Home › Archive for Ethiopian News
Blog Archives
ትምህርት ቤቶቹ የተዘጉት ከባለፈው የመጋቢት ወር ጀምሮ ደሞዝ አልተከፈለንም ያሉ መምህራን ሥራ በማቆማቸው ነው ተብሏል ፡፡ የትምህርት ቤቶቹን መዘጋት ለዶቼ ቬለ ያረጋገጡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር ሊቀመንበር በበኩላቸው “ የመምህራኑን ጥያቄ ለመፍታት ማህበሩ ከዞን እና ከክልል ትምህርት ቢሮች እየተነጋገረ ይገኛል “ ብለዋል...
የጀርመን ፌዴራል ፕሬዝደንቶች በሥልጣን ላይ እያሉ መጽሐፍ መፃፍ ብዙ ጊዜ የተለመደ ባይሆንም፤ ከሰባት ዓመታት በላይ ጀርመንን በፕሬዚዳንትነት እየመሩ ያሉት ፍራንክ ዋልተር ሽታይንማየር ይህንን አድርገዋል።ሽታይንማየር በቅርቡ ባወጡት «እኛ» በተሰኘው አዲሱ መጽሃፉቸው በብዝሃነት ውስጥ አንድነትን ይፈልጋሉ።...
የሰላም ጥሪ ምንጊዜም ተቀባይነት ያለው ሀሳብ መሆኑን የገለፁ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች፤ ይልቁንም ፓርቲዎች መሰል ጥሪ ሲያደርጉ መቆየታቸውን በመግለጽ ሰሚ እንዳላገኙ ገልፀዋል። ይህ የመንግሥት ጥሪ እውነተኛ እና ለዘላቂ መፍትሔ ታምኖበት የተደረገ ስለመሆኑ ጥርጣሬ እንዳላቸውም አብራርተዋል።...
የምስራቅ ሀገሪቱ የአገልግሎት እና የኢንዱስትሪ ማዕከል በሆነችው ድሬደዋ የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት ሽፋን የፍላጎቱን ሃምሳ በመቶ እንኳን እንደማይደርስ የሚያነሳው የመስተዳድሩ ውሀ እና ፍሳሽ ባለስልጣን "ፍላጎት እና አቅርቦት አለመጣጣም" ህብረተሰቡ ለገጠመው ችግር ዋንኛ ምክንያት መሆኑን ገልጿል...
የ25 ዓመት ፎዝያ ጀማል ሳዉዲአረብያ ስትኖር አምስት ዓመት ሆኗታል። የማዳም ቤት ገጣሚ ነኝ፤ የደሴ ልጅ ወሎዬ ስትል ራስዋን ታስተዋዉቃለች። በቲክቶክ የመጽሐፍት አንባብያንና ገጣምያን መድረክ ላይ ግጥሞችዋን በማቅረብም ትታወቃለች። በቅርቡ ቲክታክ ላይ በነበረ የሥነ-ግጥም ዉድድርም አሸናፊ ሆናለች። የግጥም መድብሏ በቅርቡአንባብያን እጅ ይደርሳል።...
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio251
አህጉረ አፍሪካን በፍጥነት በሩጫ በማቋረጥ ክብረ-ወሰን ለመስበር ያለመው ግለሰብ በደኅንነት ስጋት ምክንያት ዕቅዱ ሊከስምበት እንደሆነ ተናግሯል።
ሰኞ ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም. የመን ውስጥ በስደት ሲንከራተቱ ቆይተው ወደ አገራቸው ለመመለስ የተነሱ ሰባ ሰባት ኢትዮጵያውያንን አሳፍራ ወደ ጂቡቲ ያቀናችው ጀልባ ወደ ባሕር ዳርቻው ብትቃረብም በሰላም ካሰበችበት አልደረሰችም። በገጠማት የመገልበጥ አደጋ ከ20 በላይ ኢትዮጵያውያን ባሕር ላይ ቀርተዋል። ከአደጋው የተረፈ አንድ ኢትዮጵያዊ አደጋው እንዴት እንደተከሰተ ለቢቢሲ ተናግሯል።...
በዕድሉ መንገሻ እና አበባ ተስፋዬ በተለያየ ጊዜ ከሱዳን ተነስተው፣ የሊቢያ በርሃን አቆራርጠው፣ የሜድትራኒያንን ባህር ሰንጥቀው ነበር ጣልያን የደረሱት። በዚያ ጉዞ የሰው ልጅ ሊሸከመው የማይችለው ፈተናን አይተዋል። ጭው ባለ በርሃ የሰው ልጆችን የሰውነት ቅሪት እየተመለከቱ፣ እየተደበደቡ፣ እየተራቡ፣ እየተጠሙ እና በህይወታቸው ‘እየቆመሩ’ የተመኟትን ጣልያን ከረገጡ ዓመታትን አስቆጥረዋል። ተስፋ ያ...
በኬንያ መዲና ናይሮቢ በተከሰተ ከባድ ጎርፍ መንገዶች በውሃ ተጥለቅልቀው የታዩ ሲሆን የሀገሪቱ ባለስልጣን የጎርፉ መጠን “እጅግ በከፋ ደረጃ እየጨመረ ነው” ብለዋል።
...
በኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ግቢ ውስጥ ለአንድ ሳምንት ያህል ድንኳኖችን ተክለው በፍልስጤማውያን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት እየተቃወሙ ያሉ ተማሪዎች በተቃውሟቸው እንደሚቀጥሉ ተናገሩ።...
መንግሥትን የሚቃወሙ እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ የታሰረው ኢራናዊ ራፐር በሞት እንዲቀጣ በፍርድ ቤት ውሳኔ መተላለፉን ጠበቃው ገለጸ።
“ክራይስት ኤምባሲ” የተባለው ቤተክርስቲያን መሥራች እና መሪ የሆኑት ናይጄሪያዊው ፓስተር ክሪስ ኦያኪሂሎሜ በስብከታቸው ውስጥ የሚያስተላልፉት መልዕክት ላይ ክስ ይቀርብባቸዋል። በተለይ በክትባት ዙሪያ የሚያሠራጩት የሴራ ትንተና በተለያዩ የአፍሪካ አገራት የሚገኙ ተከታዮቻቸውን ጤና አደጋ ላይ የሚጥል ነው እየተባለ ነው። ፓስተሩ ምን አሉ?...
ባለፈው ሳምንት የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ፍልስጤም የድርጅቱ ሙሉ አባል ለመሆን ባቀረበችው ጥያቄ ላይ ድምፅ ሰጥቷል። ዩናይትድ ስቴትስ ድምፅን በድምፅ የመሻር ሥልጣኗን ተጠቅማ ይህን ጥያቄ ውድቅ ብታደርገውም 12 የምክር ቤቱ አባላት ድጋፋቸውን ሰጥተዋል። ነገር ግን የአገርነት ጥያቄዋ ተቀባይነት አላገኘም። አንዳንድ አገራት ለፍልስጤም የአገርነት ዕውቅና ለምን ይነፍጓታል?...
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio251
የጎንደሩ የምስራች ዜናና የአገዛዙ ውጥንቅጥ
ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ ዛሬ ጠዋት ከቤተሰብ እና ጠበቃው ጋር መገናኘቱ ተገለጸ
ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ “እብደት በሕብረት” የተሰኘ የአንድ ሰው ቴአትሩን ለማሳየት ወደ እስራኤል አገር ሊጓዝ ሲል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት በፖሊሶች መያዙ ይታወሳል።
በአዲስ አበባ ፖሊስ መምሪያ ውስጥ ታስሮ የሚገኘው ተዋናዩ የቅርብ ወዳጅ የሆነው ያሬድ ሹመቴ እንደገለጸው አማኑኤል ሃብታሙ “እጁ ከተያዘበት ሰዓት አንስቶ የተከሳሽነት ቃል ሳይሰጥ እንዲሁ በእስር ላይ” እንደሚገኝ ቤተሰቦቹን ዋቢ አድርጎ ጽፏል።
ይኹን እንጂ የቤተሰብ ጠበቃ የማግኘት መብቱ ተጠብቆለት ከቤተሰብ እና ከጠበቃ ጋር ዛሬ ጠዋት ሊገናኝ መቻሉን እና “በመልካም” ሁኔታ ላይ መኾኑ ተመልካቷል።
በሕጉ መሰረት ወደ ቀጣይ ሕጋዊ ሂደቶች ለማምራት እስከ ነገ የሚሆነውን ለማየትም ቤተሰቦቹ እየተጠባበቁ ነው ተብሏል።
እያዩ ፈንገስ የአንድ ሰው ቴያትር ‘ቧለቲካ’ የተሰኘው ምዕራፉ ለዕይታ ከቀረበ ከእጭር ጊዜ በኋላ ማለትም ከጥር 2 ቀን 2016 ጀምሮ የመንግስት የፀጥታ አካላት ለዓለም ሲኒማ የስራ ሀላፊዎች ባስተላለፉት ትእዛዝ ለህዝብ እንዳይታይ መከልከሉ አይዘነጋም።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከ ‘ ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ‘ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።
በቃለምልልሱ ፥ ባለፉት ሳምንታት በአማራ እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች የነበረው ግጭት በ ” የሚሊሻ አባላት ” መካከል እንጂ መደበኛ ኃይሎች የተሳተፉበት አልነበረም ብለዋል።
” አማራ ክልል በኩል የነበሩ ሚሊሻዎች የተለያዩ አስጊ እንቅስቃሴያዎችን ሲያደርጉ ነበር። በእኛ በኩል ያሉ የሚሊሻ አባላት ምላሽ ሰጥተዋል ” ሲሉ ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ያወጣውን መግለጫም ” መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያላገናዘበ ” ብለዋል።
የሰላም ስምምነቱ ተፈጻሚ እንዳይሆን እያደረገ ያለው ” ሕጋዊ የልሆነ የአማራ አስተዳደር ነው ” ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ጌታቸው በዚሁ ቃለ ምልልስ ፥ በሰላም ስምምነቱ መሰረት በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉትን ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ከስምምነት መደረሱን አስታውሰዋል።
” ሕጋዊ ያልሆኑ አስተዳደሮችን ለማፍረስ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር አብረን እየሠራን ነው። ከአማራ ክልል ጋርም ቢሆን በተወሰነ ደረጃ አብረን እየሠራን ነው ” ብለዋል።
” የፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚሹ አካላት እንዳሉ ግን በጣም እርግጠኞች ነን ” ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ጌታቸው እነዚህ አካላት እነማን እነደሆኑ በግልጽ በስም ጠርተው አልጠቀሱም።
የአገር ጉዳይ ሲነሳ የብዙዎች ቀልብ የሚሳበው ሥጋት ወደ የሚያጭረው የሰላምና የፀጥታ ዕጦት ነው፡፡ በእርግጥም በአሁኑ ጊዜ የአገር ተስፋ የሚያጨልሙ ድርጊቶች ከየአቅጣጫው በብዛት ይስተዋላሉ፡፡ ነገር ግን አገር አጥፊ ከሚባሉ ሥጋቶች ይልቅ በጋራ ብሔራዊ ራዕይ ወደ ልማት፣ ዴሞክራሲ፣ እኩልነት፣ ማኅበራዊ ፍትሕና የጋራ ተጠቃሚነት የሚያሸጋግሩ ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች ላይ ለመረባረብ የሚያስችል ምኅዳር ለመፍጠር መረባረብ ለአገር ይጠቅም ነበር፡፡ ይሁንና የአገሪቱ የፖለቲካ ልሂቃን በሕዝብ ስም በሚያቀነቅኑት የሥልጣንና የጥቅም አጀንዳ ምክንያት፣ ቢያንስ ላለፉት ሃምሳ ዓመታት አገር ጤና አጥታ የኢትዮጵያ ሕዝብም መከራ እያጨደ ነው፡፡ ከአገር ሰላም፣ ደኅንነትና ጥቅም በፊት ምንም ዓይነት የሚቀድም ዓላማም ሆነ አጀንዳ ማራመድ አይገባም ቢባልም አዳማጭ ሊገኝ አልቻለም፡፡ በዚህም የተነሳ አየሩን የሞላው ተስፋ ሳይሆን ሥጋት ነው፡፡
ብዙዎቹ የፖለቲካ ልሂቃን ኢትዮጵያ ለገጠማት ችግር መንስዔው ምንድነው ሲባሉ፣ ምላሻቸው የሚመሠረተው ከቆሙለት የፖለቲካ ፍላጎት አኳያ ነው፡፡ በዜግነትም ሆነ በብሔር ፖለቲካ የተደራጁ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት፣ አንዳቸው ለሌላቸው ዕውቅና ሰጥተው በልዩነት ውስጥ ለአገር አብሮ መሥራት እንደሚቻል መገንዘብ አይፈልጉም፡፡ ልዩነቶችን በፀጋ ከመቀበል ይልቅ ለግጭት ምክንያት እንዲሆኑ አጥብቀው ይሠራሉ፡፡ በሕግና በሥርዓት ለመተዳደር የሚያስችል ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲገነባ ለሚያስፈልጉ ጠቃሚ ጉዳዮች መጨነቅ ሲገባቸው፣ አንዱ ሌላውን እንዴት ጠልፎ ጥሎ የበላይነቱን እንደሚይዝ እንቅልፍ አጥተው ስለሚያድሩ ለሴራ ፖለቲካ አመቺ መደላድል እንዲፈጠር አድርገዋል፡፡ ብዙዎቹ ለስሙ ፖለቲከኞች ይባሉ እንጂ ርዕዮተ ዓለማዊ መሠረት የሌላቸው ብቻ ሳይሆኑ፣ ለሚያቀነቅኑት ዓላማ የረባ ፕሮግራምና ማኒፌስቶ እንደሌላቸውም የታወቀ ነው፡፡ በኋላቀር አስተሳሰብ የታጀሉ ስለሆኑ ሥራቸው ግጭት
ስምምነት ሊደረስበት ያልቻለው የኢትዮጵያና የአይኤምኤፍ ድርድር
ኢትዮጵያ የገጠማትን ከፍተኛ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ለማስተካከል በፅኑ የሚያስፈልጋትን የውጭ ብድር ወይም የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ለዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) እና ለፓሪስ ክለብ አበዳሪ አገሮች ጥያቄ አቅርባ ድርድር ከጀመረች ከሁለት ዓመት በላይ ቢቆጠሩም አሁንም…
https://www.ethiopianreporter.com/128989/
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio251
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ከፍተኛ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት በጋራ ያቀረቡትን ምክረ ሐሳብ ተከትሎ፣ የሽግግር ፍትሕ ሥርዓት ለመዘርጋት ታምኖበት ወደ ሥራ ከተገባ ከአንድ ዓመት በላይ ተቆጥሯል፡፡
የሽግግር ፍትሕ በአገሪቱ ለዘመናት የተፈጸሙና አሁንም የቀጠሉ ያልጠሩ ትርክቶች፣ ቁርሾዎች፣ አለመተማመኖች፣ የእርስ በርስ ግጭቶችና የሰላም ዕጦቶች፣ አለመረጋጋቶችና እነዚህን አስታከው የሚፈጸሙ ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና ችግሮችን ዘላቂ መፍትሔ በመስጠት ሁሉ አቀፍ ፍትሕ ለማስፍን እንደሚረዳ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡
በታኅሳስ 2015 ዓ.ም. በፍትሕ ሚኒስቴር የተዋቀረው 15 የባለሙያዎች ቡድን የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ አቅጣጫ አማራጮች ሰነድ በማዘጋጀት፣ በየካቲት 2015 ዓ.ም. የጀመረውን ሕዝባዊ ምክክርና የግብዓት ማሰባሰብ ሥራዎችን አጠናቆ መስከረም 2016 ዓ.ም. ይፋ አድርጎ ነበር፡፡
የባለሙያዎች ቡድኑ በምክክሩ ወቅት በሕዝብ አስተያየት ግብዓቶች የተገኙ ዋና ዋና ግኝቶችንና የራሱን ምክረ ሐሳብ ይፋ ባደረገበት ወቅት፣ ክስ የመስማትና ውሳኔ የመስጠት ተግባር ያለውና በሽግግር ፍትሕ የሚታዩ ጉዳዮችን የሚዳኝ ልዩ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም ሐሳብ ቀርቦ ነበር፡፡ በምክረ ሐሳቡ እንደተብራራው ጉልህ በሆኑ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ወይም ወንጀሎች ላይ ያተኮረ የክስ ሒደት ሊኖር እንደሚገባ፣ የምርመራና የክስ ሒደቶችን የሚያስተባብርና ልዩ ነፃና ገለልተኛ የምርመራና የክስ ሥራ የሚያከናውን ተቋም እንዲቋቋም ሐሳብ መቅረቡ አይዘነጋም፡፡
በተጨማሪም እውነታን የማፈላለግና የዕርቅ ሥራ ወይም ሒደት የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ውክልናና ተሳትፎ ባረጋገጠ መንገድ በሚመሠረት አዲስ የእውነት አፈላላጊ ተቋም አማካይነት እንዲካሄድ፣ ከፍተኛ ደረጃ ተሳትፎ ባላቸው አጥፊዎች ላይ ያተኮረ የክስ ሒደት ሊኖር እንደሚገባና ምሕረት
በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የተነሳውን ሰደድ እሳት መቆጣጠር አለመቻሉ ተገለጸ
በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበውና በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኘው የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ ከሰባት ቀናት በፊት ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም. የመነሻው ምክንያት ሳይታወቅ የተነሳውን ሰደድ እሳት በቁጥጥር ሥር ማዋል አለመቻል በአካባቢው ነዋሪዎች…
https://www.ethiopianreporter.com/128918/
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio251
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሁለት ካምፓሶች በፀጥታ ችግር ተዘግተው ተማሪዎች እንዲሸጋሸጉ ተደረገ
በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሥር የሚገኙ የዘንዘልማና የሰባታሚት ካምፓሶች በፀጥታ ችግር ምክንያት በመዘጋታቸው የግብርና፣ የጤና፣ የጂኦሎጂና የዲዛስተር ማኔጅመንት ተማሪዎች የፀጥታው ችግር እስኪቀረፍ፣ ከተማ ውስጥ ባሉ ካምፓሶች ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ማድረጉን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ፡፡ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ጉዳዮች…
https://www.ethiopianreporter.com/128920/
የጥሬ ቡና ወጪ ንግድ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት መደረጉ የአገር ውስጥ ባለሀብቶችን ሥጋት ውስጥ ከቷል
ከዚህ በፊት ለውጭ ባለሀብቶች ዝግ ተደርጎ የነበረው የጥሬ ቡና ወጪ ንግድ የገበያ ሁኔታ ሳይስተካከል ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት መደረጉ፣ የአገር ውስጥ ባለሀብቶችን ከገበያ ሊያስወጣ እንደሚችል ሥጋት እንዳለ ተነገረ፡፡ በወጪና በገቢ ንግድ፣ እንዲሁም በጅምላና በችርቻሮ ንግድ የውጭ…
https://www.ethiopianreporter.com/128916/
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio251
የአውሮፓ ኅብረት ተግባራዊ ሊያደርግ ያቀደው ሕግ ለአርሶ አደሮችና ለላኪዎች ፈታኝ ይሆናል ተባለ
የአውሮፓ ኅብረት ቡናን ጨምሮ ወደ አባል አገሮቹ የሚላኩ ሰባት የምርት ዓይነቶች ከደን ጭፍጨፋና መመናመን ነፃ መሆናቸው ሳይረጋገጥ፣ ለግብይት እንዳይቀርቡ የሚከለክል ሕግ አውጥቶ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱ፣ ለገበሬዎችና በወጪ ንግድ ለተሰማሩ ነጋዴዎች ፈተና…
https://www.ethiopianreporter.com/128934/
በቀይ ባህር የመርከቦች እንቅስቃሴ መስተጓጎል አስገዳጅ ደረጃ ለመተግበር ፈተና መሆኑ ተነገረ
ሃያ አንድ ቀናት የሚፈጀው ጉዞ 66 ቀናት እየወሰደ ነው ተብሏል የምግብ ዘይትና የስንዴ ዱቄት በቫይታሚንና በሚኒራሎች ለማበልፀግ የተዘጋጀውን አስገዳጅ የኢትዮጵያ ደረጃ ለመተግበር፣ በቀይ ባህር መተላለፊያ የመርከቦች እንቅስቃሴ መስተጓጎል እንቅፋት መሆኑ ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በስንዴ ዱቄትና…
https://www.ethiopianreporter.com/128931/
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio251
ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የበጀት እጥረትና የሠራተኞች ፍልሰት ፈተና ሆነውበታል
በዘጠኝ ወራት ሥራ አፈጻጸም ከዕቅዱ በላይ 722 ሚሊዮ ብር አግኝቷል የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሪፖርት 722 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ቢያሳይም፣ የበጀት እጥረት የታቀዱ ግዥዎችን ለመፈጸም አዳጋች እንዳደረገበትና የሠራተኞች ፍልሰት ተግዳሮቶች እንደገጠሙት…
https://www.ethiopianreporter.com/128937/
በምሥራቅ አፍሪካ አካባቢ ከፍተኛ ዝናብ እየጣለ በመሆኑ፣ ሶማሊያ እና ኬንያ የጎርፍ አደጋ ማስጠንቀቂያ ለማውጣት ተገደዋል። የኬንያው ቀይ መስቀል ማኅበር እንደሚለው ከበድ ባለው ዝናብ ምክያት ባለፈው ሳምንት ስድስት ሰዎች ሲሞቱ፣ ከ11ሺሕ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ተፈናቅለዋ...
በጋዛ እና በዩክሬን በግልፅ የሚታየውን የዓለም ሕግጋት ጥሰት፣ እየተዛመተ የመጣውን የትጥቅ ትግል እና በሱዳን፣ በኢትዮጵያ እና በሚየንማር እየጨመረ የመጣውን አምባገነን አገዛዝ ተከትሎ፣ ዓለም አቀፍ ሕግጋት ለመፈራረስ መቃረባቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተሰኘው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ቡድን ዛሬ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርቱ አስታውቋል።
(በአሶሽየትድ ፕሬስ የተጠናቀረውን ዘገባ ከተያያ...
ኢኒሼቲቭ ፎር ቼንጅ በተባለው ድርጅት ውስጥ የሚሰሩት አቶ ገረሱ ቱፋ የሰሞኑን የኦሮሚያ ሁኔታ በተስፋም በስጋትም እንደሚመለከቱት ያስረዳሉ።የፖለቲካ ሳይንስ ምሁርና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፖለቲከኛ መረራ ጉዲና አሁን በኦሮሚያም ይሁን በመላ አገሪቱ ግጭቶች የመባባስ እንጂ የመርገብ ምልክት አላሳዩም ብለዋል፡፡...
በትግራይ ለ2 ዓመት በተካሄደው ጦርነት ለደረሰው ሰብዓዊ ችግር ለመድረስ "እኛ ለትግራይ ዓለም ነን" የተሰኘ ዓለም አቀፍ የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ተጀመረ።አስተባባሪው ኘሮፌሰር ሙሉጌታ ገብረእግዚአብሄር ለዶይቸ ቨለ እንደገለጹት፣በትግራይ ከተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት በኃላ የደረሰው ሰብዓዊ ቀውስ ፣አስቸኳይ እርምጃ ያስፈልገዋል።...
በአሜሪካ ሁለቱ ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎች የአህያ እና የዝሆን ምስሎችን ለመለያነት ይጠቀማሉ። የአህያው ምስል የዲሞክራቶቹ ምልክት ሲሆን፣ ሪፐብሊካኖቹ ደግሞ የዝሆን ምስልን ይዘዋል። ምስሎቹም በምርጫ ዘመቻ ወቅት በብዛት ጥቅም ላይ ይውላሉ።ለመሆኑ እነዚ እንስሦች ለምንና እንዴት ሊመረጡ ቻሉ? ያስ ሞነም እና ቨኔሳ ጃንስተን ያዘጋጁትን እንግዱ ወልዴ ወደ አማርኛ መልሶታል። ...
በዓለም አቀፉ የሰላም ጥናት ተቋም መግለጫ መሠረት በ2023 ዓ.ም. ዩናይትድ ስቴትስ ቻይናና ሩስያ ዋነኛዎቹ የጦር መሣሪያ ሻጭ አገራት ናቸው። የሩስያ ወታደራዊ ወጪ በ24 በመቶ ማለትም በ109 ቢሊዮን ዶላር አድጓል።ዩክሬን ለጦር መሣሪያ ግዥ ያወጣችውና ከውጭ ያገኘችው ወታደራዊ እርዳታ በአጠቃላይ ከሩስያ ወታደራዊ ወጭ 91 በመቶው ያህል ሆኗል።...
አዲሱ ጥናት እንዳረጋገጠው አረቢካ የቡና ዝርያ የተገኘው ከ610,000 እስከ አንድ ሚሊዮን ዓመታት በፊት ባለው ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ደኖች ውስጥ ነው። ይህ የቡና ዝርያ ከዛሬ 300,000 ዓመታት በፊት በአፍሪካ ከነበረው ዘመናዊ የሰው ዝርያ /Homo sapiens/ በዕድሜ ቀደምት ነው።...
ኦርቶዶክሳዊነታቸውን ለዘር እና ለጥቅም ሽጠው ከቤተ ክርስቲያን ጠላት ጋር የቆሙት ሲጋለጡ! ፟ "ተነቅቶባችኋል" ሊባሉ የሚገባ "አቡኖች"
የምሥራች ለዐማራውያን…!
“… በራሳቸው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ነቢያት በሆኑት ጎንደሬዎች፣ በአፄ ቴዎድሮስ ልጆች፣ በጀግኖቹና በአርበኞቹ ጋባዥነት ለአንድ ዓላማ ቆመው ሳለ በሓሳብ ልዩነት ከሁለት ጎራ ተከፍለው ቁርሾ ገብቷቸው የነበሩት ጀግኖች ባቀረቡልኝ “የአሸማግለን” ጥሪ መሠረት እኔ ዘመዴ አባ ደፋር አንድ ለእናቱ፣ ሺ ለጠላቱ፣ የሥላሴ ባርያ የድንግል አሽከር፣ የምሥራቁ ሰው፣ ባለማዕተቡ የተዋሕዶ ልጅ፣ የሐረርጌውን መራታ ጥሪያቸውን ተቀብዬ እንደ መጽሐፍም ቃል “የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና።” ማቴ 5፥9 ባለው አምላካዊ ቃል መሠረት የማሸማገል ሥራውን ጀመርኩ።
“…ጎንደሬዎቹን ጆኒ፣ ዘመንና አዱኛን ከጀርባ አሰልፌ፣ የሸዋውን ካህን ከኦሀዮ በጸሎት አስጀምሬ፣ በመጨረሻም ከወሎ የደብረ ሮሀ ቅዱስ ላሊበላ አስተዳዳሪ የነበሩትን አባ ጽጌሥላሴን ጨምሬ፣ ገዳማውያን በጸሎት እንዲያግዙን ፈቃደ እግዚአብሔርንም ጠይቀን ስናበቃ ወደ ውይይቱ ገባን። ውይይቱ ሲጀመር ከባድ ነበር። ውሎ ሲያድር እየቀለለ መጥቶ ዛሬ ሚያዚያ 16/2016 ዓም እግዚአብሔር ከብሮ ሰይጣን ዲያብሎስም አፍሮ፣ በእለተ ኪዳነምህረት በደስታ፣ በእንባ፣ በፍቅር የሽምግልናውን ሂደት በይቅርታ ተፈጸመ።
“…አርበኛ መሳፍንት ተስፉ የጎንደር ዕዝ የበላይ ጠባቂ፣ አርበኛ ባዬ ቀናው የዐማራ ፋኖ በጎንደር ሰብሳቢ፣ አርበኛ ሀብቴ ወልዴ የዐማራ ፋኖ በጎንደር ዕዝ መሪ፣ ኮ/ል ታደሰ የዐማራ ፋኖ በጎንደር የጦር አዛዥ በተለይ አርበኛ ፋኖ ደረጀ ሁላችንንም አስለቅሶን ሁላቸውም ታርቀው፣ ይቅር ተባብለው፣ የደስታ ጥይት ተተኩሶ፣ የተራራቁት ተቀራርበው በአጭር ጊዜ ውስጥ የጋራ የተዋሐደ አመራር መርጠው በአንድ የጎንደር ፋኖ ሊገለጡ ወስነው ይሄንኑ ለመላው ዐማራ ንገር ብለው አዘውኝ ነገሩ ተቋጭቷል።
• እግዚአብሔር ይመስገን
ዘመድኩን በቀለ (መምህር)
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ የኾኑትን ቀሲስ በላይ መኮንንን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ 8 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን የአገር ውስጥ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
የቀሲስ በላይ መኮንን እና ተጠርጣሪ ግብረ አበሮቻቸው ጠበቆች፣ ፖሊስ ዋስትና ለማስከልከል ያቀረባቸው ምክንያቶች አሳማኝ አይደሉም በማለት ተከራክረው እንደነበር ዘገባዎቹ አመልክተዋል።
ፖሊስ ካኹን ቀደም በተሰጠው የ7 ቀን የምርመራ ጊዜ፣ በወቅቱ የነበረ የካሜራ ቅጂ ከአፍሪካ ኅብረት መጠየቁን፣ ለወንጀል ተግባር የዋለ ተሽከርካሪ ማረጋገጫ ለማግኘት ለሚመለከተው አካል ጥያቄ ማቅረቡን፣ በተጠርጣሪው ኹለት መኖሪያ ቤቶች ላይ ብርበራ ማድረጉንና በብርበራ የተገኘ አንድ የጦር መሳሪያ ሕጋዊነቱን የማረጋገጥ ሥራ እየሰራ መኾኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል ተብሏል።
ቀሲስ በላይ ከሳምንት በፊት በቁጥጥር ስር የዋሉት፣ ከአፍሪካ ኅብረት የባንክ አካውንት በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በሐሰተኛ ሰነዶች ለማውጣት ሞክረዋል ተብለው ተጠርጥረው እንደኾነ አይዘነጋም።
ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራዊ ምክክር ላይ በአጀንዳነት የሚቀርቡ ጉዳዮችን እንዲያዘጋጁ ተጠየቁ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ በሀገራዊ ምክክር ላይ “አጀንዳ ሊሆኑ ይገባሉ” የሚሏቸውን ጉዳዮች እንዲያዘጋጁ ለተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በደብዳቤ ጥሪ አቀረበ። የፖለቲካ ፓርቲዎቹ በሚያቀርቧቸው አጀንዳዎች ላይ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት እና የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት የሚያካሄዱበትን ሁኔታ እንደሚመቻች ኮሚሽኑ አስታውቋል።
“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው እና ባለፈው ሳምንት ለተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተላከው ደብዳቤ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከባለድርሻ አካላት “አጀንዳዎችን የመሰብሰብ ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ” ጠቅሷል። በዚህም መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎቹ “ለሀገራዊ ምክክር ሊቀርብ ይገባል” የሚሏቸውን “የአጀንዳ ነጥቦች” የማዘጋጀት ስራ እንዲያከናውኑ ኮሚሽኑ በደብዳቤው ጠይቋል።
በታህሳስ 2014 ዓ.ም. በጸደቀው የኮሚሽኑ የማቋቋሚያ አዋጅ፤ የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ “በተለያዩ የፖለቲካ እና የሃሳብ መሪዎች፣ በመንግስት እንዲሁም በህብረተሰብ ክፍሎች መካከል፤ ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ያሉ ልዩነቶችን ወይም የአለመግባባት መንስኤዎችን በትክክል የሚዳስሱ ጉዳዮች” መሆናቸውን አስቀምጧል። ኮሚሽኑ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የሚቀርቡለትን እነዚህን አጀንዳዎች ካደራጀ በኋላ ውይይቶች የሚካሄዱባቸውን ርዕሰ ጉዳዮች የመለየት ሚናም በአዋጁ ተሰጥቶታል።
* ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13001/
ከብልፅግና ጋር የሚያገናኘው የጋራ አጀንዳው የፕሪቶርያው ውል መሆኑን የገለጸው ህወሓት ውሉ በሙሉ እንዲተገበር አጋዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብልፅግና ፓርቲና ህወሓት በመቐለና አዲስአበባ መወያየታቸውን አስታውቋል። ከዚህ ውጭ ህወሓትና ብልፅግና ፓርቲ በመገናኛ ብዙሐን እንደተባለው የጀመሩት ወደ ውህደት የሚመራ ውይይት የለም ሲል አስተባብሏል።...
በአማራና ትግራይ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች በተከሰተ ግጭት ከ50 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ያለፈው ሰኞ አስታውቋል። እንደ ድርጅቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፤ በተለይ ሴቶችና ህጻናት የሚገኙበት ሁኔታም አሳሳቢ ነው።...
የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤቱ ያስቀመጣቸው መፍትሔዎች “በሙሉ” በገዢው ፓርቲ የተያዙ ናቸው አለ
በኢትዮጵያ ውስጥ የትጥቅ ትግል እያደረገ የሚገኘው እና በአገሪቱ ፓርላማ “አሸባሪ” ተብሎ የተፈረጀው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነሠ) ዛሬ ረፋድ የብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት ለአገሪቱ ስብራት ያስቀመጣቸው መፍትሔዎች በሙሉ በገዢው ፓርቲ አለ።
አዲስ ማለዳ ከድርጅቱ ይፋዊ የኤክስ ገጽ እንደተመለከተችው “የብልጽግና ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት” የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ እና ለትውልድ የተሸጋገሩ ቀውሶች ለመፍታት ፍኖተ ካርታውን “አሳትሟል” በማለት ገልጿል።
የብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤቱ በመግለጫው “የታሪክ ስብራቶቹን” ለመጠገን ፖለቲካዊ ችግሮችን በአገራዊ ምክክር፤ እንዲሁም በሽግግር ፍትሕ እና በተሐድሶ ለመጠገን መስራት እንደሚገባ መግለጹን አዲስ ማለዳ ዘግባ ነበር።
ታጣቂ ቡድኑ “ሦስቱም ሂደቶች ሙሉ በሙሉ በገዢው አካል ባለቤትነት የተያዙ እና በጥቃቅን የሚተዳደሩ ናቸው” ማለቱን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልታለች። “እንደ የሽግግር ፍትህ እና ብሔራዊ ውይይት ያሉ የቃላት ቃላቶችም ሕዝቡን ለማደናገር እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እጅ መንሻ ነው” ሲል የኦርሞ ነጻነት ግንባር አስታውቋል።
ተጨማሪ ያንብቡ https://addismaleda.com/archives/36504
ከትዕግሥት በኋላ የሚከሠት “ሕግ የማስከበር ሥራ” ያለውን አስከፊ ውጤት “ከቅርቡ ታሪካችን ልንማር ይገባል”- ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት
👉🏿 በትግራይ ክልል ያለው የልማት ስራ “መንግሥታዊ ኃላፊነት እንጂ ፍርሃት” አይደለም ተብሏል
ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ከተመካከረ በኋላ ባወጣው መግለጫ “በስምምነቱ መሠረት የህሐት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው” ብሎ “የማንነት እና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄ ያለባቸውን አካባቢዎች ጉዳይ እልባት ለመስጠት እንዲቻል የተቀመጠው አቅጣጫ ተግባራዊ መደረግ አለበት” ሲል አስታውቋል።
መንግስት “እንቅስቃሴያቸው ሕገ ወጥ ስለሆነ ብቻ ጉዳዩን በጉልበት ብቻ ይፈታ ማለት እንደሌለበት ይገነዘባል”… https://addismaleda.com/archives/36504
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ ህወሓትን ከብልፅግና ፓርቲ ጋር ስለማዋሃድ፣ ስለሰሞኑ ግጭት፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ስላለቸው ግንኙነት እና የይገባኛል ጥያቄ ስለሚነሱባቸው አካባቢዎች ለቢቢሲ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።...
ለበርካታ ወራት ብዙ ሲያወዛግብ የቆየው ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ የሚልከው ሕግ በዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ ጸድቆ ሕግ ሆኗል። ይህ ሕግ ምን አካቷል? የትኞቹንስ ስደተኞች ይመለከታል?...
የዩናዩትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሀገራትን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በተመለከተ የሚያወጣውን ዓመታዊ ሪፖርት በትላንትናው ዕለት ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር “በፀጥታ ችግር” ምክንያት በተቋረጡ እና በቆሙ የመንገዶች ፕሮጀክቶች ላይ 34.95 ቢሊዮን ብር ካሳ በተቋራጮች መጠየቁን አስታወቀ። አስተዳደሩ እስከ 2016 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ድረስ “በፀጥታ ችግር” ምክንያት “ሙሉ በሙሉ የኮንትራት ውላቸው የተቋረጠ” 31 የመንገድ ፕሮጀክቶች መኖራቸውንም ይፋ አድርጓል።...
ሐሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከስድስት ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማውጣት በመሞከር የተጠረጠሩት ቀሲስ በላይ መኮንን፤ ድርጊቱ በተፈጸመበት ቦታ የተገኙት “ሰዎች አታልለዋቸው” እንደሆነ ለፍርድ ቤት መግለጻቸውን ጠበቃቸው አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ ተናገሩ።...
አሜሪካ ውስጥ በድንገት በደረሰ አደጋ ምክንያት ከመንገድ ወጥቶ በእሳት በተያያዘ መኪና ውስጥ የነበረ ግለሰብን ሕይወት ያተረፉ ሁለት ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና ሌሎችም አድናቆት እየተቸራቸው ነው። መኪና ላይ በተገጠመ ካሜራ የተቀረጸው ቪዲዮ እንደሚያሳየው ትውልደ ኢትዮጵያዊያኑ እና ሌሎችም በመንገዱ ላይ ሲያልፉ የነበሩ ሰዎች በእሳት ከተያያዘው መኪና አንድን ግለሰብ ለመታደርግ ያደረጉትን አስደናቂ ...
በአዲስ አበባ ከተማ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጂድ በተባለ አካባቢ ለቤት ግንባታ የተከመረ ድንጋይ እና አፈር ተንዶ የሰባት ሠዎች ሕይወት አለፈ።...
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio251
ከጥቂት ወራት በፊት በሶማሊያ እና በቱርክ መካከል የተደረሰውን የወታደራዊ ትብብር ስምምነትን ተከትሎ የቱርክ ባሕር ኃይል የጦር መርከብ ሞቃዲሾ ወደብ ደረሰች።...
Ethiopian news and analysisPlease subscribe and share:- https://bit.ly/subscribetomereja#Ethiopia #Mereja #ethio251
በዚህ የመንግሥት ውሳኔ መሠረት የውጭ ባለሃብቶች ቡናና የቅባት እህሎችን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ምርቶችን እና የቁም እንስሳትን ወደ ውጪ እንዲልኩ ፣ ከነዳጅ እና ማዳበሪያ በስተቀር በሁሉም ገቢ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ይፈቀድላቸዋል።...
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የምስራቅ ሀረርጌ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ መልዓከ ገነት ቀሲስ ንጋቱ ደሣለኝ ለዶይቼ ቬለ በስልክ በሰጡት መረጃ በሀረር ከተማ የቤተ ክርስትያኒቱ ንብረት የነበረና በደርግ መንግስት ተውርሶ ለማስመለስ በፍርድ ቤት ሂደት ላይ የሚገኝ ይዞታ እንዲፈርስ መደረጉን ገልፀዋል ።...
አጣዳፊ የተቅማጥና ትውከት (አተት) በሽታ ከመጋቢት 27/2016 ዓ ም ጀምሮ በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መከሰቱን የወረዳው ጤና ጽ/ቤት የባቲ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የጥራት ቁጥጥር ባለሙያ አቶ ፉአድ ቶፊቅ በባቲ ወረዳ 5 ቀበሌዎች 86 ሰዎች በበሽታው ተይዘው ህክምና እየተከታተሉ እንደሆነ አመልተዋል፡፡...
መረጃውን ያጋራው ግለሰብ የቤተሰባቸው አባል የሚገኙበት ዘጠን ሰዎች በምዕራብ አርሲ ዞን አዳባ ወረዳ ወሻ እና ቡቢሳ በተባሉ ቀበሌያት ተገድለው ተጥለው ቢገኙም አንስተው ለመቅበር እንኳ እድሉን መነፈጋቸውን ጠቅሰው ለማን እንንገር በማለት አስተያየታቸውን በሀዘን አጋርተዋል፡፡...
በጋዛ ናስር እና አል-ሺፋ ሆስፒታሎች ላይ የደረሰው ውድመት እና ከእስራኤል ወረራ በኋላ በሆስፒታሎቹ "የጅምላ መቃብሮች" መገኘታቸው "አሰቃቂ" ነው ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኃላፊ ገለጹ።...
በትግራይ፣ዕድሜአቸው ከ15 እስከ 29 የሆኑ ወጣቶች ቁጥር 2 ነጥብ 9 ሚልዮን ይገመታል።የሁለት ዓመቱ ጦርነት ዋነኛ ሰለባዎች መሆናቸው የሚገለፅላቸው እነዚህ ወጣቶች ከጦርነቱ በኃላ ባለው ግዜም በስራ እጦት፣ ተስፋ ማጣት እና ሌላ ግጭት ስጋት እግራቸው ወደመራቸው መሰደድ፣ ለተለያዩ ሱሶች እና ወንጀሎች መጋለጥ በስፋት እየታየባቸው መሆኑ ይገለፃል።...
በሁለት ሳምንት ልዩነት ለሁለተኛ ጊዜ ሰኞ ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም. ሰባ ሰባት ኢትዮጵያውያንን ይዛ ከየመን ወደ ጂቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ሰምጣ ሴቶች እና ሕጻናትን ጨምሮ 16 ሰዎች መሞታቸውን በጂቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና የመንግሥታቱ ድርጅት የፍልሰተኞች ተቋም አስታወቁ።...
በአሁኑ ጊዜ ለኦቲዝም የተጋለጡ ልጆች ቁጥር እየጨመረ መሄዱን የአሜሪካው የበሽታዎች መቆጣጠሪያን መከታተያ ማዕከል ይፋ ያደረጋቸው መረጃዎች ያመለክታሉ። የዓለም የጤና ድርጅት ከአንድ መቶ ልጆች ውስጥ ቢያንስ በአንዱ ላይ ኦቲዝም ሊያጋጥም እንደሚችል ይገልጻል።...
ሁለት የማሌዥያ አየር ኃይል ሄሊኮፕተሮች ለወታደራዊ ትዕይንት በልምምድ ላይ እያሉ መጋጨታቸውን ተከትሎ አስር ሰዎች ሞቱ።
ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑት የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ኤምባሲዎች “አከራካሪ” ከተባሉት ከሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚወጡት የግጭት ዘገባዎች እንዳሳሰቧቸው ገለፁ። ኤምባሲዎቹ ቅዳሜ ዕለት በጋራ ባወጡት አጭር መግለጫ፣ ውስብስብ ፖለቲካዊ እና የደኅንነት ቀውስን ለመፍታት እንዲሁም በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ፣ ሁሉንም ያካተተ ውይይት ማድረግ ብቸኛ መንገድ መሆኑን ገልፀዋል። ...
በዚህ ዓመት ከጥር እስከ ሚያዚያ እስራኤል ከጀርመን የገዛችው የጦር መሣሪያ 326.5 ሚሊዮን ዩሮ የወጣበት ነው።ይህም በ2022 ለጦር መሳሪያ ከወጣችው 32 ሚሊዮን ዩሮ በአስር እጅ ይበልጣል። በግዥው ከተካተቱ ውስጥ 20.1 ሚሊዮን ብር የወጣባቸው ፀረ-ታንክ መሣሪያዎች እና የአውቶማቲክና የመለስተኛ አውቶማቲክ ጠመንጃ ጥይቶች ይገኙበታል።...
የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት በሀገሪቱ ቲክቶክን ሊያግድ የሚችል አወዛጋቢ አዋጅን አጽድቋል።
አዋጁ የቲክቶክ ባለቤት ባይትዳንስ የማህበራዊ ትስስር ገጹን ድርሻ በ9 ወር ውስጥ የማይሸጥ ከሆነ በአሜሪካ አገልግሎት እንዳይሰጥ ያግዳል።
...
በአውሮፓውያኑ 2016 የመከላከያ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የተሾሙት የ47 ዓመቱ ኢቫኖቭ የሩሲያ ወታደራዊ መሠረተ-ልማት በማበልፀግ ይታወቃሉ። አክቲቪስቶች በሩሲያ ሙስና ተንሰራፍቷል ሲሉ ትችት ማቅረብ ከጀመሩ ሰነባብተዋል።...