Home › Archive for Ethiopian News
Blog Archives
መንግስት ወደ ኦሮሚያ ክልል የመለሳቸው ተፈናቃዮች “የከፋ በመሆኑ” ወደ ደብረብርሃን እየተመለሱ ነው
ወደ ኦሮሚያ ክልል የተመለሱ ተፈናቃዮች ወደመጡበት ደብረ ብርሃን መልሱን የሚል ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑን አዲስ ማለዳ ሰምታለች።
ተመላሾቹ በኦሮሚያ ክልል ዞኖች የሚገኙበትን ሁኔታ ሲገልጹ “እንጨት እንኳን መስበር አንችልም። ለህይወታችን አስጊ ነው፤ ከመጠለያችን መውጣት አንችልም።
በዛ ላይ ከመንግስት ምንም አይነት ድጋፍ እየተደረገልን አይደለም” ብለዋል።
ደብረ ብርሃን የሚገኙትም የከፋ ችግር ውስጥ ሲሆኑ ተፈናቃዮቹ ወደ ኦሮሚያ ክልል እንዲመለሱ ሆን ተብሎ እንዲቸገሩ እየተደረገ ስለመሆኑና… https://addismaleda.com/archives/36342 የአዲስ ማለዳን ልዩ ዘገባ ሙሉ ያንብቡ
ለወሊድ ወደ ደሴ ሆስፒታል የሄደች እናት ለቀናት ወደ ቤቷ ሳትመለስ ለመቆየት ተገዳለች፣ ለነርቭ ህመማቸው የሚወስዱት መድኃኒት ያለቀባቸው አባት ሞታቸውን እየጠበቁ ነው፣ ለአእምሮ ጤና የሚወስደው መድኃኒት የተቋረጠበት ልጃቸው እና እሳቸው በስቃይ ውስጥ መሆናቸውን እናት ይናገራሉ፣ የጤና ባለሙያዎች የጠፉ በሽታዎች እንዳያንሰራሩ ስጋት ተፈጥሮባቸዋል...እነዚህን ታሪኮች ለቢቢሲ የተናገሩት መንገድ በተ...
ከሁለቱም የአሜሪካ አውራ ፓርቲ የተውጣጡ ፖለቲከኞች አዲስ ያረቀቁት አዋጅ የቲክቶክ ባለቤት የሆነው ባይትዳንስ መተግበሪያውን ቻይናዊ ላልሆነ ኩባንያ ካልሸጠ ይዘጋል ይላል። ሕግ አውጪዎቹ ቲክቶክ በአሜሪካ የሚገኙ 170 ሚሊዮን ደንበኞችን መረጃ ለቻይና መንግሥት አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው።...
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio360
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በሩሲያ ጠቅላላ ምርጫ አገሪቱን ለአምስተኛ ዙር መምራት የሚያስችላቸውን ድምጽ ማግኘታቸውን ይፋ አደረጉ።
ትላንት ዕሁድ በቱርክ ሱፐር ሊግ ትራብዞንስፖር እና ፌኔነርባቼ ካደረጉት ጨዋታ በኋላ የፌነርባቼ ተጨዋቾች ወደ ሜዳ በገቡ የትራብዞንስፖር ተጨዋቾች ጥቃት ደርሶባቸዋል።
በፓፓራ ፓርክ የተደረገውን ጨዋታ ፌንርባቼ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት ረትቷል። ይህንን ድል ተከትሎ ደስታቸውን እየገለጹ በነበረበት ወቅት ከተቃራኒ ብድን ደጋፊዎች ጥቃት ተሰንዝሮባቸዋል።
...
የእስራኤል ኃይሎች በጋዛ በሚገኘው አል ሺፋ ሆስፒታል ላይ በሌሊት በከፈቱት ጥቃት በሆስፒታሉ ውስጥ በታንክ የታገዘ ከባድ ተኩስ እንደነበር ተዘገበ።
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio360
ዋዜማ- ቅዳሜ ዕለት በየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል መዋቅር ላይ የተከሰተውን ግድፈት ተጠቅመው ገንዘብ የወስዱ አካላትን ለማደን ግብረ ኀይል መቋቋሙን ዋዜማ ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች ሰምታለች።
ከብሔራዊ ባንክና ንግድ ባንክ ባለሙያዎች እንዲሁም የፀጥታ አካላት የተካተቱበት ይህ ግብረ ኀይል በስድስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ከባንኩ ያለ አግባብ ተወስዷል ያለውን ገንዘብ ለማመለስ ያለመ ነው። ባንኩ የተወሰደበትን የገንዘብ መጠን አላሳወቀም። ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ግን ከ66 ሺህ በላይ ደንበኞች አካውንት በችግሩ መታወኩን፣ ቅዳሜ ለስድስት ሰዓታት በቆየው መታወክ 25 ሺ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር መደረጉን እንዲሁም ሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊየን ብር ተንቀሳቅሷል። ባንኩ መረጃውን ማረጋገጥ አልፈለገም።
አንዳንድ የትምህርት ተቋማት ከወዲሁ ገንዘብ ከክፍያ ማሽኖች የወሰዱና በህገወጥ ዝውውሩ የተሳተፉ ተማሪዎች ገንዘቡን ለባንኩ እንዲመልሱና ራሳቸውን ከህግ ተጠየቂነት እንዲያተርፉ የሚያሳስብ ጥሪ አድርገዋል።
በባንኩ ላይ የደረሰው ችግር የሳይበር ጥቃት አለመሆኑንና ውስጣዊ ግድፈት መሆኑን ባንኩ አበክሮ ገልጿል።
የባንኩ የውስጥ ምንጮች ለዋዜማ እንደተናገሩት ግን ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የተከናወነ አንድ መንግስታዊ የባንክ ክፍያ (ከአንድ መቶ ሚሊየን ብር ያላነሰ) ከአንድ በላይ የከፋይ ወገን በዲጂታል ፊርማ ሊያፀድቀው ሲገባ በአንድ ሰው ፈራሚነት ወደ ተከፋይ መተላለፉ የባንኩን ሀላፊዎች አስደንግጦ ነበር። አርብ ዕለት ችግሩን ለማወቅና ለመፍታት ሙከራ ሲደረግ መዋሉንና የቅዳሜ ሌሊቱ ቀውስ መከተሉን ሰምተናል።
ባንኩ የሳይበር ጥቃት አለመፈፀሙን ይናገር እንጂ ክስተቱ በባንኩ ዲጂታል መዋቅር ላይ በውስጥ አዋቂ የተፈፀመ ጥቃት ሊሆን እንደሚችል የሳይበር ደህንነት ባለሙያዎች ይናገራሉ። ባንኩ ከተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ ጋር በተያያዘ
ሰሞኑን አምስት መንግሥታዊ ተቋማት ማለትም የግብርና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ኢትዮጵያ ፖስታና ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የስኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በሥራቸው የተመሰከረላቸው ተቋማት ሲሸለሙ መልካም የሆነውን ያህል፣ ሽልማቱም የበለጠ ለመሥራት የሚያነሳሳ መሆን ይገባዋል፡፡ የግብርና ሚኒስቴር በስንዴ ልማት ፕሮግራም ከተሸላሚዎች ተርታ የተገኘ ብቸኛ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ሲሆን፣ ሌሎቹ ግን ተጠሪ ተቋማት ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ አንቱታን ያተረፈና የበርካታ ሽልማቶች ባለቤት በመሆኑ፣ በኢትዮጵያ ብቸኛው ታላቅ ደረጃ ላይ የደረሰ ተቋም ነው ቢባል የተጋነነ አይደለም፡፡ ሥራው በከፍተኛ ፉክክር የተፈተነ የላቀ ውጤት አስመዝጋቢ ነው፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም በከፍተኛ ዕድገት ላይ ሲገኝ፣ ኢትዮጵያ ፖስታ እመርታዊ ለውጥ እያሳየ ነው፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለአገር ዕድገት ትልቅ ምሳሌ ነው፡፡
ከላይ የተጠቀሱት መንግሥታዊ ተቋማት በጣም ብዙ ከሚባሉት ውስጥ ተመርጠው በአርዓያነት የስኬት ተሸላሚ ሲሆኑ፣ ሌሎችም የሚጨበጥ ሥራ አከናውነው ለስኬት ይበቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ነገር ግን አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ብዙዎቹ መንግሥታዊ ተቋማት በመዳህ ላይ ናቸው ቢባል ይቀላል፡፡ እርግጥ ነው ከተወሰኑ ጊዜያት ወዲህ ምሥጉን ሥራዎችን የሚያከናውኑ ተቋማት እየታዩ ነው፡፡ እነሱ አሳማኝ የሆነ ተግባር አከናውነው ተመራጭ የሚሆኑበት ዕድል አለ፡፡ ይሁንና የብዙዎቹ ተቋማት ጉዳይ ግን ሰፊና ጥልቅ ምርመራ ያስፈልገዋል፡፡ ተቋማቱ መሠረታዊ ለውጥ አድርገው ተመራጭ ሊሆኑ የሚችሉት ግን አሁን ባሉበት ሁኔታ አይደለም፡፡ ተቋማዊ የአደረጃጀት ሪፎርም ተደርጎባቸው ብቁ አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ ሠራተኞች፣ ዘመኑ ያፈራቸው ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችና የመሳሰሉት ድጋፎች
የፕሪቶሪያ ስምምነት ትግበራ ሊፈጥረው የሚችለው የፖለቲካ ኃይል አሠላለፍ ልዩነት
የሰላም ጥረት ገና ሲጀመር ጀምሮና ወደ ፕሪቶሪያ ስምምነትም ሲገባ አርቆ አሳቢ ወገኖች ሒደቶቹ ሁሉንም ወገን አቃፊ እንዲሆኑ ሲወተውቱ ነበር፡፡ በጦርነቱ ተሳታፊ የነበሩ ሁሉም ኃይሎች…
https://www.ethiopianreporter.com/127688/
የኢትዮጵያ አርታኢያን ማኅበር በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን መከታተል የሚያስችለውን ድረ ገጽ ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ አርታኢያን ማኅበር (ኢአማ) በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከታተልና ለመመዝገብ የሚያስችል ድረ ገጽ ወይም ‹‹ፖርታል›› አዘጋጅቶ በሥራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ፡፡ ማኅበሩ በአገር አቀፍ ደረጃ በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን በመከታተልና በመመዝገብ በየሦስት…
https://www.ethiopianreporter.com/127631/
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ሐኪሞች በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ ማከም መቸገራቸውን ተናገሩ
‹‹ሆስፒታሉ ማስተማሪያ እንጂ ሙሉ በሙሉ ሕክምና የመስጠት ግዴታ የለበትም›› ጅማ ዩኒቨርሲቲ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሕክምና መስጫ ዕቃዎችና መድኃኒቶች እጥረት በመፈጠሩ፣ ታካሚዎችን ማስተናገድ የማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል ሲሉ የሕክምና ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የሚሠሩ ስማቸው…
https://www.ethiopianreporter.com/127634/
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሕጎችን እንድታፀድቅና የሠራተኞች መብት እንዲከበር ተጠየቀ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) መንግሥት ሠራተኞችን የተመለከቱ ዓለም አቀፍ ሕጎች እንዲያፀድቅና የሠራተኞችን መብት እንዲያከብር ጥያቄ አቀረበ፡፡ ኢሰመጉ ሐሙስ መጋቢት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ መንግሥት የሠራተኞች ሰብዓዊ መብቶችን አስመልክቶ ልዩ ልዩ የሕግና የተቋማት…
https://www.ethiopianreporter.com/127641/
በትግራይ ክልል በጦርነት ንብረታቸው የወደመባቸው ባለሀብቶች ብድር የሚከፍሉበት ጊዜ እንዲራዘምላቸው ጠየቁ
በትግራይ ክልል በጦርነቱ ንብረታቸው የወደመባቸው ባለሀብቶች ከጦርነቱ በኋላ ምንም ዓይነት የሥራ እንቅስቃሴ ማድረግ ስላልቻሉ፣ ከተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ሌላ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጣቸው ጥያቄ አቀረቡ፡፡ የትግራይ ክልል ባለሀብቶች ጥያቄውን ያቀረቡት ዓርብ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. በጠቅላይ…
https://www.ethiopianreporter.com/127653/
‹‹እንኳን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት የአገሪቱ ህልውናም እንዴት ነው ተጠብቆ የሚቀጥለው የሚለው ጉዳይ ጥያቄ እየሆነ መጥቷል›› መላኩ ተገኝ (ዶ/ር)፣ አንጋፋ ፖለቲከኛና ጸሐፊ
‹‹እንኳን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት የአገሪቱ ህልውናም እንዴት ነው ተጠብቆ የሚቀጥለው የሚለው ጉዳይ ጥያቄ እየሆነ መጥቷል›› መላኩ ተገኝ (ዶ/ር)፣ አንጋፋ ፖለቲከኛና ጸሐፊ – ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best And Reliable News Source In Ethiopia
የሕግ የበላይነት አለመከበርና ሌሎች ምክንያቶች ለሰላምና ለደኅንነት ፈተና መሆናቸውን የፍትሕ ሚኒስትሩ አስታወቁ
በፅዮን ታደሰ የፍትሕ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የሕግ የበላይነት አለመከበር፣ ሙስና፣ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሠራጩ ሐሰተኛ መረጃዎች፣ እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በሚከሰት የድርቅና የጎርፍ አደጋ፣ ለሰላምና ለደኅንነት ፈተና መሆናቸውን አስታውቁ፡፡ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ዓለም አቀፍ የልማት…
https://www.ethiopianreporter.com/127637/
በፓርላማ በተፎካካሪ ፓርቲ ተይዞ የነበረው የመንግሥት ወጪ ቁጥጥር ሰብሳቢነት ለብልፅግና ተሰጠ
የአቶ ክርስቲያን ታደለ ያለ መከሰስ መብት ሲነሳ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በዋስ ከእስር ተለቀዋል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለረዥም ዓመታት በምርጫ አሸንፈው ፓርላማውን ለተቀላቀሉ ተፎካካሪና አጋር የፖለቲካ ፓርቲ አባላት በመስጠት ሲሠራበት የነበረውን፣ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና…
https://www.ethiopianreporter.com/127655/
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በሁለት ወራት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ከልዑካን ቡድናቸው ጋር ለሥራ ጉብኝት ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አሥመራ መግባታቸው ተገለጸ። የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል በኤክስ ገጻቸው ላይ እንደገለጹት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ዛሬ እሁድ መጋቢት 8/2016 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ አሥመራ ገብተዋል።...
አፈራራሚዎቹ በግጭቱ የተጎዱትን መልሶ ማቋቋምን ጨምሮ ተጎጂዎችን ያማከለ የሽግግር የፍትሕ ሂደት እና ተጠያቂነትን ለማስፈን የስምምነቱ ፈራሚዎች መገናኘታቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አድርገዋል።እነዚህ የበለፀጉ እንዲሁም በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተከሰቱት ቀውሶች በተመሳሳይ ቁርጠኝነት ችግሩ እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል።...
“ብሔራዊ መግባባት በገለልተኛ አካል ነው መመራት ያለበት፡፡ ሁሉም የውይይቱ ተካፋዮች የሚያምኑበት መሆን ይገባል” ያሉት ፕሮፌሰር መረራ በኢትዮጵያ የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ የተቋቋመውን አገራዊ ኮሚሽን የገለልተኝነት እና አቃፊነት ሁኔታን ነቅፈዋል፡፡...
Join Mereja TV: www.mereja.tv
Ethio 360 Zare Min Ale የዝግ ሸንጎው ጥብቅ ምስጢር እና ከፒያሳ መፍረስ በስተጀርባ! Sun March 17, 2024
ካባና ዲዛይን ከመደበኛ ሥራ ውጪ በትርፍ ጊዜ ከሚሠራ የጊዜ ማሳለፊያ ‘ሆቢ’ የተወለደ እና ጥቂት ለማይባሉ ሰዎችም ሥራ እና ተስፋን ያስገኘ የሥራ ፈጠራ ሙከራ ነው። ካባናን እንዴት ተጀመረ? ስኬታማ ቢዝነስንስ እንዴት መጀመር ይቻላል? ሰምሃል ያለፈችበትን እና ልምዷን አጋርታናለች። ...
ከጥቁር ዛምቢያዊ እናት እና ከነጭ የዌልስ አባት የተወለዱት ቮውን ገተን የመጀመሪያው የዌልስ መሪ ሊሆኑ ነው።
የመከላከያ ሚኒስቴሩ ደግሞ አራት ድሮኖች በሞስኮው ሰሜናዊ አቅጣጫ ወደ ምትገኘው ያሮስላልቭል ግዛት እየበረሩ ሳለ መክሸፋቸውን አስታውቋል። ከሰሜን ዩክሬን ጋር ድንበር በምትዋሰነው ቤልጎሮድ ግዛትም እንዲሁ ጥቃት እንደተሰነዘረባት የግዛቲቱ አስተዳዳሪ ገልጠዋል።...
25 ዓመት የሞላው ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን 139 መንገደኞች እና 6 የበረራ ሠራተኞችን ጭኖ ነበር። የአውሮፕላኑ አካል እንደጠፋ ሳይታወቅ አውሮፕላኑ ቢያርፍም ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰም።
...
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በወንበዴ ቡድኖች እየታመሰች ካለችው ሄይቲ ዜጎቿን በልዩ በረራ እንደምታስወጣ አስታወቀች።
በዓለም ላይ ስማቸው ከገነነ ሙዚቀኞች መካከል አንዷ ናት - አያ ናካሙራ። አያ በፈረንሳይኛ በመዝፈን ከቋንቋው ተናጋሪዎች ባሻገር በዓለማችን ተደማጭ ከሆኑ ጥቂት ሙዚቀኞች መካከል አንዷ ናት። በዚህም ከወራት በኋላ በፓሪስ በሚካሄደው የኦሊምፒክ ውድድር መክፈቻ ላይ እንድትዘፍን ተመርጣለች። ነገር ግን ይህ ውሳኔ በፈረንሳውያን ዘንድ ውዝግብን አስከትሏል። ለምን?...
Ethio 360 Zare Min Ale ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በስተጀርባ የመሸገው የጥፋት ኃይልና የዛሬ የፋኖ ድል! Saturday March 16, 2024
Maedot 1 Media Daily News March 16/2024 #anchorethiopia #ethio360 #orthodox #merejatv #derenews
ሔለን የወር አበባ ማየት ብታቆምም ልጅ ለማግኘት የተለያዩ የህክምና ባለሙያዎችን ጎብኝታ የተሰጣትን መድኃኒት ብትወስድም ለውጥ አላገኘችም። አሁን ግን ተስፋ ሊሰጥ የሚችል መፍትሔ እንዳገኘች ትናገራለች። ይህም እንቁላል የምትለግሳት ሴት ካገኘች ማርገዝ እንደምትችል ተነግሯታል።
ይህን ዓይነቱን ህክምና የሚሰጠው ደግሞ በመቀለ ከተማ በሚገኝ አንድ የህክምና ማዕከል ነው። እንዴት? ምን ያህልስ ሕጋዊ ነ...
ከፈረንሳይ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም በባሕር በኩል ሲያቋርጥ የሞተ አንድ የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ በፈረንሳይ መንግሥት ላይ ክስ መሠረተ።
ላታም የተባለው አየር መንገድ ንብረት በሆነ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን ላይ ያለ ቁልፍ በድንገት በመነካቱ በመንገደኞች ላይ ቀላል ጉዳት ካጋጠመ በኋላ ምርመራ ተጀመረ።...
የኬንያ መንግሥት የገቢዎች ባለሥልጣን አዳዲስ ሠራተኞችን ለመቅጠር የእርግዝና እና የኤችአይቪ/ኤድስ ምርመራ አድርጎ አመልካቾችን ውድቅ ማድረጉ ጥያቄ አስነሳበት።...
በሱዳን ውስጥ እየተካሄደ ያለው ጦርነት የጽንፈኛ እስላማዊ እንቅስቃሴ ወደ አካባቢው የሚመለስበትን ሁኔታን ሊያባብስ ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው አዲሱ በሱዳን የአሜሪካ መልዕክተኛ ቶም ፔሪዬሎ ለቢቢሲ ተናገሩ።...
ዋዜማ- በአዲስ አበባ በተለያየ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች በማያውቁት ስልክ እየተደወለላቸው ገንዘብ እየተጠየቁ ፤ ገንዘቡን የማይሰጡ ከሆነም ለደህንነታቸው የሚያሰጋ ማስፈራርያ እየደረሰባቸው እንደሆነ ዋዜማ ካሰባሰበችው መረጃ ተረድታለች ።
አዳማና ባህርዳር ያሉ ባለሀብቶችም በታጣቂዎች ከአንድ ጊዜ በላይ ገንዘብ መጠየቃቸውን ነግረውናል።
እየደወሉ በማስፈራርያ ገንዘብ የሚጠይቁ ግለሰቦች ፤ ባለሀብት ነው ብለው ያሰቡትን ሰው ሙሉ አድራሻ ብቻ ሳይሆን ፤ በባንክ ውስጥ የሚያንቀሳቅሱትን ገንዘብ እና የባንክ መረጃቸውን የሚያውቁ መሆኑ ደግሞ በግለሰቦች ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ተረድተናል ።
ለዚህ ዘገባ ሲባል ጉዳያቸውን የተከታተልነው እና ለደህንነታቸው ስማቸው እና የኩባንያቸው ስም እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ ግለሰብ ፤ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ማምረቻ ፋብሪካ አሏቸው ሌሎች የንግድ ስራዎች ላይም ተሰማርተዋል ።
ሆኖም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በስልካቸው እየተደወለ መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ እየተጠየቁ ፤ ይህን ማድረግ የማይችሉ ከሆነ ዛቻ እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል።የሚደውሉላቸው ሰዎች ግለሰባዊ ጉዳዮቻቸውን ሳይቀር የሚያውቁበት ደረጃ ስላሰጋቸውም መጀመርያ ይኖሩበት ከነበረበት ቦታ ሁለት ግዜ የመኖርያ ሰፈር እንደቀየሩም መረዳት ችለናል።ሁኔታውን በስራ እና ኑሯቸው ላይ ስጋት እንደፈጠረባቸውም ገልጸዋል ።
ሌላው ባለሀብት እንዲሁ በአዲስ አበባ በንግድ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ፤ በተመሳሳይ በስልክ እየተደወላላቸው መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብን እየተጠየቁ እንደሆነ ያስረዳሉ። በዚሁ ሳቢያ የእጅ ስልካቸውን ለቤተሰብ አባላቸው ሰጥተው በሌላ ስልክ እንደሚጠቀሙ ይገልጻሉ ።ሆኖም ለቤተሰብም እንፈልጋቸዋለን እየተባለ እንደሚደወል ይናገራሉ ።
ለዚህ ዘገባ ጉዳያቸውን የተመለከትናችው ግለሰቦች ከሚደውሉላቸው ሰዎች ንግግር በመነሳት ገንዘብ ካላመጣችሁ ብለው
የኤርትራ መንግሥት፣ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ዋና ጸሃፊ ኤሊዜ ኪሪስ “ኤርትራ ሕግ የሌለባት አገር ናት” በማለት በተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በቅርቡ መናገራቸውን አጣጥሎታል።
የኤርትራ መንግሥት፣ ረዳት ዋና ጸሃፊዋ የኤርትራ ወታደሮች ትግራይ ውስጥ እንደሚገኙ መግለጣቸው፣ አውቀውም ኾነ ሳያውቁ የዓለማቀፉን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ አለመቀበላቸውን ያሳያል በማለት ተችቷል።
ሃላፊዋ ያወጡት መግለጫ፣ ያልተረጋገጡና ሐሰተኛ መረጃዎችን ያካተቱ እንደኾነም ኤርትራ ጠቅሳለች።
የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ዓለማቀፍ ወንጀል ፈጽማ የማታውቀውን ኤርትራ ለቀቅ አድርጎ፣ በሌሎች የዓለም ክፍሎች ለሚፈጸሙ ዓለማቀፍ የመብት ጥሰቶች ቅድሚያ ቢሰጥ ይሻላል በማለትም ኤርትራ መክራለች።
የአሜሪካ ዓለማቀፍ ተረድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ አይ ዲ) ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ትናንት በድጋሚ በመቀሌ ጉብኝት አድርጓል።
በሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ የዋና ዳይሬክተሯ ረዳት ሶናሊ ኮርዴ የመሩት ልዑካን ቡድን፣ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ሃላፊዎች ጋር በክልሉ በተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስና በወቅታዊ ኹኔታዎች ዙሪያ መክሯል።
ልዑካን ቡድኑ ወደ አፋር ክልልም አቅንቶ፣ የዕርዳታ ሥርጭት ሂደቱን ተመልክቷል።
ከጥር ወር ወዲህ፣ ድርጅቱ በትግራይ፣ አፋር፣ አማራ፣ ኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች ለ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ተረጂዎች አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ማቅረቡን ገልጧል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሚጻፍ ደብዳቤ ከአራት ወራት በፊት የታሰረው ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ከእስር እንዲፈታ የሚጠይቅ ዘመቻ ጀመረ።...
አራት ተማሪዎችን በሚቺጋን ትምህርት ቤት ተኩሶ የገደለው አሜሪካዊ ታዳጊ አባት በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተባለ።
በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሠፋ መዝገብ ስር ከተካተቱት 53 ተከሳሾች መካከል 21ዱን በተመለከተ ዛሬ ፍርድ ቤት ሦስት ውሳኔዎችን አሳለፈ ። ከ21ዱ ውጪ ቀሪ ተከሳሾች በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው መወሰኑንም ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ሰለሞን ገዛኸኝ ዛሬ ለዶይቸ ቬለ በስልክ ተናግረዋል ።...
በስላም ተጀምረዉ የሚጠናቀቁ የኢትዮጵያ ሀይማኖታዊና ህዝባዊ የአደባባይ በዓላት ከቅርብ ግዜ ወዲህ የመንግስት የፀጥታ ችግር እየሆኑ መጥተዋል፤ በዓላቱን ከሚታደሙት ታዳሚውን የሚጠብቁት እየበለጡ፤ የከተማው መንገድ እየተዘጋ በአብዛኛው አንዳንዴ ከበዓሉ 2 ቀናት በፊት ጭምር እየተዘጋ ለእንቅስቃሴ ፈተና የሚሆንበት ግዜ እየጨመረ መጥቷል ተባለ።...
ለሥራ ማስኬጅያ ከመንግሥት የተሰጠውን 2.7 ሚሊዮን ብር ከታለመለት ዓላማ ውጪ ማዋሉ እና ከፍተኛ ገንዘብ ለፓርቲው አመራሮች እና ሌሎች አባላት የግል ጥቅም አውሏል የተባለው አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የወንጀል ምርመራ እንዲደረግበት ተጠየቀ። ፓርቲው እና አመራሮቹ እንዲታገዱ መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።...
ለአንድ ሳምንት ያህል የዘለቀው እና ሩሲያ የተካሄደው የዓለም ወጣቶች ፌስቲቫል ባለፈው ሳምንት ሀሙስ ተጠናቋል። በዚህ ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያን ወክለው 70 የሚሆኑ ወጣት ኢትዮጵያውያን ተካፍለው ነበር።ስለ ፌስቲቫሉ እና ተሞክሯቸው ጠይቀናል።...
የከተመን ማክተም፤ ድሃ ጠል የከተማ ዝመና ፖሊሲ ውጤት ነው ፟ ( ያሬድ ሃይለማርያም ፡ የሰብዐዊ መብት ተሟጋች )
+++++
“Eviction is a cause, not just a condition, of poverty.”
Matthew Desmond
የዛሬው የመልዕክተ ቅዳሜ ትኩረት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እና በዙሪያዋ እየታየ ያለው የጅምላ ቤት ፈረሳ እና የዜጎች ስቃይና እንግልት ላይ ነው። ለአብዛኛው የአገራችን ሕዝብ ትንሽ የምትባለውም ደሳሳ ጎጆ ሁሉ ነገሩን ያሳረፈባት ደሴቱ ነች። ያችን ደሴቱን ስታፈርስበት ልክ አውላላ ውቂያኖስ መሃል አንድ መዋኘት የማይችልን ሰው ከነቤተሰቡ ዋኝተህ ውጣ ብለህ ከጀልባ ላይ እንደወረወርከው ያህል ነው የሚቆጠረው። በዛሬዋ ኢትዮጵያ ሚሊዮን ዜጎች ይህ እጣ ፈንታ ገጥሟቸዋል። ልጆቻቸውን ይዘው፣ እቃቸውን በየሜዳው ላይ በትነው፣ ገሚሱም ተዘርፎባቸው በተንጣለለ ውቃኖስ መሃል የመጣል ያህል አደጋ ተጋርጦባቸዋል። በላዩ ላይ መቆሚያ ያጣው የኑሮና የገበያ ግሽፈት በውቂያኖሱ ላይ የሚጋልብ ማዕበል ነው። ሌሎች ሚሊዮኖች ደግሞ ይሄው እጣ ፈንታ ዛሬ ወይ ነገ ይገጥመናል በሚል አንድ አይናቸውን ጨፍነው ተኝተው እንድ አይናቸውን ገልጠው በሌሊት በተኙበት መጥተው በላያቸው ላይ ቤት የሚንዱና የሚያፈርሱ ሕገ ወጥ ግብረሃይሎችን ኮቴ ሲጠባበቁ ያድራሉ። ያገዛዝ ሥርዓቶቹ አንድ ያልተረዱት ነገር ቢኖር ከመሬቱና ከቤቱ በከተማ ዝመና ወይም በልማት ስም ያፈናቀልከው ሕዝብ ከልቡ ፈንቅሎ ይጥልሃል። ሕዝብ ከልቡ ያወጣው ሥርዓት ደግሞ አክራሞቱ በግጭት የተሞላ ብቻ ሳይሆን አወዳደቁ እጅግ የከፋና ዘግናኝ መሆኑን ነው።
የከተማ ዝመና እና ሰፋፊ የልማት ሥራዎች ሁሌም የሚነሳባቸው ጥያቄ ምን ያህል ሰዋዊ ገጽታ አላቸው
የአብይ ቀይ መስመር ለአባቶች – የእስክንድር ነጋ የቪዲዮ መልዕክት
!function(r,u,m,b,l,e){r._Rumble=b,r[b]||(r[b]=function(){(r[b]._=r[b]._||[]).push(arguments);if(r[b]._.length==1){l=u.createElement(m),e=u.getElementsByTagName(m)[0],l.async=1,l.src="https://rumble.com/embedJS/u4"+(arguments[1].video?'.'+arguments[1].video:'')+"/?url="+encodeURIComponent(location.href)+"&args="+encodeURIComponent(JSON.stringify([].slice.apply(arguments))),e.parentNode.insertBefore(l,e)}})}(window, document, "script", "Rumble");
Rumble("play", {"video":"v4gw84h","div":"rumble_v4gw84h"});
በናይጄሪያ፣ ባለፈው ሳምንት በታጣቂዎች ለተጠለፉት ከ250 ለሚበልጡ ተማሪዎች፣ የመንግሥቱ የጸጥታ ኀይሎች ፈጽሞ የማስለቀቂያ ገንዘብ እንዳይከፍሉ፣ ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ ትዕዛዝ እንደሰጡ የአገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር ተናገሩ፡፡...
ሩሲያ የቫግነር ግሩፕን መጠሪያ “ልዩ የውጭ ተልዕኮ ክፍለ ጦር” በሚል ስያሜ ቀይራለች። በአሁኑ ጊዜ ኢ-መደበኛው ሠራዊት፣ በሩሲያ የወታደራዊ ደኅንነት ክፍል ዕዝ ሥር እንዲውል ተደርጓል። ...
Ethio 360 Zare Min Ale "የኦህዴድን አከርካሪ እየሰበሩ ያሉ አዳዲስ ድሎች!" Friday March 15, 2024
በአፋር ክልል በኢሳ እና አፋር ጎሳዎች መካከል ግጭት መቀጠሉ ተሰምቷል ።
ትናንት በአፋር ክልል ዞን 6 ወይም ማሂ ረሱ ዞን ውስጥ በሚገኘውና አፋር እና ሶማሌ ክልሎች በሚወዛገቡበት አዳዶ ወረዳ በኹለቱ ጎሳዎች መካከል ግጭት ማገርሸቱን ምንጮች ተናግረዋል።
በኹለቱ ጎሳዎች መካከል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተደጋጋሚ ግጭቶች የተከሰቱ ቢኾንም፣ ኹለቱ ክልሎች ግን ስለ ጎሳ ግጭቶች መግለጫ ሲያወጡ አይሰሙም።
የጎሳ ግጭቱ ትናንት በድጋሚ ያገረሸው፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስተባባሪነት የኸለቱ ክልሎች የጎሳ እና የአገር ሽማግሌዎች ተገናኝተው ከመከሩና ለግጭቶችና አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሄ ለመፍታት ጠቅላይ ምክር ቤቱ የሚመራው መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ካቋቋሙ ከጥቂት ቀናት በኋላ ነው።
ዋዜማ ራዲዮ
18 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በኬንያ ዋጅር ተያዙ
በኬንያ ዋጅር ካውንቲ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገሪቱ ገብተዋል የተባሉ 18 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የዋጅር ፖሊስ ገልጿል።
18ቱ ፍልስተኞች የተያዙት በዛሬው እለት ኮሮንዲሌ በሚባል የከተማይቱ አውራጃ በተደረገ ኦፕሬሽን መሆኑ ተነግሯል።
ፍልሰተኞቹ በኮሮንዲሌ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ ሲሆን በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኬንያ በመግባት ክስ እንዲመሰረትባቸው የሚያስችለውን ሂደት በመጠባበቅ ላይ እንዳሉ ተጠቁሟል።
በኬንያ በህገ-ወጥ መንገድ ገብተው የተገኙ የሌላ ሀገር ዜጎች የመባረር ወይም እስራት ሊገጥማቸው እንደሚችል ሲገለፅ በተጨማሪም፣ በኬንያ የኢሚግሬሽን ህጎች በተገለፀው መሰረት ቅጣት ሊጣልባቸው እንደሚችልም ነው የተገለፀው።
አሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የግጭትና መረጋጋት ረዳት ሚንስትር የኾኑት አን ዊትኮውስኪ ከመጋቢት 8 እስከ 17 በኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሞዛምቢክ ይፋዊ ጉብኝት ያደርጋሉ።
ረዳት ሚንስትሯ በኢትዮጵያ እና ኬንያ በሚኖራቸው ቆይታ፣ አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን ለቀጠናዊ ጥረቶች የምታደርጋቸውን ጥረቶች ለማጠናከር ያለመ ውይይት እንደሚያደርጉ መስሪያ ቤታቸው ዛሬ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።
ረዳት ሚንስትሯ፣ በሦስቱ አገራት ከመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከሲቪል ማኅበረሰብና ከዓለማቀፍ አጋሮች ተወካዮች ጋር የግጭት ተጎጂ ማኅበረሰቦችን መልሶ ለማቋቋም በማደረጉ ጥረቶች ዙሪያ ጭምር እንደሚወያዩና አሜሪካ በዚኹ መስክ ለሦስቱ አገራት እያደረገች ያለችውን ድጋፍ እንደሚገመግሙ ተገልጧል።
ለ2 ሳምንት ያህል ታግተው የነበሩ 5 የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች ተገድለው መገኘታቸውን ስሜ አይጠቀስ ያሉ አንድ የፋብሪካው ኃላፊ ተናገሩ።
እኚሁ ኃላፊ ለቢቢሲ አማርኛው ክፍል በሰጡት ቃል ፤ የአምስቱ ሠራተኞች አስከሬን ዛሬ ጠዋት መጋቢት 6/2016 ዓ.ም. መገኘቱን ገልጸዋል።
” አስከሬናቸው ከፋብሪካው ማሳ ወጣ ብሎ ጨካ በሚባል የገጠር አካባቢ ነው የተገኘው ” ብለዋል።
ከተገደሉት መካከል 3ቱ ሠራተኞች ከወንጂ አካባቢ ሲሆኑ፣ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ዛሬ ተፈፅሟል።
ሁለቱ ሠራተኞች አንደኛው ከአዳማ የመጣው ቀብሩ ዛሬ የተፈፀመ ሲሆን ሌላኛው ከደሴ የመጣው ግለሰብ አስከሬን ወደ ስፍራው ተልኳል ተብሏል።
4ቱ ሠራተኞች በፋብሪካው ውስጥ በትራክተር ኦፕሬተርነት ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ እና ዕድሜያቸው ከፍ ያለ እንደሆኑም ተገልጿል።
ሌላኛው የኤሌክትሪክ ሠራተኛ (ፎርማን) ወጣት ሲሆን በቅርብ የተቀጠረ እና ለአንድ ዓመት ያህል በፋብሪካው አገልግሏል።
አንደ ኃላፊው ገለጻ ከሆነ ግለሰቦቹ ከሁለት ሳምንታት በፊት የአዳር ስር ላይ ምሽቱን አሳልፈው ጥዋት ላይ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ” ዶዶታ ” ከሚባለው ፋብሪካው ከሚገኝበት ስፍራ በታጣቂዎች ታግተው ተወስደዋል።
ሠራተኞቹን ያገቷቸው ሰዎች ገንዘብ ጠይቀው እንደነበር ? ወይም የጠየቋቸው ጉዳዮች እንዳሉ ዝርዝሩን እንደማያውቁ አስረድተዋል።
ነገር ግን ፋብሪካው ከአጋቾቹ በኩል ምንም ነገር እንዳልተጠየቀ ገልጸው፣ ወዲያውኑ ለመንግሥት አካል ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።
ፓሊስም ሠራተኞቹን ለማስለቀቅ እየተከታታለ እንደነበር የገለጹት ኃላፊው ነገር ግን አስከሬናቸው ዛሬ ጥዋት 2 ሰዓት አካባቢ ተገኝቷል ብለዋል።
ስለ ግድያው እንዴት ? እና ስንት ሰዓት ? ተፈጸመ የሚለውን ባያውቁም ምናልባትም ትናንት ምሽት ተገድለዋል
የአሜሪካ የላይኛው ምክር ቤት አባላት የባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ እንዲሰጥ ጠየቁ
የአሜሪካ የላይኛው ምክር ቤት አባላት ሴናተር ቲና ስሚዝ፣ ጄፍ ሜርክሌይ፣ ኤሚ ክሎቡቻር፣ ጆን ሂክንሎፐር፣ ክሪስ ቫን ሆለን፣ እና ቲም ኬይን፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ እንዲሱጡ ጠይቀዋል።
ሴናተሮቹ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አንቶኒ ብሊንከን እና የአሜሪካ አለማቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) ዋና ዳይሬክተር ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ በጦርነት እና ግጭት ምክንያት ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ ድጋፍ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጡ በፃፉት ደብዳቤ ጥሪ አቅርበዋል።
በኢትዮጵያ ያለው የእርስ በርስ ግጭትና የአየር ንብረት መዛባት በሀገሪቱ ያለውን አስከፊ ሰብዓዊ ቀውስ አባብሶታል ያሉት የምክር ቤት አባላቱ 4.4 ሚሊዮን ሰዎች በአገር ውስጥ እንደተፈናቀሉና ኢትዮጵያ ወደ 942,ሺ የሚጠጉ የጎረቤት ሀገራት ስደተኞችን አስጠልላ እንደምትገኝ ገልፀዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ 20.1 ሚሊዮን የሚገመቱ ሰዎች አፋጣኝ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ሴናተሮቹ የጠቆሙ ሲሆን በኢትዮጵያ በ2024 የሰብዓዊ እርዳታ እቅድ መሰረት ለዜጎች ድጋፍ ለማድረግ 3.24 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገውና ለ6.6 ሚሊዮን ሰዎች የምግብ እርዳታ ለማድረግ 500 ሚሊዮን ዶላር በአስቸኳይ የሚያስፈልግ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ሴናተሮቹ የባይደን አስተዳደር በሀገሪቱ የሚደረገውን ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማሳደግ ከሌሎች ለጋሽ አገራትና የተራድኦ ድርጅቶች ጋር እንዲተባበር የጠየቁ ሲሆን በተጨማሪም በሀገሪቱ ሰብአዊ ፍጡራን ላይ ተፅዕኖ የሚያደርጉ ግጭቶችን ለማስወገድ ግፊት እንዲደረግም ጠይቀዋል።
በአብይ አህመድ አገዛዝ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በር ላይ ታፍነው ከተወሰዱ ተማሪዎች መካከል፦
1 ,ጆን ተሻገር
2, ቃልኪዳን እያሱ
3, ቴዎድሮስ ይበልጣል እና
4, አራጋው ሞሳው ይገኙበታል።( ምስላቸው ከታች ይገኛል
ከተማሪዎቹ መካከል ሦስቱ የ4ኛ አመት እና አንደኛው ደግሞ የ3ኛ አመት የህግ ተማሪዎች መሆናቸውን ለማወቅ ችለናል። ተማሪዎቹም እስካሁኗ ሰዓት የት እንዳሉ እንደማይታወቅ ከቅርብ ጓደኞቻቸው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በአብይ አህመድ አረመኔአዊ አገዛዝ አማራ ከሆንክ የትም እና በምንም አይነት ሁኔታ ትታገታለህ፣ ትታፈናለህ፣ ትገደላለህ፣ ትፈናቀላለህ።
በታዋቂው ቱር ደ ሩዋንዳ የብስክሌት ውድድር ላይ ቢቢሲ የኢትዮጵያ ተወዳዳሪዎችን ሁኔታ በቅርበት ተመልክቷል። የመወዳደሪያ ብስክሌት እና ትጥቅ፣ በቂ የዝግጅት ጊዜ እና ድጋፍ የሌላቸው ተወዳዳሪዎች ውድድሩን እንዳይጨርሱ ምክንያት እንደሆናቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የብስክሌት ስፖርት ፈተናዎች አገሪቱ ወደፊት በዘርፉ እንዳትሳተፍ እንቅፋት ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት በስፖርተኞቹ ላይ ፈጥሯል።...
እስራኤል እደመስሰዋለሁ ብላ የተነሳችው ሐማስ የፍልስጤማውያን ፖለቲካዊ፣ ርዕተ ዓለማዊ፣ ማኅበራዊ እንዲሁም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ነው። ሐማስ ጥቃት ከፈጸመባት በኋላ እስራኤል ቡድኑን “ለመደምሰስ” የያዘችው ዕቅድ ሊሳካ የሚችል ነው?...
በፕላስቲክ በተሰራ አነስተኛ ጀልባ ተጭነው በሜዲትሪኒያን ባሕር ላይ ሲጓዙ ከነበሩ ስደተኞች መካከል ቢያንስ 60 ያህሉ መሞታቸውን በሕይወት የተረፉ ተሳፋሪዎች ተናገሩ።...
የኢትዮጵያ መንግሥት የፍትህ ሚኒስቴር በእነ ሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው መዝገብ ቀርበው የነበሩ ክሶች ለሕዝብ ጥቅም ሲባል እንዲቋረጡ መወሰኑን አስታወቀ።
የአል ሻባብ ታጣቂዎች በዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ ከሶማሊያው ፕሬዝዳንት ቤተ መንግሥት አቅራቢያ በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን የደኅንነት ምንጮች እና የዐይን እማኞች ተናገሩ።...
በጎርጎርሳውያኑ 1870 ዎቹ እና 80 ዎቹ ውስጥ ለሞቃታማ አካባቢዎች የሕክምና ምርምር ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረበት ጊዜ ነበር። ጊዜው ደግሞ የአውሮጳ ሃገራት መላው አፍሪቃን ለመቀራመት የሚሯሯጡበት ወቅትም ነበር።...
ከሰሜን እስከ ደቡብ በሚገኙ በርካታ የአፍሪካ አገራት የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡ ተገለጸ።
ቅዳሜ እና እሁድ የፕሪሚየር ሊግ እና ተጠባቂ የኤፍኤ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ይደረጋሉ። በኤፍኤ ዋንጫ ዩናይትድ ከ ሊቨርፑል እንዲሁም ሲቲ ከ ኒውካስል ግጥሚያ ያደርጋሉ። የቢቢሲ የእግር ኳስ ተንታኝ ክሪስ ሱተን የጨዋታዎቹን ግምት እንደሚከለው አስቀምጧል።...
የቻጋ ሕዝብ በአፍሪቃ እጅግ ታዋቂ እና ትልቁ በሆነው የኪሊማንጃሮ ተራራ ተዳፋታማ አካባቢ የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው ። ህዝቡ የተራራውን አናት ኪቦ ብለው ይጠሩታል።
ነገር ግን በዘመናዊው ታሪክ ታንዛንያውያን ተማሪዎች የኪሊማንጃሮ ተራራ በጀርመን ሚሺነሪ ዮሃንስ ሬብማን አማካኝነት በ1848 እንደተገኘ ያስባሉ ።...
የራይንሽ ተልዕኮ ቤተክርስትያን የተባለችው የጀርመን ቤተክርስታያን ከሄሬሮ ህዝቦች ጋር ጥሩ ግንኙነት ፈጥራ እንደነበር ይነገርላታል። ጀርመኖቹ በኦካሃንጃ፣ ኦትጂምቢንግዌ እና በዊንድሆክ በስምምነት አብረው መኖር የጀመሩበት አጋጣሚም ነበር ። በዚህም በርካታ ሄሬሮዎችም ወደ ክርስትና እምነት እንዲመጡ መንገድ ከፍቶላቸዋል።...
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio360
በአዲስ አበባ በጎዳናና በወሲብ ንግድ የሚተዳደሩ ብሎም ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የተዳረጉ ሴቶችን ተጠቃሚ ያደርጋል የተባለው የሴቶች የተሀድሶና የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ዛሬ ተመርቋል፡፡ማዕከሉ በዋነኛነት በሴተኛ-አዳሪነት የተሰማሩትን በመቀበል ሙያዊና ስነ ልቦናዊ ድጋፍና ስልጠናዎችን በመስጠት ወደ ስራ ያሰማራልም ነው የተባለው፡፡...
ፓርቲው የዜጎች ግዲያ መበራከትና ፍትህ አለመስፈን በክልሉ በሰኔ ይካሄዳል በተባለው ምርጫ ላይ ተጽእኖ ሊያሳድር ይችላል የሚል ስጋቱን ገልጿል። የከፍተኛ ፖሊስ መኮንን ጨምሮ በግለሰቦች ላይ በመተከል ዞን እና አሶሳ ዞን ግድያ የፈጸሙ ወደ ህግ አለመቅረባቸው ስጋት የፈጠረና የፍትህ አካላትን ተአማኒነትንም ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ድርጊት ነው ብሏል፡፡...
ህወሓት ከተፈረመ 16 ወራት ያለፈው ውል በከፊል መፈፀሙን፣ በርካታ የስምምነቱ ይዘቶች ደግሞ አሁንም በእንጥልጥል እንዳሉ በውይይቱ መነሳቱን ገልጿል።ህወሓት በስምምነቱ መሰረት ከመከላከያ ሰራዊት ውጭ የሆኑ ሐይሎች አሁንም ከትግራይ አለመውጣቸውን፣ 40 በመቶ የትግራይ ግዛት አሁንም ወደ ክልሉ አስተዳደር እንዳልገባ ማንሳቱን በመግለጫው ጠቁሟል።...
የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ ለማስፈታት፣ ለመበተን እና ወደ ማህበረሰቡ መልሶ ለማዋሃድ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ የገለፁት የበለፀጉ ሀገራት በአማራ በኦሮሚያና በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተከሰቱት ቀውሶች በተመሳሳይ ቁርጠኝነት ችግራቸው እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል። ሁለቱ ወገኖች በቂት ወራት ተመሳሳይ ውይይት ለማድረግ ስለመወሰናቸውም ተነግሯል።...
የክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በክልሉ የመምህራንን ደሞዝን ጨምሮ ሌሎች የፋይናንስ ውጪዎችን ለማሟላት ያልተቻለው የገቢ አሰባሰብ በሚፈለገው መጠን ባለመሠራቱ መሆኑን ተናግረዋል ። በቀጣይ የፋይናንስና የገቢ ሰብሳቢ ተቋማትን አቅም በማጠናከር የደሞዝ ክፍያን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ጥረት እንደሚደረግ ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል ፡፡...
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ከእስር ተፈቱ
ላለፈው አንድ ወር ከ12 ቀን በእስር ላይ የቆዩት፤ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ዛሬ ከሰዓት መለቀቃቸውን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ)፣ የቀድሞው የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘውም “በምህረት” ከእስር እንደሚፈቱ ታማኝ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ዶ/ር ደሳለኝ “በዋስትና እንደሚለቀቁ” የተነገራቸው፤ ዛሬ ምሳ ሰዓት ገደማ መሆኑን በስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ገልጸዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ፤ ጥር 22፤ 2016 ምሽት በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ታስረው የቆዩት በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው የፌደራል የወንጀል ምርመራ የእስረኞች ማቆያ ስፍራ ነው።
ዶ/ር ደሳለኝ ከእስር ከመለቀቃቸው ከሰዓታት በፊት በተካሄደ የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ፤ ከፓርላማው “የምክር ቤት ጉዳዮች አማካሪ ኮሚቴ” አባልነታቸው ተነስተዋል። ይህ ኮሚቴ “የተወካዮች ምክር ቤት የሚወያይበትን ማንኛውም አጀንዳ የመቅረጽ” ኃላፊነት ያለበት ሲሆን የሚመራው በፓርላማው አፈ ጉባኤ ነው። በዛሬው ስብሰባ፤ ላለፉት ሰባት ወራት በእስር ላይ ያሉት ሌላኛው የአብን የፓርላማ ተወካይ አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት መነሳቱ ይታወሳል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ጀርመናዊትዋ የፊልም ተዋናይ ሳንድራ ሁለር በምርጥ ዘርፍ ተዋናይት ኦስካር ባታሸንፍም፤ የሚሊዮኖችን ልብ በተወነችበት ፊልም አግኝታለች። ቀደም ሲል አዉሮጳ ላይ ሽልማትዋን እንድትወስድ ወደ መድረክ ስትጠራ፤ በአዳራሹ የነበረዉን ህዝብ ለዓለም ሰላም በፀጥታ መልክት እንዲያስተላልፍ ለሰላም እንዲቆም ጠይቃ ነበር።...
ዋሽንግተን ዲሲ — በሶማሊኛ ቋንቋ የሚተላለፈው ‘ካልሳን ቲቪ’ የቀድሞ ዘጋቢ እና ከአንድ ወር በፊት በሶማሌ ክልል ውስጥ የታሰረው ሙሄዲን መሐመድ፣ ያለቅድመ ኹኔታ በአስቸኳይ እንዲለቀቅ፣ ሲፒጄ ጠየቀ።
ጋዜጠኞችን በዘፈቀደ ማሰርም መቆም እንደሚገባው፣ የጋዜጠኞች ደኅንነት ተሟጋች ድርጅቱ አሳስቧል፡፡
መቀመጫውን ለንደን ላደረገው ‘ካልሳን ቲቪ’ የሶማልኛ ቋንቋ ብዙኀን መገናኛ ሲሠራ የነበረው...
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አዲስ አበባን ጨምሮ ከተለያዩ ክልሎች ተወካዮች ጋር ተከታታይ ውይይቶች ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ወክለው በውይይቶቹ የተገኙ ግለሰቦች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በርካታ ጥያቄዎች አቅርበዋል፡፡ ከጥያቄዎቹ መካከል የልማትና የፀጥታ ጉዳዮች ሰፊ ትኩረት ያገኙ ነበሩ፡፡ የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ፣ የውኃ፣ የጤና፣ የትምህርትና መሰል መሠረተ ልማቶች ከኑሮ ውድነትና ተዛማጅ ጉዳዮች ጋር ተነስተው ነበር፡፡ በፀጥታ ጉዳይም በየአካባቢው በሚካሄዱ ግጭቶች ምክንያት እየደረሱ ያሉ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳቶች በስፋት ተዳሰዋል፡፡ ብዙዎቹ የተነሱት ጥያቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ በገዥው ፓርቲና በሚመሩት መንግሥት የሚታወቁ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ምላሽ ሲሰጡ ጥያቄዎቹን ተራ በተራ በማንሳት በማነፃፀሪያዎች እያስደገፉ ነበር፡፡ ሕዝብና መንግሥት በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ሊያግባባቸው የሚችል አማካይ እንዲኖር አንዳንድ መሠረታዊ ጉዳዮች መነሳት አለባቸው፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ ‹‹በወንዝ ዳር ፕሮጀክት›› እና ‹‹በመንገድ ኮሪደር ልማት›› መርሐ ግብሮች፣ ይዞታዎችን የማፍረስና አጥሮችን ወደ ውስጥ የማስገባት ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ነው፡፡ ‹‹ስማርት ሲቲ›› በተሰኘው ከተማን የመለወጥ ግዙፍ እንቅስቃሴ፣ የከተማዋን ገጽታ የሚለውጡ ተግባራት ሲከናወኑ በከተማ አስተዳደሩና በነዋሪዎች መካከል መግባባት መኖር አለበት፡፡ አገሩ ወይም ከተማው በልማትና በዕድገት ስትለወጥለት የሚጠላ ዜጋ ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ልማቱም ሆነ ዕድገቱ የጋራ ሲሆን፣ ከአንድ አካባቢ ተነስተው ወደ ሌላ የሚሠፍሩ ዜጎች፣ በተቻለ መጠን ከነበሩበት ያላነሰ ተስማሚ የመኖሪያና የመሥሪያ ቦታ ማግኘታቸው መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ በከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ እንደተነገረው ነዋሪዎች የተሻለ መኖሪያና መሥሪያ አግኝተው ከሆነ መልካም ነው፡፡ ነገር ግን የተባለውና እየተደረገ ያለው የማይመጣጠን ከሆነ ማስተካከያ
የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር (አብዲ ኢሌ) ከእስር መፈታታቸውን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ። ከስድስት ዓመት በፊት ነሐሴ 21/2010 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውለው አስካሁን በእስር ላይ የቆዩት አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር ከእስር የተለቀቁት ዐቃቤ ሕግ ክሱን በማንሳቱ መሆኑን ጠበቃቸው ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።...
በዮናስ አማረ
ኒቫዳ ግዛት በአሜሪካ ለመናፈሻ እየተባለ የሚተከል የሳር መስክን በመከልከል የመጀመሪያዋ ግዛት መባሏን፣ ቢዝነስ ኢንሳይደር ከዘጠኝ ወራት በፊት በለቀቀው አጭር ዶክመንተሪ መግለጹ ይታወሳል፡፡ ናሽናል ጂኦግራፊ ከስምንት ዓመታት በፊት በሠራው ዘጋቢ ፊልም፣ በካሊፎርኒያም ቢሆን ለምለም የሳር መስክ መናፈሻ መሥራት እየቀረ የመጣ ፋሽን ስለመሆኑ ይተርካል፡፡ በአሜሪካ በተለይ ሞቃታማ በሚባሉ ምዕራባዊ የአገሪቱ ክፍሎች የሳር መናፈሻ መሥራት እየተተወ የመጣ መሆኑ ይነገራል፡፡ ይህ የሆነው ደግሞ በእነዚህ የአገሪቱ ክፍሎች የሕዝብ ቁጥር መጨመርና የከተሜነት መስፋፋት ብቻ ሳይሆን፣ ከአሥር ዓመታት በላይ በአካባቢው በተከሰተው ድርቅ አስገዳጅነትና በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ጭምር መሆኑን የተለያዩ ዘገባዎች ይጠቁማሉ፡፡
የአሜሪካ ቱጃሮች የግል ጎልፍ ሜዳ በመገንባት ሰፊ ሔክታር መሬት ሳር ያለብሳሉ፡፡ የሌላቸው ደግሞ በቅጥር ግቢያቸው ወይም በደጃቸው ያለ መሬትን ሳር ማልበሳቸው የተለመደ ነው፡፡ የከተማ ማዘጋጃ ቤቶች፣ የመንገድና የመናፈሻዎች ልማት የሚመለከታቸው ሁሉ ብዙ ቦታዎችን በሳር መሸፈን ልማዳቸው ሆኖ መቆየቱ ይነገራል፡፡ ይህ ሁሉ በየቦታው መሬቱን የሳር መስክ ለማልበስ የሚደረግ ጥረት ደግሞ፣ በየቀኑ 34 ቢሊዮን ሊትር ውኃ የሚፈልግ ሥራ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በአሜሪካ በአየር ንብረት ለውጥና በድርቅ ተፅዕኖ የተነሳ ይህን እያደረጉ መቀጠል አገሪቱን ለኪሳራ እንደዳረገ ይነገራል፡፡ ሳር ማብቀል ከፍተኛ የመስኖ ውኃ የሚጠይቅ በመሆኑ፣ ዜጎች ድርቅ የሚቋቋሙ ተክሎችን በምትኩ ለመናፈሻና ለውበት እንዲጠቀሙ ግፊትና ግዴታ መደረግ ስለመጀመሩ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ሲዘገብ ቆይቷል፡፡
በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየቦታው በለመለመ ሳር እንዲሸፈኑ የሚደረጉ መናፈሻዎችና የመንገድ ዳር ልማቶች ይታያሉ፡፡ ኢትዮጵያ ድርቅ ደጋግሞ