ትራምፕ የሕዳሴውን ግድብ ምርቃት ሪቫን የመቁረጥ ሕልም አላቸው ሲሉ የኢትዮጵያ ልዑክ ገለጹ

በውጭ ጉዳይ ሚ/ር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተመራው የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በአሜሪካን የገንዘብ ሚንስትር ጋባዥነት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ሲያካሄድ የነበረውን ውይይት አጠናቀቀ::

የውይይቱን መጠናቀቅ አስመልክተው ሚንስትሩ  ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል::

በመግልጫቸውም ውይይቱ:-
1) የኢትዮጵያን ፍትሃዊ አቋም ለማስረዳት አመቺ ሁኔታ በመፍጠሩ:

2) የተጏተተውን የቴክኒክ ውይይት በተፋጠነ ሁኔታ ለማስቀጠል ከስምምነት በመደረሱ

ስኬታማ እንደነበር ገልጸዋል::

አያይዘውም:-

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ በቦታው በመገኘት ሪቫን አብረው በመቁረጥ ለመመረቅ ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን ጠቁመዋል::