Blog Archives

መማር የማይችሉ እብዶች የድሃ ልጆችን እያስፈጁ ነው #ግርማካሳ

ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ/ም የብልጽግና አገዛዝ ለአራተኛ ጊዜ ትልቅ ኦፐሬሽን ጀምሯል፡፡ ታላቁ የፊዚክስ ሳይንቲስት አልበርት አነስታይን፣ ” አንድ ነገር እየደጋገሙ በማድረግ የተለየ ውጤት መጠበቅ እብደት ነው” እንዳለው፣ ይህ የነ አብይ አህመእድ ዘመቻ፣ የእብደትና የድንቁርና ዘመቻ ነው፡፡ ነበርሱ እብደትና ድንቁርኛ መከላከያ የተባለውን ተቋም፣ የኦሮሞ ልዩ ኃይልን በግዳጅ ይሁን ብሬን ዎሽ ተድርገው፣ ወይንም በቅንነት አገር እናገለግል ብለው፣ የተቀላቀሉ የድሃ ልጆች እንደ ቅጠል እየረገፉ ነው፡፡ 👉 1ኛው የከሸፈው ዘመቻ የመጀመሪያው ትልቅ ኦፐሬሽን የተጀመረው ሚያዚያ 20 ቀን 2015 ዓ/ም ነበር፡፡ በወቅቱ ፣ “የአማራ ልዩ ኃይል ተበትኗል” ብለው በጀብደኝነትና ህገ ወጥ በሆነ መልኩ አወጁ፡፡ በሁለት ሳምንት ውስጥ ፋኖን ትጥቁን ብቻ ሳይሆን ቀበቶዉንም እናስፈታለን ብለው ዛቱ፡፡ ፋኖዎች ለሶስት ወር በአስደማሚ ሁኔታ ጥቃቶችን መመከት ብች ሳይሆን ከሐምሌ 20 እስከ ሐምሌ 28 2015 ዓ/ም ባደረጉት የስምንት ቀናት ብቻ ዘመቻ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃንን ጨምሮ ከ46 በላይ ከተሞችን፣ ከመቶ በላይ ወረዳዎችን በመቆጣጠር የህዝብ ኃይል ምን ማለት እንደሆነ አሳዩ፡፡ 👉 2ኛ የከሸፈው ዘመቻ አገዛዙ ደነገጠ፡፡ ቆም ብሎ ፣ሽንፈቶቹን አይቶ የተሽለ አቋም ከመውሰድ፣ ችግሮችን በሰላም ከመፍታት፣ በጥጋቡ ላይ ጥጋብ ጨመረ፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ፣ ከነሐሴ አንድ ቀን ጀምሮ ሁለተኛ የማጥቃት ዘመቻዉን አወጀ፡፡ በከተሞች ላይ ከባባድ መሳሪያዎች፣ ድሮኖችን እየተኮሰ፣ ከአለም አቀፍ የጦርነት ስነ መግባር ውጭ፣ ሰላማዊ ዜጎችን የመጨፍጨፍ፣ ታሪካዊ ቅርሶች ለአደጋ የማጋለጥ ተጋብራት መፈጸም ጀመረ፡፡ የጦር ወንጀሎችን፡፡ ሃላፊነት የሚሰማቸው ፋኖዎች፣
Posted in Ethiopian News

የአገዛዙ የ እብደት ሶስተኛ ዙር የመስከረም ዘመቻ #ግርማካሳ

የአብይ አህመድ ኤትኖ ፋሺስቱ የኦሮሞ ብልጽግና አገዛዝ፣ በአማራው ላይ በይፋ ጦርነት የከፈተው ሚያዚያ 20 ቀን 2015 ዓ/ም ነበር፡፡ አምስት ወራት አለፉት፡፡ ብርሃኑ ጁላ፣ “አማራዉን ትጥቁን ብቻ ሳይሆን ሱሬዉን እናስፈታለን” ፣ አበባው ታደሰ ደግሞ ፣ “ህወሃትን ልክ እንዳስገባን እነርሱንም (ፋኖዎች) ልክ እናገባቸዋለን” ነበር ያሉት፡፡ አለቃቸው አብይ አህመድን፣ “አማራዉን ትጥቅ ለማስፈታት የሚፈለገውን መስዋትነት ሁሉ ይከፈላል” ሲልም ነበር የዛተው፡፡ ሰዎቹ ጦርነት ሲከፍቱ፣ “የአማራው ማህበረሰብ በቀላሉ እጁን ይሰጣል፣ በሶስት ሳምንት ውስጥ ትጥቁን እናስፈትዋለን፣ የፋኖ መሪዎችን እንገድላለን ወይንም እናስራለን’ ብለው በመደምደም ነበር፡፡ ወደዚህ ድምዳሜ የደረሱትበ ዋና ምክንያት በዋናነት፣ ላለፉት 5 አመታት፣ ህዝቡ መከራና ስቃይ ሲፈጸምባት፣ ለአገርና ለሰላም ሲል በመታገሱ፣ የህዝቡን ትእግስት እንደ ፈሪነት፣ የህዝቡን ለአገር አሳቢነት እንደ ደካማነት በመቁጠራቸውና በህዝቡ፣ “ከወሬና ከጩከት በቀር ምንም አያደርገም” በሚል ትልቅ ንቀት ስለበራቸው ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ከኮረም፣ አላማጣም፣ ከአላማጣ ቆቦ፣ ከቆቦ ወሊድያ፣ ከወልዲያ ደሴ፣ ከደሴ ደብረ ሲና እያለ ሲያራውጧቸው የነበሩትን ህወሃቶች፣ የአማራ ኃይሎች ማስቆም እንደቻለ መርሳታቸውና ፣ እነርሱም ራሳቸው “እኛ አቅቶናል፡፡ በመደበኛ ሰራዊት የመጣውን አደጋ መከላከል አንችልም” ብሎእው የአማራ ኃይሎች ሲማጸኑ እንደነበረ መዘነጋታቸው ነው፡፡ ከሚያዚየ 20 ቀን እስከ ሐምሌ 20 ቀን ድረስ የአማራ ኃይሎች ራሳቸውን በመከላከል ላይ ነበር ያተኮሩት፡፡ ከሐምሌ 20 እስከ ሐምሌ 28 ባሉት ስምንት ቀናት ውስጥ ፋኖዎች የመጀመሪያዉን የማጥቃት ዘመቻ ከፈቱ፡፡ ከደሴ አካባቢ፣ ከምንጃር ፣ ከኦሮሞ ብሄረሰብ ልዩ ዞን ፣ ከአዊ ዞንና ከዋገመራ ውጭ ያለውን የአማራ
Posted in Ethiopian News

የወሎና የጎንደር የፋኖዎች እንቅስቃሴ #ግርማካሳ

የወሎና የጎንደር የፋኖዎች እንቅስቃሴ #ግርማካሳ ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ/ም የአማራ ማህበረሰብን ትጥቅና ሱሪ እናስፈታለን በሚል በጥጋብና በጀብደኝነት በአማራ ክልል ጦርነት የከፈተው ኦነግ መራሹ የብልጽግና ጦር፣ በሁሉም ቦታ ማለት ይችላል ከፍተኛ ፖለቲካዊም ወታደራዊም ሽንፈቶች እየተከናነበ ነው፡፡ በክልሉ ያሉ በርካታ የብልጽግና የወረዳ አመራሮች፣ ፖሊሶች፣ ሚሊሺያዎች ከህዝብ ጎን ሆነው ከፋኖዎች ጋር እየሰሩ ነው፡፡ በብዙ ቦታዎች ጊ ብዙ ሳይደረጉ፣ የወረዳ አመራሮች ከጎን በማሰለፍ አካባቢዎችን ነጻ ማውጣት ተችሏል፡፡ በሌሎች ቦታዎች ፋኖዎች ለዘረኛው አገዛዝ ታዛዥ የሆኑ የወረዳም ሆነ የዞን ሚሊሺያዎችና ፖሊሶች እንዲሁም በወረዳዎቹ የተሰማሩ የመከላከያ ጦር አባላት ጋር ተናንቀው፣ ከህዝቡ ጋር በመሆን ነጻ ያወጧቸው ወረዳዎችም ቀላል አይደሉም፡፡ በዚህም ሆነ በዚያ አገዛዙ አንገት አስደፋለሁ ብሎ አንገቱን እንዲደፋ፣ ልክ አስገባለሁ ብሎ ልኩን እየገባ ያለበት ሁነታ ነው ያለው፡፡ የወሎ እንቅስቃሴዎች =========== እነ ሰቆጣ፣ ላስታን በሰሜን ደቡብ አቅጣጫ ከነ ተንታና ወረኢሉ፣ ወልዲያን ደብረ ታቦርን፣ በምስራቅ ም እራብ አቅጣጫ፣ የሚያገናኙ መንገዶች የሚተላለፉባት ፣ እጅግ በጣም ወሳኝ በሆነችው በጋሸና ከተማ፣ የአማራ ኃይሎች መግባታቸው በአገዛዙ ካምፕ ያሉትን በእጅጉ አስደንግጧል፡፡ የነጋሸናን መያዝ ተከትሎ፣ በጋሸናና በወልዲያ መካከል የምትገኘው ሐሙሲትን፣ እስታይሽን እንዲሁም ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ/ም፣ ከሰሜን ጎንደር ዞን ዋና ከተማ ታላቋን ወልዲያ ፣ በጥቂት ኪሎሜተር ርቅት ላይ ያለችውን የሳንቃ ከተማ በድንገተኛ ጥቅት የአማራ ኃይሎች ተቆጣጥረዋል፡፡ በምእራብ ወሎ፣ በአማራ ሳይንትና በለጋምቦ ወረዳ አካባቢ ፋኖዎች ከፍተኛ እንቅስቃሴ እይደረጉ ነው፡፡ በአምባሳል ወረዳ ፣ ኡርጌሳም ትንቅንቅ ያለ
Posted in Ethiopian News

የሶስት ወር አጭር የአማራ ክልል ጦርነት ዘገባ #ግርማካሳ

አብይ አህመድ፣ ብርሃኑ ጁላና የኦሮሙማ ጓዶቻቸው ፣ አንደኛ የነማይክ ሃመርን ድግፍና ከውጭ ገንዘብ ለማግኘት፣ ከህወሃት ጋር በመናበብና በመቀናጀት ፣ ህወሃቶች እነ ወልቃይትን ለመቆጣጠር እንዲያመቻቸው፣ ከወዲሁ ፋኖዎችን ትጥቅ ለማስፈታት፣ ሁለተኛ ፣ “በመሃል አገር ታላቋን ኦሮሚያ እንዳንመሰረት ችግር የሚሆንብን አማራው ስለሆነ፣ አማራውን መሰበር አለብን፡፡ አማራውን ትጥቁን ብቻ ሳይሆን ሱሪዉን እናስፈታለን” በሚል፣ በጥጋብና በጀብደኝነት ጦርነት የከፈቱት፣ ሚያዚያ 20 ቀን 2015 ዓ/ም ነበር፡፡ ሐምሌ 20 ቀን 2015 ዓ/ምን አለፍን፡፡ ጦርነቱ ሶስት ወራትን ደፍኖ፡፡ በመከላከል ላይ አተኩሮ የነበረው ፋኖ በትንሹም ቢሆን ወደ ማጥቃት የተሸጋገረበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ አገዛዙ ከመሃል አገር ወታደር በየብስ የሚያመላልሰው፣ ስንቅና ትጥቅ፣ ሎጂስቲክ የሚያቀርበው፣ በአዋሽ፣ ሚሌ በኩል አድርጎ ነው፡፡ ከሚሌ በካሳጊታ ባቲ አድርጎ ወደ ወሎ ኮምቦልቻ፣ ከሚሌ በጭፍራ፣ ሃራ፣ ጉብዬ አድርጎ ወደ ወልዲያ ባለው መስመር ነው፡፡ ኮምቦቻልቻና ወልዲያ ለአገዛዙ ከሎጂስቲክ አንጻ በጣም አስፈላጊ ናቸው፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ፣ ከመሃል አገር በደጀን በኩል ወደ ጎጃም መሄድ የማይታሰብ ነው፡፡ በድብረ ብርሃኑ፣ ደብረ ሲና በኩል የግል መኮኖች ካልሆኑ ወታደሮችን ማመላለስ አይቻልም፡፡ ከኮምቦልቻ በመካነ ሰላም አድርጎ ወደ ጎጅማ መርጦ ለማሪያም የሚሄደው አይቻልም፡፡ የቀረችው ከወልዲያ በጋሸና በኩል ወደ ደብረ ታቦር፣ ወሮታ አድርጎ ወደ ሰሜን ወደ ጎንደር፣ ወደ ድቡብ ወደ ባህር ዳር የሚወስደው መንገድ ነው፡፡ ይህንን መንገድ አገዛዙ መጠቀም እንዳይችል ተደርጓል፡፡ 1ኛ # በሰሜን ወሎ ዞን፣ መስቀለኛና ስትራቲጂክ ቦታ ላይ የምትገኘው፣ ከህወሃት ጋር ጦርነት ሲደረግ ብዙ ጊዜ ስትያዝ፣
Posted in Ethiopian News

የብልጽግና ጦር  ህዝብ ይገድላል፣ ፋኖ ህዝብን ለማዳን ይዋደቃል #ግርማካሳ

አብይ አህመድ በአማራ ብልጽግና ገጽ ላይ፣ ባለፉት ሁለት ቀናት ብቻ መከላከያን አስመልክቶ ሶስት ተመሳሳይ መግለጫዎች እንዲወጣ አድርጓል፡፡ “መከላከያ ሠራዊታችን የሀገራችን የመጨረሻው ምሽግ እና የኢትዮጵያ የከፍታ ማማ ነው”፣ “ሁለገቡ የኢትዮጵያ ኩራት” እና “”የአማራ ህዝብ ትናንት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ደጀን ነበር ፤ ዛሬም አስተማማኝ ደጀን ሆኖ ይቀጥላል ” በሚሉ ርእሶች፡፡ ተመሳሳይ መግለጫዎች በተደጋጋሚ ለምን ማውጣት አስፈለ ? ብሎ መጠየቁ አስፈላጊ ነው፡፡ ዋልተር ላንገር የተባለ አሜሪካዊ የስነ አይምሮ ጠበብት፣ “ትልቅ ውሸት፣ ተደጋግሞ ከተነገረ እንደ እውነት ይቆጠራል፣ ( “If you tell a big enough lie and tell it frequently enough, it will be believed.) እንዳለው፣ ውሸትን ደጋግሞ በመጻፍና በመናገር በህዝቡ አይምሮ ለመጫወት ያሰቡ ይመስላል፡፡ ምን አልባትም ዙሪያቸው ያሉ የስነአይምሮ ባለሞያዎች የመከሯቸው ሊሆንም ይችላል፡፡ አንድ ውሸት ተደጋግሞ ሲነገር የሚዋሸው ሰው የለየለት ውሸታም መሆኑ ሰዎች ካወቁ፣ ሰምተው ንቀው ይተውታል እንጂ ስውዬው የተናገረውን እንደ እውነት የሚቀበል አይኖርም፡፡ የነ ዋልተር ላንገር አባባል የሚሰራው፣ የሚዋሸው ሰው ቢያንስ በህዝብ እንደ ውሸታም የማይቆጠር ከሆነ ነው፡፡ ለዚህም ነው ላለፉት 5 አመታት፣ ህዝብ፣ በዶር አብይ አህመድና በብልጽግናዎች ላይ ትንሽ ቢሆን እምነት ስለነበረው፣ ሲዋሹ፣ ሲሸረድዱ የነበረውን ነገር፣ እንደ እውነት ሲቀበል የነበረው፡፡ በመልካም ቃላቶች ህዝቡን ግራ ሲያጋቡትና ሲያወናብዱት ነበር፡፡ ባዶ ተስፋ እየሰጡት አጋንጦ እነርሱን ብቻ እንዲጠብቅ ሲያደርጉት ነበር፡፡ አሁን ግን ሁኔታ እጅግ በጣም ተቀይሯል፡፡ አብይ አህመድና ጨምሮ ጓዶቹ የለየላቸው ውሸታሞች (Certified liers) መሆናቸውን ህዝብ አውቋል፡፡
Posted in Ethiopian News

አይሁድነት ለናዚዎች እንደነበረው፣ አማራነትም ለኦህዴድ/ብልጽግዎች ነው #ኖሃሚን በጋሻው

ገዢው የብልጽግና አገዛዝ፣ ራሱን ከኢህአዴግ አገዛዝ የተሻለ አድርጎ ሲያቀርብ እየተመለከትነው ነው፡፡ “‘እኔ ብቻ ነኝ ልክ – አይሰራም” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ፣ በህወሃት ጊዜ የዜጎች ሃሳብ በግለሰብ ሃሳብ ይጨፈለቅ ነበር ካለ በኋላ፣ ስለራሱ ሲያወራ ግን ፣ “ብልጽግና ነፃ በሆነ መንገድ በሚንሸራሸር ሃሳብ የራሱን የበሰለ እና ተራማጅ አስተሳሰብ ይዞ አገራችንን ከፍ ለማድረግ የሚተጋ ፓርቲ ነው” ነው ሲል የዜጎችን የመጻፍ፣ የመናገር፣ ህሳባችውን በነጻነት የመግለጽን መብት እንደሚያከብር ለመግልተ ሞክሯል፡፡ የብልጽግና ሰዎች የመግለጫ ጋጋታ ሲያወጡ፣ በዚህ ሊቅ ሲዋሹ፣ ህዝቡን ቢንቁት፣ እንደው የራሳቸው ህሊና ፣ የቅርብ ወዳጆቻቸውን፣ ቤተሰቦቻቸው ምን ይሉናል ብሎ አለማሳባቸው አስገራሚ ነው፡፡ የብልጽግና ገዢዎች፣ የዜጎችን የመናገር፣ የመጻፍ፣ አስተያየት የመስጠት መብት መርገጥ ብቻ አይደለም፣ ዜጎች ሳይጽፉም፣ ሳይናገሩም፣ በፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ሳይሳተፉም፣ ምንም አይነት ትችት በአገዛዙ ላይ ሳያቀርቡም፣ በማነንታቸው፣ አማራ ስለሆኑ ብቻ በመቶ ሺሆች፣ ከፍርድ ቤት ማዘዣ ሳያመጡ ያፈኑ ፣ አስረው እያሰቃዩ ያሉ አሸባሪዎች ናቸው፡፡ ማሰር ቀላል፣ በማንነታቸው ብቻ ዜጎችን እያፈናቀሉ፣ ቤቶቻቸውን እያፈረሱ፣ ህጋዊ ድሆች አደረግን ብለው የሚደነፉ፣ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳቶችን እየፈጸሙ ያሉ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማያውቅ እጅግ በጣም ክፉና አረመኔ ገዢዎች የሆኑ ናቸው፡፡ በአዲስ አበባ ነው፡፡ ይህ ወንድም በሰፈሩ፣ በመልካም ስራው፣ ችግረኞችን፣ ድሆችን ፣ ደካሞችን በማገዝና በመጠየቅ የሚታወቅ ነው፡፡ በሰፈሩ አንዲት ድሃ፣ የአካል ጉዳተኛ እህት አለች፡፡ እርሷን ለማገዝና ለመርዳት ወደ ቤቷ ይሄዳል፡፡ ከዚች እህት ጋር እያለ፣ ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ/ም የኦህዴድ/ብልጽግና ታጣቂዎች መጡ፡፡ በር
Posted in Ethiopian News

እጅ አንስተው ማሉ፣ ከኦህዴድ ጋር ወግነው በህዝብ ላይ እጅ አንስተው ዱላ አሳረፉ #ግርማካሳ

“ለራሳቸው ክብር ባይኖራቸውም፣ ራሳቸውን የሚወዱ በመሆናቸው፣ የኦህዴዶች ተላላኪና ተልክስካሽ መሆን በአሁኑ ወቅት ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ተረድተው፣ ለራሳቸው ሲሉ ኦህዴዶችን እምቢ ማለት ይጀምሩ ይሆናል” በሚል የአማራ ክልል ምክር ቤት ቢያንስ አሁን እንኳን ከህዝብ ጋር ይወግናል የሚል ግምት ነበረኝ፡፡ ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋዬ የደቡብ ወሎ ቃሉ ወረዳ ተወካይ ናት፡፡ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈጉባዬ ፡፡ አቶ አማረ ሰጤ በጎንደር፣ የአለፋና ታኩሳ ወረዳን ወክሎ፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዬ ነው፡፡ ዶር ይልቃል ከፍያለ፣ በጎጃም በዱር ቤቴ ወረዳ ህዝብ ተመርጦ፣ የክልሉ ምክር ቤት አባል የሆነና በክልሉ ምክር ቤት የክልሉ ርእስ መስተዳደር የሆነ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ያለ ህዝብ ምንም አይደሉም፡፡ አለን ያሉትን ሁሉ ስልጣን ያገኙት ከህዝብ የተነሳ ነው፡፡ ተመርጠው ስራ ሲጀምሩም፣ እጆቻቸውን አንስተው ቃለ መሃላ አድርገዋል፡፡ “ህዝብን እናገለግላለን፣ ታማኝነታችን ለህዝብ ብቻ ነው” ብለው፡፡ ሆኖም ግን መሃላቸውንና የገቡትን ቃል ረስተው፣ በህዝቡ ላይ ክህደት ፈጽመው፣ ህዝብን ከማገለገለና ከመጠበቅ፣ ህዝቡን ለችግርና ለመከራ ዳርገውታል፡፡ ፣ ህወሃቶች ተፈናቃዮች ካልተመለሱ እያሉ ሌትና ቀን ሲሰሩ፣ እነርሱ በመሪነት ቦታ ተቀምጠው፣ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ከኦሮሞ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎችን ጉዳይ ያደረጉት ነገር የለም፡፡ በአማራ ክልል በአብይ አገዛዝ ጦርንበት ሲከፈትም ማስቆም አይደለም፣ ከዝህብ ጋር ሆነ የአብይን አገዛዝ መመከት ሲገባቸው ተባባሪ ነው የሆኑት፡፡ በአብይ አህመድ ትእዛዝ በአስር ሺሆች የህዝብ ልጆች ፣ ፋኖዎችን አስረው እያሰቃዩ ነው፡፡ ምክር ቤት ሳይፈቅድ፣ የክልሉ መንግስት ጥሪ ሳያቀርብ፣ በነ አብይ አህመድ ጀብደኝነትና
Posted in Ethiopian News

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ፣ “ህዝብ ይወቅልን” እያሉ ነው #ግርማካሳ

በወልቃይት ጉዳይ ላይ ዶር አብይ አህመድ ከተወሰኑ የአማራ ክልል አመራሮች ጋርና  ከህወሃት ሰዎች ጋር በተናጥል ስብሰባ ማድረጉ በስፋት ተዘግቧል፡፡ ከህወሃቶች ጋር ባደረገው ውይይት፣ እነ ወቅላኡይትን ህወሃቶች እንዲረከቡ ፍላጎት እንዳለው የገለጸላቸው ሲሆን፣ በፌዴራል መንግስት ደረጃ የቻለውን ሁሉ እንደሚያደርግ ቃል መግባቱን አንከር ሜዲያ ዘግቧል፡፡ አንከር ሜዲያ ሲያክልም፣ አማራዎች ፍቃደኛ ካልሆኑ፣  እና እዚህ እናዳክምላቹሃልን፣ በስንቅ በትጥቅ እናግዛቹሃለን፣ ራሳችሁ በጦርነት ያዙ” የሚል አስተያየት እንደሰጡም አትቷል፡፡ የቻልኩትን አድርጋለሁ ባለው መሰረትም፣ የአማራ ክልል ሃላፊዎችን በመሰብሰብ  ማስፈራሪያና ዛቻ አዘል መመሪያዎች ለመስጠት ሞክሯል፡፡ ከአብይ አህመድ ጋር የተመካከሩትና የተስማሙት የአማራ ክልል አመራሮች አምስት እንደነበሩ ኢትዮ ኒዉስ ዘግቧል፡፡ እነርሱም የክልሉ ርእስ መስተዳደርና ምክትል ርእስ መስተዳደር፣ ዶር ይልቃል ከፍያለ እና ዶር ጌታቸው ጀምበር፣ ዶር ሰማ ጥሩነህ፣ የደቡብ ጎንደር አስተዳዳሪ የነበረውና ለአብይ አህመድ ባለው ትልቅ ታማኝነት፣ አሁን ግርማ የሺጣላን ተክቶ የአማራ ብልጽግና ጽ/ቤት ሃላፊ የሆነው አቶ ሲሳይና ፣ አቶ ስዩም መኮንን ናቸው፡፡ በዚህ ስብሰባ አብይ አህመድ ቀጭን ትእዛዝና መመሪያ አስተላልፎላቸዋል፡፡ “በወልቃይት ጠገዴና ቃፍታ ሁመራ፣ በጠለምትና በራያ የዘረጋችሁት የአማራ ክልል መስተዳደር ጠራርጋችሁ አስወጡ” የሚል፡፡ እነ ወልቃይትን ምእራብ ትግራይ በሎ በመጥራት ፣ ከዚያ የተፈናቀሉ በሙሉ እንዲመለሱ መመሪያ ሰጥቶ ፣ ተፈናቃዮችንም በተመለከተ፣ በስብሰባው የተገኙ የአማራ አመራሮች አሜን ብለው ተቀብለዋል፡፡ይህ ብቻ አይደለም፣ እነዚህ የአማራ ክልል አመራር ነነ የሚሉትን ህወሃቶች በፈለጉት መንገድ ፣ ህዝብ ውሳኔ የተባለውን ተቀብለው ለመተግባር ቃል ገብተዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ኮሎኔል ደመቀ አስተያየት እንደሰጡ
Posted in Ethiopian News

ታልቅ ክህደት በብአዴኖች በወልቃይት/ራያ/ጠለምት ህዝብ ላይ #ግርማካሳ

ወልቃይት በተመለከተ አብይ አህመድ በፓርላማ ያው የተለመደውን አስተያየት ሰጥቷል፡፡ በቅቤ የተለወሰ፣ ለአማራ ማህበረሰብ አሳቢ በመመስል የቀረበ ጸረ አማራ መርዛማ አስተያየት፡፡ ” በመሬት ምክንያት መባላት ፣ መገዳደል አያስፈልግም ፤ መሬት የፀብ ምንጭ መሆን የለበትም፤ “ህዝቦች ተወያይተው ተመካክረው በ ‘ win win approach ‘ ጊዜ ወስደው በሰከነ መንገድ የትኛው ክልል መኖር እንደሚፈልጉ መወሰን ይችላሉ ፤ ይህንን ሲዳማ ላይ አድርገነዋል፣ ደቡብ ምዕረብ ላይ አድርገነዋል፣ ትላንትም ወስነናል ስለዚህ በሰከነ መንገድ ሰዎች ወስነው ሰው ሳይሞት ማድረግ ይቻላል ፤ ከዛ ውጭ ያለው አማራጭ ጥሩ አይደለም:: መነጣጠቅ ጥቅም የለውም፤ ዘላቂ ሰላም ማምጣት ያስፈልጋል:: አማራን እንዳለ ቆርጦ ከትግራይ ጉርብትና ማንሳት አይቻልም:: ትግራይንም እንዲሁ ፤ አብሮ የሚኖር ህዝብ ነው ፤ ዋናው አስፈላጊ ነገር ሰላም ነው ፤ ይሄን ታሳቢ በማድረግ ፦ በሰከነ መንገድ በውይይት፣ የተፈናቀለውን መልሰን፣ የተጎዳውን ጠግነን፣ የተጣላውን አስታርቀን ፣ በህዝብ ውሳኔ ነገሮች በህጋዊ መንገድ ለዘለቄታው እልባት እንዲያገኙ በልበ ሰፊነት ካልሰራን በስተቀር ጥፋት ነው ፤ ብንዋጋም ዘላቂ ድል አናመጣም” ነበር  ያለው፡፡ ራሱን የአማራ ክልል መንግስት ነኝ ብሎ የሚጠራው የብአዴን ወይንም የአማራ ብልጽግና ስብስብ፣ “ወልቃይት ቀይ መስመራችን ነው” ሲሉ እንዳልነበረ፣ በቃል አቀባዩ ግዛቸው ሙሉነህ በኩል፣ የጌታቸው ረዳንና አብይ አህመድ፣ የሕወሃትና የኦህዴድ ፍላጎትና አቋምን ማስተጋባት ጀምሯል፡፡  እንወክለዋለን ባሉት ማህበረሰብ ላይ፣ እጅግ በጣም ትልቅና ኣሳፋሪ ክህደት በመፈጸም፡፡ “የማንነት እና የወሰን ጥያቄ ቢያንስ ከ30 ዓመት በኃላ በሕዝበ ውሳኔ በሕጋዊ መንገድ እንዲያልቅ ስራዎች እየተሰሩ
Posted in Ethiopian News

እነ አብይ አህመድ በሰላም ከመልቀቅ ውጭ ምርጫ አይኖራቸውም #ግርማካሳ

ከሁመራ እስከ ምንጃር አረርቲ፣ ከጃዊ እስከ ኮምቦልቻ፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ፣ የአማራ ክልል ህዝብ፣ በገጠር በሉ በከተማ፣ ትንሹ በሉ ሽማግሌው፣ ሙስሊሙ በሉ ክርስቲያኑ፣ ጎጃም በሉ ጎንደር፣ ሸዋ በሉ ወሎ፣ ሴት በሉ ወንድ፣ በሁሉም፣ በሁሉም ቦታ፣ ለመብቱ፣ ለነጻነቱ፣ ለህልውናው ድምጹን እያሰማ፣ የህዝብ ኃይል ምን ማለት እንደሆነም እያሳየ ይገኛል፡፡ ለአገር፣ ለህዝብና ለሰላም ሲል፣ በህወሃት ጊዜ ጀምሮ፣ በብልጽግና ዘመን የቀጠለው የማያባራው፣ በአማራ ላይ የሚፈጸመውን ግፍ፣ ሰቆቃ፣ ኢፍትሃዊነት፣ ሲስተማቲ አፓርታይዳዊና ናዚዛዊ ጥቃትን ለረጅም ጊዜ ታግሶ ቆይቷል፡፡ ሆኖም በተለይም የአሁኖቹ ናዚዛዊ የኦሮሙማ ገዢዎች ፣ የህዝቡን ትእግስት እንደ ፍርሃት፣ የህዝቡን ለአገር ብሎ ግፍን ተሸክሞ ለመቀጠል ትከሻዉን ማስፋቱን እንደ ደካማነት፣ ቆጥረው፣ ህዝቡን ንቀውት፣ ገደብ የለሽ፣ ዘረኛና ሰይጣናዊ ተግባራቶችን በመፈጸም፣ የአማራ ማህበረሰብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር ሆኖ ከገነባትና ካቆማት አገሩ ሊያጸዱት ተነስተውበታል፡፡ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጻዳት ናዚዛዊና ኢንተርሃይሚያዊ ስራቸውን ጀምረዋል፡፡ ከዚህም የተነሳ የግፍ ጽዋ ሞልቶ ስለፈሰሰ፣ ትእግስትም ልክ ስላለው፣ የአማራው ማህበረሰብ እምቢኝ ብሎ ተነስቷል፡፡ አምሯል፡፡ በተለይም በአማራ ክልል ነገሮች ተደበላልቀዋል፡፡ አሳዳጅ የነበሩ መሳደድ ጀምረዋል፡፡ ህዝባዊ አብዮት፣ የህዝብ ቁጣ እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለ ነው፡፡ ሰዎቹ የተኛውን አንበሳ ቀስቅሰውታል፡፡ በአማራ ክልል የተደረጉ ሰልፎችና ተቃውሞዎች በሶስት የሚከፈሉ ናቸው፡፡ የመጀመሪያ በወረዳ የብልጽግና አመራሮች ድጋፍና እውቅና የተደረጉ ሰልፎችና ተቃውሞዎች ናቸው፡፡ ሁለተኛው ያለ ብልጽግና አመራሮች በፍቃድ ህዝብ ገንፍሎ ወጥቶ የተደረጉ ሰላማዊ የ እምንቢተኝነት እንቅስቃሴዎችን ሰልፎች ሲሆኑ፣ ሶስተኛው የትጥቅ ትግል ውጊያ የተደረገባቸው እንቅስቃሴዎች ናቸው፡፡ በወረዳ ብልጽግናዎች
Posted in Ethiopian News

አገዛዙ ህዝብን ማሸነፍ አይችልም #ግርማካሳ

የኦህዴድ/ኦነግ ጀነራሎች፣ እነ ብርሃኑ ጁላ ደረታችውን ነፍተው የአማራውን ማህበረሰብ እናንበረክካለን ብለው እየፎከሩ ነው፡፡ ምን አልባት አሰለጠንን ያሉትን ሰራዊትና በኢትዮጵያ ህዝብ ገንዘብ የገዟቸውን ድሮኖችና ከባባድ መሳሪያዎች ተመክተው ሊሆን ይችላል፡፡ የአገዛዙን ጥሪ ተቀብለው እጅ የሰጡትና ትጥቃቸውን የፈቱት የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት ከ10% እስከ 25% ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገመታል፡፡ 25% ነው ብለን ብንወስድ፣ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት ቢያንስ ከ75% በላይ ፋኖን ተቀላቅለዋል፣ ወይንም ጫካ ገብተዋል ማለት እንችላለን፡፡ በአማራ ክልል ምን ያህል የልዩ ኃይል አባላት እንዳሉ ባይታወቅም ከ60 ሺህ እስከ 100 ሺህ ሊደርስ ይችላል፡፡ ቁጥሩን አሳንሰነው 60 ሺህ ነው ያለው ብለን ብንወስድ፣ ቢያንስ 45 ሺህ የልዩ ኃይል አባል በአገዛዙ ላይ ያመጸ ነው ማለት ነው፡፡ የአማራ ልዩ ኃይሎች ከፋኖ አደረጃጀቶች ጋር፣ ከአማራ ሚሊሺያዎች ጋር ሲደመሩ ደግሞ፣ ቢያንስ ከመቶ ሺህ በላይ የታጠቀ የአማራ ህዝባዊ ሰራዊት አባላት ይኖራሉ፡፡ እነ አብይ አህመድና ብርሃኑ ጁላ፣ ከጥጋባቸው ሰከን ብለው፣ የህዝቡን ጥያቄ ለመስማትና ለመመለስ ካልተዘጋጁ፣ የህዝቡ ላይ የከፈቱትን ጦርነት ካላቆሙ፣ ያለ ምንም ጥርጥር በአማራ ክልል ከፍተኛ ውርደትና ሽንፈትን ነው የሚከናነቡት፡፡ ይሆን ስል በስሜት አይደለም፡፡ በምክንያት ነው፡፡ ለማያሻንፉት፣ ያቀዱትን ለማያሳኩት ወደ አላስፈላጊ ቀውስና ጦርነት አገሪቷን እንደገና ባይከቷት ይሻላል፡፡ ሰለም እንዲመጣ የሚፈልጉ ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች እንዳይጠፋ ራሱን የሚከላከለውን ሳይሆን፣ ለማጥፋት ለመግደል የተነሳውን አራት ኪሎ ያለውን ቡድን ይምከሩ፡፡ ለምን በብርሃኑ ጁላ የሚመራው ጦር በቀላሉ እንደሚሸነፍ ለማስረዳት ልሞክር፡ 1ኛ ምክንያት – የአዲስ አበባና የጅቡቲ
Posted in Ethiopian News

በወልቃይት-ጠገዴ የዘመናት ጥያቄ ላይ የሚሰራ ስህተት ..(የወልቃይት/ጠገደ/ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

*የጨለማ አበጋዞች ከትንሳኤያችን አያስቀሩንም!!* በቅድሚያ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! አደረሰን! በክርስትና ኃይማኖት አስተምህሮ መሰረት ከትንሳኤው በፊት መከራና ፈተናዎች አሉ፡፡ የእውነት መንገድ በፈተና የተሞላ ስለመሆኑ ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን ወደዚች ምድር ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ቀራኒዮ ድረስ በከፈለው ዋጋ እንረዳለን፡፡ ክርስቶስ ሞትን ድል የነሳበት የመከራ መንገድ ለእውነት ሊከፈል ስለሚገባው ዋጋ ሕያው ተምሳሌት ነው፡፡ በዚህ ተምሳሌት፣ በትንሳዔ ጉዞ ውስጥ ሕማማት ስለመኖሩ እንገነዘባለን፡፡ ሕማማት የፈተናዎች መብዛት፣ ከዓላማቸው ወጥተው የሚክዱን መኖር፣ ለጊዜያዊ ጥቅም የመንበርከክ፣ ዘላቂውን ሳይሆን በዕለት ፍላጎት ተጠልፎ መውደቅ የሚበዛበት የፈተና ወቅት ነው፡፡ ነገር ግን ለሚበረቱ ሁሉ ድል ከእነርሱ ጋር ነውና በፈተናዎች መጽናት ትንሳኤን ያቀርባል፡፡ ትንሳኤ ዋጋ ተከፍሎበት የሚመጣ የመዳን ብስራት ነውና ከትንሳኤው በፊት ዋጋ የከፈለልንን ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስን እንደምናመሰግን ሁሉ ዛሬ ኢትዮጵያ ለምትገኝበት አንፃራዊ ሠላም ዋጋ የከፈሉ የኢትዮጵያ ልጆችን እናመሰግናለን፡፡ ኢትዮጵያ ህልውናዋ አደጋ ውስጥ በገባ ጊዜ የሕይወትና የአካል መስዋዕትነት ከፍለው አደጋውን የቀለበሱ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ለሰሩት የማይሞት ታሪክ ሁሌም ቢሆን ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል፡፡ የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል ስናከብር፡- ተጋምደንና ተዋሕደን በኖርበት የኢትዮጵያዊ አብሮነት ስሜት ችግረኞችን በመርዳት፣ የታመሙትን በመጠየቅ፣ በየካምፓቸው የሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የልዩ ኃይል ፖሊሶችን፣ የሚሊሻና ሠላም አስከባሪ ወንድም እህቶች ጋር በፍቅርና በደስታ የትንሳኤ በዓልን እንድናከብር ጥሪየን አስተላልፋለሁ፡፡ የወልቃይት-ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሕዝብ ትላንትም፣ ዛሬም ሆነ ነገ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያዊነት ክብር ዘብ
Posted in Ethiopian News

የብልጽግና ትሩፋቶችና የዘር ፖለቲካ መዘዞች ፣ እልቂት፣ ጦርነትና ድህነት #ግርማካሳ

ላለፉት 10 ቀናት፣ ከመጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በአማራ ክልል የተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞ በማያሻማ መልኩ አንድ ግልጽ ያደረገው ነገር አለ፡፡ እርሱም በአንድ ወይንም በሁለት ቦታ ብቻ አይደለም፣ በመላው ጎጃም፣ ጎንደር፣ ወሎና ሸዋ፣ ህዝብ አራት ኪሎ ላለው ተረኛውና ዘረኛው አገዛዝ ያለውን ምሬትና ተቃውሞ ነው፡፡ የአማራ ክልል አሁን መንግስት አለው ማለት አይቻልም፡፡ መከላከያ በሚል ስም የተረኛው ቡድን ታጣቂዎች በታንክና በመድፍ ታግዘው ትላልቅ ከተሞችን ለመቆጣጠር እየሞከሩ ነው፡፡ በብዙ ቦታዎች ከፍተኛ ግጭቶች ፣ ወታደራዊ ሳይቀር ተከስተዋል፡፡ ሰላማዊ ዜጎች ሞተዋል፡፡ ከአማራ ሃይሎችም ፣ መከላከያ ነን ካሉትም፣ ብዙ ሰዎች ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡ ዶር ይልቃል ከፍያለ የቁም እስረኛ ናቸው እየተባለ ነው፡፡ ግርማ የሺጣላ ፣ የአማራ ብልጽግና ጽ/ቤት ሃላፊ፣ በአማራ ክልል የአብይ አህመድ ቀኝ እጅ፣ 30% የአማራ ልዩ ኃይል ከካምፕ እንደወጣ ተናግሯል፡፡ “ከካምፕ ወጥቶ ፣ መሳሪያዎቹን እንደያዘ የት ነው የሄደው ? ” የሚለውን ለመመለስ የሚከብደው ሰው ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡ 70% በካምፕ ያሉ የልዩ ኃይል አባላት ደግሞ “ትጥቅ አንፈታም”ብለው የተቀመጡበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ እስከአሁን የነ አብይ አህመድ ሩጫ፣ ማስፈራራት፣ ዛቻና ወታደራዊ እንቅሳሴዎች ሽንፈትን ከማስተናገድ ውጭ ያሳከው ምንም ነገር የለም፡፡ አንድ የአማራ ልዩ ኃይል አባላ ትጥቁን አልፈታም፡፡ የአማራ ብልጽግናዎች ላለፉት 3 ቀናት የኃይማኖት አባቶችን፣ ሽማግሌዎችን፣ “እኛ የአማራ ልዩ ኃይሎችን ትጥቅ ለማስፈታት ሀሳብ የለንም” በሚል ዉሸትና ቅጥፈት፣ መረጋጋት እንዲመጣ እንዲያግዟቸው ሲማጸኑም እንደነበረ በስፋት ተዘግቧል፡፡ ከዚህ በኋላ ሊከሰት የሚችለውን በመስጋት፣ ባህር ዳር
Posted in Ethiopian News

የአማራ ክልል ውሎ፣ ሚያዚያ 3 ቀን 2015 ዓ/ም #ግርማካሳ

የአማራ ክልል ከ9 ቀናት በፊት ሰላም ነበር፡፡ በዚያ ያሉ የአማራ ልዩ ሃይሎችም የክልሉን ጸጥታ፣ አኩሪና አስደሳች በሆነ ሁኔታ ነበር ሲያስጠብቁ የነበሩት፡፡ በአማራ ክልል ብቻ አይደለም፣ እነ ብርሃኑ ጁላ የሚመሩት መከላከያ ማድረግ ያልቻለውን፣ የቤኔሻንጉል ክልል መንግስት፣ እነ አሻድሊ ሁሴን በጠየቁት መሰረት፣ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ወደ መተከል እንዲገባ ተደርጎ፣ በዚያ የነበረው እልቂት በእጅጉ የቀነሰበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ በመተከል በፊት እንደምንሰማው አይነት እልቂት ከሰማን ረጅም ጊዜ ሆኗል፡፡ይህ በአማራ ልዩ ኃይሎች ትልቅ ገድል የተነሳ ነው፡፡ እንግዲህ ሰላም ያለበትን ቦታ ነው፣ ከህወሃቶች ጋር ተስማምቶ፣ የአማራ ልዩ ኃይሎችን ትጥቅ ማስፈታት አለብኝ በሚል ጥጋብና ማን አለብኝነት ተወጥሮ፣ አብይ አህመድ ቀውስና ግጭት እንዲፈጠር ያደረገው፡፡ የብልጽኛ አገዛዝ አገር ገንቢ ሳይሆን አገር አፍራሽ፣ ቀውስ አስወሃጅ፣ ችግር ፈቺ ሳይሆን፣ መወገድ ያለበት ቀውስና ግጭት ጠማቂ ነው የምንለው፡፡ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ዘመቻው ============== በአማራ ክልል፣ መጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ/ም የተጀመረው ህዝባዊ ተቃውሞ 9 ቀን ሆነው፣ አሁንም በተጠናከረ መልኩ እየቀጠለ ነው፡፡ ከ50 በላይ ከተሞች በእንቅስቃሴ ላይ ናቸው፡ እውነት ለመናገር የት ከተማ እንቅስቃሴ ተደረገ ከማለት፣ የት ከተማ አልተደረገም ብሎ መጠየቁ ነው የሚሻለው፡፡ ምስራቅ ጎጃም ሞጣ፣ ደቡብ ምእራብ ወሎ መካነ ሰላም፣ የአዊ ዞኗ ጃዊ፣ በሰሜን ሸዋ ደብረ ሲናና ሌሎችም ተቃውሞዉን ተቀላቅለዋል፡፡ በደብረ ብርሃን፣ በጃዊ፣ በኮምቦልቻ፣ በመራዊ፣ በወረታ፣ በደጀን፣ በቆቦ የተረኛው አገዛዝ ታጣቂዎች በርካታ ሰላማዊ ዜጎችን፣ በተቃውሞ የተሳተፉ ወጣቶችን ገድለዋል፡፡ የተሰው ወገኖች ቁጥር ከ40 ሊበልጥ እንደሚችል
Posted in Ethiopian News

የአማራ ክልል ውሎ (ሚያዚያ 1 ቀን 2015 ዓ/ም) #ግርማክስ በአማራ ክልል፣ በኦነጋዊው የአብይ አህመድ ተረኛውና ዘረኛው አገዛዝ ላይ ህዝባዊ ተቃውም ከተጀመረ አንድ ሳምንት ሆነው፡፡ የህዝብን ጥያቄ ከማዳመጥና ችግሮችን ከማለዘብ ይልቅ፣ ግጭትና ቀውስ ጠማቂ የሆነው የአብይ አህመድ አገዛዝ የአማራ ክልልን ፣ ከሰላማዊነት ወደ ቀውስ ቦታ እየወሰደው ነው፡፡ አንድ ሚሊዮን ዜጎቿን በጦርነት ባጣችና፣ በቅርብ ከጦርነት ባረፈች አገር፣ አንፃራዊ መረጋጋት መጣ ሲባል፣ በፀሐይ ፍጥነት ኢትዮጵያ ወደ ጦርነት እየገባች መሆኑ እጅግ በጣም ያሳዝናል:: ወደዚህ እንድትገባ እያደረገ ያለው ደግሞ አብይ አህመድ ነው፡፡ ሰላም የነበረን ክልል፣ በአንድ ጀምበር፣ በአንድ እብድ ሰው ውሳኔ የጦርነት ቀጠና እየሆነ ነው፡፡ ውጊያ በስሜን ወሎ ዞን ቆቦና በደቡብ ጎንደር ወረታ ======================== ለአብይ አህመድ ታዛዥ የሆኑ የኦነግ የመከላከያ መኮንኖች፣ ሕገ ወጥ በሆነና በማን አለብኝነት፣ የምስራቅ አማራ ፋኖ መሪ የሆነውን ሻለቃ ምሬ ወዳጆን፣ ለመያዝ በሚል እንቅስቃሴዎች አድርገው ነገር፡፡ የዚህ እንቅሳሴ መሪ ጀነራል ሰለሞን ኢታፋ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የፋኖ መሪን ለመያዝ በጀነራል ሰለሞን ኢታፋ የሚመራው ጦር መንቀሳቀሱን የሰማው የራያ ቆቦ ህዝብ ግልብጥ ብሎ በመውጣት፣ ተቃውሞዉን አሰምቷል፡፡ እነ ጀነራል ሰለሞን ኢታፋ በህዝቡ ላይ በመተኮስ ቀላል የማይብል ጉዳት በሰላማዊ ዜጎች ላይ አድርሰዋል፡፡ ከፋኖዎችም ጋር የተኩስ ልውውጥ የነበረ ሲሆን፣ የቆቦ ከተማ ላይም መድፍና ሮኪት በመተኮስ ብዙ ጉዳት አድርሰዋል፡፡ በቆቦና አካባቢው በነበረው ተኩስ፣ የተደናገጡ ነዋሪዎች፣ ወያኔ የመጣች መስሏቸው እንደነበረና፣ መድፍ ከተማዋ ላይ ተኩሶ ውድመት ሲያደርስ የነበረው የአገር መከላከያ መሆኑን
Posted in Ethiopian News

የአማራ ክልል ውሎ፣ መጋቢት 30 ቀን 2015 ዓ/ም #ግርማካሳ

በአማራ ክልል ያለው ውጥረት ግለቱን ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ነው፡፡ ችግርና ቀውጥ በተነሳ ቁጥር ህዝብ መረጃ እንዳያገኝ ኔትዎርክ መዝጋት የለመደው፣ የአብይ አህመድ አገዛዝ በብዙ ቦታዎች የኦንተርኔትና የኔትዎርክ አገልግሎቶች እንዲቆራረጡ የማድረግ አሳፋሪና አፋራሽ ስራዎችን እየሰራ ነው፡፡ እንደዚያም ሆኖ ግን፣ የአብይ አገዛዝ ትልቅ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበረሰባዊና ወታደራዊ ክስረት እየደረሰበት እንደሆነ የሚያሳዩ በርካታ ምልክቶች እየታዩ ነው፡፡ የህዝብ አመጽና ቁጣ ========= ከመጋቢት 24 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ፣ ህዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ ፣ እንዲሁም የአማራ ልዩ ኃይልንና ፋኖዎችን ትጥቅ አስፈታለሁ ያለውና፣ ለኦነጋዊው አብይ አህመድ አገዛዝ የሚታዘዘውን ጦር እንደልቡ እንዳይንቀሳቀስ ለማድረግ ፣ መንገዶችን የመዝጋት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች በበርካታ የአማራ ክልል አካባቢዎች እየተደረጉ ነው፡፡ – በዋገመራ ዞን ፡ በኮረም፣ ኦፍላ፣ ዛታ፣ ሰቆጣ ከተሞች፣ – በሰሜን ወሎ ዞን ፡ በቆቦ፣ ወልዲያ፣ መርሳ፣ ኡርጌሳ፣ ጎብዬ፣ ጋሸና፣ መቄት፣ ዓላማጣ፣ – በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በይፋት/ራሳ፣ ምንጃር/አረርቲ፣ ሸዋሮቢት፣ – በምዕራብ/ደቡብና ሰሜን ጎንደር፣ በመተማ፣ ገንዳ ውሃ፣ ዳባት፣ ወረታ ፣ ፎገራ እንዲሁም ጎንደር ዙሪያ፣ – በምስራቅ ጎጃም ዞን፣ በደብረ ማርቆስ፣ ደጀን፣ አባይ በረሃ፣ ቢቸና፣ ግንደ ወይን፣ ደብረወርቅ፣ ሉማሜ አዋበል፣ – በምእራብ ጎጃም ዞን፣ በደምበጫ፣ ቡሬ፣ ጅጋ፣ መራዊ፣ ፍኖተ ሰላም፣ እና ሌሎች ቦታዎች፣ ባመረረ መልኩ ነው በብልጽግና አገዛዝ ላይ፣ ያለውን ብሶት፣ ምሬትና ተቃውሞ ህዝብ እየገለጸ ያለው፡፡ ጀነራል አበባው ታደሰ፣ በቴሌቪዥን መስኮት በመቅረብ፣ “ከትግራይ ተማሩ፣ እምቢ ያለ ካለ (አብይ አህመድን የማይታዘዝ ማለቱ ነው) ፣ ልክ እናስገባቸዋለን” በሚል
Posted in Ethiopian News

የአማራ ክልል ውሎ ፣ መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ/ም

በአንጻራዊነት ሰላማዊና የተረጋጋ በሆነው የአማራ ክልል፣ ከህዝብ ፍላጎትና ጥያቄ ውጭ፣ በማን አለብኝነት፣ የአማራ ልዩ ኃይሎችን ለመበተንና ትጥቃቸውን ለማስፈታት የተደረገውን ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ ተከትሎ፣ በተነሳው ቀውስ ፣ ከሰላማዊነት ወደ ከፍተኛ ውጥረትና አለመረጋጋት ክልሉ የተሸጋገረበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ የአብይ አህመድ አገዛዝ፣ ችግር ባለበት ችግሮችን መፍታት፣ ሰላም በሌለበት ሰላምን ማስፈን፣ የዜጎችን ሰላምና ደህነት ማስጠበቅ፣ የደቡብ አፍሪካውን ስምምነት ህወሃቶች እንዲያከብሩና በሰሜን ያለው ስጋት እንዲቀንስ ማስደረግ ስራዉና ሃላፊነቱ ነበር፡፡ ሆኖም ሰላም ባለበት ቀውስ፣ መረጋጋት ባለበት ግጭት እንዲኖር እያደረገ ያለና ግጭትና ቀውስ ጠማቂ መሆኑን እያሳየ ነው፡፡ ያለ ቀውስና ግጭት መኖር የማይችል አገዛዝ የሆነ ይመስል። መጋቢት 28 ቀን ያልተሳካው፣ የአማራ ልዩ ኃይሎችን ትጥቅ የማስፈታት እንቅስቃሴ፣ መጋቢት 29 ቀንም ለማድረግ ተሞክሮ ነበር፡፡ ሆኖም በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣንና ተቃውሞን በማስነሳቱ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ ህዝባዊ እምቢተኛነት፣ የህዝቡ ቁጣና አጋርነት ለአማራ ልዩ ኃይል ============================== መጋቢት 24 ቀን 2014 ዓ/ም በበርካታ የአማራ ክልል ከተሞች፣ በዋገመራ ዞን ኮረም፣ ዛታ፣ ኦፍላ፣ በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ፣ ዓላማጣና ኡርጌሳ፣ በሰሜን ሸዋ ምንጃር አረርቲ፣ በምእራብ ጎጃም ዞን መራዊ፣ ጂጋ፣ ደምበጫና ቡሬ በአብይ አህመድ አገዛዝ ላይ ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ ተሰምቶ ነበር፡፡ በብዙዎቹ ዘንድ አብይ አህመድ ከስልጣን ይልቀቅ የሚሉ ድምጾች ሲሰሙም ነበር፡፡ መጋቢት 29 ቀን በሰሜን ወሎ ወልዲያ፣ መርሳ፣ በሰሜን ሸዋ ይፋት/ራሳ፣ በምስራቅ ጎጃም ቁልፍ በሆነችው የደጀን ከተማና ቢቸና፣ በምእራብ ጎንደር፣ገንዳ ውሃ (መተማ)፣ ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞዎች የነበሩ ሲሆን፣ የአብይ ጦርን
Posted in Ethiopian News

የአማራ ክልል ውሎ (መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ/ም) #ግርማካሳ

የአማራ ክልል ውሎ #ግርማካሳ መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ/ም የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ተጠሪነቱ ለአማራ ክልል ምክር ቤትና ለክልሉ መንግስት ነው፡፡ ተጠሪነቱ ለአንድ ፓርቲ አይደለም፡፡ ሆኖም የብልጽግና ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ልዩ ኃይሎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው የሚል ውሳኔ በማሳለፍ ውሳኔው ህገ ወጥ በሆነ መንገድም፣ በጉልበት ለመተግብር እንቅሳሴዎች እነ አብይ አህመድ ጀምሯል፡፡ ይህ ውሳኔ 1ኛ የክልል ምክር ቤቶች እንዲነጋገሩበት አልተደረገም፡፡ 2ኛ የብልጽግና ፓርቲ መዓከላዊ ኮሚቴም አልተነጋገረበትም፡፡ 3ኛ አብይ አህመድ ከህወሃቶች ጋር ተነጋግሮ ለብልጽግና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አቅርቦ ያስወሰነው ነው፡፡ በስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውስጥ ከአማራ ብልጽግና የተወከሉት ሁሉም፣ አብይ አህመድን በመፍራት ውሳኔው ላይ ፊርማቸውን አሳርፈዋል፡፡ እነርሱም ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ፣ አቶ ደመቀ መኮንን፣ አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ አቶ ብናልፍ አንዷለም፣ አቶ መላኩ አለበል፣ ዶር ሰማ ጥሩነህ፣ አቶ ግርማ የሺጥላና ዶር ይልቃል ከፍያለ ናቸው፡፡ ይህ ውሳኔ የአማራ ክልል ህዝብን ለጉዳት የሚዳርግ፣ ጊዜውን ያልጠበቀ እንደሆነ እየታወቀ፣ በብልጽግና የስራ አስፈጻሚ ውስጥ አንድም የአማራ ብልፅግና ተወካይ ለመቃወም አለመቻሉ በጣም አሳዛኝና የአማራ ብልጽግና ከፍተኛ አመራሮች ከሃዲዎች መሆናቸው በግልጽ ያመላከተ ነው፡፡ 4ኛ የኣማራውን ማህበረሰብ ጥቅም የማያስጠብቅ ብቻ ሳይሆን፣ የህዝቡን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል፣ በአማራው ማህበረሰብ ላይ የታወጀ ጦርነት ነው፡፡ ይህ ውሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ለማድረግ፣ የክልሉ የዞንና የወረዳ አመራሮችን፣ እንዲሁም የልዩ ኃይሉ የብርጌድ አዛዦችን በመሰብሰብ ለማሳመን ተሞክሮ ነበር፡፡ የአማራ ልዩ ኃይሎችና ፋኖዎች እንደሚበተኑና ትጠቃቸውን እንደሚፈቱ ተነገራቸው፡፡ በስብሰባዎቹ ከፍተኛ
Posted in Ethiopian News

በጥፊ የተመቱት ኢትዮጵያዉያን እናቶችና እህቶች በሙሉ ናቸው #ግርማካሳ

መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ/ም ነው፡፡ ከቀኑ 11 ሰዓት አካባቢ፡፡ አዲስ አበባ ብስራተ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የላፍቶ ሞል የአገዛዙ ታጣቂዎች መሳሪያዎቻቸውን ይዘው ከፒካፕ መኪና ወረዱ፡፡ ብዛት አላቸው፡፡ ወደ ሞሉ ገቡ፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ፣ አንዲት አረንጓዋዴ ሱሪና ጥቁር ሸሚዝ ያደረገች እህት በካቴና አስረው ከሞሉ ወጡ፡፡ እየገፈተሩ፣ እየጮኹባትና እያዋከቧት፡፡ መኪናው ጋር ሲደርሱ፣ ወደ መኪናው እንድትወጣ ጪኹባት፡፡ “እንዴት ልውጣ ? እጆቼን እኮ በካቴና ታስረዋል” አለቻቸው፡፡ለሁለት ጎንና ጎን ይዘዋት ፒካፑ ላይ ጫኗት፡፡ “ቆይ እናንተ ማን ናችሁ ?” አለቻቸው፡፡ “ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ” ከማለት በቀር መልስ አልሰጣቷትም፡፡ “ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ፖሊስ ትፈለጊያለሽ ስላለኝ ብቻ አልሄድም” ትላለች፡፡ ሰዎቹ ምንም አልመሰላቸውም፡፡ ሹፌሩም ሳይቀር ከመኪና ወርዶ እጁን ፊቷ ላያ አሳረፈ፡፡ በጥፊ መታት፡፡ ሴትነቷ ላይ ያነጣጠረም፣ እዚህ ሊጠቀስ የማይችል ጸያፍ ስድቦችን ሰደቧት፡፡ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ሁኔታውን ይመለከታሉ፡፡ ካሜራ ይዞ የሚያነሳ ካለ በጥይት በለው ብሎ አንዱ ለሌላው ትእዛዝ ሰጠ፡፡ የተሰበሰቡትን ሰዎች በኃይል ይበትኑና፣ ይችን እህት ይዘዋት ይሄዳሉ፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ፣ ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ አከባቢ ወደሚገኘው የፌድራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጽህፈት ቤት ነበር መጀመሪያ የወሰዷት፡፡ ምሽቱን ከሜክሲኮ ወደ ፒይሳ ወደሚገኘው የፌድራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጽህፈት ቤት አመጧት፡፡ ይች እህት ገነት አስማማው ትባላለች፡፡ በሞያዋ ጋዜጠኛ ናት፡፡ የዪኔታ ትዩብ ጋዜጠኛ፡፡ አንዲት ኢትዮጵያዊነት ናት፡፡ በአገሯ ፣ በምድሯ፣ በሞያዋ እየሰራች ያለች እህት ናት፡፡ በዚህ ልክ ግን የአገዛዙ ታጣቂዎች፣ ጃል መሮን የያዙ ይመስል፣ በብዛት ሆነው፣ ያልታጠቀች፣
Posted in Ethiopian News

የአብይ ኦህዴድ አገዛዝ፣ የጭካኔና የኢሰብአዊነት ተምሳሌት #ግርማካሳ

የአብይ ኦህዴድ አገዛዝ፣ የጭካኔና የኢሰብአዊነት ተምሳሌት #ግርማካሳ የህወሃቱ አባት፣ አቦይ ስብህት ነጋ ለህክምና ከአገር ወጥተዋል፡፡ የኩላሊት ህመምተኛ እንደሆኑ ይሰማል፡፡ አቦይ ስብሃት ታስረው የነበረ ሲሆን፣ “እድሚያቸው ስለገፋ፣ ለሰብአዊነት ነው፣ ጌታ ተናግሮን ነው” በሚል ነበር እነ አብይ አህመድ፣ ከእስር ቤት የለቀቋቸው፡፡ በወቅቱ የነ አብይን ቅጥፈት ባልቀበለውም፣ የአቦይ ስብሃትን መፈታት ግን ተገቢ ነው ብዬ ነበር፡፡ የሰማኒያ አመት ሽማግሌ ማሰር ምን ይባላል ? እነ አብይ አህመድ ያኔ አቦይ ስብሃትን የፈቱት፣ ሰብአዊነት ተሰምቷቸው፣ አቦይ ስብሃት እድሚያቸው የገፋ ስለነበረ ግን አይደለም፡፡ አንሳሳት፡፡ ከህወሃት ጋር ሚስጥራዊ ዉይይት ጀምረው ስለነበር ነው፡፡ ኦህዴዶች ለሰብአዊነት ቦታ የሚሰጡ ቢሆኑ ኖሮማ፣ የእድሜ ባለጠጋ የሆኑትን፣ የሰማኒያ አመቱን፣ የሕዝብ ልጅ፣ ጀግና ፣ ጋሽ ታዴዮስ ታንቱን በአሁኑ ጊዜ በግፍና በጭካኔ፣ ምንም ወንጀል ሳይኖርባቸው፣ አስረው አያሰቃዩም ነበር፡፡ አቦይ ስብሃት ከተፈቱ ብዙ ጊዜ ሆኗቸዋል፡፡ እስከ አሁን ወደ ውጭ ወጥተው እንዲታከሙ ለምን እንዳልተደረገ ብዙ መረጃ የለኝም፡፡ ያንን አቦይ ስብሃት ናቸው የሚያውቁት፡፡ ይመስለኛል፣ የቁም እስረኛ እንዲሆኑ ተድርጎ፣ አሁን ግን ከህወሃት ጋር ስምምነት ስለተፈረመ ለዚያ ሳይሆን አይቀርም፣ የቁም እስረኝነታቸው የተነሳውና እንዲወጡ የተደረገው፡፡ በዚህም ሆነ በዚያ ፣ ከአቦይ ስብሃት ጋር የፖለቲካ ልይነት ቢኖረኝም፣ ጥሩ ሕክምና ወደሚያገኙበት ቦታ መሄዳችው ጥሩ ነው ባይ ነኝ፡፡ በነገራችን ላይ ብርሃኑ ጁላም፣ ለህክምና ወደ ዱባይ እንደሄደ ይነገራል፡፡ እርሱ ብቻ ሳይሆን በርካታ የኦህዴድ ገዢዎች ወደ ውጭ ወጥተው ነው የሚታከሙት፡፡ ለቀላል ህክምና ሳይቀር፡፡ አገር ትልቅ ችግር ውስጥና አደጋ ውስጥ
Posted in Ethiopian News

ታላቁ የአማራ ጉባዬ ፟፣ ብሶት ማሰሚያ ወይስ ለትግል ክተት የሚያውጅ ? #ግርማካሳ

ታላቅ የአማራ ማህበር ጉባዬ በዋሺንገትን ዲሲ ነገ ቅዳሜ ማርች 25 እና እሁድ ማርች 26 ይደረጋል፡፡ በዚህ ጉባዬ በርካታ የማውቃቸው ወገኖች ይሳተፋሉ፡፡ ዋሺንግተን ዲሲ አካባቢ ያላችሁ ፣ በየቤታችሁ በአገራችሁ እየሆነ ባለው ነገር የታመማችሁ፣ በቤታችሁ ማልቀሳችሁን አቁማችሁ፣  ወደ ዚህ ስብሰባ ሄዱ፣ ከሌሎች ወንድሞቻችሁና እህቶቻችሁ ጋር ለተግባራዊ ስራ ምከሩ፡፡  በዚህ አጋጣሚ ይህ ጉባዬ የተሳካ እንዲሆን ምኞቴን እየገለጽኩ ጉባዬው ትኩረት ቢሰጣቸው ጥሩ ነው የምላቸውን አንዳን ሃሳቦች  በአክብሮት ለማቅረብ እሞክራለሁ፡፡ ጉባዬው በተለይም ያሉትን ችግሮች በመተንተን ላይ ጊዜዉን ማጥፋት ያለበት አይመስለኝም፡፡፡ ከበቂ በላይ፣ ያለውን ችግር ሁሉም ሰው ያውቀዋል፡፡ ለቀባሪው አደረኡት ነው የሚሆነው፡፡ ጥናታዊ ጽሁፎች እንደሚቀርቡ የጉባዬው ተሳታፊዎች በአዲስ ድምጽ ሜዲያ ላይ ቀርበው ሲናገሩ ሰምቻለሁ፡፡ በግሌ በተለያም ያለፈውን በመተንተን ላይ ጥናታዊ ጽሁፎች በማቅረብ ተሰባሳቢዉን ማሰልቸት ተገቢ አይደለም፡፡ በኔ እምነት ስብሰብው “ምን ተደረገ ? ምን ሆነ ?” በሚለው አጀንዳ ሳይሆን ፣ “ምን እናድርግ ?” በሚለው ላይ ነው 95% ጊዜውን ማጥፋት ያለበት ባይ ነኝ፡፡ ተግባራዊ የሆነ፣ የተጨበጠ፣ ህዝቡን የሚያንቀሳቀስ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ተላልፈው፣  አዘጋጆች በአዲስ ድምጽ ሜዲያ ያሉት፣ “ክተት” የሚለውን አባባል ልጠቅምና፣ በክተትና በቁርጠኝነት እንቅስቃሴ የሚጀመርበትን ሁኔታ በጉባዬውይመቻቻል ብዬ እጠብቃለሁ፡፡ ሌላው ደግሞ ይህ የአማራ ስብስብ፣ አማራ ካልሆኑት ጋር አብሮ የመስራት ፕሮቶኮል ቢዘረጋ ጥሩ ነው፡፡ ጎንደር፣ ጎጃም፣ ወሎ፣ ወዘተ እየተባለ፣ አማራ ክልል ላይ ብቻ ያተኮረ፣ በተለይም የአዲስ አበባን ህዝብ ያላቀፈ እንቅስቃሴ የትም አይደርስም፡፡ የአዲስ አበባ ህዝብ ደግሞ ምን አይነት አመለካከት እንዳለው
Posted in Ethiopian News

ለጎንደር ህዝብ የተገባው ቃል መከበር አለበት #ግርማካሳ

ለጎንደር ህዝብ የተገባው ቃል መከበር አለበት #ግርማካሳ   ዶ/ር መሠረት ዘላለም በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእናቶችና ሕጻናት ጤና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ናት፡፡ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሣይንስ ኮሌጅ በሕጻናት ትምሕርት እና ሕክምና ክፍል ባለሙያ ሆና አገልግላለች፡፡ አቶ መላኩ ፈንታ የቀድሞ የብአዴን አመራርና የገቢዎች ሚኒስቴር ሆኖ ያገለገለ ነው፡፡ በህወሃቶች ለረጅም ጊዜ ታስሮ የነበረ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ የአማራ ባንክን በማቋቋም ትልቅ አስተዋጾ ያደረገ፣ አሁንም የቦርድ ሰብሳቢ ሆኖ እየሰራ ያለ እንደሆነ ነው የሚነገረው፡፡ ዶር መሰረት ዘላለም በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ውስጥ፣ አቶ መላኩ ፈንታ ደግሞ በአማራ ባንክ ውስጥ እያደረጉት ስላለው ነገር አይደለም አሁን ለማንሳት የምፈልገው፡፡ ዶር መሰረት፣ ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴሯ ዶር ሊያ ታደሰ፣ አልፎም ለጠቅላይ ሚኒስተሩ፣ አቶ መላኩ ፈንታ ደግሞለአማራ ባንክ ባለ አክሲዮኖች ነው ተጠሪነታቸው፡፡ ስለዚህ ስራቸውን ስላልገመገምኩ የመገምገምም መብት ስለሌለኝ፣ በዚህ ረገድ የምለው ነገር አይኖረኝም፡፡ ሆኖም እነዚህ ሁለት ወገኖች በሌላ በጣም ትልቅና አንገብጋቢ ጉዳይ ጋር በተገናኘ ግን ልሞግታቸው እፈልጋለሁ፡፡ ከሁለት አመት ተኩል በፊት የጎንደር ከተማን ህዝብ ፣ “እናገለግልሃለን፣ ያነተ ድምጽ እንሆናለን” ብለው ለምርጫ ቀርበው፣ ህዝቡም ድምጽ ሰጧቸው ነበር፡፡ አቶ መላኩ ፈንታ 24035 ድምጽ በማግኘት የጎንደር ምርጫ ወረዳ አንድን፣ ዶር መሰረት ዘላለም 19228 ድምጽ በማግኘት የጎንደር ከተማ ምርጫ ወረዳ ሁለትን አሸንፈው፣ ጎንደር ከተማን በመወከል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ሆነዋል፡፡ ለውጥ ተብሎ የነበረው እንዲመጣ ጎንደር ቁልፍ ሚና የተጫወተች ከተማ ናት፡፡ ከወልቃይት ጥያቄ ጋር በተገናኘ፣ በጎንደር ተጀምሮ
Posted in Ethiopian News

እነ አብይ አህመድ/ኦህዴዶች ከአራት ኪሎ መባረር አለባቸው #ግርማካሳ

ሰኔ 16 ቀን 2011 ዓ/ም ከአራት አመት ተኩል በፊት ነው፡፡ ቢያንስ 3 ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ ፣ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንደ ማእበል ተመመ። አጋርነቱንና ድጋፉን ለኦሮሞዎቹ ለዶር አብይ አህመድና ለሚመራው ኦህዴድ ሰጠ፡፡ ይህ ህዝብ ከዘር በላይ መሆኑን፣ በግልጽ አመላከተ፡፡ (አሁን የአዲስ አበባ ህዝብ ኦሮሞን ይጠላል እያለ አብይ አህመድ ራሱን ቢያቀልም) ያ ሁሉ ድጋፍ፣ እነ ዶር አብይ አህመድ፣ ኢትዮጵያዊነት ፣ አንድነት፣ መደመር፣ ፍቅር በማለት ሚሊዮኖች ልብ ውስጥ ተስፋ እንዲያድር በማድረጋቸው ነበር፡፡ የዚህ ጦማር ጸሃፊንም ጨምሮ፡፡ በዚህ ወቅት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ሲያዩ ወባ እንደያዛቸው የሚያንቀጠቅጣቸው፣ የጥቁር ነጮች የሆኑ ጽንፈ ኦነግች ፣ እነ አብይ አህመድን ለመግደል ተንቀሳቀሱ፡፡ ቦምብ ይዘው መጡ፡፡ በመስቀል አደባባይ ለሰልፍ ከመጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች መካከል፣ በነ አብይ አህመድ ላይ የታሰበው ቦምብ አደባባዩ ላይ በስህተት ፈንድቶ ዜጎች ህይወታቸው አለፈ፡፡፡ በዚህ መልክ ነበር አዲስ አበቤዎች ህይወታቸውን ለነ አብይ አህመድ የገበሩት፡፡ ይህ እንግዲህ ያኔ ነው፡፡ አብይ አህመድና ኦህዴዶች፣ ህወሃትን ከአራት ኪሎ ለማስወጣት፣ በፌዴራል መንግስቱ ውስጥም በአስተማማኝ ሁኔታ የበላይነቱን ለመያዝ፣ የሌላው ኢትዮጵያዊ በተለይም የአማራው ድጋፍ ያስፈልግ ስለነበረ፣ አማራዉና ማንነቴ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለውን በዋናነት የአዲስ አበባን ህዝብ ድጋፍ ለማግኘት፣ ህዝቡ መስማት የሚፈልገውን መልእክት በጥሩ ቃላት መናገራቸውን ቀጠሉ፡፡ የህወሃትን የሃይል ሚዛን ለመቀልበስ ከኤርትራ መንግስት ጋር ስምምነት አደረጉ፡፡ ውስጥ ውስጡን ግን ፣ ሃይላቸውን እያጠናከሩ፣ የኦሮሞ ክልል ልዩ ሃይልን እያሰለጠኑ፣ በመቶ ሺህ ለሚቆጠሩ ሰራዊታቸው፣ መከላከያ የሌለውን መሳሪያዎች ማስታጠቅ ጀመሩ፡፡
Posted in Ethiopian News

በጎንደር ሁኔታ የአሁኑ ትውልድ ማፈር አለበት #ግርማካሳ

ጎንደር የጥምቀት በዓል ይከበራል፡፡ ትልቅ ዝግጅት ነው፡፡ “እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፡ አደረሰን” እላለሁ፡፡ እርግጠኛ ነኝ፣  በጎንደር ትልቅ ደስታና ትልቅ ፌሽታ ነው የሚሆነው፡፡ በተለይም በሰሜን የተገኘውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ፡፡ ስለ ጎንደር በውስጤ ያለውን ላጋራችሁ፡፡ ውስጤን ያሳዘነ፡፡ ጎንደር አንድ ወቅት የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች፡፡ ጎንደር የበጌምድር ዋና ከተማም ነበረች፡፡ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ ብዙ ህዝብ ይኖርባቸዋል ከሚባሉ ከተሞች መካከል አንዷ ጎንደር ናት፡፡ ታዲያ ፣ ” ጎንደር እንደ ህዝብ ብዛቷ፣ እንደ ታሪኳ ናት ወይ ?”  ብለን ብንጠይቅ መልሳችን  ምን ሊሆን ይችላል ? አንገት የሚያስደፋ መልስ አይደለምን? አሁን ምን ያህል እንደተለወጠ ባላውቅም፣ ከሶስት አመት ተኩል በፊት እንዳየኋት ፣ ጎንደር ከተማ የወደቀች ከተማ ናት፡፡ የቱሪስት ከተማ በጭራሽ አትመስልም፡፡ ዘመናዊ ሪስቶራንቶች፣ ኬክ ቤቶች፣ የመሳሰሉ የሉም፡፡ አንድ ሃሪፍ ሆቴል የሚባል ነበር ያረፍኩት፡፡ በዚያ ምግቡ ራሱ ያን ያህል ነበር፡፡ ስፓጌቲ አዝዤ በርበሬ ባለበት ስጎ ነው ፓስታዉን አምጥተው ያቀረቡልኝ፡፡ የመያሳው ሃዉልት ያለበትን ፒያሳ የሚባለውን፣ ብዙ ጊዜ በፎቶ የሚታየው፣ እንደገና አራዳ የሚባለውን አካባቢዎች ያየ፣  የአንድ ትሎቅ ከተማ መዓከል(downtown) ሳይሆን ተራ መንደር ነው የሚመስሉት፡፡ ምን አለፋችሁ የጎንደር ዉበት፣ ከነ መቀሌ፣ ከነ አዋሳ ፣ ከነ ባህር ዳር ጋር ሲወዳደር እዚያ ማዶ ታች ሆኖ ነው የምታገኙት፡፡ ያውም እንደ ፋሲል ግንቦች፣ ቁስኳም ማሪያም እንዳለው እንደ እቴጌ ምንትዋብ ቤተ መንግስት ያሉ  አስደማሚ ቅርሶች ያሉባት ከተማ ሆና፡፡ የጎንደር ከተማ ስታዲየምንስ አይታችሁታል ? በጣም አሳፋሪና አስቂኝ ነው፡፡ በጎንደር
Posted in Ethiopian News

ኦሮምኛ እንዲጠላ ሳይሆን እንዲወደድ ማድረግ ብልህነት ነው #ግርማካሳ

ወ/ሮ አዳነች አበቤ ከጥቂት እርሷ ከሾመቻቸው ካቤኔ አባላት ጋር፣ የአዲስ አበባ ተማሪዎች በሙሉ ኦሮምኛ በግዴታ እንዲማሩ መወሰኗን እየሰማን ነው፡፡ ቋንቋ ማወቅ፣ መማር ጥቅም አለው እንጂ ጉዳት የለውም፡፡ አንድ ኢትዮጵያዊ ኦሮምኛ ተማረ ማለት የራሱን ቋንቋ ተማረ ማለት ነው፡፡ ለምን ኦሮሞነት ኢትዮጵያዊነት ስለሆነ፡፡ ነገር ግን ለሁሉም ነገር ስርዓትና ደንብ አለው፡፡ ህዝብን በናቀና ባዋረደ መልኩ የሚሰራ ስራ ከጥቅሙ ጉዳቱ ነው የሚበልጠው፡፡ ከሶስት አመታት በፊት የትምህርት ሚኒስቴር ፍኖተ ካርታ የሚል ተዘጋጅቶ ነበር፡፡ በአገር ደረጃ ሁሉም ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መምር እንዳለለባቸው እና እንግሊዘኛና አማርኛም ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ ትምህርት እንዲሰጥ ያስቀመጠ፡፡ በወቅቱ እነ ሺመለስ አብዲሳ፣ እነ ጃዋር እንዲሁም ህወሃቶች አማርኛን ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ አናስተምርም በሚል ተቃውሞ አሰሙ፡፡ ህወሃቶች ያው ለመቃወም በሚል ነው እንጂ በፊትም ከሶስተኛ ክፍለ ጀምሮ አማርኛን ያስተምሩ ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ደግሞ ፊደል ተማሪዎች ስለሚማሩ፣ ትግሪኛ ማንበብ ተማሩ ማለት አማርኛም ማንበብ ተማሩ ማለት ነበር፡፡ እነ ሺመለስ አብዲሳ ጃዋር የተቃወሙት ግን አማርኛ ላይ complex ስላለባቸው ነበር፡፡ አማራ ክልል ኦሮምኛ እንዲማሩ ሳይደረግ እንዴት የኛ ልጆች አማርኛ ይማራሉ በሚል፡፡ ኦሮምኛን ከአማርኛ ጋር በማፎካከር፡፡ ቋንቋን ማፎካከር ደግሞ ድንቁርና ነው፡፡ ለምን ቋንቋ የማንነት መለያ ሳይሆን መግባቢያ ብቻ ስለሆነ፡፡ ያለፈው አመት በዶር ብርሃኑ ነጋ አመራር፣ የትምህርት ፍኖተ ካርታው፣ የኦሮሞ ፖለቲከኞች ለማስደሰት በሚል ተከልሶ፣ አማርኛና እንግሊዘኛ ይማሩ የሚለው፣ እንግሊዘኛና ሌላ ሶስተኛ የኢትዮጵያ ቋንቋ፣ ከአንደኛ ክፍለ ጀምሮ ሳይሆን ከሶስተኛ ክፍል ጀምሮ
Posted in Ethiopian News

በአ/አ በዙሪያ ያሉ ችግሮች የሚፈቱበት ዘመናዊ ምክረ ሃሳብ #ግርማካሳ

#dismantleethnicfederalis #StupidEthnicFederalism የኦህዴድ ብልጽግና መንግስት ቀድሞ የፊንፊኔ ዙሪያ ብለው ሰይመውት የነበረውን ልዩ ዞን፣ የሸገር ከተማ የሚል ስያሜ ሰጥተውት፣ በዚያ ዙሪያም አንዳንድ እንቅስቃሴዎች ጀምረዋል፡፡ ሲጀመር ይህን አካባቢ ለይተው ለምን የፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን እንዳደረጉት ግልጽ አልነበረም፡፡ እንደዚያ ካደረጉ በኋላ ደግሞ አሁን ከዞንነት ወደ ከተማ አስተዳደርነት መቀየራቸው ብዙዎችን ግራ ያጋባበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡እርሱ ብቻ አይደለም የከተማውን ስም፣ አዲስ አበባ የምትጠራበትን ሌላ ስሟን በመጠቀም የሽገር ከተማ ማለታቸው የሰዎቹ አጀንዳ ምንድን ነው ብለን እንድንጠይቅ ነው ያደረገን፡፡ አንዳንድ የማይካዱ መሰረታዊ ሃቆች አሉ፡፡ ይህ የፊንፊኔ ዙሪያ የሚባለው አካባቢ ፡ ከ75% በላይ ነዋሪው አማርኛ ተናጋሪ ሕብረ ብሄራዊ የሆነ ማህበረሰብ ነው፡፡ ከሶስት አመት ተኩል በፊት፣ ሰበታ፣ ቡራዩ ሄጄ ነበር፡ በዚይ በየሱቂ፣ በየገበያው በየመናኸሪያው ሰው የሚያወራው፣ የሚነጋገረው በአማርኛ ነው፡፡ አዲስ አበባ ያላችሁ ነው የሚመስላችሁ፡፡ አዲስ አበባ አለመሆናችሁን የምታውቁት፣ በሱቆች ላይ ላቲኑ ተጽፎ ስታዩ ብቻ ነው፡፡ ይህ አካባቢ በአዲስ አበባ ዙሪያ ያለ ከመሆኑ በተጨምሪ፣ ከአማራ ክልልና ከደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን ርቀቱ ወደ 10 ኪሊሜትር ብቻ ቢሆን ነው፡፡ በዚህ አካባቢ የሚኖረው ማህበረሰብ ከአንድ እስከ ሁለት ሚሊዮን የሚጠጋ ማህበረሰብ ነው፡፡ ብዙ ሕዝብ ነው ያለው፡፡ ይህ አካባቢ ለአዲስ አበባ ቅርበት ስላለው፣ ከአዲስ አበባ መጥተው የሚሰሩ፣ ወይንም አዲስ አበባ ሄደው የሚሰሩ ብዙ ዜጎች ስላሉ፣ በዚህ አካባቢ ያሉ መሬቶች በጣም ውድ የሆኑና፣ አካባቢዉን ለሚያስተዳደሩ የኦህዴድ/ብልጽግና ባለስልጣናት ከፍተኛ የመክበሪያና ፣ የመዝረፊያ መንገዶችን የከፈተ፣ ወደፊትም የሚከፍት ነው፡፡
Posted in Ethiopian News

የኦሮሞና የትግራይ ብሄረተኞች ምርጫቸው ምንድን ነው ? #ግርማካሳ

#DismantleEthnicFederalism #StupidEthnicFederalism የኦሮሞ ፖለቲከኞች በአማራ ብሄረተኞች ላይ ብሶት እያሰሙ ነው፡፡ አማራዎች መስፋፋት ላይ ነው እየተጠመዱ ያሉት ይላሉ፡፡አንድ መረሳት የሌለበት ነገር የአማራ ብሄረተኝነት ያልነበረ በቅርብ የተወለደና ያደገ መሆኑ ነው፡፡ የወለዱትም፣ ያሳደጉትም፣  የኦሮሞና የትግራይ ብሄረተኞች ናቸው፡፡ ወልደው ያሳደጉት አሁን ለምን አደገ ማለት ትክክል አይደለም፡፡ “የትግሬ መሬት፣ የአማራ መሬት፣ የኦሮሞ መሬት…” የሚል የዘር ሕገ መንግስትና የዘር አወቃቀር ባለበት፣ የኦሮሞና የትግራይ ፖለቲከኞች፣ ኦነግና ህወሃት፣ አማራውን አግለው፣ ብቻቸውን ተደራድረው ፣ አማራዎች በብዛት የሚኖሩባቸውን እንደ ወልቃይት፣ ራያ ያሉትን ወደ ትግራይ፣ እንደ ደራ፣ ግራር ጃርሶ፣ ፈንታሌ፣ ቦሰት፣ አዳማ፣ አሰላ፣ ኪረሙ፣ አቤ ደንጎሮ ..የመሳሰሉትን ወደ ኦሮሞ ክልል፣ መተከልንና በአሶሳ ዘን የአሶሳና ባምቢሳ ወረዳዎች ወደ ቤኔሻንጉል ጠቅልለው ፣ ለነርሱ ሰፊ መሬት ሰጥተው፣ ለአማራው የሰጡትን ስንጥር መሬት፣ አማራው አሜን ብሎ ተቀብሎ እንዲቀመጥ አስበው ከነበረ ተሳስተዋል፡፡ አሁን ህወሃቶች በጉልበት ወስደዉት የነበረውን ወልቃይት፣ ራያና ጠለምትን የአማራ ኃይሎች በእጃቸው አስገብቷል፡፡ እስከ አሁን ድረስ ታግሰው ምንም ነገር አላደረጉም እንጂ፣ የአማራ ኃይሎች መተከልን፣ ደራን፣ ሰላሌን፣ አዳማን፣ ፈንታሌን አብዛኛው ሸዋን፣ አማራዎች በብዛት የሚኖሩባቸው አካባቢዎችንም፣ መጠቅለላቸው፣ ወይንም ለመጠቅለል መሞከራቸው አይቀርም፡፡ የአማራ መሬት፣ የትግሬ መሬት፣ የኦሮሞ መሬት የሚል ነገር እስካለ ድረስ፣ ሁሉም አቅም ካለው ለርሱ ዘር የተመደበውን መሬት ለማስፋት ይሞክራል፡፡ ይህ ተፈጥሯዊ ነው፡፡ እነ አቶ ለማ መገርሳ ስልጣን ሲይዙ እነ ሞያሌ፣ እነ ሃረር፣ እነ አዲስ አበባ የኦሮሞ ነው እያሉ ቀውስ አልፈጠሩም እንዴ ? ታዲያ አማራው ጋር ሲሆን መደነቁ፣
Posted in Ethiopian News

ደም መፋሰስ እንጂ ሰላም በጭራሽ  የማያመጣው የዘር ህገ መንግስት/አወቃቀር #ግርማካሳ

ደም መፋሰስ እንጂ ሰላም በጭራሽ  የማያመጣው የዘር ህገ መንግስት/አወቃቀር #ግርማካሳ #DismantleEthnicFederalism #StupidEthnicFederalism አንድ ነገር እርግጠኛ እንሁን፡፡ የዘር ፖለቲካ፣ የዘር ህገ መንግስት፣ የዘር አወቃቀር እስካለ ድረስ ደም መፋሰስ እንጂ የሚመጣ ምን አይነት ሰላም የለም፡፡ የትግሬ መሬት፣ የአማራ መሬት፣ የኦሮሞ መሬት ፣ የትግሬ ባንዲራ፣ የኦሮሞ መዝሙር እየተባለ እንዴት ነው እንደ አንድ አገር መቀጠል የሚቻለው ???? በዚሁ የዘር ፖለቲካ ምክንያት፡ በሰሜኑ ጦርነት ከ600 ሽህ በላይ ዜጎች በጦርነትና ከጦርነት ጋር በተገናኘ፣ በረሃብ በበሽታ …፣ መፈናቀል አይደለም፣  ሞተዋል፡፡ ሚሊዮን የሚደርሱ ደግሞ ተፈናቅለዋል፡፡ የትግራይና የአማራ ክልል 40 አመት ነው ወደ ኋላ ነው የተመለሱት፡፡ በኦሮሞ ክልል ከሁለት ሚሊዮን በላይ ዜጎች ከቅያቸው ተፈናቅለዋል፡፡ 800 ሺህ ጌዲዎች ፣ 800 ሺህ ከምእራብ ኦሮሚያ አማራዎች፣ 400 ሺህ ሶማሌዎች፡፡ በአስር ሺሆች ደግሞ ተገድለዋል፡፡ ከሶማሌ ክልል 600 ሺህ ኦሮሞዎች ተፈናቅለዋል፡፡ ብዙዎችም ተገድለዋል፡፡ በአድን ቀን በአወዳይ ከ67 በላይ ሶማሌዎች በሶማሌነታቸው መታረዳቸው ማስታወሱ ብቻ ይበቃል፡፡ በቤነሻንጉል፣ በጉሩፈርዳ፣ በአማሮ፣  በኮንሶና በቡርጁ ደቡብ ክልል አካባቢዎች በመቶ ሺሆች ተፈናቅለዋል፡፡ ብዙዎች ህይወታቸው ተቀጥፏል፡፡ በአፋርና በሶማሌ ክልል መካከል በተነሱ የመሬት ይገባኛል ውዝግቦች፣ በየጊዜው በመቶዎች እየሞቱ ነው፡፡ እንደ አዳይቱ ያሉ ከተሞች ሙሉ ለሙሉ ወድመዋል፡፡ በስሜን ሸዋ ይፋት፣ በተከታታይ ከአምስት ጊዜ በላይ በዜጎች ላይ ከፍተኛ ጭፍጨፋ ተፈጽሟል፡፡ እንደ አጣዬ፣ ካራቆሬ፣ ቆሪ ሚዳ ያሉ ከተሞች ወድመዋል፡፡ ምን አለፋችሁ የትግሬ፣ የአማራ፣ የሲዳማ እየተባለ አሁንም በየቦታው ከፍተኛ ውዝግቦች ነው ያሉት፡፡ በአማራና በኦሮሞ መካከል ያለው ግብግብ
Posted in Ethiopian News

በራሳቸው ኮተት ህገ መንግስት ልሞግታችሁ፣ ከደፈሩ መልስ ይስጡ #ግርማካሳ

የኦሮሞ ብሄረተኞችና ፖለቲከኞች አሁን ያለ ህወሃትና ኦነግ የጻፉት ፣ እነርሱ የብሄር ብሄረሰቦችን መብት አስክበረ የሚሉት ሕገ መንግስት በደማችን በመስዋትነታችንን እናስቀጥላለን ይላሉ፡፡ በምክንያት በማስረጃ ይህ ሕገ መንግስት፣ የዘር አወቃቀሩ ፣ እነርሱ ቆመንለታል የሚሉትን የኦሮሞ ማህበረሰብ በጣም እንደጎዳ ብዙ ጊዜ ለማሳየት ሞክረናል፡፡የዚህ ህገ መንግስት ቁሻሻነትን፣ ዶር ኃይሌ ላሬቦ እንዳሉት ኮተቱነት፣ እጅግ በጣም ጎጂ መሆኑ ማሳየታችንን እንቀጥላለን፡፡ በዚህ ጽሁፍ ግን በነርሱ ሳይድ (devil advocate) ሆኔ ፣ በደማችን እናስቀጥለዋለን ያሉትን ሕገ መንግስት ራሱ በመጥቀስ ፣ ነገሮችን ገልብጬ ልሞግታቸው ፈለኩ፡፡ በሕገ መንግስቱ ብሄር ብሄረሰብና ሕዝቦች የሚለው ቃል ትርጓሜ በአንቀጽ 30 ንኡስ አንቀጽ 5 ላይ ተቀምጧል፡፡ “በዚህ ሕገ መንግሥት ውስጥ “ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ” ማለት ከዚህ ቀጥሎ የተገለጸውን ባህርይ የሚያሳይ ማኀብረሰብ ነው። ሰፋ ያለ የጋራ ጠባይ የሚያንጸባርቅ ባሕል ወይም ተመሳሳይ ልምዶች ያላቸው፣ ሊግባቡበት የሚችሉበት የጋራ ቋንቋ ያላቸው፣ የጋራ ወይም የተዛመደ ሕልውና አለን ብለው የሚያምኑ፣ የሥነ ልቦና አንድነት ያላቸውና በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖሩ ናቸው” ይላል፡፡ በአዲስ አበባ አካባቢው ከ10 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ አለ፡፡ በደብረ ዘይት ከ300 ሺህ በላይ፣ በናዝሬት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ፡፡ በወለንጭቲ ከተማ ወደ 100 ሺህ የሚጠጋ ህዝብ ይኖራል፡፡ በነዚህ ከተሞች የሚኖረው ማህበረሰብ በአብዛኛው አማርኛ ተናጋሩ ማህበረሰብ ነው፡፡ “ሊግባቡበት የሚችሉበት የጋራ ቋንቋ ያላቸው” የሚለውም አንዱ ምስፈርት እንመለከት፡፡ በነዚህ ቦታዎች የሚኖረው ማህበረስበ ሊግባባት የሚችለው ቋንቋ አማርኛ ነው፡፡ በነዚህ አካባቢዎች የሚኖረው ማህበረሰብ ጉሊሶ ወይንስም ሻኪሶ፣ ቡሌሆራ ወይንም መቻራ፣
Posted in Ethiopian News

ከቦረና መጥተን ከወሎ/ጎጃም የመጡትን ሰፋሪ ማለት ነውር ነው #ግርማካሳ

ከዚህ በታች ላለለው ጽሁፍ እንደ መነሻና ምንጭ የወሰድኩት፣ ኦሮሙማ የሚለው ቃል ያመጡት፣ የታወቁ የኦሮሞ ብሄርተኛ ሶሲዮሎጂስትና ምህር፣ ዶ አሰፋ ጀለታ፣ የታሪክ ምሁሩ ኦሮሞው ዶር መሃመድ ሃሰን፣ የሜጫ ኦሮሞዎች ተመሰረሩት፣ ለቃ ነቀምቴ መንግስት ንጉሱ ወይንም ሞቲ የነበሩት፣ የንጉስ በክሬ ጎዳና 4ኛ ትውልድ የሆኑት የብልታ ደሬሳ አመንቴ ልጅ፣ አቶ ይልቅማ ደሬሳ፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት፣ የቀድሞ የኦነግና የኦህዴድ አባል፣ በኋላ የአንድነት ፓርቲ አመራር የነበሩ፣ የወለጋ ደምቢደሎ ተወላጅ ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የኦሮሞ ክልል ርእስ መስተዳደርና የኦህዴድ አባት የሚባሉት አባ ዱላ ገመዳ፣ አምስቱ ኦሮሞዎች፣ በኦሮሞ ታሪክ ዙሪያ ከጻፏቸው መጽሀፍት በመነሳት ነው፡፡ የኦሮሞ ፖለቲከኞች፣ የኦሮሞ ታጣቂዎች ምንም አይነት መሸማቀቅ ሳይኖርባቸው ኦሮሚያ ብለው የሚጠሩት፣ ህወሃት በዘር ሸንሽና የሰጠታቸው አካባቢ የኦሮሞ ነው ይላሉ፡፡ በወለጋ ኦሮሞ ያልሆነ ማህበረሰብን መጤ፣ ሰፋሪ እያሉ ይከሳሉ፡፡ “መሬታቹም አይደለም” በሚልም ኦሮሞ ባልሆኑት ላይ በዋናነት አማራው ላይ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጻዳት ወንጀሎች እየፈጸሙበት ነው፡፡ በሺሆች ተገድለዋል ፣ በመቶ ሺሆች ተፈናቅለዋል፡፡ ወለጋ የጥንት ስሙ ቢዛሞ ነበር፡፡ ኦሮሞዎች በቢዛሞ እግሮቻቸው የረገጡት በሙለታ ገዳ ዘመን፣ እ.ኤ.አ. ከ1586 እስከ 1594 ዓ/ም ባለው ጊዜ የነበረ ሲሆን፣ ዶክተር ነጋሶ ጉዳዳ፣ እ.ኤ.አ. በ1984 ዓ.ም በጻፉት የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ወረቀታቸው በጠቀሱት መሰረት፣ ኦሮሞ ወደ ወለጋ ከመፍለሱ በፊት በወለጋ ሙጬጮ፣ ገበቶ፣ ካዛ፣ ዳሞታ፣ ወረጎ፣ ጋንቃ፣ ማኦ ቡሳሴ ፣ ክዌጉ፣ ክዋማ፣ መጀንግ እና አማራ ካንቺ የሚባሉ ማህበረሰባት እንደነበሩ ነው የገለጹት፡፡ የኦሮሞ ጎሳዎች በሁለት ትላልቅ ዋና
Posted in Ethiopian News

ሃረር ክልል ሆና ሃምሳ ሃረሮች የሚወጣት ሸገር ግን በሌሎች ተጨፍልቃለች #ግርማካሳ

ሃረር ክልል ሆና ሃምሳ ሃረሮች የሚወጣት ሸገር ግን በሌሎች ተጨፍልቃለች #ግርማካሳ በስታቲስቲክ መስሪያ ቤት ኦፊሴላዊ ግምት መሰረት፣ የአዲስ አበባ ሕዝብ ብዛት ባለፈው የ2014 ዓ/ም 3434000 ነው ይላል፡፡ ይህ ለአዲስ አበባ እጅ በጣም ያነሰ ቁጥር ነው፡፡ ሆን ተብሎ የአዲስ አበባን ህዝብ ለማሳነስ፣ የፖለቲካ ውክልና እንዳይኖረው ለማድረግ ፣ ያኔ ሕወሃቶች እንዳደረጉት፣ አሁን ደግሞ ኦህዴዶች በስታቱስቲካል ኤጀንሴው በኩል አሻጥር በመስራታቸው የተለቀቀ ቁጥር ነው፡፡ የአዲስ አበባ ሕዝብ በስታቲኡስቲካል ኤጀንሲ ከተጠቀሰው በሶስት እጥፍ የሚበልጥ እንደሆነ ብዙዎች የሚናገሩት፡፡ ትክክለኛው የአዲስ አበባ ቁጥር ኦህዴዶች ለነርሱ ፖለቲካ ስለማያመቻቸው ሆን በማሳነ፣ የአዲስ አበባን ህዝብ ለማዳከም ነው የፈለጉት፡፡ በነገራችን ላይ ዶር አብይ አህመድ የዚህ ወሳኝ መስሪያ ቤት ሃላፊ አድርጎ የሾመው፣ አቶ በከር ሻሌ ነው፡፡ እኝህ ሰው ለረጅም ጊዜ የኦህዴድ አመራር፣ በናዝሬት ከንቲባ ሆኖ የሰሩ ሰው ናቸው፡፡ በናዝሬት ከንቲባ የነበሩት የናዝሬት ህዝብ መርጧቸው ወይም ሺሟቸው ሳይሆን ከማእከላዊ በኦህዴድ ነው፣ ከቦረና መጥተው የተሾሙት፡፡ የአቶ የበከር ሻሌ ወንድም ላቸው፡፡ ብርጋዴር ጀነራል ከማል ሻሌ ይባላሉ፡፡ በመከላከያ ደህንነት መምሪያ፣ የካዉንተር ኢንቴሊጀን ዳይሬክተር ናቸው፡፡ የአብይ አህመድን ቁሻሻ ስራ የሚሰሩ ሰው፡፡ ኢትዮ360 እንደዘገበው፣ ጀነራሉ በቀጥታ ኮማንዶዎች ይዘው፣ በአብይ አህመድ በራሱ በመታዘዝ፣ ጀነራል ተፈራ ማሞ አፍነው እንደወሰዱ ዘግበው ነበር፡፡ ለአሁን ለዛሬው ጽሁፍ መነሻ እንዲሆን ብቻ ፣ ኦህዴድ መራሹ የስታቲስቲክ መስሪያ ቤት ራሱ ያወጡትን ቁጥር ብንወሰድ፣ 1ኛ የአዲኦስ አበባ ህዝብ ብዛት፣ በሃረር፣ በጋምቤላ፣ በአፋር እነ በቤኔሻንጉል ክልልች በአንድ ላይ
Posted in Ethiopian News

ሸገር እንደ ብራሰልስ፣ በርሊን የፌዴራል መስተዳደር መሆን አለባት #ግርማካሳ

ሸገር እንደ ብራሰልስ፣ በርሊን የፌዴራል መስተዳደር መሆን አለባት #ግርማካሳ የአብይ አህመድ ብልጽግና ካድሬዎች፣ ዶ/ር ትዕግስት ውሂብ ላይ ዘመቻ መጀመራቸውን አየሁ፡፡ ዶር ትዕግስት የአዲስ አበባን አንድ ወረዳ ወክላ ለፓርላማ የተመረጠች ናት፡፡ ከአንድ አመት በፊት ነጭ፣ ጥቁር ቀዩን የኣባ ገዳ አርማ አድርጋ ፣ ዶር ብርሃኑ ነጋ በሌላ ሃላፊነቶች ፣ በሞያው ፣ እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር ባሉ ማለቷ መሰለኝ፣ ቢመደብ ይሻላል፣ ትምህርት ሚኒስቴር ከሚሆን በሚል ጥያቄ አቅርባ ነበር፡፡ ይች እህት የአዲስ አበባ ልጅ ናት፡፡ ኦሮሞም ትሆናለች ብዬ አስባለሁ፡፡ በርካታ ኦሮሞ የሆኑ የአዲስ አበባ ልጆች፣ አዲስ አበቤዎች አሉ፡፡ የአባ ገዳዎችን አርማ ማድረጓም፣ መብቷ ነው፡፡ ከቀናት በፊት በተደረገው የፓርላማ ውሎ ላይ፣ የአካሄድ ጥያቄ አለኝ ብላ ጥያቄዎች ባልተለመደ መልኩ አቀረበች፡፡ ጠቅላዩን የጠየቀችው ጥያቄዎች ከአንድ የሕዝብ ተወካይ የሚጠበቅ ነበር፡፡ “ትላንት እንዲህ ለብሳ ነበር፣ እንደዚያ አድርጋ ነበር” ለሚለው ነገር ብዙ ቦታ አልሰጠውም፡፡ ነገር ግን ዶ/ር ትዕስግት፣ ተወካይ፣ ድምጽ ፣ የሚጮህለት ለሌላው የአዲስ አበባ ሕዝብ፣ አስደማሚ በሆነ መልኩ ድምጿን ያሰማች፣ አዲስ አበቤ እንደ ጀግና ሊቆጥራትና ሊጠብቃት ከጎኗም ሊቆም የሚገባ እህት እንደሆነች ነው የሚሰማኝ፡፡ የኦህዴድ/ብልጽግና ሰዎች ከአንድ አመት በፊት የአባ ገዳዎችን አርማ አድርጋ ነበር ብለው፣ ያኔ ምንም ነገር ሳይሉ፣ አሁን እርሷን ለማሳነስ ደፍ ደፍ ማለታቸው የሰዎቹን ማንነት፣ የፖለቲካቸውን ምንነት አመላካች ነው፡፡ በዛቻ በርሷ ላይ እንደሚነሱ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ድርጊቶቹ አሳፋሪ ናቸው፡፡ ያኔ ምንም ያላሉት፣ አሁን የያኔው አንስቶ ማውራት ድንቁርና ነው፡፡ በነገራችን ላይ
Posted in Ethiopian News

የደቡብ አፍሪካ ስምምነትና ተቃውሞ ከሁለት ማዕዘናት #ግርማካሳ

የደቡብ አፍሪካዉ ስምምነት ለኢትዮጵያዉን መልካም ዜና ነው፡፡ የተለያዩ ቅር የተሰኘንበት ነገር ሊኖር ቢችልም፣ ቢያንስ ጦርነቱን አቁሟል፡፡ ቢያንስ ዛሬ ሰው እየተገደለ አይደለም፡፡ አንዳንድ የትግራይ ተወላጅ ዳያስፖራዎች እንዲሁም የሕወሃትን አቋም ሲያንጸባርቁ የነበሩ አክቲቪስቶችና የሚዲያ ተቋማት፣ የደቡብ አፍሪካን ስምምነት እየተቃወሙ ነው፡፡ በተለያዩ ቦታዎች ሰልፍች እየተደረጉ ነው፡፡ በሲያትል በተደረገው ተቃውሞ በመኪና፣ ቢጫና ቀይ የሆነውን የቪትናም የሚመስለውን አርማ ለጥፈው ዋና መንገድን እስከመዝጋትም ደርሰዋል፡፡ የርዮት ሜዲያ ቴዎድሮሶ ጸጋዬ ፣ የደቡብ አፍሪካውን ስምምነት፣ “የትግራይን ሕዝብ ለአራጆች ያቀረበው ሰንድ” ብሎታል፡፡ “Military and Foreign Affairs Network” በሚል ዩቲብ ሜዲያ ላይ ካርታ እያሳየ ዘገባ የሚሰራ፣ ብዙ የህወሃት አክቲቪስቶችም የሚጠቅሱት ፣ ግ ስሙን የማይገልጸው፣ ራሱን ፣ “voice of reason”፣ አንድ ወዳጄ ግን “voice of unreason”ብሎ የሚጠራው፣ አፍቃሪ ሕወሃት ግለሰብ፣ “extermination agreement” ነው ያለው፡፡ እነዚህን እንደ ምሳሌ ጠቀስኩ እንጂ ተቃውሞው በውጭ አገር መጠነ ሰፊ ነው፡፡ ላለፉት ሁለት አመታት ነገሮች እጅግ በጣም ጦዘው ነበር፡፡ እንኳን አክቲቪስቶች ሰላማዊ በሆኑ የትግራይ ሰዎችና ሌሎች መካከል፣ በባልና ሚስቶች መካከል ፣ ለረጅም ጊዜ ጓደኛሞቹ በነበሩ መካከል መከፋፈሉ፣ መቃቃሮች ነበሩ፡፡ ሁላችንም በጦርነቱ ምክንያት አብደን ነበር፡፡ ሁላችንም ውስጣችን እሳት ነው የነበረው፡፡ እሳት ላይ የነበረ ምጣድ እንዲቀዘቅዝ ትንሽ ጊዜ እንደሚያስፈልገው፣ አሁንም ነገሮች እስኪቀዘቅዙ ትንሽ ጊዜ ይወስዳል፡፡ በመሆኑም የነዚህ ወገኖች ተቃውሞ ለምን እንደሆን ይገባኛል፡፡ በኔ እምነት ምጣዱ ቶሎ እንዲቀዘቅዝ የማድረግ ሃላፊነት ያለበት የብልጽግና መንግስት ነው፡፡ እነዚህ ተቃውሞ የሚያሰሙ ወገኖችን ልብ የማሸነፍ ስራ
Posted in Ethiopian News

የሁለቱ ኮሎኔሎች ጉዳይ #ግርማካሳ

ሁለቱም ኮሎኔሎች ናቸው፡፡ አንዱ ከህወሃት ጋር እየሰራ፣ በስለላና ደህንነት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ፣ በኢንሳ፣ የዜጎችን ስልክ እየጠለፈ ሲያሳስር የነበረ ነው፡፡ ሌላው “መሬቱ የትግሬዎች ነው” በሚል፣ ሕወሃት በወልቃይት በአማራዎች ላይ ስትፈጽም የነበረውን ግፍ በመቃወም ህወሃትን ሲታገል የነበረ ነው፡፡ ኮሎኔል አብይ አህመድ እና ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ፡፡ ኮሎኔል አብይ አህመድ በነ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ትግል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ፡፡ እየሸወደ፣ በቃላት እየደለለ፣ አራት ኪሎ ገባ፡፡ ነገር ግን፣ ስራውና መላቅጡ ሁሉ ለወልቃይቴዎች ሳይሆን በወልቃይቴዎች ላይ ሆነ፡፡ ወልቃይት በአንጻራዊነት ሰላምና መረጋጋት የነበረባት ብትሆንም፣ ኮሎነል አብይ አህመድ ግን ፣ ለገንዘብ ሚኒስቴሮች ለአህመድ ሺዴና ለወዳጁ ዶር እዩብ ታረቀኝ ቀጥተኛ ትእዛዝ በመስጠት፣ ለሁለት አመት ለወልቃይት በህግ የሚገባት ባጀት እንዳይሰጣት አደረገ፡፡ በኢኮኖሚ እነ ኮሎኔል ደመቀ ዘዉዱን፣ ወልቃይትን ሲቀጣ ቆየ፡፡ አሁንም እየቀጣ ነው፡፡ የደቡብ አፍሪካን ስምምነት ተከትሎ፣ እነ ጀነራል ጻድቃን እንደጠየቁት፣ ኮሎኔል አብይ አህመድ፡ – በህወሃትና ኦነግ በተጻፈው፣ – አማራ ጠል በሆነው፣ – ለዉህድ ኢትዮጵያዊነት፣ ለዜግነት፣ ለአንድነት ቦታ በማይሰጠው፣ – ኢትዮጵያን ትግሬ፣ አማራ፣ ኦሮሞ እያለ በዘርና በጎጥ እንድትከፋፈል ባደረገው፣ – አስር ሚሊዮኖች በማይቀበሉትና እንዲቀየር ጉትጎታ ሲያደርጉበት በነበረው፣ – ኦህዴዶች(አብይ አህመድን ጨምሮ) ሙጭጭ ብለው ለአራት አመት፣ አንዴ በዚህ ኮሚሽን ይታያል፣ ሌላ ጊዜ በዚያ ኮሚሽን ይታያል እያለ፣ እያወናበዱ እንዳይሻሻል ባደረጉት፣ – በአገራችን ለተፈጠሩ የዘር ግጭቶች፣ ጦርነቶች፣ መፈናቅሎች፣ የዘር ማጻዳትንማ ማጥፋት ወንጀሎች ምክንያት በሆነው፣ – በዘረኛውና በበሰበሰው ፣ በኃላ ቀሩ ኮተትና ቆሻሻ ሕገ መንግስት
Posted in Ethiopian News

ሁላችንም ተሸንፈናል፣ ሁላችንም አሸንፈናል #ግርማካሳ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርባ ምንጭ ንግግር እድርጓል፡፡ የንግግሩን መንፈስ አልወደድኩትም፡፡ ሰውዬው ዝም ቢል ጥሩ ነበር፡፡ ከአራት አመት በፊት የቀን ጅብ ወዘተ እያለ፣ አላስፈላጊ ንግግርቾ እያደረገ ነበር በትግራይ ችግሮች እንዲፈጠሩ ያደረገው፡፡ አንደኛ ፣ “አሸንፈናል” ሲል ነበር፡፡ ሌሎች የተሸነፉ ይመስል፡፡ ይህ አባባል በጣም የተሳሳተ አባባል ነው፡፡ ባዶ ፉከራ ነው፡፡ ይህ ጦርነት እርሱና ድርጅቱ ብልጽግና እንዲሁም ሕወሃቶች የቀሰቀሱት ጦርነት ነው፡፡ በዚህ ጦርነት፣ አንደኛ፣ ሁለተኛ፣ ሶስተኛ ዙር እየተባለ በመቶ ሺሆች ፣ ኢትዮጵያዊያን እንደ ቅጠል ረግፈዋል፡፡ ትግራይ፣ ሰሜን ጎንደር፣ ደቡብ ጎንደር፣ ሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎ፣ ዋገመራ፣ በአፋር ክልል ዞን 2 እና ዞን 4፣ ሰሜን ሸዋ ወድመዋል፡፡ ለዚህ ሁሉ ከሕወሃቶች ባልተናነሰ እነ አብይ አህመድም ተጠያቂ ናቸው፡፡ የመቶ ሺሆች ደም በእጃቸው ነው ያለው፡፡ ይሄ ሁሉ እልቂት፣ ይሄ ሁሉ ፍጅት አስፈላጊ አልነበረም፡፡ እኔ ዶር አብይ አህመድን ብሆን፣ እኔ በምመራት አገር ይሄ ሁሉ እልቂት በመፈጠሩ፣ አፍር ነበር፣ ስልጣኔን እለቅ ነበር፡፡ እንኳን በአደባባይ ወጥቼ ልደነፋ !!!!! ያለፉት ሁለት አመታት እልቂት ስናስብ፣ በዚህ ጦርነት ሁላችንም ነው የተሸነፍነው፡፡ ተጋሩዎች ተሸንፈዋል፡፡ አማራው፣ አፋሩ ተሸንፈዋል፡፡ በዚህ ጦርነት 20፣ 30 አመት ወደ ኋላ ቀርተናል፡፡ የአለም መሳቂያ ሆነናል፡፡ ተዋርደናል፡፡ ይሄ አንዱ ነጥብ ነው፡፡ ስምምነቱ ባይኖር ኖሮ ከዚህ በኋላ ጦርነቱ ሊቀጥል ይችል ነበር፡፡ ነገሮች መስመር ካልያዙና ትልቅ ማስተዋልና ጥንቃቄ ካልተደረገ፣ ስምምነቱ ፈርሶ ወደ ጦርነት ሊገባም ይችላል፡፡ ጥምር ጦሩ በርካታ ከተሞች የተቆጣጠረ ቢሆንም፣ የሕወሃት ታጣቂዎች ትጥቃቸውን እንደያዙ አሁን በመላው
Posted in Ethiopian News

የተዳከመች እንጂ የጠፋች ሕወሃትን አለመፈለግ #ግርማካሳ

ዶር አብይ አህመድ፣ “አሁን እየሰራን ያለነው ህውሓትን የማሳመን ስራ ነው ። ህውሓቶች የአገሪቷን ህግ እና ሕገ መንግሥት እንዲያከብሩ እና እንደ አንድ ክልላዊ መንግስት እንዲንቀሳቀሱ ነው ። ህውሓቶች ፍላጎታችንን ከተረዱና የራሳቸውን ሕገ መንግሥት አምነውበት በሕገ መንግሥቱ መሰረት ከተንቀሳቀሱ ሰላም ይረጋገጣል። ከግራ እና ከቀኝ የተለያዩ ጣልቃ ገብነቶች ቢኖሩም እኛ ኢትዮጵያውያን የራሳችንን ጉዳዮች በራሳችን ከፈታን ሰላማችንን እናረጋግጣለን” በሚል የተነገረበት መልእክት ለጥፌ፣ አስተያየት እንዲሰጥበት ጠይቄ ነበር፡፡ አንዳንዶች አንተስ ምን ትላለህ የሚል ጥያቄም አቅርበዋልኛል፡፡ ጠቅላዩ በስጠው አስተያየት ዙሪያ ያለኝ ምልከታ እንሆ፡፡ በቅድሚያ ሁለት ነገር ግልጽ ላድርግ፡፡ አንደኛው ብዙ ጊዜ ፣ “ለሕወሃት መሪዎች የማሪያም መንገድ ይሰጥ፣ ከህወሃቶች ጋር ድርድር ይደረግ ወዘተ” እያልኩ ስናገር፣ ለሕወሃቶች ግድ ሰጥቶኝ አይደለም፡፡ እነርሱ እየፈጠሩት ባለው ችግር ምክንያት የድሃ ልጅ እንደ ቅጠል መርገፉ እንዲቆም ነው፡፡ ለ27 አመት ህወሃትን ሲያገለግሉ የነበሩ፣ የህወሃት የዘር ፖለቲካን፣ የጎሳ ሕግ መንግስት ከልባቸው ደግፈው እያስቀጠሉ ያሉ፣ ኦህዴዶችና ተደማሪ ተለጣፊ ደጋፊዎቸው ፣ ህወሃትን ሲታገል የነበረን ግርማ ካሳ፣  ለሕወሃት ፍቅር አለው ብለው ሲናገሩ፣ ራሳቸውን ነው ግምት ውስጥ የሚያስገቡት፡፡ ሁለተኛ ጦርነትን በሌላ ጊዜ በቀጠሮ የሚያስቀጥል ተኩስ አቁም፣ ሜዳ ላይ ሊተገበር የማይችል ቅንነትና ውሸት የተሞላበት፣ ባላደርሻ አካላትን ያገለለ፣ ድርድር የትም አያደርስም፡፡ ጦርነት ሆነ ድርድርም ቢደረግ፣ በዘላቂነት ችግሩን መፍታት ካልቻለ አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፡፡ ወደ ዶ/ር አብይ ንግግር ስመጣ፣ 1ኛ “ይህ ንግግር ምን ያህል የመንግስትን አቋም የሚያንጸባርቅ ነው ?” ብለን ብንጠይቅ ግልጽ የሆነ ምላሽ
Posted in Ethiopian News

የኦሮሞ ድርጅቶችን  ፖለቲካ ጨፍላቂነትን ማሳያ ፣ ናዝሬት #ግርማካሳ

የኦሮሞ ድርጅቶች ፖለቲካ ህዝብን የሚያከብር ፖለቲካ አይደለም ያላቸው፡፡ የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት ይላሉ፡፡ ሌላዉን በአሃዳዊነት ይከሳሉ፡፡ ግን በዋናነት የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት የሚረግጡት፣ በኦሮሞ ክልል ደረጃ “አሃዳዊ” የሆኑት እነርሱ ናቸው፡፡ በአዲስ አበባ፣ በሃረር፣ በድሬዳዋ በመሳሰሉት የኦሮሞ መብት መከበር አለበት ይላሉ፡፡ ግን በኦሮሞ ክልል እነርሱ የሌላውን መብት ይጨፈልቃሉ፡፡ ለነርሱ ለኦሮሞ መቆም ማለት ሌላውን መጨፍለቅ ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ ወደ ናዝሬት እንምጣ፡፡ የናዝሬት ሕዝብ የራሱን እድል በራሱ እንዲወስን፣ የራሱን ከንቲባዎች እንዲመርጥ አይፈልጉም፡፡ እኛ የኦሮሞ መብት አይከበር አላልንም፡፡ እኛ የናዝሬት ነዋሪዎች፣ ኦሮሞ ይሁኑ ሌላ ፣ እንደ ናዝሬት ሕዝብ፣ እኩል መብታቸው ይከበር፣ ሁሉም አንድ ላይ ሆነው የፈለጉት ይሹሙ፣ የማይፈለጉት ይሻሩ ባዮች ነን፡፡ ያን በማለታችን እነርሱ ኝ ኦሮሞፎቢክ(የኦሮሞ ተላት ) ይልናል፡፡ እንዴት ነው የናዝሬት ሕዝብ የራሱን እድል ይወስን ማለት ፣ ኦሮሞን መጥላት የሚሆነው ? በናዝሬት ባለፈው ኦፌሳላዊ የሕዝብ ቆጠራ መሰረት ፣ 74% የሚሆኑት ነዋሪዎች ኦሮምኛ ተናጋሪ አይደሉም። ሆኖም በከተማዋ አስተዳደር ፣ በቀበሌዎች የሚቀጠሩት፣ ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦሮሞዎች ብቻ ናቸው። የከተማዎ ፓሊስ ሆነው የሚሰሩት አብዛኞቹ የናዝሬት ተወላጆች አይደሉም፡፡ ከሌላ ቦታ የመጡ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ናቸው፡፡ ኦሮሞዎችም ኦሮምኛ የማይናገሩ ከሆነ በከተማዋ ቦታ የላቸውም፡፡ በከተማ የስራ እድሎች ካሉ ማስታወቂያ የሚወጣው በናዝሬት ሳይሆን በነ ወለጋ፣ አርሲና ባሌ በመሳሰሉት ነው፡፡ የናዝሬት ከንቲባዎችን ብንመለከት፣ አቶ አብርሃም አዶሌ፣ አቶ በከር ሻሌ፣ አቶ ሲሳይ ነጋሽ፣ አቶ ጉቱ፣ አቶ ጀማል አባስ፣ አቶ ሀብታሙ ሃይለሚካኤል፣ ወ/ሮ
Posted in Ethiopian News

የሰሜኑ ጦርነት ሁኔታ፣ መቀሌ ከተያዘች ሕወሃት ያከትምላታል #ግርማካሳ

ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ/ም የአፍሪካ ህብረት የጠራው ስብሰባ ሰኞ ጥቅምት 14 2015 ዓ/ም ይጀመራል ተብሎ በነጋታው ማክሰኞ ጥቅምት 15 ነው የተጀመረው፡፡ ተኩስና ግጭት ማቆም ላይ ስምምነት ተደርጎ ፣ ቀጣይ የፖለቲካ ውይይቶች ይደረጋሉ የሚል ግምትና ተስፋ ነበረኝ፡፡ ይህ አይነቱን የጦርነት ዘገባ እጽፍለሁ ብዬም አላሰብኩም ነበር፡፡ ጦርነቱ፣ ግጭቱ ይቆማል በሚል፡፡ሆኖም ውይይቱ ያመጣው ምንም አይነት ውጤት የለም፡፡ ጦርነቱን ቀጥሏል፡፡ አንዳንድ ወገኖች መቀሌ ተይዟል የሚል ዘገባ ቢያወጡም እስከአሁን መቀሌ ከተማን ጥምር ጦሩ አልተቆጣጠረም፡፡ የህወሃት ታጣቂዎች በብዙ ቦታ ውጊያዉን መቋቋም እንዳካታቸው እየታየ ነው፡፡ ብዙ አካባቢዎች በጥምር ጦር እስር እየሆኑ ነው፡፡ ብዙ የህወሃት ታጣቂዎች እጅ እየሰጡ ነው፡፡ ሆኖም ሌሎች የደፈጣና የሽምቅ ውጊያዎችን እያደረጉ ነው፡፡ ገና እነ ሽሬ ሳይያዙ፣ እነ ሽሬ ከተያዙ በኋላም እነ አክሱምና አድዋ ሳይያዙ፣ የሕወሃት ታጣቂዎች ሊያሸንፉ እንደማይችሉ በመግለጽ፣ የማሪያም መንገድ ተፈልጎላቸው በሰላም ነገሮች ተጠናቀው ህዝቡ ሰላም እንዲያገኝ፣ ጦርነቱ እንዲቆም ስንወተውት ነበር፡፡ እንደወተወትነው ግን አልሆነም፡፡ ይኸው እስከ ዛሬ ቀን ድረስ ጦርነት እየተደረገ ነው፡፡ ቀላል ጦርነት እንዳይመስላችሁ፣ ከባድ፣ የብዙ ዜጎችን ሕይወት እያረገፈ ያለ ጦርነት ነው እየተደረገ ያለው፡፡ መሰረታችውን አገር ቤት ያደረገው፣ ካሉ ሜዲያዎች በኔ እይታ ተዓማኒነት ያለው ኢትዮኒውስ Ethio News የዘገበውን፣ ከአፍቃሪ ወያኔ ሜዲያዎች የሚነገሩትን ከግምት በማስገባትና ዜናዎችን በማገናኘት፣ እንዲሁም የራሴን መረጃ በመጠቀም ከዚህ በታች ያለው የጦርነቱን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጽ መረጃዎችና ለማሰባሰብ ሞክሪያለሁ፡፡ እንሆ፡ በደደቢትና በማይጠምሪ አካባቢ ከዋና መንገድ ራቅ ባሉ በረሃማ ቦታዎች በመመሸግ
Posted in Ethiopian News

ችግሩ የራስን እድል ከመወሰን ጋር አይደለም፣ ከጥላቻና ዘረኝነት ጋር ነው #ግርማካሳ

ሽሬ፣ አክሱም፣ መቀሌ…በአጠቃላይ proper Tigray በሚባለው ፣ ህዝቡ የራሱን እድለ በራሱ እንዳይወስን፣ በቋንቋው(በትግሪኛ) እንዳይማር፣ አገልግሎት እንዳያገኝ የተቃወመ፣ የማይደግፍ ሰው ሰምቼ አላውቅም፡፡ ማንም ማንንም በትግራይ ለመጨፍለቅ፣ ለመዋጥ ፍላጎት የለውም፡፡ ካለውም አይሳካለትም፡፡በተመሳሳይ ሁኔታ በደምቢደሎ፣ በዶዶላ ወዘተ ኦሮሞው በኦሮምኛ አይማር፣ አገልግሎት አያገኝ፣ የራሱን እድል በራሱ አይወስን ያለ የለም፡፡ ችግር ያለው እንደ ወልቃይት፣ ራያ ባሉ፣ አማራዎች በብዛት በሚኖርባቸው አካባቢዎች ፣ ከትግሪኛ ውጭ ሌላ ነገር የለም፣ እንደ ናዝሬት፣ አሰላ ባሉ አማርኛ ተናጋሪዎች በብዛት በሚኖርባቸው አካባቢዎች ከኦሮምኛ ውጭ ሌላ ነገር የለም መባሉ ነው፡፡ በምእራብ ጉጂ  ከአንድ ሶስተኛ እስከ ግማሽ የሚሆኑት ነዋሪዎች ከጌዴኦ ማበረሰብ ናቸው፡፡ ሁሉም ነገር በኦሮምኛ ነው ተብለው መብታቸው መገፈፉ ነው፡፡ የአብይ አህመድን ብልጽግና አሁንም ለምንደገፍ ወገኖች፣ እስቲ ልጠይቅ፡፡ ናዝሬት እንዲሁም የፊንፊኔ ዙሪያ የሚባሉት፣ እነ ቡራዩ፣ ሱሉልታ፣ ዱከም፣ ሰበታ ወዘተ ያሉበት ዞን ፣ ከ75% በላይ ነዋሪው አማርኝ ተናጋሪ ነው፡፡ በደራ፣ በፈንታሌ፣ በግራር ጃርሶ፣ በአዳማ ወረዳዎች ከ65% በላይ ነዋሪዎች አማርኛ ተናጋሪዎች ነው፡፡ ኦነግ ችግር እየፈጠረባቸው ባሉ ፣ በጊዳ፣ ኪረሙ፣ ኡሙሩ ፣ ጃርቴና አቢ ደንጎሮ የወለጋ ወረዳዎችም አንድ ሶስተኛው ኦሮሞ አይደለም፡፡ በነዚህ አካባቢዎች ግን ባሉ የቀበሌ፣ የከተማ፣ የዞን መስተዳደሮች፣ በፖሊስ ጣቢያዎች፣ ፍርድ ቤቶች በአጠቃላይ በአካባቢው ባሉ የመንግስት መዋቅሮች ያለው ፉጹም ዘረኛና አፓርታዳዊ አሰራር ነው፡፡ 1ኛ በነዚህ አካባቢዎች የሚሰሩት፣ የሚሾሙት ሁሉም ኦሮሞዎች ብቻ ናቸው፡፡ ልክ በአፓርታይድ ደቡብ አፍሪካ ነጮች ብቻ ይሾሙ እንደነበረው፡፡ ዳኞቹ፣ ፖሊሶቹ የፖሊስ አዛዦቹ፣ የቀበሌ ሰራተኞቹ
Posted in Ethiopian News

የዓለም አቀፍ ማሀበረሰብ ጦርነቱ እንዲቆም ጠየቀ #ግርማካሳ

የዓለም አእፍ ማህበረሰብ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ጦርነት በአስቸኳይ እንዲቆም ከፍተኛ ግፊት እያደረገ ነው፡፡ የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፣ የአሜሪካና የአውሮፓ መንግስታትም ጠንካራ ፣ “የተኩስ ይቁም “ጥያቄ እያቀረቡ ነው፡፡ በአሜሪካን ሴኔት የውጭ ጉዳይ ዋና ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የኒውጀርዚው ሴኔቴር ሮበርት ሜኔንዲዝም፣ ጦርነቱ የማይቆም ከሆነ የእቀባ እርምጃዎች እንዲወሰዱ እንቅስቃሴዎችን እንደሚጀምሩ አስጠንቅቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ ለሰላምና ለድርድር ያለውን ቁርጠኝነት ገልጾ፣ በማናቸውም ጊዜ፣ በማናቸውም ቦታ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ለመነጋገር ዝግጁ እንደሆነ አሳውቋል፡፡ ሆኖም የኢትዮጵያ ግዛትን በመድፈር፣ የዉጭ ኃይሎች አይሮፕላኖች ወደ ኢትዮጵያ ግዛት እያስገቡ እንደሆነ በማሳወቅ፣ መንግስት የኢትዮጵያን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት ላለማስደፈር የድንበር አካባቢዎችንና አይሮፕላን ማረፊያዎችን በሙሉ ለመቆጣጠር እንዲንቀሳቀስ መገደዱን አሳውቋል፡፡ ከነሐሴ 18 ቀን 2015 ዓ/ም (August 11 2022) ጀምሮ በተቀሰቀቀሰው ሶስተኛው ዙር ጦርነት፣ ከሁሉም ወገን በአስር ሺሆች የሚቆጠሩ ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል፡፡ የህወሃት ጦር ሲጀመር የዉጭ ኮሪዶር ለማስከፈትና በተለይም ወልቃይትን ለመያዝ አስቦ የነበረ ቢሆንም እንዳሰበው አልሆነለትም፡፡ ላለፉት ሁለት ወራት በተደረገው ጦርነት፣ ነሐሴ 18 በፊት በሕወሃት ቁጥጥር ስር የነበሩ በርካታ አካባቢዎች ከህወሃት ቁጥጥር ስር ውጭ ሆነዋል፡፡ እነርሱም፡ # እጅግ በጣም ስትራቲጂክ የሆነችዋን የሽሬ ከተማን ጨምሮ እንዳለ የሰሜን ምእራብ ዞን በሙሉ፣ # ዋና ከተማዋ ማይጠምሪ የሆነችው ጠለምት፣ # በደቡብ ትግራይ ዞን የተካተቱት እነ ኮረም፣ አላማጣና ዋጃ ያከተቱት፣ የራያ ኦፍላ፣ የራያ ዓላማጣና ሰሜናዊ የራያ ባላ(ጨርጨር) አካባቢዎች በሙሉ፣ # ከዋገምራ ተወስደው የነበሩ እንደ አበርገሌ ያሉ ወረዳዎች # ለኤርትራ
Posted in Ethiopian News

የጦርነቱ ሁኔታ፣ መቀሌ በመግባት አስተማማኝ ድል አይገኝም #ግርማካሳ

በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው፡፡ በኮረም፣ በአላማጣ፣ በአዲግራት፣ በአክሱምና በአድዋ አቅራቢያዎች ውጊያዎች አሉ፡፡ አንዳንድ ሜዲያዎችም ኮረም፣ ዓላማጣ፣ ማይጠምሩ. በጥምር ጦሩ ስር እንደገቡ እየተናገሩ ነው፡፡ በጥምር ጦሩ በሽሬ ዙሪያ ሆኖ ፣ የከተማ ውጊያ ላለማድረግ ወደ ከተማዋ አልገባም፡፡ ከህወሃት ቁጥጥር ውጭ በወጡ አካባቢዎች የመንግስት አገልግሎቶችን ለማስጀመር እንቅስቃሴዎች አሉ፡፡ ሕወሃቶች፣ “ጦርነቱ የህልውና ጉዳይ ነው፡፡ ከተሸነፍን ጠላቶቻችን ጄኖሳይድ ይፈጽሙብናል፣ ያጠፉናል” የሚል ቅስቀሳ እያደረጉ፣ ሕዝቡን በነቂስ በክተት እንዲዋጋ እያደረጉት ነው፡፡ ብዙ ወጣቶች እያፈሱ ነው፡፡ ሆኖም ብዙ የተሳካላቸው አይመስልም፡፡ በተለይም በሽሬ መስመር ያለው ሁኔታ እንዳሰቡት ስላልሆነ፣ የበለጠ ጥፋት ከሚከሰት ፣ ብዙዎቻችን ስንጠይቅ የነበረውን ሃሳብ፣ የማርያም መንገድ ተከፍቶላቸው፣ በሰላም የሕወሃት አመራሮች ከአገር ወጥተው ፣ ጦርነቱ እንዲቆም የማድረጉ ተቀባይነት ሊያገኝ እንደሚችል የሚያሳዩ ምልክቶች እያየን ነው፡፡ አንዳንድ ወገኖች የማሪያም መንገድ ስንል የሚናደዱ አሉ፡፡ አንዳንዶቹ አሁንም ሕወሃት የወታደራዊ የበላይነት አላት ብለው የሚያምኑ አሉ፡፡ ትላንት ሕወሃቶች “ኮሪዶር እናስከፍታለን፣ ወልቃይትን እንይዛለን፣ ከበባዉን እንሰብራለን” ብለው በጉልበታቸው ተማምነው ሲናገሩት የነበረውንና አሁን ሜዳ ላይ ያለውን ወታደራዊ ሁኔታ ማነጻጸር የተሳናቸው፣ የትግራይ ከተሞች እንደ ማሪዮፖልና አሌፖ ሊሆኑ እንደሚችሉ የዘነጉ ናቸው፡፡ እስካሁን ያለቀው ተጋሩ ሳያሳስባቸው ከዚህ በኋላ በሺሆች እንዲያልቁ፣ የህወሃት መሪዎች እስከ መጨረሻ ጠብታ እንዲዋጉ ​እየጠየቁ ነው፡፡ ያሳዝናል፡፡ ሌሎች ደግሞ የህወሃት መሪዎች ተይዘው ለፍርድ መቅረብ አለባቸው፣ ሕወሃት ሙሉ ለሙሉ መደምሰስ አለባት፣ ከነርሱ ጋር ምንም አይነት ድርድር ሆነ ውይይት አያስፈልግም የሚሉ አሉ፡፡ እነዚህ ወገኖች ከሁለት አመት በፊት የነበረውን
Posted in Ethiopian News

የጦርነቱ ሁኔታ፣ አሁንም ጦርነቱን ለማቆም አልረፈደም #ግርማካሳ

ነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ/ም ሶስተኛው ዙር ጦርነት ተቀሰቀሰ፡፡ ጦርነቱ ሁለት ወር አልፎታል፡፡ እጅግ በጣም ብዙ ዜጎች ከሁሉም ወገኖች አልቀዋል፡፡ የአስመራ፣ የጎንደር፣ የባህር ዳር፣ የወልዲያ፣ የደሴና መቀሌ ሆስፒታሎች በቁስለኞች ተጥለቅልቀዋል፡፡ ለአገርና ለሕዝብ ትልቅ ስራ ሊሰሩ የሚችሉ ወጣቶች እንደ ቅጠል ረግፈዋል፡፡ በዚህ ጦርነት በተለይም ሕወሃቶቸ እንደማያሸንፉ ፣ ለማያሸንፉት ወደ ዉጊያ እንዳይገቡ፣ ያሉ ችግሮችን በግትርነት ሳይሆን ሰጥቶ በመቀበል መርህ ችግሮች ለመፍታት እንዲዘጋጁ ብዙዎቻችን ስንመከርና ስናስጠነቅቅ ነበር፡፡ ነሀሴ 18 ቀን ሕወሃቶች ገፍተው በመሄድ እስከ ወልዲያ ድንበር ደረሱ፡፡ ቆቦ፣ ሮቢት፣ ጎብዬ፣ ወርቄ፣ ተኩለሽ የመሳሰሉትን ያዙ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን በተደረጉ ጦርነቶች ሕወሃቶች የወታደራዊ የበላይነታቸውን ያጡ ይመስላል፡፡ በአሁኑ ወቅት ተቆጣጥረው ከነበሩበት ከሰሜን ወሎ ወረዳዎች ፣ ከነቆቦ ለቀዋል፡፡ ያ ብቻ አይደለም፣ ቆቦን በማለፍ ዋጃ በጥምር ጦር ስር ስትገባ፣ ሕወሃቶች ከዓላማጣ ጥለው እየወጡ እንደሆነም እየተሰማ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ በኮረምና በግራጋሶ ውጊያ እየተደረገ ነው፡፡ ግራካሶና ኮረም ከተያዙ ዓላማጣ በአስተማማኝ ሁኔታ በጥምር ጦሩ ስር ወደቀች ማለት ነው፡፡ ከዚያ በኋላ በድሮው ጣሊያን በሰራው መንገድ፣ በነ አምባላጌና ማይጨው በኩል ሳይሆን፣ በአዲሱ ቆላማ መንገድ በመኾኔ በኩል፣ ተራራማ አካባቢዎች በግራ በኩል ጥሎ በመሄድ፣ ሕዋኔ ከተማ መግባት ይቻላል፡፡ ሕዋኔ ከተገባ እንደርታና መቀሌ በደቡብ በኩል ፊት ለፊት ገላጣማ ሜዳ ላይ ነው ያሉት፡፡ በሰሜን ጥምር ጦሩ ራማን ተቆጣጥሮ በአድዋና በራማ መካከል፣ አድዋ ደጃፍ ላይ ባለችው ደዓሮ ተክሌ ውጊያ እያደረገ ነው፡፡፡ በዛላማባሳ በኩል በትግራይ ሁለተኛዋ ታላቋ ከተማ አዲግራት
Posted in Ethiopian News

ከሰላምና አገር ደህንነት አንጻር ብልጽግና ሲመዘን #ግርማካሳ

“የዶር አብይ አህመድ የብልጽግና መንግስት አገር ማስተዳደር አቅቶታል ወይ ? የብልጽግና መንግስት ከቀጠለ የተሻለ ነገር የሚመጣ ይመስላቹሃል ወይ” በሚል ላቀረብኩት ጥያቄ ብዙ አንባቢያን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ መልሶቹ ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያዉን የብልጽግ ና መንግስት አካሄድ አገሪቷን ወደ ጨለማና ጥፋት እየወሰዳት እንዳለ ነው እየተናገሩ ያሉት፡፡ የዶር አብይ አህመድ ገዢው ፓርቲ ስሙ የብልጽግና ፓርቲ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ብልጽግና የሚለው ቃል የሚያመለክተው እድገትን፣ የኑሮ መሻሻልን፣ ሃብትን ነው፡፡ አንድ አስተያየት ሰጭ በብልጽግና መንግስት ያለውን እድገት፣ የካሮት ምሳሌ በመጥቀስ ነበር ያቀረቡት፡፡ “ ብልፅግና ከመጣ ጀምሮ እንደ ካሮት ቁልቁል ነው ያደግነው !!” በሚል፡፡ ሌላ አስተያየት ሰጭ፣ መልሱ የሚታወቅ ጥያቄ በመጠየቁ ቅሬታቸውን ገልጸው፣ “የ አምስት አመት ልጅ በትክክል የሚመልሳቸው ጥይቄዎች ናቸው፡፡ ከብልፅግና የማይሻል የለም፡፡ ሂዊ (ህወሃት) እንኳ ብትሆን” በማለት በህወሃት ጊዜ ከነበረው ሁኔታ አሁን ያለው የባሰ እንደሆነ ለማሳየት ሞክረዋል፡፡ ያለው ነባራዊ ሁኔታ እንደሚያሳየው፣ የሚሰጡ አስተያየቶችም እንደሚጠቁሙት፣ ብዙ መከራከር የሚያስፈልገን አይመስለኝም፡፡ የዶር አብይ አህመድ የብልጽግና መንግስት፣ አገሪቷን ማስተዳደር አልቻለም ብቻ ሳይሆን፣ አገርን ወደ ባሰ ችግርና መከራ ውስጥ እያደረጋት ነው፡፡ ይሄንን ከአራት ማእዘናት ወይም Perspectives በምክንያት እናያለን፤ ከሰለምና ከአገር ደህንነት አንጻር ( Peace and national security perspective) ከከኢኮኖሚ አንጻር (economic Perspective)፣ ከፖለቲካ አንጻር (political perspective) እና ከማህበረሰባዊ ጉዳዮች አንጻር(social perspective)፡፡ በዛሬ ክፍል አንድ ከሰለምና ከአገር ደህንነት አንጻር ( Peace and national security perspective) የብልጽግና መንግስት ምን ያህል አገር ማስተዳደር እንዳልቻለ
Posted in Ethiopian News

በአንድ ወር ብቻ አስር ሺሆችን የጨረሰው ጦርነት መቆም አለበት #ግርማካሳ

ኢትዮጵያ አሁንም እያነባች ነው፡፡ ልጆቿ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍል እንደ ቅጠል እየረገፉ ነው፡፡ በሰሜኑ የአገራችን ክፍል፣ ነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ/ም የተጀመረው ጦርነት አንድ ወር ሆኖታል፡፡ በዚህ ሶስተኛ ዙር ጦርነት የሞቱ ኢትዮጵያዉያን ቁጥር በአንደኛው ዙር ከሞቱት በብዙ እጥፍ የጨመረ መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ ነው፡፡ በአጭሩ አነጋገር እየተላለቅን ነው፡፡ በወለጋ ዜጎች በግፍና በጭካኔ እየሞቱ ነው፡፡ በሰሜን ቢያንስ ማን ከማን ጋር እየተዋጋ እንዳለ ይታወቃል፡፡ የሚሞቱትም በዋናነት በዉጊያው ላይ ያሉ ወገኖች ናቸው፡፡ በወለጋ ግን ንጹሃን ሰላማዊ ዜጎች ናቸው እየተጨፈጨፉ ያሉት፡፡ ብዙዎቹ የሚገደሉት ዘር ተኮር በሆነ መልኩ በማንነታቸው ሲሆን፣ ገዳዮቹ በትክክል እነ ማን እንደሆኑ እንኳን አይታወቅም፡፡ የህዝብን ሰላም ደህንነት ይጠብቃል የተባለው የአገር መከላከያ ሰራዊት ሆነ የኦሮሞ ክልል ልዩ ኃይል ዜጎችን መጠበቅ አልቻሉም፡፡ የፌዴራልና የኦሮሞ ክልል መንግስታት ሸኔን የሚሉትን ይከሳሉ፡፡ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የኦሮሞ ብልጽግና ይከሳል፡፡ በመሃል ግን ህዝብ እያለቀ ነው፡፡ በተለይም አማራዎች በማንነታችው እየተጨፈጨፉ ነው፡ እዚህ ጋር አንድ በትልቁ ሊሰመርበት የሚገባ ነገር በወለጋ እየተጨፈጨፉ ላሉት በዋናነት ተጠያቄ የአብይ አህመድና የሺመልስ አብዲሳ የኦህዴድ/ብልጽግና መንግስት መሆኑ ነው፡፡ 1ኛ ሸኔ በሚሉት እያሳበቡ ጭፍጨፋዉን የሚፈጽሙት እነሱ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ 2ኛ እነርሱ አይደሉም እንኳን ቢባል፣ ሕዝብን የመጠበቅ ግዴታ ያለባቸው ስለሆኑ፣ ህዝብን መጠበቅ ባለመቻላችው፣ ጨፍጫፊዎች ህዝብን እንዲጨፈጭፉ ሁኔታዎችን በማመቻቸታቸው ይጠየቃሉ፡፡ ወደ ስሜኑ የአገራችን ክፍል ስንመለስ በአሁኑ ጊዜ በዋናነት ጦርነት በዘጠኝ መስመሮች እየተደረጉ ነው፡፡ በበዛላምባሳ/አዲግራት፣ በጾሮና፣ በራማ፣ በሽራሮ/ሽሬ፣ በደደቢት/ሽሬ፣ በጠለምት፣ በተኩለሽ/ቆቦ፣ በጎብዬ/ቆቦ እና
Posted in Ethiopian News

ለይቅርታ ያልተዘጋጀ ማህበረሰብ ፣ የተረገመና ጠፊ ማህበረሰብ ነው #ግርማካሳ

እንኳን ለብርሃኑ መስቀሉ አደረሳችሁ፣ አደረሰን፡፡ መስቀል የሰላም፣ የፍቅር የእርቅ ምልክት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶር አብይ አህመድ የመስቀል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ የሚያሳዝነው ግን መስቀልን እያከበርን ባለበት ወቅት በአስር ሺሆች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን በኢትዮጵያዉያን እየተገደሉ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ራሳቸው በመስቀል መልእክታቸው ስለ ጦርነት አውርተዋል፡፡ ምንድን ነው ችግራችን ? ምንድን ነው የሚያጣለን ? ምንድን ነው የሚያገዳድለን ? ኢትዮጵያ አገራችን ለሁላችንም ሳትበቃ ቀርታ ነው ? በቅርቡ ብቻ በጠሊሞ በተደረገው ውጊያ በአስር ሺሆች ነው ከሁሉም ወገን በአጭሩ የተቀጩት፡፡ በወርቄ በአንድ አካባቢ በተደርገ ጦርነት በአንድ ቀን ውጊያ ወደ 4 ሺህ ዜጎች እንደሞቱ ሰምቻለሁ፡፡ የትግራይ ታጣቂዎች፣ ፋኖዎች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የአማራና የአፋር ልዩ ኃይሎች፣ የኤርትራ ወታደሮች .. ፡፡ አንዳንዶች ለእናት አባቶቻቸው አንድ ልጅ የነበሩ ናቸው፡፡ አንዳንዶች ባይሞቱ ኖሮ ሃኪሞች፣ ኢንጂነሮች፣ ታላላቅ ቢዝነስማኖች፣ የተከበሩ ዳኞች፣ ሚኒስቲሮች፣ ሳይንቲስቶች …ሊሆኑ የሚችሉ ነበሩ፡፡ የመስቀልን ቀንና በአገራችን እየተደረገ ያለውን ጦርነት ሳስብ አንድ ነገር ውስጤ መጣ፡፡ የትግራይ ታጣቂዎች ብዙዎቹ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ አንገቶቻቸው ላይ መስቀል ያደረጉ ብዙ ይኖራሉ፡፡ ከጥምር ጦሩም እንዲሁ ብዙዎች መስቀል አንገታቸው ላይ ያጠለቁ ይኖራሉ፡፡ አስቡት፣ በየ አብያተ ክርስቲያናቱ አንድ አይነት ቅዳሴ የሚያስቀድሱ፣ “እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ” የሚሉ፣ እግዚአብሄር በማይፈሩ፣ አንድ ወቅት ማርክሲስት በነበሩ፣ እንፈራለን ቢሉም ደግሞ፣ በከንፈር እንጂ ልባቸው ከእግዚአብሄር በራቀ የፖለቲካ መሪዎች፣ እርስ በርስ እንዲጨራረሱ እየተደረገ ነው፡፡ የአገራችን ትልቁ ችግር ግለሰቦች አይደሉም፡፡ ዶ/ር አብይ አህመድ፣ ዶ/ር ደብረ ጽዩን ፣ ጃል መሮ ወዘተ አይደሉም፡፡
Posted in Ethiopian News

የግጭት ጠማቂው ብልጽግና ክህደት #ግርማካሳ

አርበኛ ዘመነ ካሴን መታሰሩን ሰማን፡፡ ጫካ ተዋግተው፣ ማርከው፣ አሸንፈው ሳይሆን ባህር ዳር ከተማ በሽምግልና ምክንያት ሲመጣ ነው ዘመነን ያዝን እያሉ እያወሩ ያሉት፡፡ በኔ እምነት አርበኛ ዘመነ ካሴ አንድ የሰራው ትልቅ ስህተት አለ፡፡ እርሱም የክህደትና የውሸት ቋት ፣ የአብይ አህመድ አሽከሮችን ትርፍ አንጀቶች የሆኑ ብልጽግዎችን አምኖ ባህር ዳር መምጣቱ ነው፡፡ ለነገሩ ዘመነን ማሰራችው ማሰብ ተስኗቸው፣ ደንቆሮዎች ሆነው እንጂ፣ የሚጎዳው እነርሱን መሆኑን በተረዱ ነበር፡፡ ዘመነ ካሴ የህዝብ ልጅ ነው፡፡ በሕዝብ ኃይልም ይፈታል፡፡ የብልጽግና መንግስት በአስር መለያዎችና ባህሪያቶች ብዙ ጊዜ ስገልጸው ነበር፡፡ 1ኛየጦርነት፣ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት መንግስት 2ኛ የመፈናቀል መንግስት 3ኛ ሰላም ባለበት ግጭትና ቀውስ ጠማቂ መንግስት 4ኛ የዉሸት ቋት የሆነ አታላይና አጭበርባሪ መንግስት 5ኛ ዘረኛና ተረኛ ፣ አባገዳዊ መንግስት 6ኛ የረሃብና የድህነት መንግስት 7ኛ የመከፋፈለና የመለያየት መንግስት 8ኛ ብቃት የሌለው የመኃይማን ካድሬዎች ስብስብ መንግስት 9ኛ አፋኝና አጋች ፣ አምባገነንና ጸረ ዴሞክራሲያዊ መንግስት 10ኛ በሌበነት፣ በዝርፊያ የበሰበሰ መንግስት አሁን 11ኛ ጨምሬበታለሁ፡፡ ከሃዲ መንግስት የሚል፡፡ የአብይ አህመድ ኦህዴድ ብልጽግናዎችን ከሃዲነት በጥቂቱ ለማሳየት ልሞክር፡ # ወደ ስልጣን የመጡት በአዴፓ/ብአዴኖች ትከሻ ላይ ነበር፡፡ ስልጣን ከያዙ በኋላ ግን አንድ በአንድ እነ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን፣ እነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው የመሳሰሉትን አየር ላይ አንሳፈዋቸዋል፡፡ ክህደት ፈጸመውባቸው፡፡ # ከኤርትራዊያን ጋር ስምምነት አድርገው ነበር፡፡ ከነ ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በፍቅር እፍ ብለው ነበር፡፡ በኋላ ግን ሕወሃት ትሻለናለች ብለው ኤርትራዉያንን ክደው፣ ከሕወሃት
Posted in Ethiopian News

ባንሰማም ተኩስ ይቆም፣ ደም አይፍሰስ እንላለን #ግርማካሳ

በሰሜን ኢትዮጵያ እየተደረገ ያለው ሕዝብ ጨራሽ ጦርነት ከሰሞኑ ጋብ ብሎ የነበረ ቢሆንም፣ እንደገና አገርሽቶ በብዙ ግንባር ሲካሄድ ዉሏል፡፡ በዋናነት በኤርትራ ድንበር አካባቢ ከፍተኛ ውጊያዎች ተጀምረዋል፡፡ በአጭሩ አነጋገር የኤርትራ ወታደሮች በይፋ ጦርነቱን ተቀላቅለዋል ማለት ይቻላል፡፡ የኤርትራ ወታደሮች ጦርነቱን የተቀላቀሉት በሶስት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛው የሕወሃት ተጠናክሮ መውጣት እኛንም ስጋት ውስጥ ይከተናል የሚል እምነት ስላላችው፡፡ ለምን ከከበባ ለመውጣት አንዱ አማራጭ አድርገው ህወሃቶች የወሰዱት ኤርትራን ወሮ ምጽዋን መቆጣጠር ስለሆነ፡፡ ሁለተኛ ሕወሃቶች በኤርትራ በኩል ብዙ ጊዜ ትንኮሳዎች ስላደረጉና ኤርትራውያንን ራሳቸውን የመመከት መብት ስላላቸው፡፡ ሶስተኛ በኢትዮጵያ መንግስት ስለተጠየቁና ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነት ስላደረጉ ነው፡፡ የኤርትራ ወደ ጦርነቱ መግባት ትክክል ነው፣ ትክክል አይደለም የሚለውን ክርክር ለጊዜው እናቆየውና ህጋዊ ነው ሕጋዊ አይደለም የሚለውን እንመልከት፡፡ በዓለም አቀፍ ሕግ መሰረት ፣ ኤርትራ አንዲት ሌላ ሉዓላዊ አገርን አልወረረችም፡፡ በኢትዮጵያ ሉዓላዊ መንግስት ተጠይቃ ወታደሮቿ በኢትዮጵያ ምድር እንዲገቡ መደረጉ ያ አለም አቀፍ ሕግን መጣስ አይደለም፡፡ ሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ/ም ፣ መከላከያ ከትግራይ እንዲወጣ ዶር አብይ አህመድ ትእዛዝ ሲሰጥ፣ ለኤርትራ ወታደሮችም ተመሳሳይ ትእዛዝ ስለሰጠ፣ ኤርትራውያን ለቀው ወጥተዋል፡፡ ለምን የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት ሳይፈቅድላችው ኢትዮጵያ ውስጥ መቆየት ስለማይችሉ፡፡ አሁን ደግሞ ወደ ትግራይ የተመለሱት በፌዴራል መንግስቱ ጥሪና ጥያቄ ነው፡፡ ስለዚህ ኤርትራዉያን ለምን ገቡ የሚል ጥያቄ ከተነሳ፣ ጥያቄውን መመለስ ያለባቸው አራት ኪሎ ያሉት ናቸው፡፡ እነ አብይ አህመድ ያው የዉሸት ቋት መሆናቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ከሃዲዎች ናቸው፡፡ ያለፈው ጊዜ
Posted in Ethiopian News

መሸነፍ ሳይሆን ጦርነት መቀጠሉ ነው ትግራይን የሚያጠፋው #ግርማካ

“የጦርነቱን ሁኔታ አስመልክቶ፣ ሰከን እንበል” በሚል ርእስ የጻፍኳት ጦማር፣ ትንሽ ጠንከር ያለ ትችት ከአንዳንድ ወገኖች አስነስታብኛለች፡፡ ብዙዎች፣ “ሕወሃት ነህ፣ ጁንታው ነህ” እያሉ ሲከሱም ታዝቢያለሁ፡፡ አንድ ትንሽ ያሳቀችን አስተያየት ላጋራችሁ፡፡ አንዱ የለጠፈልኝ፣ “ይህን ሁሉ አንብቤ ምን እንዳልኩ ታውቃለህ? መጀመሪያ ታደሰ ወረደ፣ ቀጥሎ ያንተ ፅሁፍ ወረደ…ለስላሳ ታደሰ ወረደ ነህ! ” የሚል፡፡ በዚህ አጋጣሚ የተሰማቸውን አስተያየት ለሰጡኝ በሙሉ ፣ የድጋፍም፣ የተቃውሞም፣ ላመሰግን እወዳለሁ፡፡ ቢያንስ በጦማሩ ብንስማማም፣ ባንስማም ብዙዎቻችን ራሳችንን እንድንጠየቅ እያደረገ ስለሆነ ተደስቻለሁ፡፡ እኔን በተመለከተ ስለተባለው ፣ ብዙም እዚያ ላይ ጊዜ አላጠፋም፡፡ “ወያኔ ነህ፣ ገንዘብ ተከፍሎህ ነው…” ወዘተ ለምትሉ እንዳላችሁ ይሁንላችሁ ብዬ እተወዋለሁ፡፡ አሁን የኔ ጉዳይ ሳይሆን አሳሳቢው፣ በሰሜኑ አገራችን ክፍል፣ በሕወሃትና ብልጽግና ጸብ ምክንያት፣ እንደ ቅጠል እየረገፉ ያሉ ወገኖች ጉዳይ ነው፡፡ ጦርነቱን በተመለከተ ባሰባሰብኩት መረጃ፣ አሁንም ዉጊያዎች በከፋ ሁኔታ እንደቀጠሉ ናቸው፡፡ ያሳዝናል፡፡ በጠለምት መስመር የህወሃት አዋጊዎች ተከዜን ተሻግረው ወደ አዲ ገብሩ መሄዳቸው ተሰምቷል፡፡ ጥምር ጦሩም እንዳይከተል የተከዜ ድልድይ ላይ ጉዳት እንዳደረሱ እየተነገረ ነው፡፡ በአጭሩ አነጋገር፣ ማይጠምሪን ጨምሮ ሙሉ ጠለመት በጥምር ጦሩ ስር ወድቋል ማለት ነው፡፡ እንግዲህ አስቡት ማይጠምሪ ፣ ከደርግ በኋላ አራት ጊዜ ከአንድ መስተዳደር ወደ ሌላ መስተዳደር ዞራለች፡፡ ደርግ ሲወድቅ ሕወሃቶች ከጎንደር ወስደው በጉልበት ወደ ትግራይ ጠቀለሏት፡፡ የትግራይ ክልል አካል አደረጓት፡፡ በሕዳር 2013 ዓ/ም ደግሞ በኃይል በጉልበት ወደ ጎንደር አማራ ክልል ተቀላቀለች፡፡ በነሐሴ 2013 ዓ/ም በሕወሃት እንደገና ወደ ትግራይ መጣች፡፡ በመስከረም
Posted in Ethiopian News

የጦርነቱን ሁኔታ አስመልክቶ፣ ሰከን እንበል #ግርማካሳ

ጀነራል ታደሰ ወረደ በጦርነቱ ዙሩያ የሰጠውን ረጀም ገለጻ አደመጥኩ፡፡ የጦርነቱ ሁኔታ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ጥሩ ግንዛቤ የሚሰጥ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ የህወሃት ጦር በራያ ግንባር ጥሩ ደረጃ ላይ እንዳለ ፣ እስከ ወልዲያ ድረስ በአስተማማኝ ሁኔታ እንደተቆጣጠረ፣ ቢፈልግ ወልዲያን በቀላሉ መያዝ እንደሚችልና ወታደራዊ የበላይነት እንዳለው ነው የገለጸው፡፡ በርካታ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እንደተማረኩም ጠቁሟል፡፡ ጀነራሉ በምእራብ በኩል ግን ችግር እንዳለ ነው ያመላከተው፡፡ ሽራሮንና ደደቢት ከቁጥጥራችው ውጭ እንደሆነ፣ በአደርቃይ/ጠለምት መስመርን አጣቢቅኝ ውስጥ እንደገቡ ነው የገለጸው፡፡ ከሽራሮ፣ ከደደቢትና ከጠለምት የመጡት እንዳይገናኙ እየሰራን ነው ብሏል፡፡ በሌላ አባባል ሽሬ እንዳትያዝ ማለቱ ነው፡፡ ለምን ከደደቢትና ከሽራሮም፣ ከጠለምት የሚመጡት የሚገናኙት ሽሬ ላይ በመሆኑ፡፡ በጦርነት ህወሃት ምንም ነገር ማሳካት አትችልም ብለን ብዙዎቻችን ስንናገርና ስናስጠነቅቅ ያሾፉ የነበሩ አፍቃሪ የህወሃት ደጋፊ ሜዲያዎች፣ ብሎገሮች …ነበሩ፡፡ የጀነራል ታደሰ ማብራሪያ፣ እነዚህ ወገኖች አይናቸውን እንዲከፍቱ ሊያደርግ ይችላል ብዬ አስባለሁ፡፡ በሌላ በኩል የሽራሮና የደደቢትን መያዝ በጀነራል ታደሰ መገለጹን ተከትሎ ብዙዎች ሕወሃት አለቀላት እያሉ ነው፡፡ የብልጽግና ተለጣፊ ተደማሪ አጋር ፓርቲዎች፣ አብንና ኢዜማም ፣ ጦርነቱ መቆም እንደሌለበት፣ ወያኔን እስከመጨረሻ መደምሰስ እንዳለበት የሚገልጹ መግለጫዎች አውጥተዋል፡፡ ከነዚህ ድርጅት መግለጫ ጋር በተገናኘ የኢዜማን አደርባይነትና ግብዝነትን ሳልጠቁም ማለፍ አልፈልግም፡፡ ኢዜማ በመግለጫው ሕወሃትን የዘር ፖለቲካን በአገራችን ያመጣ ነው ብሎ ይከሳል፡፡ የህወሀሃትን የዘር ፖለቲካ፣ የዘር አወቃቀር፣ የዘር ሕገ መንግስት በአምስተኛ ማርሽ እያስቀጠለ ካለው፣ ከህወሃት ከባሰው ዘረኛና ተረኛ የኦህዴድ/ብልጽግና አገዛዝ ጋር አጋር ሆነው እየሰሩ ባለበት ሁኔታ፣
Posted in Ethiopian News

የሕወሃት ጀነራሎች ትላልቅ ስህተቶች #ግርማካሳ

ነሐሴ 18 ቀን ሕወሃቶች ለሶስተኛ ጊዜ የከፈቱት ጦርነት አድማሱን አስፍቶ ፣ ከፍተኛ የዜጎች ሕይወት መቀጠፍንና ጥፋት እያስከተለ ነው፡፡ በራያ በኩል በስሜን ወሎ በሶስት አቅጣጫ የተጀመረው ውጊያ ቀጥሎ ውሏል፡፡ በአፋር ክልል ዞን 4፣ በሰሜን ሸዋ ቆቦና ጊዳን ወረዳዎች ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች አሉ፡፡ ላለፉት ሁለት ቀናት ደግሞ በወልቃይት መስመር፣ በሱዳን በኩል፣ በማይጠምሪ/አደርቃይ መስመር፣ በተንቤን/አበርገሌ/ሰቆጣ መስመር፣ ከኤርትራ ጋር በሽራሮና በራማ መስመር ውጊያዎች ተቀስቅሰዋል፡፡ ጀነራል ጻድቃን የቀድሞ የኢትዮጵያ የኤታ ማጆር ሹም የነበረ ሰው ነው፡፡ ሌተና ጀነራል መዓረግነት ያለው፡፡ በተለያዩ አለም አቀፍ ድርጅቶች የሚሊተሪ ጠበብት ተብሎ በአማካሪነት ሲያገለግል የነበረ ነው፡፡ ቢቢሲ እንደውም አንድ ዘገባ ሰርቶ። “The commander of Tigrayan rebel forces, Gen Tsadkan Gebretensae, is regarded by international security analysts as one of the finest military strategists of his generation in Africa.” ብሎ ነው ያወደሰው፡፡ የወጣነት ጊዜውን በጦርነት ያሳለፈ፣ የጦርነትን አስከፊነት የሚያውቅ ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ጀነራል ታደሰ ወረደም (ወዲ ወረደ) በኢትዮጵያ መከላከያ ውስጥ ላይ ከደረሱ የጦር አዛዦች መካከል አንዱ ነበር፡፡ እርሱም ሌተና ጀነራል የነበረ ሲሆን፣ በደቡብ ሱዳን በአብዬ፣ የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ጦር ዋና አዛዥ ሆነ የሰራ ሰው ነው፡፡ በወቅቱ በሱዳን በሰራው ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ መድረክ ከፍ ብላ እንድተጠራ ያደረገ፡፡ አንድ በሳል፣ አስተዋይ ጀነራል ወደ ጦርነት ከመግባቱ በፊት መስራት ያለባቸው የቤት ስራዎች አሉ፡፡ ከሁለት ሺህ አመት በፊት የነበረው ታዋቂው የቻይና ሚሊተሪ ስትራቲጂስት ዙጌ ሊያን፡ “አዋቂ
Posted in Ethiopian News

“ተለቀቀ፣ ተያዘ” ከሚለው ጨዋታ እንውጣ #ግርማካሳ

“ይሄ ተያዘ፣  ያ ተለቀቀ” ለሚል ስሜታዊ ፕሮፖጋንዳ ጊዜ መስጠቱ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ከዚህ ጋር በተገናኘ የማዘንና የመደሰት የዥዋዥዌ ጨዋታ ውስጥ መግባት ያለብን አይመስለኝም፡፡ ይልቅ ሁላችንም ልንጠይቃቸው፣ ሊያስጨንቀን የሚገቡ ጉዳዮችና ጥያቄዎች አሉ፡፡ “ተለቀቀ፣ ተያዘ”  የሚል ጨዋታ መቼ ነው የሚቆመው ? ጦርነቱ በድርድር ይሁን በአንዱ አሸናፊነት መቼ ነው የሚጠናቀቀው ? ትግራይ፣ ጎንደር፣ ወሎና እፋርም ያለው ህዝብ መቼ ነው ሰላም የሚያገኘው ? ወዘተ የሚሉት ናቸው:: ኢትዮጵያ ውስጥ ፣ “መንግስት አለ” ነው የሚባለው፡፡ ራሱን የብልጽግና መንግስት ብሎ የሚጠራ፡፡ ሆኖም በዚህ መንግስት አገራችን ኢትዮጵያ ያየችው ቢኖር ረሃብ፣ ጦርነት፣ መፈናቀል፣ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጻዳር ወጀሎች፣ የኑሮ ዉድነትና በአገራቸውን የዜጎች ተስፋ መቁረጥ ነው፡፡ ይህ መንግስት ህዝብን የሚዋሽ፣ ለህዝብ ስቃይና መከራ ደንታ የማይሰጠው መንግስት ነው፡፡ በስሜኑ የአገራችን ክፍል ላለው ስቃይም መከራ፣ ደም መፋሰስና እልቂት በዋናነት ተጠያቂው የብልፅግና መንግስት ነው፡፡ 1ኛ ብዙ ጊዜ ፣ በጦርነት ህወሃትን ሙሉ ለሙሉ ማሸነፍ ሲቻል፣  ጫፍ ሲደረስ፣ ተኩስ አቁሙ እያሉ፣ ህወሃትን ማዳን ብቻ ሳይሆን እንደገና እንድትጠናከር እድል የሰጡና እየሰጡ ያሉት ብልጽግናዎች ናቸው፡፡ በቀዳሚነት የኦህዴድ/ብልጽግና፡፡ 2ኛ ህወሃቶች ለድርድር ፍቃደኛ እንዲሆኑ፣  ቢያንስ ሁሉንም ባይሆን ግማሹን  ህወሃቶች የጠየቁትን ፣ የአብይ አህመድ የብልጽግና መንግስት መሟላት ይችል ነበር፡፡ መብራት: ኔትዎርክ የመሳሰሉት ማስጀመር ችግር አልነበረም፡፡ ለህዝብ የሚያስብ መንግስት ቢሆን ኖሮ ህወሃቶች ሳይጠይቁ ማድረግ ነበረበት፡፡እነዚህን መሰረታዊ አገልግሎቶች ማሟላት ቢቻል ኖሮ ምን አልባት ህወሃት ወደ ውጊያ እንዳትሄድ ህዝቡም ጫና ያደርግባት ነበር፡፡  ህወህት ጦርነቱን
Posted in Ethiopian News

በጦርነት ውድቀት እንጂ ትእስርነት አይመጣም #ግርማካሳ

በጦርነት ውድቀት እንጂ ትእስርነት አይመጣም #ግርማካሳ #NoMoreWar #stopwar በአገራችን እየሆነ ባለው በጣም አዝኛለሁ፡፡ እጅግ በጣም፡፡ ልዩነቶችን በድርድር መፍታት ሲቻል፣ በህዝብ መካከል ምንም አይነት አብሮ በሰላም የመኖር ችግር ሳይኖር፣ ለፖለቲካው ልሂቃኑ ድንቁርናና ከዘር ፖለቲካው የተነሳ፣ በማይረባ ጦርነት ውስጥ እንድንገባ ተደርገን ኢትዮጵያውን ወገኖቻችን እንደ ቅጥል እንዲረግፉ መደረጉ ውስጥን የሚሰብር ነው፡፡ በሰሜን ሸዋ፣ በዋገመራ፣ በሰሜን ጎንደር፣ በአፋር፣ በጦርነቱ ምክንያት በአፋሩና በአማራው ላይ እየደረሰ ያለው ሰቆቃና ችግር እጅግ በጣም አሳሳቢ ነው፡፡ ማህበረሰቡ በመንግስት እየደረሰበት ያለው አሻጥር፣ መረሳትና ወከባ እጅግ በጣም አሳዛኝ ነው፡፡ የአፋር ክልል ቢያንስ ለህዝብ የሚቆረቆር መንግስት አለው፡፡ የአማራ ክልል ማህበረሰብ ግን በአንድ በኩል በህወሃት፣ በሌላው በኩል በአብይ አህመድ የብልጽግና መንግስት መከራዉን እየበላ ያለ፣ የተካደ ማህበረሰብ ነው፡፡ የሕዝብ ልጆች የሆኑት ፋኖዎች ከብልጽግዎች ችግር እየደረሰባቸው ቢሆን ለህዝቡ እየቆሙ ነው፡፡ ቢያንስ ሕዝብ ፋኖዎች አሉልን እያለ ነው፡፡ በፖለቲካው ረገድ ግን ለአማራው የሚቆምለት፣ የሚቆረቆርለት፣ የሚሟገትለት የፖለቲካ ኃይል የለውም፡፡ የአማራ ብልጽግናዎች ሽጠዉታል፡፡ የአብኖቹን ሁኔታ የምታወቁት ነው፡፡ በአማራ፣ አፋር ክልልና በፌዴራል መንግስት ደረጃ ስላለው ሁኔታ በሌላ ጊዜ በስፋት እመለስበታለሁ፡፡ የዛሬው ጦማሬ ትኩረት የትግራይ ወገኖች ጋር ይሆናል፡፡ በጦርነት መተላለቅ ትልቅነት አይደለም፡፡ ጀብድ አይደለም፡፡ ስለዚህ እዚህ ጋር ይሄ ቦታ ተያዘ፣ ያ ተለቀቀ እየተባለ የሚነገረው ላይ ማተኮር አልፈለግም፡፡ ጦርነቱ በመደረጉ፣ ቦታ የያዘው አላሸነፈም፣ ቦታ የለቀቀውም አልተሸነፈም፡፡ ሁላችንም ነው የተሸነፍነው፡፡ ሕወሃት ለሶስተኛ ጊዜ ነሃሴ 18 ቀን 2014 ዓ/ም በሺሆች የሚቆጠር ሰራዊት አሰልፋ ፣
Posted in Ethiopian News

የመረጃ ቲቪ ሁለተኛ አመት ዝግጅት – ልዩ ዝግጅት

የመረጃ ቲቪ ሁለተኛ አመት ዝግጅት – ልዩ ዝግጅት በተመለከተ  ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ይችን ይጫኑ ፡፡ https://www.eventbrite.com/e/mereja-tv-2nd-anniversary-event-in-silver-spring-maryland-tickets-385348707357
Posted in Ethiopian News

የአማራ ክልል ነዋሪ መሆን ወንጀልና ነውር የሆነ ይመስል .!!!!! #ግርማካሳ

ከትግራይ ዛላምበሳ ወደ ኤርትራ ሰንዓፈ ማለፍ አስቸጋሪ እንደሆነው፣ ከደብረ ብርሃን ወደ አዲስ አበባ ማለፍም አስቸጋሪ የሆነበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ በትግራይና በኤርትራ መካከል ችግር ቢኖር በጦርነቱ ምክንያት ነው፡፡ በመሃል ሸዋ ግን በጦርነት ምክንያት አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድን ነው ችግሩ ? ዜጎች በሰላም አገር ከደብረ ብርሃን ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ የሚከለከሉት በምን ምክንያት ነው ?በኔ እይታ አራት ምክንያት ያሉ ይመስለኛል፡፡ 1ኛ የዘመኑ ሰዎች ጡንቻቸውን ለማሳየትና ምን ታመጣላችሁ ለማለት ስለፈለጉ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ 2ኛ ሌላው ማህበረሰብ መብቱ ሲገፈፍና ሲሰቃይ ከማለቃቀስ ውጭ መብቱን ለማስክበር የተዘጋጀ ባለመሆኑ ነው፡፡ ባርነት፣ ግፍን፣ ጭቆናን አሜን ብሎ በመቀበሉ፡፡ 3ኛ ባለተረኞች የአማራ ማህበረሰብ አባላት በአዲስ አበባ እየበዙ ናቸው ከሚል፣ ከአማራ ክልል ፍልሰቱን ማስቆም አለብን ከሚል ነው፡፡ 4ኛ ትልቁ ምክንያት ደግሞ ሌብነት ነው፡፡ እንደ እሮሞ ክልል ሃላፊዎችና ፖሊሶች ሌባና ዘራፊ፣ ጉቦኛ የለም፡፡ አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ናት፡፡ ከሁሉም የአገሪቷ ግዛት ኢትዮጵያዉያን ወደ ዋና ከተማቸው የመምጣት፣ በዚያም የፌዴራል መንግስትን አገልግሎቶች የማግኘት መብት አላቸው፡፡ በአዲስ አበባ በተለያዩ ጉዳዮች ዜጎች ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ፡፡ ዘመድ ለመጠየቅ ለህክምና ፣ በአዲስ አበባ በኩል ወደ ውጭ አገር ለመውጣት፣ በአዲስ አበባ ቢዝነሶች ለመከፈት ወዘተ …። ግን ተረኞች ለዚያ ደንታ የላቸውም፡፡ ፍጹም ጋሪዪሻዊና ዘረኛ ገጽታቸውን እያሳዩ ነው፡፡ በጣም የሚገርመውና የሚያሳዝነው የኦሮሞ ክልል ፖሊሶች፣ በፖለቲካ አመራሩ መመሪያ መሰረት፣ ዜጎችን እያስቆሙ፣ መታወቂያ እያዩ፣ አማራ ክልል ነዋሪ መሆን ወንጀልና ነውር የሆነ ይመስል፣
Posted in Ethiopian News

የጉራጌ ማህበረሰብ ከሸገር ጋር ቢቀላቀል የሚመርጥ ይመስለኛል #ግርማካሳ

የዘር ፖለቲካው ጡዘት ቀጥሏል፡፡ የአገር ችግር የዘር ፖለቲካው ነው፡፡ የዘር ሕገ መንግስቱ ነው፡፡ ዜጎች በዘራቸው እንዲያስቡ፣ በዘራቸው እንዲሰባሰቡ፣ በዘር መነጽር ሁኔታቸውን እንዲመለከቱ የሚያደርግ ስርዓትና ፖለቲካዊ ሲስተም ባለበት፣ የአገርን ችግር ለመፍታት መሞከር በድንጋይ ላይ ዉሃ እንደ ማፍሰስ ነው፡፡ በአገራችን ከሰሞኑ ከተፈጠሩ በርካታ ክስተቶች መካከል አንዱ በደቡብ ክልል ያለው የአከላለል ውዝግብ ነው፡፡ በተለይም በጉራጌ ዞን ፣ “የጉራጌ ክልል መኖር አለበት” በሚል ከፍተኛ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፡፡ ከዚህ በፊት በወላይታ የነበረውን ተመሳሳይ እንቅስቃሴ በኃይል ለመጨፍለቅ እንደተሞከረው፣ ይሄንን የጉራጌዎች ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በጠመንጃ አፈሙዝ ለመድፈቅ በብልጽግና መንግስት እየሞከረ ነው፡፡ የጉራጌ ማህበረሰብ፣ “እኛ ነን የምናውቅልህ” ብለው የግፍ ዱላ እያወረዱበት ነው፡፡ የጉራጌ ማህበረሰብ ለምን የራሱ ክልል እንዲኖረው ፈለገ ? በኦህዴድ የሚመራውስ የብልጽግና መንግስት ለምን የጉራጌ ክልል መሆንን ተቃወመ ? ለነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ከመስጠቴ በፊት፣ የጉራጌ ማህበረሰብን በተመለከተ ሁለት መሰረታዊ ጭብጦችን ለማስቀመጥ ልሞከር፡፡ 1ኛ ፣ ከ15 አመታት በፊት በተደረገው የመጨረሻው ይፋዊ የሕዝብ ቆጠራ ሪፖርት መሰረት፣ ጉራጌዎች ቁጥራቸው 1859831 እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡ በጉራጌ ዞን ያሉ ጉራጌዎች 1049305፣ በደቡብ ክልል 1125929፣ በአዲስ አበባ 447777 በኦሮሞ ክልል 248100 ናቸው፡፡ በአገር ደረጃ ካሉ ጉራጌዎች 56 % የሚኖሩት በጉራጌ ዞን ሲሆን፣ 24.1% በአዲስ አበባ፣ 13.3% በኦሮሚያ፣ 4.1% ከአስር አመታት በፊት ከጉራጌ ዞን ውጭ ደቡብ ክልል ይባል በነበረው ክልል የሚኖሩ ናቸው፡፡ 2.1% የሚሆኑት በሌሎች የአገሪቷ ክፍል የሚኖሩ ናቸው፡፡ በኦሮሞ ክልል በደቡብ ምእራብ ሸዋና በምስራቅ
Posted in Ethiopian News

የተዘረጉ እጆችን ፈጣሪ ይመልከትልን #ግርማካሳ

ጎይቲቶም ገብረስላሴ፣ ለተሰንበት ግደይ፣ ጉዳፍ ጸጋዬ በሴቶች ማራቶን፣ በ 10 ሺህና በ 5 ሺህ ወርቅ በማስገኘት፣ ኢትዮጵጵያ በአለም አቀፍ መድረክ ከፍ ከፍ ያስደረጉ ትግራይ የተወለዱ ፣ ብርቅዬ የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ ​ በአትሊቶቻችን ውስጤ ደስ ብሎታል፡፡ ኮርቼባቸዋልሁ፡፡ የአምስት ሺሁን ሩጫ ላይቭ ነበር ስከታተል የነበርኩት፡፡ ፈነጠዝኩ፡፡ ትንሽ ቆይቼ ግን አዘንኩ፡፡ አንዳንዶቻችን ሩጫውን ላይቭ ስንከታተል፣ ሌሎቻችንም በሶሻል ሜዲያ ስናይ፣ ደስታችንን ስንገልጽ፣ የነለተሰንበት፣ ጎይቲቱምና ግዳፍ ወለጆች፣ እህቶች፣ ወንድሞች፣ ዘመድ አዝማድ፣ ያሳደጓቸው ሰፈርተኞች ግን መከታተል አልቻሉም፡፡ በትግራይ መብራት የለም፣ ኔትዎርክ የለም፣ ሁሉም ነገር ጨለማ ነው፡፡ በትግራይ ሰላም የለም፡፡ የጦርነትና የእልቁት ስጋት ብቻ ነው ያለው፡፡ እነ ለተሰንበት ሩጫቸውብ ሲቸርሱ እጆቻቸውን ወደ ፈጣሪ ዘርግተው አምላካቸውን አመስኘዋል፡፡ ምስጋና ብቻ አይመስለኝም፡፡ ልመናም ያቀረቡ ይመስለኛል፡፡ ተግራይ ያሉ ቤተሰቦቻቸውን አስታውሰው፡፡ እግዚአብሄር አምላክ፣ የነ ለተሰንበትን የተዘረጉ እጆች ተመልክቶ፣ ሰላምን በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ያውርድልን፡፡ በዚህ አጋጣሚ ክርዝሺህ በፊትም ብዙ ጊዜ እንደጠየኩት፣ የፌዴራል መንግስቱ በአስቸኳይ የስልክና የኤሌትሪክ አገልግሎት እንዲጀመር በአጽንኦት እጠይቃለሁ፡፡ አዎን ድርድር የሚሉት ይህ ድርድር የሚሉት ነገር አለ፡፡ ግን ይህ ድርድር ከሚባለው ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡ የተበላሹ ፣ መታደስ፣ መልሶ መገንባት ያለባቸው፣ የኔትዎርክና የመብራት መስመሮች ካሉ፣ የሕወሃት መንግስት ምንም ዓይነት እክል እንደማይፈጥር ቃል ገብቶና በግልጽ አሳውቆ፣ የመብራት ኃይልና የቴሌ ሰራተኞችን ወደዚያ ተልከው በአስቸኳይ ጥገናዎችን መደረግ አለባቸው፡፡ ድርድሩ የተባለው ከተጠበቅ ችግር ነው የሚሆነው፡፡ ድርድሩ በአሁንጁ ወቅት ላይሳካም ይችላል፡፡ በጣም እየተጓተተ ነው፡፡ ኮሚቴ አዋቀርን ይላሉ፣
Posted in Ethiopian News

የኦሮሞና የትግራይ ብሄረተኞች በኦሮሞና ትግራይ ማህበረሰብ ላይ ያመጡት መዘዝ  #ግርማካሳ

    የትግራይና የኦሮሞ ብሄረተኞች በስፋት የራሳቸው የሆኑ ባንዲራዎችን ይጠቀማሉ፡፡ በተለያዩ የትግራይ ብሄረተኞች ዝግጅቶች ቢጫና ቀዩ አርማ ነው የሚታየው፡፡ የኦሮሞ ብሄረተኞች ጋር ደግሞ፣ በውጭ ያሉት የኦነግን ቀይና አረንጓዴ፣ የማዳጋስካር የሚመስል አርማ፣ በአገር ውስጥ ደግሞ የኦሮሞ ክልል አርማ ነው፣ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው፣ የጀርመን፣ ግብጽ፣ ሲሪያ፣ ኦራቅ .ባንዲራዎችን የሚመስለው ቀይ ነጭ ጥቁሩ አርማ፡፡ አዲስ አበባ ከተማ ላይ በጉልበት በትምህርት ቤቶች ላይ ለመስቀል እየሞከሩት ያለው አርማ፡፡ የኦሮሞም ሆነ የትግራይ ብሄረተኞች የኢትዮጵያን አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ አላማም መያዝ አይደለም፣ ሲያዩት ወባ የያዛቸው ይመስል ያንቀጠቅጣቸዋል፡፡ ምክንያቱን “ኢትዮጵያን አንፈልግም፣ ኢትዮጵያዊ አይደለንም” የሚል እሳቤ ስላላቸው፡፡ ታላቋን የትግራይ ሪፑብሊክና ታላቋን የኦሮሚያ ሪፑብሊክ እንመሰርታለን በሚል ስለሚቃዡ፡፡ በዘር ጥላቻ ስለተሞሉ ነው፡፡ ማንም ሰው፣ የኢትዮጵያን ባንዲራ ቢጠላና፣ ሌላ እኔን ይወክላል የሚለውን ባንዲራ ቢይዝ ችግር የለውም፡፡ ምክንያቱም መብቱ ስለሆነ፡፡ ከፈለገ ለምን ጥቁሩን የአይሰስ ባንዲራ ለብሶ አይተኛም፡፡ የኦሮሞም ሆነ የትግራይ ብሄረተኞች የኦሮሞም ይሁን የትግራይ ሪፑብሊክን እንመስርት ብለው ሲንቀሳቀሱ፣ ሕዝቡ ከደገፋቸው፣ የኢትዮጵያ አካል ሆኖ መቀጠል የማይፈልጉ ወረዳዎችም ቀበሌዎች አካባቢዎች፣ ኩታ ገጠም ከሆኑ፣ እነርሱን ይዘው ቢገነጠሉ መብታቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት በግድ የሚሆን ነገር አይደለምና፡፡ ትልቁ ችግሩ ግን ፣ ከብዙሃኑ ጋር የሚያጋጫቸው እነዚህ የትግራይና የኦሮሞ ብሄረተኞች የሌላውን መብት ለመርገጥ መፈለጋቸው ነው፡፡ ሌሎች የሚኖሩባቸውን አካባቢዎች የኦሮሞ መሬት ነው፣ የትግሬ መሬት ነው ብለው ለመስፋፋት፣ ለመውሰድ መፈለጋቸው ነው፡፡ ለምሳሌ አዲስ አበባ ፣ ናዝሬት ወዘተ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ከ20% በታች
Posted in Ethiopian News

ሕገ መንግስቱ አማራ ብቻ ሳይሆን ተጋሩ ጠልም ነው፣ ዜጋ ጠል ..#ግርማካሳ

ዶ/ር ቴዎድሮስ አዳኖም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የነበረ ነው፡፡ ከዚያ በፊት ደግሞ የጤና ሚኒስቴር ሆኖ አገልግሏል፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር የሆነው፣ ከኢትዮጵያ አልፎ አፍሪካንም ይወክላል በሚል፣ በርካታ የአፍሪካ አገራት ድጋፍ ስላደረጉለት ነው፡፡ ይህ ሰው ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ፣ ከአፍሪካ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ቦታ የደረሰ ነው፡፡ ከርሱ ዓለም አቀፋዊ አመለካከት ፣ አቃፊነትን እንጂ ዘረኛና የጎጥ አመለካከትን ማንጸባረቅ አይጠበቅም ነበር፡፡ ለርሱ፣ ከዓለም አቀፋዊነት ወደ ትግራይ ጎጠኝነት መውረድ አይመጥነውም፡፡ እንደ ዶር ቴዎድሮስ አዳኖም ያሉትን ሳስብ፣ ለትግራይ ሕዝብ አዝናለሁ፡፡ ተማሩ፣ ትልቅ ደረጃ ደረሱ የተባሉ፣ ከትግራይ ሕዝብ የወጡ፣ ለትግራይ ሕዝብ የሚጠቅመውን መረዳትና ማወቅ ሲሳናቸው ከማየት የበለጠ የሚያሳዝን ነገር የለም፡፡ ማንም በትክክል የሚያገናዝብ፣ የሰፋ አይምሮ ያለው ተጋሩ፣ የትግራይ ብሄረተኝነት ፖለቲካ፣ ትግራይን እንደጎዳ መረዳት ይችል ነበር፡፡ እነ ዶር ቴዎድሮስ፣ አዎን በግለሰብ ደረጃ ትልቅ ቦታ ነው ያሉት፣ ግን አሁን የትግራይ ሕዝብስ ምን ደረጃ ላይ ነው ያለው ???? ብለን ብንጠይቅ መልሱ ለሁላችንም ግልጽ ነው፡፡ ሕወሃቶች የሚመጻደቁበት፣ ከኦነግ ጋር ሆነው ያመጡት፣ የብሄር ብሄረሰብ ፖለቲካ የሚሉት፣ የዘር ፖለቲካ፣ የዘር ሕገ መንግስት፣ የዘር አወቃቀር፣ ስሜታዊነትን ለጊዜው እንተወውና፣ ሜዳ ላይ ያለውን ሁኔታ ስንመለከት፣ በእጅጉ የትግራይን ሕዝብ የጎዳ ብቻ ሳይሆን ወደፊትም የበለጠ የሚጎዳ ነው፡፡ የትግራይ ሕዝብ ለጦርነት የተዘፈቀው፣ ከጎሮቤት አካባቢዎች ጋር ፣ ከጎንደር፣ ከወሎ፣ ከአፋር፣ ከኤርትራ ማህበረሰብ ጋር እሳትና ጭድ እንዲሆን የተደረገው፣ በዘር ፖለቲካው ነው፡፡ በህወሃቶች ጠባብና ዘረኛ እልህና እብሪት፡፡ ለዚህ ነው፣ ከማንም
Posted in Ethiopian News

ሕዝብ በሌለበት ስልጣን ምን ያደርጋል ? አቶ ታዬ ደንድዓ

የብልጽግና  ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባልና የሰላም ሚኒስቴር ፣ ሚኒስቴር ዴኤታ ናቸው፡፡ በቄሌም ወለጋ የተፈጸመው ጭፍጨፋ አስመልክቶ በፌስ ቡክ ገጻቸው በለተፉት ጦማር፣ “ተጠያቂነት ይስፈን!”፣ እርሷቸው አካል የሆኑበት መንግስት ስራዉን እንዳልሰራ ነው የገለጹት፡፡ “እኛ ደግሞ እንደመንግስት የዜጎችን ደህንነት ማስከበር ትንሹ ኃላፊነታችን ይመስለኛል” ያሉት አቶ ታዬ ፣ ተጠያቂነት ከሌለና ህዝብ የዜግችን ደህንነት ማስጠበቅ ካልቻለ የአገር ህልውና አደጋ ውስጥ እንደሚገባ ነው የገለጹት፡፡ አቶ ታዬ የጻፉትን እንደሚከትለው ቀርቧል፡ ንፁኃን ዜጎች በግፍ ሲገደሉ የሁሉም ጤነኛ ሰዉልብ ያዝናል:: ያዘነ ሀዘኑን መግለፁም አግባብ ይሆናል:: እኛ ደግሞ እንደመንግስት የዜጎችን ደህንነት ማስከበር ትንሹ ኃላፊነታችን ይመስለኛል:: ሰላምና ፀጥታ ከሰፈነ ሌላዉን ህዝቡ ራሱ ይሰረዋል:: ነገር ግን የዜጎች ሞት በየቀኑ ይሰማል:: ግምቢ ላይ የተፈፀመዉን አስነዋሪ ጭፍጨፋ ሳንረሳ ሌላ ጭፍጨፋ በቄለም ዛሬ ተደግሟል:: በነገራችን ላይ ጥፋቱ የማነዉ? ጠያቂና ተጠያቂ ሊኖር ግድ ይላል! ተጠያቂነት ባለመኖሩ አንድ ችግር መቶ ጊዜ ራሱን ይደጋግማል! በርግጥ ላለፉት ሦስት ዓመታት ኦሮሚያ ላይ የፀጥታ ችግር ገንግኗል:: ከመቼዉም ጊዜ በላይ ህዝባችን እጅግ የከፋ መከራ አይቷል:: እዉነታዉን መናገር ” ስልጣን ፈላጊ” ያስብላል:: እዉነትን ለመደፍጠጥ የስልጣን ልበወለድ ተፅፎ ወደ ላይ ይተረካል:: ለመሆኑ ህዝብ በሌለበት ምድር ስልጣን ለምን ይጠቅማል? አሁን ተጠያቂነትን በማስፈን እንቆቅልሹን መፍታት የህልውና ጉዳይ ሆኗል! ከዚህ ካለፈ አደጋዉ ከቁጥጥር ይወጣል!
Posted in Ethiopian News

ዶር አብይ አህመድ አገር መምራት አልቻለም፣ መሄድ አለበት #ግርማካሳ

የብልጽግና መንግስት ሕወሃት ይጠላ ከነበረው በባሰ ሁኔታ በሕዝብ እየተጠላ የመጣ ስለመሆኑ የሚከራከር ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡ እነ አብይ አህመድ ከኦሮሞ ድርጅት የመጡ ናቸው፡፡ ግን ምን ያህል የኦሮሞ ማህበረሰብ ይደገፋቸዋል ብለን ብንጠይቅ መልሱ ከባድ አይመስለኝም፡፡ በምርጫው ወቅት ብቻቸውን ተወዳድረው 100% አሸነፍን ያሉት እንደማይመረጡ ስለገባቸው ነበር፡፡በአሁኑ ወቅትም አብዛኛውን የኦሮሞ ወጣት እየገደሉ፣ እያሰሩ፣ እያፈኑ ጨፍልቀው ነው የያዙት፡፡ የተወሰኑትን በጥቅም በመያዝ፣ በነ አዲስ አበባ ስራዎችን በመስጠት፣ በኦሮሞ ልዩ ኅይል ውስጥ በማስገባት ወዘተ የነርሱ መጠቀሚያ እያደረጓቸው ነው፡፡ ቀላል የማይባሉ ሌሎች ደግሞ ኦነግን እየተቀላቀሉ ነው፡፡ የኦሮሞ ክልል አራቱ የወለጋ ዞኖች (ምስራቅ፣ ምእራብ፣ ቄሌምና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ)፣ ከሸዋ አራት ዞኖች (ምስራቅ፣ ሰሜንና ምእራብ ሸዋ)፣ የጉጂና የጉጂ ምእራብ ዞኖች፣ የቦረና ዞን ፣ ሲደመሩ ከሃያ አስር የሚደርሱ የኦሮሞ ክልል ዞኖች ሰላምና መረጋጋት የሌለባቸው ናቸው፡፡በቅርቡ በምእራብ ወለጋ፣ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ የተፈጸመው፣ ከአንድ ሺህ አምስት መቶ በላይ የሞቱበትን አሰቃቂ የአማራዎች ጭፍጨፋን እንደ ምሳሌ መጥቀስ ብቻ በቂ ነው፡፡ የአብይ አህመድ ኦህዴድ ብልጽግና በኦሮሞ ክልል በሕዝብ መጠላት ብቻ አይደለም፣ በክልሉ ሰላም፣ መረጋጋትና አስፍኖ የዜጎችን ደህንነት መጠበቅ አልቻለም፡፡ አንድ በሉ፡፡ ትግራይ ሙሉ ለሙሉ ከብልጽግና ቁጥጥር ውጭ ናት፡፡ ከትግራይ ማህበረሰብ ጋር ብልጽግናዎች ላይታረቁ ተፋተዋል፡፡ መብራት፣ ኔትዎርክ ወዘተ እንዲዘጋ አድርገው ሕወሃት በሚፈጽመው ግፍ ላይ፣ እነርሱም ተጨምረው የትግራይን ሕዝብ መከራ አባዝተውታል፡፡ ወይ ሕወሃትን አሸንፈውና ደምስሰው ህዝቡ እንዲረጋጋ አላደረጉም፤ እንደ እንድ አገር መንግስት፤ ወይም ተደራድርው ችግሮችን አልፈቱም፡፡ ነገሮች
Posted in Ethiopian News

አልተመለሰም የሚሉት የኦሮሞ ጥያቄዎች ? #ግርማካሳ

ኦሮሞን እንወክላለን የሚሉ የኦሮሞ ድርጅት መሪዎች፣ እነ ዶር መራራ ጉዲና፣ ጃዋር መሐመድ የኦሮሞ ጥያቄ አልተመለሰም ይላሉ፡፡ የኦሮሞ ጥያቄ አልተመለሰም ለማለት ሁለት ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘት አለባቸው፡፡ አንደኛው ፣ “ማን ነው ኦሮሞ ?” የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የኦሮሞ ጥያቄዎች ምንድ ናቸው ? የሚለው ነው፡፡ “ኦሮሞ ማለት ማን ነው ?” የሚለው በራሱ አከራካሪና አወዛጋቢ ነው፡፡ “ኦሮሞ ነኝ” የሚል ነው ኦሮሞ ? ኦሮምኛ የሚናገር ነው ኦሮሞ ? ኦሮሞ ክልል የሚኖር ነው ኦሮሞ ? ወይንስ የኦሮሞ መሪ ነን የሚሉ የኦሮሞነት ሰርተፊኬት የሚሰጡት፣ ኦሮሞ ነው የሚባለው???? ይህ ራሱን የቻለ ሰፊ ርእስ ስለሆነ በሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ፡፡ ቀጥሎ የሚነሳ ጥያቄ ፣ “የኦሮሞ ጥያቄዎች ምንድን ናቸው ?” የሚለው ነው፡፡በኔ እምነት የኦሮሞ ጥያቄዎች የምላቸው፣ ከሌላላው ማህበረሰብ ጥይቄዎች ጋር የተገናነኙ የኦሮሞ ሳይሁን በአጠቃልይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄዎች የሆኑ ናቸው ባይ ነኝ፡፡እነርሱም፣ 1ኛ በሰላም የመኖር፣ 2ኛ የፍትህ፣ 3ኛ የእኩልነት፣ 4ኛ ራስን በራስ የማስተዳደርና የዲሞክራሲ ፣ 5ኛ የልማት እና ሃብትና የሪሶርስ እኩል የመጠቀም፣ 5ኛ በራስ ቋንቋ የመጠቀም፣ ባህልና ቅርስ የማሳደኛ የማስፋፋት ጥያቄዎች ናቸው፡፡ እነዚህ 5 ጥያቄዎች የኦሮሞ ጥያቄዎች ብቻ ተደርገው መወሰድ የለባቸው፡፡ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥያቄዎች ናቸው፡፡ በዚህ ጉዳይ በቅርቡ የኦፌኮ መሪ ዶር መራራ ጉዲና የሰጡት አስተያየት አለ፡፡ ከሁለት አመት በፊትም መዓዛ መሐመድ ጃዋርን ቃለ መጠይቅ አድርጋ የነበረ ጊዜ እርሱም፣ በቅርቡ ዶር መራራ የተናገሩትን ነበር፣ ያኔም የተናገረው፡፡ እነዚህ ሁለት መሪዎች የተናገሩትን በመውሰድ የኦሮሞ ጥይቄዎች ያሏቸውን
Posted in Ethiopian News

እየተተራመሰ ያለው የአማራ ክልል መንግስት #ግርማካሳ

ኦህዴዶች አራት ኪሎ የገቡት በብአዴኖች ትከሻ ላይ ነበር፡፡ የፈለጉትን ካገኙ በሗላ ግን ብአዴኖችን መቀለጃ ነው ያደረጏቸው፡፡ መሳያቂያ፡፡ አንድ ጆክ ነበር ድሮ፡፡ “አበላል እንደ ደርግ አባል፣ አለባበስ እንደ ፍቅረ ስላሴ ወግደረስ፣ የአገዳደል ስልቱ እንደ ሊቀመንበር መንግስቱ” የሚል፡፡ አሁን ደግሞ ክሽፈትና ጭንገፋ እንደ አማራ ብልፅግና የሚል ጨምሬበታለሁ፡፡ የአብይ አህመድ ኦህዴድ መንግስት አራት ኪሎን ከተቆጣጠረ አራት አመት ብቻ ቢሆነውም በአማራ ክልል አምስት ጊዜ የአስተዳዳሪ ለውጥ እንዲኖር አስደርጓል፡፡ ለውጥ የተባለው አንዳንዶች ተጭንግፏል/ተቀልብሷል የሚሉት፣ ሌሎች ደጎ መጀመሪያውን የማስመሰል እንጂ ለውጥ አልነበሩ የሚሉት፣ ለውጥ የተባለው ሲመጣ፣ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ነበር የአማራ ክልል ርእስ መስተዳደር፡፡ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለሕዝብ ግልጽ ባልሆነ ምክንያት በአብይ አህመድና ደምቀ መኮንን ሴራ እንዲለቅ ተደረገ፡፡  ምክትሉ አቶ ላቀ አያሌው በምክትል ርእስ መስተዳድርነት ማእረግ ርእሰ መስተዳደር ሆኖ መስራት ጀመረ:: አንድ በሉ:: አቶ ላቀው አያሌው ለወራት ካስተዳደረ በሗላ፣ እርሱ በሃላፊነቱ ሊቀጥል ሲችል፣ ከጀነራል አሳምነው ጋር ባለው ቅርርብና በክልሉም የአማራ ልዩ ኃይል እንዲጠናከር በማድረጉ እንዲቀጥል አልተፈለገም፡፡ በአዴፓ የባህር ዳሩ ጉባዬ ዶር አምባቸው ትልቁን ድምጽ ያገኘ የነበረ ቢሆንም፣ በደመቀ መኮንን ምትክ የአዴፓ ሊቀመንበርና ምክርትል ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ሲገባው፣ በአሻጥር ደመቀ መኮንን እንዲቀጥል ተደረገ፡፡ ዶር አምባቸውን  ወደ ጎን መግፋት ስላልቻሉ፣  የአማራ ክልል  ር እስ መስተዳደር እንዲሆን ተደርገ፡፡ አቶ ላቀው በዶር አምባቸው ተተካ:: ሁለት በሉ፡፡ ዶር አምባቸው መኮንን ፣ ከአቶ ዪሐንስ ቧያሌው ጋር በመሆን፣ በሁሉም የአማራ ክልል አካባቢዎች በመዞር
Posted in Ethiopian News

ሀገር በሕግና በሥርዓት እንጂ በአፈና አትመራም- እናት/መኢአድ/ኢሕአፓ

ሀገር በሕግና በሥርዓት እንጂ በአፈና አትመራም! የአገራችን ችግር ሁሉ ምንጭ የጎሳ ፖለቲካው ነው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከእናት ፓርቲ፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ሀገራችን ኢትዮጵያን ከገባችበት የችግር አረንቋ ለማውጣት የሕግ የበላይነትን እንዲሁም መንግስት ተቀዳሚ ሚናው የሆነውን የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ኹኔታ እንዲያረጋግጥ ከላይ ስማችን የተጠቀሰው ፓርቲዎችን ጨምሮ ብዙ አካላት ወትውተናል፡፡ ሀገራችን ካለችበት ቀጠናዊና ውስጣዊ የፖለቲካ ምስቅልቅል አንጻር በቦታውና በጊዜው ተገቢ የእርምት እርምጃዎች ካልተወሰዱ በችግር ላይ ችግር እየተደራረበና እየተወሳሰበ ይሄድና ማጣፊያው ያጥረናል የሚሉ ሥጋቶች በኹሉም አካላት ይስተጋባ ነበር፡፡ የችግሮቻችን ኹሉ ምንጭ የሆነው የጎሳና ማንነት አደረጃጀት ይስተካከል የሚሉና መሰል የሕግ የበላይነት ይከበር ጩኸቶች ሰሚ አጥተው ሀገር የጥቂት ቡድኖች ሀብት ወደ መምሰል እየተጓዘች ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በኹሉም የሀገራችን ክፍል ሥርዓት አልበኝነት የሕጋዊነት ያህል ነገሰ፡፡ ሕዝብ ተስፋ ያደረገው የለውጥ ጅምርም በእንጭጩ ተቀጭቶ ከየአካባቢው መፈናቀል፣ ጅምላ ፍጅትና ጦርነት ትቶልን ላይመለስ በሚመስል አኳኋን ርቆ እየሄደ ነው፡፡ እንደ አብዛኛው ሰው እኛም የለውጥ ጅምር ላይ የሚያጋጥም መንገራገጭ ነው ብለን በታጋሽነት ተመለከትን፡፡ ምርጫውና ውጤቱ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅምና ፍላጎት አንጻር እንደማይሆን እያወቅን ከሚያነክስ መንግስት በኹለት እግሩ የቆመ ይሻላል በሚል በሚል በደሉን አፍነን የገባንበት ቢሆንም ተስፋ እንደተጣለበት ሳይሆን ገዢው ፓርቲ መጨረሻውን ለበጎ ሳያውለው እየቀረ ነው፡፡ በምጣኔ ሀብት በኩልም የገጠመን ምስቅልቅል ምን አልባትም በፖለቲካውና በጸጥታው ከገጠመን ምስቅልቅል የባሰ እንጂ የተሻለ አይደለም፡፡ ለምሳሌ በያዝነው ዓመት ሚያዝያ ወር እንኳን ይፋ በሆኑ መረጃዎች
Posted in Ethiopian News

ሕግ በማስከበር ሰበብ ህዝብን ማሸበር ይቁም – መኢአድ

ሕግ በማስከበር ሰበብ ህዝብን ማሸበር በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል!!! ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሠጠ መግለጫ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከአምባገነኖች አገዛዝ ተላቅቃ ወደ ዴሞክራሲያዊ የአስተዳደር ሥርዓት ለመሸጋገር በርካታ ሙከራዎችን አድርጋለች፡፡ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን የማይተካ የሕይወት መስዋዕትነት የጠየቁት እነዚህ ሙከራዎች ህዝብ የሚፈልገውን ለውጥ ያመጡ ናቸው ባይባልም ብዙ የተማርንባቸው መሆኑ ግን የአደባባይ እውነት ነው፡፡ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብዙ መስዋዕትነት ከፍሎ ያስወገደው የሕወሓት አገዛዝ ሥርዓት በብልፅግና ተሸፍኖ ለዳግማዊ ጥፋት ተመልሶ እንዲመጣ ለአፍታም ቢሆን ልንፈቅድለት አይገባም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ወያኔን በእልህ የታገለውና አሁንም እየታገለ ያለው በጉልበት የተጣለበትን አፈና በመፀየፉ እንደሆነ ሊዘነጋ አይገባም፡፡ ከህወሓት ውድቀት ያልተማረው የሕወሓት የመንፈስ ወራሽ የሆነው የብልፅግና ሥርዓት በአሁኑ ወቅት በአማራ ህዝብ እና የአማራ ተቆርቋሪ በሆኑ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ላይ እየፈፀመ ያለውን አፈና ድርጅታችን መኢአድ በፅኑ ያወግዛል፡፡ የአማራ ህዝብ ከምድረ ገፅ እንዲጠፋ በህወሓት ተፈርዶበት ጦርነት በተከፈተበት ወቅት ሕዝባችንን ለሚገድሉ፣ ሀገራችንን ለሚያፈርሱ ጠላቶች ዕድል አንሰጥም ብለው፣ ከገዳዮች ፊት ቆመው የሕዝብን እልቂትና የሀገርን የመፍረስ አደጋ የተከላከሉ በዚያ ክፉ ጊዜ ለህዝብ ብለው ደረታቸውን ለጥይት አረር በመስጠት ሲታገሉ የነበሩ የጦር መሪዎችና ወንድሞቻችንን እንዲያፍኑ ልንፈቅድላቸው አይገባም፡፡ ችግሮች እንኳን ቢያጋጥሙ በሰለጠነ አካሄድ ተነጋግሮ ለችግሮቹ መፍትሔ መፈለግ እንጂ በዛ የጭንቅ ወቅት ያለምንም ማመንታት ኃላፊነትን ወስደው ሀገርን ለታደጉ የጦር መሪዎች ክብር መስጠት ሀገራዊ ግዴታ ሲሆን ማዋከብ ግን የነውር ጥግ ነው፡፡ ድርጅታችን የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በሕዝባችን ላይ የሚፈፀመውን አፈና እና ወከባ
Posted in Ethiopian News

በፋኖ ላይ የተጀመረው አፈና የኦነግn ኢትዮጵያን የማፍረስ አጀንዳ ለማሳካት ነው – ባልደራስ

በወቅታዊ የአገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ከባልደራስ የተሰጠ መግለጫ ተረኛው ኦህዴድ መራሹ መንግሥት፣ በሃሰት ክስና ውንጀላ በተደጋጋሚ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ አባላትንና መሪዎችን በግፍ ማሰሩን እንደቀጠለ ነው። በአሁኑ ወቅት ከ12 የማያንሱ የባልደራስ አባላትና የአዲስ አበባ ወጣቶች ያለምንም ወንጀል በእስር ላይ ይገኛሉ። መንግሥት ሌሎች የባልደራስ አባላትንም ለማሰር በማሳደድ ላይ ይገኛል። ባልደራስ አገራዊ ፓርቲ ለመሆን በተለያዩ ክልሎች በጀመረው የፊርማ ማሰባሰብ ዘመቻም ላይ እንቅፋት የመፍጠር ሂደቱ እንደቀጠለ ነው። በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር በአርባምንጭ፣ በድሬደዋ፣ በሐረር የፊርማ ማሰባሰቡን ሥራ እየሰሩ በሚገኙ አባላት ላይ ወከባ እንግልት እና እስራት እየተካሄደባቸው ነው፡፡ በተመሳሳይ እስሩና አፈናው በነፃ ሃሳባቸውን በሚገልፁ ወታደራዊ አዛዦች፣ ጋዜጠኞችና የታሪክ እና የፖለቲካ ምሁራን ላይ ተፋፍሞ ቀጥሏል። ታዋቂው ጀነራል ተፈራ ማሞ፣የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ም/ል ኮሚሽነር ቢሰጥ ጌታቸዉ፣ታዋቂው የታሪክ እና የፖለቲካ ጋዜጠኛ ታዲዮስ ታንቱ፣ ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ መምህርት እና የፖለቲካ ተንታኝ መስከረም አበራ የዚሁ ዘመቻ ሰለባ ከሆኑ ቀናቶች አልፈዋል። ከዚህ ቀደምም ጋዜጠኛ ታምራት ነገራ እና ጎበዜ ሲሳይ ላይም ተመሳሳይ አፈናና እስር ደርሶባቸው እንደ ነበርም ይታወሳል። ይህ የመንግሥት የማናለብኝነት አካሄድ በሰላማዊ ትግል የሚያምኑ የፖለቲካ ቡድኖችንና ሃሳባቸውን በነፃነት የሚገልጹ ምሁራንን፣ ጋዜጠኞችን እንዲኹም መላው የኢትዮጵያ ህዝብን ተስፋ በማስቆረጥ፣ ህዝቡን ወደ ህዝባዊ አመጽ እንዲሸጋገር እየገፋው ይገኛል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የኦህዴድ መራሹ የብልፅግና መንግሥት በአሁኑ ሰዓት በአማራ ክልል በፋኖ ላይ የከፈተው የመግደለና የማሳደድ ዘመቻ ቀይ መስመር ያለፈ አደገኛ አካሄድ መሆኑንና መጨረሻው እንደማያምር ሊታወቅ ይገባል። ፋኖና
Posted in Ethiopian News

እውነት ከመናገር ውጭ ሌላ ወንጀል የለውም – ዶር ሲሳይ መንግስቴ የብልጽኝ የአ/አ ምክር ቤት አባል

እውነት ከመናገር ውጭ ሌላ ወንጀል የለውም ፟ ዶር ሲሳይ መንግስቴ ዶር ሲሳይ መንግስቴ የብልጽግ ና ፓርቲን ወክለው የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባልና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ምህሩ ናቸው፡፡ እርሳቸው የወከሉት የብልጽግ ና መንግስት፣ አንጋፋውን ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይን ማሰሩን ተከትሎ የሚከተለውም ብለዋል __________________________________ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ታሰረ የሚለው መረጃ እውነት ከሆነ መንግስት ለሁለተኛ ጊዜ ተሸነፈ ማለት ነው። አንደኛው ለምን እውነትን ዘገብህ ብሎ ከኢሳት እንዲባርረ ሲያደርገው ሲሆን ሁለተኛው አሁን እየተባለ እንዳለው በእርግጥም ጎበዜን አፍነው የወሰዱት የመንግስት ሀይሎች ከሆኑ ማለት ነው። ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ የራያ ልጅ ነው፣ በዚህም ምክንያት በጦርነቱ ወቅት ከራያና አካባቢው ወቅታዊውን ሁኔታ የሚገልጽ መረጃ ይደርሰው ነበር። ይህን እውነት ለማረጋገጥ ወደ ስፍራው አቀና፣ በጆሮው የሰማውን በአይኑ አይቶ አረጋገጠና እውነታውን ያውም በልኩ አድርጎ ሁሉም ሰው እንዲያውቀው በራሱ የፌስ ቡክ ገጹ ላይ ለጠፈው። ይኸኔ ከብልጽግና ጉያ ተወሽቆ የኢትዮጵያ ሕዝብ አይንና ጆሮ ነኝ ሲል የነበረው የኢሳት ሀላፊዎች ተከፉ። እናም በግል የፌስ ቡክ ገጽህም ቢሆን መንግስትን እንዲህ በድፍረት የሚያጋልጥ ዘገባ የምታወጣ ከሆነማ ከእኛ ጋር መቀጠል አትችልም ብለው አባረሩት። በሙያው የሚተማመነው ጋዜጠኛ ጎበዜም ምንም ሳይደናገጥ ስራውን አጠናክሮ ቀጠለ። ከእኛ ቴሌቪዥን ጋር በመሆንም በዛ ቃውጢ ወቅት በአፋር ክልል ጭፍራንና አካባቢውን አቆራርጦ ዞብል በመግባት ጉራ ወርቄ ድረስ ሄዶ የራያ-ቆቦ ወረዳ ሕዝብ ለትህነግ ታጣቂዎች የጎን ውጋት እንደሆነባቸው በግልጽ አሳየን። ይህም ሆኖ የመንግስት ድጋፍ ባለመኖሩ ሚሊሻውና ፋኖው ብቻ ሳይሆን የአካባቢው
Posted in Ethiopian News

ፖሊስ የባልደራስን ቢንያም ታደሰን ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር ከሰሰ!

# ፖሊስ የባልደራስን ቢንያም ታደሰን ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር ከሰሰ! # ፍርድ ቤቱ ለግንቦት ዘጠኝ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል! / የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አባል የሆነው ወጣት ቢንያም ታደሰ ካለፈው ቅዳሜ ሚያዚያ 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በእስር ላይ ይገኛል። ወጣቱ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዚያ 25 ቀን 2014 ዓ.ም. የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ቀርቧል። መርማሪ ፖሊስ “የሰውና የሰነድ ማስረጃ ለማሰባሰብ” በሚል ሰበብ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ የጠየቀ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ሙሉ በሙሉ ተቀብሎት ለፊታችን ግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ.ም. ለረፋድ 3፡30 ቀጥሮል። የቢንያም ታደሰ ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 13 መሰረት የዋስትና መብቱ ተጠብቆለት ቢንያም ከእስር እንዲፈታ ቢጠይቁም፣ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል። ፖሊስ በአቀረበው ክስ፣ በ22/08/2014 በአዲስ አበባ ፒያሳ ሲንማ አምፒር አካባቢ ቢንያም ‘ኦርቶዶክስ ተነስ’ እያለ በጎንደር የተፈጠረውን ግጭት መሰረት አድርጎ ሕዝብ ሲቀሰቅስ እንደነበር ቢገልፅም፣ ተፈጠረ ያለውን ሁከትና ብጥብጥ ማስረዳት አልቻለም። የደረሰ ጉዳት እንዳለ በጠበቃው ሲጠየቅም፣ ቢንያም በእስር ቤት ሆኖ ትናንት በኢድ አልፈጥር በዓል ላይ የደረሰውን የንብረት ጉዳት ጠቅሷል። ጠበቃ ሔኖክ በበኩላቸው፣ በዚህ ዕለት ቢንያም እስር ቤት ውስጥ በመሆኑ ማስረጃ ሊሰበሰብበት እንደማይገባ ገልፀው ተከራክረዋል። ቢንያም ታደሰ በበኩሉ፣ በዕለቱ በአዲስ አበባ እንኳንስ ብጥብጥ ሊፈጥር ቀርቶ፣ ወደ ናዝሬት ከተማ ለመሄድ መኪና ውስጥ ሲገባ ፖሊስ እንደያዘው አስረድቷል። በቅርቡ ከእስር ቤት በመውጣቱ ገና ውጭውን በመለማመድ ላይ እንደነበር
Posted in Ethiopian News

የባልደራሱ ቢንያም ታደሰ በድጋሜ ታሰረ

የባልደራሱ ቢንያም ታደሰ በድጋሜ ታሰረ / የአድዋና የካራማራ የድል በዓላትን ሰበብ በማድረግ ከአንድ ወር በላይ በግፍ በአባ ሳሙኤል ወህኒ ቤት ታስሮ የቆየው የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) አባሉ ቢንያም ታደሰ በድጋሜ በፖሊስ መታሰሩን ባልደራስ  በፊስ ቡክ ገጻኡ አሳውቋል፡፡  ወጣት ቢንያም ታደሰ  ከሰሞኑ በጎንደር እና በስልጤ አካባቢዎች የእምነት ተቋማት ላይ እየደረሰ ያለውን ሃይማኖታዊ ጥቃት ሲያወግዝና አንድነትን ሲሰብክ እንደነበረ ያሳወቀው ባልደራስ፣ በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባ፣  በቀድሞው ማዕከላዊ ይባል በነበረውም 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣  በፖሊስ ኮሚሽን መታሰሩ ገልጿልLL
Posted in Ethiopian News

የአራት አመት የኦህዴድ የጨለማ አገዛዝና የጥፋት የቁልቁለት ጉዞ #ግርማካሳ

የአብይ አህመድ የኦህዴድ/ብልጽግና መንግስት ላለፉት 4 አመት አገሪቷን ሲመራ ለአገር ያመጣው ነገር ቢኖር፡ – ብልጽግናን ሳይሆን የድህነትና የኑሮ ውድነት ጥግን እና ረሃብን፣ – መደመርንና ሳይሆን መከፋፈልን ፣ ልዩነትንና መቀነስን፣ – የዜጎችን ደህንነት፣ ወጥቶ በሰላም መግባት ሳይሆን የዜጎችን ጭፍጨፋ፣ እልቂት፣ መፈናቀልን፣ – ሰላምንና መረጋጋት ሳይሆን ጦርነትንና ሽብርን፣ – እኩልነትን ሳይሆን ተረኝነት፣ ልዩ ጥቅም በሚል የአንድን ጎሳ የበላይነት ማስፈንን እና በሕወሃት ጊዜ ከነበረው የባሰ ዘረኝነትን፣ – ፍትህን ሳይሆን የዱርዬ ፍትህ አልባ ፣ ህገ አልባ አሰራርን፣ – መልካም አስተዳደርን ሳይሆን የለየለት ሌብነትንና መንግስትዊ ዝርፊያን – የሰለጠነ ዘመናዊ ፖለቲካን ሳይሆን የዘርና የኃይማኖት አክራሪነትን – አገርን ማስከበር ሳይሆን አገርን በአለም አቀፍ መድረክ ማዋረድን – ልማትን ሳይሆን ውድመትን – አንድነትን ፣ ኢትዮጵያዊነትን ሳይሆን ጎጠኝነትን፣ ጸረ ኢትዮጵያዊነትን – ዲሞክራሲን ሳይሆን የለየለት አፈናንና አምባገነናዊነትን ነው፡፡ ትግራይ ሄዱ፣ ኦሮሞ ክልል እነ ወለጋ ሂዱ፣ አማራ ክልል ሂዱ፣ አፋር ክልል ሂዱ ፣ ደቡብ ክልል ሄዱ ….ከተለያይ ጎሳዎች ወይንም ኃይማኖቶች ይሁኑ፣ “አሁን ያላችሁበት ሁኔታ ነው ወይስ ከአራት አመት በፊት የነበራችሁበት ሁኔታ ነው የሚሻላችሁ ?” የሚል ጥያቄ ብታቀርቡላቸው፣ ከ 4 አመት በፊት የነበረው በአስር እጥፍ እጥፍ ይሻል ነበር የሚል መልስ ነው የሚሰጧችሁ፡፡ አማራው፣ ትግሬው፣ ኦሮሞው፣ ወላይታው፣ ጉራጌው….፣ ዉህድ ኢትዮጵያዊው ፣ ሙስሊሙ፣ ክርስቲያኑ ሁሉም እያማረረ፣ እያለቀሰ ነው፡፡ ምን አልባት ከጥቂት ዘራፊና ሌባ የኦህዴድ/ብልጽግና ሰዎች፣ ለኦህዴድ ታዛዥ የሆኑ የሌሎች ክልል የብልጽግና ቅርንጫፍ አብሮ ሰራቂና ዘራፊ
Posted in Ethiopian News

በጎንደር ለሆነው ጥልቅ ሃዘኑን የገለጸው ባልደራስ ፣ ጥፋተኞች ለህግ እንዲቀርቡ ጠየቀ

“በጎንደር በደረሰው ጉዳት ከልብ አዝነናል፣ አጥፊዎች በአሰቸኳይ ወደ ህግ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን!” ሲል ባልደራስ በጎንደር የተከሰተውን አሳዛኝ ክስተት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡ የባልደራስ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡ በጎንደር በደረሰው ጉዳት ከልብ አዝነናል፣ አጥፊዎች በአሰቸኳይ ወደ ህግ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን! / በአማራ ክልል፣ ጎንደር ከተማ ሚያዝያ 17/2014 ዓ/ም ከሰዓት ከቀብር ስነ ስርዓት አፈፃፀም ጋር በተያየዘ የተነሳ ግጭት በርካታ አማኞች በመሞታቸው፣ መስጂዶች በመቃጠላቸው፣ ግለሶቦች እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በመድረሱ ባልደራስ ፓርቲ በእጅጉ አዝኗል። የችግሩ መነሻ ምንም ይሁን ምን፣ የተፈፀመው ነገር በፍጱም ሊወገዝ የሚገባ ነው፤ በተለይም የእምነት ተቋማት እና አማኞች ላይ የደረሰው ጥቃት አሳዛኝ ነው። በኦሮሚያ ክልል ሙስሊምና ክርስቲያን አማሮች ያለ ምንም ልዩነት በጋራ በሚጨፈጨፉበት፣ በሚፈናቀሉበትና የጋራ መከራ በሚቀበሉበት በዚህ ግዜ፣ እንዲሁም ሚሊዮኖች የእለት ደራሽ ምግብ በአጡበት ክልል እንዲህ ዓይነት ችግር መፈጠሩ በእጅጉ አሳዛኝም አሳፋሪም ነው። ግጭቱ እንዳይሰፋና የፀረ-ኢትዮጰያ ኃይሎች መጠቀሚያ እንዳይሆን፣ የሚመለከታቸው የክልሉ የፍትህ አካላት፣ የእምነት አባቶች እና ተፅእኖ ፈጣሪዎች በሙሉ በአስቸኳይ የተቀናጀ እንቅስቃሴ አድርገው የከተማውን ፀጥታ ለማስጠበቅ መረባረብ አለባቸው። በከተማዋ ነዋሪ በኩል፣ በግጭቱና በደረሰው ጉዳት እጃቸው ያለበትን አካላት ያለምንም ይሉኝታ ለሕግ አሳልፎ በመስጠት ተጠያቂነት እንዲኖር ማድረግ ይገባቸዋል። በቀጣይነት ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር መመካከር እንደሚያስፈልግ ባልደራስ ያምናል። በስተመጨረሻም፣ በዚህ ችግር የሞቱትን ፈጣሪ ነፍሳቸውን እንዲቀበል፣ ወዳጆቻቸውን ላጡ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን። እናት ዓለም ኢትዮጰያ ክፉሽን አያሳየን!!! ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ሚያዚያ 19 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ / #ኢትዮጵያ
Posted in Ethiopian News

የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽና የቤቶች ሕገ ወጥ ፈረሳ ውዝግብ

# “እናንተ ለብዙ ዓመታት በልታችኋል፣ አሁን ተራው የእኛ ነው” የመንግሥት ባለስልጣን የተናገሩት! # ቤቶች ኮርፖሬሽን አንበሳ ፋርማሲና ኒኦን አዲስ አይፈርሱም አለ፣ ውል ያቋረጠው ግን ከህግ ውጭ ነው! / የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አንበሳ ፋርማሲ እና ኒኦን አዲስ እንዲፈርሱ አልተወሰነም ሲል አስተባበለ፡፡ ኮርፖሬሽኑ ባወጣው መግለጫ፣ “አንበሳ ፋርማሲ እና ኒኦን አዲስ የተባሉ ድርጅቶች በኪራይ ሲገለገሉበት የነበሩት እና የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ንብረት የሆኑት ቤቶች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶቹ የቅርስነት ይዞታቸው ሳይቀየር ባሉበት ምንም ዓይነት የቅርስነት ይዞታቸው ሳይቀየሩ አስፈላጊውን እድሳት እና እንክብካቤ እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል…በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ውሳኔ ቤቶቹ የቅርስነት ይዞታቸው ሳይቀየር…በአካባቢው ከሚገነባው አዲስ ግንባታ ጋር ለአልሚ አባላት እንዲተላለፉ ከማድረግ ውጭ በቅርሶቹ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አይደርስባቸውም ” ብሏል፡፡ ሆኖም፣ ቤቶቹ የማይፈርሱ ከሆነ ያለምንም ምክንያት ከአንዱ ተከራይ ወደ ሌላ ተከራይ በምን የህግ አግባብ እንዲተላለፍ እንደተወሰነ ኮርፖሬሽኑ ምንም ያለው ነገር የለም፡፡ ሆኖም፣ ከዚህ በፊት አንድ የመንግሥት ባለሥልጣን አሁን ላሉት ተከራዮች በንዴት ሲናገር፣ “እናንተ ለብዙ ዓመታት በልታችኋል፤ አሁን ደግሞ የእኛ ተራ ነው” በማለት እንደተናገራቸው ይታወሳል፡፡ አሁን ያሉት ተከራዮች ያለ ምንም ምክንያት ውጡ ተብለው ቤቶቹ ለናዝሬት ከተማ ባለሀብቱ ጀርመን አመንቴ መዘዋወራቸው የባለሥልጣኑ አባባል ትኩረት እንዲሰጠው የሚያደርግ ነው። / #ኢትዮጵያ / #ኢትዮጵያ (ምንጭ ባልደራስ)
Posted in Ethiopian News

ታዋቂው የአንበሳ ፋርማሲ የኪራይ ውል ተቋረጠ!

# ታዋቂው የአንበሳ ፋርማሲ የኪራይ ውል ተቋረጠ! # ፋርማሲው ያለበትን ታሪካዊ ህንፃ ለማፍረስ መስተዳድሩ ይፈልጋል! / የታዋቂው የአንበሳ ፋርማሲ የኪራይ ውል ተቋረጠ፡፡ ፋርማሲው ያለበት ህንፃ በቅርስነት የተመዘገበ ሲሆን፣ ላለፉት ሁለት ዓመታት የአዲስ አበባ መስተዳድር ህንፃውን ለማፍረስ፣ ፋርማሲው ደግሞ እንዳይፈርስ ታግለዋል፡፡ አሁን ደግሞ የፌደራል ቤቶች አስተዳደር ለፋርማሲው በ05/08/2014 ዓ.ም. በፃፈው ደብዳቤ፣ “የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ቅርንጫፍ 4 ጽ/ቤት የሚያስተዳድረው በአራዳ ክፍለ ከተማ በቀድሞ ወረዳ 2 ቀበሌ 15 የቤት ቁጥር 158 የሆነው የንግድ ቤት ተከራይ መሆናችሁ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ከቤቶች እና ይዞታዎች ማስከበር እና ማከራያ ዳይሬቶሬክት መጋቢት 30/07/2014 ዓ.ም በቁጥር 50/1/1/3377 በፃፈልን ደብዳቤ በተወሰነው ውሳኔ መሠረት ከሚያዚያ 1 /2014 ዓ.ም. ጀምሮ በመካከላችን የነበረውን የቤት ኪራይ ውል ያቋረጥን መሆኑን እያሳወቅን፣ የተገለገላችሁበትን የቤት ኪራይ፣ የመብራት እና የውሃ ፍጆታ ሂሳብ አጠናቃችሁ በመክፈል ቤቱን እንድታስረክቡን እናሳስባለን” ብሏል፡፡ የውሉ መቋረጥ ህንፃው እንዳይፈርስ የሚከራከር አካል እንዳይኖር የሚያደርግ በመሆኑ፣ ህንፃውን ለማፍረስ እየተሰራ እንደሆነ አመላክቷል፡፡ / #ኢትዮጵያ (Source  Balderas )
Posted in Ethiopian News

በሕገ መንግስቱ መሰረት ሸገር/ናዝሬት/ደራ/ፈንታሌ …አማራ ክልል መሆን ነበረባቸው #ግርማካሳ

በ1986 ዓ/ም አሁን ያለው፣ የሕወሃትና የኦነግ የአሸናፊዎች ሕገ መንግስት ከመጽደቁ በፊት የሕዝብ ቆጠራ ተደርጎ ነበር፡፡ የሕዝቡ ቆጠራውን ያደረገው የስታቲስቲካል ኤጀንሲ ሲሆን፣ ተቋሙ እንደሌሎች ተቋሞች በሕወሃትና በኦሮሞ ፖለቲከኞች ተጽኖ ሰር ወድቆ የነበረ መሆኑን የሚታወቅ ነው፡፡ ሕወሃቶችና የኦሮሞ ድርጅቶች፣ ሆን ብለው የዘር ፖለቲካቸውን ሊቃወሙ የሚችሉትን ማሀረሰባት ቁጥራቸው እንዲያንስ ማድረጋቸው ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ በሕወሃት ጊዜ የተደረጉ የሕዝብ ቆጠራዎች ሙሉ ለሙሉ ትክክል ነበሩ ብሎ መናገር አይቻልም፡፡ እንደዚያም ሆኖ ግን ያለው ብቸኛው ኦፌሴላዊ ሪፖርት እርሱ እስከሆነ ድረስ፣ እስከነ ችግሩ ልንጠቀምበት የምንችለው ሪፖርት እርሱን ነው፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች ለቀረበው ጽሁፍ የ1986 የሕዝብ ቆጠራ ሪፖርት እንደ ምንጭ ቀርቧል፡፡ የሕወሃት/ኦነግ ሕገ መንግስት በአንቀጽ አንቀጽ 46 ስለፌዴራል ክልሎች አመሰራረት ያስቀምጥና፣ በአንቀጽ 47፣ በአንቀጽ 46 መሰረት የተመሰረቱ ክልሎችን ያላቸውን ይዘረዝራል፡፡ አንቀጽ 46፣ የፌዴራሉ መንግሥት በክልሎች የተዋቀረ እንደሚሆንና ክልሎች የሚዋቀሩት በሕዝብ አሰፋፈር፣ ቋንቋ፣ ማንነት እና ፈቃድ ላይ በመመሥረት እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡ እዚህ ጋር ልብ እንበል ሕገ መንግስቱ አራት መስፈርቶችን ነው ያስቀመጠው፣ የሕዝብ አሰፋፈር፣ ማንነት፣ ቋንቋና የሕዝብ ፍቃድ ናቸው፡፡ የኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ሰሜን ሸዋ ዞኖች እንዲሁም አዲስ አበባን ለናሙና ያህል ስንመለከት በአንቀጽ 47 ላይ የተመሰረቱት ክልሎች አንቀጾ 46 ላይ ያለውን መስፈርት ራሱ ያላከበሩ መሆናቸውን ነው እናያለን፡፡ ቋንቋና ማንነት አንዱ መስፈርት ነው፡፡ በ1986 የሕዝብ ቆጠራ መሰረት የደራ፣ እነ ፍቼ፣ ደብረ ሊባኖስ ያሉበት የግራር ጃርሶ ፣ እንዲሁም ዋና ከተማው መተሃራ የሆነው የፈንታሌ እና
Posted in Ethiopian News

HR6600 እና S3199 ከጉዳቱ ጥቅማቸው የላቀ ነው – ግርማ ካሳ

በአሜሪካ ሶስት የመንግስት አካላት አሉ። ሕግ አውጭው ( legislative branch) ሕግ አስከባሪው ( executive branch) እና ሕግ ተርጓሚው (judiciary branch) ሕግ አውጭው ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። በሕዝብ ብዛት በየ ሁለት አመቱ የሚመረጡ 435 አባላት ያሉት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (House of Representatives) ነው። ሁለተኛው በአሜሪካ ካሎ 50 ክፍለ ሃገራት የተመረጡ 100 ሴኔቴሮች ያሉት ሴኔት ነው። ከ እያንዳንዱ ሴኔት 2 ሴኔቶሮች ይመረጣሉ። በየ ስድስት አመቱ። – አንድ ሕግ ረቆ ሕግ ከመሆኑ በፊት በሁለቱም ምክር ቤቶች ጸድቆ በፕሮዘዳንቱ መፈረም አለበት። ኢትዮጵያን በተመለከተ የተወካዮች ምክር ቤት HR6600 አርቅቆ በኮሚቴ ደረጃ አሳልፏል። በተመሳሳይ ሁኔታ ሴኔቱ S3199 አርቅቆ በኮሚቴ አሳልፉል። – የሚቀጥለው ረቂቅ ሕጎቹ በሁሉም አባላቱ በየምክር ቤቱ መጽደቅ አለባቸው። ያ ከሆነ በኋላ የተወካዮች ምክር ቤትና የሴኔት የተመረጡ ተወካዮች ፣ ኮንፈራንስ በሚባለው ሂደት ሁለቱን ሕጎች ያጣጥሟቸውና አንድ ሕግ ይወጣቸዋል። – ከጥቅት ሳምንታት በፊት ረቂቆቹ ብዙ የተለያዩ ነበር። በተለይም S3199 ትግራይ ላይ ብቻ ያተኮረ ነበር። ሆኖም ግን ተሻሽሎ ከመጣ በኋላ S3199 ከ HR6600 ጋር የተቀራረበ ሆኗል። ስለዚህ ማጣጣሙ አስቸጋሪ አይሆንም። – ወደ ፕሬዝዳንቱ ለፊርና ከመሄዱ በፊት የተጣጣመውን ሕግ ሁለቱም ምክር ቤቶች እንደገና ያጽድቁታል። ከዚያ በኋላ ለፕሮዘዳንቱ ይላካል። ክ67% በላይ ድምጽ ካገኘ ፕሬዘዳንቱ ፈረመም አልፈረመም ሕግ ይሆናል። ከዚያ በታች ከሆነ ግን ፕሬዘዳንቱ መፈረም አለበት። – HR6600 እና S3199 ሕግ መሆናቸው እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው የሚል እምነት አለኝ።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጥያቄ ለአዲስ አበቤ- የትኛው አማራጭ ይሻልሃል ? #ግርማካሳ

(በቅድሚያ በዚህ መልእክት የምትስማሙ ሼር አድርጉ። አንድ ህዝብን ለማደራጀትና ለማነቃነቅ መረጃዎች እንዲሰራጩ ማድረግ ነው ቁልፍ ነገር ነው) አዲስ አበባ ከ7 እስከ 10 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ይኖርባታል ተብሎ ነው የሚገመተው። አዲስ አበባ የተወለደ አለ፣ ከሌላ ቦታ መጥቶ ኑሮዉን አዲስ አበባ ያደረገ፣ አዲስ አበቤ የሆነ አለ። አዲስ አበባ ምን አለፋችሁ ማንም ኢትዮጵያዊ መጥቶ በሰላም፣ ዘሩ፣ ኃይማኖቱ ሳይጠየቅ የሚኖርባት ድንቅ ከተማ ናት። የፍቅር የአንድነት ከተማ። የሸጋ አገር ወይንም ሸገር፡፡ አሁን ይችን ውብ ከተማ፣ የፌንፌኔ ፕሮጀክት የሚሉትን ነድፈው፣ ባሌና ኮፈሌ፣ አሳሳና አቦምሳ፣ ዶሎና ያቤሎ ፣ በደኖና ኖኖ፣ ጃርሶና ጉሊሶ፣ ለማድረግ እየሞከሩ ነው። አንድ ጎሳ ብቻ በብዛት የሚኖሩባትና ኦሮምኛ የሚነገርባት ከተማ እንድትሆን። ዴሞግራፊ ለመቀየር ተፍ ተፍ የሚሉትም ለዚህ ነው። የዘር ልዩነትን፣ ተረኝነትን፣ መከፋፈልን እርስ በርስ በነዋሪቿ መካከል መናቆርን እያመጡባት ነው። እያጨማለቋት ነው። ውበቷን ክብሯን፣ ማንነቷንና፣ የእድገቷንም መሰረት እያናጉ ነው። አንድነትን (Unity) ሳይሆን አንድ አይነትነትን ( uniformity) እርሱም ኦሮሞ ብቻ፣ ኦሮምኛ ብቻ የሆነች ከተማ፣ ለኦሮሞ፣ በኦሮሞ የኦሮሞ የሆነ ብቻ፣ በኢኮኖሚም በሁሉም ኦሮሞ ቅድሚያ የሚያገኝበትን፣ ኦሮሞ ልዩ ተጠቃሚ የሚሆንበትን፣ የመንገድ የክፍለ ከተማ ስሞች ወደ ኦሮሞ ስሞች የሚቀየርበትን፣ ኦሮሞ ብቻ ከንቲባ አስተዳዳሪ የሚሆነበትን፣ ኦሮሞ ያልሆነ ወይም ኦሮምኛ የማያወቅ መቀጠር የማይችልበትን አሰራር የሰፈነፋባት ከተማ እንድትሆን እየሰሩ ነው። ኦሮሞ ያልሆንን ፣ ወይም ኦሮምኛ የማንናገር አዲስ አበቤዎች፣ ያለን ምርጫ አራት ነው፡ 1ኛ አማራጭ – ኦሮምኛ ተምረን፣ እናት፣ ወይንም አባት፣ ወይንም አንድ
Posted in Ethiopian News

የብልጽግና ጉባዬ የለውጥ ወይስ የኦነግ/ኦፌኮ ጉባዬ አይነት #ግርማካሳ

ዶር አብይ አህመድና የኦህዴድ ጓዶቹ “ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ” እያሉ ፣ የውስጥ አጀንዳቸውን ደብቀው፣ የሌላውን ማህበረስበ ድጋፍ አገኙ፡፡ አራት ኪሎን ተቆጣጠሩ፡፡ ሌላው ማህበረሰብ ኦሮሞ ስላልሆኑ ድጋፍ አልነሳቸውም፡፡ ማንም ይሁን ማንም፣ የፈለገ ዘር ይኑረው፣ አገርን በፍትሃዊነትና በእክልነት ካስተዳደረ ፣ ኢትዮጵያን ካስቀደመ፣ ህዝብ ችግር የለበትም፡፡ ህዝቡ ዘረኛ እንዳልሆነም ስላወቁም ነው፣ “ኢትዮጵያ” ብንለው ይደግፈናል ብለው፣ calculate አድርገው የመጡት፡፡ ትክክል ነበሩ፡፡ ሕዝብ ደገፋቸው፡፡ የሚፈልጉትን ስልጣን ካገኙ በኋላ ግን ድብቅ አጀንዳቸው እየመዘዙ መተግበር ጀመሩ፡፡ ሲነቃባቸው ውሸት እየተናገሩ፣ ሰውን እያታለሉ፣ convince and confuse እያደረጉ ለአራት አመት ዘለቁ፡፡ መጀመሪያ እንደሚፈለገው ለውጥ ሊያመጡ አልቻሉም፡፡ ለምን ሲባሉ “የህወሃት/ኢህአዴግ መዋቅር አስቸጋሪ ስለሆነ ነው፣ ዉህደት ስንፈጥር ፣ ችግሮች ይስተካከላሉ፣ ከዘር አስተሳሰብ ወደ ዜግነት አስተሳሰብ እንሸጋገራለን” አሉ፡፡ ሰውም የኢህአዴግ ድርጅቶችን ዉህደት መጠበቅ ጀመረ፡፡ አስታውሳለሁ እኔም ራሴ “ዉህደት ሲፈጸሙ 70% የአገራችን የፖለቲካ ቀውስ ይስተካከል” ብዬ ጽፌ ነበር፡፡ አምኛቸው፡፡ ዉህደት ሲያደርጉ የፖለቲካ ፕሮግራም መሻሻሎች ያደርጋሉ፣ አሰራሮችን ይቀይራሉ ተብሎ ተጠብቆም ነበር፡፡ ለምሳሌ በኦሮሞ ክልል ኦሮሞ ያልሆኑ የብልጽግና አባልና አመራር ይሆናሉ የሚል፡፡ ዉህደቱ ተጠናቀቀ ግን የባሰ አደረጃጀት ተፈጠረ፡፡ ኦህዴዶች ስማቸውን ወደ ኦሮሞ ብልጽግና ቀየሩ፡፡ በኢሕአዴግ 25% መቀመጫ ነበራቸው፣ አሁን ከ40% በላይ መቀመጫቸውን አሳደጉ፡፡ የበፊት የዘር አሰራር ወዘተ እንደውም በተባባሰ መልኩ ቀጠለ፡፡ ለአዲስ አበባ፣ ለሃረር፣ ለድሬዳዋ ከተመደበነው በርካታ ኮታ ፣ ከአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ከሚባለውም ሙሉ ለሙሉ ኮታ ወስደው፣ ከአጋራቸው ከሲዳማ ብልጽግና ጋር በብልጽግና ጠቅላላ ጉባኤ ከ50% በላይ
Posted in Ethiopian News

እንኳን ከአጤ ሚኒሊክ ጋር ሊወዳደሩ ከዚህ በፊት ከነበሩ መሪዎች ሁሉ የባሱ ናቸው – ግርማ ካሳ

የአድዋን ድል ስናከብር፣ የአድዋ ከተማ ሕዝብ ፣ በፌዴራል መንግስቱ የፖለቲካ አመራር ከፍተኛ ድክመት የተነሳ ፣ አሁንም በሕወሃት ቀንበር ውስጥ ያለ መሆኑ እጅግ የሚያሳዝን ቢሆንም፣  በተለያዩ የአገሪቷ  ክፍል  126ኛ  በዓል በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡ በአዲስ አበባ ፣ የብልጽግና  መንግስት ሃላፊዎች፣  የአድዋን በዓል ከአጤ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱ  ለመነጠል ካላቸው ፍላጎት የተነሳ፣   በተለምዶ በዓሉ ከሚከበርነት ከሚኒሊክ አደባባይ  የተለየ ቦታ እንዲከበር በወሰኑት መሰረት ፣ በሌላ ቦታ ካድሬዎቻቸውን ይዘው አክብረዋል፡፡ ሆኖም ግን በሚሊዮኖች የሚቆጠር የአዲስ አበባ ህዝብ በጊዩርጊስ ሚኒሊክ አደባባይ በመትመም፣ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ የኢትዮጵያን ሰንደቅን በማዉለብለብ፣ የተለያዩ ትእይንቶችን በማድረግ፣ በአስገራሚና እጅግ አስደማሚ ሁኔታ በዓሉን አክብሯል፡፡ የአድዋኦ በዓልን በተመለከተ የኦሀዴዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ ዶር አብይ አህመድ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ የኦህዴዱ ጠቅላይ ሚኒስተር ያልኩት፣ ለአንድ ጎሳ የቆመው የኦህዴድ ወይም የኦሮሞ ብልጽግና በበላይነት የሚዘውረውን፣   ተረኛና ዘረኛ መንግስትን የሚመሩ  በመሆናቸው  ነው፡፡ ብዙ ሊጻፍባቸው የሚገባ ነጥቦች ቢኖሩም በዶር አብይ መልእክት  ዙሪያ  ሁለት ነጥቦች ብቻ  ላይ አስተያየት እሰጣለሁ፡፡ 1ኛ ነጥብ፣  የኦህዴዱ  መሪ እየተሸነፈ የነበረን የህወሃት  ኃይል፣  “እኔ መርቼ አሸነፍኩ”  ለማለት ፎቶና ቪዲዮ አንሽዎችን አስከትለው፣  “ ዘመትኩ”  ብለው ነበር፡፡ ያንንም ተከትሎ  ሳር ቅጠሉ ስለርሳቸው  “ጀግንነት”  እንዲያወራላቸው  ነበር የፈለጉት፡፡ እንደ አቶ አሳማኸኝ አስረስ ባሉ ህሊናቸውን በሸጡ ግለሰቦች ሲያስጨበጭቡ፣   እንደ አቶ መላኩ አለበል ባሉ ደግሞ ፎቷቸውን ለጨረታ ሲያሻሽጡ ነበር፡፡ ሳይዋጉ ተዋጋው እያሉ ራሳቸውን ከፍ ከፍ  ለማድረግ የሞከሩት ዶር አብይ አህመድ፣ የአፍሪካ ኩራት የሆኑትን የአድዋ ድልን
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ወጣቱን ጫካ እንዲገባ ባትገፉት መልካም ነው – ረ/ፕ ሲሳይ አውግቾው

ምን አይነት ልብ ቢኖራቸው ነው? ወያኔ አማራን በጠላትን ፈርጆ ፣ ወሮ፣ ዘርፎ ፣ አውድሞ ቢሄድም፣ አሁንም ራያንና ከፊል ሰቆጣን እንዲሁም ማይጠብሪንና አዳርቃይ ወርሮ፣ ወልቃይት እና ሁመራን ለመውረር በከፍተኛ ዝግጅት ላይ መሆኑ እየተነገረ ባለበት ሁኔታ ። ጎጃምና ጎንደርን ከመናገሻዋ ከተማ (አዲስ አበባ) በመቁረጥ፣ በየቀኑ በፍልቅልቅ እና ጉሃጺዮን ንጹሃንን በመግደል፣ በቡሬ ወለጋ በአስር ሺህ የሚቆጠር ወገኑ መንገድ ተዘግቶበትና አደጋ ላይ ሆኖ፣ በባሶ ሊበል እና በአበይ ሸለቆ ጠላት ለወረራ እየተዘጋጀ። በወለጋና በጅባት-ዳኖ ወገኖቹ በግፍ እየተገደሉ፣ ቤት ንብረታቸው ተዘርፎ፣ እየተፈናቀሉ። ይባስ ብሎም ከሶሪያ እና ከየመን የተፈናቀሉትን ማረፊያ ያልነፈገች ሀገር አማራው መርገጫ እንዳያገኝ በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ ። የአማራ ካድሬ በየቀጠናው ተቧድኖ ሲናጭ፣ ተስፋ የተጣለባቸው ድርጅቶች በቁርጥ ቀን አንደበታቸው ሲዘጋ፣ በየወረዳው እና ቀበሌው ያለው ካድሬ ያስቆመውን የፋኖ ስልጠና ብዛት ሪፓርት አድርጎ በጌቶቹ ፊት ሞገስ ለማግኝት ሲጣደፍ ማየት ግርምት ይጭራል። ጎበዝ ልብ ግዙ!!! ወጣቱን ጫካ እንዲገባ ባትገፉት መልካም ነው። ነገ ወራራ ሲመጣ ምን ብላችሁ ልትቀሰቅሱት ነው? VIA ረ/ፕ ሲሳይ አውግቾው
Posted in Ethiopian News

ዳቦ ለጠየቀ ቁርጥ ስጋ ለምን አትበሉም ? #ግርማካሳ

በ18ኛው ክፍለ ዘመን፣ ከፈረንሳይ አብዮት በፊት ነበር፡፡ አውስትሪያ ነው የተወለደችው፡፡ የንጉስ ፍራንሲስ 1ኛ ልጅ ነበረች፡፡ ታላቅ ልዕልት፡፡ የአገሮችን ወዳጅነት ለማጠናከር የፈረንሳይ ንጉስ ሉዊስ 16ኛን ታገባና የፈረንሳይ ንግስት ትሆናለች፡፡ማሪ ኦንቷኔት ( Marie Antoinette) ትባላለች፡፡ በወቅቱ በፈረንሳይ እጅግ በጣም ከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር ነበር፡፡ በተለይም ቄሶቹ (clergy) መኳንቶቹ (nobility) በዋናነት ከፓሪስ ከተማ ወጣ ብላ በምትገኘው ቨርሳይ (Versailles) በምትባል፣ ቤተ መንግስት እንድትሆን በታላቁ በሉዊስ 14ኛ የፈረንሳይ ንጉስ የተቆረቆረችው  አነስ ያለች ከተማ፣ በምቾት ይኖሩ ነበር፡፡ ነገር ግን በፓሪስና በተቀረው ፈረንሳይ ሌላው ሕዝብ ትልቅ ችግር ውስጥ ወድቆ ነበር፡፡ ከፍተኛ ግብር ይከፍሉ ነበር፤፡ ኑሮ ተወዷል፡፡ ምግብ መግዛት አይችሉም፡፡ ብዙዎች ጠኔ ውስጥ ወድቀው ነበር፡፡ ቨርሳይ ያሉት ግን የአብዛኛዉ ህዝብ ስቃይና ችግር ሊሰማቸው አልቻለም፡፡ ምንም አይመስላቸውም ነበር፡፡ ህዝቡ ተማረረ፡፡ ከፓሪስ ወደ ቨርሳይ ፈረንሳዊያን  መጥተው ድምጻቸውን ማሰማት ጀመሩ፡፡ የሚፈልጉት አንድ ነገር ነበር፡፡ ዳቦ፡፡ የሚፈለጉት መሸከም ያካታቸው የድህነት ቀንበር እንዲቀንስላቸው፡፡ ማሪ አንቷኔት ከቤተ መንግስት ውጭ ድምጽ እያሰሙ ያሉትን ከሩቅ ፣ ከቤተ መንግስቱ ፎቅ ላይ አየችና፣ “ምንድን ነው የሚፈልጉት ? ” ብላ ጠየቀች፡፡ “ዳቦ ነው የሚፈልጉት” አሏት፡፡ “ታዲያ ዳቦ ከሌለ ኬክ ለምን አትሰጧቸውም ?” አለች ይባላል፡፡ ያንን ያህል ነበር እርሷም ሆነ ንጉሳዊ ቤተሰቦች፣ ገዢዎች፣ በተቀሩት ዜጎች ዘንድ ስላለው ሁኔታ out of touch የነበሩት፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶር አብይ አህመድ በፓርላማ ያደረጉትን ንግግር የተወሰነውን አደመጥኩ፡፡ ያው እንደተለመደው ውሸት፣ ማጋነን የታጨቀበት ንግግር ነበር፡፡ በተለይም ስለ
Posted in Ethiopian News

ሕወሃት ገለል ብትል የተጋሩን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ ስምምነት መፍጠር ይቻላል #ግርማካሳ

ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ጸጋዬ ከጌታቸው ረዳ ጋር ያደረገውን ረጅም ቃለ ምልልስ ከቀናት በፊት ጀምሬው ነበር። ጨረስኩት። በነገራችን ላይ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ የማከብረው ጋዜጠኛ ነው። በአንዳንድ ጉዳዮች ልዩነቶች ከርሱ ጋር ቢኖሩኝም ለረጅም አመታት ለኢትዮጵያዊነት ይተጋ የነበረ ጋዜጠኛ ነው። እንደው ሌላው ቢቀር ፣ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶር አብይ አህመድ አሜሪካ መጥቶ የነበረ ጊዜ ፣ የጠየቃቸውንና እስከ አሁን ድረስ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ መልስ ያልተሰጠባቸውን ጥያቄዎች ማሰቡ ብቻ ይበቃል። አሁን ያለውን የዘርና የጎሳ አወቃቀርንና ሕገ መንግስትን በስፋት፣ በጥልቀት ሲተች፣ ጎጂነቱን ሲያስረዳ የነበረ ነው። ጊዜው እጅግ የተበላሸና የተጨማለቀ እንደመሆኑ ሁላችንም በተወሰነ መልኩ በዘረኝነትና ጎጠኝነት የመወሰድ ነገር ይታይብናል። ቴዎድሮስም ከኛ የተለየ ሊሆን አይችልም። ከርሱ ጋር የተፈጠረ አለመግባባት ካለ፣ ነገሩን በዚያ መልኩ እንየው።የዘር ጡዘቱ ቀንስ ሲል ነገሮች ይስተካከላሉ። ቴዎድሮስ ከጌታቸው ጋር ባደረገው ቃለ ምልልሱ ጌታቸው ረዳ ስህተቶች እንደሰሩ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ የገለጸበት ሁኔታ እንዳለ ነው የተረዳሁት። “ከአማራ ልሂቃን ጋር ሂሳብ እናወራርዳለን” ያለው የተሳሳተ አባባል መሆኑን፣ “ኢትዮጵያን ሲኦል ድረስም ሄደን እናፈርሳለን” የሚባለውም እርሱ እንዳላለውና፣ እርሱም ሆነ የትግራይ ክልል መንግስት ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ፍላጎት እንዳላቸው ነው የገለጸው። የትግራይ ኦርቶዶክስ ፣ የትግራይ የእስልምና ጉባዬ ወዘተ እያሉ የኃይማኖት አባቶች እያስገደዱ፣  መከፋፈልን ለመፍጠር እያደረጉት ያለው፣ ትግይራን ለመገንጠን አስበውና አቅደው እየሰሩበት ያለ እንጂ  ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ፍላጎት እንዳላችው አመላካች ባይሆንም፡፡ በዚህ ጦማር አብዛኛው የጌታቸው ረዳ አስተያየቶች ብዙዎች ዉሸት የታጨቀባቸው እንደመሆኑ ወደ ጎን አድርጌያቸው አንድ ነገር ላይ ማተኮር እፈልጋለሁ፡፡
Posted in Ethiopian News

የወለጋዉንና የጉጂውን ጭፍጨፋና ጦርነት ለማስቆም የሚያስችል ምክረ ሃሳብ #ግርማካሳ

ከወያኔ ጋር የሚደረገው ጦርነት አንድ አመት ከአራት ወር ሆኖታል። ከሶስት አመት ተኩል በላይ እየተደረገ ያለ ሌላ ጦርነት አለ። ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው። በኦሮሞ ብልጽግናና በኦነጎች መካከልየሚደረግ። በወለጋ አራቱ ዞኖች ፣ በምእራብ ሸዋ፣ በሰሜን ሸዋ አንድ ሁለት ወረዳዎች፣ በጉጂና ምእራብ ጉጂ ዞኖች ዜጎች እየተገደሉ ነው። ደም እየፈሰሰ ነው። ቢያንስ 2800 የሚሆኑ፣ በይፋ የተረጋገጡ፣ ኦሮሞ ያልሆኑ ዜጎች፣ አማራዎችና አማራ ባይሆኑም አማራ የሚባሉ አማርኛ ተናጋሪዎች፣ በማንነታቸው ምክንያት በጭካኔ ተገድለዋል። ይፋ ያልወጡትን ስናካትት ቁጥሩ ወደ አስር ሺህ ሊጠጋም ይችላል። የሶስት አመት ልጅ እማርኛ ተናገረ ተብሎ የሚገደልበት ሁኔታ ነው በኦሮሞ ክልል ያለው። በነ ወለጋ። ከመቶ ሺህ በላይ ዜጎች ደግሞ በማንነታቸው ምክንያት ተፈናቅለዋል። ወደ 5 ሺህ የሚሆኑ ኦሮሞዎች፣ በኦሮሞ ብልጽግናዎችና በኦነጎች መካከል በሚደረገው አራት አመት ሊያስቆጥር ጥቂት ወራት በቀሩት ጦርነት ሕይወታቸው አልፏል። ብዙዎች ተፈናቅለዋል። በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ግድያዎቹ የክፉና በቀል ያለበት መሆናቸው ነው። ምንም ነገር ውስጥ የሌሉበት ሚስቶችን፣ ልጆችን፣ ከብቶችን ሳይቀር መግደል ተጀምሯል:: በአስር ሺሆች የኦሮሞ ወጣቶች ታስረዋል። ሕዝብ በፍርሃትና በሰቀቀን ውስጥ ነው የሚኖረው። ጠዋት ብልጽግናዎች ይመጡና ኦነግን ረዳችሁ ብለው ፍዳቸውን ያሳይዋቸዋል። ማታ ኦነጎች ይመጡና ብልጽግናን ረዳችሁ ብለው ያሸብሯቸዋል። ምን አለፋችሁ ሕዝቡ ተሰቃየ። በኦሮሞ ብልጽግናዎችና በኦነጎች መካከል ያለው ጠብ በዋናነት የስልጣን ጠብ ነው፡፡ እነ ዶር አብይ አህመድ ያላሟሉት ኦነጎች የሚጠይቁት የኦሮሞ ጥያቄ የሚሉት ነገር የለም። ግን ጠቡ ስልጣን ነው። ወገኖች እንዲህ ልንቀጥል አንችልም። የዶር አብይ የብልፅግና መንግስት
Posted in Ethiopian News

ዶር ሊያ ልትከበር የሚገባት ኢትዮጵያዊት ናት፤ ሃላፊነቷን ለመወጣት ባጀት ጠይቃለች፤ 36 ቢሊዮን ብር !

ዶ/ር ሊያ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ናት። ምን አልባት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ካሉ በሞያቸው በብቃት አገርን እያገለገሉ ካሉ ሚኒስቴሮች መካክል እጅግ በጣም በጣት ከሚቆጠሩት መካከል አንዷ ናት። ዶር ሊያ እርግጠኛ ነኝ በሚኒስተሮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በአማራና በአፍር ክልል በሕወሃት የወደሙ ሆስፒታሎችና የጤና ጠቋማትን መልሲ ለመገንባት ይሁን ለማዳሰ መንግስት ተጨማሪ ባጀት እንዲመድብ ይጠይቃሉ ብዬ አስባለሁ። የሚኒስተሮች ምክር ቤት ለመልሶ ማቋቋም የመደበው 5 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። ዶር ሊያ ፣ በሕወሓት የወደሙ የጤና ተቋማትን መልሶ ለመገንባት ከ36 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ እንደሚጠይቅ ነው ያስገነዘቡት። እንግዲህ ከዚህ ጋር በተገናኘ የሚነሱ መሰረታዊ ጥያቄዎች አሉ፡ ዶር ሊያ 36 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈለግ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ ወይንም ለጠቅላይ ሚኒስተሪ ጽ/ቤት (ለዶር አብይና ለአቶ ደመቀ መኮንን) አቅርበዋል ወይ ? ሳሰበው ያቀርባሉ የሚል እምነት ነው ያለኝ። ወደ ሜዲያ ከመውጣቸው በፊት ያለው አሰራር እንደዚያ ስለሆነ። ታዲያ በዶር አብይ አህመድና በአቶ ደመቀ መኮንን የሚመራው የሚኒስተሮች ምክር ቤት ለምንድን ነው 5 ቢሊዮን ብር ብቻ እንዲመደብ ያደረገው ?????? እዚህ ጋር ልብ እንድትሉ የምኪያስፈለገው 5 ቢሊዮን የተባለው ለሁሉም ነገር ነው። ትምህርት ቤቶች፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ ድልድዮች ወዘተ ብዙ የፈረሱ ተቋማት አሉ። 5 ቢሊዮን ለነዚህ ሁሉ ሲከፋፈል፣ 36 ቢሊዮን ብር የሚያስፈለገው የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር 1 ቢሊዮን ብር ብቻ ቢደርሰው ነው። በኔ እይታ በፌዴራል ደራጃ ያለው የብልጽግኛ፡መንግስ ት የአማራና የአፋር ክልል እንደ ወደመሙ፣ እንደደኸዩ እንዲቀጥሉ የሚፈልጉ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አዲስ አበባ ሰላም ከሆነች ሌላው ቢጋይ ደንታ የሌለው መንግስት #ግርማካሳ

ከታህሳስ 20 ጀምሮ እስከ ታህሳስ 22 ባለው ጊዜ ብቻ በደራ ወረዳ ጮካና ድሬዳዳ ቀበሌዎች ከ33 በላይ ዜጎች በታጣቂዎች ተጨፍጭፈዋል፡፡ በባቡቡሬ ቀበሌ ቁጥራቸው ገና አልታወቀም እንጂ ብዙዎች እንደተገደሉ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡ በአምቦ ዙሪያ 11 ዜጎች አማራዎች ናችሁ በሚል በታጣቂዎች ተገድለዋል፡፡በኖኖ ወረዳ 28 አማራዎች፣ 4 ኦሮሞዎች ፣ ሲደመር 32 ዜጎች በታጣቂዎች ተገድለዋል፡፡ሲደመሩ ቢያንስ 76 ዜጎች መሆናችው ነው፡፡ ይሄ እንግዲህ ከአዲስ አበባ አቅራቢያ ያሉ አካባቢዎች ናቸው፡፡ በሸዋ ውስጥ እየሆነ ያለ ነገር ነው፡፡ በሙገር በመሳሰሉ ቦታዎች የመንግስት ተቋማትን፣ ፋብሪካዎችን ታጣቂዎች የተቆጣጠሩበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ እነዚህ ታጣቂዎች እነ ማን ናቸው ? የብልጽግና መንግስት በነጃል መሮ የሚመራው ኦነግ ሸኔ የሚላቸው ናቸው ይላል፡፡ ራሳቸውን ኦነሰ (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ወይም ኦላ Oromo Liberation Army) ብለው የሚጠሩት እነ ጃል መሮ፣ እኛ ንጹሃን ዜጎችን አንገድልም ፣ ብልጽግና ነው ይሄን የሚያደርገው ይላሉ፡፡ ማንም ይሁን ማንም እነ ጃል መሮ ይሁኑ ኦህዴድ ያደራጃቸው ታጣቂዎች ኦነጎች ናቸው፡፡ የኦነግን አርማ ይዘው፣ በኦነግ ስም የሚንቀሳቀሱ፡፡ ስለዚህ ታጣቂዎችን የኦነግ ታጣቂዎች ነው የምላቸው፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ፣ ከአዲስ አበባ እስከ ሆሎታ ካለው አካባቢ በቀር ዋና ከተማዋ አምቦ ከተማ ዙሪያ ያሉ፣ የአምቦ ዙሪያ ወረዳን ጨምሮ በሁሉም የኦሮሞ ክልል ምእራብ ሸዋ ዞን፣ በሁሉም አራቱ የወለጋ ዞኖች (ምስራቅ፣ ምእራብ፣ ሆሮ ጉድሩና ቄሌም) ፣ በስሜን ሸዋ ደራ፣ ኩዩ፣ ደገምና ሂዳቶ አቦቴ ወረዳዎች ፣ በአጠቃላይ ወደ 52 ወረዳዎች፣ መንግስት በአስተማማኝ ሁኔታ ሰላምና መረጋጋት አስፍኖ
Posted in Ethiopian News

የኦነግ/ኦሀዴድ አካሄድ የኦሮሞ ክልልን የደም ጎርፍ የሚያደርግ ነው #ግርማካሳ

ኦነግ በሕወሃት ጊዜ አንድ ቀበሌ ተቆጣጥሮ አያውቅም። ሆኖም ግን ኦነግ በኦህዴድ ውስጥ ነበር። የኦነግ ፖለቲካ፣ የኦነግ አስተሳሰብ ሙሉ ለሙሉ ማለት ይቻላል በኦህዴድ ውስጥ ቀጥሎ ነበር። በኦነግ እና በኦህዴድ ፣ አሁን የኦሮሞ ብልጽግናዎች ነን ይላሉ፣ መካከል ያለው ልዩነት የስልጣን ብቻ ነው። በኦሮሞ ክልል እርስ በርስ እየተገዳደሉ ያሉት ለኦሮሞ ማህበረሰብ በማሰብ ሳይሆን ለስልጣናቸው ብለው ነው። እነ ዳዎድ ኢብሳ የተኮፈሱት፣ ጀሌዎቻቸውን እነ ጃልመሮን በሽፍትነታቸው እንዲቀጥሉ ያደረጉት፣ ለስልጣናቸው ብለው ነው። ኦህዴዶች ኦነጎችንና ኦፌኮዎችን የገፉት ለስልጣናቸው ብለው ነው። ዶር አብይ አህመድ ጃዋር መሐመድን ያሰረው ወንጀል ሰርቷል ብሎ አይደለም። ለስልጣኔ ያሰጋኛል ብሎ ነው። ያ ባይሆን ኖሮ ጥቅምት 2012 ጃዋር ተከበብኩ ብሎ ያ ሁሉ እልቂት እንዲፈጠር ምክንያት ሲሆን ያስረው ነበር። ግን ከስምንት ወር በኋላ ፣ ሰኔ 2013 የሃጫሉን ግድያ ተከትሎ ነው ያሰረው። ለምን ያኔ ለስልጣኔ ያሰጋኛል ስላለ። የኦሮሞ ብልጽግና በብልጽግና ደረጃ ከሌሎች ብልጽግናዎች ጋር፣ በተለይም ከአማራና ከሶማሌ ብልጽግና ጋር ትልቅ መቃቃር አለበት። በኦሮሞ ብልጽግና ውስጥም እርስ በርስ ተከፋፍለው፣ አንዳቸው በአንዳቻቸው ላይ አሻጥር እየሰሩ ነው። በኦሮሞ ብልጽግና ውስጥ የነ ዶር አብይ አህመድ ቡድን አለ፤ ቀን ቀን መሪያችን አብቹ እያለ ማታ ማታ ከኦነጎች ጋር የሚሰራ ፣ ከኦነጎች መመሪያ የሚቀበል፣ ለኦነጎች መረጃ የሚሰጥ አለ።(በነገራችን ላይ ኦነግን መቆጣጠር ያልተቻለው በዚህ ምክንያት ነው) በአንዱ የኦሮሞ ብልጽግና ቡድን መካከል በአንድ በኩል፣ በኦነግና በሌላው የብልጽግና ቡድን መካከል በሌላው በኩል ባለው ፍትጊያ ከፍተኛ ደም መፋሰስ
Posted in Ethiopian News

ጠዋት አይቆምም የተባለው ትግል ከሰዓት ቆሟል – ባዬ ተሻገር

“በአለህበት ጽና”  ተብሎ የተላለፈው ውሳኔ የመንግሥት የልብ ትርታ የቱ ጋር  እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። አዲርቃይ፣ አላማጣና የመሳሰሉ ቦታዎች ያለውን ኢትዮጵያዊ ግፍና መከራ የካደ፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ለመንግሥት የሰጡትን ድጋፍ ዋጋ ያሳጣ፣ ኢትዮጵያ በሕወሃት ታጣቂ እየተወጋች ዘለዓለም እንድታነባ መንገድ የሚጠርግ ድምዳሜ ነው። ሰሞኑን እስከ ዞን ወደታች ወርዶ ጦርነቱን በድርድር ስለማጠናቀቀ የተሰጠው ስልጣና ይፋዊ ውጤት ነው። የሕወሃት ታጣቂ እጅ ሳይሰጥ፣ መሳሪያ እንዲያወርድ ሳይደረግ፣ ለደረሰው ሰብዓዊና ቁሳቂ ውድመት ካሳ ሳይተመን፣ የወንጀለኛው ቡድን መሪዎች ለፍርድ ሳይቀርቡና ፍትህ  ሳይበየን  አሸባሪው ቡድን እጁ በደም እንደተጨማለቀ with impunity እንዲያመልጥ ዕድል የከፈተ ነው። ይህን ውሳኔ ሕዝባችን መቀበል የለበትም። የመንግሥትን ውሳኔ ደግፈው የሚያሽቃብጡ ጥቂቶች በጭንቁ ጊዜ ከጎናቸው የቆመውን ሕዝብ የካዱ የእናት ጡት ነካሾች ናቸው። የዓለም አቀፉን ጫና በመፍራት ሕዝባችን የጅብ ራት አድርገውታል። በሺህዎች የሚቆጠሩ ወንድሞቻችን ደም በከንቱ ፈሶ እንዲቀር እየተደረገ ይገኛል። የዛሬ ዓመት የፈፀሙትን ትጥቅ ያለማስፈታት ጥፋት ደግሞውታል። ወያኔ እንደገና ተደራጅቶ መልሶ ሕዝባችን እንዲወጋ አጋጣሚውን ፈጥረውለታል። ውሳኔው ከመለስ ዜናዊ ውሳኔ የሚለይ አይደለም። ከዚህ ውሳኔ የሚገኘው ትርፍም ከአልጀርሱ ስምምነት የተለየ አይሆንም። መንግሥት ለትግራይ ሕዝብ የጥሞና ጊዜ ለመስጠትና ገበሬውም እንዲያርስ በማሰብ ትግራይ ክልልን ለቅቄ ወጥቻለሁ የሚለውን ውሳኔ በከፍተኛ አድናቆት ሲያራግቡና ሲያንቆለጳጵሱ የነበሩ ሰዎች የውሳኔውን ስህተትነት ለመገንዘብ በሕዝባችን ላይ የደረሰውን ዘግናኝ ግፍ ማየት ይችላሉ። ግን ያንን ማድረግ ካለመፈለግም በላይ የዛሬውን ውሳኔ የሚያደንቁትና የሚያሞግሱት እነዚሁ ሰዎች ናቸው። ስህተትን ማንገስ አይሰለቻቸውም። አያፍሩምም።
Posted in Ethiopian News

የአብይ መንግስት ወያኔ በትግራይ እንድትቀጥል ወሰነ፣ መከላከያ ቁም ተባለ #ግርማካሳ

  “ኦህዴድ ለምን ከሕወሃት ጋር ድርድር ፈለገ ? ክፍፍል በብልጽግና ውስጥ” በሚል ርእስ አንድ ጽሁፍ አስነብቤ ነበር፡፡ ብዙዎች ከመደናገጥ ይሁን የተሳሳተ መረጃ ስለተሰጣቸው፣ ጠንካራ ተቃውሞና ትችት አቅርበውብኛል፡፡ የቀረቡ ትችቶችን የሚያንጸባርቅ አንድ ወንድም የሰጠኝን አስተያየት ላጋራችሁ፡፡ “ብሄራዊ የምክክር መድረክ ረቂቅ ሀሳብ ለውይይት ቀርቧል ከትህነግ ጋር እንወያይ የሚል ሀሳብ የለም ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠር የሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል ከሚል በተፎካካሪነት ያሉም ቢሆኑ ለመነጋገር እንዲያስችል የቀረበ እንጂ ወደ መቃብር ከወረደው እና በሽብርተኝነት ከተፈረጁ አካላት ጋር አንደራደር የሚል ሀሳብ አልቀረበም ” ነው ያለኝ። የዶር አብይ መንግስት ከሕወሃት ጋር ለመደራደር አያሰበ እንደሆነ በመግለጽ፣ ሕዝብ እውነቱን አውቆ፣ እንዲጠይቅ፣ የመንግስት ሃላፊዎችን ከሕዝብ ፍላጎት ውጭ እንዳይወጡ ግፊት እንዲያደርግ፣ እንደ መረጃ ቲቪ፣ ኢትዮ360 ያሉ ሜዲያዎችና ጦማሪያን ፣ እኔን ጨምሮ በስፋት ስንዘግባ መረጃዎች ስንሰጥ ነበር፡፡ ብዙዎች “መንግስትን ከሕዝብ ጋር ለማጣላት የሚሞክሩ ተበለን” በመንግስት ደጋፊዎች እየተከሰስን ነበር፡፡ በነገራችን ላይ የአብይ መንግስት ሕዝብ እውነትን እንዳያውቅ፣ መረጃ እንዳያገኝ የሚተጋ መንግስት ነው፡፡ ከሕወሃት በምንም ያልተናነሰ፡፡ ጋዜጠኞችን የሚያስር፣ ገለልተኛ ሜዲያዎችን የሚያፍን ፡፡ የመረጃ ቲቪ ትልቅ አገልግሎት ለሕዝብ እየሰጠ እንደሆነ የሚታወቅ ነው፡፡ የአብይ መንግስት ግን ቀደም ሲል በአገር ቤት ያለውን የመረጃ ቲቪ ቢሮ፣ በብሮድካስቲንግ ባለስልጣን በኩል እንዲዘጋ አድርጓል፡፡ አሁን ደግሞ በሳተላይት በቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይተላለፍ፣ በፈረንሳይ መንግስት በኩል የሳተላይት ኩባንያው ላይ ጫና በማሳደር፣ ለጊዜው ተሳክቶለታል። መረጃ ቲቪን ማቋረጥ ችሏል፡፡ ደግነቱ መረጃ ቲቪ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በተጠናከረ መልኩ የሳተላይት
Posted in Ethiopian News

ኦህዴድ ለምን ከሕወሃት ጋር ድርድር ፈለገ ? ክፍፍል በብልጽግና ውስጥ #ግርማካሳ

ወያኔዎች በወታደራዊ እንዲሁም በፖለቲካው መስክ ከፍተኛ ውድቀትና ሽንፈት እያጋጠማቸው ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ የዶር አብይ መንግስት ከሕወሃት ጋር ለመደራደር ተፍ ተፍ እያለ መሆኑን ተከትሎ በብዙዎች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣንና ተቃዉሞን እያሰነሳ ነው። የዶር አብይ አህመድ መንግስት ስለ ብሄራዊ መግባባት ምክክር በሚል፣ የድርድርን አስፈላጊነትን ያስቀመጠ ሰነድ አዘጋጅቶ፣ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፎች እንዲወያዩበት መመሪያ ያስተላለፈ ሲሆን፣ በዚያ መሰረተም የብልጽግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ዉይይቶች እያደረጉበት ይገኛሉ። ኢትዮ360 እንደዘገበው፣ በብልጽግና የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በተደረገ ዉይይት ዶር አብይ አህመድና ኦህዴዶች ፣ ራያንና ጠለምት ሳይጨምር፣ ወያኔ ከአማራና አፋር ክልል ለቃ ከወጣች በኋላ፣ ገፍተን መሄድ የለብንም፣ መደራደር አለብን የሚል ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን፣ የአማራ ብልጽግናዎች ሙሉ ለሙሉ ሃሳቡን ውድቅ አድርገዉታል። ከፍተኛ ጭቅጭቅ የነበረ ሲሆን፣ በመሃል፣ ከኦህዴድ ብልጽግና የተወሰኑ ሰዎች የቀረበውን ሃሳብ አሻሽለው፣ ከራያና ከጠለምትም ወያኔን ካስወጣን በኋላ እንደራደር የሚል ሃሳብ አቅርበዋል። ይሄን ሃሳብ በተወሰኑ የአማራ ብልጽግናዎች ሊቀበሉት እንደሚችሉ ቢገልጹም፣ ብዙዎቹ ግን እንደዚያም ሆኖ ህወሃት ትግራይ ውስጥ እስካለች ድረስ የአማራ ማህበረሰብ እንቅልፍ መተኛት አይችልምና፣ እስከ ወዲያኛው ሕወሃትን መወገድ አለባት የሚል ጠንካራ አቋም ይዘዋል። መስማማት ስላልተቻለም በጥቅሉ ከሕወሃት ጋር የመደራደሩ ሃሳብ ወደ ታች ተወስዶ ፣ ሰነድ ተዘጋጅቶ፣ ዉይይቶች እንዲደረግበት ውሳኔ አሳልፈው ተለያይተዋል። በዚህ መሰረት ከብልፅግና ሥራ አስፈፃሚ የወረደ ሰነድ ነው በሚል፣ ከወያኔ ጋር የእንደራደር ሀሳብ ዙሪያ፣ በአዲስ አበባ ውይይቶች ተደርገዋል። በውይይቶቹ ሃሳቡ በአዲስ አበባ ብልጽግና አባላት ውድቅ መደረጉን እየሰማን ነው። ከውይይቱ በፊት ማንኛውም የፓርቲ
Posted in Ethiopian News

ሕገ መንግስቱንና የጎሳ አወቃቀሩ በቶሎ ካልተቀየረ ደም መፋሰሱ ይቀጥላል #ግርማካሳ

ብዙዎች የማናውቀው ወይንም ልብ የማንለው አንድ ነገር አለ። አሁን ባለው ሕገ መንግስት፣ አሰራርና ፖለቲካዊ ሲስተም ኢትዮጵያ የለችም። ኢትዮጵያዊነት በሕገ መንግስቱ ቦታ የለውም። ኢትዮጵያዉያን እንደ ዜጋ እንደ ኢትዮጵያዊ እውቅና የላቸውም። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ብሎ ነገር የለም።ቴክኒካሊ ኢትዮጵያ የለችም።   ያለው አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ ጉራጌ የሚሏቸው ብሄር ብሄረሰቦች ናቸው። የአማራ መሬት፣ የኦሮሞ መሬት፣ የትግሬ መሬት የሚል ነው ያለው። ለአንድ ጎሳ/ዘር አንድ አካባቢ ተሸንሽኖ ተሰጥቶታል። ተከልሎ። ታጥሮ። የዚህ ጎሳ አባላት ለነርሱ በተመደበው ክልል ወይም ዞን ውስጥ ባለአገር ናቸው። ከዚያ ውጭ ደግሞ በሌሎች በጎ ፍቃድ ነው የሚኖሩት።   ባይገርማችሁ ውህድ ኢትዮጵያዊነት ብሎ ነገር የለም። አንድ ዜጋ የግድ አንዱ ጎሳ መምረጥ አለበት። አንድ ኢትዮጵያዊ በአንዳንድ የኢትዮጵያ ግዛቶች ውስጥ ካለው መብት ይልቅ በውጭ አገር ያለው መብት ይበልጣል። አንዳንድ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሄዶ ኢንቨስት ከማድረግ ታምራት ነገራ እንዳለው ኬኒያ ሄዶ ኢንቨስት ማድረግ ይቀላል።   እንግዲህ አሁን ያለው ስርዓት ሲስተም ይህ እንደመሆኑ፣ ኢትዮጵያን ማግኘት ከፈለግን ኢትዮጵያን ያጣፈውን ሕግ መንግስትና የጎሳ አወቃቀር መቀየር አስፈላጊ ነው።   ሕግ መንግስቱ የሚሻሻልና የጎሳን አወቃቀሩ የሚቀየር ከሆነ ያኔ የኢትዮጵያ ትንሳኤ ይሆናል። ከኦሮሞ ልዩ ኃይል፣ ከፋኖ፣ ከአማራ ልዩ ኃይል፣ ከአፋር፣ ሶማሌ .…ልዩ ኃይሎች ጠንከር ጠንከር ያሉት፣ ብቃት ያላቸው ተወስደው፣ ወደ መከላከያ እንዲገቡ ተደርጎ ፣ ጠንካራ የአገር መከላከያ ሰራዊት መገንባት ይቻላል። ፋኖም፣ ልዩ ኃይሎችም ሆነ ሌሎች የታጠቁ ሚሊሺያዎች እንዲከስሙ ይደረጋል። የአብይ መንግስት ይሄን ካደረገ፣ ቀደም ሲል ለሰራቸው ስህተቶችና ጥፋቶች ይቅርታ አድርግለታለሁ።  
Posted in Ethiopian News

የኢትዮጵያ ጠቅላላ የሰላምና መረጋጋት ሁኔታ #ግርማካሳ

ይህ የምታዩት ካርታ ከሞላ ጎደል አሁን በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ የሚያሳይ ነው። በአረንጓዴ የተቀቡ አካባቢዎች፣ ችግር፣ ጦርነት ፣ ውድመት የነበረባችው አሁን ግን በአንጻራዊነት መረጋጋትና ሰላም የሰፈነባቸው አካባቢዎች ናቸው። ብርቱካማ ቦታዎች ከሕወሃት ጋር ዉጊያ እየተደረገባቸው ያሉ፣ ሕወሃቶች አሁንም ያሉባቸው አካባቢዎች ናቸው። በቢጫ የተቀቡት ኦነግ አሁንም የሚንቀሳቀስባቸው ፣ ከኦነግ ያልጠሩ አካባቢዎች ናቸው። ቀያማ አካባቢዎች በሕወሃት ስር ያሉ አካባቢዎች ናቸው። እንግዲህ ላለፊት አራት አመታት በኢትዮጵያ መጥቷል ተብሎ የተነገረው መደመርና ብልጽግና ይሄን ነው የሚመስለው። የብልጽግና መንግስት አገሪቷን እንዲህ አይነት ትርምስ ውስጥ ነው የከተታት። አሁን ሕዝ በሁሉም አቅጣጫ እየተንቀሳቀሰ ያለው፣ ብልጽግናዎች አገሪቷን ካስገቡባር አዘቅት ውስጥ ለማውጣት ነው። ሌላው አረንጓዴ የተቀቡ ቦታዎች መብዛታቸው ሕዝባዊ ትግሉ ምን ያህል ውጤት እንዳመጣም አመላካች ነው። ምንም እንኳን በነዚህ ቦታዎች ከፍተኛ ውድመት የደረሰ ቢሆንም፣ ቢያንስ የወገን ጦር አሸባሪዎችን ማጽዳት ችሏል። ሕልማቸውን አጨናግፎባቸዋል። በቅርቡም ብርቱካማ የሆኑ ወደ አረንጓዴነት ይቀየራሉ ተብሎም ይጠበቃል። በቀይ የተቀቡ አካባቢዎች =========== ትግራይ፣ ጠለምትና ራያ በወያኔ ስር ናቸው። ጠለምትን መልሶ የመያዝ አቅም አለ። ግን ለምን የማጥቃት ዘመቻ እንደማይደረግ ለብዙዎች ግልጽ አይደለም። ራያም የወገን ጦር በቀላሉ የማስለቀቅ አቅም አለው። የአብይ መንግስት “ራያ የትግራይ ናት” በሚል የወገን ጦር ወደፊት እንዳይገሰግስ እንቅፋት ካልሆነ በቀር ራያን ማስለቀቅ አስቸጋሪ አይሆንም። የትግራይ ነገር የተለየ ስትራቴጂ ያስፈልገዋል። የወገን ጦር ትግራይን መልሶ መያዝ ይችላል፣ አለበትም። ነገር ግን አንደኛ የአብይ መንግስት ያንን የመወሰን ፍላጎት አለው ወይ የሚለው አጠያያቂ ነው።
Posted in Ethiopian News

ሕግ በማስከበር ስም ህዝብን ማሸበር ይቁም #ግርማካሳ

ይች እህት ያጠፋችው ጥፋት፣ የሰራችው ወንጀል የለም፡፡ ቤቷ ተበርብሮ መሳሪያ ወይም በህግ የሚያስጠይቁ ቁሳቁሶች አልተገኘባትም። ወንጀለኛ ስለመሆኗ ጥቆማ በርሷ ላይ አልቀረበም፡፡ ነገር ግን ሰባት ጊዜ ታስራለች። አራት ጊዜ ከሰፈሯ ወጥታ በድንገት ፍተሻዎች ሲደረግ። ሶስት ጊዜ ዘመዶቿን ልትጠይቅ ስትሄድ። ስድስት ጊዜ እንድ ቀን አሳድረው ለቀቋት። እንድ ጊዜ ሶስት ቀን አሰሯት። ይች እህት አሁን ከቤቷ አትወጣም። በተወለደችበት፣ ባደገቸት ከተማ የቁም እስር ሆናለች:: ወንጀሏ ምንድን ነው ? መታወቂያዋ ላይ ያለው ስሟ የትግሬ ስም መምሰሉ ነው። ለነገሩ ወላጆቿ ትግሬዎች ናቸው፡፡ ከትግራይ የመጡ፡፡ አሳሪዎቿ ግን ትግሬ መሆኗን አያውቁም ነበር። በስሟ ነበር ትግሬ ትሆናለች ብለው ያስሯት። ስሟ ጫልቱ ወይንም ሙኸባ ወይንም የምወድሽ ቢሆን፣ ወይም የአባቷ ስም ደቻሳ ወይንም ከድር ወይንም ዘጥአርጋቸው ቢሆን ኖሮ አትታስርም ነበር:: አንድ አባት ናቸው፡፡ ሰማኒያ ሶስት አመታቸው ነው፡፡ በደርግ ጊዜ የኢሰፓ አባል ነበሩ፡፡ ወያኔን ሲታገሉ የነበሩ በወያኔ የሚጠሉ፡፡ ወያኔም ስልጣን ስትያዝ ብዙ ፋዳ ያሳየቻቸው፡፡ በሽተኛ ናቸው፡፡ አልዛይመር ሳይዛቸው አልቀረም፡፡ ብዙ መርሳት ጀምረዋል፡፡ ከትግራይ ስለሆኑ ወስደው ያለምንም ማስረጃ በዚህ እድሚያቸው አስረዋቸዋል፡፡ እነዚህን እንግዲህ እንደምሳሌ ነው ያቀረብኩት፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተለይም በአዲስ አበባ እየሆነ ያለው ነገር እጅግ በጣም የሚያሳፍርና አንገት የሚያስደፋ ነው፡፡ አሳዛኝ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያን በማንነታቸው ብቻ፣ ትግሬ ስለሆነ ወይንም የትግሬ ስም የሚመስል ስም ስላላቸው ወከባና እንግት እየደረሰባቸው ነው፡፡ በይፋ የታወቀ 30 ሺህ፣  ነገር ግን በግልጽ ይፋ ያልሆኑት ሲጨምር እስከ 70 ሺህ የሚጠጉ ትግሬዎች ታሰረዋል፡፡
Posted in Ethiopian News

ብልጽግና ከወያኔ ጋር ቢደራደር ምንድን ነው የሚኮነው ? ግርማ ካሳ

ብልጽግና ከወያኔ ጋር ቢደራደር ምንድን ነው የሚኮነው ? #ግርማካሳ – ከ3 ወር በፊት ወያኔ ጋሸናን ይዛ ወደ ጋየንት መስመር አቀናች። በሰሜን ወሎ ጎንደር ድንበር አካባቢ ያለችዋን የደብረ ዘቢጥ ከተማን ተቆጣጠረች። እጅግ በጣም ጠመዝማዛ፣ ተራራማና ስትራቴጂ ከተማ። ጎንደር እንደተገባ ደግሞ ጨጨሆ ላይ የወገን ለመመከት ተዘጋጀ። አቶ ደመቀ መኮንን በጨጨሆን ግንባር ተገኝቶ ጉብኝነት አድርጎ ነበር። ያኔ የአማራ ክልል ክተት ባወጀ ገና ወሩ ነበር። – ብዙም አልቆየም የወገን ጦር ከጨጨሆ ደብረ ዘቢጥ ላይ ጥቃት ከፈተ። ደብረ ዘቢጥ ከተማን ተቆጣጠረ። አልፎም ኮኪት ደረሰ። የተረፉት የወያኔ ታጣቂዎች ወደ ፍላቂት ሸሹ። መከላከያ ቆርጦ በመግባት ጋሸናን ተቆጣጠረ። በጣም ከፍተኛ የወያኔ ጦር በጋሸናና በኮኪት መካካል ተከበበ። ያኔ ከትግራይ ከ25 ሺህ ተጨማሪ ኃይል ተላቀ። መልሰው ጋሸናን ያዙ። ያ ብቻ አይደለም፣ ፍላቂት ካለው ጋር ተቀላቅለው እንደገና ፊታቸውን ወደ ጎንደር አዞሩ። ኮኪት አልፈው ደብረ ዘቢጥን ያዙ። ለመጀመሪያ ጊዜ ደቡብ ጎንደር ዞን ገቡ። ጨጨሆ፣ ንፋስ መውጫ፣ ጋየንት፣ ክምር ድንጋይ እያሉ ደብረ ታቦር ደጃፍ ደረሱ። የጉና ተራራን ያዙ። – የደብረ ታቦር ህዝብ፣ ፋኖ፣ ሚሊሺያ፣ የአማራ ልዩ ኃይል ከመከላከያ ጋር በመሆን ከ15 ቀን በላይ ከፍተኛ ዉጊያ በየወረዳዉ ተደረገ። በ15 ቀናት ውስጥ የወገን ጦር ከደቡብ ጎንደር ሙሉ ለሙሉ ወያኔን አጸዳ። በዚያ ብቻ አልተወሰነም፣ ከፍተኛ ዉጊያ አድርጎ የወያኔ ዋና ምሽግ የነበረችውን ደብረ ዘቢጥን መልሶ ያዘ። ወያኔዎች መሸሽ ጀመሩ። ወደ ፊት የወገን ጦር መገስገስ ጀመረ። ኮኪት፣ ፍላቂት፣
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የጦርነት ሁኔታ – ዘገባ ዘገርማ #ግርማካሳ

ወያኔዎች በቀለኛ፣ ዘረኛ በጥላቻ የተሞሉ ናቸው፡፡ ፖለቲካቸው የትግራይን ሕዝብ በመጥቀም ላይ የተመሰረተ ሳይሆን፣ ምን እንዳደረጋቸው ባላውቅም፣ አማራ የሚሉትን ማህበረሰብ በመጥላት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ተጋሩን እንዴት እንጠቅም ሳይሆን አማራን እንዴት እንጉዳ የሚል ነው አጀንዳቸው፡፡ ለዚህ ነው፣ ጎንደር ወሎ በመሄድ፣ ለድሃው የትግራይ ነዋሪ ምንም ባይፈይድም፣ ከአማራ ጋር ሂሳብ እናወራርዳለን ብለው በአማራና በአፋር ክልል ወረራ የፈጸሙት፡፡ 1) ወያኔዎች ጦርነት ሲጀምሩ መጀመሪያ ያሰቡት ነገር የሱዳንን ኮሪዶር መቆጣጠር ነበር፡፡ ከሃያ ጊዜ በላይ፣ ወልቃይትን ለመያዝ ብዙ ሞክረው አልተሳካላቸውም፡፡ በነኮሎኔል ደመቀ ዘዉዱ የሚመራው የወልቃይት ህዝባዊ ሰራዊት ወልቃይትን የወያኔዎች መቀበሪያ ነው ያደረገው፡፡ 2) ሲቀጥሉ አላማቸውን የአማራ ክልልን በማፍረስ ላይ አድርገው፣ በአራት መስመር በተለያዩ ጊዜያት ጎንደር ብለው ባህር ዳር ለመግባት ሞከሩ፡፡ 1ኛ በማይጠምሪ አድርገው በደባርቅ በኩል፣ 2ኛ በአምደወርቅ አድርገው በእብነት በኩል፣ 3ኛ በሰሜን ወሎ መቄት አድርገው በደብረ ታቦር በኩል፣ 4ኛ ከሱዳን ሳምሪ የሚባለውን አሸባሪ ቡድናቸውን በማሰለፍ በመተማ በኩል፡፡ በነዚህ ሁሉ ግንባሮች በጣም ከፍተኛ ሽንፈት የተከናነቡ ሲሆን በመቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ታጣቂዎቻቸውን ገብረዋል፡፡ በጎንደር በኩል ወያኔ አሁን ያለችው፣ በጠለምትና በሰሜን ጎንደር አደርቃይ ወረዳ ላይ ብቻ ነው፡፡ 3) ወያኔ ጎንደርን ትታ ኃይሏን በአንድ አቅጣጫ አድርጋ፣ ከመቶ ሺህ በላይ በከባድ መሳሪያ የታጠቀ ሰራዊት አሰልፉ፣ በደሴ መስመር፣ መስከረም 27 ቀን አዲስ ዉጊያ ከፈተች፡፡ ሁለት ዋና ዋና ግቦችን ሰንቃ፡፡ 1ኛ የጅቡቲ አዲስ አበባን መስመር በመዝጋት አዲስ አበባን ማነቅ ነበር፡፡ 2ኛው ደግሞ በሸዋ አልፎ አዲስ አበባ
Posted in Ethiopian News

ደሴ፣ኮምቦልቻ፣ ሃይቅና ቢስቲማ – #ግርማካሳ

ደሴና ኮምቦልቻ በቅርብ ርቀት ላይ ያሉ ከተሞች ናቸው።ደሴ ተራራ ላይ ከፍ ብላ፣ ሸዋ ሮቢት ደግሞ በቆላው ወረድ ብላ ያሉ ከተሞች። ደሴ ከፍተኛ ዉጊያ ከተደረገና፣ በተለይም በቦሩሜዳ እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሕወሃት ታጣቂዎች ከተቀጠፉ በኋላ፣ አስቀድሞ “ተፈናቃዮች ናቸው” በሚል በደሴ ከተማ የሰረጉ ወያኔዎች፣ የወገንን ጦር ከጀርባ በመውጋታቸው ፣ ያንንም ተከትሎ በተፈጠረው ክፍተት፣ ወያኔ ደሴን መያዟ ይታወሳል። የመሬቱ አቀማመጥ ከላይ ወደ ታች በመሆኑም ኮምቦልቻንም መያዝ አስቸጋሪ አልነበረም። ወያኔዎች ከኦነግ ጋር ጥምረት በመፍጠራቸው፣ ኦነጎች ለሁለት አመታት ያለምንም ችግር ሲንቀሳቀሱበት የነበረውንና በአማራ ክልል ውስጥ የሚገኘው የኦሮሞ ሄረሰብ ዞን : ለወያኔዎች ደጀን ዞን በመሆኑ፣ በሰዓታት ውስጥ ባቲን ይዘው አፋር ድንበር፣ ኬሚሴን ይዘው ሰሜን ሸዋ ድንበር ደረሱ:: ሆኖም ግን በአፋር ግንባሮች ሆነ በስሜን ሸዋ ግንባሮች እንዳሰቡትና እንደጠበቁት እልሄደላቸው:: የጅቡቲ አዲስ አበባን መስመር መያዝም ሆነ ሸገር መግባት አልቻሉም። እንደውም ባለፉት ሁለት ቀናት ከደቡብና ከምእራብ የወገን ጦር ባደረጋቸው እንቅስቃሴዎች ደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ሃይቅና ቢስቲማ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ነጻ ሊወጡ እንደሚችሉ የሚያሳዩ ምልክቶች እያየን ነው። 1ኛ – የወገን ጦር ከሃይቅ ከተማ በስተምስራቅ የምትገኝዋን ቢስቲማ ከተማ ለመያዝ እንቅስቃሴዎች እንደነበሩ ሰምቻለሁ፡፡ እዚያ አካባቢ ኔትዎርክ ብዙ ስለሌለ እንጂ፣ ይሄን ጊዜ ቢስቲማም በወገን ስር ልትሆንም ትችላለች፡፡ ከቢስቲማ ጎን ያለችው የሃይቅ ከተማም የወገን ጦር ገና ያልገባባት ቢሆንም ወያኔዎች ብዙ የማይታይባት ባዶ ከተማ መሆኗን የሚገልጹ መረጃዎች አሉ፡፡ በቢስቲማ ነገሮች ከጠሩ በቀላሉ ሃይቅም ገቢ መደረጓ አይቀሬ
Posted in Ethiopian News

የዉጊያው ሁኔታ – ዘገባ ዘግርማ #ግርማካሳ

የዉጊያው ሁኔታ – ዘገባ ዘግርማ #ግርማካሳ 11/23/2021 ሕወሃቶችና ኦነጎችብዙ ጥፋት ፈጽመዋል። እየፈጸሙም ነው። እነዚህን አሸባሪዎች ማስቆም የአገርን ሕልውና ማsቀጠል ነው። የፖለቲካ አመራሮች እንዋጋለን ብለው መነሳታቸው የግድ ጠምንጃ ይዘው ይተኩሳሉ ማለት አይደለም። ጦርነት መተኮስ ብቻ አይደለም። ትልቁ ነገር የፖለቲካ አመራሪ በዉጊያ አቅራቢያ መሆናቸው አንደኛ ስንቅና ትጥቅ በማቅረብ ዙሪያ፣ ሁለተኛ ውሳኔዎችን በቶሎ በመወሰን ዙሪያ፣ ሶስተኛ በዚያ ለሚዋጋው ሰራዊት ሞራልና ወኔን በመቀስቀስ ዙሪያ እጅግ በጣም ትልቅና ወሳኝ ሚና አለው። በአሁኑ ወቅት ጦርነቶች በበርካታ ግንባሮች እየተካሄዱ ነው። 1. የማይጠምሪ ግንባር 2. የጋሸና ግንባር 3. የዳዉንት ግንባር 4. የወረኢሉ ግንባር 5. የመንዝ ግንባር 6. የሸዋ ሮቢት/ደብረ ሲና ወይንም ይፋት ግንባር 7. የአፋር ካሳጊታ ግንባር 8. የአፋር ቡርቃ ግንባር 9. የአፋር ጭፍራ ግንባር 10. የአፋር /ሸዋ ሮቢት ግንባር 11የዋገመራ ግንባር 12. የራያ ቆቦ ግንባር 13 የሰሜን ወሎ ሃብሮ.ወረባቦ ግንባር ከነዚህ መካከል በመጀመሪያዎቹ አስሩ ፣ በመከላከል ላይ ብቻ ነበር እንቅስቃሴ ሲደረግ የነበረው። በዋገመራ፣ በራያ ቆቦና በስሜን ወሎ ሃብሮ/ወረባቦ ግንባሮች ግን የአማራ ልዩ ኃይሎችም ፋኖዎች ሚሊሺያዎች የሽምቅ ዉጊያዎች እያደረጉ ወያኔ ላይ ከፍተኛ የማጥቃት ዘመቻዎች ሲያደረጉ ነበር። በርካታ የዋገመራ ዞን ወረዳዎች ሰቆጣ ከተማን ጨምሮ በወገን ጦር ቀደም ሲል ነጻ ወጥተዋል። በዞብል ተራራ መደራጀት የጀመሩት የራያ ቆቦ ሚሊሺያዎችም የቆቦ ወረዳ ተቆጣጥረው፣ ወልዲያ ደጃፍ እስከ ጎብዬ ደርሰዋል። ወያኔ በቆቦ በኩል መውጣትና መግባት ካቆመች ሳምንታት አልፈዋል።፡እነ ጀግናው ሃሰን ኪረሙ በሃብሮና ወረባቡ ቆላማው
Posted in Ethiopian News

በርግጥም አገር ለማዳን፣ መንግስት ለመሆን ከተነሱ ሊደገፉ ይገባል – ግርማ ካሳ

“በመከላከል ላይ ብቻ የሚደረግ እንቅስቃሴ ውጤት አያመጣም፣ የማጥቃት ዘመቻ ይጀመር፣ በዓለ ሲመት ምጥርቅሾ እያላችሁ አትቀልዱ፣ ፋኖዎችና ሊዋጉ የመጡትን አስታጥቁ ..።” እያለን ስንጨቃጨቅና ስንሞግት ነበር፡፡ ኮረም፣ አላማጣ፣ ዋጃ፣ ሮቢት፣ ጎብዬ፣ ወልዲያ፣ መርሳ፣ ሁርጌሳ፣ ዉጫሌ : ሃይቅ፣ ደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ሃብሮ፣ ኬሚሴ፣ ካራቆሬ፣ አጣዬ፣ ሰንበቴ፣ ሸዋ ሮቢት ብለው ደብረ ሲና ደጃፍ እስኪደርስ መጠበቅ አልነበረበትም፡፡ እዚህ የዘረዘርኳቸው ከተሞችና የሌሎች የሰሜንና ደቡብ ወሎ፣ የሰሜን ጎንደር፣ የስሜን ሸዋ፣ የዋገመራ፣ የአፋር ወረዳዎች መያዝ፣ በዚያ ያለው የሕዝብ ስቃይና ሰቆቃ ተሰምቷቸው ጦርነቱን ዋናና ትልቁ አጀንዳቸው ማድረግ ነበረባችው፡፡ ለ4 ወራት ያንን ሳያደርጉ ቆይተው ነበር፡፡ ከዚህም የተነሳ እጅግ በጣም ትልቅ ዋጋ ተከፍሏል፡፡ አሁን ወያኔዎች ሸዋሮቢትን ይዘው ደብረ ሲና ደጃፍ ሲደርሱ ፣ ለአዲስ አበባ እየቀረቡ ስለሆነ፣ የፖለቲካ አመራሮች ከእንቅልፋቸው ነቀተዋል፡፡ በመጨረሻ፡፡ ከጠቅላይ ሚኒስተሩ ጀምሮ፣ በተለያዩ ግንባሮች በመሰማራት በሕወሃትና ኦነግ የተደቀነው የአገር ህልውና አደጋ ለመመከትና ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለጉዳዩ እልባት ለመስጠት ተዘጋጅተናል ብለዋል፡፡ የረፈደም ቢሆን እጅግ በጣም ትልቅና ወሳኝ ውሳኔ ነው፡፡ ወደ ኋላ ሳይሆን ወደፊት ነው ማየት ያለብን፡፡ የአገርንና የሕዝብን ጥቅም ማስቀደም አለብን፡፡ ከብልጽግና የፖለቲካ አመራር ጋር መሰረታዊ ልዩነቶች ቢኖረዉም፣ ግርማ ካሳ፣ በዚህ ወቅት እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ሙሉ ለሙሉ ከጎናቸው ይቆማል፡፡ ማድረግ የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነው፡፡ አሁን የሚደረገው ትግል በብልጽግናና በወያኔ/ኦነግ መካከል አይደለም፣ ከሕዝብ ጋር የሚደረግ ትግል ነው፡፡ በዚህ ወቅት ዶር አብይ አህመድ፣ የተመረጠ ነው የምንልና በነጻና ፍታሃዊ ምርጫ አልተመረጠም የምንል ፣
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የመጋረጃ ጀርባና የዉሸት ምስክርነት በ”አዲሱ ምዕራፍ” ይቀጠል ይሆን ? #ግርማካሳ

የባልደራስ አመራር አባላት፣ እስክንድር ነጋ፣ ስንታየሁ ቸኮል፣ አስቴር ስዩም፣ አስካለ ደምሌና ሌሎች ይኸው ከታሰሩ አንድ አመት ከአራት ወር ሊሆናቸው ነው፡፡ የታሰሩት “ሳናጣራ አናስራም” ባሉት የዶር አብይ አህመድ የብልጽግና መንግስት ነው፡፡ ከብዙ መንገላታትና መጉላላት በኋላ የኦህዴድ/ብልጽግና አቃቤ ሕግ ጳጉሜን 5 ቀን 2012 ዓ/ም አስራ ሶስት ገጽ ያለበት፣ ከአንድ አገር አቃቤ ሕግ የማይጠበቅ እጅግ በጣም የወረደ፣ ክስ መሰረተ፡፡ ( እዚህ ጋር የኦህዴድ አቃቤ ሕግ የምለው የአቃቤ ሕግ ጽ/ቤት ለአገር ጥቅም፣ ለፍትህ መስፈን ሳይሆን ለኦህዴድ/ኦሮሞ ብልጽግና የሚሰራ ነው ብዬ ስለማምን ነው) ክሱ ሁለት ክሶችን ያካተተ ነው። በአንደኛው ክስ እስክንድር ነጋ፣ ስንታየሁ ቸኮል፣ አስቴር ስዩም ፣ አስካለ ደምሌ ተካተዉበታል። ከ”ሽብርተኝነት” ጋር በተገናኘ የቀረበው 2ኛ ክስ ደግሞ እስክንድር ነጋንና ሌሎች የማይታወቁ፣ ያልተያዙ ሁለት ተከሳሾችን ያካተተ ነው። የመጀመሪያው ክስ በሁለት የሚከፈል ነው። አንደኛው ክፍል ከሃጫሉ ግድያ በፊት ተፈጸሙ የተባሉትን ያካተተ ሲሆን፣ ሁለተኛ ክፍል ከሃጫሉ ግድያ በኋላ ተፈጸመ ያሉትን ያካተተ ነው። ሁለተኛ ክስ የሽብርተኝነት ክስ ነው በክሱ ምንም አይነት የሰነድ፣ የፎረንሲክ፣ እንደ ኦዲዮ፣ ቪዲዮ ኤሜል፣ የፌስ ቡክና የትዊተር ፖስቶች የመሳሰሉ የኤሌክቶሮኒክስ መረጃዎች አልቀረቡም፡፡ ኢንሳ የነ እስክንድር ስልክ እየጠለፈ እንደሚሰማ የሚታወቅ ነው፡፡ እንደ ማስረጃ የተጠለፈ ንግግር እንኳን አልቀረበም፡፡ “ምክንያቱ ምንድን ነው ?” ቢባል መልሱ ቀላል፡፡ ምንም አይነት የከሰሱበትን ክስ የሚያረጋግጥ ማስረጃ ባለማግኘታቸው ነው፡፡ ጳጉሜን 5 ቀን 2012 ዓ/ም ክስ እስኪመሰረትባቸው ጊዜ የባልደራስ አመራሮች በርካታ ጊዜ ፍርድ ቤት ተመላልሰዋል፡፡
Posted in Ethiopian News

አብሮ መስራት ሽርፍራፊ ስልጣን መጋራት አይደለም – ተክሌ በቀለ የኢዜማ ከፍተኛ አመር

አቶ ተክሌ በቀለ የኢዜማ የስራ አስፈጻሚ አባልና በድርጅቱ ውስጥ ከፍተኛ ተሰሚነት ካላቸው አመራሮች መካከል አንዱ ናቸው። ገዢው ፓርቲ ብልጽግና  ስልጣን ከተቃዋሚዎች ጋር እጋራለሁ በሚል ለአንዳንድ የተወሰኑ ሃላፊነቶች አንዳንድ የተቃዋሚ አመራሮች እየሾመ መሆኑ ይታወቃል። እንደምሳሌም አቶ ግርማ ሰይፉ ሌላ የኢዜማ አመራር በአዲስ አበባ መስተዳደር ካቢኔ ውስጥ ፣ ከአቡ አቶ ዩሲፍ ኢብራሂም ጋር ስማቸው እንዲካተት ተደርጓል። ይሆነ በተመለተ አቶ ተክሌ “አብሮ መስራት ሽርፍራፊ ስልጣን መጋራት አይደለም” ሲሉ ተቃዋሚዎች ለ እውነተኛ ለውጥ እንዲሰሩ አሳስበዋል።  “ሽርፍራፊ ስልጣን ለግለሰብ ኢጎ እና ጥቅማጥቅም እንደሆነ እንጂ ለህዝብ የተለየ አማራጭ ሃሳብ እንዲያገኝ አያደርግም” በማለት  አስተያየት አቅርበዋል። የአቶ ተክሌ ሙሉ አስተያየትን እንደሚከተለውን ቀርቧል ======================== አንዳንድ ወገኖች በተመሰረቱ የክልል ምክር ቤቶች እና እየተመሰረተ ባለው የፌደራሉ መንግስት የስልጣን አሰጣጥን ጨምሮ አንዳንድ ጉዳዮች እያነሱ የተለያየ ሃሳብ ሲሰጡ ይሰማል/ይነበባል ፡፡ እንደብዙው ሰው እኔም የመንግስት ምስረታ ላይ የምጠብቀው አዲስ ነገር የለም ፡፡ ወሳኝ ሰዎቹ በአባዛኛዎቹ እነሱው ናቸው ፡፡ ምናልባትም ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ በስተቀር ሌላው ሃሳብም ሆነ አሰራር ያው የድሮው ህወሓት/ኢህአዴግ ነው ፡፡ መሆን የሚችለው እና መሆን ያለበት ነው እየሆነ ያለው ፡፡ ይሁን እንጂ ለሃገር መረጋጋት ሲባል የሚመሰረተው መንግስት ነገሮችን በእርጋታ እሚያይበት ምቹ ግዜ እንዲኖረው እመኛለሁ ፡፡ ሃገር የሚረጋጋው ግን ፤ መዋቅራዊ ችግራችንን ( ህገ መንግስቱን-የዚህን ሰነድ መሻሻል ተከትሎ ለሚመጡ መሻሻሎች) ለማሻሻል ስምምነት ላይ ስንደርስ እና ስራው ሲጀመር የሊሂቃን ( የሃገራችን የፖለቲካው በሽታ አምጪ ዋና ተስህቦዎች
Posted in Ethiopian News

የአዋሳን ህዝብ ያገለለ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ስብሰባ

የሲዳማ ክልል ም/ቤት ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደን አፈ-ጉባዔ አድርጎ የመረጠ ሲሆን፣  አቶ ደስታን የክልሉ ር እስ መስተዳደር  አደርጎ መርጧል። የሲዳማ ምክር ቤት ስብሰባ የተደረገው በአዋሳ ከተማ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ በሲዳሚኛ ቋንቋ ነበር። ክልሉ በተለይም የአዋሳ ከተማ አብዛኛው ሲዳምኛ የማይናገር ፣ በዋናነት አማርኛ ተናጋሪ ማህበረሰብ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ግን አዲስ የሲዳማ ክልል  ከጅምሩ በዘር ላይ የተመሰረተና የሌሎች ማህበረሰባት ጥቅምና እኩልነት ለማረጋገጥ ያልተዘጋጀ መሆኑን አመላካች ነው።፡  
Posted in Ethiopian News

አገር ወደ በለጠ ጥፋት እየሄደች ነው፣ የመስቀሉ ጌታ ከዚያ ያውጣን #ግርማካሳ

ዛሬ መስከረም 17 2014 ዓ/ም ምህረት ነው። የመስቀል በዓል። እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። ይሄን በዓል ማክበር ላልቻሉ በተፈጥሮ ችግር ፣ በጎርፍ ፣ በኮሮና እንዲሁም በሰው ሰራሽ ሰይጣናዊ የዘር ተኮርና የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ፍጅት፣ ሰው ሰራሽ የኋላ ቀር ጦርነት በመሳሰሉት ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖችን ነፍስ ይማርልን። እናት፣ አባት፣ ልጅ፣ ሚስት፣ ባል፣ አያት፣ ጓደኛ ላጡት፣ ላጣነው መጽናናቱን ይስጠልን። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ከቅያቸው ለተፈናቀሉ፣ በችግር በመከራና በረሃብ ውስጥ ያሉ ወገኖችን እግዚአብሄር ያስባቸው። “መስቀልከ ለእለ አመነ ፣ ብርሃነ ከፈኑ ዲቤነ” ይላል የያሬዳዊ ግእዝ ዜማ። “መስቀልህን ለምናምን ለኛ ፣ ብርሃንህን ከሰማይ ላክልን” ነው ትርጓሜው ባልሳሳት። አገራችን ኢትዮጵያ ጨለማ ውስጥ ነው ያለችው። በእገሪቱ ካሉ አስር ክልሎች በአምስቱ በትግራይ፣ በአማራ: በኦሮሚያ፣ በቤኔሽንጉልና በአፋር ክልሎች ጦርነት አለ። የሰብአዊ ቀውሱ ከቁጥጥር በላይ ሆናል። በጣም አክረናል። ተማሩ በሳል ትልቅ ሰው የሚባሉ ሳይቀሩ እንደ ሕፃን ማሰብ ጀምረዋል። ስለሰላም ስለእርቅ መናገር እንደ ወንጀልና እንደ ጥፋት እየታየ ነው። ዜጎች ያለ ጥፋታቸው በውሽት ክስ ታስረው ይንገላታሉ። ህግ የለም። ለህግና ለፍትህ የቆሙ ዳኞች የሉም። በስንት መከራ ትንሽ ከተገኙም እነርሱ የሚወሰኑት ውሳኔ አይከበርም። “ስልጣን ለምን አጣን” ተብሎ “ሂሳብ እናወራርዳንለ” በሚል በህዝብ ላይ ጦርነት ይከፈታል። በብዙ ሺህ ወጣቶች ሕይወታቸው እንደ ቅጠል እየረገፈ ነው። ሴት ልጆች በጭካኔና በአውሬነት መንፈስ ይደፈራሉ። የገበሬዎች ከብቶች ሳይቀሩ በክፋት ይገደላሉ። በንብረት ላይ ሆን ተብሎ ውድመት ይፈጸማል። ጥላቻው፣ ክፋቱና ዘረኝነቱ ተቆጣጥሮን እግዚአብሄር የሰጠንን
Posted in Ethiopian News

እነ ሺመልስ አብዲሳ ተመረጡ፣ አፓርታይድ ይቀጥላል #ግርማካሳ

ላለፉት 3 አመታት በኦሮሞ ክልል የነበረውንና አሁንም ያለውን አሳዛኝ ሁኔታ ሁላችንም የምናውቀው ነው። እንደዚያም ሆኖ ግን በርካታ ወገኖች የዶር አብይ አህመድ የብልጽግና መንግስት ላይ ተስፋ እንዳላቸው ሳይ በጣም ይገርመኝ ነበር። “ግድ የለም ከምርጫው በኋላ መንግስት ሲመሰረት ለውጦች ይመጣሉ” እያሉ። በኦሮሞ ክልል ምክር ቤት ጨፌ ከ500 በላይ የክልሉ ምክር ቤት ተወካዮች አሉ። ለነዚህ ተወካዮች ምክር ቤት ተደረገ በተባለው ምርጫ በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በሚመራው ምርጫ ቦርድ ፣ ኦህዴድ በኋላ ኦዴፓ የነበረው የኦሮሞ ብልጽግና ወይንም በዳዲና ፣ መቶ በመቶ አሸናፊ እንደሆነ ተገልጽዋል። ከ99% በላይ ወረዳዎች በዳዲና/ብልጽግና ብቻውን ነው የተወዳደረው። በተቀሩት 10% ደግሞ ሌሎች፣ ለመወዳደር እጩ ያቀረቡ ቢኖሩም፣ የመቀስቀስ ሆነ ለምርጫ የሚያስፈልጉ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ለማድረግ አልቻሉም። በአጭሩ እነጋገር ከተባለ፣ የኦሮሞ ክልል ማህበረሰብ ምርጫ አንዲቀርብለት አልተደረገም። “እኛ ነን የምንመርጥልህ ” ተብሎ አንድ አማራጭ ብቻ እንዲሰጠው ነው የተደረገው። ከፖለቲካ አላማቸው ጋር ባንስማም ቀላል የማይባሉ ዜጎች የሚደግፏቸው በአቶ ዳዎድ ኢብሳም ሆነም በአራርሶ ቢቀላም የሚመሩት ኦነጎች ፣ በዶር መራራ ጉዲና የሚመራው ኦፌኮ በምርጫው አልተሳተፉም ወይም እንዳይሳተፉ ተደርጓል። እንደ ኢዜማ ያሉ እጩዎቻቸው ተገድለዉባቸዋል። በኦሮሞ ብልጽግናዎች አፈና ለደህንነታቸው ከመስጋታቸው የተነሳ ከ125 በላይ ወረዳዎች እጪዎች ማቅረብ አልቻሉም።፡ ባቀረቧቸውም ወደ 50 የሚሆኑ ወረዳዎች መቀስቀስ አልቻሉም። እንደዚያም ሆኖ፣ ብዙዎች ብልጽግና አጭበርብሮና አፍኖ ስልጣን ቢይዝም ፣ ላለፉት 3 አመታት በኦሮሞ ክልል የነበረውንና አሁንም ያለውን አሳዛኝ ሁኔታ ይሻሻል ዘንድ፣ ብዙዎች መንግስት ሲመሰርት መሰረታዊ ለውጦች ያመጣል
Posted in Ethiopian News