Home › View all posts by VOA Amharic
Blog Archives
ትላንት ማክሰኞ በዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ፊት የቀረቡት የተመራጩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ዕጩ የመከላከያ ሚንስትር ፒት ሄግሴት የሴኔቱ ወታደራዊ አገልግሎት ኮሚቴ አባላት ከሆኑ ዲሞክራት አባላት የበረታ ሙግት ገጥሟቸዋል፡፡
የአሜሪካ ድምጽ የመከላከያ ሚንስቴር ዘጋቢ ካርላ ባብ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች፡፡ ቆንጅት ታየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች፡፡
...
እሳቱን የሚያዛምት ነፋስ ሊኖር እንደሚችል ባለሞያዎች አስጠንቅቀዋል
ደቡባዊ ካልፎርኒያ ሎስ አንጀለስ አካባቢ ለቀናት የቀጠለውን ሰደድ እሳት ለማጥፋት የእሳት አደጋ ሠራተኞች ዛሬም መረባረባቸውን ቀጥለዋል፡፡ በቃጠሎው እስካሁን ቢያንስ ሃያ አምስት ሰዎች የሞቱ ሲሆን ኅይለኛ ንፋስና ደረቅ የአካባቢው ሁኔታ ቃጠሎውን ይበልጡን ያስፋፋዋል የሚል ስጋት ፈጥሯል፡፡
ትላንት ማክሰኞ ቀን ላይ...
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን መተሐራ ከተማ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ እንዳሰጋቸው ነዋሪዎች ገለጹ። ትላንት ማምሻውን የተከሰተውን መንቀጥቀጥ ተከትሎ የግንብ አጥሮች መሰንጠቃቸውን እና በፈንታሌ ተራራ ላይም ናዳ በመከሰቱ ከተማዋ በአቧራ ተሸፍና መዋሏን ነዋሪዎችና የወረዳው አስተዳዳሪ ገልጸዋል።
...
በደቡብ አፍሪካ ከሚገኝ አንድ የማዕድን ማውጪያ ጉድጓድ ውስጥ 60 አስከሬኖችን ማውጣቱን የሀገሪቱ ፖሊስ ዛሬ አስታውቋል። ሕገ ወጥ ያላቸውን ማዕድን ቆፋሪዎች 2.6 ኪ ሜ ከሚረዝመው ጉድጓድ ለማውጣት ፖሊስ ለወራት ሲጥር ቆይቷል። አንድ መቶ ስድስት ሰዎችን ማዳኑንም ፖሊስ አስታውቋል።
ከጆሃንስበርግ 140 ኪ.ሜ. ደቡብ ምዕራብ ርቀት ላይ ከሚገኘው የማዕድን ማውጪያ ሥፍራ ጉድጓድ ውስጥ ከመቶ በላ...
ሥር በሰደደ የአደንዛዥ ዕፅ ሱስ ውስጥ ያሉ ወጣቶች ሳይቀሩ፣ "ለመዳን ከቆረጡና ተገቢውን ርዳታ ካገኙ ከችግሩ መውጣት ይችላሉ፤" ያሉን፣ በቅዱስ ጳውሎስ ሜዲካል ኮሌጅ ሥር በሚገኘው የሱስ ማገገሚያ ማዕከል የሥነ አእምሮ ጤና ባለሞያ እና በሆስፒታሉ የአእምሮ ሕክምናና ትምህርት ክፍል ሓላፊ ዶክተር መስከረም አበበ የምሽቱ እንግዳችን ናቸው።
ሱስ እና ሱሰኛነት ምን እንደኾነ በማስረዳት የሰጡንን ቃ...
በሞዛምቢክ በተካሄደው አጨቃጫቂና የሰው ሕይወት በጠፋበት ምርጫ አሸናፊ የሆኑት ዳንኤል ቻፖ ዛሬ ቃለ መሃላ ፈጽመዋል። ሃገሪቱን አንድ ለማድረግ እንደሚሰሩ ቻፖ ተናግረዋል።
ቃለ መሃላው በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ቢካሄድም ዛሬ በተደረገው ተቃውሞ ተጨማሪ ሰባት ሰዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ ተዘግቧል።
ባለፈው ጥር ወር በተካሄደው ምርጫ አሸናፊ እንደሆኑ የታወጀው የ48 ዓመቱ የገዢው ፓርቲ ዳን ኤል ቻፖ...
በፑንትላንድ የፀጥታ ኅይሎች ከአይሲስ ታጣቂዎች ጋራ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በተባለ ባደረጉት ውጊያ ቢያንስ ሁለት የቡድኑ ዓባላት መገደላቸውን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ቡድኑ በካማካዚ ድሮኖች ሊፈጽም ያቀደውን ጥቃት ማክሸፋቸውንም የሶማሊያ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
አይሲስ በሶማሊያ በመቶ የሚቆጠሩና ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተወጣጡ ተዋጊዎች ሲኖሩት፣ ከእነዚህም ውስጥ ኢትዮጵያውያን፣ ሱዳናውያን...
ሃገሪቱን በወታደራዊ አዋጅ ለማስተዳደር ሞክረው ያልተሳካላቸውና ክስም የቀረበባቸው የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝደንት ዩን ሱክ ዩል ዛሬ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተነግሯል።
ዩል ለ10 ሰዓታት ያህል በሃገሪቱ የጸረ ሙስና መ/ቤት የምርምራ ጥያቄዎች ከተደረገላቸው በኋላ በመዲናዋ ሶል አቅራቢያ ወደሚገኝ እስር ቤት መወሰዳቸው ታውቋል።
በመንግሥት ላይ በማመጽ ክስ የቀረበባቸውን ፕሬዝደንት ከመኖሪያ ቤታቸው...
እንደ ብርቱ የጤና ችግር የሚታየው "እጅግ ከፍተኛ" የሰውነት ክብደት፣ ሊያስከትላቸው የሚችላቸው ልዩ ልዩ የጤና ጠንቆች እንዳሉ ይታመናል።
በሕክምናው ዓለም የእንግሊዘኛው አጠራር ‘ኦቤሲቲ’ በመባል የሚታወቀውን ይህን ‘እጅግ ከፍተኛ የሰውነት ክብደት’ በማከሙ ረገድ፣ "ከአሁን ቀደም ያልታየ" የተባለን ውጤት ያሳዩትና ከፍተኛ ትኩረት የሳቡት እነኚኽ መድኃኒቶች፥ “የጥቅማቸውን ያህል በሐኪም የ...
በሐዋሳ ምርት ጥራት ምርመራ እና ማረጋገጫ ማዕከል ገጠመን በሚሉት እንግልት እና አገልግሎት አሰጣጥ ችግር ቡናቸውን ለማዕከላዊ ገበያ በወቅቱ ማቅረብ እንዳልቻሉ የቡና አቅራቢዎች ተወካዮችና እና አሽከርካሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ገለጹ።
የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጠን የምርት ጥራት መርመራ እና ማረጋገጫ ማዕከል ችግሩ የተፈጠረው በቦታ ጥበት እና ወደ ማዕከሉ የሚመጣው የምርት መጠንና የማዕከሉ የ...
ተመራጩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ፣ በምርጫ ዘመቻዎቻቸው ወቅት በእርሳቸው የአስተዳደር ዘመን ሊፈጽሙ ያሰቧቸውን በርካታ የሀገር ውስጥም ኾነ የውጪ ፖሊሲ ጉዳዮችን በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት ሲያተዋውቁ እንደነበር ይታወሳል።
ሊፈጽሙ ያቀዷቸው በርካታ የፖሊሲ ለውጦች በአጭርና ረጅም ጊዜ በአሜሪካ የውስጥ ጉዳይ እና በዓለም አቀፍ ግንኙነት ላይ ትልቅ አንድምታ እንደሚኖረው ተንታኞች ይገልጻሉ።
የ...
ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልካቸው በተለይም የቡና ምርት ትልቋ ተቀባይ ሀገር የኾነችው አሜሪካ፣ የቀረጥ ነጻ ዕድል(አጎዋ) ተጠቃሚነትን ስትከለክል፤ የኢትዮጵያ የውጪ ምርቶች አነስተኛ ተቀባይ የኾነችው ቻይና፣ የቀረጥ ወይም የዜሮ ታሪፍ ተጠቃሚነትን ፈቅዳለች፡፡
በዚኽ ሥርዓት፣ የኢትዮጵያ የውጭ ንግድ ተጠቃሚ ነው? በዚኽ ጉዳይ ላይ፣ የአሜሪካ ድምፅ በውጭ ንግድ ላይ የተሰማሩትን የኢትዮጵያ ጥራጥሬ ...
የኢትዮጵያውያን ፍጹም የበላይነት በታየበት የዱባይ ማራቶን፣ ለመጀመሪያ ጊዜ የተወዳደረው ቡቴ ገመቹ አሸንፏል።
አስከፊው የሎስ አንጀለስ ከተማ እና አካባቢው ሰደድ እሳት፣ የአሜሪካ የሴቶች ቡድን፣ የሥልጠና ካምፑን ወደ ሌላ ቦታ እንዲያዛውር አስገድዷል፡፡
አርሰናል በማንችስተር ዩናይትድ መሸነፉን ተከትሎ፣ በማኅበራዊ ብዙኀን መገናኛ ዛቻ እየደረሰባት እንደኾነች፣ የአርሰናሉ አጥቂ የትዳር አ...
ቻይና የዩናይትድ ስቴትስ ወደ ውጭ የሚላከውን የሰው ሰራሽ ልህቀት (አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ) በሚመለከት ያወጣቻቸውን አዳዲስ የቁጥጥር እርምጃዎች “በጽኑ እንደምትቃወም” ገልጻ የኩባንያዎቿን ጥቅም ለመጠበቅ “ቆራጥ እርምጃዎችን” እንደምትወስድ አስታውቃለች።
የባይደን አስተዳደር ትላንት ሰኞ የሰው ሰራሽ ልህቀትን ለማዳበር የሚያገለግሉ ቺፕስ የተባሉትን ልዩ የዘመናዊ ኮምፒውተር ክፍሎችን ወደ ውጭ ...
በደቡብ አፍሪካ የማዕድን ማውጫ የነፍስ አድን ሠራተኞ ዛሬ ማክሰኞ 8 ተጨማሪ አስክሬኖችን ከጉድጓዱ አውጥተዋል፡፡መውጣት ያልቻሉ ከ400 የሚበልጡ ቆፋሪዎች አሁንም ጉድጓዱ ውስጥ እንዳሉ ተነግሯል፡፡ የሞቱት ማዕድን ቆፋሪዎች ቁጥር 100 መድረሱም ተመልክቷል፡፡
በጎ ፈቃደኛ የነፍስ አድን ሠራተኞች በጉድጓዱ ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁኔታ እየተከታተሉ ሲሆን ፖሊስ ህገ ወጥ የማዕድን ሠራተኞች ናቸው ...
ካታር ጋዛ ሰርጥ ላይ በእስራኤል እና በሃማስ መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ የተያዘው ድርድር የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ተናገረች፡፡ ሁለቱ ወገኖች ስምምነት ላይ ለመድረስ በእጅጉ “የተቃረቡ” መሆኑን ካታር ዛሬ ማክሰኞ አስታውቃለች፡፡
የካታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማጅድ አል-አንሷሪ በሳምንታዊ መግለጫቸው ድርድሩ አዎንታዊ እና ውጤታማ መሆኑን ገልፀው ሆኖም "ተስ...
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከስልጣን ጊዜያቸው ማብቂያ አንድ ሳምንት አስቀድሞ ትላንት ሰኞ ባሰሙት ንግግር የተመሩበትን የውጭ ፖሊሲ መርህ ዘርዝረዋል።
አገሪቱን ወደ ፍጹም አዲስ ወደ ሆነ አቅጣጫ እንደሚመሩ በመግለጽ የዛቱት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የመንግስቱን ሥልጣን ሊረከቡ የቀናት እድሜ ብቻ በቀረበት ሰዓት ባይደን ባሰሙት በዚህ ንግግራቸው፤ ዩናይትድ ስቴትስ ለምን በያዘችው መንገድ ...
በደቡባዊ ካሊፎርኒያ ግዛት የቀጠለው ሰደድ እሳት፣ እስከ አኹን የ24 ሰዎችን ሕይወት ሲቀጥፍ፣ 12 ሺሕ የሚደርሱ ቤቶችን አውድሟል። ከሟቾቹ መካከል ስምንቱ በፓሲፊክ ፓላሳዴስ አካባቢ በተዛመተው እሳት የሞቱ መሆናቸውን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
ሰደድ እሳቱን ለማጥፋት የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ባሉበት በዚህ ወቅት፣ እንደ ዐዲስ ሊነሳ ይችላል ተብሎ የተሰጋው ጠንካራና ደ...
የጀርመን መከላከያ ሚኒስትር ቦሪስ ፒስቶሪየስ ከሦስት ዓመታት በፊት በሩሲያ የተከፈተባትን ወረራ ለመመከት የምትዋጋውን ዩክሬንን ዛሬ ማክሰኞ ጎብኝተዋል፡፡
የጀርመኑ የመከላከያ ሚኒስትር ዩክሬንን የጎበኙት ከተመራጩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በዓለ ሲመት አንድ ሳምንት በፊት ሲሆን በአዲሱ አስተዳደር የዩክሬን ፖሊሲ ለውጥ ሊለወጥ ይችላል የሚሉ ጥያቀዎች እየተነሱ ባሉበት በዚህ ...
ዩናይትድ ስቴትስ፣ በሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ኀይሎች እና ተባባሪዎቹ ሚሊሽያዎች "የዘር ማጥፋት እየፈጸሙ ነው፤" ስትል ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ አስታውቃለች፡፡
ሄነሪ ዊልኪንስ ባስተላለፈው ዘገባ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ይፋ ያደረገችውን ብይን በተመለከተ፣ ተንታኞች እና የመብት ተሟጋቾች የሰጡትን አስተያየት በማካተት ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
...
በኢትዮጵያ በሱስ እና ተያያዥ ችግሮች የሚጠቁ ወጣቶች ቁጥር እጅግ ከፍተኛ ቢኾንም፣ ከሱስ ለማገገም የሚረዱ ተቋማት ግን በስፋት አለመኖራቸውን ባለሞያዎች ይገልጻሉ።
ይኹን እንጂ፣ በቅዱስ ጳውሎስ ሜዲካል ኮሌጅ ሥር የሚገኘው የሱስ ማገገሚያ ማዕከል፣ ለበርካታ ወጣቶች ድጋፍ በማድረግ ወደ መደበኛ ሕይወታቸው እንዲመለሱ እየረዳ ይገኛል። በተቋሙ ውስጥ ከነበረበት ሱስ ለማገገም መቻሉን ለአሜሪካ ድም...
የኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲ ለውጥ ማድረጉን ተከትሎ፣ የሳተላይት ስርጭት ኪራዩ በእጥፍ በመጨመሩ ለመክፈል መቸገራቸውንና ስርጭታቸውን አቋርጠው ለመውረድ መገደዳቸውን፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየታቸውን የሰጡ የቴሌቭዥን ሓላፊዎች ተናግረዋል፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ባገኘው መረጃም መሠረት፣ በሳተላይት ስርጭታቸውን ከሚያስተላልፉ የቴሌቭዥን ጣቢያዎች መካከል እስከ አሁን 13 የሚኾኑቱ ከሳተላይት...
በደቡባዊ ካሊፎርኒያ ግዛት ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰው ያለውን ሰደድ እሳት ለማጥፋት የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ባሉበት ወቅት፣ እንደአዲስ ሊባባስ ይችላል ተብሎ የተሰጋው ጠንካራ ንፋስ እሳቱን ሊያባብሰው እና ከቁጥጥር ውጪ ሊያደርገው ይችላል ሲሉ የትንበያ ባለሞያዎች አስጠንቅቀዋል።
የአሜሪካ ብሔራዊ የአየር ትንበያ አገልግሎት በአወጣው ማስጠንቀቂያ፣ ነገ ማክሰኞ ሊጨምር ይችላ...
በጋዛ የሚካሄደውን ጦርነት ለማስቆም፣ አሸማጋዮች የመጨረሻ ያሉትን የእርቅ ስምምነት ረቂቅ ሐሳብ ለእስራኤል እና ለሐማስ ማቅረባቸውን፣ በድርድሩ ዙሪያ ማብራሪያ የቀረበላቸው አንድ ባለሥልጣን አስታወቁ። በድርድሩ ላይ የጆ ባይደን እና የዶናልድ ትራምፕ ልዑካን መገኘታቸውንም አመልክተዋል።
ባለሥልጣኑ እንደተናገሩት፣ የተኩስ ማቆምን እና የታጋቾችን መለቀቅ በሚመለከት ኳታር ያቀረበችው ረቂቅ የስምምነ...
በሰሜናዊ ምስራቅ ናይጄሪያ፣ ቦርኖ ግዛት ውስጥ እስላማዊ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት፣ ቢያንስ 40 ገበሬዎች መግደላቸውን የመንግሥት ባለሥልጣናት ዛሬ ሰኞ አስታወቁ።
ጥቃቱ የተፈፀመው እሑድ ዕለት ሲሆን፣ ለጥቃቱ የቦኮ ሃራም ቡድን እና ከቡድኑ ተገንጥሎ የወጣ እና በቦርኖ ግዛት የሚንቀሳቀስ ለእስላማዊ መንግሥት ታማኝ መኾኑ የተገለፀ ቡድን ተጠያቂ መደረጋቸውን የቦርኖ ግዛት አስተዳዳሪ የሆኑት ባባጋ...
በሞዛምቢክ አከራካሪ የነበረውን ምርጫ ውጤት ተቃውመው፣ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የሥራ ማቆም አድማ መጥራታቸውን ተከትሎ ዋና ከተማው ጭር ባለበት ዕለት አዲሱ ፓርላማ ሥራ ጀምሯል።
ሁለት አነስተኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የምርጫ ውጤቱን አንቀበልም በማለት ተቃውሟቸውን ለመግለፅ የመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ላይ ያልተገኙ ሲሆን፣ ለወራት የተካሄደው እና የሰው ህይወት የጠፋበትን አለመረጋጋት ተከትሎ በተከፈተው...
የትግራይ ክልልን መነሻ ባደረገው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ተፈናቅለው በመቐለ ከተማ የሚገኙ ዜጎች፣ “ይኣክል”(ይበቃል) በሚል መሪ ቃል ለሦስት ቀናት የጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ እየተካሔደ ነው።
በመጠለያ ካምፕ ለአራት ዓመታት እንደቆዩ የሚናገሩት ተፈናቃዮቹ፣ ደኅንነታቸው ተጠብቆ በአስቸኳይ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ ይደረግ ዘንድ ጠይቀዋል። የክልሉ አመራሮች "ክደውናል፤ በተፈናቃዮች ሥቃይ እየተጫ...
ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በያዝነው የአውሮፓውያኑ ወር መጨረሻ፣ 47ኛው የዩናይትድ ስቴትስ መሪ በመኾን ቃለ መሐላ ይፈጽማሉ።
የዩናይትድ ስቴትስ መራጮች፣ ከቀጣዩ ፕሬዚዳንታቸው በሚጠብቁት ጉዳይ ላይ ይለያያሉ፡፡
የቪኦኤው ዘጋቢ ስካት ስተርንስ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
...
በአሜሪካ ሎስ አንጀለስ ከተማ እና በአካባቢው የተቀሰቀሰውን የሰደድ እሳት መስፋፋት ለመግታትና ለማጥፋት እየተደረገ ካለው መጠነ ሰፊ ርብርብ በአንጻሩ፣ እስከ አሁን ለመቆጣጠር አልተቻለም።
እንዲያውም ከፍተኛ ፍጥነት ባለው ነፋስ ደረቅ በመታገዝ እየተባባሰ ያለው የሰደድ እሳቱ፣ በየሰዓቱ የሚያደርሰው ውድመት አስከፊ እንደኾነ ነው የተገለጸው። የጠፋውም እሳት ቢኾን፣ ረመጡ በደረቁ ነፋስ ዳግም ሊቀ...
ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ ወደ አዋሽ ከተማ ሲቃረብ ሐዲዱን ስቶ በመገልበጥ ቁጥሩ ከ418 የሚበልጥ ሕይወት የጠፋበት የባቡር አደጋ የደረሰው ከአርባ ዓመታት በፊት በ1977 ዓ.ም. በዛሬው ዕለት ነበር፡፡ የፈረንሳይ እና ኢትዮጵያ የባቡር መስመር ኩባኒያን ጠቅሶ አሶሲየትድ ፕሬስ በዕለቱ ያስነበበው ዘገባ እንዳተተው በአደጋው ከሞቱት በተጨማሪ 559 ሰዎች ቆስለዋል፡፡
1 ...
በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሱሉላ ፊንጫ ወረዳ በሚገኘው የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ፣ ከ450 በላይ ቋሚ እና የኮንትራት ቅጥር ሠራተኞች መታሰራቸውን፣ ቤተሰቦቻቸው እና የፋብሪካው ሠራተኞች ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
የሱሉላ ፊንጫ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ፋንታሁን ታዬ፣ ሠራተኞቹ የታሰሩት "በፋብሪካው ይዞታ ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ የግብርና ሥራ ላይ ተሰማርተው በመገኘታቸው ነው፤" ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ተ...
ከአራት አመት በፊት በሚዲያ ተቋም ይሰሩ በነበሩ ጋዜጠኞች የተመሰረተው ሀቅ ቼክ በኢትዮጵያ ሆን ተብለው ሆነ ባለማወቅ የሚሰራጩ መረጃዎችን በማጣራት የሀሰተኛ መረጃዎችን ስርጭት ለመቀነስ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህ ተቋም የመረጃ አጣሪዎች አስተባባሪ ሆኖ የሚያገለግለው ኪሩቤል ተስፋዬም የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘበትን የምህንድስና ሙያ በመተው ሀሰተኛ መረጃ በማህበረሰቡ ውስጥ እያደረሰ ያለውን ጉ...
ዛሬ እሑድ ጥር 4 ቀን በተካሔደው የ2025 የዱባይ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያን ከአንደኛ እስከ አሥረኛ ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል፡፡
በዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ ባለው የዱባይ ማራቶን፣ በወንዶች ምድብ አሸናፊ የኾነው በማራቶን የመጀመሪያ ውድድሩን ያደረገው ቡቴ ገመቹ ሲኾን በሴቶቹ በዳቱ ሂርጳ አሸንፋለች፡፡
ባለፈው ሰኔ ወር በቻይና ጉይዡ ዜኒንግ የግማሽ ማራቶን ውድድርን ...
ባለፈው ሰኞ፣ ታኅሣሥ 28 ቀን 2017 ዓ.ም, ከዚኽ ዓለም በሞት የተለዩት አንጋፋው ፖለቲከኛ እንዲሁም የምጣኔ ሀብት እና የፋይናንስ ባለሞያ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ሥርዐተ ቀብር፣ እሑድ፣ ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በዐዲስ አበባ ከተማ ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ተፈጽሟል።
ከሥርዐተ ቀብራቸው አስቀድሞ፣ በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ በተከናወነው የአስከሬን ሽኝት መርሐ ግብር ላይ በተነበበው...
ለሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ የቆዩት እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ጋራ የተወያዩት፣ የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼኽ መሐመድ በኢትዮጵያ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው፣ ዛሬ እሑድ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
የፕሬዝደንቱን መመለስ ይፋ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ፣ "የሁለትዮሽ ግንኙነቶቻችንን ለማጠናከር ውጤታማ ውይይቶች ካደረግን በኋላ ዛሬ ከሰዓት ፕሬዝደንት ሐ...
የናይጄሪያው ፕሬዝዳንት ቦላ ቲኒቡ ባለፈው ሳምንት በሰሜን ምሥራቅ ቦርኖ ግዛት በዳምቦዓ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ላይ ስድስት ወታደሮችን የሞቱበት የሽብር ጥቃት እንዲጥራ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ባወጡት መግለጫ የአሁኑ ምርመራ ወደፊት ሊከሰቱ የሚችሉ ሁኔታዎችን ለማስወገድ እና ያሉ የደህንነት ክፍተቶችን ለመለየት ይረዳል ብለዋል።
የፕሬዚዳንቱ መግለጫ ሐሙስ ዕለት በመረጃ አማካሪያ...
በፕሬዝዳንት ባይደን አስተዳደር የዩናይትድ ስቴትስ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሆነው ያገለገሉት ተሰናባቹ ጄክ ሱሊቫን፤ መጭው የትራምፕ አስተዳደር ጆ ባይደን አስጀምረውት ቻይናን እና ሰሜን ኮሪያን በመዋጋት ረገድ መልካም ደረጃ ላይ ያለውን የኢንዶ ፓስፊክ ቀጠና ስልታዊ ወዳጅነት እንዲያስቀጥል ጠይቀዋል።
ጄክ ሱሊቫን አርብ ዕለት ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ “ለትራምፕ አስተዳደር እያልን ያለ...
የአዲሱ የሶሪያ መንግስት የድህንነት ሃላፊዎች እራሱን እስላማዊ መንግስት እያለ የሚጠራው አሸባሪ ቡድን በደማስቆ ሳይዳ ዘይነብ አካባቢ በሺዓ ሙስሊሞች የአምልኮ ስፍራ ላይ ሊያደርስ የነበረውን የቦምብ ጥቃት ማክሸፋቸውን እንዳስታወቁ የሀገሪቱ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የሀገሪቱ መንግስት የሚተዳደረው ሳና መገናኛ ብዙሃን በሀገሪቱ ደህንነት ውስጥ የሚያገለግሉ ስማቸው ያልተጠቀሰ ባለሥልጣ...
በድጋሚ የታደሰ
የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሳን ሼክ መሃሙድ ከኢትዮጵያ ጋር ለአንድ ዓመት ያክል ሻክሮ የቆየውን ግንኙነታቸውን ለማደስ ስምምነት ላይ በደረሱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አዲስ አበባ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ፕሬዝዳንቱን በቦሌ አየር ማረፊያ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ጽ/ቤታቸው ፕሬዝዳንቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በተደረገላቸው ግብዣ መሰረት ወደ አዲስ አበባ...
በኢትዮጵያ የሚታዩት ግጭቶች እና የግብአቶች እጥረት፣ የወባ በሽታን ለመከላከል ፈተና መደቀናቸውን፣ የክልሎች የጤና ቢሮዎች አስታወቁ፡፡
የዐማራ፣ የኦሮሚያ እና የትግራይ ክልሎች የጤና ቢሮዎች ለአሜሪካ ድምፅ እንደገለጹት፣ በክልሎቹ የሚታየው የወባ በሽታ ስርጭት "አሳሳቢ" ኾኗል፡፡ የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል የሚያስችሉ እንደ አጎበር እና ኬሚካል ያሉ ግብአቶች እጥረትም እንዳለ የጠቆሙት ቢ...
የወጣቶች የሱስ ተጋላጭነት ከጊዜ ወደጊዜ እየሰፋ መሔዱን ጥናቶች ያመለክታሉ።
በዐዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ያነጋገርናቸው ነዋሪዎችም፣ የሱስ ዐይነቶች እና የተጠቃሚነት መጠን እየጨመረ መምጣቱ፣ በርካታ ወጣቶችን ራስን እስከማጥፋት ለሚያደርስ ድባቴ እንደሚያጋልጣቸው ነግረውናል።
ወጣቶች በሱሰኛነት ላይ የሰጡንን አስተያየት ከተያያዘው ፋይል ተከታተሉ።
...
ቻይና፥ በብድር፣ በንግድ ግንኙነት እና የውጭ መዋዕለ ነዋይን በማፍሰስ ረገድ ከኢትዮጵያ ጋራ ያላት የኢኮኖሚ ግንኙነት፣ ኢትዮጵያን ተጠቃሚ ማድረጉን በተመለከተ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ባለሞያዎች የተለያየ አቋም አላቸው፡፡
በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ተመራማሪው ዶክተር ዳር እስከዳር ታዬ፣ በግንኙነቱ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ መኾኗን ሲገልጹ፤ በአንጻሩ ከዊሊያም ፓተርሰን ኒውጀርሲ ፕሮፌሰ...
በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶችን ያወደመውን እና እስካሁን 10 የሚደርሱ ሰዎችን የገደለውን ሰደድ እሳት ለመቆጣጠር የእሳት አደጋ ሠራተኞች ዛሬ ለአራተኛ ተከታታይ ቀን እሳቱን ለማጥፋት ብርቱ ግብግባቸውን ቀጥለዋል። ለጊዜው ፍጥነቱን ቀንሶ የሚነፍሰው ነፋስ የከሰተውን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ውሃ የሚረጩ ሄሊኮፕተሮችን ጨምሮ እስከማለዳው ድረስ ለሊቱንም ሳያቋርጡ መቀጠላቸው ተዘግቧል።
ከትላንት ጀምሮ እ...
ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች እንደሆኑ በሚጠረጠሩ ግለሰቦች በአንድ ቤት ውስጥ ታግተው የነበሩ 26 ኢትዮጵያንን እርቃናቸውን ማግኘቱን የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ ዛሬ ዓርብ አስታውቋል።
ፍልሰተኞቹን ከታገቱበት ከማዳኑ በፊት 30 የሚሆኑት በተሰበረ መስኮት ሾልከው ሳያመልጡ እንዳልቀረ የገለፀው ፖሊስ፣ በአካባቢው ተደብቀው ሊሆን እንደሚችልም አስታውቋል።
በተደረገው ቅድመ ማጣራት 26ቱ ኢትዮጵያውያን ሳንድሪ...
የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው በሱሰ ውስጥ ያለፉ ወጣቶች፥ የአልኮል መጠጥን፣ ሲጋራንና ጫትን ጨምሮ እንደ ቀልድ የጀመሯቸው ሱስ አማጭ ልምምዶች፣ እያደር ሕይወታቸውን እንዳመስቃቀሉባቸውና የጤና እክልም እንዳመጡባቸው ነግረውናል፡፡
በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የሥነ ልቡና ባለሞያዎች በበኩላቸው፣ የወጣቶች የሱስ ተጋላጭነት እያስከተለባቸው ካለው ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ባለፈ፣ ለአእምሮ ጤና ሕ...
በሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ የተከሠተውን ድርቅ ተከትሎ አስቸኳይ የምግብ ርዳታ ያስፈልጋቸዋል ከተባሉ 109ሺሕ ሰዎች ውስጥ እስከ አሁን ማድረስ የተቻለው ለ27ሺሕዎቹ ብቻ እንደኾነ፣ የዞኑ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
በወረዳው ከ16ሺሕ ኩንታል በላይ የርዳታ እህል እንደሚያስፈልግ ለመንግሥትም ኾነ ለረጂ ድርጅቶች ማሳወቃቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ያስታወሱት...
በትግራይ ክልል የጤና ባለሞያዎች ፍልሰት እየጨመረ ነው፤ ያለው የክልሉ የጤና ባለሞያዎች ማኅበር፣ በየወሩ ከ80 በላይ የጤና ባለሞያዎች ክልሉን ለቀው እየሔዱና በክልሉ ውስጥም የሥራ ዘርፍ እየቀየሩ ናቸው፤ ሲል አስታውቋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፍሥሓ አሸብር ለአሜሪካ ድምፅ ሲናገሩ፣ በክልሉ ቀጥሏል ያሉት የፖለቲካ አለመረጋጋትና የኢኮኖሚ ችግር ለጤና ባለሞያዎቹ ፍልሰት መጨመር ምክንያት ...
በሎስ ኤንጀለስ አካባቢ የቀጠለው የዱር ሰደድ እሳት፣ እስከ አኹን የ10 ሰዎችን ሕይወት ሲቀጥፍ፣ 10ሺሕ የሚደርሱ ቤቶችን አውድሟል።
አንዳንድ መንደሮችንና ውብ መኖሪያ ቤቶችን ወደ ትቢያ የቀየረው የዱር እሳቱ፣ በአሜሪካ ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ በኾነችው ሎስ ኤንጀለስ ያስከተለው ውድመት፣ የቋያ እሳት በሚደጋግማት ከተማም እጅግ አስደንጋጭ ኾኗል።
በሆሊውድ አካባቢ የንግድ ቤት ያላቸው ትዕግሥ...
የኢትዮጵያን የሰነደ ሙዓለ ነዋዮች ገበያ፣ ዛሬ ዐርብ ይፋ ያደረጉት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ስኬታማ እንደሚኾን ተስፋቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው፣ የካፒታል ገበያው ለሁለት ዓመት ተኩል ዝግጅት ሲደረግበት እንደቆየ አውስተው፣ ባለሀብቶች ስጋት ሳይገባቸው ሊሠሩ እንደሚገባም አሳስበዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
...
የአፍሪካ ሀገሮች የግብርና ሚንስትሮች በዚህ ሳምንት ዩጋንዳ ዋና ከተማ ካምፓላ ላይ ጉባኤ ላይ ናቸው። የተሰበሰቡት የአህጉሪቱን የምግብ አመራረት ሥርዐቶች ለማሻሻል ስለሚቻልበት መንገድ ለመምከር ነው። ሚንስትሮቹ አፍሪካ ከውጭ በሚገባ ምግብ ላይ መተማመኗን ለመቀነስ ብሎም የአሕጉሪቱን አስተራረስ ከአየር ንብረት ለውጡ እና ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋራ በሚጣጣም መንገድ ለማሻሻል በታለመው የዐስር ዓመት...
ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ለአእዋፋት ኢንፍሉዌንዛ የተጋለጠ አንድ ሰው ህይወቱ ማለፉን፣ የሉዊዚያና ክፍለ ግዛት የጤና ባለሥልጣናት ባለፈው ሰኞ ይፋ አደረጉ።
የዓለም ጤና ድርጅት በበኩሉ በማኅበረሰብ ደረጃ ለበሽታው የመጋለጥ እጣ አሁንም አነስኛ መሆኑን ቢገልጽም፤ የአሜሪካ ድምጿ ዶራ መኩዋር ባጠናቀረችው ዘገባ እንደጠቆመችው ግን አንዳንድ የሕክምና ባለሞያዎች የሥጋት ድምጽ ማሰማታቸውን ቀጥለዋል...
በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭት በአገር አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ ቢኾንም፣ በጋምቤላ ክልል እና በከተሞች ውስጥ እየጨመረ እንደሚገኝ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኤችአይቪ/ኤድስ ፕሮግራም(ዩኤንኤድስ) አስታውቋል።
የተቋሙ ከፍተኛ አማካሪ የኾኑትና ኢትዮጵያን ጨምሮ በአምስት የአፍሪካ ሀገራት እየተሠራበት ባለው የኤች.አይ.ቪ መቆጣጠርያ የአምስት ዓመት መሪ ዕቅድ እና ስትራቴጂ ዝግጅት ላይ ...
ባለፈው እሑድ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት 39ኛው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተር ለስድስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የሐዘን እና የአስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዐት ተጠናቆ፣ በትውልድ ሥፍራቸው ጆርጂያ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ተፈጽሟል።
በሥፍራው የተገኘው የቪኦኤው ኬን ፋርቦ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
...
በየመን ሁቲ አማጽያን ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ለበርካታ ሳምንታት ሲቃጠል የቆየው የነዳጅ ዘይት ጫኝ መርከብ ቀር ባህር ላይ ከፍተኛ መጠን ያለው ብክለት እንዳያስከትል አሳድሮ የነበረውን ሥጋት ማስቀረት መቻሉን አንድ የግል በጸጥታ ጉዳዮች ተቋም ዛሬ አስታወቀ።
አንድ ሚሊየን በርሜል መጠን ያለው ድፍድፍ የነዳጅ ዘይት ጭኖ በመጓዝ ላይ ሳለ እስራኤል በጋዛ የምታካሂደውን ጦርነት በመጻረር ዘመቻ የከ...
ትላንት ከምሽቱ 1 ተኩል አካባቢ በሀገሪቱ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ክፍሎች “ሰብሰብ ያለ እና በከፍተኛ ፍጥነት የሚንቀሳቀስ ነገር ሰማይ ላይ መታየታቱን የሚያመለክት ሪፖርት ደርሶኛል” ሲል የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ አስታወቀ።
ድርጅቱ በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ባሰፈረው ጹሑፍ በሰማይ ላይ የታየው ነገር የጠፈር ፍርስራሽ አካል አልያም ጸሃይን ከሚዞሩት አነስተኛ አለት መሰል አካላት (ሜትሮይ...
የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች፣ በማኅበረሰብ ውስጥ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በማቃለል ኹለንተናዊ ለውጥን ለማምጣት ኹነኛ ሚና አላቸው፡፡ ሰው ሠራሽ እና ተፈጥሯዊ ቀውሶች በሚፈራረቁባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አዳጊ ሀገራት ደግሞ፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡
በኢትዮጵያ፣ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር በጦርነትም ኾነ በሌሎች ሰው ሠራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች የተጎዱ እና ተጋላጭ የኾኑ የማኅ...
ኢትዮጵያ ዛሬ አርብ የአክሲዮን ገበያ መጀምሯን ይፋ አደረገች። ርምጃው እየተከመ የመጣውን ኢኮኖሚዋን ነፃ ለማድረግ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከያዙት ጥረት የቅርብ ጊዜው ተደርጎ ተወስዷል።
በአክሲዮን ገበያው የተመዘገበው የመጀመሪያ ኩባንያ መንግሥታዊው ኢትዮ ቴሌኮም ሲኾን፤ የተለያዩ ባንኮችን እና የመድን ኢንሹራንስ ኩባንያዎችን ጨምሮ በደርዘን የሚቆጠሩ ሌሎች የንግድ ተቋማ...
በቅርብ ሳምንታት ጋዛ እና ሄይቲ ውስጥ በጋዜጠኞች ላይ የተፈጸሙት ግድያዎች ብዙኀን መገናኛ ላይ የተደቀኑትን አደጋዎች አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ባለፈው 2024 ዓም ከአንድ መቶ በላይ ጋዜጠኞች ተገድለዋል። በዓመቱ ጋዜጠኞች ላይ ለተፈጸመው ግድያ ጦርነት፥ አለመረጋጋት እንዲሁም የተጠያቂነት አለመኖር አስተዋጽኦ ማድረጉን ተንታኞች ይናገራሉ።
የአሜሪካ ድምጽ የፕሬስ...
የጦር መሣሪያና ምሳር የያዙ፣ ሁለት ደርዘን የሚሆኑና የኮማዶ አባላት ናቸው የተባሉ፣ በቻድ የፕሬዝደንቱ ቤተ መንግሥት ላይ ትላንት ምሽት ጥቃት መሰንዘራቸው ሲነገር፣ መንግሥት በበኩሉ ማክሸፉን አስታውቋል። ተቃዋሚው ፓርቲ ደግሞ የመንግሥትን መግለጫ እንደሚጠራጠር ገልጿል።
የመንግሥት ቃል አቀባይ የሆኑት አብደራማን ኩላማላህ፣ ሃያ አራት የሚሆኑ የኮማንዶ ዓባላት በቤተ መንግሥቱን ጠባቂዎች ላይ ጥ...
የዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ ፍርድቤት፣ የማኅበራዊ ሚዲያን በብሔራዊ ደኅንነት ምክንያት ማገድ የሚያስችለው አዲስ ሕግ በመጠቀም፣ የቲክ ቶክ ባለቤት የሆነው ባይትዳንስ የቻይና ኩባንያ የሚያደርገው የቃል ክርክር በፍጥነት እንዲጠናቀቅ እያደረገ ነው።
የአሜሪካ ድምፁ ስቲቭ ኸርማን በዚህ ዙሪያ ያደረሰንን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
...
በኢትዮጵያ፣ ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ በሥራ ላይ የዋለው አዲሱ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ፣ አሁን እየታየ ያለውን የኑሮ ጫና ያባብሰዋል ሲሉ አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እና የታክሲ አሽከርካሪዎች ስጋታቸውን ገለጹ፡፡ ነዋሪዎቹ፣ በነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ዙርያ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት አስተያየት፣ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ፣ የትራንስፖርት ወጪን ያንራል፣ በአገልግሎቶችና ሸቀጦች ዋጋ ላይም አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድ...
የእሳት አደጋ ሠራተኞች ብርቱ ትንቅንቅ እያደረጉ ላሉበት አደገኛ የሰድድ እሳት ቃጠሎ፣ ከ130 ሺሕ በላይ የሎስ አንጀለስ አካባቢ ነዋሪዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ታዘዋል። እስካሁን ቢያንስ አምስት ሰዎች በአደጋው ሕይወታቸውን ማጣታቸው እና ከ1 ሺሕ በላይ ሕንፃዎች መውደማቸው ታውቋል።
ትላንት ከቀትር በኋላ ላይ አዲስ የተቀሰቀሰው እና በጥድፊያ እየተዛመተ ያለው ቃጠሎ ‘ሆሊውድ ሂልስ’ በመባ...
በ100 ዓመታቸው ባለፈው እሑድ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተር አስከሬን ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ብሔራዊ ካቴድራል ዛሬ የአሸኛኘት ሥነ ሥርዓት ተደርጎለታል።
ከብሔራዊ ካቴድራሉ የአስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት በኋላ 39ኛው ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተር በትውልድ ከተማቸው ፕሌይንስ፣ ጆርጂያ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ቅጥር ጊቢ ውስጥ ባለፈው ዓመት በሞት ከተለዩት...
ባለፈው መስከረም መጨረሻ በሞዛምቢክ በተካሄደው ምርጫ አሸናፊ እንደሆኑ የሚገልጹት የተቃዋሚ መሪው ቬናንሲዮ ሞንድላኔ ዛሬ ከስደት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ሞንድላኔ አጨቃጫቂውን የምርጫ ውጤትና የጠበቃቸውን መገደል ተከትሎ ሀገር ጥለው ወጥተው ነበር።
የሀገሪቱ የሕገ መንግሥት ም/ቤት ገዢው ፓርቲ ምርጫውን እንዳነሸነፈ ማወጁን ተከትሎ በተነሳው ተቃውሞ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል...
ከፍልስጤም የነፃነት ድርጅት (ፒ ኤል ኦ) ተወካዮች ጋራ ዛሬ የተገናኙት የግብጹ የውጪ ጉዳይ ምኒስትር የፍልስጤማውያን ራስ ገዝ አስተዳደር እንዲጠናከርና ፍልስጤማውያን በአንድነት እንዲቆሙ ጥሪ አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት የውጪ ጉዳይ ምኒስትር ባድር አብደላቲ ለፍልስጤማውያን ራስ ገዝ አስተዳደር ሃገራቸው ያላትን ድጋፍ እንደገለጹ ከቢሯቸው የወጣው መግለጫ አመልክቷል።
በተጨማሪም ፍልስጤማውያ...
የልብ እና የመተንፈሻ አካላት የአሠራር ሥርዓት መመለስ በማይችልበት ደረጃ ሥራቸውን ሲያቆሙ፣በመሣሪያ ላይ የተመሠረተ አተነፋፈስን እንዲቋረጥ ተወስኗል። ይህን ሁኔታ የሚደነግግ ዐዋጅ ባለፈው ሳምንት በምክር ቤት ጸድቋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የተለያዩ አካላት የሰጡት አስተያየት የተካተተበት ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
...
በኢትዮጵያ፣ 84 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመማር ማስተማር ሥራው እንዳይቀጥሉ እንደተወሰነባቸው የሀገሪቱ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን አስታወቀ። ርምጃው የተወሰደው፣ ተቋማቱ ዳግም እንዲመዘገቡ የወጣውን መመሪያ ባለማክበራቸው እንደሆነ የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ቃለአቀባይ ማርታ አድማሱ ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቀዋል፡፡ አስተያየት የሰጡን፣ የዘርፉ ተዋናዮች ደግሞ ለዳግመ ምዝገባው የተሰጠው...
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ በኦሮሞ ነፃነት ታጣቂዎች ተፈፀመ በተባለ ጥቃት ሁለት ሰዎች ትላንት መገደላቸውን ነዋሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቁ።
የኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ሰላም እና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት፣ ከብቶቻቸውን ሲጠብቁ ነበሩ ያላቸው ሁለት ሲቪሎች ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ወሰን የተሻገቱ ባሏቸው ታጣቂዎች መገደላቸውን አስታውቋል።
በግድያው ስሙ ተ...
የየመን አማፂያን በአሜሪካ የጦር መርከቦች እና የንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት ለመፈፀም ሲጠቀሙባቸው የነበሩ የጦር መሣሪያ ማከማቻዎችን መደብደቡን የአሜሪካ ጦር አስታውቋል።
በርካታ ድብደባዎች መደረጋቸውንና በአሜሪካ የጦር ኃይል ዓባላትም ሆነ መሣሪያዎች ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ የአሜሪካ ጦር ማዕከላዊ ዕዝ አስታውቋል።
የዕዙ መግለጫ ድብደባው የተፈፀመበትን የመሣሪያ ማከማቻ ሥፍራ አላሳወቀም።
...
"ፈረንሣይ እስላማዊ አማጺያንን ለመታገል ወታደሮቿን ለዐሥርት ዓመታት ለማሠማራቷ የአፍሪካ ሀገራት ምስጋና አላቀረቡም" ብለው ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን መናገራቸው በአፍሪካ በሚገኙ አጋሮቻቸውና በፈረንሣይ በሚገኙ ለዘብተኞች ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል። የማክሮን ንግግር "የቅኝ ገዢዎች አስተሳሰብ ነው" የሚል ነቀፋም ገጥሞታል።
ማክሮን ሰኞ ዕለት ለፈረንሣይ አምባሳደሮች ባደረጉት ንግግር፣ “ይመስለኛ...
ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአኹን ቀደም የፓናማ ቦይን እና ግሪንላንድን በወታደራዊ ኃይል ወይም ኢኮኖሚያዊ ጫና በማድረግ ለመቆጣጠር ፍላጎት እንዳላቸው ያንጸባረቁትን ሐሳብ ትላንት ማክሰኞ ፍሎሪዳ ክፍለ ግዛት ውስጥ በሰጡት ምላሽ ገፍተውበታል።
ልጃቸው ወደ ግሪንላንድ ድንገተኛ ጉዞ ካደረጉ ጥቂት ሰዓታት በኋላ የተሰማውን የትራምፕን አስተያየታቸውን የተከታተለችው የአሜሪካ ድምጿ የዋይት...
አፍሪካ ምሥራቃዊ ጠረፍ ላይ የምትገኘው የደሴቶች ሀገር ሲሼልስ ሰፊ የባሕል ስብጥር ያላቸው ሰዎች አብረው የሚኖሩባት ሀገር ነች። በዘር ሐረግ ቻይናዊያን የሆኑ ለረጅም ጊዜ ሲሼልስ የሚኖሩ ሰዎች አሉ። አሁን ደግሞ ቻይናዊን ሀገራቸው በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጧ ቁልፍ በኾነችው ሀገር መዋዕለ ነዋይ በመመደብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ተስበው የንግድ ሥራ ለመጀመር ሲሼልስ በብዛት በመግባት ላይ ናቸው።...
ተመራጩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ጥፋተኛ በተባሉበት የአፍ ማሳዢያ ክፍያ ክስ ጉዳይ ዳኛው የቅጣት ውሳኔያቸውን እንዳያሰሙ እንዲታገድ ጠበቆቻቸው ጠቅላይ ፍ/ቤቱን ጠይቀዋል።
ዳኛዋን መርቻን ፣ ትረምፕ ባለፈው ሐምሌ የንግድ ሰነዶችን በማጭበርበር በ34 ክሶች ጥፋተኛ ኾነው በመገኘታቸው የቅጣት ውሳኔያቸውን ከነገ በስቲያ ዐርብ ሊሰጡ ቀጠሮ ይዘዋል።
የቅጣት ውሳኔው መሰማቱ በፕሬዝደንታዊ ተ...
በጸረ ስደተኛ እና በመድብለ ባሕላዊ ኅብረተሰብ ጠል ንግግራቸው የሚታወቁት የፈረንሳይ ቀኝ አክራሪ ፓርቲ መሥራች ዣን ማሪ ለ ፔን በ96 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
በከረረው ቀኝ ክንፍ አቋማቸው ብርቱ ደጋፊዎች የነበሯቸው እና በተቃዋሚዎቻቸው በስፋት ይወገዙ የነበሩት የብሔራዊ ግንባር ፓርቲው መሥራች ማረፋቸውን የፓርቲያቸው ፕሬዝደንት ዦርዳን ባርዴላ ዛሬ በኤክስ ገጻቸው ላይ አስታ...
በአፍሪካ ምሥራቃዊ የውቅያኖስ ጠረፍ ላይ የምትገኘው ትንሿ የደሴት ሀገር ሲሼልስ ሳትጠበቅ ትላልቅ ኃያላን ፉክክር ቦታ ሆናለች፡፡ ቻይና ከሲሼልስ ጋራ ለዓመታት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን ስትገነባ ቆይታለች፡፡ ዩናይትድ ስቴትስ ግን ወሳኝ ወደ ሆነቸው የህንድ ውቅያኖስ ደሴት የተመለሰችው በቅርቡ ነው። ኬት ባርትሌት ቻይና እና ዩናይትድ ስቴትስ የደሴቲቱን ነዋሪዎች ልብ ለመማረክ ምን እያደረጉ እንደ...
በኢትዮጵያ በሚደርሱ የትራፊክ አደጋዎች ዋነኛ ተጎጅዎቹ ወጣቶች መኾናቸው የሚደርሰውን ሰብአዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ከፍ እንዲል አድርጎታል ሲሉ ባለሞያዎች ይናገራሉ፡፡
ለችግሩ ዘላቂ መፍተሔ ለማምጣትም መንግሥት በትኩረት እንዲሠራ አሳስበዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንገድ ደኅንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት በበኩሉ የትራፊክ አደጋ አሁንም ሀገራዊ ስጋት መሆኑን ጠቅሶ የተጎጅዎች መጠን ግን እየቀነሰ መ...
ኬኒያ ውስጥ ካለፈው 2024 ዓመተ ምሕረት መስከረም ወር ወዲህ ባለሥልጣናት የመዘገቧቸው በሴቶች ላይ የተፈጸሙ ወሲባዊ እና ሊሎችም ጾታዊ ጥቃቶች ቁጥር ከሰባት ሺህ አንድ መቶ መብለጡ ተነግሯል። የሀገሪቱ የደኅንነት ሚኒስቴር እየተባባሰ ላለው በሴቶች እና በልጃገረዶች ላይ የሚፈጸም ጥቃት መፍትሔ የሚፈልግ ልዩ ቡድን አቋቁሟል።
መሐመድ ዩሱፍ ከናይሮቢ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታ...
"ሩሲያ ሱዳን ውስጥ የሚዋጉትን ሁለቱን ወገኖች በገንዘብ ትደግፋለች" ስትል ዩናይትድ ስቴትስ ትላንት ሰኞ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከሳታለች፡፡ ይህም ሞስኮ የራሷን የፖለቲካ ዓላማ ለማሳካት ሁለቱንም ወገኖች ደጋፊያቸው እየመሰለች መጫወት ይዛለች የሚለውን የቀደመውን ዋሽንግተን ድምዳሜ ከፍ ያደረገ ሆኖ ታይቷል፡፡
በሱዳን ጦር ኃይሎች እና በፈጥኖ ደራሽ ቡድኑ መካከል በጎርጎርሳውያኑ...
ሄይቲ ውስጥ እየጨመረ በመጣው የተደራጁ የወሮበሎች ቡድን ጥቃት፤ ባለፈው የአውሮፓውያን 2024 ከ5 ሺሕ 600 በላይ ሰዎች መሞታቸው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዛሬ ማክሰኞ በአወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎችም መጎዳታቸውን እና መታገታቸውን አክሎ አመልክቷል፡፡
የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ኃላፊ ቮልከር ተርክ በሰጡት መግለጫ "እነዚህ አሃዞች ብቻቸውን በሄይ...
በኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ተከታዮች የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት - ገናን በማክበር ላይ ሲኾኑ፣ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ተከታታይ ግጭቶች በሚታዩበት የአፍሪካ ቀንድ ክፍል ሠላም እንዲመጣ ጸልየዋል።
በሺሕዎች የተቆጠሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች አዲስ አበባ ቦሌ በሚገኘው መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በሙሉ ነጭ ልብስ በአሸበረቀ አለባበስ ደምቀው በእጆቻቸው የጧፍ መብራት ለኩሰው፣ በጸሎትና በ...
የሶሪያ እስላማዊ አማፂያን ባለፈው ወር ላይ የሀገሪቱን ፕሬዝዳንት በሽር አል አላሳድን ከሥልጣን ካስወገዱ በኋላ፤ በዋናው የደማስቆ አውሮፕላን ማረፊያ ተቋርጠው የቆዩት ዓለም አቀፍ በረራዎች ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ መቀጠላቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
በአውሮፕላን ጣቢያው ከካታር የተጓዙ መንገደኞች ደስታቸውን ሲገልጹ ታይተዋል፡፡ የአየር ማረፊያው ዳይሬክተር አኒስ ፋላህ “ዛሬ አዲስ ም...
በየዓመቱ ታኅሣሥ 29 ቀን የሚከበረው የገና በዓል፣ በኤርትራ የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው በዓል ነው።
የእምነቱ ተከታይ የኾኑ አስመራ ነዋሪዎች፣ ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ ጀምሮ የእርድ እንስሳትን ለመግዛት ገበያ ውለዋል።
አስመራ የሚገኘው ዘጋቢያችን፣ የኤርትራ የገና በዓል ሃይማኖታዊ አከባበር እና ገበያ ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ዘገባ አጠናቅሮ ልኮልናል። ከ...
የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት - ገና በዓል በልዩ ኹኔታ ከሚከበርባቸው የኢትዮጵያ አካባቢዎች በቀዳሚነት የምትጠቀሰው፣ በዐማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ የምትገኘው የላሊበላ ከተማ ናት።
በዩኔስኮ የሰው ልጆች ቅርስ ኾኖ የተመዘገቡት የ11 ውቅር አብያተ መቅደሶች መገኛዋ ላሊበላ፣ በገና በዓል ሰሞን፣ ዐያሌ የአገር ውስጥ እና የውጭ ጎብኚዎችንና ተሳላሚ ምእመናንን በሞቀ አቀባበል ታስተናግዳለች...
በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት በድርድር ለመፍታት፣ በክልሉ የጸጥታ አመራር አካላት ለወራት የተካሔደው ጥረት እንዳልተሳካ የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ ሌተናንት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።
ምክትል ፕሬዝደንቱ ትላንት እሑድ ለክልሉ ብዙኀን መገናኛ በሰጡት መግለጫ፣ በጉባኤ ላይ የተሳተፉትና ያልተሳተፉት በሚል የለዩዋቸው ሁለቱ የተከፋፈሉት የህወሓት አመራሮች...
ገናን ለመቀበል በበዓል ግብይት ላይ ያገኘናቸው አስተያየት ሰጪዎች፣ አንዳንድ የበዓል ፍጆታ ምርቶች ተመጣጣኝ ዋጋ ሲኖራቸው ገሚሱ ጭማሪ ማሳየቱን ተናግረዋል።...
ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የመንግሥታቸውን ወጪ መቀነስ ይፈልጋሉ። ‘የመንግሥት ብቃት መምሪያ’ የሚል መጠሪያ የተሰጠውም አማካሪ ኮምሽን በዋናነት ይህን ጥረት እንደሚመራ ይፋ ተደርጓል። ይሁን እንጂ ውጥኑ በጽንሰ-ሐሳብ ደረጃ ሲቀርብ አዲስ አይደለም።
የአሜሪካ ድምጿ ዶራ መኩዋር ባጠናቀረችው ዘገባ እንደጠቆመችው፣ የዩናይትድ ስቴትስ መሪዎች ገና ከሃገረ መንግሥቱ ምሥረታ ወቅት አንስቶ የመ...
በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ዶናልድ ትረምፕ በፕሬዝደንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን ማረጋገጫ ሥነ ሥርዓት ዛሬ ተካሂዷል።
ከ50 ግዛቶች የተላኩትን የድምጽ ቆጠራ ውጤቶችን የማረጋገጡን ሥነ ሥርዓት የመምራት ኅላፊነት የሃገሪቱ ምክትል ፕሬዝደንት በመሆኑ፣ በፕሬዝደንታዊ ምርጫው የተሸነፉት ካመላ ሄሪስ የዶናልድ ትረምፕን ማሸነፍ ብቻ ሳይሆን፣ የራሳቸውንም መሸነፍ ማረጋገጫ ሰጥተዋል።
በጋራ ም/ቤቱ...
በበርካታ የአሜሪካ ግዛቶች ከትላንት ዕሁድ ጀምሮ የጣለው በረዶና ኅይለኛ ነፋስ ትምህርት ቤቶችና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እንዲዘጉ አስገድዷል።
በመካከለኛው፣ በደቡብ እና በምሥራቅ የሃገሪቱ ክፍሎች በመጣል ላይ ያለው በረዶ በተለይም በአንዳንድ ሥፍራዎች በአሥርት ዓመታት ያልታየ መጠን ሊሆን እንደሚችል በመነገር ላይ ነው።
የአሜሪካ ድምጽ የሚገኝበት ዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ ያሉ ግዛቶች ...
የአሜሪካ ጦር በፈጸመው የአየር ጥቃት 10 የአል ሻባብ አባላት መገደላቸውን የሶማሊያ መንግሥት አስታውቋል።
የሶማሊያ የማስታወቂያ ሚኒስቴር በመግለጫው እንዳለው፣ የአየር ጥቃቱ የተፈጸመው ቢርሃኒ በተባለና ከኪሲማዮ ሰሜን ምዕራብ 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ሥፍራ ነው። የሚኒስቴሩ መግለጫ የወጣው ትላንት እሑድ ሲኾን፣ የአየር ጥቃቱ መቼ እንደተፈጸመ ግን አላሳወቀም።
የሶማሊያው የማስታወ...
የካናዳው ጠቅላይ ሚንስትር ጀስቲን ትሩዶ ከለዘብተኛው ፓርቲ መሪነት ራሳቸውን ማግለላቸውን ዛሬ አስታውቀዋል።
በአመራራቸው ላይ ተቃውሞ የበረታባቸው ትሩዶ በተለይም የገንዘብ ሚንስትራቸው ከሥልጣናቸው መልቀቃቸው በመንግሥታቸው ውስጥ ያለው ችግር የበረታ መሆኑን አመላክቶ ነበር።
በፓርቲያቸው ውስጥ ያለው መፋተግ የሚያመለክተው በመጪው ምርጫ ለመሳተፍ እርሳቸው ጥሩ አማራጭ አለመሆናቸውን እንደሆነ...
ጦርነት ባደቀቃት ሱዳን አብዛኞቹ ሕፃናት የኾኑ ከ30 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ርዳታ እንደሚሹ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዛሬ አስታውቋል።
30.4 ሚሊዮን ከሚኾኑት ውስጥ 20.9 ለሚሆኑት 4.2 ቢሊዮን ዶላር የገንዘብ ርዳታ የጠየቀው ተመድ፣ በሱዳን ያለውን ሁኔታ “ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ሰብአዊ ቀውስ” ሲል ገልጾታል።
ላለፉት 20 ወራት በሱዳን ሠራዊት እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መካከል...
የቀድሞ የግሪክ ጠቅላይ ሚንስትር እና ሀገራቸው ወደ አውሮፓ የጋራ መገበያያ ገንዘብ እንድትቀላቀል ያደረጉት ኮስታስ ሲሚቲስ በ88 አመታቸው መመሞታቸውን የሃገሪቱ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡
በሙያቸው የስነህንጻ ባለሙያ የሆኑት ኮስታስ ሲሚቲስ የሶሻሊስት ፓሶክ ፓርቲ መስራችም ናቸው፡፡
ግሪክንም እአአ ከጥር 1996 እስከ 2004 ድረስ ለስምንት አመታት በጠቅላይሚንስትርነት መር...
የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮል የጸጥታ ሃላፊ የፖለቲካ ቀውሱን ወደ ሌላ ከፍተኛ ግጭት ሊገፋው ይችላል ባሉት የተከሰሱትን መሪ በቁጥጥር ስር ለማዋል ከሚደረገው ጥረት ጋር መተባበር እንደማይችሉ ዛሬ እሁድ ተናግረዋል፡፡
የእስር ትዕዛዙ ቀነ ገደብ ነገ ሰኞ እኩለ ሌሊት ላይ የሚጠናቀቅ ሲሆን የጸጥታ ሃላፊው ፓርክ ቾንግ-ጁን በትብብር ማዘዣው ዙሪያ ያለውን የሕግ ክርክርም ላለመተባበራቸው...
የሶሪያ የሽግግር መንግስት ሚኒስትሮች ፕሬዝዳንት በሽር አል አሳድን ከስልጣን ካነሱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኳታር ባደረጉት ጉብኝት ዩናይትድ ስቴትስ በደማስቆ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ እንድታነሳ አሳስበዋል፡፡
የኳታር ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ የባህረ ሰላጤው ሀገራት ጠቅላይ ሚኒስትሮች ከሶሪያ ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሳድ አል-ሻይባኒ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ሙርሃፍ አቡ ቃስራ እ...
የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ትላንት ቅዳሜ ከዶናልድ ትራምፕ ጋር ለመገናኘት ወደ ፍሎሪዳ ድንገተኛ ጉዞ አድርገዋል።
የአውሮፓ መሪዎች እአአ ጥር 20 ከሚካሄደው በዓለ ሲመት በፊት ከትራምፕ ጋር ያላቸውን ግኑኝነት ለማጠናከር ይፈልጋሉ፡፡
የትራምፕ የማር-አ-ላጎ ሪዞርት አባላት ተመራጩ ፕሬዘዳንት ትራምፕ ሜሎኒን ሲያስተዋውቋቸው በጭብጨባ ሲቀበሏቸው የሚያሳዩ ቪድዮዎች በማህበራዊ ሚድ...
በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ርዕደ መሬት በተከሰተበት ማዕከል አዋሳኝ ከሚገኙት አፋር፣ ኦሮሚያ እና አማራ ክልል አካባቢዎች 80 ሺሕ ነዋሪዎችን ማራቁን መንግሥት አስታወቀ።
በርዕደ መሬት መለኪያ እስከ 5.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ መንቀጥቀጥ ዛሬ አርብ ታኅሣሥ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት መከሰቱን የኢትዮጵያ የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መሥሪያ ቤት አስታውቀዋል።
መሥሪያ ቤቱ በአወጣው መረጃ፣...
“ህንፃዎቹ የተወሰነ የርዕደ መሬት መጠንን ይቋቋማሉ” መንግሥት
በኢትዮጵያ ያሉት አብዛኞቹ ህንፃዎች በዲዛይን ወቅት በሚፈጠር ክፍተትና በግንባታ ጥራት ጉድለት የተነሳ ለርዕደ መሬት አደጋ የተጋላጡ እንደሆኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባለሞያዎች ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከ1976 ዓ.ም ጀምሮ ህንፃዎች ርዕደ መሬትን እንዲቋቋሙ በሚያስችል መልኩ ዲዛይን እንዲደረጉ አስገዳጅ የህንፃ ኮድ ብታዘጋጅም...