Blog Archives

በአዲስ አበባ ስራ በመስሪያ እድሜያቸው ላይ ከሚገኙ 100 ሰዎች 18ቱ ስራ አጥ ናቸው ተባለ፡፡

በአዲስ አበባ ስራ በመስሪያ እድሜያቸው ላይ ከሚገኙ 100 ሰዎች 18ቱ ስራ አጥ ናቸው ተባለ፡፡ በየጊዜው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስራ ፈላጊ ወደ ከተማዋ ይገባል፡፡ የከተማዋ ስራ ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ለስራ አጦቹ ምን እየሰራ ነው (  sheger FM )
Posted in Amharic News, Funny

በጦርነቱ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብን እያለ ወደ ሌላ ጦርነት መገባቱ እንደ ሀገር የለየለት እብደት ነው

የፌዴራል መንግሥት እና ትግራይን እየመራ የሚገኘው ሕወሓት ለአምስት ወራት ግድም ቆሞ የነበረው የሰብዓዊ ተኩስ አቁም መጣሱን በተመለከተ አንዳቸው ሌላኛቸውን እየከሰሱ ነው። ስለ ጦርነቱ አስተያየታቸውን ለዶቼ ቬለ የሰጡ ሰዎች ፣ የጦርነቱ ዳግም መጀመር ድንጋጤ ፈጥሮብናል ብለዋል።”ሕዝቡ ትኩረቱ የሰላም ድርድሩ ላይ ነበር። ግን ይህ አለመሆኑ ጥሩ ዜና አይደለም” ያሉ የመኖራቸውን ያህል “በጦርነቱ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብን እያለ ወደ ሌላ ጦርነት መገባቱ እንደ ሀገር የለየለት እብደት ነው” ሲሉ ሁኔታው የፈጠረባቸውን ስሜት አጋርተውናል። በሌላ በኩል የጦርነቱ ሰለባ መሆኑን የገለፀ አንድ ሰው “በየጊዜው ትውልድ መገበር?” በማለት ይጠይቃሉ። አስተያየት ሰጭዎቹ “ጦርነት በቃ ሊባል ይገባል። ሕዝቡም በመሪዎች ላይ ጫና ሊያሳድር ይገባል” የሚል ሀሳባቸውን ገልፀዋል። https://radiodownloaddw-a.akamaihd.net/downloads/Events/dwelle/dira/mp3/amh/383ECE56_2.mp3
Posted in Amharic News, Funny

ለሰላም ድርድሩ ‹‹ከአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ውጭ ሌላው ተቀባይነት የለውም›› የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ለሰላም ድርድሩ ‹‹ከአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ውጭ ሌላው ተቀባይነት የለውም›› የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነትና ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተጀመረው የአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ብቸኛ አማራጭ በመሆኑን ከዚህ ውጭ የሚደረግ ሌላው ጥረት ተቀባይነት እንደሌለው መንግሥት አስታወቀ፡፡ መንግሥት የተጀመረውን የሰላም ድርድር በፖለቲዊ መፍትሔ እንዲፈታ ቁርጠኛ አቋም እንዳለው፣ የውጭ ጉዳይ… https://www.ethiopianreporter.com/109444/
Posted in Amharic News, Funny

የፓርላማ አባላት በትራንስፖርት ዘርፍ የሚስተዋለው የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቅሬታቸውን አሰሙ

የፓርላማ አባላት በትራንስፖርት ዘርፍ የሚስተዋለው የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቅሬታቸውን አሰሙ የፓርላማ አባላቱ የትራንስፖርት ዘርፉ ችግሩ እንዲፈታ የጠየቁት፣ ግንቦት 18 ቀን 2014 ዓ.ም. የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን የ2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ አሥር ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በገመገሙበት ወቅት ነው፡፡ – https://ethiopianreporter.com/article/25624
Posted in Amharic News, Funny

”ሴቶች የጥቃት፣ የመደፈር ኢላማ መሆን ጨርሶ የለባቸውም! ከመፈክር ባለፈ ከሥር መሠረቱ እንሥራበት፡፡”ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ

”ሴቶች የጥቃት፣ የመደፈር ኢላማ መሆን ጨርሶ የለባቸውም! ከመፈክር ባለፈ ከሥር መሠረቱ እንሥራበት፡፡”ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ማክሰኞ የካቲት 29 ቀን 2014 (አዲስ ማለዳ) ሴቶች የጥቃት፣ የመደፈር ኢላማ መሆን ጨርሶ የለባቸውም! ከመፈክር ባለፈ ከሥር መሠረቱ እንሥራበት ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዚደንት ሣህለወርቅ ዘውዴ አሳሰቡ፡፡ የኢፌዴሪ ፕሬዚደንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ዓለም ዓቀፉን የሴቶች ቀን (ማርች 8) በተመለከት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የመልዕክቱ ሙሉቃል እንደሚከተለው ቀርቧል:- ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ኘሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ያስተላለፉት መልዕክት የካቲት 29 ቀን 2014 እንኳን ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በደህና አደረሰን! ይህ ቀን በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀ መሪ ቃል እንደየአገሩ ሁኔታ በመላው ዓለም ይከበራል፡፡ ባለፉት ዓመታት በአገራችን የሴቶች እኩልነት፣ የመብታቸው መከበር፣ የንቃተ ሕሊና ማሳደግ፣ ለሃላፊነት መብቃትን … ወዘተ በተመለከተ የማይናቅ ዕድገት ተመዝግቧል፡፡ የሴቶች ምኞት ገደብ ሊኖረው እንደማይችል አሳይቷል፡፡ የተሻለ ተስፋ እንዲኖራቸው ረድቷል፡፡ በርትተን የምንቀጥልበት ነው፡፡ በአንጻሩ ደግሞ ባለፉት 15 ወራት የተካሄደው ጦርነት፣ በተከታታይ የተከሰቱት የተፈጥሮ አደጋዎች ሰቆቃ ተቀባይ የሆኑት፣ ልጆቻቸውን ይዘው የተሻለ ደህንነት፣ የሚበሉት የሚጠጡትን ለማግኘት የተሰደዱት፣ የተፈናቀሉት፣ የተደፈሩት …. ሴቶች ናቸው፡፡ በመቀሌ መጠለያ ጣቢያ ያገኘኋት “ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን ሁለት ወንድ ልጆቼን አጣሁ”ያለችኝ፣ በደሴ የተጠለለችው የደረሰች ነፍሰ ጡር፣ በርካታ ኪሎ ሜትር ተጉዛ “ልጆቼን ምን ላድርጋቸው?” ያለችኝ እናት፣ በተለያዩ ቦታዎች የተደፈሩ ሴቶች የደረሰባቸው ቃላት የማይገልጹት ሰቆቃ፣ በሆስፒታል በመታከም ላይ የሚገኙት፣ በሱማሌ ክልል ድርቅን ለመቋቋም የተፈናቀሉት ሴቶችና ልጆች፣ በአፋር ክልል በጦርነት የተጎዱ ሕጻናት፣ ቤተሰባቸውን ትተው
Posted in Amharic News, Funny

በአየር መንገዳችን የጭነት ማእከል ውስጥ በአይነቱ ልዩና አዲስ የሆነ የኢ-ኮሜርስ መጋዘን እየገነባን ነው። – አቶ ተወልደ ገ/ማርያም

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የአፍሪካ ኢ-ኮሜርስ ማዕከል ለመሆን የሚያስችለውን የጭነት /cargo/ ኢንቨስትመንት በላቀ ደረጃ በማሳደግ ላይ ይገኛል። – አቶ ተወልደ ገብረማርያም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ከብሉምበርግ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በሰጡት አስተያየት “እኛ አሁን በአየር መንገዳችን የጭነት ማእከል /cargo terminal/ ውስጥ በአይነቱ ልዩና አዲስ የሆነ የኢ-ኮሜርስ መጋዘን እየገነባን ነው። አየር መንገዳችን በአፍሪካ ግዙፉ የጭነት አመላላሽ እንደመሆኑ መጠን አምስት የቦይንግ ካምፓኒ ስሪት የሆኑ B777 የእቃ ጫኝ አውሮፕላኖችን አስገብተን ለመጠቀም አስበናል። ከዚህም በተጨማሪ በምርት ሂደት ላይ የሚገኘውን የኤርባስ SE A350s አውሮፕላን ለማስገባት በማጤን ላይ ነን።” ብለዋል። – ሙሉ መረጃውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን /ሊንኩን/ ይጫኑ፤ https://www.bloomberg.com/news/articles/2022-01-22/ethiopian-ramps-up-cargo-investment-for-african-e-commerce-hub  
Posted in Amharic News, Funny

ኦላፍ ሾልስ የጀርመን መራኄ መንግሥት ሆነው ተመረጡ።

ኦላፍ ሾልስ የጀርመን መራኄ መንግሥት ሆነው ተመረጡ። የ63 ዓመቱ ሾልስ በፖለቲካ አቋማቸው ሶሻል ዴሞክራት ናቸው። በምርጫው ከፍተኛ ድምፅ ካገኙት ከአረንጓዴ ፓርቲ እና ከነጻ ዴሞክራቶች ፓርቲዎች ጋር በመቀናጀት ሀገራቸውን ለመምራት ተስማምተዋል። Germany has a new government. Chancellor @OlafScholz got elected by the Parliament @Bundestag this morning. The team of Ministers around him is complete, half of them are women. Many firsts, including the ruling 3-party-coalition of Social-Democrats, Greens, Liberals. 🔴🟢🟡 pic.twitter.com/70KcQY9FvE — German Mission to UN 🧡 (@GermanyUN) December 8, 2021 ሾልስ ዛሬ በጀርመን ምክር ቤት በተካሄደው ምሥጢራዊ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ከ707 አባላት የ395ቱን በማግኘት ኦላፍ ሾልስ አዲሱ የጀርመን መሪ ሆነው ተመርጠዋል። እንዲያም ሆኖ የተጣማሪ ፓርቲዎቹን አባላት ሙሉ ድምፅ አላገኙም። በምርጫው ሂደት 303 አባላት ተቃውመዋል፤ ስድስት የምክር ቤት አባላት ደግሞ ድምፅ አልሰጡም። ከድምፅ አሰጣጡ ሥርዓት በኋላ ወደ ፕሬዝደንቱ መኖሪያ በመሄድ የሹመት ደብዳቤያቸውን ተቀብለዋል። ዛሬ ከፕሬዝደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር የመራኄ መንግሥትነት ሥልጣናቸውን የተቀበሉት ሾልስ ወደ ምክር ቤት በመሄድ ቃለመሃላ ፈጽመዋል። የካቢኔ አባሎቻቸውን በማቅረብም አዲስ ሚኒስትሮቻቸውን በይፋ ሰይመዋል።  
Posted in Amharic News, Funny

ጋብቻ ጎዶሎ መሙያ ሳይሆን የህይወት አላማን ለማሳካት የአብሮነት ጉዞ ነው

ለምን ላግባ? በአናናስ ግርማይ ጋብቻ በማህበረሰብ ጥናት መዝገበ ቃላት ላይ እንደተቀመጠው ለዓቅመ አዳም በደረሱ አንድ ወንድና ሴት መካከል የሚደረግ ጋብቻና የራሱ የሆነ ህግና ግዴታዎች ያሉት ነው ይልና፣ ነገር ግን አሁን ዘመናዊ አስተሳሰብ ባለው ህብረተሰብ (Contemporary society) ውስጥ ደግሞ ትዳር ወይም ጋብቻ ነፃ አስተሳሰብ (Liberal) እየሆነ በመምጣቱ አብሮ መኖር (Cohbitation) እየተመረጠ መሄዱን ያስቀምጣል፡፡ በሃገራችን የቀደመ ታሪክ ጋብቻ በሁለቱ ተጋቢዎች ፍላጎት ተመርኩዞ የሚደረግ እንዳልነበረ ይታወቃል፡፡ ለምሳሌ ሁለት የሚዋደዱ ሰዎች የበለጠ ቅርበታቸውን ለማጠናከር ልጅህን ለልጄ በማለት ልጆች ገና ሳይፀነሱ ይሰጣጡ እንደነበርና በተጨማሪም በሁለት ማኅበረሰብ ውስጥ ትስሰር ለመፍጠር ወይም የተጣሉ ማኅበረሰቦችን ለማቀራረብና እርቅ እንዲፈጠር ልጆቻቸውን በማጋባት ኅብረት ያደርጉ ነበር፡፡ ኾኖም ግን በአሁኑ ጊዜ ሕፃናት 18 ዓመት ሳይሞላቸው ጋብቻ እዳይፈፅሙ በመደረጉ ባህላዊ ጋብቻ እየቀነሰ መጥቷል፡፡ እዚህ ላይ ለመጥቀስ የፈለግሁት በሃገራችን ብዙውን ጊዜ ማኅበራዊ፤ ሃይማኖታዊ፣ ኢኮኖሚያዊ አንዳንዴም ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት የተጋቢዎችን ፍላጎት ሳያጤን በቤተሰብ፤ በጎረቤት በዘመድ አዝማድ ፍላጎትና ህልም ላይ ተመስርቶ ጋብቻ እንደሚፈጸም ነው። ታድያ አንባቢያን ልብ እንድትሉ የምፈልገው በእርግጥም በእድሜ የበሰሉ ስለ አጠቃለይ ቤተሰብ፤ አካባበቢ እና የማኅበረሰብ ሁኔታ ትልቅ ግንዛቤ ያላቸው ሰዎች ለተጋቢዎች እሰፈላጊውን ምክርና ድጋፍ ማድረጋቸው፣ በጣም ጠቃሚና ወደፊትም መቀጠል ያለበት ነገር ቢሆንም፣ በጋብቻ ስም በሁለቱ ተጋቢዎች ህይወት ላይ ሁሉም እጁን እያስገባ ጋበቻ ወደ አልተፈለገ መጠላለፍ እንዳይገባ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ለማለት ነው፡፡ ምክንያቱም በአሁኑ ጊዜ ተጋቢዎች በጥሩ ሀኔታ አስበውበትና አቅደው ጋብቻ ስለማይፈፅሙ
Posted in Amharic News, Funny

በህወሓት ስር የምትገኘዉ ላሊበላ ነዋሪዎቿ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።

በህወሓት ስር የምትገኘዉ የላሊበላ ወቅታዊ ሁኔታ DW ፡ በዓለም የቅርስ የተያዙ አብያተ ክርስትያናት የሚገኙባት ላሊበላ ከተማ በህወሓት እጅ ሥር የገባችዉ ሐምሌ 29 እለተ ሃሙስ ቀትር ላይ ነበር። ላሊበላ ወደ 700 ካህናቶች ይገኛሉ፤ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ። የላሊበላ ችግር የጀመረዉ ህወሓት ከገባ በኋላ ሳይሆን ኮሮና በዓለማችን ከተስፋፋ ወዲህ ጀምሮ ነዉ። አሁን ግን ችግሩ ተባብሶአል። ወጣቱ ወደ ባህርዳር እየተሰደደ ነዉ የዓለም ቅርስ ሆነው የተመዘገቡ የአስደናቂ ውቅር አብያተ ክርስትያናት ባለቤት የሆነችው ላሊበላ ከተማ እንዴት ከረመች ? በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ በህወሓት ታጣቂ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር እንደገባች የተነገረው ላሊበላ ከተማ፣ ሕዝቧ እና ቅርሶቿ አሁን በምን ሁኔታ ይገኛሉ ? ከሁለት ቀናት በፊት ከተማዋን ለቅቆ የወጣ አንድ ወጣትን አነጋግረናል። https://radiodownloaddw-a.akamaihd.net/downloads/Events/dwelle/dira/mp3/amh/E021F8AC_2.mp3
Posted in Amharic News, Funny

ወደ ደብረ ታቦር ከባድ መሳሪያ ተወርውሮ እንደነበር ተሰምቷል

ዛሬ ወደ ደብረ ታቦር ከባድ መሳሪያ ተወርውሮ እንደነበር ተሰምቷል። የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ቀለመወርቅ ምህረቴ ዛሬ ወደከተማዋ የተወረወሩት የከባድ መሳሪያዎችን አስመልክቶ ፤ “ከባድ መሳሪያዎቹ ጠላት ያለ የሌለ አቅሙን ተጠቅሞ ደብረታቦርን የማጥፋት ከፍተኛ ፍላጎት ማሳያ ነው” ሲሉ ገልጸውታል። ዋና አስተዳዳሪው ፤ “ጠላት እየተመታ እግሬ አውጭኝ ብሎ እየፈረጠጠ ስለሆነ እንረጋጋ፤ አሁን ከወረወረው ውጭ ወደ ከተማችን ለመወርወር እንዳይችል እየተቀጠቀጠ ነው” ሲሉ አክለዋል። በሌላ በኩል የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህወሓት ቡድን አባላት ሰርገው በገቡበት የጋሸና አካባቢ ሽንፈትን ተከናንበው ተደምስሰዋል ሲል አሳውቋል። የሀገር መከላከያ የደቡብ ዕዝና ሌሎች የፀጥታ አካላት ባደረጉት ፈጣን ኦፕሬሽን ድል መገኘቱ ተገልጿል። ከ4 የሰሜን ወሎ ወረዳዎች ህወሓት ተጠራርጎ እንደወጣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።
Posted in Amharic News, Funny

ትግራይ የሚገኙ ሲቪሎች ከነጭ ፎስፈረስ ጋር ተመሳሳይ የሆነ አሰቃቂ የቃጠሎ አደጋ ደርሶባቸዋል – ቴሌግራፍ

Exclusive: Ethiopians suffer horrific burns in suspected white phosphorus attacks Weapons experts said images obtained by the Telegraph show injuries consistent with the chemical የቴሌግራፍ ሪፖርትና የመንግስት ምላሽ : ‘ቴሌግራፍ’ ጋዜጣ ባወጣው ሪፖርት በሰሜን ኢትዮጵያ (ትግራይ) የሚገኙ ሲቪሎች ከ ‘ነጭ ፎስፈረስ’ ጋር ተመሳሳይ የሆነ አሰቃቂ የቃጠሎ አደጋ ደርሶባቸዋል፥ይህም የጦር ወንጀል ሊሆን ይችላል ብሏል። Civilians in northern Ethiopia have suffered horrific burns consistent with the use of white phosphorus, a potential war crime, the Telegraph can disclose. Exclusive footage and accounts of witnesses and victims smuggled out of the war in Tigray suggests the Ethiopian and Eritrean armies may have used powerful incendiary weapons in civilian areas. Leading chemical weapons experts said the footage is consistent with white phosphorus, which is banned from use against human targets under international law.  ቴሌግራፍ ጋዜጣ ከትግራይ ተገኙ ባላቸው ምስክሮችን፣ ተጎጂዎች እና ልዩ ምስሎች የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጦር በሲቪል አከባቢዎች ኃይለኛ የሆነና በከፍተኛ ሁኔታ የሚነድ መሳሪያ ተጠቅመው ሊሆን ይችላል ሲል ገልጿል። አናገርኳቸው ያላቸው የኬሚካል የጦር መሣሪያ ባለሞያዎች ከትግራይ ተቀረፀው የወጡህ ምስሎች በዓለም አቀፍ ሕግ በሰው ዒላማዎች ላይ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ከሚከለከለው ከ ‘ነጭ ፎስፈረስ’ ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነው ስለማለታቸው አስነብቧል። ከተጎጂዎቹ መካከል በማዕከላዊ ትግራይ የ ‘አዲአይቆሮ’ መንደር ነዋሪ የሆነች የ13 ዓመት ታዳጊ ኪሳነት ገብረሚካኤል የምትገኝበት
Posted in Amharic News, Funny

በኢትዮጵያ የኮቪድ ክትባት የሚሰጠው ለማን ነው ? ለመንግስት ኃላፊዎች ለጤና ባለሙያዎች ወይንስ … ?

“ክትባቱ በመጀመርያ የሚሰጠው ለመንግስት ሀላፊዎች ነው”— ካፒታል ጋዜጣ “የጤና ባለሙያዎች እና እድሜያቸው ከ65 በላይ የሆኑ ግለሰቦች በቅድሚያ ክትባቱን ያገኛሉ”— የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ለኢትዮጵያ ቼክ May be an image of text that says 'Capital Capital 20h COVID vaccines to be rolled out in two weeks' time Gov't officials will be the first to get vaccine By Metasebia Teshome, Government officials are said to be the first to take COVID-19 vaccine in Ethiopia when the Ministry of Health plans to start the vaccination in two weeks' time. The country will receive the vaccine made by AstraZeneca British-Swedish multinational pharmaceutical and Biopharmaceutical Company with its headquarters in Cambridge, England.'የመጀመሪያዎቹ የኮቪድ-19 ክትባቶች በትናንትናው እለት ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ደርሰዋል፣ በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ በኮቫክስ የግዢ ስርዓት የተገኙ የመጀመሪያዎቹን 2.2 ሚሊዮን ክትባቶች ትናንት ተረክባለች። በርክክቡ ስነ ስርአት ወቅት እንደተገለፀው ክትባቶቹ በህንዱ ሴረም ኢንስቲትዩት የተመረቱ የአስትራ ዜኔካ ክትባቶች ናቸው። በርክክቡ ወቅት በይፋ እንደተገለፀው በርካታ ሀገራት እንደሚያደርጉት ክትባቱ በቅድሚያ የሚሰጣቸው ቫይረሱን በመዋጋት ረገድ ግንባር ቀደም ለሆኑት የጤና ባለሙያዎች እና እድሜያቸው ለገፉ ሰዎች ነው። ይሁንና ካፒታል ጋዜጣ ትናንት በፌስቡክ ገፁ እና በድረ-ገፁ እንዳስነበበው ክትባቱ በመጀመርያ የሚሰጠው ለመንግስት ሀላፊዎች ነው ብሏል። ይህንን በተመለከተ ኢትዮጵያ ቼክ ከጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ዛሬ መረጃ ጠይቋል። ዶ/ር ሊያ ጋዜጣው መረጃውን ከየት እንዳገኘው እንደማያውቁ ገልፀው የጤና ባለሙያዎች እና እድሜያቸው ከ65 በላይ የሆኑ ግለሰቦች በቅድሚያ ክትባቱ እንደሚሰጣቸው አብራርተዋል። አክለውም “ጥቂት የመንግስት የስራ ሀላፊዎች የክትባቱ መጀመርን በማስመልከት እና ለሌሎችም አርአያ በመሆን ለማሳየት ሊከተቡ ይችላሉ” ብለው ለኢትዮጵያ ቼክ የገለፁ ሲሆን በአጠቃላይ ግን የመንግስት ሀላፊዎች የመጀመርያ ክትባት ያገኛሉ መባሉ ትክክል እንዳልሆነ አስረድተዋል።
Posted in Amharic News, Funny

የቀሩት የስግብግብ ጁንታ አመራሮች ነፍስም እንደ ወፏ ሁሉ በእጃችን መዳፍ ውስጥ ነው – አቶ ተመስገን ጥሩነህ

“ራስ ሳይጠና ጉተና” “የማያድግ ልጅ ከእናቱ ጀርባ ላይ ታዝሎ ያፉጫጫል” – ከላይ የተጠቀሱት አባባሎች የአበው ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ናቸው። ራስ ሳይጠና ጉተና ማለት ራስን መሸከም በማያስችል ሁኔታ ሌሎች ግዝልዛል ጌጣጌጦች በአናት ላይ ደራርቦ ለመሸከም መሞከር ለራስ ህልውና አደገኛ መሆኑን አመላካች ነው። ቅድሚያ የራስን ደህንነት፣ ህልውና፣ የመኖር ዋስትና ሳያረጋግጡ ሌሎች ድሪቶዎችን መከማመር የመኖር ተስፋን እንደማጨለም ይቆጠራል እንደማለት ነው። አንዳንዴ ገደል አፋፍ ላይ ቆሞ ትልቅ ቋጥኝ ከቆምንበት የገደል አፋፍ በላይ ከፍታ ነጥብ ላይ ሆኖ ቋጥኙን ለማንከባለል የሚታገልን አካል እንደ መርዳት ይቆጠራል። የምንረዳው ራሳችንን ለመጥፋት ነው ማለት ነው። እኛ ገደል አፋፍ ላይ ቆመን ትልቁ ቋጥኝ ተንከባሎ እኛንው ወደ ገደል ገፍቶ እንዲያንኮታኩተን ሌት ተቀን መስራት ማለት ነው። – ሁለተኛው አባባል በእግሩ መሄድ የማይችል፣ መሄድ ቢችልም ብዙ እርቀት የማይጓዝ ህፃን በእናቱ ጀርባ ላይ መታዘሉ ግድ ነው። ይሁን እንጅ ታዝሎም የእናቱን ጆሮ የሚያደነቁር ፉጨት መልቀቅ ብቻ ሳይሆን ፋጨቱ ከጨቅላው ህፃን በላይ ሲሆን አስገራሚ ነው። እናቱ እሩህሩህ የእናትነት አንጀት፣ አዝሎ የማሳደግ የተፈጥሮ ግዴታ፣ እስከ ዘጠኝ ወር በውስጥ አቅፎና ተንከባክቦ ራስን የመተካት አስገራሚ የፍጡራን ተግባራዊ ትዕይንት እና ሌሎችም ምክንያቶች የአስገራሚ ልጇን ፉጨት ተቋቁማ ለማሳደግ ጥረቷን አታቋርጥም። እናት በልጇ ድርጊት አንጀቷ እጥፍ፣ ቆሽቷ እርር እና ጨጓረዋ ቅጥል ቢልም ሀዘኗ ቢኖርም ለልጇ ክፉ አትመኝም። ባይሆን እርር ብላም ልቦና ስጠው ልትል ትችላለች። ሆኖም ሌላው ተመልካች የልጁን እናቱ ጀርባ ላይ ሆኖ ማፏጨት የሚያዬው
Posted in Amharic News, Funny

ሱዳን የኢትዮጵያን መሬት በኃይል የያዘችው በሀገር ውስጥ የገጠማትን ችግር አጀንዳ ለማስቀየር ነው

May be an image of 1 person, indoor and text that says 'gency'ሱዳን ኢትዮጵያን የወረረችው በሀገር ውስጥ የገጠማትን ችግር አጀንዳ ለማስቀየር መሆኑን የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ መምህር አቶ እንዳለ ንጉሴ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያውያን ለውጡንና አንድነታቸውን አጠናክረው ማስቀጠል እንዳለባቸው አስታወቁ ። በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ቤት መምህርና የክፍሉ ኃላፊ እንዳለ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደተናገሩት፤ ወረራው ግብጽ የተወሰነውን የሱዳን ወታደራዊ ክፍል በመግፋት የተፈጠረ ነው፡፡ ሱዳናውያን በእዚህ ወቅት ስለድንበር የሚያወሩበት ጊዜ አይደለም ። በውስጣቸው ከፍተኛ ያለመረጋጋት ይስተዋላል የሚሉት ምሁሩ፤ ዳርፉር ላይ ከባድ ፈተና ተጋርጦባቸዋል ፤ በሀገሪቱ የተሰማራው ሰላም አስከባሪ ኃይል ከአካባቢው ለቅቆ የወጣው የውስጧን ሰላም ሳታረጋግጥ በምታሳየው የድንበር መሻት ነው ብለዋል፡፡ የችግሩ ፈጣሪ ሲቪሉ አስተዳደር አይደለም፤ ከግብጽ የቤት ሥራ የወሰደው በጦር ኃይሉ ውስጥ ያለ አካል ነው ያሉት አቶ እንዳለ ፣ ምክንያቱ ደግሞ በአልበሽር የአገዛዝ ዘመን እነዚህ ወታደራዊ አዛዦች በዳርፉርና በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች የፈጠሩት የሰብአዊ መብት ጥሰት ወንጀል ወደፊት ያስጠይቀናል በሚል ሲቪል መንግስቱ እንዳይቀጥልና እንዳይጠናከር ለማደናቀፍ ነው ብለዋል። ‹‹ይሄ የማይሆን ነገር ነው። ሱዳናውያን ንቁ ናቸው። የግብጽ ህዝብም ወደ ኢትዮጵያ የሚደረገውን ወረራ አልደገፈም ፤ ዓለምም አልደገፋቸውም›› ያሉት መምህሩ፣ ኢትዮጵያውያን ለውጡንና አንድነታቸውንም አጠናክረው ማስቀጠል እንዳለባቸው አስታውቀዋል። የህዳሴ ግድቡን ግንባታ አጠናክሮ ሁለተኛውን የውሃ ሙሌት ማጠናቀቅ እንደሚገባም ጠቁመዋል። ‹‹ዋናው ጉዳይ ያለው ግድቡ ላይ ነው። ይሄ ሁሉ ግርግር የህዳሴው ግድብ ግንባታ በስነ ስርዓት እንዳይሄድ ለማደናቀፍ ነው›› ብለዋል። (ኢ ፕ ድ) https://www.press.et/Ama/?p=41223
Posted in Amharic News, Funny

በመተከል ጭፍጨፋ የተገደሉ በጅምላ ተቀበሩ

በመተከል ጭፍጨፋ የተገደሉ በጅምላ ተቀበሩ There is no Genocide Watch ! There is no Amnesty International – Ethiopia is becoming one of the worest countries to live Amhara for ethnic groups – More than 250 Amharas being murdered in one night – The government of Abiy Ahmed is responsible all this… He didn’t protect the right to life the people of Amhara. More than 3 million Amharas have been killed for the last 30 years. But the international community acts like they don’t know about it. God be with their souls for those who died. Image may contain: outdoorImage may contain: outdoor and natureImage may contain: outdoor –  
Posted in Amharic News, Funny

ጫምሽቱ : ጃንሆይ፣ ጸሐፊ ትእዛዝ አክሊሉና ጄኔራል ጃጋማ ኬሎ

ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው ‼️ – “ጃገማ” አሉ ንጉሠነገስቱ “አቤት ጃንሆይ” አለ ጃገማ ቀረብ ብሎ “ጫምሺቱን አምጥተሃል”አሉት ፈገግ ብለው “አምጥቻለሁ ጃንሆይ!” አለ ጄኔራል ጃገማ “ጫምሽቱ ካለ አታቻኩሉ… ተዉት” አሉ – ጃገማ ኬሎ የጦር ሃይሎች ስፖርት ክፍል መሪ በሆነበት ግዜ ንጉሰ ነገስቱ ጠ/ሚ አክሊሉ ሀብተወልድ እና ሌሎች ሚኒስቴሮች በተገኙበት አመታዊ የጦር ሰራዊት የስፖርት ውድድር ሲደረግ ሰማዩ ክፉኛ ጠቋቁሮ ነጎድጓዱ ሲጮኽ እንግዶቹ ወደ ቤታቸው ለመሄድ ጄኔራሉን ሲያዋክቡት ያስተዋሉት ንጉሥ። – ጫምሽቱ ማለት”ዝናብ የሚያስቆም” ማለት ነው።በኦሮሞ ውስጥ እንደ ጫምሺቱ የማያርሱ የማይነግዱ “ማሊማዎች”የሚባሉ ጎሳዎች አሉ።የአካባቢያቸው ሰው ነው የሚያርስላቸው።ሶስት ቀን ለራሱ አንድ ቀን ለነሱ ያርሳል።የማሊሞዎቹ ስራ ቀንና ለሊት ዋቃን መለመንና ማመስገን ነው ።ካስፈለገ በበጋ ዝናብ ያዘንባሉ፣ካላስፈለገ በክረምት ዝናብ ያስቆማሉ!ስለዚህ ዝግጅት ሲኖር ጫምሽቱ ይጠራና አንጋጦ ሰማይ ሰማይ እያየ ይለማመናል።አይዘንምም።ዝግጅቱም ያለ ስጋት ይጠናቀቃል።ንጉሰነገስቱና ጄኔራል በጫምሺቱ ያምናሉ።አክሊሉ ደግሞ ፈረንሳይ ተምረው የተመረቁ ምሁርም አይደሉ? ለዚህ አይነት Nonsense ቦታ የላቸውም! – “ቶሎ ሸኘኝ እንጂ ሞን ጄኔራል “እያሉ በጭንቀት ይጣደፋሉ።ወደ ንጉሱ ቀረብ ብለው “ጃንሆይ ይህ የማይረባና ኋላቀር እምነት እኮ ነው”አሉ። “ሂድ ጄኔራል ቀጥሉ”አሉ ንጉሱ – Objection overruled!! ዶፍ ዝናብ ዝግጅቱ በሚካሄድበት ዙርያ ቢዘንብም ዝግጅቱ በሚካሄድበት ሜዳ ላይ አንዲት ዘለላ ውሃ ጠብ አላለችም። ዝግጅቱ አልቆ ንጉሱ ወደ መኪናቸው መሄድ ሲጀምሩ ማንጠባጠብ ጀመረ። ንጉሱ በዚህን ግዜ ዘወር ብለው “አክሊሉ”ሲሉ ተጣሩ፣ ፀሐፌትዕዛዝ ቀረብ ብለው “አቤት ጃንሆይ” “ያንተን ሳይንስ አየነው!”ብለው ስቀው ወደ መኪናቸው ገቡ። – ከፍቅረማርቆስ ደስታ
Posted in Amharic News, Funny

ከድምጻዊ ሀጫሉ ግድያ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ ሁከት 67 ምዕመናን እንደተገደሉባት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስታወቀች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተፈጠረው ሁከት ምክንያት ተጎድተዋል ወደ ተባሉ አካባቢዎች ተሰማርታ ምልከታ ካካሄደች በኋላ በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት መግለጫ በመስጠት ላይ ትገኛለች። መግለጫውን ከታች ያገኙታል። ቤተ ክርስቲያኗ በዚህ ጊዜ እንዳለችው ከድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በኦሮሚያ ፣ በሐረሪ እና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳድር በተፈጠረ ሁከት 67 ምዕመናን ሲገደሉ ከ7 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። በአጠቀላይም ሁከቱን መነሻ በማድረግ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የምዕመናን ንብረት መውደሙም በመግለጫው ላይ ተገልጿል። በኦሮሚያ ክልል፣በድሬዳዋ ከተማ አስተዳድር እና በሌሎች አካባቢዎች ምዕመናን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል፣ እንደ ሰውም አስክሬናቸው በክብር አልተቀበረም ፣ ሴቶች በባለቤታቸው፣በወንድምና በአባታቸው ፊት መደፈራቸው በምልከታ መረጋገጡ በመግለጫው ላይ ተገልጿል። ጥቃቱ ሆን ተብሎ የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮችን በመለየት የተፈጸመ እንደነበር ያስታወቀችው ቤተ ክርስቲያኗ መንግስት ሕግን እንዲያስከብርም ጠይቃለች።
Posted in Amharic News, Funny

በዛሬው እለት የኮሮና ቫይረስ ከተገኘባቸው 129 ሰዎች ውስጥ 101 ሰዎች ከአዲስ አበባ ናቸው

በዛሬው እለት የኮሮና ቫይረስ ከተገኘባቸው 129 ሰዎች ውስጥ 101 ሰዎች ከአዲስ አበባ መሆናቸውን የጤና ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎም በመዲናዋ የኮሮናቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 444 መድረሱን የከተማ አስተዳደሩ ጤና ቢሮ መረጃ ያመለክታል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ በከተማዋ የቫይረሱ ስርጭት በክፍለ ከተሞች ደረጃ የሚያመላክት መረጃ አውጥቷል። የከተማ አስተዳደሩ ዝርዝር ሪፖርት እንደሚከተለው ቀርቧል፦
Posted in Amharic News, Funny

በመውደቅ መነሳት፣ በፆምና በስግደት፣ በጥሞናና ፀሎት የተጋችሁበት ወራት ወደ ደስታና እረፍት እንደሚያመጣን ምኞቴም እምነቴም ነው” – ኢ/ር ታከለ ኡማ

የአዲስ አበባ ም/ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ ለትንሳኤ በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት “ምንም እንግልት፣ ምንም ስቃይ፣ ምንም መከራ ዘላለማዊ አይደለም” ብለዋል። ምክትል ከንቲባው “በመውደቅ መነሳት፣ በፆምና በስግደት፣ በጥሞናና ፀሎት የተጋችሁበት ወራት ወደ ደስታና እረፍት እንደሚያመጣን ምኞቴም እምነቴም ነው” በማለት ነው የእኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን ያስተላለፉት። ምን ብዙ ብንደክም፣ ምን ሀዘን ቢገባን፣ አለመፅናናትን ግን አንችልምና ምን ብንፈትን መንገላታታችን ቢበረታ፣ ከመከራችን ተስፋችን ከድህነታችን ፍቅራችን ይበልጣልና የተጋርጠብንን ከባድ ፈተና አሽንፈን እንደ ትንሳኤው ብሩህ ቀናችን ላይ እንደምንደርስም ያላቸውን እምነት ገልፀዋል። “ትንሳኤ ከመንፈሳዊ ሀሳቡ ባለፈ ለምድራዊ ህይወታችንም ጉልበት ሰጪ ነው፤ ትንሳኤ ለእውነትና እምነት ዋጋ የመክፈል ምልክት ነው፤ ትንሳኤ ለሌሎች ህይወት ዋጋ እስከ ህይወት ድረስ የመክፈል ማሳያ ነው። ሀገራችን ከዛ አልፎ ዓለማችን አሁን ያለችበት ወቅታዊ ሁኔታ መጥፎ የሚመስል ነገር ግን ደግሞ እንደ ህዝብ ያለን ጥንካሬ የሚለካበት መተሳሰባችንና መተባባራችን በጋራ የሚያቆመን ብርቱ ምሶሶ የሆነበት ወቅት ላይ ነው የምንገኘው፡፡ በመተሰሳሰብ ስንራመድ ለሌሎች ማሰባችን በተግባር ሲገለጥ ይህ ጊዜ አልፎ ትንሳኤ ይመጣልⵆ” EBC  
Posted in Amharic News, Funny

አዲስ አበባ ታክሲዎች የነዋሪዎችን ጤንነት ለመጠበቅ ቸልተኝነት ስላሳዩ ከስራ ይታገዳሉ ተባለ

በአዲስ አበባ ታክሲና ባጃጆችን ስራ ሊያስቆም እንደሚችል የከንቲባ ፅህፈት ቤት አስጠነቀቀ፡፡ ሸገር 102.1   የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በከተማዋ የትራንስፖርት ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ተሽከርከሪዎች ትርፍ ከመጫን እንዲቆጠቡ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ አውቶሰብሶችም በወንበር ልክ ብቻ እንዲጭኑ መደረጉ ይታወቃል፡፡   ይሁንና የከተማ አስተዳደሩ አደረግሁት ባለው ቁጥጥር ታክሲዎችና ባጃጆች ትርፍ እየጫኑ መሆኑን ታዝቤያለሁ ብሏል ስለሆነም በፍጥነት የማያስተካክሉ ከሆነ የነዋሪውን ጤንነት ለመጠበቅ ከስራ ውጭ ለማድረግ እንደሚገደድ የከንቲባ ፅ/ቤት አስጠንቋል  
Posted in Amharic News, Funny

በደብረዘይት ለተሰበሰቡ የብልጽግና ፓርቲ አባላት የሚከፈል 2 ሚሊዮን ብር አበል ከአቶ ታዬ ደንድዓ መኪና ውስጥ መዘረፉ ተሰማ።

BBC Amharic የብልጽግና ፓርቲ አመራር የሆኑት አቶ ታዬ ደንደአ በቢሸፍቱ ከተማ ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው ብርና ሌሎች ንብረቶች ዝርፊያ እንደተፈጸመባቸው ለቢቢሲ ተናገሩ። አቶ ታዬ ዘረፋው ያጋጠማቸው ለሥራ ጉዳይ ወደ ቢሾፍቱ በሄዱበት ወቅት መሆኑንና በዚህም ይጓዙበት ከነበረው መኪና ውስጥ ሁለት ሚሊዮን ብር እና ሌሎች ንብረቶች እንደተወሰደባቸው ገልጸዋል። ዝርፊያው የተፈፀመበት ሁኔታም ሲያስረዱም፤ ቢሾፍቱ ከተማ ውስጥ ቢን ኢንተርናሽናል በተባለ ሆቴል ምሳ ለመመገብ መኪናቸውን አቁመው በገቡበት ጊዜ “የመኪናቸው በር በማስተር ቁልፍ ተከፍቶ” የተጠቀሰው ገንዘብና የተለያዩ ንብረቶች እንደተዘረፈባቸው ተናግረዋል። አቶ ታዬ ደንደኣ ይህ ከፍተኛ መጠን ያለውን ገንዘብ በመኪናቸው ይዘው የነበረው በቢሾፍቱ ከተማ ስልጠና እየተከታተሉ ለነበሩ ለሰልጣኞች የሚከፈል አበል እንደነበር ጨምረው አስረድተዋል። ከገንዘቡ በተጨማሪ ላብቶፕ ኮምፒውተር እና ሁለት የሥራና የግል ጉዳዮችን የሚጽፉባቸው ማስታወሻ ደብተሮች እንደተሰረቁባቸው ተናግረዋል። ጨምረውም ስርቆቱ ከተፈፀመ በኋላ “የታዬ ማስታወሻ ደብተር እጄ ገብቷል” ብሎ የፌስቡክ ገፁ ላይ የጻፈ ግለሰብ መኖሩንና ጉዳዩን ወደ ሕግ መውሰዳቸውንም ያስረዳሉ። የቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ ስለጉዳዩ ተጠይቆ ምርመራ እየተካሄደ ስለሆነ ተጣርቶ ሲያልቅ ይፋ እንደሚደረግ የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ደረጀ ሙለታ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የአቶ ታዬ ደንደአ የማስታወሻ ደብተር መሰረቁን ፌስቡክ ገፁ ላይ ጻፈ ያሉት ግለሰብ በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሃሳብ በመስጠት የሚታወቀው ደረጀ ቤጊ የተባለ ግለሰብ ነው። በጉዳዩ ላይ ቢቢሲ ያነጋገራቸው አቶ ደረጀ “እንደማንኛውም ጊዜ በፌስቡክ የመልዕክት ሳጥኔ እንደተላከልኝ አስታውቄ ነው ማስታወሻዎቹ መሰረቃቸውን የፃፍኩት” ብለዋል። “በውስጥ መስመር ነው የተላከልኝ፤ የለጠፍኩትም [ኢንቦክስ] ብዬ ነው። ታዬ
Posted in Amharic News, Funny

ኢዜማ በአርባ ምንጭ የጠራው ሕዝባዊ ስብሰባ በከተማው መስተዳደር ተሰረዘ

ኢዜማ በአርባ ምንጭ ሊያካሂድ የነበረው ህዝባዊ ውይይት ተከለከለ። ስብሰባቹ ላይ ሁከት ለመፍጠር የጋዴፓ አባላት እና አንዳንድ ባለሃብቶች እየተንቀሳቀሱ ስለመሆኑ መረጃ ደርሶናል”- የከተማ አስተዳደሩ ህጋዊ ዕውቅና ያለውን ኢዜማን ስብሰባ ለመከልከል የጋዴፓ አባላት አደጋ ለማድረስ እየሰሩ ነው በሚል የተገለፀው ብልፅግናዎች የኢዜማ እና ጋዴፓ ደጋፊዎችን በማጋጨት እርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ያሰቡት ሴራ ነው – የጋዴፓ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር አቶ መርዕድ ሽብሩ የ #ኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (#ኢዜማ) በአርባምንጭ ከተማ ሊያካሂድ የነበረው ሕዝባዊ ስብሰባ ተሰረዘ።https://t.co/ptgRdFAzzE pic.twitter.com/8IorxbjfXI — Ethiopian Citizens for Social Justice #Ezema (@ETHZema) February 1, 2020 GMN | የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ /ኢዜማ/ በነገው ዕለት በአርባ ምንጭ ከተማ ሊያካሂደው የነበረው ህዝባዊ የውይይት መድረክ መሰረዙ ታወቀ። የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በተገኙበት ሊካሄድ ቀነ-ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው ይህ ህዝባዊ የውይይት መድረክ የከተማ አስተዳደሩ በፃፈው “ቀድም ብዬ የፈቀድኩትን የመሰብሰብያ አዳራሽ ፍቃድ ሽርያለው” ደብዳቤ ሊሰረዝ ችሏል። በጉዳዩ ላይ ጂ ኤም ኤን ያነጋገራቸው የፓርቲው ከፍተኛ አመራር እንደገለጹት አስቀድሞ የመሰብሰብያ አዳራሽ ፍቃድ የተሰጠውን ይህን ህዝባዊ የውይይት መድረክ ማካሄድ እንደማንችል የመንግስት ባለሥልጣናቱ በትላንትናው ዕለት ነግረውናል ብለዋል። Image may contain: 4 people, people standing and suit የውይይት መድረኩ እንዳማይካሄድና ቀደም ብሎ የተሰጠው የስብሰባ አዳራሽ ፍቃድ እንደተሻረ ከመግለጻቸው ባሻገር “ስብሰባቹ ላይ ሁከት ለመፍጠር የጋዴፓ አባላት እና አንዳንድ ባለሃብቶች እየተንቀሳቀሱ ስለመሆኑ መረጃ ደርሶናል” በሚል እንደገለጹላቸው ነገር ግን እኛ እንደውም ከጋዴፓ አባላት ጋር በትብብር እየሰራን ነው፤ ይሄ ስብሰባውን ለመከልከል በቂ ምክንያት ሊሆን አይችልም
Posted in Amharic News, Funny

በቦሌ አካባቢ መንግስት የሰጣቸውን መሳሪያ ተጠቅመው የውንብድና ወንጀል የፈፀሙት የፖሊስ አባለት በጽኑ እስራት ተቀጡ፡፡

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 አካባቢ መንግስት የሰጣቸውን መሳሪያ ተጠቅመው የውንብድና ወንጀል የፈፀሙት የፖሊስ አባለት በጽኑ እስራት ተቀጡ፡፡ የክሱ ዝርዝር እንደሚያስረዳው 1ኛ ተከሳሽ ኮን/ል ወንድሙ ሞሲሳ 2ኛ ተከሳሽ ኮን/ል ደረሰ ማርቆስ ሲሆኑ ተከሳሾች ተገቢ ያልሆነ ብልጽግና ለማግኘት በማሰብ ጥቅምት 20 ቀን 2011 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡45 ሰዓት ከላይ በተጠቀሰው ቦታ ዲኤች ገዳ የገበያ ማዕከል ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ወንጀል ለመስራት አቅደውና ተስማምተው ካልተያዙት ግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆን በመኪና በመተገዝ ለወንጀሉ መፈፀሚያ የሚሆን ክላሽ የጦር መሳሪያ እና ዱላ በመያዝ የግል ተበዳይ አሚር አሊ እና በወቅቱ ሱቅ ውስጥ የነበረውን ዳውድ አሊን በያዙት ካቴና በማስር እና በመደብደብ የያዙቴን መኪና ወደ ሱቁ በማስጠጋት ካቆመ በኃላ ተ/ሀይማኖት ገ/መድን የተባለው ያልተያዘው ግብርአበር ዶላር ይዣለሁ ትዘረዝራለህ በማለት ዳወድን እየጠየቀው እያለ ሱቅ ውስጥ በመግባት ተቀምጦ የነበረውን ሁለት መቶ ሺ ብር በመውሰድ በተዘጋጀው መኪና በመሄድ የግል ተበዳይንና አብሮት የነበረውን ጓደኛ ከሱቁ አርቅው ጨለማ ቦታ ላይ በመውሰድ ከፈቷቸው በኋላ እንዳያዩ በማስጠንቀቅ ለቀዋቸው ብሩን ይዘው የተሰወሩ ሲሆን በወቅቱ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች ሲያዙ ሌሎች የተሰወሩ በመሆኑ በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት የከባድ ውንብድና ወንጀል ተከሰዋል፡፡ ዐቃቤ ሕግ በምርምራ መዝገብ መሰረት የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎች በመያዝ በማስረጃነት አቅርቧል:: ተከሳሾች ማንነታቸው ተረጋግጦ ክሱ ተነቦላቸው እንዲረዱት ከተደረገ በኃላ የወንጀል ድርጊቱን አልፈፀምንም በማለት ክደው በመከራከራቸው ዐቃቤ ሕግ ምስክሮች ቃል ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡ ፍርድ ቤትም ግራ ቀኙን መርምሮ ተከሳሾችን በተከሰሱበት
Posted in Amharic News, Funny

ጠ/ሚ አብይ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በስልክ ተወያዩ

ጠ/ሚ አብይ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በስልክ ተወያዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ በስልክ ውይይት አደረጉ፡፡ በውይይቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ 100ኛውን የኖቤል የሰላም ሽልማት በማግኘታቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አሜሪካ ታሪካዊውን የለውጥ ሂደት እንደምትደግፍ ጠቅሰው፥ በአሜሪካና ኢትዮጵያ መካከል ስላለው ጠንካራ ወዳጅነት አስፈላጊኒት አንስተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩና ማይክ ፓምፒዮ በወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ እንዲሁም ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው መወያየታቸውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል፡፡ በደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነትና የጥምር መንግስቱ ተግባራዊ እንዲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ድጋፍ እንዲያደርጉ ማይክ ፖምፒዮ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ Source (ኤፍ.ቢ.ሲ)
Posted in Amharic News, Funny

ኦሮምኛን ጨምሮ ተጨማሪ ቋንቋዎችን የፌደራል የሥራ ቋንቋ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠ/ሚ ዐብይ ተናገሩ

BBC Amharic : ኦሮምኛን ጨምሮ ተጨማሪ ቋንቋዎችን የፌደራል የሥራ ቋንቋ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኦሮሚያ ክልል ቴሌቪዥን (ኦቢኤን) ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት ኦሮምኛን ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የፌደራል መንግሥቱ የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ ነው። ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ ሌላ ቋንቋ የፌደራል መንግሥቱ የሥራ ቋንቋ ማድረግ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮች ካሉና ያላቸውን አመለካከት የተጠየቁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በሰጡት መልስ “በዚህ ረገድ ምንም ችግር የለውም” ሲሉ በአፅንኦት መልሰዋል። አክለውም “ሁለት፤ ሦስት ቋንቋዎች መጠቀም ሰውን ይጠቅማል እንጂ ምንም ዓይነት ጉዳት የለውም” ሲሉ አብራርተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዚህ ቃለ ምልልስ ላይ ተጨማሪ የፌደራል የሥራ ቋንቋዎች ለመጨመር እየተሰራ መሆኑን ተናግረው፤ ለዚህም ጥናት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ ይህ ሊሆን የሚችለው በስሜትና በኩርፊያ ሳይሆን በእውቀትና በተረጋጋ አኳዃን ነው ብለዋል። ስለሆነም በቅርብ ጊዜ ሌሎች ቋንቋዎችን የፌደራል የሥራ ቋንቋ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንና ጥናቱም ሲጠናቀቅ “ከኦሮምኛ በተጨማሪ ሶማልኛ እና ሌሎች ቋንቋዎች የፌደራል መንግሥት የሥራ ቋንቋ ቢሆኑ የምንጎዳው ነገር የለም” ሲሉ ተናግረዋል። ተጨማሪ ቋንቋዎችን የሚጠቀሙ ሀገራትን እንደ ምሳሌ በማንሳት የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ከዚህ ኤርትራ ቢኬድ፣ ኬኒያ ቢኬድ፣ ጅቡቲ ቢኬድ እንዲህ አይነት ነገር የተለመደ ነው” በማለት ችግር እንደማይኖረው አብራርተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከኦቢኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምላሽ የሰጡ ሲሆን ስለ መደመር፣ ስለ እሬቻ፣ ሪፎርምና እና ስለ ቤተ መንግሥት እድሳት ዘርዘር ያለ
Posted in Amharic News, Funny

“ልጃችሁን ምን መሆን ትፈልጋለህ ብላችሁ አትጠይቁ?” ፌቨን ሰይፉ

Posted in Ethiopian News, Funny, Music, Psychology

የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ከትናንት ምሽት ጀምሮ የእሳት አደጋ አጋጥሞታል፡፡

የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ከትናንት ምሽት ጀምሮ የእሳት አደጋ አጋጥሞታል፡፡ ከፓርኩ የተለያዩ አካባቢዎች የተነሳው እሳት በጨለማውና ነፋሱ እንዲሁም በአካባቢው መልክአ ምድርና ተቀጣጣይ ነገሮች መብዛት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ ሆኖ አድሯል፡፡ወደ ስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ከክልልና ፌዴራል ቡድን ተንቀሳቅሷል፡፡ የአርግንና አምባራስ አካባቢ አርሶ አደሮች፣ የፓርኩ የጥበቃ ሠራተኞችና አስጎብኝዎች እሳቱን ለመቆጣጠር ጥረት ቢያድርጉም መቆጣጠር አልቻሉም፡፡ ከደባርቅ ተጨማሪ ኃይል ለመሄድ በመኪና እጥረት እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ አልተሳካም ነበር፡፡ አብመድ ደባርቅ ከሚገኙ የፓርኩ ጽሕፈት ቤት ባለስልጣናትና ከደባርቅ ወረዳ ባሕልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች ሌሊቱን ባገኘው መረጃ መሠረት እሳቱን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ተሽከርካሪ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል፡፡Image may contain: one or more people, night and fire የአማራ ክልል የአካባቢ፣ የደንና የዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር በላይነህ አየለ ለአብመድ በስልክ እንደገለጹት እሳቱን ለመቆጣጠርና የአደጋውን መንስኤና ጉዳት ለማጣራት ከክልልና ፌዴራል የተደራጀ ቡድን ወደ አካባቢው አቅንቷል፡፡ አሁን ላይ እሳቱ ያለበትን ደረጃ ለማዎቅ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፤ የጋዜጠኞች ቡድን በቦታው እንደደረሰ ዝርዝር መረጃዎችን የምናደርስ ይሆል፡፡  (አብመድ)
Posted in Amharic News, Funny

“ማብረርን ወደላቀ ደረጃ የማድረስ ህልም ነበረው”የረዳት አብራሪው አህመድ ኑር ጓደኛ

BBC Amharic በቅርቡ የተከሰከሰው ቦይንግ 737 ማክስ 8 ረዳት አብራሪ የነበረው አህመድ ኑር ፓይለት ከመሆኑ በፊት በልደታ ህንፃ ኮሌጅ በአርክቴክቸር የትምህርት ክፍለ ዘርፍ እንደተመረቀ የሚናገረው በተቋሙ ሲማር በነበረበት ወቅት የዩኒቨርስቲ ጓደኛው ፈክሩዲን ጀማል ይናገራል። ከጓደኝነት በተጨማሪ በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ለሶስት አመታት ያህል በአንድ ዶርም ውስጥ አድረዋል። አህመድ ኑርን ለመግለፅ ቃላት ያጠረው ፈክሩዲን “አህመድ ኑርን ለመግለፅ ይከብዳል። በጣም የተረጋጋ ሰው ነበር። ምንም ነገር ሲያደርግ በጣም ተረጋግቶ ነው። ትዕግስተኛ ነው” ይላል። ፈክሩዲን እንደሚናገረው የአርክቴክቸር ትምህርት ፈታኝ ቢሆንም “አህመድ ኑር በተረጋጋ መንፈስ ነገሮችን ስለሚያከናውን እንደፈተነው መገመት ይከብዳል።” ይላል። ለጓደኞቹ ፈጥኖ ደራሽ ነበር የሚለው ከሰባት አመት በላይ ጓደኛው ፈክሩዲን “ማብረርን እንደ ጥናት ሳይሆን ወደላቀ ደረጃ የማድረስም ህልም ነበረው” ብሏል። አብዛኛውን ጊዜም ስለበረራ ሲያስረዳቸው በአይነ ህሊናቸው እንዲታያቸው አድርጎ በጥልቀት እንደሚተነትንም ያስታውሳል። “በሕይወቱ አቋራጭ ነገር ሲጠቀም አይቼው አላውቅም” ሁልጊዜም በአንድ ጉዳይ ላይ የጠለቀ እውቀት እንዲኖረው ስለሚፈልግም ጊዜውን እንደሚሰጥ ይናገራል። ልደታ በነበረበትም ወቅት ለማብረር ከፍተኛ ፍቅር እንደነበረው የሚናገረው ፈክሩዲን በህይወቱ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች አትኩሮት ሰጥቶም እንደሚከታተል ይገልፃል። በማያጠናበት ወቅት እግር ኳስ ይጫወት የነበረ ሲሆን፤ ለቀድሞ የአማርኛ ሙዚቃዎች ለየት ያለ ፍቅር ነበረው። ” እኩል እድሜ ላይ ብንሆንም እኛ የማናውቀውን ሙዚቃ ይዘፍንና ይሄ ልጅ ግን መቸ ነው የተወለደው ያስብለን ነበር።” በማለት ፈክሩዲን ይናገራል። ድሬዳዋ ተወልዶ ያደገው የ26 አመቱ አህመድረ ኑር ወደ አዲስ አበባ የመጣውም በዩኒቨርስቲ ድልደላ በምህንድስና የትምህርት ዘርፍ አዲስ
Posted in Amharic News, Funny

ተንኳሹ ዝንጀሮ – ቪዲዮ

$bp("Brid_15099_1", {"id":"12272","stats":{"wp":1},"title":"Monkey attacks passersby","video":"228884","width":"550","height":"309"}); ለፈገግታ ያህል
Posted in Funny