገር አለ፡፡ በዓለማችን የሰው ልጅ ብዛት የሰባት ቢሊዮንን መሥመር ያለፈው ባልፈው ዓመት ይመስለኛል፡፡  ከ200 ዓመታት በፊት አንድ ቢሊዮን ነበርን፡፡ ከመቶ ዓመታት በኋላ ሁለት ቢሊዮን ደረስን፡፡ ከዚያም ወደ ሰባት ቢሊዮን ዘለልን፡፡ እመርታው እየፈጠነ ነው፡፡ ይህ የሚያሳስበው ካለ፣ ይረጋጋ፡፡ ይህ ሁሉ ሰው ትከሻ ለትከሻ ቢቆም፣ ከማዳጋስካር ደሴት በላይ የማይፈለግ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ሲናገሩ ስምቻለሁ። ዓለም በቂ ቦታ አላት፡፡ ህይወትን የሚያክል ውድና ብርቅ ነገር ለመቋደስ ወደዚች ዓለም የሚመጡትን ሁሉ በፀጋ መቀበል አለብን ብዬ አምናለኹ፡፡ እንደ ማለዳ ጤዛ ብልጭ ብላ የምትጠፋው የዚህች ዓለም ቆይታችን፣ ያለውን ተካፍለን ለመብላት አይከብደንም፡፡ ባለው ላይ በእጥፍ እጥፍ ለመጨመርም ጥበቡ አልጠፋንም፡፡ ቁም ነገሩ ቁጥራችን አይደለም፡፡ ወደዚህች ዓለም መምጣታችንም አይደለም፡፡ ቁም ነገሩ፣ ይህችን ብርቅዬ ህይወት እንዴት ነው የምንኖራት? የሚለው ነው፡፡ ሁለት መንገዶች አሉ፡፡ አንደኛው መንገድ፣ በፈጣሪ የምንመራበት ነው፡፡ ሁለተኛው፣ በራስ ህሊና መመራት ነው፡፡ በሁለቱም፣ “ሞራል” በምንላቸው ህጎች አሉ፡፡ ልዩነታቸው ህጎቹን የሚያወጣው አካል ነው፡፡ በአንደኛው፣ ደንጋጊው ፈጣሪ ሲሆን፣ በሁለተኛው የፈጣሪን ቦታ ሰው ወስዶታል፡፡ በቅዱስ ሚካኤል ስም እየማለና የእኔን ልብ በሀዘንም በደስታም ተርትሮ ወደ መቃብሩ የወረደው የሸዋ ሮቢቱ እሸቴ ሞገስ፣ በፈጣሪው መንገድ ተግቶ ለመገኘት እየወደቀና እየተነሳ በዚህች ዓለም የነበረውን ሩጫ ጨርሷል ብዬ
Posted in Ethiopian News

ህወሓትና አዲሱ የኮንፌዴሬሽን ዓላማው – እስክንድር ነጋ

እስክንድር ነጋ፣ የህሊና እስረኛ ቂሊንጦ፣ አዲስ አበባ 1.1 አንድነት ሲባል…. በአንድ በኩል የቀድመው የናይጀሪያው ፕሬዝዳንት ኦባሳንጆ፣ በሌላ በኩል፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ልዩ መልዕክተኛ ጄፈሪ ፌልትማን፣ የስሜኑን ጦርነት በድርድር ለማስቆም ታች ላይ ብለዋል፡፡ በንፅፅር፣ ከፌልትማን ይልቅ የኦባሳንጆ እንቅስቃሴ ራቅ ብሎ ሄዷል፡፡ ዐቢይንም ደብረፅዮንንም አነጋግረዋል፡፡ ከዐማራ፣ ከኦሮሞና ከአፋር ርዕሰ መስተዳሮችም ጋር ተወያይተዋል፡፡ ከዚያም ለአፍሪቃ ህብረትና ለተባበሩት መንግስታት ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም፣ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ እንከን የማይወጣለት አካሄድ ነበር፡፡ ፈረንጆቹ Very professional እንደሚሉት ነው፡፡ አባሳንጆ የዋዛ ሰው አይደለም፡፡ ከማንም በማይተናነስ ደረጃ የናይጄሪያ ዴሞክራሲ ባለውለታ፣ በብዙዎች የሚደነቀው የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ስብሰብ ኤኬዋስ (ECOWAS) መሃንዲስ፣ የተዋጣላቸው ወታደር፣ ደራሲ፣ ሙህርና ዘመናዊ ገበሬ ናቸው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ፣ ሽምግልናውንም ተክነውበታል፡፡ ከአፍሪቃ ዕንቁዎች አንዱ ናቸው፡፡ እንደ ኦባሳንጆ ገለፃ ከሆነ፣ እስከ አሁን ባለው ሂደት፣ ሁለቱም ወገኖች የኢትዮጵያን አንድነት ያከብራሉ ብለው እንደሚተማመኑ ተናግረዋል፡፡ ግን፣ ህወሓት በዋናነት የሚታገለው ለትግራይ ነፃነት መሆኑን በተደጋጋሚ ተናግሯል። ነፃነቱ የማይቻል ከሆነ ደግሞ፣ እንደ ሁለተኛ አማራጭ አንድነትን የሚቀበለው በኮንፌዴሬሽን ጥላ ስር ብቻ መሆኑንም እየገለፀ ይገኛል። ጦርነቱ በፌዴራል መንግሥቱ የበላይነት ቢጠናቀቅ እንኳን፣ ሌሎች የብሄር ድርጅቶች (በተለይ የኦሮሞዎቹ) ሃሳቡን ተቀበለው ለመቀጠል መሞከራቸው ስለማይቀር፣ ኮንፌዴሬሽን ምን ማለት እንደሆነ እንደ ሀገር ግንዛቤ መጨበጥ ይገባናል። የምንደግፈውንም ሆነ የምንቃወመውን ነገር ጠንቅቀን ማወቅ ይገባናል። ይቺ ፅሁፍ ጥልቀት ያለው እውቀት ለማስጨበጥ ከቶ አትከጅልም። መነሻ ሃሳብ ግን ትሆናለች። 1.2 ኮንፌዴሬሽን በግርድፉ በኮንፌዴሬሽን ዙሪያ የተፃፉ የተለያዩ መፅሃፍትና ጥናታዊ ፅሁፎች፣ ጥቅል
Posted in Ethiopian News

የከለላ ወረዳ አመራሮች የክህደት ስራ

ሰኢድ ሶሻል አሸባሪውን ወራሪ ሃይል ለመመከት ከደገር እስከ ልጓማ ያሉ የከለላ ሚሊሻዎች ተሰባስበው ለሳምንት የዘለቀ ተጋድሎ ባደረጉበት ወቅት የከለላ ወረዳ አመራሮችና ባለሃብቶች የሰሩት ስራ እጅግ አስነዋሪ እጅግ አስፀያፊ ነበር። እነዚህ የህዝብ ጠላት የሆኑ ባንዳዎች የፀጥታ ሃይሉ ወደ ግንባር ማቅናቱን እንዳወቁ ቀጥታ የገቡት ወደ ዘረፋ ነበር ። ጥይትና ሌሎች በትግሉ አስፈላጊ የነበሩ ቁሳቁሶችን ሳይቀር የዘረፉት ሌባዎቹ አመራሮች ህዝባቸውን አደራጅተው ከፊት መምራት ሲጠበቅባቸው እነርሱ ግን የመረጡት ከሗላ ህዝባቸውን መምታት ነበረ። የወረዳ አመራሮቹ ከአንዳንድ ባለሀብቶች ጋር በመሰማራት ከተራ ሱቅ ዘረፋ እስከ መንግስት ተቋማት ድረስ ሙልጭ አድርገው በመዝረፍ ከከተማ ሲያሸሹ ነበር የከረሙት ። ወራሪው የትግራይ ሃይል ወደ ከለላ እንደሚገባ እርግጠኛም ስለነበሩ ለህወሃት አቀባበል ለማድረግ ዝግጅታቸውን ጨርሰው ነበር ። አዎ እነርሱ ይህን ክህደት በሀገራቸውና በህዝባቸው ላይ ፈፀሙ !! የሚመሩትን ህዝብ እንደ ተራ ዱርየ ዘረፉት ። የሚያስተዳድሩትን ተቋም ሙልጭ አድርገው ሰረቁት ። ከዚያም አልፎ ለመከላከያ ሃይሉ የተዘጋጁ በሶና ኮሾሮዎችን ሳይቀር ነበር ሙልጭ አድርገው የዘረፉት ። ጥይት አለቀብን አቀብሉን እያለ የሚማፀናቸውን ሚሊሻ ክደው የወረዳውን የጥይት ክምችት ለመሸጥ በጆንያዎች ቆጥረው እያዘጋጁ ነበር። ግና እነርሱ ያሳቡት ሳይሆን ቀርቶ አሸባሪው ሃይል ከለላን ሳይረግጥ ከልጓማ ተመለሰ። የአማራ ልዩ ሃይልና ፋኖ ከለላ ሲገባ ግን ለነርሱ ጨለማው ነው የተደፋባቸው ። ፋኖና ልዩ ሃይሉ እነዚህን ሌባ ቀማኛና ህዝብን የካዱ አመራሮችን ከነዘረፉት ንብረት በቁጥጥር ስር አውሎ ” እኔን ያየ ይቀጣ ” እያስባለ አሸክሞ ከተማውን አዙሯቸዋል
Posted in Ethiopian News

የሶስተኛዉ ታላቅ የኣፍሪካ ሩጫ በደማቅ ሁኔታ ዋሽንግተን ዲሲ ተካሄደ

አትሌት ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ ከ 20 በላይ ኦሎምፒያኖች እና የዓለም ሻምፒዮኖች በዝግጅቱ ላይ በክብር እንግዳነት ተሳትፈውበታል። አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የኣፍሪካ ኢምፓክት ኣዋርድ ተሸላሚ ሆነች። ዋሽንግተን ዲሲ (ጥቅምት 6፣ 2014 ዓ.ም)፤ የሶስተኛዉ ታላቅ የኣፍሪካ ሩጫ በዲሲ ባሳለፍነው ቅዳሜ ጥቅምት 6, 2014 ዓ.ም. በዋሽንግተን ዲሲ ተካሄደ። በዝግጅቱ ላይ ከ20 በላይ ታዋቂ ኦሎምፒያኖች እና የዓለም ሻምፒዮን የሆኑ የአገር ባለውለታዎች የዝግጅቱ ተሳታፊዎችን ለማበረታታት የተካፈሉበት ሲሆን የኢትዬጲያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ኘሬዚደንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ አትሌት ቁጥሬ ዱለቻ እና ብርሃኔ ኣደሬ በክብር አንግድነት የተገኙበትም በውድድሩ የተሳተፉበትም ዝግጅት ሆኖ ኣልፏል። ‘አብሮነት መሻል ነው’ በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ይህ ዝግጅት፤ ኢትዮጵያዊያንን ለማሰባሰብ፣ የመጀመሪያው ትውልድ ልጆችን ከባህላቸው ጋር የበለጠ ለማቀራረብ፣ እና ለተለያዩ በጎ ስራዎች ገቢ ለማሰባሰብ ዓላማው አድርጎ የተከናወነ ነው። በዚህ ዝግጅት፥ በሺወች የሚቆጠሩ የዲያስፖራው ማህበረሰብ አባላት ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛት ተጉዘው የታደሙበት ነበር። በአለፉት ታላቅ የኣፍሪካ ሩጫ ዝግጅቶች፣ የአገራችን ብርቅዬ አትሌቶች ደራርቱ ቱሉ፣ ቀነኔሳ በቀለ፣ የዲባባ ቤተሰብ፣ ሚሊዮን ወልዴ፣ ፋጡማ ሮባ እና ሌሎችም በክብር እንግድነት ተገኝተዉበታል። በዚህ ኣመት ኣምባሳደር ፍፁም ኣረጋ አና ደራርቱ ቱሉ ውድድሩን ያስጀመሩት ሲሆን በሴቶቹ ምድብ ብርሃኔ ኣደሬ እና ቁጥሬ ዱለቻ 1ኛ እና 2ኛ ሆነው ኣጠናቀዋል። የታላቅ የኣፍሪካ ሩጫ ዋና አዘጋጅ ዶክተር ጋሻው አብዛ ፤ ዝግጅቱ ኣትሌትክስን እንደ መድረክ በመጠቀሞ፤ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያንን በማቀራርብ ረገድ ጉልህ ሚና በመጫወት ላይ አንደሚገኝ ገልፀዋል። አያይዘውም፣ አርቲስት መሰረት መብራቴን የበጎ ፈቃድ
Posted in Ethiopian News

እንጋፋው ጋዜጠኛ እና የነጻነት ታጋይ አቶ ከፋለ ማሞ አረፉ

የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪና አንጋፋው ጋዜጠኛ አቶ ከፋለ ማሞ ከዚህ አለም በሞት ተለይተውናል፡፡ አቶ ከፋለ ማሞ አለሜ ከአባታቸው ከአቶ ማሞ ዓለሜ እና ከእናታቸው ወይዘሮ ደስታ በጋሻው በቀድሞ አጠራር ሸዋ ክፍለ ሀገር በሰላሌ አውራጃ ሀምሌ 16 ቀን 1930 ዓ/ም ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ የመጀመርያ ደረጃ ትምህርታቸውን አዲስ አበባ በሚገኘው አምሃ ደስታ ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በታዋቂው በጀነራል ዊንጌት ትምህርት ቤት ተምረዋል፡፡ ከዛም ወደእንግሊዝ ሃገር በማቅናት በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ለንዶን በፖለቲካል ሳይንስ የማስተርስ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል። አቶ ከፋለ ማሞ ለትምህርት ባላቸው ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ አሜሪካ በሚገኘው ዩኒቨርስቲ ኦፍ ዊስኮንሲን ማዲሰን በመሄድ በጋዜጠኝነት የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል። ሃገራቸውን ለማገልገል ባላቸው ጽኑ ፍላጎት የተነሳ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ ወደ አገርቤት ተመልሰው በከፍተኛ ሃላፊነት ቦታዎች በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ኢትዮጵያን በቅንነት አገልግለዋል። በመጀመሪያም በኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት መንግስት የቀድሞው የባህር ሀይል መምሪያ የአድሚራል እስክንድር ደስታ ልዩ አማካሪ በመሆን የሚጠበቅባቸውን አገልግሎት ሰጥተዋል። ከዛም በመቀጠል በማስታወቅያ እና መርሃብሄር ሚኒስቴር መስሪያቤት የሬድዮ መምሪያ ሃላፊ በመሆን ለረጅም ዓመታት በመስራት በኢትዮጵያ የሚድያ እና የጋዜጠኝነት ታሪክ ውስጥ ጉልህ አሻራቸውን አኑረዋል። በዚህ አገልግሎታቸው ወቅት የኢትዮጵያ ሬድዮን በማዘመን በሃገራቸን ታዋቂ የሆኑ ጋዜጠኞችን፣ ሙያዊ ክህሎት በማሳደግ ረገድ ያደረጉት አስተዋጾ በነባር ጋዜጠኞች ዘንድ እስካሁን ሲዘከር ይኖራል። ከኢትዮጵያ ሬድዮ አስኪያጅ ሀላፊነት በተጨማሪ በተለያዩ ጋዜጦች ላይ በዋና አዘጋጅነት በመስራት፣ የሃገራችንን ጋዜጠኝነት ወደ አንድ ከፍታ ካሸጋገሩ ጋዜጠኞች አንዱ በመሆን ገናና ስም አግኝተዋል። ከዚህ
Posted in Ethiopian News

የመተከሉ ኮማድ ፖስት አዛዥ ጀኔራል አስራት ዲኔሮ በሙስና ይታማሉ

ሰሞኑን ዋነኛው ጠላት ህወሀት ወደ ጥልቅ ገደል ሊወረወር ጅራቱ በተያዘበት በእዚህ ወቅት ሌላ አጀንዳ ማስገባት ተገቢ አይደለም በሚል የመተከልን እና የወለጋን ጉዳይ ባልሰማ ዝም ብዬ ነበር ። ነገር ግን የመተከሉም ሆነ የወለጋው ነገር ብርቱ ችግር ሁኗል። ጀነራል አስራት ዲኔሮ መተከልን ሊያረጋጋ የኮማንድ ፖስቱ ሰብሳቢ ሆኖ ከተመደ አመት አለፈው ። ነገር ግን ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሲከፋ እንጅ ሲሻሻል አላየንም። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉኝ ጀነራል አስራት ለጥቂት ቀናት አዲስ አበባ እያለ የ22ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል ሰይፈ ኢንጌ የተባለ ሰው ተመድቦ ቀጠናውን እሱ እስከነበረበት ሰዓት ድረስ ማረጋጋት ችሎ እንደነበረ መተከሎች ይናገራሉ ። ኮሎኔሉም በአጭር ቀናት በመተከል ህዝብ ዘንድ ተወዳጅነትን ማትረፍ ችሎ ነበር ነገር ግን ከቀናት በኋላ ጀነራል አስራት ሲመጣ ችግሩ ተባብሶ ቀጥሏል ። ማረጋገጥ ባልችልም ጀነራል አስራት ከገዳይ ቡድኑ በርከት ያለ የወንበራ ወርቅ በእጅ መንሻነት እንደተሰጠው ሀገሬው ያወራል (ምክንያቱም ጉምዞቹ እንደ ባህል ሀሰት መናገር ስለማያውቁ ከእነሱ የተገኘ መረጃ ነው)። ዛሬ ከዞኑ ዋና ከተማ ግልገል በለስ ወደ ድባጢ ወረዳ መስመር 3 ኪ/ሜ ርቀት ኤሲፃ የተባለች ንዑስ ቀበሌ ላይ ከማለዳው 1:00 ጀምሮ ይሄንን ጹህፍ እስከጻፍኩበት 5:30 ድረስ በመከላከያውና በጉምዝ ገዳይ ቡድኑ መካከል ከባድ ጦርነት እየተደረገ ይገኛል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በልዩ ሁኔታ በሚመሩት መተከል ዞን ቦታው ድረስ በመሄድ ለህዝቡ በአንድ ወር ውስጥ ወደ ቀድሞው ሰላም እንመልሰዋለን ቢሉም ችግሩ እስከ አሁን ድረስ ሊቀረፍ አልቻለም። የእኔ ጥያቄ
Posted in Ethiopian News

ራያ ዳግማዊቷ አጣዬ ሆናለች – ወንድወሰን ተክሉ

ወንድወሰን ተክሉ መንግስት በአላማጣ ኮረምና አካባቢው ላይ የፈጸመው ታላቅ ክህደታዊ ወንጀል ቅዳሜ ሀምሌ 10 ቀን 2013 አላማጣ፣ ኮረም፣ ዋጃና አካባቢው ሙሉ በሙሉ በህወሓት ቁጥጥር ስር መሆኑን የሚያረጋግጥ መረጃን መግኘት ከመቻሌ ይልቅ ባላገኘሁትና ቀደም ብሎ ባሰራጨነው አካባቢዎቹ በእኛ የአማራ ልዩ ኃይሎች እጅ ስር እንዳለች አድርጌ እያስተጋባሁ ብገኝ ስል ተመኘሁና ደግሞም ስለምን እውነትን እንዳልተከሰተ አድርገህ ለመካድ ትሻለህ የሚለው ውስጣዊ ህግ አገደኝና ቢያመኝም ይህንን ሀቅ ማሳወቁን በመወሰን አዎን አላማጣ፣ ኮረም፣ ዋጃና አካባቢው ዛሬም በህወሓት እጅ ስር ያሉ ከተሞቻችን ናቸው የሚለውን ይህንን ዜና መከተብ ጀመርኩ፡፡ ራያ ዳግማዊቷ አጣዬ ሆናለች፡፡ አጣዬ ምንድነው የሆነችው ብላችሁም እራሳችሁን በጥያቄ ሳታስጨንቁ በአጭሩ በራያ አላማጣ ኮረም የሆነውን ልንገራችሁ፡፡ በአላማጣ ኮረምና አካባቢው ያሉ ምሽጎች ከአካባቢው እጅግ ወሳኝ ገዢ ስፍራነት የተነሳ ምሽጎቹ በጣም የጠነከሩና ልዩ ኃይል ስር የነበሩ ናቸው፡፡ ከአዲስ አበባ አራት ኪሎ ቤተመንግስት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ አቢይ አህመድ በተላለፈ ቀጭን ትእዛዝ ከትግራይ disorganized በሆነ ሁኔታ እየፈለሰ ወደ ወልዲያ ሲተም ከነበረው ሰራዊት የተረፈውና በኮረም አላማጣና አካባቢው ከተሞች ሰፍሮ ያለው በአማራ ልዩ ኃይል እጅ ያለውን ምሽግ እንዲረከብ ይታዘዝና ወደ ምሽጎቹ ያቀናል፡፡ የአማራ ልዩ ኃይልም በዚህ የመከላከያ ሰራዊቱ እርምጃና ትእዛዝ ግራ በመጋባት «ምሽጋችንን ለቀን አንወጣም» በማለት ለመከላከያው እንቢታውን ይገልጽና ወዲያውን ወደ አቶ አገኘሁ ተሻገር በመደወል ጉዳዩን ያሳውቃል፡፡ የልዩ ኃይላችንን የስልክ ጥሪ የተቀበለው አቶ አገኘሁ ተሻገርም «አሁን እናንተ ማድረግ ያለባችሁ የመከላከያውን ትእዛዝ ተቀበሉና ምሽጉን
Posted in Amharic News

የአገኘሁ ተሻገር የድምፅ መልእክት ትክክለኛ ስለመሆኑ – ሠአሊ አምሳሉ ገብረኪዳን

በሠአሊ አምሳሉ ገብረኪዳን ተጻፈ የፀረ አማራው የወያኔ አህያ የብአዴን መሪ አቶ አገኘሁ ተሻገር “ለታማኝ በየነ የላከው የድምፅ መልእክት (voice message) ነው” የተባለውን 9 ደቂቃ ከ53 ሰከንድ የፈጀ የድምፅ መልእክት አዳመጥኩት፡፡ በሶሻል ሚዲያ የተለያዩ ሰዎች “የተቀናበረ ነው፣ ተመሳሳይ ድምፅ ባለው ሰው የተቀዳ ቅጅ ነው” ምንንትስ ባሉ ሰዎች ጭፍንነትና ማስተዋል አለመቻል በጣም አዘንኩ ተደነኩም፡፡ ድምፁ የአገኘሁ ለመሆኑ ፈጽሞ የሚያጠራጥር ነገር የሌለውና ከፍተኛ ጥራት ያለው የድምፅ መልእክት ነው፡፡ “ከሌሎች ንግግሮች እየተቆረጠ የመጣና የተቀናበረ ነው” እንዳይባል የድምጹ ቶን ወጥ መሆኑና ከጀርባ የሚሰማው ድምፅ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ድረስ መኖሩ “ከሌሎች ንግግሮች ተቆራርጦ የተቀናበረ ነው” የሚለውን ግምት ያፈርሳል፡፡ “ድምፁ የአቶ አገኘሁን የሚመስል ሰው ድምፅ ነው እንጅ የአቶ አገኘሁ አይደለም” የሚለው የጨነቃቸው ሰዎች አስተያየትም የድምፅ ቅጁ ፈጽሞ ለመለየት በማያስቸግር ደረጃ ጥርት ብሎ የሚሰማ ድምፅ በመሆኑና የአቶ አገኘሁ ድምፅ መሆኑን ለመለየት ምንም የማያስቸግር በመሆኑ ይሄ አስተያየትም የሚረባ አይደለም፡፡ የገረመኝ ነገር “ተሰደብን” ያሉ የጎጃምና የወሎ ሰዎች ቅሬታ ነው፡፡ ቆይ እንጅ እኔ የምለው በዓይናቸው በብረቱ አሻጥር ሲሠራባቸው ያዩ እና በአሻጥር ተጨፍጭፈው ከማለቅ በስተቀር በቅጥረኛው ፀረ-አማራ ብአዴን ትዕዛዝ ስር ተሰልፈው ጠላትን በመደምሰስ ያሰቡትን ጀብድ መፈጸም የማይችሉ መሆናቸው የገባቸው በራያ ግንባር የተሰለፉት የጎጃምና የወሎ ፋኖዎች “ወደቤታችን መልሱን!” አሉ መባላቸው ምንድን ነው ነውሩና ስድቡ? እኔን ይገርመኝ የነበረው ይሄንን ባይሉ ነበር እንጅ ይሄንን ማለታቸውማ ንቃታቸውንና ብስለታቸውን ነው እንጅ የሚያሳየው ፈጽሞ ፍርሐታቸውን አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሊዋጉ
Posted in Ethiopian News

የኤርሚያስ ለገሰ ደንቃራነት

ከሰመረ አለሙ ኤርምያስ ለገሰ ቀደም ባለዉ ጊዜ ትምህርቱን እንደ ጨረሰ ለህወአት መንግስት ተቀጥሮ ሲሰራ ከቆየ በሁዋላ መዉጫዉን እንዳገኘ ከሞቀዉ ወምበሩ ተነስቶ ወደ ሀገረ አሜሪካ ኮብልሎ መጠለያ ሲፈልግ እዉር ድምብሩ የጠፋባቸዉንና ታዋቂ ኢትዮጵያንን አነፍንፎ በመጥለፍ የተካነዉ የግምቦት 7 ሀይል ላይ ወደቀ። እንግዲህ ልብ በሉ ለሀገሩ እንግዳ ለሰዉ ባዳ የሆነ ሰዉ ግምቦት 7 ያቀረበለትን ፍቃድ አሰጥሀለሁ የሚለዉን አማራጭ የሌለዉን ምርጫ ተቀብሎ በግምቦት 7 ቅኝት ኢሳት በሚባለዉ የዜና ተቋም ገብቶ ኢሳትን ነብስ ዘራበት በምሁራዊ አስተያየቱና ትንታኔዉም የዜና ተቋም መልክ አስያዘዉ። ታዲያ ጊዜያቶች እያለፉ ሲሄዱ ኤርምያስ ለገሰና መሰሎቹ ኢሳት ዉስጥ ያለዉ ነገር ስላልጣማቸዉ ኢሳትን ጥለዉ ኢትዮ 360 የተባለ የሚዲያ ተቋም ከፈቱ። ኢትዮ 360ም በኤርምያስና በባልደረቦቹ የፖለቲካ ትንታኔ የወያኔን አካሄድ ዱካ ዱካዉን እየተከታተሉ በማጋለጥ፤ ኤርምያስም የአይን እማኝነቱንና ዉስጥ አዋቂነቱን በመጠቀም የሰጠዉ ምስክርነትና ትንተና የተመልካችና የእድማጭን ቀልብ በመሳቡ የሚዲያዉ ተከታታዮች ከእለት ወደ እለት እያሻቀበ ሄደ። ይህም አካሄድ ኢሳትና ግምቦት 7 አካባቢክፉኛ መደናገጥን ፈጠረ። ኢትዮ 360 የሀገራችንን ፖለቲካ በመግራት፤ የህወአትን አሰራር በማጋለጥ፤ ህወአት ሊያደርግ ያቀደዉን ቀድሞ በምሁራዊና በፖለቲካዊ እይታ ለህዝብ በማሳጣት፤ እዉቅ ምሁራንና ሀገር ወዳድ የአንድነት ሀይሎችን በመጋበዝ፤ እይታቸዉን ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያጋሩ በማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ አደረገ። እንደሚባለዉ የኢትዮጵያ ሚኒስተሮችም ከተራዉ ህዝብ ባላነሰ ማስታወሻ እየያዙ እንደሚከታታሉ ከሀገር ቤት የሚደርሱ መረጃዎችም ይጠቁማሉ ያለባቸዉን የእዉቀት ክፍተት ለመድፈንም ኢትዮ 360ን በቋሚነት ይታደማሉ። በቅርቡ እንኳን የአባይ ድርድር ከአሜሪካኖች እጅ ወጥቶ ኢትዮጵያ ሚዛን
Posted in Ethiopian News

“እኛና አብዮቱ” – የጓድ ፍቅረ ሥላሴ ውዳሴ ከንቱ

ሶሎ ቴስላ ትናንት ታኅሣስ 02/2013 ዓ.ም ጓደኛዬን ጥየቃ ወደፈረንሳይ ሌጋሲዮን አካባቢ ብቅ ብዬ ነበር፡፡ ሻይ ቡና ካቀረበልኝ በኋላ አንድ ቆየት ያለ መጽሔት አሳየኝ፡፡ መጽሔቱም አዲስ ጉዳይ ነበር፡፡ እዚያም ላይ ታትሞ የነበረውን የመጽሐፍ ግምገማ ትችት ተመለከትኩት፡፡ እኔም ሆንኩ ጓደኛዬ የሟቹን የደርግ ዘመን ጠ/ሚ/ር ፍቅረ ሥላሴ ሞት አልሰማንም፡፡ ለማንኛውም፣ ጥራትም ባይኖረው የመጽሔቱን ሽፋን ፎቶ አንስቼዋለሁ፤ ብታዩት ለማመሳከሪያም ያህል ይረዳችሁ ይሆናል፡፡ … ጽሑፉ/ሐቲቱ የተጻፈው የዛሬ ሰባት ዓመት ከስምንት ወር ገደማ ነው፡፡ በመጋቢት 8/2006 ዓ.ም ነበር ታትሞ የወጣው፡፡ ጽሑፉ፣…የዚያን ጊዜውን ሰሎሞን አተያይም የሚያንጸባርቅ ነው፡፡ አሁን ላይ በብዙ መልኩ የተለወጥኩ ያህል ይሰማኛልና ነው፡፡ ማለትም፣ ፈረንጆቹ “Critical Distance” የሚሉትን ጽንሰ-ሃሳብ (ዘይቤ) አሁን ላይ አለኝ ለማለት ነው፡፡ ለማንኛውም፣ …መልካም ንባብ እመኛለሁ፡፡ መንደርደሪያ፤ የጓድ ፍቅረ ሥላሴ ወግ-ደረስ “እኛና አብዮቱ” የተሰኘው መጽሐፍ በአውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ12/25/2013 ዓ.ም ታትሟል፡፡ 440 ገጾች ያሉት መጽሐፍ ሲሆን፣ ዋጋው 34.95 ዶላር ነው፡፡ አሳታሚውም “ፀሐይ ፐብሊሸር” የተባለው በአሜሪካን አገር የሚገኝ አሳታሚ ድርጅት ነው፡፡ (ይህ አሳታሚ ድርጅት የጓድ መንግሥቱ ኃ/ማርያምንም “ትግላችን” የተሰኘ መጽሐፍ ያሳተመ ነው፡፡) የጓድ (የሻምበል) ፍቅረ ሥላሴን መጽሐፍ ገጽ በገጽ እየገለጡ ሲያነቡት እጅግ ያዳግታል፡፡ ሽቅብ እያዩ እንደሚወጡት ዳገት ያህል አንባቢውን ያስለከልካል፡፡ ጸሐፊው በቋንቋ አጠቃቀማቸውም ሆነ በመረጃ አቀራረብ ችሎታቸው እጅግም ናቸው፡፡ የአንድ ወገንን ትችትና ሐተታ ለመስማት ካሻችሁ፣ የጓድ ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ መጽሐፍ አለላችሁ፡፡ መግቢያ፤ ስለጓድ ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቅኩትም ሆነ ያነበብኩት በ1976/7 ዓ.ም
Posted in Amharic News

የእንጦጦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅና የተፈሪ መኮንን ቀድሞ ተማሪዎች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ 206 ነዋሪዎች ድጋፍ አደረጉ  

የኮሌጁ ማህበረሰብ ድጋፉን ያደረገው በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ የቀድሞ የኮሌጁ ተማሪዎች 253ሺ600 ብር እና የኮሌጁ ማህበረሰብ 35ሺ ብር በድምሩ ከ288ሺ 600 ብር በመሰብሰብ ለ206 በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች ድጋፋቸውን አድርገዋል፡፡ በድጋፉ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አማካሪ ወ/ሮ ባንቺ ተሾመ የኮሌጁ ማህበረሰብና የቀድሞ ተፈሪ መኮነን ለወገናቸው ያደረጉት ድጋፍ ለሃገርና ህዝባቸው በችግር ጊዜ ደርሰው ድጋፍ በማድረጋቸው በአስተዳደሩ ስም ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የእንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምክትል ዲን ወ/ሮ ዋጋየ ገ/መድህን ኮሌጁ ከቀድሞ የተፈሪ መኮነን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ማህበር ጋር በመቀናጀት መንግስት ባደረገው የማእድ ማጋራት ጥሪን ተቀብሎ የኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ በሃገራችን ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ ለ3ኛ ጊዜ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በተደረገው ድጋፍ ለ206 ሰዎች ለእያንዳንዳቸው 25 ኪሎ ግራም ዱቄት፣5ኪሎ መኮረኒ፣5 እሽግ ፓስታ፣ 3ሊትር ዘይት እና 2 የአፍ መሸፈኛ ማስክ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ምንጭ፦ ጉለሌ ፕሬስ
Posted in Amharic News

ኦሞ የኢትዬጵያ አንድነትና ፍትሕ ማዕከል በወላይታ በተከሰተው ቀውስ ዙሪያ የተሰጠ መግለጫ

ኢትዮጵያ ከ27 አመታት በላይ ካስቆጠረው ከአፋኙ የህወሀት ኢህአደግ አገዛዝ ተላቃ የተሻለ የለውጥና የሽግግር የሽግግር ሂደት ከጀመረች 3 አመታት ተቆጥሯል። ይሁን እንጂ በዚህ ሃያ ሰባት ዓመታት ባስቆጠረው ረጅም ጊዜ ተወልደው በዚሁ ሥርዓት ውስጥ ያደገው ትውልድ በዘርና በቋንቋ በተቃኘው ክልልና ማንነት ራሳቸውን አቆራኝተው ከአገራዊ አንድነት ይልቅ ልዩነት እየተሰበከ ፅንፈኝነትን በሰፊው በመንገሡ በዚህ ስሜት በመጠመድ በህዝብ መካከል ጥርጣሬና ልዩነት እንዲፈጠር ተደርጓል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ በእልፍ ወጣቶች መስዋዕትነት ዕውን የሆነው ለውጥ አንፃራዊ መረጋጋትና ዲሞክራሲና ነፃነትን በመስፈኑ በተገኘው አጋጣሚ በውጪው ዓለም ጭምር በስደትና የብረት ትግል ይሳተፉ የነበሩት አገራቸው ገብተው በሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ ሁኔታዎች በመመቻቸታቸው በርካታዎች ከጎሬቤት አገራት ፣ አውሮጳና አሜሪካ ጥሪ የተደረገላቸው ጥሪውን ተቀብለው በአገራቸው የወደፊት ዕጣ ፋንታ ሚና እንዲኖራቸው ተደርገዋል፤ በዚህም አንዳንድ ድርጅቶችና ስብስቦች ዕድሉን ለጥሩ አገራዊ ግንባታ ማዋል ሲገባቸው ድርጅታዋዊ መዋቅራቸውን በተቃራኒው ዘረግተው ሕወኃት በዘረጋው መንገድ ሕዝባችንን በዘርና ሐይማኖት በማለያየትና ግጭት በመቀስቀስ በሀገራችን ከፍተኛ መፈናቀል ሞትና ንብረት ውድመት እንዲከሰት ተደርጓል! በወላይታ ዞንም የዚህ ፅንፈኛ ቡድን ቀስ በቀስ ሥር በመስደድ የወላይታ ለብቻው ክልል መሆን የችግሮች ሁሉ መፍቻ እንደሆነ ሕዝብንና ወጣቱን በመቀስቀስ አብሮት ለዘመናት ከኖረው የአካባቢውና አጎራባች ህዝቦች ጋር በማጋጨት፣ ከአብሮነት ይልቅ ለብቻ ክልል የመሆን ጥያቄ ብቻ እንዲጎላ ተደርጓል። ይህም መሆን ካለበት አገራችን የኮሮናን ተስቦ በመከላከል አደጋና በሕዳሴው ግድብ ግንባታ ከግብፅ ጋር በገባቺው የፍጥጫ ውስጥ በምንገኝበት ምቹውን ጊዜ ጠብቆ እንደ አንድ ሁነኛ ዜጋ ሀገር ሲረጋጋ
Posted in Ethiopian News

ክሹፍ ፖለቲካዊ ውይይት አገራዊ መግባባትን አይወልድም – ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ መግለጫ መንግስት ከሰሞኑ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በሚል የጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት ከመረጣቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ብቻ ንግግር ማድረጉን ከመንግስት መገናኛ ብዙሃን ፖርቲያችን ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ተከታትሏል። በዚህም ጉዳይ ላይ ፓርቲያችን ተወያይቶ ተከታዩን ዕይታ እና አቋም ይዟል። አገራችን ኢትዮጵያን ወደ ብሔራዊ መግባባት እና ልማት ይወስዳታል ተብሎ በህዝባችን እምነት ተጥሎበት የነበረው ከ2010 ዓ.ም መጨረሻ የጀመረው የለውጥ ሽግግር የመቀልበስ አደጋ አጋጥሞታል። ትናንት የነበርንበትን ሁኔታ የሚያስንቅ ተረኝነት እና የዜጎች ሰላም ማጣት ውስጥ ገብተናል። በዓለም ሶስተኛ ታላቋ የዲፕሎማት ከተማ የሆነችው አዲስ አበባ በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ብቻ ለሶስተኛ ጊዜ የህይወት መጥፋት እና ንብረት ውድመት ተጋልጣለች። ከትናንቱ ጉዳት ይልቅ የነገው ዕጣ ፈንታችን እጅግ ያሰጋናል። አገራችን በኦህዴድ/ብልፅግና ፓርቲ ዘመን ዜጎች በላባቸው ያፈሩትን ሃብት በጠራራ ፀሐይ የሚያጡበት፣ ሴቶች የሚደፈሩበት እና ወንዶች የሚታረዱበት የምድር ሲኦል መሆኗን እየታዘብን ነው። ከዚህ አሳዛኝ፣ አገራዊ እንዲሁም ትውልዳዊ ምስቅልቅል ውስጥ እንዴት መውጣት እንዳለብን ራዕይ አልባ የሆኑት ገዢዎቻችን ከመንግስት የሚሰጣቸውን አበል ብቻ የሚያስቡ የፖለቲካ አመራሮችን ፊት ወንበር ላይ አስቀምጦ የአገሪቱን ችግር ለመፍታት የተያያዘው ድራማ የሽግግሩ ትልቁ ቀልድ ሆኖ አግኝተነዋል። መንግስት በሃሳብ ገበያ ተወዳድሮ እንደማያሸንፈው የተረዳውን ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲን፣ ሕግ ማስከበር ተስኖት በአዲስ አበባ ከተማ ለደረሰው ጉዳት በፈጠራ ወንጀል ያለአንዳች ማስረጃ ተጠያቂ ለማድረግ አመራሮቹን እስር ቤት በመከርቸም፣ ጠቅላይ ሚንስትሩ ቀልባቸው ከወደዳቸው ፓርቲዎች ጋር ብቻ ተሰብስቦ “ስለብሔራዊ መግባባት” ተወያየን መባሉ፣ ከመነሻው የከሸፈ ሂደት ሆኖ
Posted in Amharic News

ከኦሞ ኢትዬጵያ አንድነትና ፍትህ ማዕከል የተሰጠ መግለጫ

በደቡብ ኢትዬጵያ ጋሞ ፣ ወላይታና ዳውሮ የክልል ጥያቄን አስመልክቶ በሚታዩ ውጥረቶች ዙሪያ ከኦሞ ኢትዬጵያ አንድነትና ፍትህ ማዕከል የተሰጠ መግለጫ!! ሰሜን አሜሪካ እናት አገራችን ኢትዮጵያ የጥንታዊ ታሪክ መዘክር የሰው ዘር መገኛ ስትሆን ፤ በመላ ህዝቦችዋ ጀግንነትና አንድነት በቅኝ ገዥዎች እጅ ሳትወድቅ ነፃነትዋን ጠብቃ ለመላው ጥቁር ሕዝብ ተምሳሌት በመሆን ታፍራና ተከብራ የቆየች ታሪካዊና ጥንታዊ ሀገር ነች። ሆኖም ላለፉት 27 ዓመታት በህወሀት/ኢህአደግ የአገዛዝ ዘመን ሀገሪቱን በቋንቋና በዘር ብቻ በማካለል ፌዴራሊዝም ሸንሽኖ በህዝብ መሀል ጥርጣሬ እንድነግስና የሰው ልጅ ሰው መሆኑን ረስቶ ለዘሩና ለጎሳው ብቻ እንዲያስብ አድርጎታል። አሁን በአራቱ የአገሪቱ ማዕዘናት ከኢትዬጵያዊነት ብሔረተኝነት ወጥቶ የማንነትና የግለኝነት ጥያቄዎች በእጅጉ ገነው እንዲወጡ ተደርገዋል! በመሆኑም ባለፉት 27 ዓመታት ተወልደውና ተኮትኩተው ያደጉ ለእናት አገራቸው ብዙም ኃላፊነት የማይሰማቸውና ይህንኑ የአካባቢ ብሔረተኝነት የሚያስተጋቡናት ይህንንም ተከትሎ ፅንፈኝነት የተፀናወታቸው ቡድኖች እንደ አሸን እንዲፈሉና እንዲጠናከሩ በመደረጉ ኢትዬጵያዊነት ከቶውንም እንዲዳከም የሕወኃት/ኢህአደግ አገዛዙ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል ፤ በዚህም መንስኤነት ከዚህ በፊት ለዘመናት በኢትዬጵያዊነት አንድ ሌላው አካባቢ አብሮ ይኖር የነበረው ሕዝብ በአሁኑ ወቅት ሰላም ርቆት በግጭትና አለመረጋጋት ለዘመናት ከኖረበት ቀዬው መፈናቀል የዚህ ውጤትም መሆኑን ማጤን ይገባል፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ብሄረሰቦችም የህወሀት/ኢህአደግ ፓለቲካ ሰለባ በመሆን እርስ በእርስ እንዲጋጩና እንዲገዳደሉም ተደርገዋል! በተለይ በጅምሩ ወጋጎዳ የተሰኘ የቋንቋ ማዳቀል የህወሀት/ኢሕአደግ ፕሮጀክት ሳቢያ ለዘመናት አብሮ የኖረውን ጋሞንና ወላይታን አጋድሏል አፈናቅሏል ፤ በሲዳማ የክልል ጥያቄ በሎቄ በሕወኃት/ኢሕአደግ ህዝብ ተጨፍጭፋል! ይህን ሁሉ እዳ የተሸከመው የደቡብ
Posted in Amharic News

በልዩነት ሳይሆን በአንድነት መቆም … – አበባየሁ አሉላ

በልዩነት ሳይሆን በአንድነት በመቆም ዛሬን በድል መሻገር ለነገም ዲሞክራሲያዊ መሠረቱን ማመቻቸ ዋስትና መስጠት፤ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ድርብ ግዴታ ሊሆን ይገባል! አበባየሁ አሉላ ዋሽንግተን ዲሲ እናት አገራችን ከፊት ለፊቷ አስከፊና አሳሳቢ አደጋዎች ተጋርጠውባታል! መላውን ዓለማችንን ያናጋው ሃብትና ስልጣኔ ረድፍ ላይ ያሉ አገራትን እየተፈታተነ ያለው የኮሮና ወረርሽኝ አደጋና በወገኖቻችን ሕይወት ላይ የደቀነው ስጋት እጅግ ከፍተኛ መሆኑ እውን ነው፤ ይህንን ተከትሎ የሚያስከትለው ማህበራዊ ቀውስና የምጣኔ ሀብት ውድመት ለደኃይቷ አገራችን እጅግ ከባድ ነው ፣ በተመሳሳይምን ወኃችንን ለመጠቀም ባለመው የሕዳሴው ግድብ ግንባታ ሳቢያ በሉዓላዊነታችን ላይ ያጠላው የግብፅ ምኞት ፤ ጎሬቤት ሱዳንንም በመደለል ፣ አረብ ሊግንና አባል አገራትን በማስተባበር ፣ ወሮታ ፍለጋ አሜሪካንን ጨምሮ በአንድ ግንባር ማስተባበር መሞከርዋና በውጭ ግንኙነት ዘርፍ ያለ ዕረፍት በሃሰት ፕሮፓጋንዳ ኢትዬጵያ ላይ እየዘመቱ ነው! አልፈውም የመንግሥታቱ ፀጥታውን ምክር ቤት ግንባታውን እንዲያስቆም መንቀሳቀሳቸው ምንስ ያክል ለጉዳዩ ትኩረት ስጥተው መስራታቸው ከፊት ለፊታችን የአጠላብን አደጋ ከባድ መሆኑን ጠቋሚ ነው። እንደዚሁም የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ ሕገመንግሥቱና ሕገመንግሥታዊ ቀውሱ ከአስከተለው መንገጫገጭ ጋር አገራችንን ለማሻገር ከምን ጊዜውም በላይ ሕዝባችን ፣ መንግሥት ፣ የፓለቲካ ድርጅቶችና በተለይም አንድነት ኃይሎች ፣ ሲብክ ማህበራትና ምሁራን ልዩነትን በማስወገድ በጋራ መቆም ታሪካዊ ግዴታችን ሊሆን ይገባል። በዚህ ፁሑፌ እንዲሁ ሁኔታዎችን መተንተን ሳይሆን አገራችንና ሕዝባችን ትላንት ያለፈበትን ውጣ ውረድና የከፈለው መስዋዕትነት ያስገኘውን ውጤትና ያጣውን ማሳየት፣ ዛሬ የምንገኝበትን ነባራዊ ሁኔታውን የሚገመግም ፤ አፍጠው የሚጠብቁንን ችግሮች የሚዳስስና የመፍትሔ
Posted in Amharic News

የመሬት ባንከ እና ልማት ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማህበር ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 17/2012 – የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመሬት ባንክ እና ልማት ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ አርክቴክቶች ማህበር ጋር በመሬት ይዞታ ልማት እና በዘርፉ ዕድገት ዙሪያ ተባብሮ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡ የወቅቱን ኮቪድ-19 ወረርሽኝን አስቀድሞ ለመከላከል እንዲቻል የመግባቢያ ስምምነት ፊርማው በቪዲዮ ኮንፍረንስ በመታገዝ በኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ት ሌንሳ መኮንን እና በኢትዮጵያ አርክትቴክቶች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ አማኑኤል መኮንን መካከል ተፈርሟል፡፡ በሰዎች እንቅስቃሴ አልያም በራሳቸው ዕድገት በመነጨ የኢትዮጵያ ከተሞች በፈጣን የከተማነት ሂደት ውስጥ ያሉ ሲሆኑ፤ ይህም በፍጥነት እያደገ ያለው የከተማ ቅየሳ እና ንድፍ ፍላጎቱን ተደራሽ ባደረገ መልኩ መከናወን እንዳለበት ያመላክታል፡፡ ከዚህ አንጻር የመሬት ባንክ እና ልማት ኮርፖሬሽን በፌደራል መንግሥት ተቋማት እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ስር ያሉ የመሬት ይዞታዎችን በመለየትና በማልማት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ለማስቻል እዲሁም ተለዋዋጭ ከሆነው የመሬት ልማት ዑደት ጋር ለመራመድ እንዲቻል የተቋቋመ ኮርፖሬሽን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመሬት ባንክ እና ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ት ሌንሳ መኮንን በመግባቢያ ስምምነት ፊርማው ወቅት ሲናገሩ፤ እንደ አርክቴክቶች ማህበር ካሉ ማህበራት ጋር የትብብር ስራ መስራት ማህበራቱ ያላቸውን እምቅ አቅም በመጠቀም ኮርፖሬሽኑ የሚያከናውናቸውን የመሬት ይዞታ ልማት ጥረቶች በጋራ ለማስተሳሰር የሚያስችል አይነተኛ ስልት ነው ብለዋል፡፡ ዋና ስራ አስፋፃሚዋ አክለውም፤ ˝ለራዕያችን መሳካት ልምዶቻችንን በመጋራትና የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎቱን በአግባቡ እንጠቀማለን˝ ሲሉ ገልፀዋል፡፡ በዚህ የትብብር ስምምነት መሰረት ሁለቱ አካላት በአዲስ አበባ የከተማ
Posted in Amharic News

በህብረብሄራዊነት በተጋመደ አንድነት ወደ ኢትዮጵያ ብልጽገና የተጀመረው ጎዞ መበየኛዎች

በኤ.የ.ሀ የፌደራሊዝም ዋንኛ የትርጉም መገለጫ የመንግሰት ስልጣን የሚጋራበት እና የሚከፋፈልበት ሁለት መሰረታዊ ጽንሰ-ሀሳቦችን የሚያራምድ የፖለቲካ ስርኣት ነው፡፡ እነዚህ መርሆች እራስን-ማስተዳደር በራስ ጉዳዮች (self-rule) እና የጋራ አስተዳደር በጋራ ጉዳዮች (shared-rule) አቀናጅቶ በመያዝ የሚፈጠር ማንኛውንም የመንግስት አወቃቀርን የሚመለከት ሰርኣት ነው፡፡ ስልጣንን በማከፋፈልና በማጋራት የፌደራሊዝምን ፍልስፍና ተከትለው የሚፈጠሩ የተለያዩ የመንግስት አወቃቀሮች (ኮንፌደሬሽን፣ ያልተማከለ መንግስት፣ ) የሚኖሩ ሲሆን አንድ ሰርኣት ፌደሬሽን ነው የምንለው፣ በፌደራሊዝም ሁለቱ መሰራታዊ መርሆችን ማለትም አይነትነትን (ልዩ ልዩነትን ወይም አንድ አይነት አለመሆንን) እራስን-ማስተዳደር በሚለው መርህ የተዛመደ ተጋሪነትን በአንድነትን  የጋራ አስተዳደር በማጋመድ የራስና የወል አስተዳደደር ባነድነት የሚከትሙበት ሀገረ መንግሰት የሚደራጅበት በሀቀኝነት የሚሰራበትን ሰርአትና ተቋማዊ አደረጃጀትን የሚፈጥር  ነው፡፡ ስለሆነም ፌደራሊዝም አይነትነትን (diversity) በራስ የማስተዳደርን እና የተጋመዱና የተዛመዱ ትስስሮች (shared values and interests) በወል በአሀዳዊነት ወይም በአንድነት የሚተዳደሩበትን ሁኔታ)  አዛምዶ አቻችሎ አስማምቶ የሚያኖር ስረኣትና ዘዴ ነው፡፡ እራስን ማስተዳደደር እና በጋራ በአሀድ የማስተዳደር ጉዳዩች ሁለቱም አስፈላጊ አንዱ ካላንዱ የማያስፈልግ ያንዱ መኖር ሌላው መኖር አስፈላጊ የሆኑ የሁለት ሳንቲም አንድ ገጽታዎች ናቸው፡፡ አንዱ ላይ አተኩሮ ሌላውን መዘንጋት ያልተገባ ብቻ ሳይሆን ዋጋ ያስፈልጋል፡፡   የፌደራሊዝም መሰረታዊ ጥቅሞች   ሀገራት የፌደራል ስርኣት በተለያዩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ መልካምድራዊ ገፊ ምክንያቶች ተግባራዊ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የአሜሪካ የፌደራል ስርኣት መፈጠር ዋና ገፊ ምክንያት ናቸው ተብሎው ከሚጠቀሱት ውስጥ የተሻለ ህብረት በመፍጠር ከወቅቱ የአሜሪካ ባላንጣና የቀድሞ ቀኝ ገዥ ታላቋ ብሪታንያ ሊቃጣ ከሚችል ወረራ እረስን ለመካላከል የሚስችል
Posted in Amharic News

የለማ መገርሳ የጠለፋ ፖለቲካ አይሳካም – ስዩም ተሾመ

ኦቦ ለማ መገርሳ የመደመር ፍልስፍናን ሆነ በፓርቲዎች መዋሃድ እንደማይስማሙ ገልፀዋል። የኦዴፓ ምክር ቤት ውህደቱን በሚያፀድቅበት ግዜ በአካል መገኘታቸውን ጭምር ገልፀዋል። በእርግጥ በውህደቱ ሂደት ላይ ይህን ያህል የጎላ ተፅዕኖ አሊያም ግድፈት ይኖራል የሚል እምነት የለኝም። በዚህ ረገድ የሰፋ ክፍተት ቢኖር ኖሮ እንደ ድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር ችግሩን ለመፍታት ጥረት ማድረግ አሊያም ደግሞ በጉዳዩ ላይ ያላቸውን አቋም በይፋ መግለፅ ነበረባቸው። በተመሣሣይ በመደመር ፍልስፍና አለማመን መብታቸው ነው። በኦዴፓ ከፍተኛ አመራሮች መካከል የሃሳብ ልዩነት መኖሩን እንደ ልዩ ክስተት ሊወሰድ አይገባም። ይሁን እንጂ ነገሮች በሂደት አልፈው ጫፍ ላይ ከደረሱ በኋላ “ከመጀመሪያው ጀምሮ አልደግፍም፥ አልስማማም ነበር” ማለት በአጭር ቃል አይነፋም። አሁን ላይ የተቃውሞ ድምፅ ማሰማት ውህደቱን ለማደናቀፍ ካልሆነ በስተቀር መሠረታዊ የሆነ የአቋም ልዩነት መኖሩን አያሳይም። መሠረታዊ የሆነ የአቋም ልዩነት ከነበረ ደግሞ መጀመሪያውኑ አልስማማም ብሎ የራስን መንገድ መከተል ይሻል ነበር። በአለቀ ሰዓት እንዲህ ያለ ነገር ውስጥ መግባት ያው የተለመደ የመጠላለፍ ፖለቲካ ነው። ይሄ ደግሞ ወያኔና ጃዋርን ከማስደሰት በቀር የሚያመጣው ለውጥ ያለ አይመስለኝም። ይሄም ቢሆን የአንድ ሰሞን የጨበራ ተስካር ነው። ዋናው ነገር ውህደቱ እውን ይሆናል። የኢትዮጵያም ሰላምና አንድነት ይረጋገጣል። ሀገርና ህዝብን ዋስትና አስይዞ የፖለቲካ ቁማር መጫወት አብቅቷል።
Posted in Amharic News, Ethiopian Drama

የአማራ ክልላዊ መንግስት በኦሮሞ ሚዲያ ኔትዎርክ ላይ ለብሮድካስት ባለስልጣን ቅሬታ አቀረበ

የአማራ ክልላዊ መንግስት በኦሮሞ ሚዲያ ኔትዎርክ (OMN) በኦሮሚያ ኒውስ ኔትዎርክ (ONN)፣ በትግራይ ቴሌቪዥንና በድምፂ ወያኔ (DW) ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ላይ ለብሮድካስት ባለስልጣን ቅሬታ ማቅረቡ ታውቋል፡፡ ከክልሉ ለቀረበውም ቅሬታ በተለይ ኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ (OMN) በአምስት ቀናት ውስጥ ምላሽና ማብራሪያ እንዲሰጥ ባለሥልጣኑ ጠይቋል፡፡ የአማራ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት መስከረም 29 ቀን 2012 ዓ.ም ለብሮድካስት ባለስልጣን በፃፈው ደብዳቤ፤ የኦሮሚያ ኒውስ ኔትዎርክ (OMN) ከሚዲያ ስነምግባርም ሆነ ከአገሪቱ የብሮድካስት ህግ ውጪ በሆነ አግባብ በአማራ ክልል ህዝብና መንግስት ላይ ጥላቻን የሚቀሰቅስ፣ የእርስ በእርስ እልቂት የሚሰብክና መሬት ላይ ካለው ሃቅ ፈጽሞ የራቁ የተዛቡ መረጃዎችን አሠራጭቷል ሲል ከስሷል፡፡ ድርጊቱ ለመፈፀሙም መስከረም 25 እና 27 ቀን 2012 የተሠራጩ “ሶና ሴና” የተሰኙ ፕሮግራሞችን እንዲሁም መስከረም 21 ቀን 2012 ዓ.ም የተሠራጩ “ዶ/ር ቀዲዳ ሾው” የተሰኘ ፕሮግራምን ቅጂ የክልሉ መንግስት በማስረጃነት ማቅረቡ ተጠቁሟል፡፡ በእነዚህ ቅሬታዎች ላይም የቴሌቪዥን ጣቢያው በአምስት ቀናት ውስጥ በጽሑፍ ምላሽ እንዲሰጥ ብሮድካስት ባለስልጣን አሳስቧል፡፡ በአማራ ክልል መንግስት ቅሬታ የተሰነዘረባቸው አራቱ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች የቀረበባቸውን ቅሬታ የማጣራት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ለአዲስ አድማስ የገለፁት የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ገብረጊዮርጊስ አብርሃ፤ ማጣራቱ ሲጠናቀቅ ጉዳዩ ለመገናኛ ብዙኃን ይፋ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ የአማራ ክልላዊ መንግስት በቅርቡ በጐንደር አካባቢ ተፈጥሮ ከነበረው ችግር ጋር በተያያዘ፣ መገናኛ ብዙሃን ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨት የሚያደርጉትን ጥረት እንዲያቆሙ ማስጠንቀቁ ይታወቃል፡፡ ምንጭ፦ #አዲስ_አድማስ
Posted in Ethiopian News

ለፍትሕ በጋራ እንቁም! ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የቀረበ ጥሪ

ከያሬድ ሃይለማሪያም ባለፉት ሦስት ቀናት በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች እና በአዋሳኝ አካባቢዎች በተቀሰቀሰው ግጭትና አመጽ እስከ አሁን ባለው መረጃ ቁጥራቸው ከሰባ ያላነሰ ሰዎች መገደላቸውን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቀላል እና ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ምሆኑን፣ ብዙዎች መኖሪያ ቤታቸው ተቃጥሎ እና ንብረቶቻቸው የተዘረፈ መሆኑን፤ እንዲሁም የእምነት ተቋማት ላይ እና አማኒያን ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶችም መድረሱን በተለያዩ ሚዲያዎች ሲገለጽ ቆይቷል። በአንዳንድ የኦሮሚያ ክልል ከተሞችም ድርጊቱ አሁንም አለመቆሙን መረጃዎች ያሳያሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ ይህን አመጽ በመቀስቀስም ሆነ በዜጎች ላይ ጥቃት በሰነዘሩ እና ለድርጊቱ ተባባሪ በሆኑ ግለሰቦች፣ ቡድኖች፣ የመንግስት ባለሥልጣናት፣ የማህበራት ወይም የቡድን መሪዎች እና የጸጥታ ዘርፍ አባላት ላይ ክስ ለመመስረት ስለሚቻልበት ሁኔታ አገር ወዳድ በሆኑ የሕግ ባለሙያዎች፣ የመብት ተሟጋቾች እና ሌሎች ልሂቃን ውይይት ተጀምሯል። ይህ ቡድን ዝግጅቱን አጠናቆ እና ጠበቆችን መድቦ ጉዳይ ወደሚመለከተው የፍትሕ አካላት እንዲቀርብ ለሚደረገው ጥረት መረጃ በማቀበል ትተባበሩን ዘንድ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን። + ጥቃቶችን የሚያሳዩ የቪዲዮ፣ የድምጽ እና የፎቶ ማስረጃዎች፣ + የተገደሉ ሰዎች ስም ዝርዝር፣ ዕድሜ፣ የሚኖሩበት ሥፍራ እና ድርጊቱ የተፈጸመበት ሥፍራ፣ ስለድርጊቱ ፈጸሚዎች ማንነት እና የአፈጻጸማቸው ሁኔታ፣ + ድርጊቱ በተፈጸመበት ቦታ የመንግስት አካላት የነበራቸው ሚና፣ + የመንግስት አካላት ጥፋቱን ለማብረድ የወሰዱት በጎ እርምጃዎች ካሉ፣ + የወደሙ ንብረቶች አይነት፣ የዋጋ ግምት፣ ንብረቶቹ የወደሙበት አካባቢ እና በማን እና በምን አይነት ሁኔታ ንብረቶቹ እንደወደሙ፣ + ሌሎችም በጥቃቶቹ ዙሪያ በጃችሁ የሚገኘውን ማስረጃ ወይም መረጃ በፌስ ቡክ
Posted in Ethiopian News

ለጃዋር የተመደቡ ጠባቂዎች እንዲነሱ መንግሥት መወሰኑ እና እሱ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ በፓርላማ ማክሰኞ ጥቅምት 11/2012 ተገኝተው የዓመቱን የአስፈጻሚውን አካል እቅድ እና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት ማብራሪያ ላይ የውጭ ዜግነት እያላቸው ሚዲያ ከፍተው የሚንቀሳቀሱ ምህዳሩን ለማስፋት በሚል በትዕግስት ጉዳዩን ማየት የሚቻለው ለአገር አስጊ እስካልሆነ ድረስ ብቻ መሆኑን መግለጻቸውን ተከትሎ ጃዋር መሐመድ ፈጥኖ ምላሽ ከሰጠ በሁዋላ መንግስት ያቆመለት ጠባቂዎቹ እንዲነሱ መደረጋቸውን የመረጃ ምንጮች ይገልጻሉ።ጃዋር ጠባቂዎቹ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ የተጠየቀው ከመንግስት ወገን መሆኑን የአንድ ጠባቂውን እና ትዕዛዝ ያስተላለፉ ኮሚሽነር የስልክ ልውውጥ ይፋ አድርጎ አሰምቷል። VIDEO ማምሻውን ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ጃዋር የሚከተለውን መልእክት ፌስቡኩ ላይ አስፍሯል፦ “ጉዳዩ ለሚመለከተው ሁሉ፡- በመኖሪያዬ አካባቢ በቁጥር በርካታ ታጣቂ እየተሰማራ እንደኾነ እያስተዋልን ነው፡፡ ይኸ የታጠቀ ኋይል ከሕግ አግባብ ውጪ ከሚያደርገው እንቅስቃሴ ተቆጥቦ ወደኋላ እንዲመለስ በአጽንኦት እንጠይቀለን። ማንኛውም ታጥቆ በዚህ ጭለማ ወደ መኖሪያ ግቢያችን ለጥቃት የሚንቀሳቀስ ግለሰብም ኾነ ቡድን ላይ የጥበቃ አካሉ ሕጋዊ መብቱን ተጠቅሞ የመከላከል እርምጃ እንደሚወስድ ሊታወቅ ይገባል። ይኸን ከሕግ አግባብ ውጪ የሚደረግን እንቅስቃሴ ለመከላከል በሚደርሰው ግጭት እና ጉዳት ሙሉ ኋላፊነቱን የሚወስደው ያለምንም ተጨባጭ ምክንያት እና ማሳሰቢያ ኋይል ያሰማራው አካል መሆኑን ሕዝቡ እንዲያውቅልን እንጠይቃለን።” ትዕዛዙ ከመንግስት መጥቱዋል ወይም የጃዋርን ምላሽ ተከትሎ በጸጥታ ውስጥ የሚሰሩ ባለስልጣናት ያስተላለፉት ትዕዛዝ ነው የሚለውን ከገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ አልተቻለም። ጃዋር ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ማስጠንቀቂያ በቀጥታ ለራሱ ወስዶ በሰጠው እኛም አውቀናል ጉድጉዋድ ምሰናል አለች አይጥ ከዚህ በሁዋላ ኑራችንም ሞታችንም ኦሮሚያ ውስጥ ነው የሚል
Posted in Amharic News

እያነጋገረ ያለው የከንቲባ ታከለ ኡማ ከሃላፊነት የመነሳት ዜና

ኤልያስ መሰረት እንደዘገበው የአ/አ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ ከቦታቸው ሊነሱ እንደሆነ በአንዳንድ ሰዎች ዛሬ ሲገለፅ ነበር። ይህ መረጃ ትክክል እንደሆነ እና ም/ከንቲባው ከሳምንት በላይ ስልጣናቸው ላይ እንደማይቆዩ ታማኝ ምንጮች ማምሻውን አሳውቀውኛል። ምንጭ 1: “ም/ከንቲባው ስራቸውን ለመቀጠል ፍላጎት ነበራቸው። ነገር ግን ስራቸው ላይ እንደማይቆዩ ላረጋግጥልህ እችላለሁ፣ ምናልባት ከዚህ በሁዋላ አንድ ሳምንት ቢቆዩ ነው። ለምን ሊነሱ እንደተፈለገ ግን ግልፅ አይደለም፣ ምናልባት የፓርቲያቸው ውሳኔ ሊሆን ይችላል።” ምንጭ 2: “መረጃው ትክክል ነው። አሁን ባለው ጭምጭምታ የገቢዎች ሚኒስትር ሀላፊዋ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ኢ/ር ታከለን ይተካሉ ተብሎ ተገምቷል።” በዚህ ላይ ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰኝ አቀርባለሁ! ኤልያብ ጌታቸው እንደዘገበው መደበኛ ባልሆነ መንገድ እየተገለጸ ያለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ እያገለገሉ ያሉት ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከሃላፊነት የመነሳት ዜና የተለያየ ስሜት ፈጥሮ እያነጋገረ ይገኛል። ኢንጂነሩ ለምን ከሃላፊነታቸው እንደሚነሱ በግልጽ የተነገረ ነገር ባይኖርም ሁኔታውን ጥቅምት 2 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተጠርቶ ከነበረው የባልደራሱ የተቃውሞ ሰልፍ እና ሰልፉን ለማቀብ ከተደረገው እንቅስቃሴ ጋር በማዛመድ የጠ/ሚ/ር ዓብይ አሕመድ ካቢኔ እርምጃ አድርገው የሚወስዱት ወገኖች ብዙ ናቸው። ውሳኔው እውን የሚሆን ከሆነም ከንቲባውን ከሚደግፉትና ከሚቃወሙት ወገኖች የተለያዩ ስሜቶች ሊንጸባረቁ እንደሚችሉ በጉዳዩ ዙርያ ያነጋገርናቸው አካላት የተጠቃለለ ሃሳብ ያመለክታል። በተቃዋሚዎቻቸው በኩል ምክትል ከንቲባው ከተሾሙበት ጊዜ አንስቶ ሕጋዊ አይደሉም በሚል ሲቃወሟቸው የቆዩ በመሆኑ ዜናውን በመልካም ጎኑ የወሰዱት ሲሆን የትኩረታቸው አቅጣጫ በቀጣዩ ከንቲባ ማንነት ላይ ያተኮረ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ላመነችበት የዋተተች ሕይወት – ታዲዮስ ታንቱ

ዋለልኝ አየለ፣ አዲስ ዘመን ጋዜጠኝነትን እንደነፍሳቸው ይወዱታል። ከ30ዓመታት በላይ ኖረውበታል። በመምህርነት አገልግለዋል። በፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ረጅም ጊዜ አሳልፈዋል፡፡ በታጠቅ፣ ኢትዮጲስ፣ ፍትሕ… ጋዜጦች ላይ ይጽፉ ነበር፡፡ በሚጽፏቸውና በሚያደርጉት ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በርካታ ውጣ ውረድ አጋጥሟቸዋል፡፡ በእስር ቤት ስቃይና እንግልት ደርሶባቸዋል፡፡ የዛሬ የ ‹‹ሕይወት እንዲህ ናት›› እንግዳችን ጋዜጠኛ ታዲዮስ ታንቱ ይባላሉ። በ1944ዓ.ም በቀድሞው ሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት በወላይታ አውራጃ በዳሞት ወይደ ወረዳ ግራራ ሚካኤል በሚባል አካባቢ ነው ተወልደው ያደጉት። የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የተማሩት ሻሸመኔ አጼ ናኦድ ትምህርት ቤት ሲሆን፤ ከዚያም ወደ ናዝሬት በመሄድ በአጼ ገላውዲዎስ መርሐ ሙያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተምረዋል፡፡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በውጭ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍ ተመርቀዋል፡፡ ከዚያም በእንግሊዝኛ ቋንቋ፣ አማርኛ ቋንቋና በታሪክ መምህርነት አገልግለዋል፡፡ ከእርሳቸው ጋር የነበረንን ቆይታ እነሆ! አዲስ ዘመን፡- ከመምህርነት ሙያ ወጥተው በምን ሙያ ላይ ተሰማሩ? ታዲዮስ፡- ከመምህርነት በኋላ በጦር ኃይሎች ዋና ፖለቲካ አስተዳደር በጋዜጠኝነት ተቀጥሬ በታጠቅ ጋዜጣ ላይ መሥራት ጀመርኩ፡፡ የታጠቅ ጋዜጣ ርዕሰ አንቀጽ ጸሐፊም እኔ ነበርኩ፡፡ ከዚያ በኋላም በልዩ ልዩ ጋዜጦች ላይ ሰርቻለሁ፡፡ እምቢ በይ ሀገሬ፣ አስኳል፣ ሜዲካል፣ ጦቢያ፣ ፍትሕ፣ አዲስ ታይምስ፣ ልዕልና፣ ፋክት፣ ኢትዮ ምህዳር፣ ነገረ ኢትዮጵያ እና የቀለም ቀንድ ላይ ሰርቻለሁ፡፡ አዲስ ዘመን፡- እነዚህ ሁሉ ጋዜጦች ላይ ሲሰሩ በአምደኝነት ብቻ ነው ወይስ ባለቤት የሆኑባቸው አሉ? ታዲዮስ፡- አንድም ጋዜጣ ላይ ባለቤት ሆኜ አላውቅም፡፡ አቅሜም ለዚህ የሚፈቅድ አልነበረም፡፡ ግን በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ታሪክ ውስጥ በቋሚ ዓምደኝነት የሰራሁ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በጄኔራል አሳምነው ፅጌ የተመራ ክልላዊ የመፈንቅለ-መንግሥት ሙከራ መደረጉን የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አስታወቀ (DW)

በብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ፅጌ የተመራ ክልላዊ የመፈንቅለ-መንግሥት ሙከራ መደረጉን የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) አስታወቀ። የመፈንቅለ-መንግሥት ሙከራው መክሸፉን የክልሉ ገዢ ፓርቲ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአማራ ቴሌቭዥን ጣቢያ በሰጠው መግለጫ ማሳወቁን ጀርመን ራዲዮ (DW) ዘገበ። በተጨማሪም፣ በባህር ዳር የሚገኘው ጀርመን ራዲዮ ጋዜጠኛ የሚከተለውን ዘግቧል። የፌደራል የጸጥታ አስከባሪ ኃይሎች የመፈንቅለ-መንግሥት ሙከራ በተደረገባት የባሕር ዳር ከተማ ተሰማሩ። የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት መኮድ ተብሎ ከሚጠራው የጦር ሰፈር ወደ ከተማዋ የዘለቁ ወታደሮች የጸጥታ ቁጥጥር እያደረጉ ናቸው። ከመንፈቅለ መንግሥት ሙከራው ጋር በተያያዘ የክልሉ መንግሥት መቀመጫ በሆነችው ባሕር ዳር ከምሽቱ 12 ከ30 ጀምሮ ቢያንስ ለግማሽ ሰዓት የዘለቀ የተኩስ ድምጽ ሲሰማ እንደነበር የአይን እማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። የከተማዋ ነሪዎች እንደሚሉት የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የክልሉ ምክር ቤት እና የርዕሰ-መስተዳድሩ ፅህፈት ቤት በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተኩስ ድምፅ ተሰምቷል። አንድ የከተማዋ ነዋሪ “ተኩስ የጀመረው ፖሊስ ኮሚሽን አካባቢ ነው” ሲሉ ተናግረዋል። ከፖሊስ ኮሚሽን ፅህፈት ቤት አቅራቢያ የነበሩት እኚሁ የዐይን እማኝ “የቀላል እና የከባድ መሳሪያ ተኩስ” መስማታቸውን ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። በክልሉ ልዩ ኃይል አዲስ እና ነባር አባላት መካከል ቀደም ሲል ግርግር እንደነበር መስማታቸውንም ገልጸዋል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መስሎ መኖር ከእራስ እውነታ ጋር ሲጣረስ – ፀጋ ወርቅ

ከፀጋ ወርቅ ይህንን ጽሁፍ ስናነብ ውሕድ ማንነታቸውን በአግባቡ ተቀብለውት ለዘመናት በአብሮነት ሃገራቸውን የመሩ ፣ ለሃገራቸው ህልውናና ፍቅር እራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ እና እኛን የወለዱ የምንኮራባቸው ጀግኖች ቀደምቶቻችንን ሁል ግዜ ክብራቸው ክብራችን ጉድለታቸው ጉድለታችን ብለን ተቀብለን መሆኑ እንዳይዘነጋ። መስሎ መኖር ከእራስ እውነታ ጋር ሲጣረስ ሊያመጣ የሚችለው ውጤት ምን እንደሚሆን ገምተውት ያውቃሉ? ሰዎች በውሕድነታችው ምክንያት ሊወያዩባቸው የሚችሉት ጉዳዮች በርካታ ቢሆኑም ዛሬ ጥቂቶቹን በግርድፍ ልናይ መርጠናል። ባለፈው ውይይታችን ላይ ውሕድ ኢትዮጵያዊ ከኢትዮጵያዊነት ውጭ ማንነት የለውም ከተባለ ኢትዮጵያዊነት ብቻ ላይ መወያየት ሲቻል በተናጠል ውሕዶችን ብቻ የሚመለከት ውይይት ለምን አስፈለገ የሚል ሃሳብ ተነስቶ ነበር። የውይይቱ መድረክ አስፈላጊነት ውሕድነት የራሱ የሆነ ስብእና ስላለው በጋራ የሚጋራው የማንነት ጥያቄዎች እና በተለይም በዘር እና ቋንቋ ተኮር ብድኖች ስብስቦች እና አስተዳደሮች የተደፈጠጠና ፍጹም ቦታ ያልተሰጠው በመሆኑ ምክንያት የሚፈጠሩ መብት ነክና ስነልቦናዊ ችግሮችን በጋራ ለመወያየት እና መፍትሔም ለመፈለግ ስለሚረዳ ነው ። የሰዎች የማንነት ጥያቄ ከግል ህይወት ጀምሮ እስከ ሃገር ግንባታ ድረስ ትልቅ ሚና ስላለው ውሕድነት ሊፈተሽ ሊመረመር እና በሰፊው ሊሰራበት ይገባል ወደሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰናል። በተለይም ቋንቋና ዘር ተኮር ክልል እና አስተዳደር ባለበት ሃገር ላይ ውሕዶች ምን ቦታ እንዳላቸው መነጋገር የምርጫ ጉዳይም ሳይሆን የህልውናም ጉዳይ ጭምር ነው። የተወሰነውን ሕብረተሰብ ማንነት የሚያከብር ሥርዓት ለመመሥረት በሚል ሰበብ የተቀረውን ሕብረተሰብ ማንነት መደፍጠጥ ፍትሐዊ ሊሆን አይችልም። እነዚህ ውይይቶች ግን አንድ ወጥ ማንነት ያላቸውን ወይም አለን ብለው
Posted in Amharic News

ኦዴፓን ከሞት ያነሳሁት እና ስሙን ያደስኩለት እኔ ነኝ። ከእኔ ጋር (ኦዴፓ) እንዲህ ዓይነት ሳፋጣ ቢያቆሙ ይሻላቸዋል። – ጃዋር መሃመድ

ከደረጀ ሃብተወልድ ለምን እውነቱን አወጣብኝ ብሎ ኢሳትን የከሠሰው ኦዴፓ እንደሚከተለው በOMN ኃላፊ በተራው ተከሷል፣ ማስጠንቀቂያም ተሰጥቶታል:- “ትናንት ምሽት የጃዋርን OMN ቲቪ ስመለከት አቶ ጃዋር ቃለ ምልልስ እየሰጠ ነበር:: ውይይቱ የተካሄደው በኦሮምኛ ቋንቋ ሲሆን ዋንኛው ማጠንጠኛው “ኦዴፓ” እና ወቅታዊ “መግለጫው” ነበር:: ቃለመጠይቅ አቅራቢው አቶ ተስፋዬ:- “ኦዴፓ በፓርቲዬ እና ኦሮሞ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶብናል” ያለው አንተን አፍህን ለማዘጋት ነው እያሉ ነው:: አንተ ምን ትላለህ?” ሲል ጃዋርን ጠይቆታል:: ጃዋር እንዲህ ሲል መልሷል:- – ኦዴፓን ከሞት ያነሳሁት እና ስሙን ያደስኩለት እኔ ነኝ:: ከእኔ ጋር (ኦዴፓ) እንዲህ ዓይነት ሳፋጣ ቢያቆሙ ይሻላቸዋል:: – ኦዴፓን እያዳከሙ ያሉት በውስጡ የተሰገሰጉ የድሮው ኦህዴድ ሌቦች ናቸው!! – ገላን ላይ 500 ሄክታር መሬት የሸጡ ሌቦች እሁንም ኦዴፓ ውስጥ በሥልጣን ላይ አሉ:: – ሰበታ ላይ በሌለ ድርጅት ስም 40 ሄክታር መሬት የሸጡ ሌቦች አሁንም በኦዴፓ ሥልጣን ላይ ናቸው:: – ወለጋ ላይ ኦነግ ባንኮችን ሲዘርፍ አብረው ያዘረፉ እና የተካፈሉ ኦዴፓ ውስጥ ያሉ ባለሥልጣናት አሉ:: – ወለጋ ላይ የኦነግ ወታደሮች ትጥቅ ፈትተው ካምፕ እንዳይገቡ የሚያደርጉት የኦዴፓ ሰዎች ናቸው:: ምክንያቱም ባንክ ዘርፈው መካፈላቸውን ምስጢር እንዳያወጡባቸው ነው:: – ታከለ ላይ የሚነዛው ጥላቻ ምንጩ ከኦዴፓ ከእራሱ ውስጥ ካሉ ሌቦች ነው:: – የለማ እና የዐብይ ሥርዓት እየፈራረሰ ነው:: – የኦሮሚያ መንግሥት በሙሰኞች እና በሌቦች ሽባ (paralyzed) ሆኗል:: ይህን ያለው የኢሳት ዳይሬክተር ቢኾን ኖሮ …. ብላችሁ አስቡት። ለትርጉሙ
Posted in Ethiopian News

ለአታላይ ስለማያመቹት የኢትዮጵያ ወሰን ፈጣሪ ወንዞችና ስለክልል የለሹ አማርኛ ተናጋሪ ጥቂት ነጥቦች – ኤፍሬም የማነብርሐን

ከኤፍሬም የማነብርሐን (J.S.D.) ባለፉት 27 ዓመታት፣ ማለትም ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረበት 1983 ዓመት ምህረት ጀምሮ፣ ወያኔ ኢትዮጵያን በትግራይ የበላይነት ቢያንስ ለመቶ ዓመታት ለመምራት የሚያስችለውን የወሰን አከላለልና የሕዝቦቿን የዜግነት መብት ለራሱ በሚያመቸው አኳኅን ብዛት ያለው ሕዝብ ያለተወከለበትን ሕገመንግስት ነድፎ፣ በሕዝቦቿ ላይ ከፍተኛ ሰቆቃ በመፈጸም ይህንን የክፋትና የጥፋት ዓላማ ለመተግበር ላይ ታች ሲል ከረመ። ለዚህም ዓላማ መሳካት የመጀመሪያ ዋና ኢላማ ያደረገው አገሪቱ በመጀመሪያ የተቋቋመችባቸው በዋና መሰረት በመልከዓ ምድራዊ የወንዞችን አወራርድ፣ የሕዝብን ባሕልና፣ የሕዝብን ስነልቦናዊ መስፈርቶችን ባላገናዘብ መልኩ፤ የራሱን ተስፋፊነትና፣ አማራና አማርኛ ተናጋሪውን ሕብረተሰብ በሚጎዳ አኳኃን አስልቶ፣ በማንኛውም መስፈርት ተአማኒነት በሌለው በፖለቲካ ውሳኔ ላይ የተመሠረተ የአገር ውስጥ ወሰን አከላልን በጉልበት ላለፉት 27 ዓመታት ሲተገብርና ሲያስተገብር መክረሙ ገሃድ ሐቅ ነው። በተለይ ከጥንት ጀምሮ ኢትዮጵያን ከኛ ሌላ ማነም ሊገዛት አይገባም፣ ከአጼ ዮሐንስ አጼ ሚኒሊክ ስለነጠቁን ነው እንጂ የሚለውን በሐሰት ላይ የተመሠረተ ትርክት ለረጅም ዓመታት ሲያብላላ የሰነበተው የትግራይ ጽንፈኛ ኤሊት፣ ዕድልና በለስ ቀንቶት በሸዋ የሚኒሊክን ግቢ ሲቆጣጠር፣ የሌት ተቅን ስሌቱ ይሕንን የረጅም ዓመታት የትግራይ ኤሊትን ምኞት እንዴት እንደሚተግብረው ነበር። የወያኔ መሠረታዊ ችግሩ፣ “ከኔ በላይ ብልጥ ላሳር” እንዳለው የሰፈር አውደልዳይ ሞኝ ሁሉ ነገር በገሃድ የሚታይበት መሆኑን አለመገንዘቡ ወይም “የት ይደርሳል ተወው” የሚል አባዜ ውስጥ ሁሌም የተነከረ መሆኑ ነው። በአማራው ላይ ከበባ እያደረግበት መሰንበቱ ደጋግሞ የተነገር ቢሆንም፣ የዚህ ሴራ ጥልቀት ግን በቅርቡ የቤኒሻንጉሉ የቀድሞ ባለሥልጣን “ወልቃይትም እኮ የቤኒ ሻንጉል ክልል
Posted in Ethiopian News

ማለቂያ ቢስ የሚመስለውን የህወአት ግፍ ለፍፃሜ ያበቃው ሚስጥር ኦሮማራ ነው

ማለቂያ ቢስ የሚመስለውን የህወአት ግፍ ለፍፃሜ ያበቃው ሚስጥር ኦሮማራ ነው፡፡ ለማና ደመቀ መከሩ፡፡ አብይና ገዱ ዘከሩ፡፡ ህዝቦቻችንን እያናከሱ ለዘላለም እንዳይገዙን አሁን መንቃት አለብን አሉ፡፡ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ተማከሩ፡፡ ኦሮማራ እውን ሆነ፡፡ ኦሮማራ ባይኖር አንዳርጋቸው እስር ቤት ነበር፡፡ ኦሮማራ ባይኖር በቀለ ገርባ ቃሊቲ ነበር፡፡ ኦሮማራ ባይኖር የኦሮሞና የአማራ ልጆች በማዕከላዊ ዕቶን እየተቀቀሉ ነበር፡፡ የህወአት ሴረኞች ሸራተን በእምባና በደም በተጠመቀ ውስኪ እየተራጩ ነበር፡፡ ኦሮማራ ሲጠነክር ኦሮሞና አማራ ይጠነክራሉ፤ ኢትዮጵያ ትጠነክራለች፡፡ ኦሮማራ ሲደክም ኦሮሞና አማራ ይደክማሉ፤ ኢትዮጵያ ትደክማለች፡፡ ህወአት ኦሮሞና አማራን 27 ዓመት የተጫወችባቸው እርስበርሳቸው እንዲናከሱ አጀንዳ እየሰጠቻቸው ነው፡፡ ሁለቱ ሲናከሱ ነው ህወአት ፋታ የምታገኘው፡፡ ሁለቱ ሲዝሉ ነው ህወአት የምትጠነክረው፡፡ ኦሮማራ እንዲደክም ህወአት ዲጅታል ወያኔ የተባለ የፌስቡክ ሰራዊት አደራጅታ መጥታለች፡፡ ትናንት በምድር ጦርነት ስልጣን ጨብጠዋል፤ ዛሬ ደግሞ በሳይበር ጦርነት ስልጣን ለመጨበጥ እያሴሩ ነው፡፡ ኦሮማራ ሲደክም ወያኔ ትጠነክራለች፡፡ ይህን ሃቅ ለቅፅበት እንኳን ከዘነጋን ሞታችን ቅርብ ነው፡፡ ህወአት ኦሮማራን ለማዳከም የ27 ዓመት ልምዷን አሁንም እየተጠቀመችበት ነው፡፡ ኦሮማራ ይለምልም!
Posted in Amharic News, Ethiopian News

እኛ አብይን የደገፍነው እንደልባችን መናገር፣ መቃወም፣ መተቸት ስላስቻለን ነው – ሩታ አለሙ

ሩታ አለሙ በለገጣፎ ጉዳይ ዶ/ር አብይ ተቃውሞ ገጠመው ብለው የሚፈነጩ የህወሃት አክቲቪስቶችን እዛም እዚህም እያየን ነው! እኛኮ አብይን የደገፍነው… በሀብት ላይ ሀብት ስለደረበልን አይደለም… ከህወሃት ዘመን በተለየ በቀን ሶስቴ ጠግበን መብላት ጀምረን አይደለም… መንገድና ህንፃ በመገንባትማ መለስ ተወቅሶበት አያውቅም። እኛ አብይን የደገፍነው እንደልባችን መናገር፣ መቃወም፣ መተቸት ስላስቻለን ነው! ለውጥማ ድብን አድርጎ አለ!! በፊትም ወጣት በጅምላ ይታፈስ ነበር። አሁንም ሲታፈስ አይተናል… ቢያንስ ግን ለምን ታፈሱ ብለን ኡኡ ብሎ የመጮህ መብት አለን ዛሬ። የህዝብን ጩኸት ፈርቶ እርምጃውን የሚያርም፣ የታሰሩት የሚፈታ መሪ አግኝተናል። በፊትም የዜጎችን ቤት አፍርሶ ጎዳና የሚጥል መንግስት ነበረን። አሁንም ነገሩ ሲደገም እያየን ነው። ነገር ግን ዛሬ ለምን ቤት ፈረሰ ብለን በመፃፋችን እስርና እንግልት ይደርስብናል ብለን አንፈራም። ተዘቅዝቀን አንገረፍም። ብልታችን ላይ ኮዳ አይንጠለጠልም! በፊትም መንግስትን ተቃውሞ ህዝብ ሰልፍ ይወጣ ነበር። ዘንድሮም እንደዛው። ዘንድሮ ግን ባዶ እጁን ሰልፍ የወጣ ህዝብ ላይ ጥይት አይተኮስም። በፖለቲካ አቋሙ ምክኒያት ህዝብ በሽብርተኝነት አይፈረጅም። ብሄር ከብሄር እያጣላ ዘመኑን የሚያረዝም ተንከሲስ መንግስት የለንም። ቢያንስ ቦታው ላይ ያሉ ሰዎች ሀገራቸውን ይወዳሉ። ሀላፊነት ይሰማቸዋል። በፊትም ምርጫ ነበረን፤ ዘንድሮም ይኖረናል! መቶ ፐርሰንት የሚመረጥ መንግስት እንደማይኖረን ግን እርግጠኞች ነን። አንጭበረበርም። አንታለልም። አብይን የደገፍነው እንደልቡ እንድንቃወመው ስለፈቀደልን ነው። ሲያጠፋ እንወቅሳለን። ሲያለማ እናመሰግናለን። ጥፋቱ ከልማቱ ከበለጠብን በምርጫ በክብር እናወርደዋለን። ይሄንን ማድረጉ በራሱ በታሪክ መዝገብ ላይ ስሙን አድምቀን እንድንከትበው ያደርገናል! ቅር ስንሰኝ መንግስትን መቃወም ወላዋይነት
Posted in Amharic News, Ethiopian Drama

ከተማ የሚገነባው የግድ ሰፈርን በማፍረስና ሕዝብን ለጎዳና በመዳረግ አይደለም – መላኩ አላምረው

ከመላኩ አላምረው – የግል አስተያየት እንደዚህ አይደለም! ሕግ ይከበር፤ ነገር ግን ሕግ የሚከበረው ሰዎችን በተለይም አቅመ ደካሞችን በማዋረድ አይደለም፡፡ የሕግ የበላይነት ይረጋገጥ፤ ነገር ግን የሕግ የበላይነት የሚረጋገጠው የሰውን ልጅ ተፈጥሯዊ መብት በመረጋገጥ አይደለም፡፡ ከተሞች ተውበው ይገንቡ፤ ነገር ግን ከተማ የሚገነባው የግድ ሰፈርን በማፍረስና ሕዝብን ለጎዳና በመዳረግ አይደለም፡፡ በሥርዓት እንመራ፤ ነገር ግን ዘመናዊ ሥርዓትን የምናሰፍነው እዚህ ያደረሰንን ማኅበረሰባዊ ትውፊት በመናቅና በመጣል አይደለም፡፡ ሀገር የምናሳድገው ሕዝብን በማማረርና በማስለቀስ አይደለም፡፡ የተበላሸ ሥርዓት የተጣሰም ሕግ ቢኖር እንኳን መሰተካከል የሚችለው በአግባብና በሥርዓት ቀስ በቀስ እንጅ ንቀትና ትዕቢትን ባስቀደመ ማናለብኝት አይደለም፡፡ ልዩነቶች በበዙባት ሀገር ውስጥ መግባባት የሚፈጠረው ልዩ ጥንቃቄ በተሞላበትና ቅንነት በታከለበት ሰዋዊና የሰከነ አካሄድ እንጅ በስሜት በሚመራና ለሰዎች በማይራራ የጭካኔ እርምጃ አይደለም፡፡ ሀገርን መምራትም ሆነ መገንባት የምንችለው ሁሉንም በእኩል ዓይን በመመልከት እና ፍትሕና ርትዕን በማስፈን እንጅ በራስ ወዳድነት፣ ለይቶ በማቀፍና ለይቶ በማግለል፣ በአድሏዊነት አይደለም፡፡ በታሪክ አጋጣሚ አንድንመራት ዕድል እጃችን ላይ የጣላትን ሀገር ወደተሻለ ከፍታ የምናሸጋግራት ሕዝቦቿን በእኩልነት እጆቻችን በፍቅር አቅፈን፣ የተጣሉትን አስታቀን፣ የተራራቁትን አቀራርበን፣ ስጋትን እያስወገደን ተስፋን በማለምለም እንጅ የተለመደን ጥላቻና በቀል እየሰበክን፣ በመካከላቸው ልዩነትን እያሰፋን፣ አንዱን አቅፈን ሌላውን እየገፋን፣ ለአንዱ አለኝታ ለለላው በሽታ እየሆንን…. ከችግር ወደ ችግር፣ ከአንዱ አዙሪት ወደ ሌላኛው አዙሪት በማሽከርከር አይደለም፡፡ እንደዚህም አይደለም! የሕዝብ ጠበቆች፣ የማኅበረሰብ አንቂዎች፣ የሥርዓት መሪዎች ነን የምንል ሁሉ ሕዝቡን ልንጠቅም የምንችለው የሕዝቡን ፍላጎት በትክክል ስንረዳና በዚሁ መሠረት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የለገጣፎ – ለገዳዲ ሕገወጥ ቤቶች መፍረስ የሚታወቁ ሐቆች – መንግስቱ አሰፋ

የለገጣፎ – ለገዳዲ ሕገወጥ ቤቶች መፍረስ ብዙ እያነጋገር ይገኛል። ጉዳዩን በሕግ እና ፍትሕ ዓይን ከማይታችን በፊት ስለቤቶች እስኪ የሚታወቁ ሐቆችን እናስቀምጥ። ~ቤቶቹ ገበሬዎች ተታለው በካድሬ በትንሽ ብር ከተገዙ በኋላ በደላሎች እና ኦሕዴድ (ኦዲፒ) ካድሬዎች ለነዚህ ቤት የሚፈስርባቸው ባላቤቶች በተቸበቸቡ መሬት ላይ የተገነቡ ናቸው። ከ1990ዎቹ ጀምሮ ማለት ነው። አንዳንዶቹ ከተማ አስተዳድሩ ከመቋቋሙ (1998ዓ.ም.) በፊት ነበሩ። ሕጋዊ የመሬት ባለቤትነት ካርታ ባይኖራቸውም የመብራት እና የዉሃ ውጪ አንዳንዶቹም ግብር ሁላ እየከፈሉ ነበር። መንግሥትም ለነዚህ ቦታዎች ካሳ መክፈሉን ይናገራል። ~ከጥቂት ወራት በፊት የኦሮሚያ ክልል መሬት አስተዳደር ቢሮ በፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ባደረገው ጥናት ከ 12000 በላይ ሕገ ወጥ ቤቶች መኖራቸውን እና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቆ ነበር። የዚያ አካል የሆነው ነገር ነው እንግዲህ አሁን ቤቶቹን እንዲፈርሱ የማድረግ ሥራ እየሠራ ያለው። ~ቤቶቹን ማፍረስ ምናልባት ሕጋዊ መሠረት ሊኖረው ይችላል። ሕገወጥ ከሆነ ሕገወጥ ነው። ግን ፍትሓዊ ነው ወይ? ከጥቅሙ ጉዳቱ አያመዝንም ወይ? ሕግ በማስከበር የሚከሰተው ማኅበራዊ ቀውስ ከ collateral damage ገዝፎ የችግር መንስዔ አይሆንም ወይ? ፖለቲካውን አያጦዘውም ወይ? ሕፃናት እና ሴቶች፣ አቅመደካሞች፣ እርጉዝ እና አራስ እናቶች ፣ አዛውንት ውና መበላቶች ጎዳና ተዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግ አይሆንም ወይ ብለን ስንጠይቅ የሕግ የበላይነት ማስከበር ሳይሆን በራሱ ዞሮ ትልቅ ችግር ይሆናል። ይህንን ችግር የፈጸሙ ካድሬዎች ዛሬ ወይ የትም አይገኙም ወይ እቅፋችሁ ውስጥ “የለውጥ አመራር” ሆኖ ሸገር ከትመዋል። እነሱ ላይ የኽ የሕግ ዱላ እንደማያርፍ
Posted in Amharic News, Ethiopian Drama

በእንተ ለገ ጣፎ ወለኩላ ኢትዮጵያ – አምሃ ልዑልሰገድ

ከአምሃ ልዑልሰገድ መማር ማወቅ መጠየቅ መረዳትና መመርመር ለባለጌ እንዳልተሰጡ በግልጥ ያሳየን የትናንቱ ገቢረ ጣፎ ነው። በቀዬአችን ተክለው ያሳደጉትን ዛፍ ለሥራ ፈልገው ሊቆርጡ የወጡ ገበሬዎች ብዙ የወፍ ጎጆ ከተመለከቱበት ሳይቆርጡ ያልፉታል። የዛፉ መቆረጥ ግድ ቢሆን እንኳ ለሥራ በማይውል ጠማማ ወይም ለመቆረጥ ወዳልተመረጠ ዛፍ የወፎቹን ጎጆ አዘዋውረው ይቆርጡታል። ልማት በሰው ለሰው የሚከወን ካልሆነ ምን ፋይዳ አለው? እንኳን ለሰው ለፍጥረት ሁሉ ተስማሚ ባልሆነ ሁኔታ ውስጥ የተሰራው የእስከዛሬው ልማት ለምን አላስተማረንም? አዲስ አበባ እኮ ከማዘጋጃው ፈጥኖ ጥንቧን የሚያነሳላት የዱር አውሬ ነበር እንደ ዛሬው የብሎኬት ደን ሳይከባት በፊት። ስለዚህ ልማታችን ለፍጥረት ሁሉ ተስማሚ ካልሆነ ልማት ሳይሆን ጥፋት ነው። እሱ ነው ሕገ ወጥነት። ይሔንን አሰራራችንን ነው በሐሳብ ዶዘር ማፍረስ ያለብን። እንጂማ ሰውን እያፈረስን ለማነው የምንገነባው? ሕገ ወጥ ማለት ምን ማለት ነው? ማነው ማንን ሕግ አክባሪ እና ሕግ አስከባሪ የሚለው? ስለ ሕግና ሕጋዊነት ምንም የማያውቁ ከአስተዳደጋቸው ጀምረው ጋጠወጦችና ነጣቂዎች ሆነው በንፍገትና በስግብግብነት ያደጉ ጥቂቶች በሕዝብ ውክልና ለኃላፊነት ሳይሆን በብልግና ልኬት የተሾሙ ጠማሞች ብዙሃኑን ሲያስለቅሱ ሲገድሉ ዝም የሚል ሰው አይኑር። በሃይማኖትም፣ በመንግስትም ይሁን ሰው በመሆን ሥልጣን የምንገኝ ከግፉአን ጋር ብንገፋ የሚሻለውን እናገኛለን። “ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል” እንዲሉ ለግፈኞች ያላቸው አጭር ጊዜ ስለሆነ በዚህ ግፋቸው እንዲቀጥሉ እድል አንስጥ። ከትናንት መማር ያልሆነለት የሐገሬ ሰው ዛሬም ትናንትን እየደገመ ነገ ላለመኖር በመሥራት ተጠምዷል። ሕሊና አለን የምትሉ ባለሥልጣናት የየትኛውም እምነት መሪዎች እባካችሁ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የህወሃት ከፍተኛ አመራር ዛዲግ አብርሃ ለህወሓት ያስገቡት የስንብት ደብዳቤ

ለ – ህወሐት ልዩ ዞን ጽ/ቤት አዲስ አበባ ላለፉት አመታት በህውሃት ድርጅት ስር ተደራጅቼ እንቅስቃሴ ሳደርግ እንደቆየሁ ይታወቃል፡፡ ምንም እንኳን ከዚህ ቀደም በፖለቲካው መስክ የመሳተፍ ፍላጎቱ ያልነበረኝ ቢሆንም በታሪክ አጋጣሚ የአገራችንን ፖለቲካ የመቀላቀል እድሉን አግኝቻለሁ፡፡ በተፈጠረው አጋጣሚም ስለሃገሬ የፖለቲካ ምንነት እና በፖለቲካ ገበያው ውስጥ ተሳታፊ የሆኑ ግለሰቦችንና ተቋማትን በቅርበት የማውቅና የመሳተፍ እድሉ ገጥሞኛል፡፡ በዛው ልክ ደግሞ በህወሀት ውስጥ አደርግ በነበረው ትሳትፎ በር የመዝጋት የመጠራጠርና እንደ ባዳ የመታየት ስሜት ከላይ እስከ ታች ድረስ አጋጥሞኛል፡፡ ገና ከጅምሩ ትግሉ ድርብ ድርብርብ ነበር ፡፡ በአንድ በኩል የመጣሁበት አካባቢ በክልሉ ፓለቲካ ውስጥ በዳርነት የሚመደብ ነውና አጠቃላይ ጉዞው እጅግ አቸጋሪ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ድርጅቱ ወጣቶችን የመጠራጠርና ያለማመን ከፍተኛ ችግር የተንሰራፋበት ነውና እኔም እንደማንኛውም ወጣት ጉዞየ በሳንካ የተሞላ እንዲሆን አድርጎብኛል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአንድ ሙቀጫ መውቀጥ ጥሩ አይደለምና በህይወቴ ነገሮችን በተለየ መልኩ እንዳይ ያደረጉኝ እንዲሁም ትምህርት የሰጡኝ ጥቂት ሰዎች ነበሩና በነሱ ድጋፍና ምክር በችግርም ውስጥ ቢሆን እስካሁን ድረስ ለመዝለቅ ችያለሁ፡፡ በእርግጥም! በየሃገሬ ፖለቲካ ረጅም ርቀት ተጉዤ አስተቃጽኦ ላደርግበት የምችልና የሚገባ መሆኑን የማታ ማታ ለመረዳት ችያለሁ፡፡ ይሁንና ገና ከማለዳው ጀምሮ በህውሃት ውስጥ የነበረኝ የፖለቲካ ተሳትፎ አልጋ በአልጋ አልነበረም፡፡ በአጭሩ በሴራና በአሜኬላ የተሞላ ነበር ብሎ መናገር ማጋነን አይሆንም፡፡ ሆኖም ችግር ሲመጣ መሸሽና ማፈግፈግ ሳይሆን ፊት ለፊት ተጋፍጦና ተፋልሞ ማሸነፍ እንደሚገባ ላስተማረኝ ለውድ አያቴ ለሃዋደ ሻረው አቢቱ አበራ እና
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢሳና አፋር ደም አፋሳሹ ግጭት መቼ ነው የሚያበቃው? እንዴስ ያበቃል? – አካደር ኢብራሂም

ከአካደር ኢብራሂም በኢትዮጵያ ውስጥ ዝነኛ የሆነ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ፣ ማለቂያ የለለውና መፍትሄ ያልተግኝለት ጦርነት። በተለምዶ በግጦሽና በሳር የሚፈጠር የአርብቶ አደሮች ግጭት በመባል ይታወቃል። ጉዳዩ ግን ሰፋ ያለ ሌላ ትኩረት የሚስብ ፖለቲካዊ አጀንዳ ያነገበ ስለመሆኑ ብዙ የተባለ ቢሆንም የተገኘ መፍትሄ ግን የለም። ችግሩ የሚመለከተው አካል መፍትሄ አለመስጠቱ ብቻ አይደለም። ዋናው ችግሩ መንግስታት የሁለቱ ወገኖች ግጭትን ለፖለቲካ ፍጆታ መጠቀማቸው ነው። በዚህ ጉዳይ የውጭም ሆነ የሀገር ውስጥ ምሁራን ብዙ ጥናቶች አድርገዋል። በጣም ብዙ ጊዜ ደግሞ በሃይማኖት አባቶችና በባህላዊ ሽምግልና ዕርቅ ተሞክሯል። ችግሩ ግን ሊቆም አልቻለም። ለምን ይሆን? የታሪክ ደርሳናት እንደሚናገሩትና ኢሳዎችም ጭምር የማይክዱት አንድ ሀቅ አለ። የኢሳ ሶማሌ ጎሳ ከዘላዓ ወዲህ የሚታወቁበት መሬት እንዳልነበራቸውና በተለያዩ ጊዜያቶች በተደረጉ ጦርነቶች ግዛታቸውን እያስፋፉ እንደመጡ ይነገራል። ብዙ ሰዎች በተለይ አሁን አሁን ከማንነትና ከመሬት ይገባኛል ጋር የሚያያዙ ግጭቶች ከፌደራሊዝም ጋር ያያዙታል። የኢሳና አፋር ግጭት ግን በጣም የቆየና ቁርጠኛ የሆነ ገለልተኛ ውሳኔ የሚፈልግ አንገብጋቢ ጉዳይ ነው። ከንጉሠ ነገስት ሃይለስላሤ አገዛዝ ዘመን ጀምሮ በኢሳና በአፋር መሃል የተደረጉ ስምምነቶችን ጥሶ የሚገኘው የኢሳ-ሶማሌ ጎሳ እንደሆነ ማስረጃዎች ያሳዩሉ። የኢሳ (ሶማሌ) ድንበር ከአፍደም ወደ አሁኑ የሶማሌ ክልል 147 ኪ.ሜ ርቀት ላይ እንደነበረ በ1962 ዓ.ም በኤረር ላይ በአፋርና ኢሳ መካከል በተደረገ ስምምነት ተገልጿል። ነገር ግን በአሁኑ ግዜ ኢሳዎች አፋርን እያጠቁ ያሉት ከኤረር 300 ኪ.ሜ. ወደ ውስጥ ገብቶ የአዋሽ ወንዝ ዳርቻ አዳይቱ፣ ኡንዳፎኦ እና ገዳማይቱ በተባሉ
Posted in Amharic News

የአረና ፓርቲ ተወካይ ዓምዶም ገብረስላሤ ከአዲስ ድምጽ ራዲዮ ጋር በመረጃ ቲቪ

Posted in Amharic News

ከጋዜጠኛ ደምስ በለጠ ድንገተኛ ሞት በስተጀርባ የጠላት እጅ ይኖር ይሆን? አብረን የምናይ ይሆናል!

ጋዜጠኝ ደምስ በለጠ ከመሞቱ ዋዜማ የነበረውን ውሎ አባይ ዘውዱ እንደሚከተለው ዘግቧል የታህሳስ 12 ቀን ውሏቸውን በተመለከተ ዛሬ ያገኘሁት መረጃ ይህን ይመስላል – (ለምርመራው ከጠቀመ) 1. ረፋድ 4 ስዓት ላይ ፒያሳ ቀጠሮ አለኝ ብለው መነን ት/ቤት አካባቢ ካለው ከእናታቸው ቤት ወጡ፣ 2. 4 ስዓት ላይ ከቤት እንደወጡ ከሁለት ጓደኞቻቸው ጋር እዛው መነን አካባቢ ከሰብለ አረጋ ከተባለች ቤተሰባቸው ቤት ቡና ጠጥተው፣ለ30 ደቂቃ ያህል ከቆዩ በኃላ ስልክ ሲደወልላቸው ፒያሳ የማገኘው ሰው ስላለ በኃላ እመጣለሁ ብለው ከሰዎች ተለይተው ሄዱ።(ዘመዳቸው ሰብለ አረጋ ከተናገረችው) (የተደወለላቸውን ስልክ ሳይ ልክ 4 ስዓት ከ28 ደቂቃ ላይ የደወለላቸው ደግሞ አንድ ጓደኛቸው ነው(ስማቸው ይቆየን)።በአካል ያግኛቸው በስልክ ብቻ ገና አልተጣራም። 3. ከቀኑ 6 ስዓት አካባቢ ስደውልላቸው ሩሲያ ኤግዚቪሽን አካባቢ እንደነበሩ ነግረውኛል።ማገኛቸው ሰዎች አሉ ብለውኛል። (ከእህታቸው ልጅ ከህይወት ተፈሪ ንግግር የተገኘ) 4. ከቀኑ 9 ስዓት ተኩል ወደ እናታቸው ቤት ተመለሱ፣ጥሩ የጤንነት ስሜት ላይ አልነበሩም፣የቀረበላቸውን ምግብ ቀማምሰው ነው የተውት፣የድካም ስሜት አለባቸው፣የሆኑትን ነገር ብትጠይቃቸውም ስሜታቸውን አላጋሯቸውም። (እህታቸው ወ/ሮ አዜብ በለጠ ከተናገረችው ) 5. በመሀል አቶ ወርቁ (ጓደኛቸው) እና ወ/ሮ እታፈራሁ ካሳ ወደ እናታቸው ቤት በመምጣት ጋዜጠኛ ደምስንና ቤተሰቡን ሲያጫውቱ ቆዩ፣ከተወሰነ ቆይታ በኃላ እህታቸው ወ/ሮ አዜብ በለጠ እና ልጃቸው ህይወት ተፈሪ ለስራ ጉዳይ ከቤት ወጡ። 6. ከጋዜጠኛ ደምስ በለጠ እና ከእናታቸው ጋር እነ ወ/ሮ እታፈራሁና አቶ ወርቁ ሲጫወቱ እስከ 12 ስዓት አካባቢ አብረው ቆይተዋል፣ነገር ግን በመሀል
Posted in Amharic News

የቀድሞው ደህንነት ምክትል ሃላፊ እና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ያሬድ ዘሪሁን በዱከም ከተማ የተደበቁበት ሆቴል ውስጥ እንዳሉ በቁጥጥር ስር ውለዋል

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የሴቶች መብት ተሟጋች እና ጠበቃ መዓዛ አሸናፊ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ናቸው ተሿሚዋን ተሰናባቹን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ዳኜ መላኩ ተክተው እንዲሰሩ በእጩነት ያቀረቧቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወ/ሮ መዓዛ ባላቸው የዳበረ ልምድ ምክንያት የአገሪቱን የፍትህ ስርዓቱ ወፊት ያራምዱታል በሚል በእጩነት እንዳቀረቧቸው ለምክር ቤቱ ተናግረዋል፡፡ በዚህም መሰረት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ ይሁንታውን ሰጥቷቸዋል፡፡ ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ በህግ የዳበረ ልምድ ያላቸው ፣ በተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ከፍተኛ ተቋማት ውስጥ በማገልገል አንቱታን አትረፈዋል፡፡ ከህገ መንግስት አርቃቂ ከሚሽን አባልነት በግላቸው ለሴቶች ከለላ የሚሆን ድርጅት እስከማቋቋምም ደረሰዋል፡፡ በመሆኑም በዛሬው ዕለት የተሰጣቸው የጠቅላይ ፍርድቤት ፕሬዝዳንትነት ሹመት በፍርድ ቤቱ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝዳንት ያደርጋቸዋል፡፡ ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊም ቃለ መሃላ ፈፅመው በህዝብና በመንግስት የተጣለባቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ቃል ገብተዋል፡፡ ምንጭ፦ ኢቲቪ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በለዛ ሽልማት የዚህ አመት የኢትዮጵያ ምርጥ ዘፈን ተሸላሚ – ይመልከቱ

Posted in Music

የለዛ ሽልማትን የዚህ አመት ምርጥ አልበም ያሸነፈውና ከቴዲ አፍሮ ሽልማቱን የተቀበለው አርቲስት ማነው? ይመልከቱ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሽማግሌ ቢጠፋ ዛፍ ገላጋይ ነበር! ወንድሞቼ ነብስሳችሁን ይማርልን! (ሄኖክ አያና)

ያኔ ድሮ አማራ ወጉ ሃያል ነበር! ሊኗኗር ብቻም አደል ሊገዳደል ህግ ነበረው። አማራ ሲገድልም በክብር ነበር፥ መጣሁ ሳይል የወንድ በር ሳይሰጥ ለመግደል አደለም ለማሸነፍም ቃታ አይሰብም! አማራ እምነትና ደግነት ነበረው! ሊገድለው እድል የመሸበትን ባላንጣውን በዛፍ ቢጠለል ያልፍ ነበር። አማራ ወንድ ነበር፣ መጣሁ ሳይል፣ ታጠቅ ሳይል እጁ አይስትም። ያልታጠቀን አይነካም፥ ብዙ ሆኖ አንድ አይገድልም። ትልቅ ሆኖ ትንሽን፣ ጎበዝ ሆኖ ደካማን ፍጹም አይነካም። አማራ ወጉ ግሩም፣ ልማዱና እሴቱ ድንቅ ነበር። የአማራ ስሪት የሰው ነበር! ምን ዋጋ አለው ይሄ የኛ የዝቅታ ዘመን ነው። አማራ ቢደኸይም ሃብታም ነበር። በድህነቱ ውስጥ ዘመናትን የተሻገረው በሰውነት ሃብቱ ነው። አሁን ሰውነትም የለ፥ ሃብትም የለ!! መደህየት እሱ ነው። በስማ በለው የበሬ ወለደ ጫጫታ ሙህራን በጠራራ ጠሃይ በማይማን የተወገሩበት ይሄው እኛ ቁልቁል የወረድንበት የኛው ዘመን ነው። ወንድሞቸ ነብስሳችሁን ይማርልን!
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በምዕራብ ጎጃም ዞን አዲስ አለም ከተማ ዶ/ር ወሰን ታፈረ እና የስራ ባልደረቦቹ ላይ ግድያ በመፈጸም የተጠረጠሩ ታሰሩ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

በዱራሜከተማ ደቡብ ኢትዮጵያ ስራ እንዲሰጣቸው በሰላማዊ ሰልፍ የጠየቁ የዩኒቨርስቲ ምሩቃን በፖሊሶች ተደበደቡ

(ኢሳት – ጥቅምት 16 ቀን 2011 ዓ/ም) – በከምባታ ጠምባሮ ዞን ካለፉት 4 ዓመታት ወዲህ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ተመርቀው ስራ ያጡ ወጣቶች ወደ ዞን መስተዳደር ምክር ቤት ማምራታቸውን ተከትሎ በፖሊሶች ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል። ተማሪዎቹ ቀደም ብለው ጥያቄያቸውን ለመስተዳድሩ አቅርበው ለዛሬ አርብ ተቀጥረው የነበረ ቢሆንም፣ በቀጠሮአቸው መሰረት ወደ መስተዳድሩ ሲሄዱ ያጋጣማቸው የፖሊስ ዱላ ነው። በጉዳዩ ዙሪያ የከተማውን የአስተዳደር አካላት ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። ተጨማሪ ዘገባ ከፌስቡክ ፔጅ ተከታታያችን፦ በከምባታ ጠምባሮ ዞን በተለያዩ ትምህርት መስኮች ካለፉት አራት አመታት ወዲህ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተመርቀው ስራ ያጡ ወጣቶች ዛሬ ወደ ዞን መስተዳድር ምክር ቤት አምርተው ነበር። ይሁን እንጂ ቁጥራቸው ወደ300 የሚደርሱት ወጣቶች በምላሹ መደብደባቸውንና መበተናቸውን የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። በከተማው የነበረውን መሯሯጥ እንደተሰማ ሁኔታውን እንደተከታተልኩት ዱላ የያዙ ፖሊሶች ወጣቶቹን እያሯሯጡ ሲደበድቡ ብዙዎች ታዝበዋል። ሮጠው ማምለጥ ያልቻሉ ሴቶችና የፖሊሶችን እርምጃ ለመቋቋም የሞከሩ ወጣቶች ክፉኛ ተደብድበዋል። በሶስት የወታደር ላንድክሩይዘር መኪና የተጫኑት ፖሊሶች በመቶዎች የሚቆጠሩትን ወጣቶች ከመደብደብ በተጨማሪ ቁጥራቸው ባይታወቅም የተወሰኑት ታስረው ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬ ያደረባቸው ብዙዎች ናቸው። ጥያቄያቸው ምን እንደነበረ ለማወቅ ቀርቤ ያነጋገርኳቸው ተደብዳቢዎች ውስጥ በዱላ የደረሰበትን ድብደባ እያሳየ አንድ ወጣት እንደገለፀልኝ÷ “የዞን መስተዳድር ምክር ቤቱ በክልሉ የሚታወቀው ምንም ስራ አጥ እንደሌለበት በመሆኑ ድምፃችን ታፍኖ ትኩረት ተነፍገናል ስለዚህ ዋናው አስተዳዳሪ በሰጡን ቀጠሮ መሰረት ያነጋግሩን በማለታችን ተደብድበናል። ይህ ቀጠሮ በአስተዳዳሪው ብቻ ሲቀየር ለሦስተኛ ጊዜ ነው÷ ብዙ ወጣቶችም ተጎድተዋል÷ ምናልባትም የታፈሱ ልጆችም
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የራያ ጥያቄና የሰሞኑ የአላማጣ ግጭት መንሳኤ ሲመረመር

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ንግግር በፓርላማ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የቡራዩ ነዋሪዎች ወደቤታቸው ተመልሰዋል

Posted in Amharic News, Ethiopian News

በኬንያ ተሰዶ የነበረው ጋዜጠኛ ቴዲ ካሳ – መረጃ ቲቪ 7 ደቂቃ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከሀረር ከተማ የውሃ ጥማት በስተጀርባ ያለው የሃረሪ ሊግ እና የኦህዴድ ፍጥጫ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የዲያስፖራ ትረስት ፈንድ ተጀመረ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 13/2011) የዲያስፖራ ትረስት ፈንድ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር በይፋ ተጀመረ። https://www.ethiopiatrustfund.org/ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ በይፋ ያደረጉትን ጥሪ ተከትሎ በፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም የሚመራ ታዋቂ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት አማካሪ ቦርድ መሰየሙም ይታወሳል። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሃገር ቤት የሚኖሩ ችግረኛ ዜጎችን ለመደገፍ በቀን አንድ ዶላር እንዲያዋጡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበውን ጥሪ ተከትሎ የተቋቋመው አማካሪ ቦርድ ትላንት በይፋ ...

The post የዲያስፖራ ትረስት ፈንድ ተጀመረ appeared first on ESAT Amharic.

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የትግራይ ክልል የኮምዩኒኬሽን ሃላፊ የራያ-አዘቦን ውዝግብ አስመልክቶ ማስጠንቀቂያ ሰጡ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

በጎሳ ግጭት ምክንያት የሃረር ከተማ ህዝብ በውሃ ጥም እየተሰቃየ ይገኛል

Posted in Amharic News, Ethiopian News

አባ መላ በመረጃ ቲቪ – ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ/ም እአአ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ለቄሮ መሬት አልሰጠንም። ውሸት ነው። አዲስ አበባ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ነው… – ከንቲባ ታከለ ኡማ ለኢቲቪ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ብፁዕ አቡነ መርቆርዮስ ፓትሪያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ከመረጃ ቲቪ ጋር ያደረጉት ቆይታ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የጎንደር ከተማ ከንቲባ ከአዲስ ድምጽ ጋር ያደረጉት ቆይታ – አዲስ ድምጽ በመረጃ ቲቪ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጋዜጠኛ እስክድር ነጋ ለጠ/ሚ አብይ የሰጠው ምክር

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የታጠቁ ወታደሮች ወደቤተመንግስት የመጡበት ሁኔታ ለውጡን ለመቀልበስ ነበር ሲሉ ጠ/ሚ አብይ ለፓርላማ አብራሩ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

«ራሳችንን ለመከላከል በወሰድናቸው እርምጃዎች የሰው ህይወት አልፏል፣ በዛ በጣም እናዝናለን» – የኢህአፓ ሊቀመንበር

Posted in Amharic News, Ethiopian News

«ሁሉም የአዲስ አበባ ታክሲ ሹፌር በአሁን ሰዓት መሮታል። ሰርተን መብላት አቃተን» – የታክሲ ማህበር ተወካይ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአዲስ አበባ አስተዳደር አፍኖ የወሰዳቸውን በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ሊፈታ ይገባል – ዋሜራ በመረጃ ቲቪ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

በሙስና እና ዘረኝነት የተተበተበው መከላከያ ሰራዊት የህዝብ አገልጋይ እንዲሆን ስራ መሰራት አለበት – አባ መላ በመረጃ ቲቪ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጠ/ር አብይ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ሰቃ ፏፏቴን ከጎበኙ በኋላ የጅማ ህዝብ በዚህ መልክ ተቀብሏቸዋል

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኦሞ ኩራዝ የስኳር ፋብሪካ ቁጥር 3 በጠ/ሚ አብይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ተመረቆ ተከፍቷል – ቪዲዮ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

7 ደቂቃ ከጋዜጠኛ እስክድር ነጋ ጋር – መረጃ ቲቪ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ወታደሮች ቤተመንግስት እንዲከቡ ሲያነሳሱ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው – ጄኔራል ፀዓረ መኮንን

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ቄሮ ብለው ራሳቸውን የሚጠሩ ቡድኖች በተለያዩ አካባቢዎች ህዝብ እያሸበሩ ይገኛሉ – ዋሜራ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ግንቦት ሰባት በናዝሬት – video

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የፖለቲካ መገለጫ የሆነ ባንዲራ፣ አርማ መፈቀድ የለበትም – ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ፓይለት ዮሃንስ ተስፋዬ ወደስራው መመለስ እንደሚችል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገለጸ

በማንነቴ ስራ ቦታ ላይ በደል ተፈጸመብኝ ያለው ፓይለት ዮሃንስ ተስፋዬ ወደስራው መመለስ እንደሚችል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገለጸ። ዘገባውን ይከታተሉ ↓
Posted in Amharic News, Ethiopian News

«ደረሰኝ ስጡን ስንላቸው ደረሰኙ ዱላ ነው» – የአዲስ አበባ ወጣት ነጋዴ

«ደረሰኝ ስጡን ስንላቸው ደረሰኙ ዱላ ነው» – የአዲስ አበባ ወጣት ነጋዴ በከተማው እብሪተኛ አስተዳደርና ፖሊስ ወጣቱ እየተፈጸመበት ያለውን በደል ይናገራል
Posted in Amharic News, Ethiopian News

7 ደቂቃ ከአክቲቪስት ኦባንግ ሜቶ ጋር

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የመከላከያ ሃይል ላይ ሳቦታጅ እየተደረገ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሊፈትሹ ይገባል – አባ መላ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን በወታደሮች ታግተው ነበር ወይ? የመረጃው ምንጭ «እውነታው ይህ ነው» ይላል (ሃብታሙ አያሌው)

ከሃብታሙ አያሌው መንግስት ስለሁኔታው ከዚህ በላይ እንዲል አልጠብቅም። መቼም ታገትን እንዲሉ አይጠበቅም። ያለቀጠሮ መሳሪያ ይዞ መጥቶ አስገድዶ ያናገረን ሰራዊት አብርዶ መመለሱ ጥሩ ቢሆንም በጎ ሁኔታ እና ልምድ ግን አይደለም። የሆነው ሁኖ ወደ መረጃ ምንጬ ተመልሼ የሆነውን በዝርዝር እንዲያስረዳኝ በመጠየቅ በርግጥ በርግጥ እገታ አልነበረምን ? ስል ለጠየኩት ጥያቄ እውነታው ይህ ነበር ብሎኛል! ጠዋት 4:45 ~~~~~~ ከወትሮው ባልተለመደ መልኩ የመከላከያ ሰራዊት የተውጣጡ ቀይ ቦኔት የለበሱ አባላት አራት ኪሎ በአራቱም አቅጣጫ ላይ መታየት ጀመሩ። ወዲያው ባፋጣኝ ወደ ጊቢ ገብርኤል የሚወስደው መንገድ ለተሽከርካሪ ዝግ ተደረገ። ቀትር 6:30 ~~~~~~ በተለያየ አቅጣጫ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት የሚመጡት ልዩ ሃይሎች ቁጥራቸው እየበዛ መጣ። ከቀኑ 7:45 ~~~~~~ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በሚሊኒየም አዳራሽ የኮንስትራክሽን ኤግዚቢሽን በይፋ ከፍተው ከቦሌ ወደ አራት ኪሎ ፅ/ቤታቸው አቀኑ። ከቀኑ 7:55 ~~~~~~ ከተለያየ አቅጣጫ የሚጎርፉት የሰራዊቱ አባላት ቁጥር መጨመሩን ተከትሎ፤ አራት ኪሎ አካፋይ መንገድ ላይ ወደ ቤተመንግስት የሚወስዱ መኪናዎች አቅጣጫ እየቀየሩ አከባቢው ተጨናንቆ ነበር። ከቀኑ 8:00 ~~~~~~ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀን የያዘው መኪና {ጥይት የማይበሳው} ወደ አራት ኪሎ አካፋይ መስቀለኛ መንገዱ ጋር ደረሰ። የአቶ ደመቀ ልዩ ጠባቂዎች በፍጥነት ከመኪናው ወርደው አጅበው ለማሳለፍ ፤ አልተሳካም ወታደራዊ ሃይሉ አቶ ደመቀን አግቶ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዋና ጠባቂ {Cheif Secirty} ጋር ቃላት ተመላለሱ። ይህ ሁኔታ ድንጋጤ ፈጠረ፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩን መንገድ ላይ ያገኙት በእቅድና በዝግጅት ወይስ ባጋጣሚ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አስደናቂ የፈረስ ትዕይንት በባህር ዳር – video

Posted in Amharic News, Ethiopian News

አጭር ቀሚስ የምትለብስ ሴት ስናይ ዘራፍ እያልን፣ ግን ተደብቀን ወሲባዊ ፊልሞችን በኢንተርኔት እናያለን – ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ለውጡ እንዲሳካ የጠ/ሚ አብይ መንግስት አስቸኳይ ትኩረት ሊሰጥባቸው የሚገቡ ጉዳዮች – አባ መላ በመረጃ ቲቪ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

አባ መላ አባ መላ በመረጃ ቲቪ ያለፈው ሳምንት የተካሄደውን የኢህአዴግ ጉባኤ ይገመግማል – ይመልከቱ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢህአዴግን 11ኛ ጉባኤ እኛ እንደ 1ኛው ጉባኤ አድርገን ነው የምንወስደው – ደምሴ ቱሉማ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

መንግስት በግብታዊነት የሚጨምረው ቀረጥ ነዳጅ አመላላሾችን እያከሰረ መሆኑ ተገለጸ – ዋልታ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዶ/ር ተዋበች ቢሻው ስለኢትዮጵያ መንግስት የዳያስፖራ ፖሊሲ የሰጡት ማብራሪያ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢህአዴግ 11ኛ ጉባኤ ማጠናቀቂያ ሪፖርትና የአቋም መግለጫ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም በቅርቡ ወደሀገር ቤት ስለጠሩት 90 አምባሳደሮች እና ሌሎችም ጉዳዮች ለመረጃ ቲቪ ማብራሪያ ሰጥተዋል

የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም በቅርቡ ወደሀገር ቤት ስለጠሩት 90 አምባሳደሮች እና ሌሎችም ጉዳዮች ለመረጃ ቲቪ ማብራሪያ ሰጥተዋል
Posted in Amharic News, Ethiopian News

11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ላይ የታዘብናቸው ነገሮች – አባ መላ በመረጃ ቲቪ

Posted in Amharic News, Ethiopian News

አዴፓ (የቀድሞው ብአዴን) 9 የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ እና የድርጅቱን 13 ስራ አስፈጻሚ አባላትን መርጧል

ባሕር ዳር፡መስከረም 22/2011 ዓ.ም አዴፓ 9 የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ አባላትን አሳወቀ፡፡ 1.አቶ ደመቀ መኮንን 2.አቶ ገዱ አንዳርጋቸው 3.ዶክተር አምባቸው መኮንን 4.አቶ ብናልፍ አንዷለም 5.አቶ ተፈራ ደርበው 6.ዶክተር ይናገር ደሴ 7.አቶ መላኩ አለበል 8.ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ 9.አቶ ምግባሩ ከበደ አዴፓ የድርጅቱን 13 ስራ አስፈጻሚ አባላት፡፡ 1.አቶ ደመቀ መኮንን 2.አቶ ገዱ አንዳርጋቸው 3.ዶክተር አምባቸው መኮንን 4.አቶ ብናልፍ አንዷለም 5.አቶ ተፈራ ደርበው 6.ዶክተር ይናገር ደሴ 7.አቶ መላኩ አለበል 8.ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ 9.አቶ ምግባሩ ከበደ 10.አቶ ላቀ አያሌው 11.አቶ ዮሀንስ ቧያለው 12.አቶ ጸጋ አራጌ 13.አቶ ንጉሱ ጥላሁን አዲሱ የድርጅቱ አርማ የምርጫውን ሂደት የሚያሳይ ቪዲዮ
Posted in Amharic News, Ethiopian News