Blog Archives

ለክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ጠቃሚ ምክር (ከፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ጂግሳ)

ለ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አስቸኳይ ምክር ************************************ ለ ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ትንሽ ጠቃሚ ምክር ከፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ጂግሳ ውድ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን በአለዎት ፍቅር የተነሳ ስልጣን ከያዙ ሶስት ወር እንኳን ሳይሞላ እርስዎና ባልደረቦችዎ የፈፅማችሁአቸውን ታላላቅ ተግባሮች አሁን እኔ እዚህ አልዘረዝራችውም። እርስዎ፣ እቶ ለማ መገርሳ እና አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የለኮሳችሁት ኢትዮጵያዊነት እሁን ወደ ፍቅርነት አየተለወጠ እየነደደ ነው። በፍቅር ላይ ደሞ እርስዎ መደመርን፣ እንዲሁም ይቅርታ እና ምህረት ማድረግን ጨመሩባቸው። በጣም ደስ ይላል። ዳሩ ግን የእርስዎ ፍቅር፣ መደመር፣ ይቅርታና ምህረት የማይስማሟቸው የጭለማ ሰራዊቶች መኖራቸውን በቀደም እለት ለእርስዎ አነጠጥረው በህዝብ መሀል ያለርህራሄ ባፈነዱት ቦንብ እና በአፈሰሱት ንፁህ ደም ይፋ አድርገዋል። ከቡር ጠቅላይ ሚንስትር ሆይ፡ የምንኖረው አብሪት፣ ትእቢት፣ጭካኔ፣ ሴራ እና ግድያ በሞሉበት ዐለም ውስጥ ነው። ይህ የጭለማ ዐለም የፍቅርን፣ የይቅርታን እና የምህረትን ብርሃን ጠልቶ ሊያጠፋው እንደሚጥር አሙን ነው። ሆኖም ቦምቡ የተወረወረው ከላይ ለእርስዎ ቢሆንም ከውስጥ መላውን የኢትዮጵያን ህዝብ ለማጥቃት እና አሁን የተቀዳጁትን ፍቅር፣ አንድነት እና የኢትዮጵያዊነት ስሜት ለመንጠቅ የታቀደ እኩይ ሴራ ነው። እርስዎ የአበሰሩቸው ይቅርታና ምህረት በመሰረቱ መልካም ቢሆኑም ይቅርታ እና ምህረት የሚደረጉት ስለበደሉ ተፀፅተው ይቅርታን እና ምህረትን ለሚጠይቁ ሰዎች ብቻ ነው። አጥፍቻለሁ ይቅር በሉኝ፣ ማሩኝ የሚሉ ሳይኖሩ ይቅርታ እድርጌላችኋለሁ፣ ምሬአችኋለሁ ማለት ትርጉም የለውም። በዳዮቹ ስንትና ስንት ግፍ ፈፅመው ሳይፀፀቱ በቀላሉ ምሬአችኋለሁ ሲባሉ ስላልተቀጡ ታብየው አዲስ ጥፋት ሊያደርሱ ይችላሉ። ለማድረስም ሲጥሩ
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መልክፀዲቅ የኢትዮጵ አባት የኢትዮጵያውያን አባት – ከፕሮፌስር ፍቅሬ ቶሎሳ

መልክፀዲቅ የኢትዮጵ አባት የኢትዮጵያውያን አባትከፕሮፌስር ፍቅሬ ቶሎሳ ስለ የሳሌም (ኢየሩሳሌም) ንጉሥ መልከፀዲቅ ስናወሳ የእሱን ማንነት አስመልክቶ ውዥንብር አለ;; መልክጸዲቅ በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ በኦሪት ዘፍጥረት (11. 18-21)፣ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር (109-110. 4) እና የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ እብራውያን (ምእራፍ 7) ተጠቅሶአል;; — በኦሪት ዘፍጥረት (14. 18-21) ስለ አብርሃም እና መልከፀዲቅ እንዲህ ይላል;– ››አብርሃም ኮሎዶጎምርንና ከእሱ ጋር የነበሩትን ነገሥታት ወግቶ ከተመለሰም በሁዋላ የሶዶም ንጉሥ የንጉሥ ሸለቆ በሆነው የሌዊ ሸለቆ ሊቀበለው ወጣ;; የሳሌም ንጉሥ መልከፀዲቅም እንጀራንና የወይን ጠጅን አወጣ;; እርሱም የልኡል እግዚአብሄር ካህን ነበረ;; ባረከውም (አብርሃምን)– አብርሃም ሰማይንና ምድርን ለሚገዛ ለልኡል እግዚአብህር የተባረከ ነው;; ጠላቶችህን በእጅህ የጣለልህ ልኡል እግዚአብሄርም የተባረክ ነው፣ አለውም;; አብርሃምም ከሁሉ አሥራትን ሰጠው;;›› በዳዊት መዝሙር ደግሞ (109—110‹ 4) አግዚአብሄር አብ፣ በዳዊት አፍ ውስጥ ስለ እየሱስ ክርስቶትስ ዘላለማዊ ካህንነት ምሎአል– ››እንደ መልከፀዲቅ ሥርዐት አንተ የዘላለም ካህን ነህ ብሎ፣ እግዚአብሄር ማለ፣ አይፀፀትም;;; .. ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ (እብራይስጥ 7) በመጀመሪያ ስለ መልከፀዲቅ፣ ቀጥሎም መልከፀዲቅ ምሳሌው ስለ ሆነው ስለ እየሱስ ክርቶስ ይናገራል;; እንዲህ ሲል– ..የሳሌም ንጉሥና የልዑል እግዚአብሄር ካህን የሆነው ይህ መልከፀዲቅ አብርሃም ነገሥታትን ገድሎ ሲመለስ ከእርሱ ጋር ተገናኝቶ ባረከው፤ ለእርሱም ደግሞ አብርሃም ከሁሉ አስራትን አካፈለው;; የስሙም ትርጉዋሜ በመጀመሪያ የፅድቅ ንጉሥ ነው;; ሁዋላ ደግሞ የሳሌም ንጉሥ ማለት የሰላም ንጉሥ ነወ;;›› (ስለ እየሱስ ከርስቶስ ማንነት ደግሞ ቅዱስ ጳውሎስ አያይዞ ሲናገር) አባትና እናት፣ የትውልድም ቁጥር የሉትም፣
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News