የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።

–


We strongly condemn the attack by the Tigray People’s Liberation Front against Eritrea and the attempt to internationalize the conflict. We urge the TPLF and the Ethiopian authorities to take immediate steps to de-escalate the conflict, restore peace, and protect civilians.
— Secretary Pompeo (@SecPompeo) November 17, 2020




የትግራይ ሕዝብ የ80 እና 90 ዓመት ሽማግሌዎች ምክንያት ለሶስተኛ ጊዜ ልጆቹን ለጥፋት እንዲያቀርብ እየተገደደ ነው … ለአያቶች መኖር የልጅ ልጆች መስዋዕት መሆን የለባቸውም። …….. በመከላከያ ላይ የተፈጸመው የክህደት ጥቃት ከህወሓት በኋላ ያለች ኢትዮጵያን የምናይበት ነው – ሌ/ጄኔራል ዮሃንስ ገ/ሚካኤል

ዶክተር ሙሉ ነጋ
ዶክተር ሙሉ ነጋ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
–
ዶ/ር ደብረፅዮንን ጨምሮ በወንጀል የተጠረጠሩ የምክር ቤት አባላት ያለመከሰስ መብት ተነሳ
ስግብግቡ የሕወሓት ቡድን በመከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰውን ጥቃት የሚያወግዙ ሰላማዊ ሰልፎች በክልል ከተሞች ተካሔዱ
- ወደ ትግራይ የተላከው 1.3 ቢሊየን ብር ለባንኮቹ ስለመድረሱ ብሔራዊ ባንክ እስካሁን ማረጋገጫ አላገኘም ተባለ
- የሕግ ማስከበሩ ስራ ጥፋተኛው ቡድን (ሕወሓት) ላይ እንጂ በሐሰት እንደሚነገረው የወሰን ማስከበር ወረራ አይደለም። መከላከያ ሚኒስትሩ
- በትግራይ ልዩ ኃይል በማይካድራ የተጨፈጨፉ ንፁሃን ቀብር እየተፈጸመ ነው።
- የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ።
- ህወሓት ጋር ድርድር የማይታሰብ ነው – መ/ር ዘመድኩን በቀለ
—————————————————————————————————————-
“ከግጭቱ ዋዜማ የትግራይ ክልል መሪ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ተደዋውለው ነበር” ያሉት ቃል አቀባዩ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን “ሁኔታውን በቀላሉ እንደሚይዙት እና በንግግር ሊፈቱት እንደሚችሉ ተነጋግረው ነበር” ብለዋል፡፡ …….. ሆኖም በዚያው ቀን ምሽት በክልሉ በሚገኘው የሃገሪቱ ጦር የተለያዩ ጣቢያዎች ላይ ድንገተኛ ጥቃት መከፈቱን ነው የገለጹት፡፡ – አል-አይን
By Dr Abrham Amare
ሕይወት በጦርነት ቀጣና ውስጥ በምትገኘው መቀለ ከባድ ሆኗል። በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ኃይል መካከል ግጭት ከተከሰተ ዛሬ 7ኛ ቀኑን አስቆጥሯል። ዘገቢያችን በመቀለ እና አከባቢዋ ከፍተኛ የሆነ የውሃ እጥረት መኖሩን እንዲሁም የነዳጅ እጥረት መከሰቱን ነግሮናል። ባንኮችም እንዲዘጉ መደረጉ ነዋሪዎች ሕይወት እንዲከብዳቸው ሌላው ምክንያት ሆኗል ይላል።

የተጀመረውን ተኩስ አቁመን ወደ ድርድርና ውይይት እንምጣ – ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል
ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል ለሮይተርስ የዜና ማእከል እንደተናገሩት ከፌደራል መንግስቱ ጋር የተጀመረውን ተኩስ አቁመን ወደ ድርድርና ውይይት እንምጣ ብለዋል።………
———————————————————————————
ህወሓት ከተወገደ የትግራይ ህዝብ ሰላሙንና ነጻነቱን ያገኛል ሲሉ የትግራይ ተወላጅ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ገለጹ።



የብልጽግና ፓርቲ የትግራይ ተወላጅ አባላት፣ ደጋፊዎችና ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂዷል፡፡


በኃይል ተገደው ወደ ጦርነት የገቡ የትግራይ ልዩ ኃይል አባላት ወደ አማራ ክልል በሰላማዊ መንገድ እየገቡ ነው፡፡
በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ይሄንን ጁንታ ሳያውቁት ከማገዝና ሀገራቸውን ከመጉዳት እንዲቆጠቡ፣ ወንጀለኞችንም እንዲያጋልጡ፣ ገንዘባቸውን በባንክ በመላክ ሀገራቸውን እንዲጠቅሙ መንግሥት ጥሪ ያደርጋል።

አየር ኃይሉ በወሰደው እርምጃ 300 ኪሎ ሜትሮች ድረስ መወንጨፍ የሚችሉ ሮኬቶችን ሙሉ በሙሉ አውድሟል:: የህወሓት ኃይል ላይ የተደረገው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት ተጠናቋል – ጠ/ሚ አብይ
ኢትዮጵያ ለወንጀለኛ አካላት ቦታ የላትም ! ኩሩው ኢትዮጵያዊ የሆነው የትግራይ ህዝብና ሌሎች ዜጎች ለዘለዓለም ፍትህ ሊነጠቁ አይችሉም ! ጠ/ሚ አቢይ አህመድ
Ethiopia has no place for criminal elements. The proud Ethiopian people of Tigray & other citizens cannot be taken hostage by fugitives from justice forever. We shall extract the region of these criminal elements & relaunch our country on a path to sustainable prosperity for all.
— Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 (@AbiyAhmedAli) November 6, 2020
Operations by federal defence forces underway in Northern #Ethiopia have clear, limited & achievable objectives — to restore the rule of law & the constitutional order, and to safeguard the rights of Ethiopians to lead a peaceful life wherever they are in the country.1/2
— Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 (@AbiyAhmedAli) November 6, 2020

የሰሜን ኢትዮጵያ አየር ክልል ተዘግቷል ::
ከጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ በሰሜን የኢትዮጵያ የአየር ክልል ውስጥ የሚያቋርጡ የአለም አቀፍ እና የሃገር ውስጥ የበረራ መስመሮች ለማንኛውም የበረራ አገልግሎት የተዘጉ መሆናቸው ተገልጿል።
በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ያለው የአየር ክልል ለማንኛውም በረራ የተዘጋ ነው ተብሏል።
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ይህንን ተላልፎ በረራ የሚፈጽም ማንኛውም አውሮፕላን እንዳይኖር ን አሳስቧል።
ከዛሬ ጥቅምት 27 ቀን 2013 ዓ/ም ጥዋት 2 ሰዓት ጀምሮ የመቐለ፣ ሽሬ ፣ አክሱም እና ሁመራ ኤርፖርቶች ለማንኛውም የበረራ አገልግሎት ዝግ መሆናቸውን ተገለፀ።
ይህን የገለፀው የኢትዮጵያ ሲቨል አቪዬሽን ባለስልጣን ነው።
በተመሳሳይ ሁሉም የሚመለከታቸው አካሎች (ኤርሜንስ) በተገቢው የመገናኛ ዘዴ በ (ኖታም) አንዲያውቁት መደረጉን አስታውቋል።


የአሸባሪው ትህነግ ማዘዥያ ጣቢያ የነበረው የማይደሌ ጣቢያ በዚህ መልኩ ተደምስሷል!

የአሸባሪው ትህነግ ማዘዥያ ጣቢያ የነበረው የማይደሌ ጣቢያ በዚህ መልኩ ተደምስሷል!
በሁመራ፣ በዳንሻ እና በቅራቅር አካባቢ በነበሩ ውጊያዎች የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ ያደረጉት ተጋድሎ በታሪክ የሚዘከር ነው ሲሉ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ተናገሩ።
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ፥ በመከላከያ ሰራዊት ተግባር ‘ህውሓት’ ያሻውን ሳያደርግ የሞከራቸው ሙከራዎች ከሽፈው ውለዋል ሲሉ አስታውቀዋል።

መቀሌ የሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ ከትላንት ጀምሮ በከተማዋ የነበረው ሁኔታ እንዲህ ዘግቦታል። የሚከተሉትን ፎሮ ግራፎችም ልኮልናል።
ትላንት [ማክሰኞ] እኩለ ለሊት ገደማ መቀሌ ከተማ ተኩስ ይሰማ ነበር።
የከተማው ሰው እየሆነ ባለው ነገር ተደናግጦ ነበር። ይሄኔ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ወደ ፀጥታ ኃይል ሰዎች ስደውል ‘አሁን ልናናግርህ አንችልም፤ ቢዚ ነን’ አሉኝ። ከደቂቃ በኋላ የስልክ መስመር ተቋረጠ። ስልኬ ‘ኖ ሰርቪስ’ የሚል ምልክት ያሳየኝ ጀመር።

በመቀጠል የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋረጠ። ጥዋት ስንነሳ ከተማዋ የኤሌክትሪክ አገልግሎቷ እንደተቋረጠ ተረዳሁ። መብራት የጠፋው መቀሌ ብቻ ሳይሆን ትግራይ ክልል ሙሉ እንደሆነ ማረጋገጥ ችያለሁ።
ወደ ከተማ ወጣ ስል የሰዎች ፊት ላይ ግራ መጋባት ተመለከትኩ። አብዛኛው ሰው በእግሩ ነበር ሲንቀሳቀስ የነበረው።
ከተማዋ ላይ ያሉ የባንክ ቅርንጫፎች ተዘግተው ነበር። ሁለት የባንክ አስተዳዳሪዎች እንደነገሩኝ አገልግሎት ያቋረጡ የበይነ መረብ [ኢንተርኔት] አገልግሎት ስለሌለ ነው።
ረፋድ ላይ የኢትዮቴሌኮም ሠራተኞች መስሪያ ቤታቸው ደጃፍ ላይ ሰብሰብ ብለው ቆመው ነበር።
ከረፋፈደ በኋላ ከፀጥታ ኃይል ሰዎች እንደተረዳሁት ተኩሱ የተሰማው የትግራይ ክልል ወታደሮች ከሰሜን ዕዝ ጋር በነበራቸው የተኩስ ልውውጥ መሆኑን ተረድቻለሁ።
ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢሮና ወደ ሌሎች የጉዞ ወኪሎች አምርቼ ለጊዜው በረራ ሙሉ በሙሉ መቋረጡን መረዳት ችያለሁ። በትግራይ የስልክ እና ኢንተርኔት አገልግሎት ተቋርጧል
መቀሌ ከተማ ያሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና ሆቴሎች አካባቢ ከበድ ያለ የፀጥታ ኃይል ይታያል።
የክልሉ መንግሥት ክልሉ ውስጥ ምንም ዓይነት ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዳይኖር አግዷል።
የትራንስፖርት አገልግሎትም ሙሉ በሙሉ ቆሟል። የክልሉ የአየር ክልልም ከበረራ ውጭ እንዲሆን ታዟል።
መቀሌ ከተማ አሁን ላይ ሰላማዊ ሁኔታ ላይ ትገኛለች። BBC Amharic

PHOTO : ጋዜጠኛ ግርማይ ገብሩ
በመቐለ ከተማ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
ባንኮች፣ መስሪያ ቤቶች እና ቴሌ ግን ዝግ ሆነው ነው የዋሉት።
የነዋሪዎች መደበኛ ህይወት እንደወትሮው ሁሉ ሰላም ነው።
በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሠራዊት ላይ በትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ ደርሶበት የነበረው ጥቃትን ተከትሎ ሠራዊቱ ህግ ወደ ማስከበር ስራ መግባቱን ሴክሬታሪያቱ በሰጠው መግለጫ አመልክቷል፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እንዳሉት የትግራይ ልዩ ኃይል ከአማራ ክልል ጋር ግጭት እንዲፈጥር የሚታዩ ትንኮሳዎች እየታዩ ነው፡፡
ሠራዊቱ አሁንም ቢሆን የህግ የበላይነትን ለማስከበር እየሰራ መሆኑን የገለፁት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ የትግራይ የመከላከያ ሠራዊት ከትግራይ ህዝብ ጋር ዋጋ በከፈለ የጥቃት ዒላማ መሆኑ የሚያሳዝን ተግባር ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ ክልልም ሆነ ኢትዮጵያ ህዝብ ይህን ተገንዝቦ ከሠራዊቱ ጎን እንዲሰለፍ አሳስበዋል፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው የተፈጠረው ግጭት በአጠቃላይ በፌደራል መንግስቱ እና በትግራይ ክልል መንግስት መካከል ሳይሆን ከተወሰኑ ጥቅመኛ ስብስቦች ጋር የተፈጠረ ግጭት መሆኑን የክልሉ ህዝብ ሊረዳ ይግባል ብለዋል፡፡
የመከላከያ ሠራዊቱ ደርሶበት የነበረውን ጥቃት በማካካስ አሁን ላይ የህግ የበላይነትን የማስከበር ተግባር እና ቦታዎችን የመቆጣጠር ሥራዎችን በመሥራት ላይ መሆኑንም አምባሳደር ሬድዋን ገልፀዋል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ሴክሬታሪያቱም ተጨማሪ መረጃዎችን በቀጣይ ለህዝቡ እንደሚያደርስ አስታውቋል፡፡ ምንጭ፦EBC
ከዚህ በፊት ከመከላከያ ሠራዊት ተቀንሰው የነበሩ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መኮንኖች ወደ መከላከያ ሠራዊቱ እንዲመለሱ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ትእዛዝ ተሰጥቷቸዋል:-
1. ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ
2. ሌ/ጄኔራል ዬሐንስ ገ/መስቀል
3. ሌ/ጄኔራል አበባው ታደሰ

