Blog Archives

በዜጎች ላይ መንግስታዊ ሽብርን ያማካለ የፖለቲካ አላማና የዲሞግራፊ ቅየራ

ምንሊክ ሳልሳዊ ፡  ልማት ሳይሆን ታሪክን እና ነባር ነዋሪን የማጥፋት ሂደት ነው። ልማት ካለሕዝብ ምንም ፋይዳ የለውም። በቅርስነት የተመዘገቡ በሙሉ እየፈረሱ ነው። ነጋዴዎች የንግድ ድርጅታቸው ከፈረሰባቸው ቦታ ላይ መልሰው ማልማት እንደማይፈቀድላቸው ተነግሯቸዋል። እናንተ ኖራቹበታል እኛ በተራችን እንኖራለን የሚል የፖለቲካ ንግግር ተንሰራፍቷል። በሕጋዊነት ስም ሕገወጥ ተግባር በልማት ስም ዜጎችን የማፈናቀል ተግባር እንዲሁም የመሬት ወረራና ውንብድና እየተካሄደ ነው። በዜጎች ላይ መንግስታዊ ሽብርን ያማካለ የፖለቲካ አላማና የዲሞግራፊ ቅየራ ነው። በነዋሪው እድገት ላይ ምንም ለውጥ ያላመጣ አገዛዝ በየትኛው ሞራሉ ከተማን ማሳመር ይችላል ? ነባሩን ነዋሪ ደሃውን ሜዳ ላይ ወርውሮ የጊዜውን ሰዎች መሬት ማደል የከተማ ለውጥ ማምጣት አይቻልም። ከተማው ላይ ነዋሪውን የሚያሰፍርና ተጠቃሚ የሚያደርግ ልማት ሊፈጠር ሲገባ መሬቱን ሰብስቦ የፖለቲካ ስልጣንን ተጠቅሞ ሕዝብን ማፈናቀል ነገ ከተጠያቂነት አያስመልጥም። የአዲስ አበባን ሕዝብ ያላሳተፈ ማሕበራዊ ትስስሩን የሚያፈርስ ሆን ተብሎ የሚካሄድ የጥፋት ዘመቻ ነው። ዜጎች ዛሬም ነገም መጭውን ጊዜ ሁሉ መብታቸውን ይጠይቃሉ፤ ይህ የማይቀር ሃቅ ነው። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አማራን ሲያስገድል የኖረው ደመቀ መኮንን ከስልጣን ለቀቀ።

ቀናት የስራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ሲያካሄድ የቆየው ብልጽግና ፓርቲ ደመቀ መኮንን ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ወሰነ። የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ደመቀ መኮንንን  በመሸኘትተመስገን ጥሩነህን ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በፓርቲ ደረጃ ሳይሆን በመንግስት ደረጃ በሚል የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ ደመቀን ከስልጣን እንዳነሳ መግለጫው እየተተበቀ ነው። ከህዳር 2020 ጀምሮ በውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነት በእጥፍ የቆዩት የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከሁለቱም የስራ ቦታዎች ዛሬ ማለዳ ላይ መልቀቃቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ካለው ታማኝ ምንጭ መረጃ ኮም አረጋግጧል። እ.ኤ.አ. ከ2012 ጀምሮ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ያገለገሉ ቢሆንም፣ አቶ ደመቀ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት በህዳር 2020 በትግራይ ክልል በተካሄደው ጦርነት ምክንያት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባደረጉት ታይቶ የማይታወቅ ለውጥ ነው። አቶ ደመቀ በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ገዱን ተክተዋል። ይላል የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ምንጮች ዘገባ ። የሶስት ጠቅላይ ሚኒስትሮች ቦርሳ ተሸካሚ የሆነው ሰዉዬ ባለፉት 3 አስርት አመታቶች ; አማራው ሲጨፈጨፍ ቆሞ የሚያጨበጭበው ግለሰብ …….. አማራን ሲያስገድል የኖረው ደመቀ መኮንን ከስልጣን መልቀቁን ሰምተናል። ደመቀ መኮንን ከነዘመዶቹ በትልልቅ ንግድ ላይ ተሰማርቶ ሃገርን ሲዘርፍ እየዘረፈ ያለ ከነአብይ አሕመድ እኩል ወንጀለኛ ነው። ………. በአማሮች ደም የሚሳለቀው ደመቀ መኮንን እና ቡድኑ ለስልጣን ሽኩቻና ለፖለቲካ ሴራ እንጂ ለአማራ ህዝብ ዋጋ አልነበራቸውም፤ የላቸውም ። ደመቀ መኮንን እና ቡድኑ በስልጣን ለመቆየት አማራውን የጦስ ዶሮ አድርገውታል እያደረጉት ነው። በተላላኪነት ማገልገሉ ካለተላላኪነት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከዲያስፓራ መካከል እስክንድር ጫፍ የሚደርስ ? = ትላንትም ነበርን ዛሬም አለን ነገም እንኖራለን ……. እንመሰክራለን

ከዲያስፓራ መካከል እስክንድር ጫፍ የሚደርስ ? ከእስክንድር ነጋ ራስ ውረዱ …… ትላንት ከሕወሓት የሚወረወርላችሁን ቂጣ ስትቆረጥሙ እስክንድር ነጋ ከፕሮፌሰር አስራት ጋር ስለ አማራው ይታገል ነበር…. ከየት ነው የመጣው ማነው ብላችሁ ልታሳንሱት የምትሞክሩት ዛሬ ከአብይ አሕመድ የሚወረውላችሁን ቂጣ እየቆረጠማችሁ መሆኑን ስናይ አፈርን ። ትላንትም ነበርን ዛሬም አለን ነገም እንኖራለን ……. እንመሰክራለን ….. ፕሮፌሰር አስራት ሆዳም አማሮች ያሉት እንደናንተ አይነቶቹን የፍርፋሪ ፍርፋሪ ለቃሚ ነው። እስክንድር ነጋ ለመብትና ነፃነት የከፈለው መስዕዋትነት እናንተ አንዱንም አልከፈላችሁም። እስክንድርን ከምትተቹበት የተደላደለ መቀመጫችሁ ተነስታችሁ ጫካ ግቡና እንያችሁ፤ እስክንድር እንኳን ለወዳጆቹ በጠላቶቹም ዘንድ የተከበረ የአላማ ሰው ነው። ዛሬም በፋኖ ትግል ላይ እየሰራ ያለው ስራ በተግባር እንጂ እንደናንተ በትግል ጠለፋ እና ጥቅም በመሰብሰብ ላይ አለመሆኑን ጠላትም ወዳጅም ይመሰክራል። እስክንድር ነጋ የሚያስተባብረውን ትግል ኑና አስተባብሩ ብትባሉ አንድም ስራ መስራት አትችሉም…. ባለቀ ሳዓት እስክንድርና ድርጅቱን ለማፍረስ ስሙንም ለማጠልሽት የሚካሄደው ዘመቻ አለምክንያት አይደለም:: ከጀርባው ሌላ ተንኮል ከሌለው በስተቀር በቅንነት የተነገረ ትችት ነው ብሎ ለመረዳት አስቸጋሪ ነው:: ዛሬ አማራው ድል አፋፍ ባለበት ወቅት እስክንድር ለፋኖ አስተባባሪነት አይመጥንም ማለት አማራ ነኝ የሚል ሁሉ ሊያወግዘው ይገባል:: ድል አፋፍ ያደረስን አንድነታችን ነው:: ጠላት ሊያጠቃ የሚፈልገው ይህንን ጥንካሬአችንን ነው:: ስንት ተፃፈ? ለዘመናት ስንት ውይይት ተደረገ? የስንት ሰው ህይወት ተፈተሽ? ከዚያ ዘመን በሁዋላ ዛሬ ፋኖ ወደወሳኙ የትግል ምእራፍ ሲያሽጋግረን ተናጋሪዎች፣ ፀሀፊዎች፣ አንደበታቸውንና እውቀታቸውን ከሜዳ ትግል ጋር ማገናኘት ባቃታቸው ወቅት:
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

ሮጠው የታጠቁት ……. ሮጠው ተፈቶባቸው ተዋርደዋል። የሶማሌላንድ ነገር መዘዝ ይዞባቸው ሲመጣ ……..

ሮጠው የታጠቁት ……. ሮጠው ተፈቶባቸው ተዋርደዋል።   የሶማሌላንድ ነገር መዘዝ ይዞባቸው ሲመጣ የመግለጫ ዝናባቸውን ማውረድ ጀምረዋል። የውጪ ጉዳዩ የመንግስት ኮሙኒኬሽኑ የጋኔን ክብሪቱ …. ሁሉም በየፊናው የአብይ አሕመድ ሰዎች የተፉትን እየላሱ አዲስ ትፋታቸውን ማቀርሸት ጀምረዋል። አይ ሱማሌላንድ …. የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል እንደሚባለው የወደብ ባለቤት ሆንን …. ቀይ ባሕር ላይ ተተከልን አሉን በጥሩባቸው ሳይሆኑና ሳይተከሉ ….. ቸኩለው አውርተው ቸኩለው ጨፍረው ቸኩለው ለማስቀየስ እየተሯሯጡ ነው። ሮጠው የታጠቁት ……. ሮጠው ተፈቶባቸው ተዋርደዋል። አንድም የሚያስተውል ባለስልጣንና አማካሪዎች የሌበት አገር ጥፋትና ውሸት ብቻ መሬቱን ተቆጣጥረውታል። ….. ባለስልጣናት ኮንትሮባንዳቸውን እና የዶላርና መሳሪያ ዝውውሩን ንግዳቸውን ለማጣደፍ ሶማሌላንድን የኛ ሙሽራ ሲሏት መዘዝ ይዞባቸው መቷል። አልሸባብ ሊናከስ ጥርሱን እየሞረደ ነው። ሶማሊያውያንም እንዲሁ ከየቦታው ተቃውሞ እያሰሙ ነው። ሃገራትም አህጉራትም የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ቀውስን እንደማይፈልጉ እየተናገሩ ነው። ሲንቀዠቀዡ ለሃገር እዳ እያመጡ ነው። በሃገር ስም ተበድረው የዘረፉት አልበቃ ሲላቸው የስማችን መተሪያ የሆነውንም አየር መንገድ ገለው ሊቀብሩት አሰፍስፈዋል። በጣም አሳፋሪ ነው። ማስተዋል ያስፈልጋል። የአራቱንም ማዕዘን የውስጥና የውጪ ፖለቲካ መገምገም አይችሉም ። አማካሪዎችን አቅጣጫ ጠቋሚዎችም የሉም። ለዚህ ነው በሳል መሪና በሳል ባለስልጣን ያስፈልጋል ብለን የምንጮኸው። #MinilikSalsawi   Photo credit : Amin Amir page-ka Ra’iga
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ለኢትዮጵያ 2023 እጅግ አሳዛኝ እና መጥፎ ነው፤ መንግስት በሚፈጥረው የጦርነትና የረሃብ ቀውስ አገሪቷ እየደኸየች ነው።

It has been a bad year for Ethiopia, a country with very low forex reserves, a double-digit inflation, high external debt, and just recovering from a civil war, and ……. civil war to drought, default on Eurobond የኢትዮጵያ ችግር ሁሉም ሰው ሰራሽ ነው ……. በጣም ዝቅተኛ የውጭ ምንዛሪ ክምችት፣ ባለሁለት አሃዝ የዋጋ ንረት፣ ከፍተኛ የውጭ ብድር እና የእርስ በርስ ጦርነት ፣ ድርቅ ፣ የመብት ጥያቄዎች ፣ ለነፃነት ነፍጥ ያነሱ ሃይሎች ጥያቄ ፣ አገዛዙ ለሁሉም መልስ ለመስጠት ሃይልን ብቻ አማራጭ አድርጎ የሄደበት መንገድና የገጠመው ሽንፈት፤ ከአንዱ ጦርነት አገገምን ስንል ሌላ ጦርነትና ድርቅ እንዲፈጠር የአገዛዙ ተረባርቦ መስራትና ባለስልጣናቱ በጦርነትና በሌብነት ላይ ብቻ አተኩረው መስራታቸው ሃገራችን መጥፎ አመታትን እንድታሳልፍ ዜጎች በስጋት እንዲኖሩ የሌሎች መዘባባቻ እንድንሆን ሆኗል። የውጪ ሚዲያዎች አንዱ የሆነው ኢትዮጵያን እንዲህ ዳሷታል ->> https://minilik-salsawi.blogspot.com/2023/12/ethiopias-bad-year-from-unending-civil.html
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

የአማራ ሕዝብ እያነቁት ያሉትን እነ ሽመልስን እያመሰገነ የሕልውና ትግሉን አጠናክሮ መቀጠል አለበት

የአማራ ሕዝብ እያነቁት ያሉትን እነ ሽመልስን እያመሰገነ የሕልውና ትግሉን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ። አቶ ሽመልስ አብዲሳ ማክሰኞ አዳማ በነበረው የምክክር ጉባዬ ለኦሮሞ ምሁራን ያስተላለፈው መልዕክት በአማራ ሕዝብ ላይ ቀጥታ ጂኖሳይድ አውጇል። ይህ ግለሰብ በአማራ ሕዝብ ላይ ጂኖሳይድ ሲያውጅ የመጀመሪያው ባይሆንም የኦሕዴድ አገዛዝ በአማራ ሕዝብ ላይ ያለውን አቋም እና ወደፊት ያቀደውን ያሳያል። ሕወሓት አማራውን በወረርሽኝ እና በክትባት ለማጥፋት ብዙ ሰርቶ አልተሳካለትም። የአማራ ክልል አመራሮች ይህንን እየሰሙና እያዩ ለአማራ ሕዝብ ከመቆርቆር ይልቅ የገዢው አጋር በመሆን አማራውን እያስደፈሩት ይገኛሉ። ይህ አደገኛ አካሄድ ለማስቆም ከደመቀ መኮንን ጀምሮ እስከ ታች አመራሮች ድረስ አንዳችም ስራ ሲሰሩ አልታየም። ለአማራ ቆመናል ብለው በአማራው ላይ የቆሙ ስለሆን ሕዝቡ ለነፃነቱ እና ለመብቱ ለሕልውናው ማድረግ የጀመረውን ትግል አጠናክሮ መቀጠል አለበት፤ አማራው እንዲታገል የሚያደርጉትን እንደ ሽመልስ አብዲሳ ያሉትን ሰዎች እያመሰገነ ለሕልውናው ትግል ካለመታከት ሊሰራ ይገባዋል። ይህንን ከታች ያለውን በጥሞና ያዳምጡት https://www.facebook.com/RealMinilikSalsawi/videos/338246112270670 #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ስርዐት አልበኝነትን ያነገሰው የወሮበሎች አገዛዝ

ስርዐት አልበኝነትን ያነገሰው የወሮበሎች አገዛዝ (ምንሊክ ሳልሳዊ) ስለ አብይ አገዛ ባለፉት አመታት በርካታ ጉዳዮች ተነስተዋል። የአብይ አገዛዝ በውሸቱና በማጭበርበር ፖለቲካው አፍዝዟቸው የሰገዱለት የተወሰዱት ሲነቁበት የተወሰኑት ደሞ እየሰገዱለት ሲሆን የተወሰኑት ደሞ ለስለላ በውጪ ሃገር አሰማርቷቸው የለውጥ ሃዋርያ ሆነው ለመነበብ ከመሞከራቸውም አልፎ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመተቀን አቅጣጫ በመተቆም የአማራን ሕዝብ እያስደበደቡት ነው በኢትዮጵያ የተንሰራፋው እና የዘር ፖለቲካን በተረንነት እየተጠቀመበት በሃገር እና በሕዝብ ላይ ከፍተኛ ሰቆቃና ኪሳራ እየፈጸመ ያለው የከሰረ መንግስት በዋነኛነት ስርዐት አልበኝነትን የሃገሪቱ መመሪያ አድርጎ ከመንቀሳቀሱም በላይ ባለስልታኖቹ የሕግ የበላይነትን በመደፍጠጥ ከፍተኛ የሆነ ወንጀል በሕዝብ ላይ እንዲሁም በአለም አቀፍ ዲፕሎማቶች ላይ በመፈጸም የሃገራችንን መልካም ገፅታዎችን እያበላሹ ቀጥለዋል። ስርዓት አልበኝነት የሕግ የበላይነትን ውጦታል። ጠንካራ መንግስታዊ መዋቅር ባለመኖሩ ስርአት አልበኝነት በሀገሪቱ ነግሷል። ህግና ስርዓት መከበር አለበት የሚሉ ዜጎች ወደ እስር ቤት እየተወረወሩ ይገኛሉ። ዜጎች በዘፈቀደ ከሕግ ውጪ ስለሚጋዙ በኢትዮጵያ መንግስታዊ ስርዐት አልበኝነት ከመስፋፋትም አልፎ መደበኛ የመንግስት ስራ ሆኗል። በአለም አቀፍ ደረጃ በመንግስትነት ስልጣን ላይ ተቀምጦ በህግ አልመራም እና አሻፈረኝ ያለው የአብይ አገዛዝ ብቻ ነው። ነገሮች ሁሉ ከመስመር ወተዋል። መንግስት ነኝ የሚለው አካል ሁሉም ነገር ከቁጥጥሩ ውጪ ነው። በህግ አምላክ ሀገር በህግ ትመራ ያሉት በሙሉ በሚባልበት ሁኔታ በወሕኒ ቤት ናቸው። ሃገርን እያመሱ እየዘረፉ እየገደሉ ያሉ ስርዐት አልበኛ ቡድኖች አገሪቷን እየመሩ በሕግ አምላክ የሚሉትን እያሳደዱ እያሰሩ ይገኛሉ። በሕገመንግስት እና በዲሞክራሲ ሽፋን ሕዝብን እያንገላቱ ያሉ የመንግስት ባለስልታናት
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

የሩዋንዳውን የደም ካሳ ሕወሓት በልቶታል፤ የሶማሊያው ላይ ኦሕዴድ አሰፍስፏል !

የደም ካሳ እንዳይዘረፍ ማን ዋስትና ይሰጣል ? ዘረፋውና የመሳሪያ ግዢው የፈጠረው የዶላር ማጣት በሽታ ……….. የሩዋንዳውን የደም ካሳ ሕወሓት በልቶታል፤ የሶማሊያው ላይ ኦሕዴድ አሰፍስፏል ! የሃገሪቱን የውጪ ምንዛሬ ሙጥጥ እያደረገ የሚዘርፈው የአብይ አገዛዝ፤ ለአፍሪካ ልማት ባንክ ሳይከፍል እንደተከፈለ አድርጎ በተዘዋዋሪ የዘረፈው የአብይ አገዛዝ፣ የውጪ ምንዛሬን ወደአገር እንዳይገባ የሚያደርጉና ዶላርን ከሃገር የሚያሸሸ ባለስልጣናትን የታቀፈው የአብይ አገዛዝ ከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ እጥረት ሲገጥመው አበዳሪዎች ዶላሩን ሲከለክሉት አሁን ደግሞ በሶማሊያ የሞቱ የሰላም አስከባሪ ወታደሮችን የደም ካሳ እንዲከፈለው ጠይቋል። ይህ ሁሉ የዶላር ችግር የፈጠረው ውጥረት ነው። ዶላሩ ባይዘረፍ እና ለመሳሪያ ግዢ ባይውል ኖሮ ይህን ሰዓት የዶላር ችግር ባልኖረ ነበር ። በተጨማሪም ለሃገር ውስጥ የፖለቲካ ችግሮች ፖለታዊ መፍትሄ ቢሰጥና መንግስታዊ የሃይል ተግባራት ቢቆሙ የዶላሩ ችግር መፍትሄ ያገኝ ነበር። የዶላር ችግር ያመጣው ጣጣ 8000 የፔፕሲ ሰራተኞች ስራ አጥ ሆነው ከነቤተሰባቸው ሜዳ ላይ ሊበተኑ መሆኑን የሰማነው ትላንት ነው። ባለፉት አምስት አመታት ሃገሪቷ ያገኘቻቸው ብድሮች፤ እርዳታዎች፤ ከተለያዩ መስኮች የተገኙ የውጪ ምንዛሬዎች የት ገቡ ብለው ብትጠይቅ አንድም ለሕዝብ ጥቅም አልዋሉም ። ካሁን ቀደም ወደ ሩዋንዳ ዘምቶ የነበረውን የሰላም አስከባሪ ሃይል የተከፈለውን ዶላር ሕወሓቶች ዘርፈውታል፤ አሁን ደሞ በተራው ኦሕዴድ ወደ ሶማሊያ የዘመተውን የሰላም አስከባሪ ሃይል የኢትዮጵያ ወታደሮችን የደም ካሳ ሊዘርፍ አሰፍስፏል። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአማራ ክልልን እንደ ደቡብ ክልል የመከፋፈል ሃሳብ ወደ ተግባር ለመለወጥ እንቅስቃሴው ተጧጡፏል

Minilik Salsawi  = አማራ ክልልን ለሁለት ለሶስት መከፋፈል የሚሉት ሃሳብ አዲስ አይደለም ! አብይ አሕመድ ጠረጴዛ ላይ የነበረ አሁንም ያለ ነው። ብልጽግና በሚያመቸው መልኩ እንጂ በሕዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ስራ ሲሰራ አይተን ሰምተን አናውቅም። እነጃልመሮ እና ሌሎችም ኦሮሚያ በውስጡ ያሉ እንደ ወለጋ እና ባሌ ተነጥለው ክልል እንዲሆኑ ጠይቀዋል ሸዋም እንዲሁ ፤ እነ ጀዋር የአማራ ክልል ትልቅ ነው መከፋፈል አለበት ብለው ከነገሩን አራት ዓመት ሆኖታል ። ለምን በዚህ ጉዳይ ላይ ውሳኔ አይሰጥም ? የሚለው አካል ፋይሉን አንስቶ የመበጣጠስ ሕልሙን ሊያሳካ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምሯል። አማራ ክልል ካልከፋፈልነው ሕዝቡ አይገዛልንም በሚል መነሾ እንደ ደቡብ ክልል ሊበጣጥሱት ካሰቡ አመታት ሆኗቸዋል። ለዚሁም ይሆናቸው ዘንድ የተለያዩ ቡድኖችን ለወሎ፤ ለጎንደር፤ ለአገው እና ሌሎች አከባቢዎች ቀደም ብለው አዘጋጅተው ፕሮፓጋንዳ ሲሰራባቸው ታዝበናል። ለዚህም ጉዳይ ተዘጋጅተው በምርጫ ቦርድ እውቅና ያገኙ የክልልነት ጥያቄ የሚያቀርቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በብልፅግና ተዘጋጅተዋል። ዛሬ ላይ ኮማንድ ፖስቱ ያቀረበው እና ተመስገን ጥሩነህ እንደተናገረ አድርገው ያቅርቡት እንጂ ይህ የቆየ የአብይ አሕመድ ሃሳብ እና እቅድ ነው። ፋኖ እየከረከመ ልክ ሲያስገባቸው በጭንቀት የተወጠሩት ብልጽግናዎች እቅዱን ቶሎ ወደ ተግባር ለማምጣት እየተጉ ነው። የአማራን ሕዝብ ለማንበርከክ የሚኬድበትን መንገድ የአብይን አገዛዝ ዋጋ እንዳያስከፍለው ያሰጋል። አንድ ሆኖ የኖረን ሕዝብ አንድ አይደለህም መከፋፈል አለብህ የሚል የራሳቸውን በብሄርና በቋንቋ ያደራጁትን ሕገመንግስት የሚጥስ አሰራር እያሳዩን ነው። ይህ የለመዱትና ሕገመንግስት መናድ የሚሉት ተቃዋሚዎችን ለመክሰስ ብቻ የሚጠቀሙበት ሕገ
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

ዜጎችን መታደግ የማይችሉ የሃይማኖት መሪዎች ቆባቸውን ያውልቁ::

አቡነ ኤርሚያስ ቤተክርስቲያኗን የበለጠ የሕልውና አደጋ ውስጥ ከተዋታል። ተገነዙ የሚባሉ አባቶች የድሆች እረኛ መሆን የሚገባቸው አባቶች ለተኩላዎች ቤተክርስቲያንን ከፍተው ምዕመናንን በማስበላት ላይ ናቸው ። የሬሳ ንግድ ብለው በመንግስትም ይሁን በተቃዋሚዎቹ በመላው ሃገሪቱ ግድያ በተፈፀመባቸው ንፁሃን ላይ ተሳልቀዋል። አቡነ ኤርሚያስ ወንጀል ስለጀመሩ ወንጌል ከማስተማር ይልቅ የመደመርን መንገድ ያስተምሩ። #MinilikSalsawi ዜጎችን መታደግ የማይችሉ የሃይማኖት መሪዎች ቆባቸውን ያውልቁ:: በዜጎች ላይ የሚደርሱ በደሎች የማይቆረቁራቸው የሃይማኖት አባቶች ጵጵስናቸውን/ክሕነታቸውን አስረክበው ወድ ፖለቲካው ሊቀላቀሉ ይገባል። (ምንሊክ ሳልሳዊ) በኢትዮጵያ በሃይማኖታዊ የመንፈስ ጥኡም ሰበካና ዜማ ጋር በማጣፈጥ የጨቋኞችን የበላይነት በመስበክ ሕዝብን ማስፈራራት እና ማሸማቀቅ የጳጳሳት እና የሼህዎች አብይ ተግባር ነው።ዜጎችን መታደግ የማይችሉ በአስቸኳይ ቆባቸውን አውልቀው ከተራው ሕዝብ የመቀላቀል ግዴታ አለባቸው።ቤተክርስቲያን እና መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ እጅና ጓንት ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የማያባራ ጭቆና ማካሄድ ከጀመሩ ረዥም ዘመናት ተቆጥረዋል። ይብልጡኑ የመንግስቶች ጎህ ከቀደደ ጀምሮ በተለይ የተዋህዶ ሃይማኖት መሪዎች አስፈሪ እና አስደንጋጭ እንዲሁም አሳዛኝ ደግሞም አሳፋሪ ቃላቶችን በመጠቀም ስጋዊ እና ምድራዊ ስልጣኖችን ለገዢዎች ለማደላደል ይህ ነው የማይባል ግፍ በምእመናኖቻቸው እና በሌሎች አማኞች ላይ ፈጽመዋል አስፈጽመዋል፤ እየፈጸሙ ነው፤ እያስፈጸሙ ነው። ይህ የማይዋጥለት አሊያም የሚክድ ካለ እውነት የማይደላው ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ጨቋኝ መንግስታት የሆኑ ከጥንት እስከ ዛሬ የተንሰራፉ በህዝብ ላይ የሚያደርጉት ጭቆና እና በደል ታሪክ የማይሽረው ጠባሳ በሰው ልጆች የትውልድ ሂደት ላይ መፍጠሩ እንደተጠበቀ ሆኖ የሃይማኖቶች ሚና ግን እጅግ በሚያሳዝን መልኩ ዜጎች በግፍ በጨቋኝ መንግስቶች
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአፍሪካ ባንክን ዳይሬክተር በጠባቂዎቻቸው ያስደበደቡት እነ አብይ ማጅራት መቺነታቸው እንዲድበሰበስ ይፈልጋሉ።

ብልጽግና የአለም አቀፍ ማጅራት መቺዎች ስብስብ ነው የምንለው ወደን አይደለም፤ የአብይ ሚኒስትሮች ጠባቂዎቻቸውን እየላኩ ታላላቅ ዲፕሎማቶችን በማስደብደብ እና በመዝረፍ ስራ ላይ ተሰማርተዋል። ይህ መንግስታዊ ሽብር ነው። ካሁን ቀደም የነበሩ መንግስታት የገነቡትን የሃገር መልካም ገፅታ እነ አብይ አበላሽተውታል። የውሸታሞች፣ የግፈኞችና የሌቦች ስብስብ የሆነው ብልፅግና በሃገሪቱ ለውጥ ከማምጣት ይልቅ ስርዐት አልበኝነትን አስፍኗል። ቪዲዮ https://www.facebook.com/RealMinilikSalsawi/videos/179922058517011 በኢትዮጵያ ሰላም መጥፋት እና የሕግ የባላይነት እንዳይኖር ከፍተኛው እንቅፋት እየሆኑ ያሉት የብልጽግና ባለስልጣናት መሆናቸው በተደጋጋሚ እያየን ነው። በሃገር ውስጥ በዜጎች ላይ ከሚፈፅሙት ወንጀል አልበቃ ያላቸው አለም አቀፍ ማጅራት መችነታቸውን በተግባር አሳይተዋል። የአለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር የሆኑትን ዲፕሎማት የአሕመድ ሸዴ ጠባቂዎች እንደደበደባቸውና ይህን ተከትሎ የአፍሪካ ልማት ባንክ ሰራተኞቼ የደሕንነት ስጋት አለባቸው ብሎ ድርጅቱን እንደዘጋ ባለፉት ሁለት ቀናት ከሰማናቸው መረጃዎች እና ከባንኩ ቢረጋገጥም አሁንም የአብይ አሕመድ መንግስት በይፋ ጥፋቱን አምኖ ይቅርታ መጠየቅ ሲገባው ለማድበስበስ የሚሄድበት መንገድ አሳፋሪ መሆኑን የባንኩ ሰዎች ይናገራሉ። ኢትዮጵያ በአለም መድረክ እያዋረዱ የሚገኙት የአብይ ባለስልጣናት ሃገሪቷን እና ዜጎቿን በጦርነት መግደላቸው ሳያንሳቸው አለም አቀፍ ወንጀል መፈፀማቸው ለአፍሪካ የነፃነት ቀንዲል የሆነችዋን አገራችንን በአለም አደብባባይ አዋርደዋታል። የሕግ የበላይነት አለመኖሩ ሕዝቡ ሰላሙን እንዲያጣ አብይና ባለስልጣናቱ በሕዝብ ላይ እንዲቀልዱ ሆኗል ፋኖ አዲስ አበባ ደርሶ እስኪገላግለን። #Minilik
Posted in Amharic News, Ethiopian News, Video

እያወራን ያለነው ስለ ትምሕርት ሚኒስቴር ነው ! ብርሃኑ ነጋ በገዛ ፈቃዱ ስልጣን መልቀቅ አለበት ።

እያወራን ያለነው ስለ ትምሕርት ሚኒስቴር ነው ! ብርሃኑ ነጋ በገዛ ፈቃዱ ስልጣን መልቀቅ አለበት ። አብይ በፋኖ ትግል መውደቁ አይቀርም። ትውልድን መግደል፣ አድልዎና ፖለቲካዊ ሻጥር በትምሕርቱ ላይ እየተፈጸመ ነው። የፕሪቶሪያው ውል በጦርነት ስነ ልቦና የተጎዱ ተማሪዎች ልዩ ጥቅምን አካቶ የያዘ ከሆነ ይነገረን፤ አድልዎ ተደርጓል ብለው የቤተመንግስት ሰፈር ሰዎችም እንዳያስቡ ግልፅና ዝርዝር ማብራሪያ ይሰጣቸው። በትግራይ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከወሰዱት ውስጥ 73.09% የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች እና 51.38% የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች በአጠቃላይ 66.96% ተማሪዎች 50% በላይ ውጤት በማምጣት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ማግኘታቸውን ተነግሯል።በአገር ደረጃ 3% የማይሞላ ተማሪ አልፏል ተብሎ በክልል ደረጃ ይህን ይህል አልፏል ሲባል የትምሕርት ሚኒስትሩ መክሸፋቸውን በደንብ እያሳየን ነው። ከመቶ 69. ተማሪዎች ማለፋቸው ምንም ችግር የለውም፤ በጦርነት ለተጎዱ አከባቢዎች ቅድሚያ መሰጠቱም በፍፁም የሚያከራክር ጉዳይ አይደለም ይባል ። በትግራይ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኃላም በደም አፋሳሹ ጦርነት ምክንያት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ርቀው መቆየታቸው የሚዘነጋ አይደለም። ትውልድ መግደሉና አድሎአዊ አሰራሩ ታሳቢ በማድረግ ከመነሻ እስከመድረሻው ስትገሰግስ ግን ጥያቄ የሚያስነሱ በርካታ ጉዳዮች አሉ። ፈተናው አገር አቀፍ እንጂ ክልል አቀፍ አይደለም። ትምሕርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ የት ሄደው ነው ? የክልሉ ትምሕርት ቢሮ ሃላፊ ያውም በፌስቡክ ገፃቸው ይህን ጉዳይ ሊያውጁ የቻሉት ? ትምሕርት ሚኒስትሩ አልዋጥልህ ብሏቸው ነው መግለጫ ያልሰጡት ? ያው የተለመደው የአብይ ትዕዛዝ እንደተጠበቀ ሆኖ ማለት ነው። የትምሕርት ሚኒስቴር ስልጣን ምንድነው ? ቀድሞ የትምሕርት ቢሮው መናገሩ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሕወሓት ትጥቅ ይፍታ፤ ኤርትራ ከትግራይ ትውጣ፤ አብይ አሕመድ በአማራና ኦሮሚያ የከፈተውን ጦርነት ያቁም ያሳስበናል። ( አንቶኒ ብሊንከን)

PRESS STATEMENT ANTONY J. BLINKEN, SECRETARY OF STATE NOVEMBER 2, 2023  ከአንድ አመት በፊት በፕሪቶሪያ የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ደረጃ ፓናል ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ)፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና አሜሪካ ታዛቢዎች ጋር በመተባበር በመንግስት መካከል የጦርነት ስምምነት (COHA) እንዲቆም አመቻችተዋል። ኢትዮጵያ እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)። ስምምነቱ ሽጉጡን ጸጥ በማሰኘት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩትን የገደለ እና ሚሊዮኖች ቤታቸውን ለቀው እንዲሰደዱ ያስገደደውን አሰቃቂ የሁለት አመት ጦርነት አብቅቷል። ዛሬ፣ የ COHA አንደኛ አመት የምስረታ በዓል ላይ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ሕይወታቸውን ያጡ እና በደል የደረሰባቸውን ሰዎች ታስታውሳለች። እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን ሰላምና ፍትህ ለመደገፍ ቃል እንገባለን። ዩናይትድ ስቴትስ በ COHA አተገባበር ላይ የታዩትን ከፍተኛ መሻሻሎች ትቀበላለች፣ የትግራይ ጊዜያዊ ክልላዊ አስተዳደር መመስረት፣ አስፈላጊ አገልግሎቶችን እንደገና መጀመር፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦትን፣ በትግራይ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ተደራሽ ማድረግ እና የአፍሪካ AU ክትትልን ተግባራዊ ማድረግን ጨምሮ። የማረጋገጫ እና ተገዢነት ሜካኒዝም። የሀገር አቀፍ የሽግግር የፍትህ ፖሊሲን ለማቋቋም መንግስት እና የሽግግር የፍትህ የስራ ቡድን የባለሙያዎች ቡድን ወሳኝ እርምጃዎችን ወስደዋል። While TPLF forces have disarmed their heavy weapons and begun to demobilize, more actions are needed to bring lasting peace and stability to Tigray. Eritrean forces must fully withdraw. Both Ethiopia and Eritrea must refrain from provocation and respect the independence, sovereignty, and territorial integrity of all
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከእዳ ወደ ምንዳ ወይስ ከእዳ ወደ እዳ ?

ከእዳ ወደ ምንዳ ወይስ ከእዳ ወደ እዳ ? ( በምንሊክ ሳልሳዊ ) በአማራው ትግል በፋኖ ጀግንነት ነፍስ ውጪ ነብስ ግቢ ላይ ያለው የብልፅግና አገዛዝ የሕዝብን ጥያቄ በስልጠና እና በሰልፍ የሚፈታው ይመስል ሲደክም እያየነው ነው። የሐገርን ሐብት ለብክነት ከመዳረግ ውጪ ስልጠና እና ሰልፍ ምንም ፋይዳ የለውም። ብልፅግና አንድም ቀን ለዘላቂ መፍትሔ ሲሰራ ታይቶ አይታወቅም። ሐገር ሰላም አታለች፣ ሕዝብ በኑሮ ውድነት እና በስራ ማጣት እየተሰቃየ ነው፣ ዜጎች ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ ለመስራት አዳጋች ነው፣ ስጋትና ውጥረት አገሪቱ ከመውረር አልፈው በየአቅጣጫው የጦርነት ቀጠናዎች በርክተዋል። የዚህ ሁሉ ችግር መንስኤው ብልፅግና ነው። ለችግሮች መፍትሔ መፈለግ ዳገት የሆነበት አገዛዝ በስልጠና ጊዜ ማባከኑ ሳያንስ ሰልፍ ለማድረግ ደፋ ቀና እያለ ነው። ከአሁን ቀደም መፍትሔ ባላመጡ ስራዎች ላይ ተጠምዶ አገርንና ሕዝብን ለጉስቁልና እየዳረገ ነው። ሕዝቡ ከጫፍ እስከ ጫፍ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማሕበራዊ ጥያቄዎች አሉት። ይህንን ጥያቄ መመለስ ያለበት አገዛዝ ሀይል መጠቀምን አቁሞ አስቸኳይ መልስና መፍትሔ ይስጥ ወይንም የመፍትሔ ለሚሰጥ አካል ስልጣኑን ይልቀቅ። በስልጠናና በሰልፍ የሕዝብ ችግርን መፍታት አይቻልም ፤ በሚዲያ ፕሮፓጋንዳ ፣ በውሸት ተስፋ ዲስኩር አሊያም በአጀንዳ የሕዝብ ችግር አይፈታም ። ብልፅግና የራሱንም የትውልዱንም ጊዜ በማባከን ስራ ላይ ተጠምዷል ፤ ግጭትና አጀንዳ መጥመቅ ይቁም። ምንዳ ሳይሆን እዳ የተሸከመው ሕዝብ ጦርነት ሰልችቶታል። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

እውነት ግን ጦርነት ወይስ የጀርባ ስምምነት ስለ ባሕር በር አብይ የሚጮኸው ?

እውነት ግን ጦርነት ወይስ የጀርባ ስምምነት ስለ ባሕር በር አብይ የሚጮኸው ? (ምንሊክ ሳልሳዊ) ዜጎቹን አፍሶ በጦርነት ለመማገድ ስብሰባ የሚቀመጥ መንግስት እንዴት ስለ ሰላምና ደሕንነት የማውራት ሞራል ይኖረዋል ? በባሕር በር ፉጨት አብይንም ኢሳያስንም ማመን አያስፈልግም፤ የትግራዩ ጦርነት በሕወሓት ሽፋን አስጩኸውን ሚሊዮን ንፁሃን ረግፈዋል ………. የቀይ ባሕር ጉዳይ የአማራ ትግልን ለማስቀየስ ከሆነ መልፋት አያስፈልግም፤ ፋኖ ስራውን እየሰራ ነው። . ፋኖ በተግባር እንጂ በአጀንዳ አይኖርም። ……….. ጦርነትም ላይኖር ይችላል ከጀርባ መስማማት ሌላው ጉዳይ ነው። ኢሳያስ አፍወርቂ የኢማራቱን ንጉስ እግር ተከትሎ ከሚዲያ እውቅና ውጪ አዲስ አበባ በመጣበት ወቅት የአሰብ ወደብ በባዶው ከሚያዛጋ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ 30% ወስደህ አሊያም ከአባይ ግድብ ኤሌክትሪክ ተቀብለህ ወደቡን አካፍለን የሚባለው የጀርባ ስምምነት እውን የመሆን መስመርም ሌላኛው የፖለቲካ ሰነድ ነው። ከአለም የገንዘብ ድርጅት ጋር ስብሰባ ተቀምጠው የዋጋ ግሽበቱን በእጥፍ ለማድረግ ሲደራደሩ በገበያ ለመወሰን ሲስማሙ ለሕዝብ የኑሮ ውድነት ጥልቀት ውስጥ ሲከቱት ከባሕበር ጥያቄው ጋር የማያያዝበት ምክኛቱ ምን ይሆን ? …….. ከኤርትራ ጋር ለሚኖረው ቀጣይ ጦርነት ሕዝቡ ሊዋጋልኝ አይችልም በሚል ስጋት ወጣቱን አፍሶ ወደ ጦርነት ለመማገድ ማሰብ ሞኝነት ነው። ….. በብሄራዊ ውትድርና ወሰድከውም ካለፍላጎቱ አፈስከውም …………. የታፈሰው ወጣት ሳይተኩስ እጁን ለኤርትራ መንግስት እንደሚሰጥም ማሰብ ያስፈልጋል። አሜሪካ ወደ ኤርትራ እንዲተኮስ ውክልና እንደማትሰጥ ፍንጭ አሳይታለች ፤ አሜሪካ ባለው የአብይ አገዛዝ ላይ እምነት እንዳሌላት በተደጋጋሚ አመላክታለች። የብልጽግና ሽለላና ፉከራ የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ ሆኖ እንዳይቀር
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ማዘናጊያ፣ መከፋፈያ እና ጊዜ መግዣው የድርድር ሃሳብ ………

ማዘናጊያ፣ መከፋፈያ እና ጊዜ መግዣው የድርድር ሃሳብ ……… ( ከድርድር በፊት አብይ ጦሩን ከአማራ ክልል ሊወጣ ና ቅድመ ሁኔታዎችም ሊቀመጡ ይገባል) በአማራ ክልል እንደ አዲስ ጦርነት ለመጀመር ሰራዊት በክልሉ በማስፈር ላይ የሚገኘው የአብይ አገዛዝ ከፋኖ ጋር ለመደራደር በደሕንነት ቢሮው በኩል ከ27 በላይ የፋኖ አዋጊዎችን የቡድን መሪዎችን እና ሌሎችን በማጨት ወደ ድርድር ለመግባት እቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው ሲሉ ለአገዛዙ ቅርብ የሆኑ ምንጮች እየነገሩን ነው። ይህ በአንድ በኩል ጦርነቱን አድሶ ለመጀመር እየሰራ በሌላ በኩል እንደራደር የሚለው አገዛዝ እጅግ አደገኛ የሆነ የከፋፋይነትና የማዘናጋት ስራ እየሰራ ነው። አብይ እንደፈለገው ለመደራደር ማንም ዝግጁ አይደለም። ሶስተኛ ወገን የውጪ ታዛቢ ባለበት በአንድ ወጥነት ሕዝባዊ ሃይሉ መደራደር አለበት። በአማራ ክልል የተጀመረውን ጦርነቱን እንደ አዲስ ለመጀመር አዳዲስ ክፍለጦርችን ወደ ክልሉ እያስገባ ያለው የአብይ አገዛዝ ድርድር ከፈለገ ለምን አዳዲስ በርካታ ሰራዊት ያቀፉ ክፍለጦሮችን እና ከባድ መሳሪያዎችን ወደ ክልሉ ማስገባት አስፈለገው። የአብይ አገዛዝ ድርድር ከፈለገ ያሉትን እና አዲስ ያስገባውን ሰራዊት ከአማራ ክልል ማስወጣት አለበጥ ካልሆነ ድርድር የለም። ይህ በድርድር ስም ምንም ውል ያልታሰረለትና ቅድመ ሁኔታ የሊለው አስተሳሰብ ሆን ተብሎ የአማራ ትግልን ለመከፋፈል ሲልም ለሚጀምረው አዲስ ጦርነት ዝግጅት ጊዜ መግዣ ሲሆን መጭውን ጊዜ አስልቶ በሃገራዊ ምክክር ኮሚሽንም በኩል ለማዘናጋት እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ወደ ፋኖ ሕዝባዊ ሃይል የሚሄድበት ዋና ግብ አዘናግቶ ለማስመታት መሆኑ በተደጋጋሚ ተነግሯል። ስለዚህ የአብይን አገዛዝ ማመን አያስፈልግም
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ገዢዎቹ የሚያራምዱትን የዘር ፖለቲካ እየደገፈ ስለ ዜግነት ፖለቲካ ሊሰብከን የሚዳዳው ኢዜማ አማራን ፅንፈኛ ብሎ ለመፈረጅ ሞራል የለውም።

ዶክተር ጫኔ በኢዜማ ውስጥ ያለውን አደርባይነት፣ የስልጣን ሽኩቻና አማራ ጠል ፖለቲካ ማሳያ ነው። ገዢዎቹ የሚያራምዱትን የዘር ፖለቲካ እየደገፈ ስለ ዜግነት ፖለቲካ ሊሰብከን የሚዳዳው ኢዜማ አማራን ፅንፈኛ ብሎ ለመፈረጅ ሞራል የለውም። ኢዜማ ተንቀዠቀዠ የጤና ያድርግለት ….. ኢዜማ አመራሩን ለመፈረጅ በጣም ተጣደፈ ….. ሰሞኑን በየቲክቶኩ ኢዜማ ስብሰባ ላይ የተቀዱ ድምጾችን ለገዢዎቹ አሳልፈው የሰጡት እነብርሃኑ ነጋ የዶክተር ጫኔን ስም ሲያብጠለጥሉ አይተናል ታዝበናል ። በሃገሪቱ የሕግ የበላይነት እንዳይሰፍን ጋሬጣ ከሆኑ አንዱ ኢዜማ መሆኑን አሳይቶናል። ግለሰቡ ተተርጣሪ ናቸው ተብለው ሲያዙ ንፁህም ሆነው እንደሚገኙ ሊታሰብ ይገባ ነበር መግለጫውን ከመጻፉ በፊት፤ ኢዜማ ጤናማ ያልሆነ የአደርባይነት ፖለቲከ ውስጥ መዘፈቁን የሚያሳይ መግለጫ ነው። ብርሃኑ ነጋ በድርጅታችን ውስጥ ያሉ የአማራ ጽንፈኞችን መንግሥት አይታገስም ማለቱ ለአማሮች አፈና ትልቁን ሚና እየመራ መሆኑ ምስክር ነው። ያሳፍራል ! ይህ የሚያሳየው በኢዜማ ውስጥ ያለውን የስልጣን ሽኩቻና አማራ ጠል ፖለቲካ ነው። ጫኔ ከበደን ጽንፈኛ አማራ ነው ብሎ ያሳፈነው ብርሀኑ ነጋ ነው! ተብሎ መፃፉ ይታወሳል። በተባለው መሰረት ይህንን የሚያጠናክርና የሚያረጋገጥ መግለጫ ከኢዜማ ተሰጥቷል። የኢዜማው ጫኔ ከበደ በዐቢይ አሕመድ ደኅንነቶች የታፈነው ንጹሐን ዘመዶቹ ፋኖን ትደግፋላችኹ ተብለው በደብረ ማርቆስ ከተማ ከሰሞኑ ስለተገደሉበትና መከላከያ ፋኖን ሳይኾን ሰላማዊ ሰዎችን ከቤታቸው እያወጣና በየመንገዱ እያሳደደ ያለ ፍርድ በጭካኔ እንደሚረሽን በግፍ የተረሸኑ ዘመዶቹን እንደ አብነት በኢዜማ ስራ አስፈጻሚ ስብሰባ ላይ አቅርቦ ዝም ማለት የለብንም በማለቱ መታሰሩ እና ይህንንም የስብሰባውን ድምፅ ለአገዛዙ አካላት በማቀበል አሳፋሪ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አራዳ ሕንፃ ፡// ታሪክ የሌላቸው ኢትዮጵያን የሚጠሉ ባለስልጣናት በአጋጣሚ እጃቸው የገባውን ስልጣን ለጥፋት እየተጠቀሙበት ነው።

ታሪክ የሌላቸው ኢትዮጵያን የሚጠሉ ባለስልጣናት በአጋጣሚ እጃቸው የገባውን ስልጣን ለጥፋት እየተጠቀሙበት ነው። አማራ ክልል ላይ የሚደረጉ የምድርና የአየር ድሮን ጥቃቶችን ለማስቀየስ የሚደረግ የአጀንዳ ጨዋታ ይሆንልናል ብላችሁ አስባችሁ ከሆነ አትሞኙ። እነዚህ በጥላቻ የተሞሉ ዘረኞች የአማራን ታሪክ እያጠፉ ይመስላቸዋል ፤ እያጠፉ ያሉት የአንድ ትውልድ የጋራ እሴትን ነው። አልገባቸውም እንጂ የአማራ ታሪክ በወርቅ መዝብ ላይፋቅ በአለም ልብ ውስጥ ተፅፏል። የአራዳን ትዝታ ለማጥፋት የአራዳ ሕንፃን ማፍረስ የለሊት ስራ አድርገውታል። ጨለማን ተገን አድርጎ ሕንፃን መናዳ ለፖለቲከኞች ስራ ሆኗል። በቀንማ ያፍራሉ። ተከራካሪ የሆነ አካል አለመኖሩ ሕዝብን መናቅ የተጠናወተው አገዛዝ በማናለብኝነት መንግስታዊ ወንጀል ይሰራል። ይህንን ሆን ተብሎ የሚደረግን የጥፋት ሒደት ትውልዱ ሊያስቆመው ይገባል። ነገ ወደ አዲስ አበባ ታሪካዊ ሐውልቶች መዞራቸው ስለማይቀር ሳይቃጠል በቅጠል ነው። እንደ ሕዝብ አስተዳዳሪ አዳዲስ ነገሮችን መገንባትና ማስፋፋት ሲገባ የከተማ ምልክቶችን ማፍረስ አስነዋሪ ድርጊት ነው። ታሪክ የሌላቸው ኢትዮጵያን የሚጠሉ ባለስልጣናት በአጋጣሚ እጃቸው የገባውን ስልጣን ለጥፋት እየተጠቀሙበት ነው። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በአብይ ሿሚነት የሚፈራረቁት ባለስልጣናት የአማራን ሕዝብ የግፈኞች ሰለባ አድርገውታል።

በአብይ ሿሚነት የሚፈራረቁት ባለስልጣናት የአማራን ሕዝብ የግፈኞች ሰለባ አድርገውታል። አሁንም ተዘጋጅተዋል። አዳዲስ ተመዳቢዎች አሉ ስንል እነ አብይ ሐሳባቸውን ሊቀይሩ ይችላሉ የሚሉ አስተያየቶች ቢኖሩም ያም ሔደ ያም መጣ አማራ ከጀመረው ትግል አያፈገፍግም። ለአማራ ክልል አዲስ ሹመኞች ከኦሕዴድ ሰፈር ሊመደቡለት መሆኑ ታውቋል። እነዚህ ተመዳቢ ሹማምንት ጨፌ ኦሮሚያ ኦረንቴሽን የተሰጣቸው ሲሆን ከአራት ኪሎ የሚወርድ ትእዛዝ አስፈፃሚዎች ናቸው። የአማራ ክልል ምክር ቤት የነዚህን ሰወች ሹመት አፀደቀ ማለት የአማራ ሕዝብን ጥያቄ እንዳይመለስ ተባባሪ እንደሆነ ይቆጠራል። በድሮን የደበደበውን ሕዝብ ሳያፍር አስተዳዳሪ ልሹምልህ ማለት ይሉኝታቢስነት ነው። የአማራ ሕዝብ ጥያቄው ካልተመለሰ ትግሉ አያቆምም። የአማራ ሕዝብ ላይ ዝመቱ ብሎ ለኦሕዴድ መሪዎች ደብዳቤ የላከው ይልቃል ከፋለና ጀሌዎቹ አዲስ አበባ አንዴ ገስት ሐውስ አንዴ ሆቴል በቁም እስር እየተንከራተቱ ጥቃቅን ሹመቶችን አንጋጠው እየጠበቁ ነው። ከዚህ በላይ ውርደት ይጠብቃቸዋል። በክልሉ በአብይ ሿሚነት የሚፈራረቁት ባለስልጣናት የአማራን ሕዝብ የግፈኞች ሰለባ አድርገውታል። ከሕዝብም ከግፈኞችም ሳይሆኑ እንደ ሸንኮራ እየተመጠጡ ተተፍተዋል። በቀጣይነት የሚመጡ የኦሕዴድን ተልእኮ ከማስፈፀም የዘለለ አንዳችም ነገር ለአማራ ሕዝብ የሚፈይዱት ስለሌለ ልንታገላቸው ይገባል። የአማራ ሕዝብ ጥያቄዎች እስኪመለሱ ትግሉ ይቀጥላል። በመላው ኢትዮጵያም ይዳረሳል። የአማራ ሕዝብ ጥያቄ በክልሉ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ክልሎች ነው። የሕልውና ትግል ነው። አያቆምም። ፋኖም ስራውን እየሰራ ነው። #MinilikSalsawi ባለስልጣናቱ በወጡበት እንዲቀሩ ተወሰነባቸው። ባይጸናላቸውም አዳዲስ አንዳውላዎች ሊሾሙ ነው። 1. ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ተሹመዋል። የኢንተርፕራይዞች ሃላፊ የነበሩ ሲሆን የርዐሰ መስተዳደር ይልቃል ከፋለን ቦታ ተረክበዋል።
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጥንቃቄ የሚሻው እርቅና የሽግግር መንግስት

ጥንቃቄ የሚሻው እርቅና የሽግግር መንግስት የገዱ አንዳርጋቸውን የፓርላማ ንግግር ተከትሎ ቀደም ሲል የመንግስት ባለስልጣናት ጦራቸው በፋኖ መሸነፉን ተከትሎ ሲሰብኩን የነበረው የሰላም እና እርቅ ጉዳይ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ጎን ለጎንም አፈናውና እስሩ ተስፋፍቷል። ሰላም እና እርቅ ማንም አይጠላም።የጥላቻ ንግግሮችን እና የፍረጃ ቃላት ውርዋሮዎችን በመተው፣በመከባበር ላይ የተመሰረተ ውይይትና እርቅ ያስፈልጋል።የሚለው አባባል ሁላችንም የምንደግፈው ጉዳይ ነው። የሚቋቁመው የሽግግር ስርዐት እንደ ጌታቸው ረዳ አይነት በፖለቲካ ሴራ የተጠመደና የገዳዮች ስብስብ ሊሆን አይገባም። ካለፈው ልንማር ይገባል። ጦሩን እንደ ግል እቃው ያሰማራው ብልፅግና ከባህር ዳር ሆኖ ነፍጥ ያነሳን አካል ከነፍጥ በፊት የፍቅር ጥሪ በማድረግ የማርገብና ጠላትን የማሳፈር ጥበብ መላበስ ይገባል። እያለን ጦሩ ግን ተኩስ ሊያቆም አልቻለም። እርቅ ሰላም ፍቅር መሆኑ መልካም ቢሆንም ለፖለቲካ ሴራ መጠቀም ግን አደገኛ ነው። ይህንን እርቅና ሰላም ለመመስረት የግዴታ የሽግግር መንግስት ያስፈልጋል። የሽግግር መንግስቱን የሚያቋቁሙት ደሞ ወንጀለኞች ገዳዮች እና ዘራፊዎች የሆኑት የአማራ ክልል እና የፌዴራል ክልል ባለስልጣናት ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም የባለድርሻ አካላት ሊሆኑ ይገባል፤ በዋናነት ፋኖውና የአማራ ሕዝባዊ ግንባር አመራሮች የሽግግር መንግስቱ ዋና መሪዎች ሊሆኑም ይገባል። በትግራይ ተቋቋመ ተብሎ ሕወሃት የዋጠው አይነት ጊዜያዊ አስተዳደር አማራ ክልል ሊደገም አይገባም። የሽግግሩ መሪዎች አማራ ክልል ላይ እስክንድር ነጋ አሊያም ሌሎች የፋኖ እና የአማራ ሕዝባዊ ግንባር አመራሮች ሊሆኑ ይገባል። በዚህ መልክ ሰላምና እርቅ ማምጣት ይቻላል። አትኩሮትም ሊሰጠው ይገባል። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ፖለቲካዊ መፍትሄ ለሚያስፈልገው ጉዳይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ እብሪተኝነት ነው።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መፍትሄ አይሆነም፤ አይሳካምም ። መንግስት ከሕዝብ ጋር ለመዋጋት አዋጅ ሲያውጅ ብልጽግና የመጀመሪያው ነው። ፓርላማ ውስጥ ያሉ የአማራ ክልል ተወካዮች አዋጁ እንደማያፀድቁና ስብሰባውን ረግጠው መውጣት አለባቸው። Imageምንሊክ ሳልሳዊ = የገዢው ፓርቲ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅመወሰኑን ሳይነጋ እየሰማን ነው። ይህ አዋጅ ባለፉት አምስት ወራት አብይ አሕመድ መራሹ አገዛዝ በአማራ ክልል ሲያደርግ የቆየውን ተኩስ እንዲጨምር በችግሩ ላይ ቤንዚን ያርከፈከፈ ማስተዋል የጎደለው አዋጅ ነው። የአማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል ላይ እስከሆነ ድረስ የአማራን ሕዝብ ጥያቄዎች መንግስት ሊመልስ ሲገባው ጦርነት በስፋት ማወጅ ክልሉን ለማውደም ካልሆነ በስተቀር በፍፁም መንግስት አትራፊ አይሆንም። መንግስት ባለፉት አምስት ወራት በአማራ ክልል የከፈተውን ጦርነት ተከትሎ ሕዝቡ ከፋኖ ጎን እንደሆነ የታወቀ ጉዳይ ነው፤ መንግስት በችግሩ ሰአት ከጎኑ የነበረውን ፋኖን ለማጥፋት የጀመረው ጉዞ የከፋ ከመሆኑ ውጪ አለመሳካቱ የታወቀ ሲሆን መንግስት በአማራ ሕዝብ የበለጠ ቂም ያተርፋል እንጂ ከሕዝብ ጋር መዋጋት ከጀመረ ሰነባብቷል ሕዝቡም ከፋኖ ጋር መሆኑን በተግባር አሳይቶታል። አሳፋሪ አካሄድ ነው። በአማራ ክልል ህዝብ ላይ የተከፈተው ጦርነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቷል። ጎንደር፣ ጎጃም፣ ሸዋ፣ ወሎ በተለያዩ አካባቢዎች ነገሮች ከቁጥጥር ውጭ ሆነዋል። መንግስትም ጦርነት የሚሰለቸው አልሆነም። ህዝብም ላይመለስ ተነስቷል። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከአማራ ህዝብ ጎን እንዲቆም፣ እየተደረገ ያለውን አውዳሚ ጦርነት እንዲያወግዝ እጠይቃለሁ። ከህዝብ ጋር ጦርነት ገጥሞ ያሸነፈ የለምና መንግስት የሰላም አማራጭ መከተል እንዳለበት እመክራለሁ። ከትግራይ ጋር በተደረገው
Posted in Amharic News, Ethiopian Drama

ፋኖ የመንግስትን እና የሕዝብን ንብረት አለማውደሙና አለመዝረፉ የብልፅግና አመራሮችን አበሳጭቷል።

እውነትን ከወደድከው የሰሞኑን ልንገርህ …… ( ምንሊክ ሳልሳዊ ) ፋኖ በተቆጣጠራቸው አከባቢዎች፣ ታላላቅ ኤርፖርቶች እና የመንግስት ተቋማት አለመውደማቸው፣ ሕዝብ በጅምላ አለመገደሉ፤ የሕወሓት፣ የኦነግና የኦሕዴድ ጦር ጭካኔዎች በፋኖ አለመደገማቸው ፤ ባንኮች እና የግለሰብ ንብረቶች የሃገር ሃብቶች አለመዘረፋቸው የሕዝብ አገልግሎቶች አለመቋረጣቸው ሰዎቹን አበሳጭቷል። እነ ደመቀ መኮንን የሚያሾፉበት እነ አብይ በድሮን እየደበደቡት ያልተሳካላቸው የአማራ ሕዝብ ወንድነቱን እያሳየ ነው ። ካድሬዎችን ሳይቀር መዳፋቸውን በአገጫቸውና በአፋቸው ላይ እያስጫነ ነው። ድርድርን ለፖለቲካ ሲስተም የሚተቀመው መንግስት በፋኖዎችና በአማራ ሕዝብ ዘንድ እምነትን አቷል። ካሁን ቀደም በሽምግልና ስም በርካታ የፕሮፓጋንዳ ስራ በመስራት ራሱን አሸናፊ ለማስመሰል የሄደበት መንገድ አጋልጦታል። ስለዚህ የአማራ ሕዝብ ያተኮረው ወደ ሕልውና ትግሉ እንጂ ወደ ድርድር አይደለም። ይህ መንግስት ቆም ብሎ ሊያስብ ይገባል። ለጊዜው የሕዝብን ሰላምና ደሕንነት በመበጥበጥ ስልጣንን ማስረዘም ይቻል ይሆናል ዘላቂነት ግን የለውም። ኦሮሚያ ክልል ጨምሮ በሌሎች ክልሎች ለሚደርሱ ጥቃቶችና መፈናቀሎች ምንም ድምፅ የሌላቸው ሰዎች አማራ ክልል የሕልውና ማስከበር ላይ ሊያሞተሙጡ ይከጅላሉ። መጀመሪያ መንግስት የሚሄድበትን አካሄድ አቁም ይበሉትና ባልታጠቁ ሰዎች ላይ የሚደረገውን የድሮን ጭፍጨፋ ግታ ይበሉትና ሰላማዊ እና የተረጋጋ ነገር መንግስት እንዲፈጥር ይወትውቱ እንጂ የሕልውና ትግል የሚያደርገውን ሕዝብ ለፖለቲከ ጥቃት እንዲጋለጥ ማድረግ ከባድ ወንጀል ነው። ቅድሚያ ለሕዝብ ሰላምና ደሕንነት መንግስት ሰላማዊ ዋጋ መክፈል አለበት እንጂ ጦር ሰብቆ ማሸበር ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው። የአብይ አሕመድ አገዛዝ አማራ ላይ ሲሆን ጦር መስበቅ፤ ከባድ መሳሪያ ማስወንጨፍ ማስፈራራት መዛት
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

ኢዜማ እየቃዠ ነው ! በኦነግ ሸኔ ወንጀል የሚስማማው ኢዜማ ትግራይና አማራ ላይ ሲሆን ቀስቱን ይወረውራል።

አማራ ሲደራጅ ጠንክሮ ሲወጣ ሁሉም አይኑ ደም ይለብሳል ! በኦነግ ሸኔ ወንጀል የሚስማማው ኢዜማ ትግራይና አማራ ላይ ሲሆን ቀስቱን ይወረውራል። የብልጽግና አመራሮች ዛሬ ኢዜማ ያወጣውን መግለጫ ነገ አብን እንዲደግመው ያደርጉታል። አማራ ሲደራጅ ጠንክሮ ሲወጣ ሁሉም አይኑ ደም ይለብሳል ! በኦነግ ሸኔ ወንጀል የሚስማማው ኢዜማ ትግራይና አማራ ላይ ሲሆን ቀስቱን ይወረውራል። የብልጽግና አመራሮች ኢዜማ ያወጣውን መግለጫ አብን እንዲደግመው ያደርጉታል። አማራ ክልል በሰሜኑ ጦርነት ኩፍኛ የወደመና በህወሓት ሀብቱ ተሟጦ የተዘረፈ ክልል ነው።ክልሉን ወደነበረበት ለመመለስ ብዙ ዓመታት ይፈጃል።ታዲያ የፋኖ ጦርነት ችግሩን የባሰ አያወሳስብም? ብሎ የሚጠይቅ ሳይሆን መንግስትን የሚያበረታታው የፖለቲካ ጥቅመኛ በዝቷል። ኢዜማ እየቃዠ ነው ! የአብይ አህመድ አሽከር የሆነው እና በግንቦት ሰባት ላይ ጥርሱን የነከሰው የኢዜማ አመራር ሆን ብሎ ያስተዋላውን እንዳላስተዋለ ሲሆን ማየት ይገርማል። አማራ ለምን ተደራጀ ለምን ሕልውናውን ለማስተበቅ ቃታ ወደ መሳብ ሄደ የሚለውን ለመመለስ አልፈለገም። የችግሮች ሁሉ መሰረት መንግስት ነው። የችግሮቹ ሁሉ ምንጭ በአብይ አሕመድ የሚመራው የመንግስት አስተዳደር ነኝ የሚለው አካል ነው። መንግስት መዋቅሮቹን ይፈትሽ ማለት ከጀመርን አራት አመታት አልፈውናል። ኢዜማም የችግሮቹን ምንጭ ጠንቅቆ እያወቀ ወደ ሕልውና ትግል የሚያደርገው የአማራ ሕዝብ ጣቱን መጠቆሙ የፖለቲካ ዳረጎቱን ላለማጣት መንደፋደፉን ያሳየናል። በውስጥ ችግር የሚታመሰው ኢዜማ ዝም ብሎ አርፎ ፍርፋሪውን ቢለቅም ይሻለዋል። ኢዜማ ታሟል፤ ይህን ደሞ ሁላችንም እናውቀዋለን፤ መከላከያ ሰራዊቱን ማነው የሚያሰማራው የሚለውን እውነት እያወቀ ብዙ ሊዳስሰው ይሁን ሊነካካው አልፈቀደም። ኦሮሚያ ክልል ላይ በርካታ ወንጀሎች እየተሰሩ ሕዝብ እየተጨፈቸፈ መከላከያ ሰራዊቱ እየተመታ ምንም ማለት የማይፈልጉ አካላት ኢዜማን ጨምረው ዛሬ በአማራ ትላንት በትግራይ ላይ መንግስታዊ ወንጀል ሲፈጸም ከመንግስት ጎን ቆመው መንግስትን እያባበሉ ሌላው እንዲጨፈጨፍ እየሰሩ መሆኑን ስናይ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በኢትዮጵያ ኢንሳይደር ቢሮ ዉስጥ ባለ ካዝና ውስጥ የነበሩ ንብረቶች ባልታወቁ ሰዎች ተዘረፉ

በኢትዮጵያ ኢንሳይደር ቢሮ ዉስጥ ባለ ካዝና ውስጥ የነበሩ ንብረቶች ባልታወቁ ሰዎች ተዘረፉ በሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሥር የሚተዳደረው “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ ሚዲያ እሁድ፣ ሐምሌ 9፣ 2015 ለሰኞ አጥቢያ በቢሮው ውስጥ ያለ ካዝና ባልታወቁ አካላት ተሰብሮ፣ ንብረቱ መዘረፉን የኢትዮ ኢንሳይደር መስራች እና ዋና አዘጋጅ አቶ ተስፋአለም ወልደየስ ለዳጉ ጆርናል ተናግረዋል። የሚዲያ ተቋሙ በሚሠራቸው ዘገባዎች ሳቢያ ተደጋጋሚ ጫናዎች እየደረሰበት ሲሆን፣ ይህ ዘረፋም የነዚህ ተደራራቢ ጫናዎች ተቀጥያ ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል። ትላንት እሁድ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ባልደረቦች እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት በዜና ክፍሉ ውስጥ በሥራ ላይ ቆይተው፣ ቢሮውን ቆልፈው ከወጡ በኋላ፣ ዛሬ ጠዋት 1፡00 ሰዓት ገደማ ቀድመው የደረሱ ባልደረቦች የቢሮው በር እንደተቆለፈ ነገር ግን ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጡ የዜና ክፍሉ ንብረቶች የተቀመጡበት ካዝና በኃይል ተሰብሮ የተቀመጡት ንብረቶችም ከቦታቸው እንዳልነበሩ ገልፀዋል ። በዘረፋው ካዝናው ውስጥ የነበሩ ሦስት አዳዲስ እና ዘመናዊ ዲጂታል ካሜራዎች፣ ሁለት ዙም ሌንሶች፣ ሌሎች አራት መደበኛ ሌንሶች፣ አራት ላፕቶፖች እና አንድ ለቢሮ ስራ የሚጠቀሙበት ስማርት የሞባይል ስልክ መወሰዳቸውን ዋና አዘጋጁ ተናግረዋል። እንዲሁም በህንፃው ውስጥ የነበረው የደህንነት ካሜራ እንደማይሰራ እና በቢሮው ውስጥ ግን ምንም አይነት የደህንነት ካሜራ አለመኖሩን ተናግረዋል። ዘረፋውን ቦሌ ክፍለ ከተማ ለሚገኘው ለአደይ አበባ ስታዲየም አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ያመለከቱ መሆኑን እና  የጣቢያው ፖሊሶች በ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ቢሮ በመገኘት አሻራ አንስተው፣ የተወሰኑ ባልደረቦችን ቃል መቀበላቸውንም አክለው የኢትዮ ኢንሳይደር መስራች እና ዋና ዘጋጅ አቶ ተስፋለም ወልደየስ ለዳጉ ጆርናል
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፊቱ ከባድ አደጋ ተደቅኖበታል።

ኢትዮጵያዊ ተቋማትን ለማፍረስ ያልቦዘነው የአብይ አገዛዝ አቶ ግርማ ዋቄ አየር መንገዱ ካርጎው ለቻይና ብድር ክፍያ መዋል የለበትም፣ የመንገደኞች ገቢ ለቤተመንግስት ማሰሪያ መዋል የለበትም የሕዝብ ንብረት ነው። ብለው ስለመለሱ ከቦርድ ሊቀመንበራቸው እንዲለቁ ተደርገዋል። በምትካቸው ወታደር ተሹሞበታል። የአብይ አገዛዝ የኢትዮጵያ አንድነትን ደግፈው ይዘዋል ያላቸውን ተቋማት ማፍረስ ዋነኛ አላማው አድርጎ ዘምቷል። የኢትዮጵያ አንድነት በዋነኛነት ደግፈው ይዘዋል ያላቸውን የእምነት ተቋማት ለማፍረስ በጉዞ ላይ ያለው የአብይ አገዛዝ አሁን ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ፊቱን አዙሮ የሃገራችንን መኩሪያ የሆነውን ተቋም ለማፍረስ እየተሯሯጠ ነው። የተፈረደበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቻይናን ብድር ሊከፍል የአብይን ቤተመንግስት ሊገነባ ነው ። አገር ለማፍረስ አገርን አስተሳስረው የያዙ ተቋማት መናድ አለባቸው የሚለው ኦሕዴድ አየር መንገዱን ሸጦ በመቶ ሺዎች ተፈናቅለው እየተገነባ ያለው የአብይ ቤተመንግስት ለመስራት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ገንዘብ ለመጥቀም አስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ የገባው አገዛዝ አየር መንገዱን ለቻይና አሳልፎ ለመስጠት መንገድ ጀምሯል። ጠንካራ ተቋማትን በማፍረስ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያውያንን ማዳከም የሚል ዘመቻው ተጧጡፏል። ቻይና አየር መንገዳችንን ለመቆረጣተም ጥርሶቿን አሹላ ተዘጋጅታለች፤ ሽያጩን የሙስናው የኮንትሮባንዱ አባት ደመቀ መኮንን ጨርሶት መቷል። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በኢመደበኛ የሕገ መንግስት ማሻሻያ ሽፋን አዘናግቶ ብልጽግና የፈለገውን ሕግ አምጥቶ እንዲጭንብን ልንፈቅድለት አይገባም።

ምንሊክ ሳልሳዊ ፡ ሕግ አውጪውም፣ ሕግ አስፈጻሚውም፣ ሕግ ተርጓሚውም ያላከበረው ፣ ለሕዝብ ያልበጀው፣ በኢሕአዴግ የፖለቲካ ፕሮግራም የተቀረጸው (ሕገ አራዊት) ሕገመንግስትን ከማሻሻል በፊት ሕግና ስርዐት ያለው መንግስት ይኑር ። ሕገመንግስት ማሻሻል የሁላችንም የአስርት አመታት ጥያቄ ቢሆንም የሃገርን ሰላምና የዜጎችን ደሕንነት መጠበቅ ያልቻለ መንግስት ባሌለበት እንዴት ሕገ መንግስት ይሻሻል ይባላል ? ቅድሚያ መንግስት ይኑር ! በኢመደበኛ ስም አዘናግቶ ብልጽግና የፈለገውን አምጥቶ ሊጭንብን ልንፈቅድለት አይገባም። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኮሚሽን ለሚዲያ ፍጆታ መስርቶ የሚያፈርሰው የአብይ አስተዳደር የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑን በጀት እንዳገደው ሰምተናል። እነ ኢዜማ ተስፋ የጣሉበት ይህ ኮሚሽን ወዴት እያመራ ነው ውይይት እያሰናዳሁ ነው ብሎ ሊወድቅ እየተንገዳገደ መሆኑ ሲሰማ ያው እጣው ካሁን ቀደም እንደተባለው እንደ እርቀ ሰላም ኮሚሽን እና የወሰን ማካለል ኮሚሽን የመፍረስ አደጋው ከሕገ መንግስት አሻሻይ አዳዲስ ኮሚቴዎች መቋቋም ጋር ተከትሎ መሆኑ ስንሰማ ሃገሪቷ መንግስት አልባ መሆኗን ምስክር ነው። የሕገ መንግስት መሻሻልን የሚመለክተው አካል የሕገ መንግስት አርቃቂ ጉባዬ ሆኖ ሳለ አብይ አሕመድ ፖሊሲ ይነድፉልኛል ብሎ ያሰባሰባቸው የፖለቲካ አሽከሮቹ ስለሕገ መንግስት መሻሻል ሲነግሩን አግራሞትን ፈጥረዋል። የሕገ መንግሥት መሻሻል የዘመናት ጥያቄአችን፣ ሕልማችንም ነበር። አሁን ባለው ሁኔታ ግን ለአኔ የቅንጦት ጥያቄ ነው። ኢመደበኛ የሕገመንግስት ማሻሻያ : ሕጉ ምንድነው የሚለው ? ማነውስ እንዲያሻሽለው የሚፈቀድለት ? የሕገመንግስት ጉባዬውስ ? ብዙ ጥያቄዎች የሚያስነሳ ኢመደበኛ የሕገ መንግስት ማሻሻያ ነው ። ሕገወጥነትን በጋራ ልንታገለው ይገባል። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ አቅቶት ባለሐሳቦችን ያሰረው ጠቅላይሚኒስትር እንዴት ሐሳብን በሐሳብ ስለማሸነፍ ያወራል ?

ሿሿ ትጠላለህ ! ትገላለህ ሀውልት ታስመርቃለህ፤ ከዛ በማግስቱ አዲስ ግድያ ትፈጽምና ሮጠህ ለለቅሶ ትሄዳለህ ወዲያው ደሞ ሃሳብህን በተግባር ለመከወን ንፁሃን ላይ የሆነ ታርጋ ለጥፈህ ትዘምታለህ ። ግድያውን ለተቃዋሚዎች ቀድመህ ታደርሳለህ ። በብርሃን ፍጥነት መግለጫ ታወጣለህ ። አጣዳፊ ታደርገውና አላማህን ለማሳካት ሁሉንም ወንጅለህ አማራን ትጥቁን ለማስፈታት ሰራዊትህን ታዘምታለህ ። የግርማ የሺጥላ ሕይወት የተቀጠፈው በዚህ አካሄድ ነው። ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ አቅቶት አክቲቪስቶችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ፖለቲከኞችን እና ሌሎች ባለሃሳቦችን ሰብስቦ ያሰረው ጠቅላዩ @AbiyAhmedAli በምን ሞራል ነው ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው አካላት ብሎ መግለጫ የሚያወጣው ? @danielkibret ንገረው ! pic.twitter.com/3u497tAvKw — Minilik Salsawi 💚 💛 ❤ (@miniliksalsawi) April 28, 2023 May be an image of textምንም ጥይት ሳይተኩሱ ሃሳብ ስለሰጡ ብቻ ጋዜጠኞችን አዛውንቶችን ለቃቅሞ አስሮ በሃሳብ መሞገት ባህል በሆነበት አለም ይለናል።ለምን ይዋሻል ጠቅላዩ እያደረጉ ያሉት ያሳብ ያላቸውን አፍነው ያስራሉ ጠመንጃ ያነሱትን ደግሞ ይሸልማሉ ይስማሉ። ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ አቅቶት አክቲቪስቶችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ፖለቲከኞችን እና ሌሎች ባለሃሳቦችን ሰብስቦ ያሰረው ጠቅላይሚኒስትር በምን ሞራል ነው ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው አካላት ብሎ መግለጫ የሚያወጣው ? የአመክንዮ ያለህ ! ግርማ የሺጥላ በተገደለ በደቂቃዎች ውስጥ የፌደራል መንግስት በርካታ የምርመራ ሂደቶችን እንኳን ሳይጠብቅ ስለ ግድያው መደምደሚያ ላይ የደረሰው ለምንድነው ? ምን አላማ አንግቦ ነው ? ለግድያው ጥቅም ላይ የዋለው ላውንቸር ወይስ ጥይት ? ለምን ? ፈጥኖ ጽንፈኛ ማለት ማን ላይ ሊዘመት ተፈልጎ ነው ? …. ብዙ ተያያዥ ጥያቄዎችን ማንሳት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የተወረደበት የሞራል ዝቅጠት ሰላምን ማስፈን አይሸፍነውም።

በንፁሃን ደም ላይ ሲቀልዱ አያፍሩም ! የተወረደበት የሞራል ዝቅጠት “ሰላምን ማስፈን” አይሸፍነውም። ሰላምን የሚቃወም የለም፤ ጥያቄው ብዙ ወንጀልን እና ውድመትን መሸለም እና ማሞገስ የሞራል ማረጋገጫ ነው ወይ ነው !   ስለሰላም ያወራሉ። ራሳቸው ካስታጠቁት ገዳይ ቡድን ጋርም ልንደራደር ነው ይሉናል። ይህን የውሸት ሰላማቸውን የሚሰብኩት አማራ ክልል ላይ መከላከያውን አሰማርተው እያስገደሉ እያሰሩና እያፈኑ እያጠፉ ነው። ተጠያቂነትና ኃላፊነት መውሰድ የሚባል ነገር የለም ። የሕሊና ጸሎት የሚያደርጉት ለተሰዉ ሰማዕታት ሳይሆን ራሳቸው ለገደሏቸው ሕዝቦች ነው። ይህ አደገኛ የመንግስት አካሄድ በፍጹም ለሕዝብ አይስማማም። በአዲስ አበባ የታየው የትራጂኮ ኮሜዲ መልክት ባጭሩ ሚሊዮኖችን ጨፍጭፍ፣ ድፈር፣ አፈናቅል፣ አውድም አንተም ትሸለማለህ፣ ትሾማለህ። ዛሬ የ“post truth” ዘመን ነው ቢባልም፣ የተወረደበት የሞራል ዝቅጠት “ሰላምን ማስፈን” አይሸፍነውም። ሕዝብን ለፖለቲካ ፍጆታና ለስልጣን ማቆያ መሰየፍ ወንጀል ነው። ትልቅ ወንጀል ፤ ተጠያቂው ማነው ? የፖለቲከኞች ሰላም ማስፈን የቱን ያሕል ይጓዛል። ሰላምን የሚቃወም የለም፤ ጥያቄው ብዙ ወንጀልን እና ውድመትን መሸለም እና ማሞገስ የሞራል ማረጋገጫ ነው ወይ ነው ! ሌላ ዙር ጦርነት አማራ ላይ ታውጆ እንዴት ስለ ሰላም ይወራል ? ጥፋት እየሰሩ ሰላም እያወጁ ያሉት እኮ ወንጀለኞቹ ናቸው፣ ሲፈልጋቸው ጦር ይሰብቃሉ፤ ንጹሃንን ያስጨርሳሉ ፤ የይስሙላ ሰላም ያውጃሉ። የሕዝብ ፍላጎት የማያሟላ መንግስት ሊወገድ ይገባል። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የዜጎች ደሕንነትና የሃገር ሰላም በእጁ ያሉት የደሕንነት ተቋም ሽባ ሆኗል፤ ተመስገን ጡረታ ወጥቶ ምክትሉ አቶ ታዜር ቢተካስ ?

ተመስገን ጡረታ ወጥቶ ምክትሉ አቶ ታዜር ቢተካስ ? ሲሳይ ቶላ የሽብር ኔትወርክ አጣማጅ ስለሆነ ወደ ሌላ ቢዛወርስ ? የደህንነት ተቋሙን በተመለከተ በደምላሽ ገብረሚካኤል እና በመሃመድ አደም ጊዜ በተደጋጋሚ ተናግረናል። ( * ዝርዝር ሊንኮችን ከታች አስቀምጫለሁ * ) ዛሬም ይህ አሳሳቢ ሽባ እየሆነ ስላለ ተቋም እንጩኽ ! የሃገር ሰላምና የዜጎች ደሕንነት በእጁ ያለ ተቋም ነው ። በተመስገን ጥሩነህ የሚመራው የደሕንነት ተቋም ለሃገርም ለሕዝብም የማይጠቅም ነው። ተቋሙን ማን እየገደለው ነው ? የተመስገን ስራ መልቀቂያ ተቀባይነት አግኝቶ በምትኩ አቶ ታዜር ገብረእግዚአብሄር ቢሾምስ ? መንግስት የደሕንነት ተቋሙን ጉዳይ በቸልታ መመልከት የለበትም ፤ የሃገሪቱ ሰላም ማጣትና ሌብነት እንዲሁም የዜጎች ደህንነት ጉዳይ በዋናነት ያለው በደሕንነት ተቋሙ እጅ ላይ ነው ። መንግስት የደሕንነት ተቋሙን እየገደለው ነው፤ መንግስት በባለስልጣናት የጋንጊስተሮች ቡድን እየተለፈ እየጣለው ነው ብለን ጮኸናል። ሰሚ ያልተገኘለት የደሕንነት ተቋሙ ወደ ሞት መፍጠን ይብስኑ በገዛ ተቋሙ ባለስልጣናት መሪነት የሚፈጸሙ ወንጀሎች እየበረከቱ መሄድ መንግስትን ያሳሰበው አይመስልም። የአብይ አስተዳደር ወደ ስልታን ከመጣ ጀምሮ የደሕንነት ተቋሙ እንዲጠናከር ብንወተውትም በዘር የተቧደኑ ተረኛ ባለስልጣናት የራሳቸውን ኔትወርክ በመዘርጋት እና ደሕንነት ተቋሙ ውስጥ ካሉ ተሿሚዎች ጋር በመተባበር ከፍተኛ ሃገርን አደጋ ላይ የሚጥል ወንጀል እየሰሩ መሆኑን እያየን እየታዘን ነው። የደህንነት ተቋም ኝባር ቀደም የሃገርን ደሕንነት እና ሰላም ማረጋገጥ የሚገባው ትልቅ ተቋም መሆኑ እየታወቀ በግጭት ጠማቂነትና በዘረፋ ላይ ባለስልታናቱ መሳተፋቸው ለሃገር ሕልውና ትልቅ ጋሬጣ ሆኗል። ከለውጡ በኃላ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የስብሃት ነጋ ለሕክምና ወደ አሜሪካ እንዲበሩ መፈቀዱና የጄኔራል ተፈራ ማሞ ለሕክምና እንዳይሄዱ መከልከሉ እያነጋገረ ነው

የጦር ወንጀለኞችን አስቀምጦና ታቅፎ ሃገራቸውን ከወራሪ የታደጉትን መግፋት የመንግስት ወንጀል መሆኑ ቀጥሏል። ጄኔራል ተፈራን  እና አማራ የሆኑ የጦር መኮንኖችን የጦር ወንጀለኛ ብሎ ለመፈረጅ መታሰቡን አመላካች ነው። የጦር ወንጀለኛው ማነው ? የህዝብን ሰራዊት የካደ ወይንስ ከሕዝብ ሰራዊት የወገነ ? የአብይ አገዛዝ በየዘርፉ የሚሄድበት መንገድ ነገ ዋጋ ያስከፍለዋል። መንግስት የግዴታ የአሜሪካንን ጫና የሚፈልግ መሆኑን እያሳየን ነው። ለነፃነት ዋጋ የከፈሉትን ስለኢትዮጵያ የሞቱትን የተጎዱትን (በተለይ አማራውን)የጦር ወንጀለኛ አድርጋችሁ ፍርድ ቤት ልታቆሙ ? …….. ወንጀለኞችን ሕዝብን የጨፈጨፉትን የሕወሓት አመራሮችን ደግሞ በነፃነት እንዲኖሩ ማድረግ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው። ሃገርን ለማፍረስ የተነሳን ቡድን ቁንጮ መሪ ነፃነት ሰጥቶ ፤ ሃገሬ አትፈርስም ብሎ ፤ ህይወቱን ለመገበር የወጣን ጀግና ነፃነት ቀምቶ መበደል ልብን የሚያደማ ፀያፍ ተግባር ነው። የሽብርተኛው ወያነ መስራች አቦይ ስብሀት ነጋ ለህክምና አሜሪካ ሲገቡ፣ ለሃገር በጀግንነት የተዋጉት ጄ/ል ተፈራ ማሞ ለህክምና ከሃገር አትወጡም ተብለው ሲሰቃዩ ማየት ብልጽግና ፓርቲ ከማን ጋር እንደቆመና የኢትዮጵያ ሰቆቃ የት እንደደረሰ ማሳያ ነው ። ለሃገር በጀግንነት የተዋጉት ጄ/ል ተፈራ ማሞ ለህክምና ከሃገር አትወጡም ተብለው ሲሰቃዩ ማየት በጣም ያሳዝናል:: የሚመለከተው አካል ያለምንም ቅድመ ሁኔት ከሃገር ወጥተው የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ ጥሪያችንን እናቀርባለን:: ፟ ብ/ር ጀኔራል ተፈራ ማሞ የአማራን ህዝብ ብሎም የኢትዮጵያን የወደፊት ሁኔታ በተለያዩ ሚዲያወች የመናገር መብታቸውን ተጠቅመው አሁን ላይ ያለውን የሃገሪቱን ነባራዊ እይታቸውን ቀድመውና ነቅቶው ለህዝቡ በማስረዳታችው የአገዛዙ መንግስት በተደጋጋሚ ሲያስራቸው እንደነበር የሚታወቅ ሃቅነው ።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከንቲባ አዳነች አማራውም ምርቱም እንዳይገባ ያደረጉበትን ምስጢር በአደባባይ ዘርግፈውታል።

አማራ አዲስ አበባ ከገባ ስልጣናችንን ይነጥቀናል የሚል ፍራቻ ላይ ነን ብለዋል ከንቲባዋ። አዳነች አቤቤ ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ዜጎች ለስልጣናችን አደጋና ስጋት ናቸው ማለቷ አግራሞትን እየፈጠረ ነው። አማራውን ምርቱም እንዳይገባ ያደረጉበትን ምስጢር በአደባባይ አዳነች ዘርግፋዋለች ። ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም ክልል ተዘዋውሮ የመስራት መብት እንዳለው እየታወቀ የአዲስ አበባ ከንቲባ ብሎ ብልጽግና የሾማት ሴት ከወገቤ በታች ካሜራማኖች እንዳያነሱኝ ማስጠንቀቂያ ስጧቸው ያለችው ሴትዮ ሰሞኑን አዲስ አበባ ላይ በአማራ ወጣቶች ላይ የጀመረችውና ያስጀመረችው አፈሳና እስር ስልጣንን ላለማታት የሚደረገው የትግል አካል መሆኑን ነግራናለች ። ይህ አደገኛው አካሄድ መንግስታዊ ሽብር ሲሆን የአማራ ክልል ተወላጆችን አዲስ አበባ አትግቡ የገቡትንም በማሰር፣ በማዋከብ፣ ቤታቸውን በማፍረስ፣ ባጃጆቻቸውን በመንጠቅ እንዳይሰሩ በጽጥታ ሓይሎች በማሳደድ ስራ ላይ ተሰማርታ እና አሰማርታ የዘጎችን ሕጋዊ መብት እየገፈፈች ያለችው ስልጣን ላለማታት መሆኑን አሳውቃለች በዛሬው ንግግሯ። አዳነች የተናገረችው ቀድማ በኦ ኤም ኤን በሀሰት ዜና ያሰራችውን ነው። የተቀናጀ የዘር ማፅዳት ዘመቻ ላይ ናቸው። የባጃጅ ሾፌሮችን አስወጥተዋል። በሚቀጥለው ደግሞ ጉሊት ነጋዴዎች፣ ሊስትሮና ሎተሪ የሚሰሩትን ሳይቀር ለማስወጣት መታቀዱ ታውቋል። ይህን የዘር ማፅዳት ወንጀል ሰበብ ሰጥተውታል። ኦነግም ስልጣን ላይ ያሉትም እኩል እየተናገሩ ነው። ለህክምና፣ ለገበያም፣ ቤተሰቦቹን ጠይቆ ወደ ስራ ገበታው የሚመለሰውም አማራ መፈንቅለ መንግስት ሊያደርግ ነው ተብሎ ሰበብ ተሰጥቶት በማንነቱ እየተጠቃ ነው። ይህ የሚሆነው በኢትዮጵያ ዋና ከተማ፣ በአፍሪካ መዲና፣ አዲስ አበባ ላይ ነው። ይህን የዘር ማፅዳት፣ ለቀጣይ የታሰበውን የዘር ፍጅት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የማኅበራዊ ሚድያ መዘጋት በመገናኛ ብዙኃን ሥራ ላይ ችግር ፈጥሯል – ባለሞያዎች

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለው ገደብ በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጠውን መረጃ የማሰባሰብ፤ የማደራጀትና ለሕዝብ ተደራሽ የማድረግ መብት ላይ ችግር መፍጠሩን ገለፀ፡፡ የምክር ቤቱ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ አቶ ታምራት ኃይሉ፣ እርምጃው በተለይም በበይነ መረብ ለሚሰራጩት ሚዲያዎች እንቅፋት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ማኅበራዊ ሚድያውን ተጠቅመው የተለያዩ ዝግጅቶችን የሚያቀርቡት አዘጋጆች በበኩላቸው የተጣለው ገደብ ሥራቸው ላይ ጫና መፍጠሩን ይናገራሉ፡፡ በጉዳዩ ዙርያ አስተያየት የተጠየቁ አንድ ባለሞያም በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ ሲሉ ጥሪ ቀርቧል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ለመቄዶንያ የአረጋውያን ማዕከል በማኅበራዊ ሚዲያ አንድ ሚሊዮን ዶላር እየተሰበሰበ ነው

ለመቄዶንያ የአረጋዊያን እና የአዕምሮ ህሙማን ማዕከል ማኅበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ከአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ ከፍተኛ ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው። በኮሜዲያን እሸቱ መለስ መሪነት የሚደረገው የገንዘብ ማሰባሰብ ጥረት ማዕከሉ ላስገነባው ሕንጻ ማጠናቀቂያ በር እና መስኮት ለመግጠም ያለመ ነው። የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራው በአገር ውስጥ ባንኮች በኩል፣ በጎ ፈንድ ሚ፣ በካሽ አፕ እና ዜሌ በኩል እየተከናወነ ሲሆን፣ እስከ ሰኞ ረፋድ ድረስ ገንዘብ አሰባሳቢዎቹ ከ54 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር በላይ በሰዓታት ውስጥ መሰብሰባቸውን አስታውቀዋል። እስከ ሰኞ የካቲት 27/2015 ዓ.ም. ረፋድ አምስት ሰዓት ድረስ በጎ ፈንድ ሚ በኩል ብቻ የተሰበሰበው ገንዘብ ከ700ሺህ የአሜሪካ ዶላር በላይ ሆኗል። ለሜቅዶንያ ለሚሰራዉ አዲሱን ህንፃ በር እና መስኮት ካልገጠምን ከ ላይቭ አንወጣም  https://gofund.me/216b39ce የበጎ አድራጎት ድርጅቱ እያስገነባው ለሚገኘው ሕንጻ ከ1ሺህ 600 በላይ በር እና መስኮቶች ለመግጠም በጎ ፈንድ ሚ አማካይነት እስከ 5 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የለገሱ ሰዎች አሉ። ገንዘብ የማሰባሰቡን ሥራ እየመራ ያለው ኮሜዲያን እሸቱ ለማኅበራዊ ጥሪ ምላሽ ይሆን ዘንድ የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራ ሲሰራ ይህ የመጀመሪያው አይደለም። በቅርብ ጊዜም ለክርስትና እና እስልምና ቤተ እምነት ቦታዎች ግንባታ ከፍተኛ የሚባል ገንዘብ አሰባስቧል። በቅርቡም በድርቅ ለተጎዳው የቦረና አርብቶ አድር 10 ሚሊዮን ብር እርዳታ ማሰባሰቡ ይታወሳል። መቄዶኒያ ማን ነው? መቄዶኒያ የአረጋዊያን እና የአዕምሮ ህሙማን ማዕከል ጧሪ እና ደጋፊ የሌላቸውን አረጋዊያን እና የአእምሮ ሕሙማን መጠለያ፣ ምግብ እና ሕክምና በመስጠት ይታወቃል። የመቄዶኒያ መሥራች የሆነው ቢኒያም በለጠ ትናንት እሁድ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ብልጽግና ቀውስ ጠማቂ፣ አወዛጋቢና ለሕዝብ ራስ ምታት ነው !

ብልጽግና ቀውስ ጠማቂ፣ አወዛጋቢና ለሕዝብ ራስ ምታት ነው ! (ምንሊክ ሳልሳዊ ) ኢትዮጵያ ከገባችበት ቀውስ ከማውጣት ይልቅ በቀውስ ላይ ቀውስ መፍጠር ምን የሚሉት መንግስታዊ አስተዳደር ነው ? የማሕበራዊ ድረገፆች መዘጋት፣ የኢንተርኔት መቆራረጥ፣ ወታደራዊ ጡንቻን ማሳየት እና የመሳሰሉት ሌላ ቀውስ እንደተዘጋጀ ጠቋሚ ናቸው። ለሁሉም ተጠያቂነቱና ኃላፊነቱን የሚወስደው ብልጽግና ፓርቲ ነው፤ ወደ ሌሎች እጁን ከሚጠቁም መንግስታዊ ግዴታውን ሊወጣ በተገባ ነበር። መንግስታዊ ግዴታውን ካልተወጣ ስልጣን መልቀቅ እንጂ ቀውስ መፍጠር ተቀባይነት የለውም። ይህ በርካቶች የሚጠይቁት ጥያቄ ነው። ችግሮችን፣ አለመግባባቶችን፣ ቅራኔዎችን መለጠጥ የመንግስት በተለይ የብልጽግና ሰዎች የቀንተቀን ስራ ሆኗል ። የፖለቲካ ልሂቃንም ሆኑ ምሁራን በአገራዊ ምክክር መድረኩም ሆነ በሌሎች በሚገናኙባቸው መድረኮች፣ ቅራኔ ከመፈልፈል ውጪ ፋይዳ እያጣ ያለውን የፖለቲካ አካሄድ በትኩረት መርምረው መላ ካልፈለጉ የአገሪቱ ሁኔታ አስፈሪ እየሆነ ነው፡፡ ለችግሮች መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ በችግሮች ዙሪያ ሌሎች ችግሮች እንዲወለዱ የፖለቲካ ማዕበል በመፍጠር ቀውስን ማስፋፋት ስራዬ ያለው ብልጽኛ አገሪቱ ለምትሄድበት አስፈሪ አቅጣጫ ሁሉ ተጠያቂ ነው። ማንም የሚተየቅ አካል የለም። ከመቀሌ እስከ ሞያሌ ከጋምቤላ እስከ ኦጋዴን ቀውሶችን እንደ መንግስት ከማስቆም ይልቅ እያቀጣጠለ ያለው ብልጽግና ነው። ነውረኝነት ሰፍኗል። በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ፣ በዘርፈ ብዙ ማኅበራዊ ጉዳዮችና በሌሎችም ላይ የጋራ ራዕይ በሌለበት አገር ውስጥ ስለልማትና ዕድገት ማሰብም ሆነ ማቀድ አዳጋች ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ ቅኝ ባለመገዛትና በታላቁ የዓድዋ ጦርነት ድል ምክንያት በዓለም አቀፍ መድረክ የተከበረ ስም ያላት ኢትዮጵያ፣ የተማሩ ልጆቿ በእነዚህ ሁለት ድንቅ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የተመድ ዋና ጸሃፊ ትግራይን ሊጎበኙ ነው !

UNSG Antonio Guterres is slated to visit the war-torn region of Tigray የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በቀጣዩ ሳምንት ትግራይን እንደሚጎበኙ ሪፖርተር ከዲፕሎማቲክ ምንጮች መስማቱን ጠቅሶ ዘግቧል። ዋና ጸሃፊ ጉተሬዝ፣ በትግራይ ጉብኝታቸው በክልሉ በሰሜኑ ጦርነት የደረሰውን ጉዳት ተዘዋውረው የመመልከት ዕቅድ እንዳላቸው መረዳቱን ዜና ምንጩ ጠቅሷል። ጉተሬዝ በቀጣዩ ሳምንት መጨረሻ በአዲስ አበባ በሚካሄደው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ጭምር እንደሚሳተፉ ዘገባው አመልክቷል። Read More :  https://minilik-salsawi.blogspot.com/2023/02/unsg-antonio-guterres-is-slated-to.html  
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የካቲት 5 ቀን ዓለም አቀፍ ሰልፍ እንዲካሔድ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል!!

በየካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት እና ምእመናን ከጠዋቱ 11፡00 ጀምሮ በየአጥብያቸው በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት እስከ ጠዋቱ 1፡30 ድረስ ሥርዓተ ቅዳሴው ከተፈጸመ በኃላ ከጠዋቱ 2፡00 ላይ ሁሉም ገዳማት፣ አድባራት እና አብያተ ክርስቲያናት በተመሳሳይ ሰዓት ደወል በመደወል ምእመናን በሙሉ እስከ ጠዋቱ 2፡30 ድረስ እንዲሰባሰቡ በማድረግ ከየአጥቢያው በመነሳት የጥምቀተ ባህር ወይም የመስቀል አደባባይ ላይ ታቦተ ሕጉን በማክበር፤ በማጀብ በዝማሬ እና በምህላ በአንድ ቦታ በመሰባሰብ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡የዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ዝርዝር አፈጻጸም መመሪያን በተመለከተ በአጭር ጊዜ ውስጥ የምናሳውቃችሁ መሆኑን አውቃችሁ ዝግጅት እንድታደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡ማንኛውም የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ቤተ ክርስቲያን ያዘዘችውን ሰላማዊ ጥያቄ በሚከወንበት ማንኛውም የአገልግሎት ጊዜ ተግባራቱ ሰላማዊ መሆናቸውን በመገንዘብ ተገቢውን ጥበቃ የማድረግ ግዴታ እንዳለበት አውቆ እንዲያስፈጽም ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፤
Posted in Amharic News, Ethiopian News, Video

ችግር ለመፍጠር ካልሆነ በቀር የወልቃይት ጉዳይ ግልጽ ነው፤ የወልቃት ሕዝብ ፍትሕ እንጂ ሪፍረንደም አያስፈልገውም።

(ምንሊክ ሳልሳዊ ) የጠላነው የሰላም ስምምነቱን ሳይሆን አቋም የለሾችን ነው። አቋም ያሌላቸው ሰዎች የሕዝብ ጠላቶች ናቸው። የብልጽግና ገደል ማሚቱዎች ወልቃይትን ለወልቃይቶች ተዉላቸው። ወልቃይቴዎች ላይ ሊጀመር የታሰበው ዘመቻ መንግስትን አያዋጣውም። ችግር ለመፍጠር ካልሆነ በቀር የወልቃይት ጉዳይ ግልጽ ነው። የወልቃይት ሕዝብ ፍትሕ እንጂ ሪፍረንደም አያስፈልገውም። ባለስልጣኑም ካድሬዉም ወዶ ገቡም ትላንት የተናገረውን ዛሬ አይደግመውም። እያንዳንዱ እንቅስቃሴያቸው በሌብነት እና በዉሸት የተሞላ ነው። የምናውቃቸውም የማናውቃቸውም ውሸትና የፖለቲከ ማጭበርበርን እንደ ምቾት አይተውታል። የብልጽግና ካድሬዎች እና ወዶ ገቦች ወልቃይት ወደ ትግራይ ይመለስ ማለት ጀምረዋል። የወልቃይት ጉዳይ በሕገ መንግስቱ መሰረት ይታይ ብለው የሚያጮኹት ካድሬዎቹ ሳይሆኑ ወዶ ገቦቹ ናቸው ። ወደ ገቦቹ ትላንትና ሕገመንግስቱ አይሰራም፣ አያስፈልግም፣ ይሰረዝ ይቀየር ሲሉ የነበሩ አቋም ያሌላቸው በብልጽግና ዳረጎት እና ጉርሻ የሚኖሩ የመብትን እና የነጻነትን ትርጉም የማያውቁ ድኩማን ናቸው። ትላንት ሕወሓት ካልጠፋ ስሙም ሊኖር አይገባም ሲሉ የነበሩ ዛሬ ላይ የተዋጋነው ሕወሓትን ለማጥፋት ሳይሆን ሕግ ለማስከበር ነው የሚሉትን አጅበው ያጨበጭባሉ። ትላንት ሰላም እንዲሆን እንጩኽ ሲባሉ የወያኔ ቅጥረኛ ሲሉ የነበሩ ያሁሉ ሞትና ውድመት ከተከሰተ በኋላ ዋነኛ የሰላም አቀንቃኝ ሆነው መምጣታቸው እፍረተቢስነታቸውን ያሳያል። ብልጽግና በነፈሰበት አብረው ነፍሰው ለሕዝብ ሰቆቃ ያተርፋሉ፤ አቋም የለሾቹ ። የብልጽግና ገደል ማሚቱዎች ! ወልቃይትን በተመለከተ መንግስት የሚሄድበት መንገድ እጅግ አደገኛ ከመሆኑም በላይ ለማንም ወገን አይበጅም። መንግስት በሕገመንግስት ስም ጉልበትም ለመጠቀም እንዳሰበ ተሰምቷል። ይህ ብቻ ሳይሆን ነጮቹ የአማራ ልዩ ኃይል ከትግራይ ይውጣ ሲሉ ከወልቃይት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አገርን መጥላትና ማስጠላት የራስ ወዳድ ፖለቲከኞች የዘወትር ሥራ በሆነባት ኢትዮጵያ በፖለቲከኞች የጠበበ ዕይታ ምክንያት አዲስ አበባ እየጠበበች ነው፡፡

በራስህን ስህተት እና የሕግ ጥሰት በሌላው ላይ ማሳበብ ወንጀል ነው። የመንግስት ባለስልጣናት ራሳቸው የፖለቲከ ወንጀሎችን እየሰሩ፣ ራሳቸውን እና ፓርቲያቸውን ከሃገር በላይ እያደረጉ፣ የጎሳ ፖለቲካቸውን ከሌላው ሕዝብ ላይ ለመስቀል እየሞከሩ፣ በሰፊ ስልጣን ላይ ተቀምጠው ጠበው በመገኘት በበታችነት እየተሰቃዩ ነው። ባለስልጣናቱ የፖለቲካ ዓላማን ለማስፈጸም በሚደረስባቸው ውሳኔዎች ተመርኩዘው ሕዝብን እየበጠበጡ ግጭት እየቀሰቀሱ ምንም የማያውቁ ሰዎችን ሕግ ይከበር ያሉ ዜጎችን እየሰበሰቡ በማሰር ላይ ናቸው።   ሪፖርተር በርዕስ አንቀጹ እንዳሰፈረው በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከኦሮሚያ ክልል ሰንደቅ ዓላማና መዝሙር ጋር የተያያዘው ውዝግብ፣ በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ ፈር መያዝ ሲገባው ወደ አላስፈላጊ ግጭት እያመራ ያለው አያያዙን ካለማወቅ የመነጨ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መንግሥትም ሆነ ሌላው አካል የመጀመሪያ ግዴታው ሕግ ማክበር ነው፡፡ ሕግ የሚከበረውም በጉልበት ሳይሆን ሕጉ በሚጠይቃቸው መሥፈርቶች መሆን አለበት፡፡ ይህንን ማድረግ ካልተቻለ ግን የፖለቲካ ቀውስ በመፍጠር አገሪቱን ወደ እርስ በርስ ጦርነት/ግጭት ውስጥ መክተት ይከተላል፡፡ ኢትዮጵያውያንን በብሔር በመከፋፈል ሌላ ዙር ፍጅት የሚቀሰቅስ ንትርክ ከመፍጠር ይልቅ፣ ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን የሚያጠናክሩ በርካታ ተግባራት ላይ ቢተኮር ተመራጭ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን አፋቸውን ከፈቱባቸው ቋንቋዎች በተጨማሪ ሌሎችንም ቢማሩ የሚጠቅመው ራሳቸውን መሆኑ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ ቋንቋ ከመግባቢያነት አልፎ ጥቅምና ዝምድና መፍጠሩ መልካም ሆኖ ሳለ፣ በግድ ለመጫን የሚደረግ ሙከራ ቅራኔ ከመፍጠር ውጪ ሌላ ፋይዳ የለውም፡፡ አሁንም በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ መከናወን የሚችል ተግባር በመተው፣ ኢትዮጵያውያንን እርስ በርስ የሚያጋጭ ድርጊት መቆም አለበት፡፡   አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል መንግሥት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኦሮሚያ ባለስልጣናት አማራውን ስብሰባ ጠርተው አደራሽ ውስጥ ከዘጉ በኃላ ለኦነግ ሸኔ ተሰብሳቢውን አስረክበው ያስገድላሉ ።

የኦሮሚያ ባለስልጣናት አማራውን ስብሰባ ጠርተው አደራሽ ውስጥ ከዘጉ በኃላ ለኦነግ ሸኔ ተሰብሳቢውን አስረክበው ያስገድላሉ ። የመንግስት አካላት ሸኔ ይገድላችኋል ኑ ወደ ካምፕ ግቡ በማለት የአማራ ገበሬዎችን ስብስበው ኪረሞ ማዘጋጃ ቤት ውስጥ አስረዋቸው ነበር፤ ሽማግሌዎች የታሰሩት እንዲፈቱ ጥረት ቢያደርጉም ኦሮሞዎች እየተለቀቁ አማራዎች ግን እንዳይወጡ ተደርጓል በምስራቅ ወለጋ ዞን በተፈጸም ጥቃት በርካቶች በአስቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገግረዋል።በኪረሙ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች ብሄራቸው እየተለየ ተገድለዋል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችም ተጨማሪ እልቂትን ሽሽት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል፡፡ ዛሬ ግድያና ዘረፋው በመንግስት ባለስልጣናት እየተመራ ከወለጋ እስከ ሸዋ፣ ከጉጂ እስከ አርሲ ሲፈጸም ውሏል። የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ዋና አስተባባሪ በመሆን የመንግስትና የግል ባንኮችን አዘርፏል። የአማራ ህዝብ የዘር ጭፍጨፋ ክስተታዊ ሳይሆን መዋቅራዊና ስርዓታዊ ስለሆነ የሚቆመውም በመዋቅራዊና ስርዓታዊ ለውጥ ነው ። ዝርዝሩን ከዚህ ያገኙታል https://minilik-salsawi.blogspot.com/2022/12/oromia-special-forces-and-ola-rebels.html  
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ስምምነቱን በጣሰ አካል ላይ ማዕቀብ እንደምትጥል አሜሪካ አስጠነቀቀች

የኢትዮጵያ ፈደራዊ መንግስትና ህወሓት በቅርቡ የተፈራረሙትን ስምምነትን የሚያዉኩ ወገኖችን በማዕቀብ እንደምትቀጣ አንድ የአሜሪካ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ከፍተኛ ባለስልጣን አስጠነቀቁ።”የአሜሪካ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ከፍተኛ ባለስልጣን” ከሚለዉ ማዕረግ ሌላ መደበኛ ሥምና ማዕረጋቸዉ በሚስጥር የተያዘዉ ባለስልጣን  «የኤርትራ ጦር ወይም የአማራ ተዋጊዎች ከትግራይ ግዛት ካልወጡ ምን ሊሆን ይችላል» የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸዉ ባለስልጣኑ በሰጡት መልስ፣ …… የአሜሪካንን ማስጠንቀቂያ እና ማስፈራሪያ ሙሉውን ይህንን ተጭነው ይመልከቱት     https://minilik-salsawi.blogspot.com/2022/11/us-says-withdrawal-of-eritrean-forces.html
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኤርትራ ጦር እና የአማራ ልዩ ሃይል ከትግራይ ሲወጣ የከባድ መሳሪያ ትጥቅ የማስፈታት ስራ ይከናወናል። የማይወጡ ከሆነ …..

የኤርትራ ጦር እና የአማራ ልዩ ሃይል ከትግራይ ሲወጣ የከባድ መሳሪያ ትጥቅ የማስፈታት ስራ ይከናወናል። የማይወጡ ከሆነ ……. ዝርዝሩን ይመልከቱት https://minilik-salsawi.blogspot.com/2022/11/disarmament-of-heavy-weapons-will-be.html ==== የኤርትራ ጦር እና የአማራ ልዩ ሃይል ከትግራይ ሲወጣ የከባድ መሳሪያ ትጥቅ የማስፈታት ስራ ይከናወናል። የማይወጡ ከሆነ ……. ዝርዝሩን ይመልከቱት https://minilik-salsawi.blogspot.com/2022/11/disarmament-of-heavy-weapons-will-be.html ====
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ተጠያቂነት፤ ኃላፊነት፣ እምነት፣ ለዜጎች ዋስትና መስጠት እና ኤርትራ ….. ስምምነቱ ብቻውን ሰላምን አያሰፍንም።

ተጠያቂነት፤ ኃላፊነት፣ እምነት፣ ለዜጎች ዋስትና መስጠት እና ኤርትራ ….. መፈረሙ ደግ ነው። ተፈረመ ብቻ ብሎ ማጨብጫብ ብቻ ሳይሆን ቀጣይ ስጋቶችና ጋሬጣዎችንም ማሰብ ያስፈልጋል። ተፈራራሚ ወገኖች ካላቸው የመታመን ታሪክ አንፃርም መገምገም ያስፈልጋል። የኤርትራ ወታደሮች ጉዳይ በስምምነቱ ውስጥ አለመጠቀሱ እንዲሁም የሰብዐዊ መብት ጥሰቶች ከሕግ አግባብ አንፃር በስምምነቱ አለመካተቱ እያነጋገረም እያከራከረም ነው ። ሁለቱ ጉዳዮች አትኩሮት ካልተሰጣቸው የግጭት ማቆም ስምምነቱት ጎዶሎ ከማድረጋቸውም በላይ ተፈጻሚነቱ ላይ ከባድ አደጋ ያስከትላሉ ። ትልቁ ፈተና የሚመጣው ይሄ ስምምነት ፈተና የሚገጥመው ወደ ተግባር በሚገባበት ጊዜ ነው። ሁለቱም ተፋላሚ ወገኖች እስካሁን ድረስ ያሳይዋቸው የተዓማኒነትን ሪከርድ ስናይ የሽግግር ጊዜ ፍትሕ ሙሉ በሙሉ ያሳካሉ የሚል እምነት የለም። ጥርጣሬ እለ። መሰል የመብት ጥሰቶች እንዳይከሰቱ ስምምነቱ ላይ የደረሱት አካላት ዋስትና ሊሰጡ የግድ ነው። ስምምነቱ ያልመለሳቸው በርካታ ጉዳዮች ሲኖሩ በቀጣይነት ጋሬታዎች እንዳይፈጠሩ ስጋቶችን ሁላችንም እንጋራለን። የኤርትራ ጉዳይ እና የተጠያቂነት ፍትሕን የማስፈን ጉዳዮች ሊታለፉ የማይገባቸው ናቸው። ስምምነቱን ወደ ተግባር ለመተርጎም ብርቱ ስራ ይጠይቃል። ስምምነቱ የጦር ወንጀል እና ሰብዓዊነት ላይ ያነጣጠረ ወንጀል የፈጸሙ አካላትን ተጠያቂ ስለሚሆኑበት ሁኔታ ግልጽ ዕቅድ የለውም ከምዕራባውያን ዲፕሎማቶች የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው ከሆነ የትግራይ ተዋጊዎችን መስመር የበታተነው ከአሥመራ ትዕዛዝ የሚቀበል የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ጥምር ጦር የማጥቃት እርምጃ ነው። በዚህ የሰላም ስምምነት ላይ ኤርትራ በስም አልተጠቀሰችም። ይሁን እንጂ በስምምነቱ ላይ “ከውጪ ኃይል” ጋር መተባበር የሚል ሃርግ በአንድ አንቀጽ ሰፍሯል። ይህም ኤርትራን የሚያመላክት ሊሆን ይችላል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጫፍ እየደረሰ ተጋጭቶ የሚመለሰው ድርድር ……. የደረሰበት እውነታ

ጫፍ እየደረሰ ተጋጭቶ የሚመለሰው ድርድር …….ምንሊክ ሳልሳዊ   በመንግስትና በህወሓት መካከል እየተካሄደ ያለው ውይይት አሁንም ከመግባባት ሊደረስበት አልቻለም። የሕወሓት ደጋፊዎች ከተለያዩ የአለም ማዕዘናት የኤርትራ ጦር ትግራይን ለቆ እንዲወጣ ኤርትራውያን በትግራይ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ በጣፈጠ አንደበት ኤርትራውያን ወንድሞቻችን እያሉ በመማፀን ላይ ናቸው።   ጫፍ እየደረሰ ተጋጭቶ የሚመለሰው ድርድር የሆነ መቋጠሪያ አገኘ ሲባል እየተጥመለመለ ይወድቃል። ከፕሪቶሪያ የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ውሃቅዳ ውሃመልስ የሆነባት አሜሪካ ከታዛቢነት ወደ ጫና ፈጣሪነት ተሸጋግራለች ። ለሕዝብ እና ለራሳችሁ ፖለቲከኞች የተለያየ መግለጫ ይሰጣል የምትለው አሜሪካ በቀጠናው ያላትን ናሽናል ኢንተረስት በሚጠብቅ መልኩ ቅርፅ ለማስያዝ ቁፋሮውን ተያይዛዋለች ። ጫናውን ጠቅላይ ሚኒስትሩም አረጋግጠውታል። ሕወሓት በጻፈው ሕገመንግስት የሚምለው ብልጽግና አሁንም ስለ ሕገመንግስቱ ቢያወራም ሕወሓት ግን ዙሪያ ጥምጥም እየተሽከረከረ ድርድሩን እያሸው እየፈተለው ከአሜሪካ ጋር እየተናበበ በማሽከርከር ላይ ነው።   በውይይቱ በተለይ የኤርትራ፣ የባድመ፣ የወልቃይት እና ራያ ጉዳይ በፍጹም ከመግባባት ሊደረስባቸው ባይችልም የወልቃይት እና የራያ ጉዳይ መንግስት በሕገመንግስቱ መሰረት እንዲፈታ እንደሚፈልግ ተናግሯል። የኤርትራ ጦር ከትግራይ ይውጣ የሚለው ሲነሳ መንግስት በበኩሉ ሕወሓት ኤርትራን መልሶ ላለመውረሩ ዋስትና ይስጥ ባድመም የኤርትራ መሆኑን ይቀበል ብሏል። ሕወሓት ደሞ ፍንክች የአባ ቢላዋ ልጅ ብሏል። እንዴት ይግባቡ ታዲያ / ሕወሓት እኮ ደረቅ ነው።   በደቡብ አፍሪካ ዋና ከተማ በሰሜን ኢትዮጵያ በሚፋለሙት ሁለቱ ወገኖች መካከል ከአንድ ሳምንት በላይ ሲካሄድ የቆየው ድርድር ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ትጥቅ እንድፈታ ዋስትና ይሰጠኝ የውጪ ኃይሎች በበላይነት ኃላፊነቱን ይውሰዱ፣ መንግስት አስፈላጊውን ጥበቃ ያድርግልን
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በድርድር መሞዳሞድ እና ሕወሓት ውድመት እስኪፈጽም እየጠበቁ ፕሮፓጋንዳ ከመስራት ቅድሚያ መከላከል የመንግስት ኃላፊነት ነው።

የሕወሓት አሳፋሪ ድርጊት እና የመንግስት መሞዳሞድ ደቡብ አፍሪካ ላይ ተኩስ አቁሙልኝ ብሎ ይለምናል። የኤርትራን ወታደሮች አስወጡልኝ ለደህንነቴ እሰጋለሁ ይላል በተመሳሳይ ሰዐት ገዳማትን ያወድማል። በከባድ መሳሪያ ይደበድባል። የሕወሓት የኖረበት የጦር ታክቲክ …… 📌የእምነት ተቋማትን ማውደም 📌የእምነት ተቋማትን ምሽግ መጠቀም 📌የእምነት ተቋማትን ማቃጠል 📌የእምነት ተቋማትን ዘርፎ ጭካኔ የተሞላበት ተግባር መፈጸም ነው። ይህ አደገኛ ወንጀለኛ እና አሸባሪ በፍጥነት ካልተወገደ አፍር ልሶ ድጋሚ ከተነሳ አደጋው የከፋ ስለሆነ ሊታሰብበት ይገባል። የሕወሓት ቫይረስ ስርጭት ገና አልተዳከመም፣ መንግስት ያስብበት ። በድርድር መሞዳሞድ እና ሕወሓት ውድመት እስኪፈጽም እየጠበቁ ፕሮፓጋንዳ ከመስራት ቅድሚያ መከላከል የመንግስት ኃላፊነት ነው። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መቀሌ > አዲስ አበባ ( ናይሮቢ) > ጆሃንስበርግ ….. ሕወሓቶች ወደ ደቡብ አፍሪካ …. ፍርሐት እና ስጋት

ብዙ ብዙ ሰማን ዛሬ በሰንበት ……. May be an image of 3 people and textሕወሓቶች ወደ ደቡብ አፍሪካ አንድ ሰው ይወከል ሁለት ሰው አሊያም ሁላችንም እንሂድ እያሉ በመነታረክ ላይ ናቸው። በውጪ ያለው የሕወሃት ክንፍ ደግሞ ጥምር ጦሩ መቀሌና አዲግራት እንዳይገባ አሜሪካንን መማፀን ማስጨነቅ ይዘዋል። እንደበቅበታለን ያሉት ዋሻ ቀድሞ በጥምር ጦሩ ተይዟል። ሕወሓቶች በሰፈሩት ቁና እየተሰፈሩ ነው። የስራቸውን ሳይመሽ በጊዜ እየተጋቱት ነው ! ሕወሓቶች እዛው ደቡብ አፍሪካ ያስቀሩናል የጦር ጄኔራሎቻቸውንም በቁጥጥር ስር መቀሌ ላይ ይውላሉ የሚል ስጋታቸው ቢያይልም አሜሪካ አይዟቹ ብትልም ጉዞው ግን በፍርሃት የታጀበ ነው። መቀሌ አዲግራት እና ….. የተባሉ ከተማከተሞች ከሕወሃት እጅ አውጥቶ ወደ ሕዝብ ለመመለስ ትግሉ ቀጥሏል። ወደ ደቡብ አፍሪካ እኔ ልሂድ እኔ የሚሉት የሕወሓት አመራሮች ጥምር ጦሩ ሰኞ መቀሌን ሊቆጣጠር ይችላል በሚል ስጋት የቆፈሩት ምሽግ ውስጥ ያስቀመጧቸው ወታደሮቻቸው ላይ እንኳን እምነት አላሳደሩም። በጌታቸው እና ፃድቃን እየተመሩ በአሜሪካ አይሮፕላን ጅቡቲ ደርሰው የተመለሱት አዲስ አበባ ትራንዚት ያደረጉት አመራሮች ደግመው ወደ ደቡብ አፍሪካ እንዳይሄዱም የጦፈ ክርክር ቢያዝም የሚሄዱት ዛሬ ይታወቃሉ ተብሏል። ደብረፂዮን ካሌድኩ እያለ ነው በዛው ሊሸበለል ይችላል በሚል ጉርሙርታ ቢበዛም አሜሪካኖቹ አይሮፕላናቸውን ትላንት ምሽቱን አስገብተውላቸዋል። አዲስ አበባ ያለም አንድ ዲፕሎማት መቀሌ ገብቷል። ትራንዚቱ ናይሮቢ ይሁን ተብሏል። እንዲህ እንዲህ እያለ ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚሄዱ ሕወሓቶችን አሜሪካ ትወስናለችም ሰምተናል። ወጣም ወረደ ሕወሓቶች የድርድር ሻማውን ሲያበሩ ጥምር ጦሩ መቀሌና አዲግራት ሲገባ እኩል እንዳይሆን አስፈርቷል። ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ወይም ናይሮቢ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የተኩስ አቁም ያለህ …….. የተቀናጀው ጩኸት !

ምንሊክ ሳልሳዊ ፡ የተኩስ አቁም ያለህ …….. የተቀናጀው ጩኸት ሕወሓት ደንግጧል፤ አመራሮቹ የሚያድናቸውን ኃይሎች ሁሉ እየተማፀኑ ነው። የተኩስ አቁሙ የሕወሃትን እድሜ ከማራዘም ውጪ ምንም ፋይዳ የለውም ። ሕወሓትን ሲጥ አድርጎ እስትፋሱን ማቆም እንጂ መደራደር የሰላም ዋስትና አይሆንም ። መንግስት በጀመረው መስመር ሊቀጥል ይገባዋል። ሕወሕቶች ጦርነቱን ወደ መሃል ለማምጣት ቢጀምሩትም እዛ በዙሪያቸው በደጃቸው እሳቱ መቀጣጠሉ ሙቀቱ ሲፈጃቸው የተኩስ አቁም ያለህ እያሉ እየጮኹ እያጯጯሁ ነው። ዛሬ ከየአቅጣጫው ነጩም ሕወሓቱን ነጭ ጩኸት ሲጮኹ ነው የዋሉት ። ባለፉት ቀናቶች በተደጋጋሚ አሜሪካ የአፍሪካ ሕብረትና የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ መንግስት እና በሕወሓት መካከል የተኩስ አቁም እንዲደረግ እየወተወቱ ይገኛሉ። ይህ የተኩስ አቁም ጥያቄ የበረታው የኢትዮጵያ ጥምር ጦር ወደ መቀሌ የሚያደርገውን ጉዞ እየገፋ በመምጣቱ መሆኑ ብዙዎቹ ይስማሙበታል። የተኩስ አቁም ያውጃል ተብሎ የሚጠበቀው መንግስት ሕዝቡና የእርዳታ ሠራተኞች ራሳቸውን ከሕወሓት ወታደራዊ ተቋማት እንዲያርቁ መንግሥት ጥሪ አቀረበ፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚካሄደውን የመከላከል ርምጃን በተመለከተ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫውም የእርዳታ ሠራተኞችን ጨምሮ በሲቪሎች ላይ ለሚደርሰው ማንኛውም ጉዳት መንግሥት ሀዘኑን ይገልጣል ብሏል። የኢትዮጵያ ጦር መግፋትን ተከትሎ የአሜሪካ የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀ መንበር ሴናተር ቦብ ሜንዴዝ የተኩስ አቁም በሌለበት ሁኔታ ጦርነቱን ለማስቆም እና ለደረሱ ጥሰቶች ተጠያቂነት እንዲኖር ተጽዕኖ ይፈጥራል የተባለውን ረቂቅ ህግ ሴኔቱ እንዲያሳልፈው እገፋለሁ ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረትም እንዲሁ የተኩስ አቁም ሲጠይቅ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳዮች ሃላፊ ጆሴፕ ቦሬል በበኩላቸው አስቸኳይ የተኩስ አቁም ተደርጎ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መንግስት በሕዝብ ላይ መቀለዱን ተያይዞታል ። — የስንዴው ፖለቲካ !!!

May be an image of 1 person, standing and grassምንሊክ ሳልሳዊ ፡ በሰንበት ምድር የመንግስት የፕሮፓጋንዳ ማሽኖች ወሬያቸው ሁሉ ስንዴ ሆኖ ውሏል። ኢትዮጵያ በዘንድሮ ዓመት የስንዴ ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረብ ትጀምራለች ሲሉ መናገር የማይደክማቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሆነ የስንዴ ማሳ ውስጥ ሆነው ጅቡቲ ላይ የቆመው የእርዳታ ስንዴ መርከብ ተራግፎ ሳይጨርስ ንግግር አደረጉ። ይህ የምስል እና የንግግር ፖለቲከ ከመነገሩ በፊት ቢታሰብበት መልካም ይመስለናል። ከተረጂነት መውጣት የሚቻለው ሃገርንም ማስከበር የሚቻለው የውስጥ ችግርን በሚገባ ፈትቶ ሕዝቡ በምግብ እህል ራሱን እንዲችል አድርጎ ነው እንጂ የውስጥ ሰብዓዊ እና ሌሎች ቀውሶችን ተሸክሞ ሳያራግፉ ስንዴን ወደ ውጪ እንልካለን የሚል የፕሮፓጋንዳ ድርደራ አያዋጣም። ከሁለት ቀን በፊት ዩክሬን ለሶማሊያና ለኢትዮጵያ ዜጎች የረዳችዉን ስንዴ ውጪ የሸፈኑት ጀርመን እና ፈረንሳይ መሆናቸው ታውቋል የሚል ዜና ሰምተናል። ዜናውበሩሲያ ወረራ ክፉኛ የወደመችዉ ዩክሬን ለረሐብ ለተጋለጡት ለሶማሊያና ለኢትዮጵያ ዜጎች 50 ሺሕ ቶን ስንዴ ረድታለች።በአዲስ አበባ የጀርመን ኤምባሲ በፅሁፍ ባሰራጨዉ መግለጫ ስንዴዉን ወደ ሁለቱ የአፍሪቃ ቀንድ ሐገራት ለማጓጓዝና ለማሰራጨት የሚያስፈልገዉን ወጪ ጀርመንና ፈረንሳይ ከፍለዋል። ይላል። በረሃብ ችግር ውስጥ ያለ ሕዝብ ይዘን ወደ ውጪ ስንዴ እንልካለን ማለት በሕዝብ ጉሮሮ ላይ እንደመቀለድ አይቆጠርም ? ወይንስ ፑቲን እንዳሉት ስንዴው በኢትዮጵያ ስም ወጥቶ ወደ አሜሪካ ነው የተሸጋገረው ? የአለም የምግብ ድርጅትስ ለኢትዮጵያ 14 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ስንዴ ረዳሁ ያለውስ እንዴት ነው ነገር ? መንግስት ለሽያጭ ከመሮጡ በፊት ሕዝቡ በምግብ እህል ራሱን ለመቻሉ ማረጋገጫ ሰቷል ? ……………. እነዚህን እና ሌሎች
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የ16 አመት የእንጀራ ልጁን ደፍሮ በጩቤ ወጋግቶ የገደላት ግለሰብ በዋስትና አልወጣም ሲል አቃቢ ሕግ ገለጸ ።

May be a closeup of 1 personአዳናዊት ይሄይስ በምትባለው ግለሰብ ላይ የአስገድዶ መድፈር እና ግድያ ወንጀል ፈጽሟል በሚል በተጠረጠረው ግለሰብ ላይ እየተካሄደ ያለው ምርመራ በጥንቃቄ እየተመራ ይገኛል፤ ግለሰቡ በዋስትና ወጥቶ ነበር ተብሎ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው መረጃም ሀሰተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡ እስካሁን በፖሊስ እና የዐቃቤ ሕግ የምርመራ ቡድን እስካሁን በተሰበሰበው ማስረጃ መሰረት ተጠርጣሪው ሚካዔል ሽመልስ ሟች አዳናዊት ይሄይስ ላይ ከ10 ዓመቷ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈጽምባት እንደቆየ እና ሟች እድሜዋ 17 ዓመት እስኪደርስም ድረስ ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈጽምባት ቆይቶ መስከረም 14 ቀን 2015 ዓ.ም ድርጊቱን ሲፈጽም ያየው ሰው ለእናቷ በተናገረው መሰረት ጥቆማው ለፖሊስ ይደርሳል፡፡ ፖሊስም በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የጠረጠረውን ይህንኑ ግለሰብ ለመያዝ እንዲችል ከፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ በማውጣት ወደ መኖሪያ ቤቱ ይሄዳል፡፡ ይሁንና ተጠርጣሪው የፖሊሶችን መምጣት ያውቅ ነበርና አስቀድሞ ከአካባቢው ይርቃል፤ በዚህም ምክንያት ፖሊስ ወደ መጣበት ተመልሶ በሌላ መንገድ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረት ማድረጉን ይቀጥላል፡፡ ከሰዓታት በኋላ ተጠርጣሪው ከሄደበት ተመልሶ ሟች ከእናቷ ጋር እንዳለች “ለፖሊስ የጠቆምሽው እና ያዋረድሽኝ አንቺ ነሽ” በማለት በስለት ወግቶ እንደገደላት እና ወደ ቤቱ ተመልሶ ልብሱን በመቀየር ሊያመልጥ ሲል በአካባቢው ህብረተሰብ ሊያዝ እንደቻለ ያስረዳል፡፡ ፖሊስ እና በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ በሴቶች እና ህጻናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በአሁኑ ጊዜ ምርመራቸውን በማጠናቀቅ ክስ መስርቶ በህግ ለማስጠየቅ በሚያስችል ሁኔታ በጥንቃቄ እየሰሩ ያለ ሲሆን ግለሰቡ ሟችን የገደላት በዋስትና ከወጣ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር ላይ የጦር ኃይል እና የጦር መሳሪያዎች ሰፍረዋል ተባለ

ኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር ላይ የጦር ኃይል እና የጦር መሳሪያዎች ሰፍረዋል ተባለ ኤርትራና ኢትዮጵያን ከሚያዋስነዉ ድንበር አጠገብ በሚገኙ በሁለቱ ሐገራት ከተሞች ዉስጥ ወታደራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን የሚያመለክቱ የሳተላይት ምስሎች መሰራጨታቸዉ ተነገረ።ሮይተርስ ዜና አገልግሎት በራሱ መንገድ ማረጋገጥ አለመቻሉን ጠቅሶ እንደዘገበዉ ምስሎቹ በሁለቱም ወገን የዉጊያ ዝግጅት መኖሩን ይጠቁማሉ። ማክሳር ቴክኖሎጂ የተሰኘዉ ኩባንያ ባለፈዉ ሰኞ አነሳዉ የተባለዉ ምስል እንደሚያመለክተዉ ሸራሮ-ትግራይ ዉስጥ የጦር ኃይል፣ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችና መድፎች ሠፍረዋል።ከኢትዮጵያ ድንበር በተለይም ከዛላንበሳ ከተማ ማዶ በኤርትራ በኩል ያለዉን ወታደራዊ ክምችትና እንቅስቃሴ ያሳያል የተባለዉ ምስል የተነሳዉ ባለፈዉ መስከረም ዘጠኝ ነዉ። ምስሉ ከኢትዮጵያዉ የዛላአንበሳ ከተማ ማዶ በምትገኘዉ ስርሐ በተባለችዉ የኤርትራ ከተማ ታንኮች፣መድፎችና ሌሎች ከባድ መሳሪያዎች መከማቸታቸዉን ያመለክታል።የሕወሓት ባለስልጣናት ባለፈዉ መስከረም 10 የኤርትራና የኢትዮጵያ ጦር ኃይላት በትግራይ ኃይሎች ላይ በሁሉም ግንባር መጠነ ሰፊ ጥቃት ከፍተዋል ብለዉ ነበር።ሮይተርስ እንደዘገበዉ ስለሳተላይት ምስሎቹ የኢትዮጵያ መንግስት የተለያዩ መስሪያ ቤቶች ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረገዉ ሙከራ አልተሳከለትም። VIDEO – satellite-images-show-army-and-weapons.html
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአዳነች አቤቤ ተጠያቂነት እስከየት ? የተበተነው የታክስ ከፋዩ 10 ሚሊዮን ብር በማን ፈቃድ ?

የአዳነች አቤቤ ተጠያቂነት እስከየት ? 10 ሚሊዮን ብሩ በማን ፈቃድ ? የታክስ ከፋዩ ገንዘብ እንከመቼ ለፖለቲካ ድለላነት ሲባል ይረጫል ? መሰረታዊ ፍላጎጽ ባልተሟላበት ከተማ እንዴት በርካታ ሕዝባዊ ስራዎች የሚሰሩ ሚሊዮን ብሮች ለክለቦች ይበተናሉ ? የሃገር ሃብት እስከመቼ በፖለቲከኞች መጫወቻ ሆኖ ይቀጥላል ?   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቡናና ጊዮርጊስ ስፖርት ክለቦች ለእያንዳንዳቸው 10ሚ ብር ሰጥቷል። አስተዳደሩ የማንን ገንዘብ በማን ፈቃድ ነው ብር እያነሳ የሚሰጠው? ተጠያቂነት የለም እንዴ? ገንዘቡ የሕዝብ ነው ። ክለቦቹ የአትራፊ ድርጅቶች ክለብ ናቸው። ክለቦቹ ሃብታም ከሚባሉና ተጫዋቾችን በውድ ዋጋ ከሚገዙና ከሚከፍሉ ክለቦች ግንባር ቀደም ናቸው።   የአዲስ አበባ ሕዝብ የተለያዩ መሰረታዊ ፍላጎቶች እና መዋቅራዊ ድጋፎች በሚፈልግበት የተለያዩ ተቋማትና ስራ አጥነትን የሚቀርፉ አገልግሎቶች ላይ መዋል የሚገባው ገንዘብ ከነዋሪው የተሰበሰበ ገንዘብ ለአትራፊ ድርጅቶች ክለቦች መስጠት ሕዝብን መናቅ እንዲሁም የሕዝብን ገንዘብ መበተን ነው። ይህ የህዝብን አደራ መብላት፣ ስልጣንን አለአግባብ መጠቀምና ኃላፊነትን መዘንጋት ስለሆነ በጥሞና ሊታይ ይገባዋል። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ህወሓት የተናጠል ተኩስ አቁም ማድረጉን አስታወቀ

ህወሓት የተናጠል ተኩስ አቁም ማድረጉን አስታወቀ ዝርዝሩን ይህን ተጭነው ያገኙታል        
Posted in Amharic News, Ethiopian News, Video

አልሸባብ በዘይት ጄሪካኖች ፎርማት ቦምቦችን ከሶማሊያ ወደ ኢትዮጵያ ለማስገባት እየሞከረ ነው።

አልሸባብ በዘይት ጄሪካኖች ፎርማት ቦምቦችን ከሶማሊያ ወደ ኢትዮጵያ ለማስገባት እየሞከረ ነው። እነዚህ በቀላሉ ሊፈነዱ የሚችሉ ገዳይ መሳሪያዎች ናቸው። Imageታማኝ ምንጮች እንዳስታወቁት አልሸባብ በዘይት ጄሪካኖች ፎርማት ቦምቦችን ከሶማሊያ ወደ ኢትዮጵያ ለማስገባት እየሞከረ ነው። እነዚህ በቀላሉ ሊፈነዱ የሚችሉ ገዳይ መሳሪያዎች ናቸው። በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ አዋሳኝ አካባቢዎች የጸጥታ ሃይሎች በተጠንቀቅ ላይ ናቸው። የውስጥ ድክመታችን ለአልሸባብ በር ከፍቶለታል። ከድንበር ከተማ ወደ መሃል ከተማ ለሽብር እንዳይዘልቅ ያሰጋል። የመንግስት መዋቅር አይታመንም ። የመንግስት የፖለቲካ ፖሊሲ በራሱ በትልቁ ለውጪ ሃይሎች አሳልፎ ሰቶናል። በምስራቅ በኩል ኢትዮጵያውያንን አደራጅቶ አስታጥቆ ያዘመተብን አልሸባብ ለነገና ተነገወዲያ ትልቅ ስጋት ነው። አልሸባብ ለሁለተኛ ጊዜ ዛሬም ጥቃት መክፈቱ ሰምተናል። አልሸባብ ከድንበሩ አራት ኪሎ ሜትር ላይ መኖሩ እየተነገረ መንግስት ዝምታን መርጧል። አልሸባብ ከኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልል ወጣቶችን መልምሎ ሲያሰለጥን መንግስት እየሰማ ዝም ብሏል። ይህ ማለት መንግስት ዜጎቹን ለጥቃት አጋልጣል ማለት ነው። አልሻባብ በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት እንደሚፈጽም በተደጋጋሚ ሲዝት የቆየ ቢሆንም ከሙከራ ያለፈ ጥቃት አድርሶ አያውቅም። አሁን ታጣቂዎቹ እየፈጸሙት ያለው ጥቃት ያልተጠበቀ ነው። የመንግስት ዝምታ ከጥቃት በኃላ ቢሰበር ምንም የሚፈይደው ነገር የለም። ከጥቃት በፊት መንግስት መከላከልን ሊለምድ ይገባል። የመንግስት መዘናጋት በርካቶችን ለሞት ለመፈናቀልና ለቁስለት ለሰቆቃ ዳርጓቸዋል። መንግስት መሳሪያ ያልታጠቁት ላይ ጡንቻውን ለማሳየት እንደሚበረታው ሁሉ በአልሸባብ ላይን ሊፈጥን ይገባል። #MinilikSalsawi Credible sources informed HR that Al-Shabab has been trying to smuggle bombs in the Oil Containers format into
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የጠ/ሚ አብይ መልዕክት ፡ – ጠቅላዩ ሆይ የሚነግሩንን በተግባርም ይኑሩት፤ እኛም እንድንኖር ይፍቀዱልን።

Imageጠቅላይ ሚኒስትሩ እስከመቼ ምላሳቸውን አጣፍጠው በተግባር ሃገር እንዲተራመስ በር ከፍተው በፈጠሪ ስም እየነገዱ ይህን ምስኪን ሕዝብ እያዘናጉ ኢትዮጵያን እያደቀቁ ይኖራሉ ? ……. ከኢትዮጵያ ጠላቶች በላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና በዙሪያቸው ያሉ ባለስልጣናት የሚሰሩት ወንጀል ሃገርን እና ሕዝብን እየጎዳ ነው። ንግግርዎን እና ጽሁፎን በተግባር ይኑሩት ። ወንድም በወንድሙ ላይ የጨከነበትን፣ አብረን የኖርን ቀርቶ አብረን የዋልን በማይመስል መልኩ የተጋጨንባቸውን ዞር ብለን ስናይ ልባችን በኀዘን ይሰበራል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “ዛሬም እንደ ትናንቱ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን፣ እጃችንን ለምስጋና እንዘረጋለን”ሲሉ ባስተላለፉት መልዕክት ገለፁ:: ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የሚለው ስም ለችግሮች ያለመንበርከክ፣ በፈተና ሳይበገሩ የማለፍና እንቅፋቶችን ተሻግሮ ድል የማድረግ የክብር ስም ነው ብለዋል:: የትናንቱን ጨለማ እንዳለፍነው ሁሉ÷ የዛሬውን ጽልመት የማንሻገርበት ምክንያት እንደሌለ እያመንን፣ ብርታትና ጥንካሬውን ለሚቸረን ፈጣሪ ዛሬም ምስጋና ከማቅረብ አንቦዝንም፡፡ አመስጋኝነት ያለፈውን ዘመን በአሸናፊነት፣ ያለንበትን ወቅት በዕድለኝነት፣ መጪውን ጊዜ ደግሞ በብሩህ ተስፋ እንድንመለከተው የሚያድርግ ታላቅ ኃይል አለው። በአንጻሩ አማራሪነትና ምስጋና ቢስነት የተሸናፊነትና የዕድለ ቢስነት ሥነ ልቡናን ይፈጥራል፡፡ ራሳችንንና ሌሎችን በአዎንታዊነትና በፍቅር መመልከት እንዳንችልም ያደርገናል። በምሬትና በምስጋና ቢስነት የተጠመደ ግለሰብም ሆነ ሕዝብ የጎደለው እንጂ በእጁ ያለው ጸጋ አይታየውም፡፡ የደረሰበት በደል እንጂ የተሰጠው ዕድል አይጎላለትም፡፡ የሚመጣው መከራ እንጂ ከፊቱ ያለው ደስታ በኅሊናው አይሳልም። አመስጋኝ ሰው በመከራውና በጭንቁ ውስጥ ድሉንና ዕድሉን ማየት የሚችል ነው፡፡ ከወጀቡና ከማዕበሉ ይልቅ የመርከቧን ጥንካሬ ያያል፡፡ ከፈተናና ከችግሩ ግዝፈት ይልቅ፣ ሁሉንም
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ባለፉት 3 አስርት አመታቶች አማራው ሲጨፈጨፍ ቆሞ የሚያጨበጭበው ግለሰብ

የሶስት ጠቅላይ ሚኒስትሮች ቦርሳ ተሸካሚ የሆነው ሰዉዬ Demeke Mekonnen Hassen ባለፉት 3 አስርት አመታቶች አማራው ሲጨፈጨፍ ቆሞ የሚያጨበጭበው ግለሰብ …….. – በአማሮች ደም የሚሳለቀው ደመቀ መኮንን እና ቡድኑ ለስልጣን ሽኩቻና ለፖለቲካ ሴራ እንጂ ለአማራ ህዝብ ዋጋ አይሰጥም። ደመቀ መኮንን እና ቡድኑ በስልጣን ለመቆየት አማራውን የጦስ ዶሮ እያደረጉት ነው። በተላላኪነት ማገልገሉ ካለተላላኪነት መኖር እንደማይቻል አምኖ ተቀምጦ አማራን በማስጨፍጨፍ የግል ምቾቱን እየጠበቀ ነው። – በኦሮሚያ ክልል በተለይ በወለጋ የሚገደሉ አማሮች ትኩረት እንዳያገኙ ከኦህዴድ ብልጽግና ይልቅ በደመቀ መኮንን የሚመራው የብአዴን ብልጽግና ከፍተኛ ጥረት በማድረግ የአማራውን ድምጽ ለማፈን ይሯሯጣል። በወለጋ በከፍተኛ ሰቆቃ ውስጥ ያሉ፣ በኦነግ ሸኔ ታፍነው የተወሰዱ፣ በከበባ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ማዳን በየካምፑ ተፈናቅለው ያሉትን መርዳትና ዜጎች ለነገ ዋስትና እንዲያገኙ መስራት ሲገባ ሆን ብሎ እያስጠቃ ፣……… ሆን ተብሎ በአማራው ጭፍጨፋ ላይ የደመቀ መኮንን ቡድን በእጅ አዙር አማራን እያጠቃ ነው። – May be an image of 3 people, people sitting and people standingየደመቀ መኮንን ቡድን ከሕወሓት ዘመን ጀምሮ በተላላኪነት ማገልገሉ ካለተላላኪነት መኖር እንደማይቻል አምኖ ተቀምጦ አማራን በማስጨፍጨፍ የግል ምቾቱን እየጠበቀ ነው። የሃገር ገንዘብ ዘርፎ ለመሸሽ ሲያሟሙቅ የነበረው የደመቀ መኮንን ቡድን ለአማራው ምንም የማይጠቅም የዜጎችን መብት ለማስከበርም ምንም የማይፈይድ ወራዳ ቡድን ነው። – ይህ ቡድን በመላው አማራ ክልል የኦሕዴድ ብልፅግና ደህንነቶች እንዲሰማሩ በመፍቀድ እንዲሁም የመሳሪያ ማስፈታት ፕሮግራሞችን በመምራትና አርሶ አደሩን መቆሚያ መቀመጫ በማሳጣት ታሪክ ይቅር የማይለው ግፍ በአማራ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ነው። ያልሰራውን ታሪክ እንደሰራ አድርጎ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

1600 አማራ መሞቱ የአይን እማኞች የተናገሩትን መንግስት በመካድ ወደ 338 አጠጋግቶታል፤ ከአይን እማኝ በላይ ምስክር የለም።

ምንሊክ ሳልሳዊ ፡ መንግስት ሆይ ከአይን እማኝ በላይ ምስክር የለም። መንግስት ያወጣው የሟቾች ቁጥር አሃዝ ሆን ተብሎ ለማታለል የተደረገ ነው። ሕዝብ የመንግስትን መዋቅራዊ ውሸት ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ባለስልጣናት ሊያውቁ ይገባል። መንግስት ጥያቄው የቁጥር ሳይሆን የመብት መሆኑን ዘግቶታትል። የተሳሳተ መረጃ ከመስጠት ወጥመድ መንግስት ራሱን ሊያላቅቅ ይገባል። – በምዕራብ ወለጋ በኦነግ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 1 ሺሕ 600 ደርሷል – የዐይን እማኞች – መንግሥት በጊምቢው ጥቃት 338 ሰዎች መገደላቸውን ገለጸ ። – ቢልለኔ ስዩም መንግስት እንደ ተቋም ባለስልጣናቱ እንደ ግለሰብ ውሸታሞችና አጭበርባሪዎች ናቸው። በወለጋው የጊምቢ ቶሌ ቀበሌ ጭፍጨፋ ከአከባቢው ነዋሪዎችና ቀባሪዎች በላይ ማንም ማስረጃ ሊሆን አይችልም። ወንጀል የፈጸመው በመንግስት መዋቅር የሚደገፈው ታጣቂ መሆኑ እየታወቅ መንግስት የሞቱትን ሰዎች ቁጥር በሚመቸው መልኩ ማቅረቡ ተቀባይነት የለውም። መንግስት የቁጥር ጨዋታ የብሄር ቆጠራ በገባ ሰዐት ሁሉ የዜጎችን መብት ይዘነጋዋል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ጦር/ሠራዊት ብሎ በሚጠራው ሸኔ የተገደሉ ሰዎች ከ1 ሺሕ 600 መሻገሩን የዐይን እማኞች መግለፃቸው የታወቀ ሆኖ ሳለ የመንግስት መግለጫ በጊንቢው ጥቃት 338 ሰዎች መገደላቸውን መንግስት ምን ያህል መዋቅሩ በውሸት እንደተተበተመ ጠቋሚ ነው። በጥቃቱ የሞቱ ሰዎችን አስከሬን በመሰብሰብ ላይ የተሰማሩና ለደኅንነታቸው ሲባል ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ዐይን እማኞች ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት ከ1 ሺሕ 600 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ እና 900 የሚሆኑ ሰዎችን ሬሳ ቆጥረን ቀብረናል ብለዋል። የመብትና የቁጥር ጥያቄን መንግስት ከኝዛቤ ሊያስገባው
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የሃይማኖት ተቋማትና የሰላም ሚኒስቴር ከፖለቲካ ቁማር ውጪ የተቋምነት ግዴታቸውን ስላልተወጡ ሊፈርሱ ይገባል።

May be an image of 2 people, people standing, outdoors and textየሃይማኖት ተቋማትና የሰላም ሚኒስቴር ከፖለቲካ ቁማር ውጪ የተቋምነት ግዴታቸውን ስላልተወጡ ሊፈርሱ ይገባል። መንግስት በሰላም ሚኒስቴር እና በሃይማኖት ተቋማት ስም በሕዝብ ደም ላይ መቆመርን ሊያቆም ይገባል። ሕዝብ ይገደላል፤ ሌላው ተሰብስቦ አበል ይበላል። – ሃገር መከራ ላይ ናት፤ ሃገር በቋፍ ውስጥ ናት ፤ ዜጎች ይገደላሉ፤ በማንነታቸው ተለይተው አማራ ስለሆኑ ብቻ ይታረዳሉ ። ይህን ሃቅ ማንም መካድ አይችልም። የሰላም ሚኒስቴር በጀት መድቦ አበል ቆርጦ ተሰብስቦ በሕዝብ ደም ይቆምራል። ባለፉት አራት አመታት የሰላም ሚኒስቴር የሰራው ነገር ቢኖር ስብሰባ አዘጋጅቶ ካድሬ እየሰበሰበ አበል መውሰድ ብቻ ነው። ጭራሽ የሰላም ሚኒስቴር ከተቋቋመ ጀምሮ ሃገሪቷ ሰላም አታላች ። የሰላም ሚኒስቴር በሰላም ስም የተቋቋመ የጦርነት ማምረቻ ተቋም ነው። – የሰላም ሚኒስቴር የሱ ቢጤ ከሆኑ ሆዳም የሃይማኖት ተቋማት ጋር ሆኖ አከሕዝብ የሚሰበሰበውን ግብር ይጨረግዳል። የሃይማኖት ተቋማት ግዴታቸውን አልተወጡም። ግብረገብነትን ለምዕመናን ከማስተማር ይልቅ የግል ጥቅማቸውን በሚያሳድዱ አባቶች ተሞልተዋል። ጥቂቶች ቢኖሩም በበርካቶች ክፋት ተሸፍነዋል። መንግስት በሰላም ሚኒስቴር እና በሃይማኖት ተቋማት ስም በሕዝብ ደም ላይ መቆመርን ሊያቆም ይገባል። ሕዝብ የሚፈልገው መፍትሄ እንጂ ስብሰባና ወሬ አይደለም። ስብሰባ የባለስልታናትንና የካድሬዎችን ኪስ ለመሙላት የሚደረግ የማጭበርበሪያ መንገድ ነው። #MinilikSalsawi – Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር ይፍረስ !
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሆን ብለው የወለጋውን ጭፍጨፋ በመሸፋፈን የተሳሳተ መግለጫ ሰጥተዋል።

May be an image of textጠቅላይ ሚኒስትሩ ኦነግ ሸኔን ኢመደበኛ ታጣቂ የሚል ስም ሲሰጡት ኦነግ ሸኔ በበኩሉ ጭፍጨፋዉን የፈፀሙት ሽመልስ አብዲሳ “Gaachana Sirna” በሚል ስም ያደራጃቸው የኦሮሞ ሚሊሻወች ናቸው ብሏል ። ጠሚው ሽብርተኛ የተባለውን ኦነግ ሸኔን ከፋኖ ለማመሳሰል የሄዱበት መንገድ ያሳፍራል። ለማስታወስ ያህል ፋኖ በመንግስት ትዕዛዝ ማርከህ ታጠቅ የተባለ የሕዝብ ልጅ እንጂ ቀድሞ የነበረውን ክላሽ ሕዝብን ለመጨፍጨፍ የተጠቀመ ቡድን ኢመደበኛ ታጣቂ አይደለም ። – ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሆን ብለው እያወቁ ወንጀሉን ለማድበስበስ ፈልገዋል። ጭፍጨፋው የተፈፀመበት ቦታ ይታወቃል። ቤንሻንጉል ላይ ወንጀል ሲፈፀም የቤንሻንጉሉን ማውገዝ እንጅ ከአሁኑ ጋር አጃምሎ ማለፉ መፍትሄ አይሆንም። ወንጀሉ የተፈፀመበት ቦታ ስም አለው። የተጨፈጨፉት ንፁሃን ቀየ ነበራቸው። ኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ነው። የግድ እርምት የሚያስፈልገው ፅሁፍ ነው በማሕበራዊ ድረገፃቸው የከተቡት ። – ኦነግ ሸኔ በፓርላማ አሸባሪ ተብሎ መፈረጁን የረሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የወለጋውን ዘግናኝ ጭፍ*ጨፋ ተከትሎ ኦነግ ሸኔን ኢመደበኛ ታጣቂ ሲሉ ስም አውጥተውለታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ደም ይቀልዳሉ። ሽብርተኛ ብለው ፓርላማቸውን ያስጨበጨቡት ጠቅላዩ ድንገት ተነስተው ኦነግ ሸኔን ኢመደበኛ ታጣቂ የሚል ስም ለጥፈው ከፋኖ ጋር ሊያመሳስሉት ዳድቷቸዋል። በኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ያሉ ገዳዮችን ኢመደበኛ ታጣቂ ሲሉ የሚፈጽሙትን የሽብር ተግባር ሊሸፋፍኑላቸው ፈልገዋል። ይህ በሕዝብ ላይ የሚሰራ መንግስታዊ የፕሮፓጋንዳ ወንጀል ነው። ኦነግ ሸኔን ከፋኖ ለማመሳሰል የሄዱበት መንገድ ያሳፍራል። – ጭፍጨፋው የተለመደና የቆየ መሆኑን እያወቁ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርብ ጊዜ የተፈፀመ ችግር እንደሆነ አድርገው ለማቅረብ ፈልገዋል
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዛሬም የግንቦት 20 ፍሬዎች እነ ብልፅግና እንደ አባታቸው አፈናውን፣ ግድያውን፣ ማሳደዱን፣ ቤተሰብን ማሰቃየትን፣ እስሩን፣ ወዘተ ቀጥለውታል።

ዛሬም የግንቦት 20 ፍሬዎች እነ ብልፅግና እንደ አባታቸው አፈናውን፣ ግድያውን፣ ማሳደዱን፣ ቤተሰብን ማሰቃየትን፣ እስሩን፣ ወዘተ ቀጥለውታል። ግንቦት 20 ዘረኞች የነገሱበት ሐገር የተዋረደችበት የተረገመች ቀን ! – የበርካቶች ተስፋ የጨለመበት፣ ከሐገር አልፎ አሕጉርንና አለምን ያስደመሙ የኢትዮጵያ የጦር ሰራዊት የተበተነባት፣ ምሁራን የተገፉበት፣ ለሐገርና ለወገን የሚጠቅሙ የተገደሉባት የተሰደዱባትና ዘረኞችና አናሳ የአፓርታይድ ስርዓት አራማጆች ስልጣን በጠበንጃ የጨበጡባት እለት ናት። ሕወ. ሓት/ኢሕአዴግ/ብልፅግና ስማቸውን እየቀያየሩ በሕዝብ አናት ላይ የሚዘፍኑባት አገር የተፈጠረችው በዛሬው እለት ነው። ይህ የሕወ።ሓትን ሌጋሲ ብልጽግናም አስቀጥሎታል – ዛሬ ላይ ቆመን የምናያቸው የሌጋሲው አስቀጣዮች ሐገርን ለማተራመስ አመጽ የሚሰብኩ፣ ፖለቲካውን በዘር የሚለኩ፣ ቢሮክራሲውን በጎጥና በብሔር የሞሉ፣ ቅድሚያ ለዜጎች ሳይሆን ለዘር የሚሰጡ፣ አደርባዮች፣ የአፓርታይድ አራማጆች፣ የሚናገሩትና የሚያደርጉት የተለያየ የሆኑ ባለስልጣኖች። አስመሳዮችና በወሬ የሚደልሉ ታሪክ አጥፊዎች፣ የፖለቲካ ደላሎችና የአዞ እንባ አፍሳሾች፣ ያዘኑ መስለው ሕዝብን የካዱ ውርጃዎች የግንቦት ሃያ ፍሬዎች ትሩፋቶች ናቸው። – በግንቦት 20 ኢትዮጵያ አገራችን በጨለማ ጉም ተሸፈነች:: አገርና ህዝብ ጥቁር የሃዘን ልብስ ለበሱ:: ሲጠሏት እና ታሪኳን እና ህዝቧን ሲያዋርዱን ሲያንቋሽሹ በነበሩት ወያኔ ህወሃት ለእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ ተዳረገች:: ዘረኛው እና ጎጠኛው ወ,ያ ኔ ህወ,ሃት በመለስዜናዊ የሚመራው የማ,ፍያ ፋሺ,ስት ግልገል እና ግብረ አበሮቹ ጸረ ሀገር እና ጸረ ህዝብ የሆኑትን ለዘመናት የተከበረው የምኒሊክ ቤተ መንግስት ተቆጣጥረው የግልገል ፋሺ,ስቶች መንደላቀቂያ ሆነ:: – ህወ. ሃት ከደደቢት ይዞት የመጣውን ህገ ደንቡን የኢትዮጵያ ህገ መንግስት አደረገው:: ኢትዮጵያን በዘር ፣ በቋንቋ እና
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከዓለም አቀፍ አሸባሪዎች ተቀድቶ በአማራ ላይ የተፈፀመ የሽብር ስልት – (ሚስጥራዊው የእነ አህመዲን ጀበል ሽብርን በሚዲያ የደገፉበት ሰነድ)

ከዓለም አቀፍ አሸባሪዎች ተቀድቶ በአማራ ላይ የተፈፀመ የሽብር ስልት – ሽብሩን በሚዲያ እንዴት ደገፉት ? (ሚስጥራዊው የእነ አህመዲን ጀበል ሽብርን በሚዲያ የደገፉበት ሰነድ) ከስር የምትመለከቱት የእነ አህመዲን ጀበል ቡድን የዓለም አቀፍ አሸባሪዎችን ሁነኛ የሽብር ፕሮፖጋንዳ ተከትሎ በአማራና በኦርቶዶክስ ላይ ተግባራዊ እያደረገው ያለው ነው። ሰነዱ ከአንድ አመት በፊት የተሰራ ሲሆን ላለፉት ወራት በርካቶችን አሰልጥነው ወደ ተግባር ገብተዋል። ሰሞኑን በጎንደሩም ሆነ ከዛ ቀደም ባሉት የሽብር ተግባራት የሚጠቀሙት ይህን ስልት ነው።ምን አልባት በዚህ ሰነድ ጠላትና ወዳጅ ተብላችሁ የተፈረጃችሁ ግለሰቦች፣ ሚዲያዎች፣ ፓርቲዎች ትኖራላችሁ። ተመልከቱት። ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ለማዳን ከጠላት ጋር በተፋጠጡበት ወቅት እነ አህመዲን ጀበል የሽብር ፕሮፖጋንዳ ስራ ላይ ነበር። በቅርቡ ከገጠሙት የእነ ሙፍቲ መጅሊስ ጀምሮ በርካቶች በጠላትነት ተፈርጀዋል። ከእነ ቴዲ አፍሮ እስከነ ሀሰን ኢንጃሞ በጠላትነት ተፈርጀዋል። እነ አብንና እናት ፓርቲ በጠላትነት ተፈርጀዋል። ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ አላማቸውን የሚደግፍ ፓርቲ ተደርጎ ተቀምጧል። አንዳንድ የመንግስት ባለስልጣናት እንቅፋት ይፈጥሩብናል ተብለዋል። በዋነኛነት ጠላት የተባለው አማራው ነው። በፕሮፖጋንዳ እናሸብር የተባለው አማራውን ነው። የዚህ ፕሮጀክት ዋነኛ ተሳታፊ ሆነው የቀረቡት እነ አህመዲን ጀበል፣ ኢሳቅ እሸቱ፣ አብዱራሂም አህመድ፣ አብዱልጀሊል፣ ኢብራሂም ሙሉሸዋ ወዘተ ናቸው። የመጅሊሱ ከፍተኛ አመራሮች ጠላት ሲባሉ 17 ኮሚቴ ዋነኛው ደጋፊ ነው። ይህን አላማቸውን ለማሳካት የማጥቃት ፕሮፖጋንዳን መጠቀም ቀዳሚው አጀንዳቸው እንደሆነ አስቀምጠዋል። በአማራ ላይ የማጥቃት ፕሮፖጋንዳን እንጠቀማለን ብለው ካስቀመጧቸው 18 ስልቶች መካከል ጥቂቶቹ! ~ወጥመድ ውስጥ መክተት ~ማዋረድ ~ ፍርሃት መፍጠር ~ ችግራቸውን
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ማእድ ማጋራት ያለበት ሕዝብ እንጂ መንግስት አይደለም፤ ሕዝብን የመንግስት ጥገኛ ለማድረግ የሚኬድበት መንገድ ያሳፍራል ።

ምንሊክ ሳልሳዊ – ሕዝብ የሚፈልገው የኑሮ ውድነቱን ሊያቀል የሚችል የረጅምና የአጭር ጊዜ እስትራቴጂና እቅድ የሚነድፍና የኑሮ ጫናን የሚያቀል የኢኮኖሚ ስርዐት እንጂ አውዳመት በመጣ ቁጥር ለፖለቲካ ትርፍ የሚደረግ ንግድ አይደለም። ማእድ ማጋራት ያለበት ሕዝብ እንጂ መንግስት አይደለም። ሕዝብን የመንግስት ጥገኛ ለማድረግ የሚኬድበት መንገድ ያሳፍራል ። ይህ በማዕድ ማጋራት ስም የሚደረግ ፖለቲካ ሕዝብ ከገባበት የኑሮ ጭንቀት አያወጣውም። ጠንካራና ዘላቂ መፍትሄ የሚሆን የረዥምና የአጭር ጊዜ የኢኮኖሚ ስትራቴጂ ያስፈልጋል። – ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የመጋቢት ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ34.7 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ – የምግብ ዋጋ ግሽበት የመጋቢት ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ43.4 በመቶ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን ከየካቲት ወር 2014 ጋር ሲነጻጸር በ1.5 በመቶ ጭማሪ አሳይቷ፡፡ በያዝነውም ወር በአብዛኛው በእህሎች የዋጋ ጭማሪ የታየ ሲሆን የአትክልት ዋጋም ላይ መጠነኛ ጭማሪ ታይቷል፡፡ ሩዝ፣ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ሽንቡራና ምሥር በአብዛኛው የዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡ – በተጨማሪም ወተት፣ አይብና ዕንቁላል፣ ቅመማ ቅመም (በዋናነት ጨውና በርበሬ) ጭማሪ አሳይተዋል፡፡ የምግብ ዘይትና ቅቤ ዋጋ በፍጥነት የጨመረ ሲሆን ቡናና ለስለሳ መጠጦች ተከታታይ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል። – ሕዝብ የሚፈልገው የኑሮ ውድነቱን ሊያቀል የሚችል የረጅምና የአጭር ጊዜ እስትራቴጂና እቅድ የሚነድፍና የኑሮ ጫናን የሚያቀል የኢኮኖሚ ስርዐት እንጂ አውዳመት በመጣ ቁጥር ለፖለቲካ ትርፍ የሚደረግ ንግድ አይደለም።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከደብዳቢያችን በላይ እጃችንን ይዘው ያስደበደቡንን መቼውንም አንረሳም !

Minilik Salsawi : ከደብዳቢያችን በላይ እጃችንን ይዘው ያስደበደቡንን መቼውንም አንረሳም ! የችግሩ ምንጮች የችግሩ መስፋፋት የሆኑ መዋቅሮቹንና ችግር ፈጣሪ ባለስልጣናቱን መንግስት ያስወግድ። ችግሩ የመንግስት የዘር ፖለቲካ ፖሊሲና የመንግስት ባለስልጣናት ናቸው። መፍትሔው እነዚህን ሁለት የቀውስ አካላት ማስወገድ ነው። – መንግስት ከመናገርና ከማውራት ውጪ ምንም አይነት ተግባራዊ ስራ አልሰራም። መንግስት በሚዲያዎቹ የሚያወራውና በተግባር የሚሰራው ስራ በፍጹም አይገናኙም። የዜጎች ደም እንደጎርፍ እየወረደ የመንግስት ባለስልጣናትና መዋቅሮቻቸው በፌሽታ ሲደግሱና ሲመርቁ ይውላሉ። ዳኞቹ ዝንጀሮ መፋረጃው ገደል እምን ላይ ተቆሞ ይነገራል በደል። ሰሚ የለም። የጸጥታ ኃይሉ የዜጎችን ደሕንነት ከመጠበቅ ይልቅ በፌስቡክ አሉባልታ ላይ እና ዜጎችን በማሳደዱ ላይ ተሰማርቷል። – በለውጡ ሰሞን ቃል ሲገባ ሲወራ የነበረው ሁሉ የለም። ወሬ ሆኖ ንፋስ ወስዶታል። መንግስት ለችግሮችና ለቀውሶች መፍትሔ ከመፈለግ ይልቅ ሲባባሱና ሲስፋፉ ከማየት ይልቅ ምንም አልፈየደም። ዜጎችም ከጥቃት ራሳቸውን እንዳይከላከሉ በሎጀስቲክና በመረጃ የተደገፈ የተጠናከረ ኃይል እየተላከባቸው እልቂት ይፈጸምባቸዋል። – ሕዝቡ ለራሱ አስቸኳይ መፍትሔ ካላመጣ በስተቀር በፍጹም ችግሮች ሊፈቱ አይችሉም። የችግሩ ምንጮች የችግሩ መስፋፋት የሆኑ መዋቅሮቹንና ችግር ፈጣሪ ባለስልጣናቱን መንግስት እስካላስወገደ ድረስ ቀውሱ በንፁሃን ላይ እልቂቱ አያባራም። ችግሩ የመንግስት የዘር ፖለቲካ ፖሊሲና የመንግስት ባለስልጣናት ናቸው። መፍትሔው እነዚህን ሁለት የቀውስ አካላት ማስወገድ ነው። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የትምህርት ሥርዓቱ መሠረታዊ የግብረገብነት/የሞራል ክስረት ውስጥ ገብቷል ። – ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሥርዓቱ መሠረታዊ የግብረገብነት ክስረት ውስጥ ገብቷል፤ ትምሕርቱ ጥራት የለውም፣ ትምሕርት ቤቶች ከደረጃ በታች ናቸው። የየ12ኛ ክፍል ፈተና በሁለት ወር መሰጠቱ ችግሩን ያባባሰ ሲሆን የፈተናው ስርጭት ላይ ደግሞ ችግሮች በስፋት ተስተውለዋል። 30 ሺህ ተማሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል። የፈተናው ቀውስ ሁሉም ነገር ፖለቲካና የፖለቲካ ትርፍ ማግኛ መሆኑ ያመጣው ጣጣ ነው። የመንግስት ባለሟሎች የሚሳተፉበትና ትምሕርትን ከክልል ፖለቲካ ጋር በማጣበቅ የመጣ ችግር ነው። ትምህርት እና ፖለቲካ ሊለዩ፣ ዘርፉ ከእየ አካባቢነት ፉክክርም ሊለይ ይገባል ። ዘርፉ በስርዐታዊ ችግሮች ስለተበተበ መፍትሄውም ስርዐታዊ ነው። – ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ –  ተጨማሪ ከታች ያለውን ይመልከቱ    
Posted in Amharic News, Ethiopian News, Video

ብልጽግና ላይ ነን ! ሃገርን እያቃጠለ ነው ! …… የነገ የሃገር ስጋት እና የህዝብ ጠላት ማነው ?

ብልጽግና ላይ ነን ! ሃገርን እያቃጠለ ነው ! …… የነገ የሃገር ስጋት እና የህዝብ ጠላት ማነው ?  ምንሊክ ሳልሳዊ – በፖለቲካና የኢኮኖሚ አሸጥር ተብትቦ …. የየትኛው አገር መንግስት ነው የዜጎቹን ሰላም የሚነሳው ? የየትኛው አገር የመንግስት መዋቅር ነው ታጣቂዎችን እያስታጠቀና በሎጀስቲክ እየረዳ የሃገርንና የህዝብን ደሕንነት ዋስትና የሚያሳጣው ? መንግስት ሃገር ማስተዳደር አልቻለም። ባለስልጣናት ሕዝብን ከፖለቲካና ኢኮኖሚ አሻጥር ውጪ እንደ አገልጋይ መምራት አልቻሉም። መንግስት ከሚያስተዳድረው ይልቅ የማያስተዳድረው የኢትዮጵያ ክፍሎች ይበልጣሉ። በስርዐት አልበኞችና በሕገወጥ ታጣቂዎች ተወረናል። ……. በየትኛው አገር ነው የሕግ የበላይነትን ያላረጋገጠ መንግስት ስለ ሰላምና ልማት የሚሰብከው። ስርዐት አልበኝነትንና ሕገወጥነትን የሚፈጥሩ ባለስልጣናትን ታቅፎ ሕዝብን እያሸበሩ የሚኖሩ ባለስልጣናትን ተሸክሞ የሚያስተዳድረውን አገር የጦርነት ቀጠና ያደረገ መንግስት የለም።   በየቀኑ የምንሰማው ዜናኮ የሕዝብ ሰላምና ደሕንነት መደፍረሱ አገር በተኩስ መናወጡንና የዋጋ ንረት የህዝብ መፈናቀል ብቻ ነው። ሕዝብ ሰላማዊ ዜና መስማት ናፍቆታል። በመንግስት ሚዲያዎች የሚተላለፉ የውሸት ክምሮች የመንግስትን እኩይ ገበና ከማጋለጥ አልዘለሉም። በተራዉ ዜጋና በባለስልጣናት፣ በድሆችና ሐብታሞች መካከል የሚታየዉ እጅግ የሰፋ የኑሮ ተባለጥ ችግረኞች የአመፅና ዘረፋ አማራጭን እንዲያማትሩ እያስገደደ ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየናረ የመጣዉ የመሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋ ሕዝቡን ክፉኛ እያስጨነቀ፣ አንዳንዶችን ደግሞ ለተመፅዋችነት እየዳረገ ነዉ። ይህ ችግር የባለስልጣናት የአስተዳደር ውጤት እንጂ ሃገርና ሕዝብ የፈጠረው ችግር አይደለም።   የመንግስት ባለስልጣናት በኦሮሚያ ክልል እያስታጠቁ ንፁሃንን ከማስገደልና ከማፈናቀል አልበቃ ብሏቸው ወደ ደቡብ ክልል በመግባትም ህዝብን እያስገደሉ እያፈናቀሉና ንብረት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኦሮሚያ ክልል መግለጫ በራሱ ጥላቻን የሚሰብክ እና የግጭት ነጋሪት የሚጎስም ሲሆን ሌላ ፍጅት ለመቀስቀስ ያለመ ነው።

የኦሮሚያ ክልል መግለጫ በራሱ ጥላቻን የሚሰብክ እና የግጭት ነጋሪት የሚጎስም ሲሆን ሌላ ፍጅት ለመቀስቀስ ያለመ ነው። በመንግሥት ተሽከርካሪዎች ጦር መሳሪያ የጫኑ ከኦሮሚያ ክልል የተነሱ ታጣቂዎች የችግሩ መነሻ እንደሆኑ በማስረጃ ተረጋግጧል። ፈስ ያለበት ዝላይ አይችልም።ክልሉን ማስተዳደር ያልቻለው በበታችነት በሚሰቃዩ ሰዎች የሚመራው የኦሮሚያ ክልል ወለጋ ላይ በየቀኑ ንፁሀንን የሚታረዱበት ክልል ይዞ የአማራ ፅንፈኛ ሀይሎች ለኢትዮጵያ ስጋት ናቸዉ ሲል አላፈረም።የአማራ ማህበረሰብ ስቃይና መከራ እየተራዘመ ያለው፤ ከህዝቡ ጥቅም ይልቅ ለኦህዴድ የሚያጨበጭቡና ኦህዴዶችን የሚለማመጡ ግብስብስ የብአዴን መሪዎች ስላሉ ነው፡፡ ፈስ ያለበት ዝላይ አይችልም። – ምንሊክ ሳልሳዊ ክልሉን ማስተዳደር ያልቻለው በበታችነት በሚሰቃዩ ሰዎች የሚመራው የኦሮሚያ ክልል መንግስት ባወጣው መግለጫ፤ የአማራ ክልል የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እና ሌሎች የመገናኛ አውታሮችን “ጥላቻ በመስበክ” እና “የግጭት ነጋሪት በመጎሰም” ከሰሰ። የኦሮሚያ ክልል መግለጫ በራሱ ጥላቻን የሚሰብክ እና የግጭት ነጋሪት የሚጎስም ሲሆን ሌላ ፍጅት ለመቀስቀስ ያለመ ነው። ወለጋ ላይ በየቀኑ ንፁሀንን የሚታረዱበት ክልል ይዞ የአማራ ፅንፈኛ ሀይሎች ለኢትዮጵያ ስጋት ናቸዉ ሲል ማውራቱ የሞራል ለልናው መውደቁንና አለማፈሩን ማሳያ ነው። በመንግሥት ተሽከርካሪዎች ጦር መሳሪያ የጫኑ ከኦሮሚያ ክልል የተነሱ ታጣቂዎች የችግሩ መነሻ እንደሆኑ በማስረጃ ተረጋግጧል። ከመግለጫ ጋጋት ይልቅ መጀመሪያ የኦሮሚያ ክልልን በስርዐት እና ሕግ በማስተዳደር ክልሉን ከታጣቂና ከስርዐት አልበኞች ነፃ አድርጋችሁ የሕዝብን ሰላም አረጋግጡ። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ወረዳ መጋቢት 20 ላይ ታጣቂ ቡድኖች አንድ ሰው እንደገደሉ እና 7 ሰዎችን እንዳቆሰሉ መረጃ ተገኝቷል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የሕዝብን አንገት ያስደፋው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአራት አመት ጉዞ

የሕዝብን አንገት ያስደፋው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአራት አመት ጉዞ- ምንሊክ ሳልሳዊ   ሕዝብ ከሕወሓት አገዛዝ ለመላቀቅ ያደረገውን ትግል ተገን በማድረግ ወደ ስልጣን የመጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፉት አራት አመታት እጅግ በሰቆቃ የተሞላ እና የህዝብን አንገት ያስደፋ የአስተዳደር ጊዜያትን አልፈዋል። ዶክተር አብይ ሕዝብን የእርካብና መንበር መጽሃፋቸው ቤተ ሙከራ አድርገውታል። ሁላችንም ቢያንስ የለውጡ ችግር ይቀረፋል በሚል ተስፋ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ብንደግፍም ለውጡን ቀልብሰውት የመለስ ዜናዊን ሌጋሲ በዕጥፍ አሳድገውት አሳይተውናል። ያለፉ መንግስታት ከቆዩባቸው አስርት አመታቶች በላይ በአብይ የአራት አመት አገዛዝ በአገርና በሕዝብ ላይ የተፈፀሙ ኃጢያቶች እጅግ የበረቱ ናቸው። ሕዝብ በገዛ አገሩ ተዘዋውሮ መስራትና መኖር እንዳይችል የተደረገው በአብይ አስተዳደር ነው።   ከመቀሌ እስከ ሞያሌ፣ ከአሶሳ እስከ መልካጀብዱ፤ ከአማራ እስከ አፋር፤ ከትግራይ እስከ ኮንሶ ፣ ከመተከል እስከ ሃረር …. ወዘተ በኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያውያን ላይ በአብይ የአገዛዝ ዘመን ከባባድና መንግስት ኃላፊነቱን ያልተወጣባቸው ችግሮች ተከስተዋል፤ አሁንም ቀጥለዋል። የመንግስት ተጠያቂነትና ኃላፊነት የጠፋው በዶክተር አብይ አስተዳደር ዘመን መሆኑ እሙን ነው። አገራችን የነበሯትን ታላላቅ መሪዎች ያለአግባብ በስሜታዊነት በማስወገዷ ሌላ የምትከፍለው ዕዳ ያለባት ይመስላል። ለማንኛውም ግን ኢትዮጵያ ጥሩ መሪ ለማግኘት አልታደልሽምና እርምሽን አውጪ።   በጦርነት፣ በመፈናቀል በሰው ሰራሽ ድርቅና ረሃብ ሃገር የታመሰችው በዚህ ዘመን ነው። የመፍትሄ አካላት ተቀባይነት ያጡት ሆዳምና አስመሳይ ሰዎች ወደ መንግስት የተጠጉት በስፋት የታየው በዚህ አራት አመት ውስጥ ነው። ለሕዝብ ከመጨነቅ ይልቅ በመንግስት ጉያ ተወሽቀው ሌብነትና ሙስናን የተስፋፉት በዚህ አራት አመት ሲሆን በርካታ ባለስልጣናት ከነዘርማንዘራቸው
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አገራዊ ምክክር ኮሚሽንን በተመለከተ ለኦፌኮ መግለጫ መልስ ሰጡ

የዛሬው የብልፅግና ጠቅላይ ሚኒስትር መልዕክት የሕዝቡ እምነት በመንግስት ላይ መሸርሸሩን በቂ ማሳያ ነው። የምክክር መድረኩ እኮ በመንግስት የተደራጀ የቅጥረኞች ሕብረት ሲሆን ኮሚሽነሮችም የዕርቀ ሰላምና የወሰን ማካለል ኮሚሽኖችን ያከሸፉ የመንግስት ታዛዦች ናቸው። ጠቅላዩ በየመድረኩ የሚናገሩት በራሱ እንኳን ለሃገራዊ ምክክር አይደለም ለማሰብም አይጋብዝም። የጠሚው መልዕክት ለኦፌኮ መግለጫ መልስ ነው። ብልጤው ጠሚው የብሔራዊ ምክክሩ አሳታፊነት የሚሳካው ሁሉም ኢትዮጵያዊ በቀናነትና በባለቤትነት ሂደቱን መደገፍ ሲችል ነው ብለዋል። አሁንም ሕዝብ ያምንነናል ብለው ያስባሉ። ካድሬዎቻቸውና ተከፋይ አክቲቪስቶቻቸው ስላጨበጨቡ ብቻ በሞቅታ የሚሰጥ መግለጫ ምንም ውጤት የለውም። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በባለቤትነትና በቀናነት እንዲደግፍ እኮ መጀመሪያ መንግስት መኖሩ በተግባር ሊረጋገጥ ይገባል። የመንግስት ባለስልጣናት ከማውራት ውጪ በተግባር የሰሩት ስራ የለም። ጥቂት ነገርን አካብዶና አግዝፎ ማውራት ለትዝብት ይዳርጋል። የምታወሩት ሌላ የምትሰሩት ሌላ ሆኖብን ነው እኮ የተቸገርነው። በሁሉም ነገር ላይ ሕዝቡ እምነት አቷል። አይገባችሁም እንዴ ? ሕዝቡ ዝም ሲል የተስማማ መስሏቹ ከሆነ ስሕተት እየሰራችሁ ነው። ለውጡ ተቀልብሷል። ተረኝነት ነግሷል። እምነት ጠፍቷል። https://t.co/LOStgKKZxH — Minilik Salsawi 💚 💛 ❤ (@miniliksalsawi) April 1, 2022 ታንኩም ባንኩም በጃችን ነው በሚል የተረኝነት ፈሊጥ የምታወሩት ሌላ የምትሰሩት ሌላ ሆኖብን ነው እኮ የተቸገርነው። በሁሉም ነገር ላይ ሕዝቡ እምነት አቷል። አይገባችሁም እንዴ ? ሕዝቡ ዝም ሲል የተስማማ መስሏቹ ከሆነ ስሕተት እየሰራችሁ ነው። ለውጡ ተቀልብሷል። ተረኝነት ነግሷል። እምነት ጠፍቷል። የምክክር መድረኩ ሰዎች ካሁን በፊት በመንግስት ተወልደው በመንግስት የተገደሉ የመንግስት ኮሚሽኖች አባላትን ያሳተፈ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የበሽታችን ስሙ ጠፋን እንጂ መታመማችንንማ እናውቃለን !

በራሳችን ላይ ያለውን ጉድፍ ማየት ሳንችል በሌሎች ላይ ጥፋት የምንደርት ከሆነ ፍፃሜያችን አያምርም፡፡ የምትናገረው ሁሉ አይጥመኝም በመባባል ልናተርፍ የምንችለው ጥላቻን ብቻ መሆኑን አንርሳ፡፡ ስንሸነፍ ከመደናበር ድል ስናደርግ ከመንጠባረር ይሰውረን::ሁለቱ አዳጋች ነገሮች ውድቀትንና ስኬትን ማመን ናቸው፡፡ውድቀታችንን አምነን ካላረምን፣ ሌላ ውድቀት ይጠብቀናል፡፡ ስኬታችንንም አምነን መጪውን ካላዘጋጀን ወደ ውድቀት እንጓዛለን፡፡ ዋናው ቁምነገር እንግዲህ በመመሪያና በመግለጫ ሳንሸፋፈን በግልጽ ራሳችንን መመርመሩ ላይ ነው ማለት ነው፡፡ ሳንታገል ታገልን ሳናድግ አደግን አንበል፡፡ እየሞሰንን ንፁህ ነን እንበል፡፡ ትክክለኛ ፍርድ ሳንሰጥ ፍትሕ ርትዕ አለ እንበል፡፡ ካድሬዎቻችን ታማኝ ስለሆኑ ብቻ እና ሌላውን ስለዘረጠጡልን ታታሪዎች ናቸው አንበል እኛ ስለፈለግነው ብቻ የምናወራለት ትግል አሊያም በገዢነት መንጠራራት የምናወጣው ደንብ በግድ ለህዝብ ጠቃሚ ነው አንበል፡፡በራሳችን ላይ ያለውን ጉድፍ ማየት ሳንችል በሌሎች ላይ ጥፋት የምንደርት ከሆነ ፍፃሜያችን አያምርም፡፡ – ወደ ራስ ማየት፣ ወደ ውስጥ ማየት እጅግ ጠቃሚው መንገድ ነው፡፡በማናቸውም የህይወት መንገድ ብልህነትን የመሰለ ነገር የለም፡፡ አቅምን በትክክል መለካት የብልህነት ትልቁ አንጓ ነው፡፡ መጐምዠት ብቻውን የዕለት እንጀራ እንደማያመጣ ሁሉ፤ መመኘት ብቻውንም ፍሬ አያፈራም፡፡በፖለቲካው ዓለም መበላላት፣ መጠላለፍና ስም ማውጣት ባህል ከሆነ ውሎ አድሯል፡፡ ምናልባት የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ፍሬ የማያፈሩት ለዚህ ሊሆን ይችላል፡፡ የበሽታችን ስሙ ጠፋን እንጂ መታመማችንንማ እናውቃለን፤ ነው ጨዋታው፡፡ከስም ምን አተረፍን ተብሎ ሲጠየቅ እልቂት፡፡ ሰላም ማጣት፡፡ ሀገርን ማቆርቆዝ፡፡ ከስም ማውጣት ይሰውራን፡፡ ሀሳብን ከማንሸራሸር ይልቅ እገሌ እንዲህ ነው ከማለት ይሰውረን፡፡ በሽተኛውን ለማዳን በሽታው ላይ እናተኩር፡፡ – የብልሆች ምክር
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በሕልውና አደጋ ውስጥ ካለው ብልጽግና ለውጥ አገኛለሁ ብሎ የሚያስብ ካለ በሃገር ላይ ትልቅ ስሕተት እየሰራ ነው።

ቆም ብለን እያሰብን የምናነበው ጽሁፍ ምንሊክ ሳልሳዊ – የመንግስት ኃላፊነቱን መወጣት ያልቻለው ብልጽግና የምትፈልገውን ሁሉ እየመረጠ እያጠነፈፈ ይነግርሃል። የሚነግርህ ነገር ሁሉ መስማት የምትፈልገውን እንጂ መፍትሄውን አይደለም። የሚሰራውና የሚናገረው ነገር የተራራቁበት በቁሳዊ ልማት ወጥመድ የሚሰቃይ ፓርቲ ቢኖር ብልጽግና ነው። ብልጽግና የኢሕአዴግ ወራሽ ድርጅት ነው። ስም ከመቀየር ውጪ ምንም ልዩነት የላቸውም። መንግስትና ፓርቲ ተደበላልቀው የመንግስት ሚዲያዎችን እያጨናነቁት ነው። መሬት ላይ ያለውእውነታ ፣ የብልጽግና አመራሮች የሚያወሩትና የብልጽግናው መንገድ የተባለው እጅግ የማይገናኙ የተራራቁ፣ ሃራምባና ቆቦ ናቸው ። የሕወሓት አመራሮችም ይሁኑ የኦሕዴድ አመራሮች አንድ አይነት ከአንድ ባሕር የተቀዱ አስተሳሰባቸው በዘር ፖለቲካ የተቀኘ ነው። ብልጽግና ውስጥ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች ሕወሓት ኢሕአዴግ በደንብ ጠፍፎ የሰራቸው በመሆኑ ሕወሓት ኢሕአዴግ ሲሰራው የነበረውን ነገር ሁሉ ይደግሙልሃል፤ ብልጽግናዎች ሲደግሙልህ ታዲያ አንድ ከሕዝቡ ልብ ያገኙት እውነትን ለሽፋን ይጠቀሙበታል ኢትዮጵያዊነት ። ብልጽግና በሆዳቸው የሚገዙ ፖለቲከኞችንም የሚፈለፍለው በሕወሓት/ኢሕአዴግ ቀመር ነው። ብልጽግና አመራሮቹ በኔትወርክ ተደራጅተው በሌብነትና በውሸት ላይ ስለተመሰረቱ ይህን ኔትወርክ ለማፍረስ ከባባድ ጥረቶች ስለሚተይቁ ለማፍረስ ከብዶት እየተሰቃየ ነው። ከታጣቂ ሃይሎች ጀምሮ እስከ ማሕበራዊ ሚዲያ አክቲቪስቶች ድረስ የብልጽግና አመራሮች የጥቅም ኔትወርክ በመዘርጋት ለሃገር የማይበጅ ትልቅ ስሕተት ውስጥ ከመዘፈቃቸውም በላይ ስልጣናቸውን ሃገርን ለማፍረስ እየተጠቀሙበት ነው። የብልጽግና አመራሮች ከአባታቸው ሕወሓት/ኢሕአዴግ የወረሱትን የዘረፋ ስራ በመተግበር ሚስቶቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን በሕገወጥ ንግድ ውስጥ አሰማርተው በሃገሪቱ ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር በመፈጸም የሃገርን ኢኮኖሚ መቀመቅ ከተውታል። የውጪ ምንዛሬ በሕገወጥ መንገድ ከማዘዋወር ጀምሮ በጉምሩክ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ያለውጭ ምንዛሬ ፈቃድ እንዲገባ የተፈቀደው ዘይት መወደድና የሸማቾች ማሕበር ዝምታ አጠያያቂ ሆኗል።

ዘይት ከማንኛውም ቀረጥና ታክስ ነፃ ነው ይላል የገንዘብ ሚኒስትሩ ደብዳቤ። ስንዴ ስኳር ሩዝ እንቁላል ወዘተ (ደብዳቤውን ይመልከቱ) እነዚህ ከቀረጥና ከታክስ ነጻ የሆኑ ሸቀጦች በከፍተኛ ደረጃ ዋጋቸው ጨምሯል። ጦርነቶችናን የተፈጥሮ አደጋዎችን ተገን በማድረግ የሚዘረፉ ገንዘቦች በዋነናነት የኢንዱስትሪውን ሂደት በማቀጨጭ ኑሮ ውድነትን ፈጥረዋል። ከወራት በፊት የ”የኑሮ ውድነት ችግርን ለመፍታት ያለውጭ ምንዛሬ ፈቃድ (ፍራንኮ ቫሉታ) ስኳር ፣ ምግብ ዘይት ፣ ስንዴ ፣ ሩዝ ፣ የዱቄት ወተት ከውጭ ሀገር እንዲገቡ ተወስኗል። 250 ሺህ ዶላር (የውጭ ሀገር ገንዘብ) ያላቸው ምንጩን በብሔራዊ ባንክ እያረጋገጡ ማስገባት ይችላሉ።” – አቶ መላኩ አለበል የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ይህንን ይፋ አድርገው እንደነበር አይዘነጋም። ለሚዲያ ፍጆታ ከአብይ አሕመድ በበለጠ መላኩ ተሻገር ዋነኛ ተዋናይ ነው። ለጋዜጠኞች የወር ደሞዛቸውን በአንድ ቀን አበል በመክፈል የሃሰተኛ ዘገባዎች ተባባሪ ስለሚያደርጋቸው ዘይት ፋብሪካዎች ሲመረቁ በጣም ብዙ ጋዜጠኞች ጠብደል ጉርሻ በልተው ሄደዋል። ዘይት አሁን እንደ ሜርኩሪ ሲወደድ ያስመረቅናቸው ፋብሪካዎች የት ገቡ ብለው አልጠየቁም። በሲሚንቶና በዘይት ሙስና ውስጥ ትልቁ ድራሻ ያላቸው የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የተባሉት የብአዴን ባለስልጣን ለበላይነህ ክንዴ ለወርቁ አይተነው እና አንድ ድሬዳዋ ለሚገኝ የዘይት ፋብሪካ ማስፋፊያ 44 ሚሊዮን ዶላር ማከፋፈላቸው ይታወሳል። ይህ ዶላር ስራ ላይ አልዋለም። ለሚዲያ ፍጆታ ከመሆን አልዘለለም። እንዲህ አይነት ከፍተኛ እና አደገኛ የሙስና አባት የሆኑ ባለሃብቶችንና ባለስልጣናት በህዝብ ላይ እየተጫወቱ ይገኛሉ። ይህ ብቻ ሳይሆን በተለያየ ጊዜ ከፍተኛ ሚሊዮን ዶላሮችና ብሮች ለማስፋፊያ በሚል
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ግልጽነት የጎደለው የሃገራዊ ምክክር መድረክ ኮሚሽን ፡ ከ632 እጩዎች ውስጥ 11 ኮሚሽነሮች እንዴት እንደተመረጡ የሚያውቅ የለም።

በኮሚሽነርነት ለመሾም የቀረቡ ዕጩዎች ዝርዝር ከምስላዊ መረጃው ይመልከቱ። የተወካዮች ም/ቤት ዛሬ እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽንን በኮሚሽነርነት የሚያገለግሉ 11 ግለሰቦችን ሹመት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ፈጣሪውም፣ አድራጊውም፣ ሿሚውም፣ አስረጅውም….. የብልጽግና ፓርቲ የሆነበት ግልጽነት የጎደለበት አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት – ምንሊክ ሳልሳዊ በጉጉት በሚጠበቀው ሀገራዊ ውይይት ሂደት ውስጥ ከሲቪል ማህበራት ስጋት ውስጥ አንዱ ኮሚሽነሮችን በመምረጥ ሂደት ላይ ግልፅ አለመሆን ነው። ከ632 እጩዎች ውስጥ 11 ኮሚሽነሮች እንዴት እንደተመረጡ የሚያውቅ የለም። መንግስት በራሱ መራርጦ የፈለገው እንዲደረግለት የሄደበት አካሄድ ህዝብን ስላላሳተፈ በሃገር ላይ ለሚደርሰው አደጋ ብልጽግና ፓርቲ ተጠያቂ ነው። የዚህ ኮሚሽን እጣ ፈንታ እንደ እርቀ ሰላም ኮሚሽንና እንደ ወሰን ማካለል ኮሚሽን ይሆናል። የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽንን በኮሚሽነርነት የሚያገለግሉ 11 ግለሰቦችን ሹመት የብልጽግና ፓርቲ የደረሰው ድርሰት ነው። ይህ ሹመት በርካታ ተቃውሞ እየቀረበበት ነው። መንግስት ለተቃውሞው ጆሮ ዳባ ልበስ ብሏል። ፈጣሪውም አድራጊውም ሿሚውም አስረጅውም የብልጽግና ፓርቲ ነው ። ተሿሚዎቹ የሁለት አገር ዜግነት ያላቸው፣ የሕወሓት አገልጋይና በኃላም የብልጽግና አምባሳደሮች የነበሩ፣ በርካታ ሃገራዊ ጉዳዮችን ያበላሹ፣ የህዝብ አመኔታ የሌለባቸውና በህዝብ ዘንድ ተቀባይነታቸው የማይታወቅ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ፖለቲካ ቅርብ የሆኑ የምሁር አደርባዮች ወዘተረፈ ናቸው። ይህ ግልጽነት የጎደለው ሹመት የኢትዮጵያን ሕዝብ ያገለለ የብልጽግና ፓርቲን አካሄድ የተከተለ ስለሆነ ተቀባይነት የለውም። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጠ/ሚ ጥሩ ተናግረዋል፤ ነገር ግን ይህ ሊሆን የሚችለው በህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካና ኢኮኖሚ መስራት ሲችሉ ነው።

ሕዳሴ ግድብ ኃይል በማመንጨቱ እንኳን ደስ አለን ! ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሩ ተናግረዋል። ነገር ግን ይህ ሊሆን የሚችለው በቅድሚያ ራሳቸውንና ፓርቲያቸውን ከፖለቲካ ንግድ አውጥተው በህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካና ኢኮኖሚ መስራት ሲችሉ ነው። ትላንት የተናገሩትን ዛሬ ረስተው ነገ ሌላ በማውራት የሚመጣ ዘላቂ ሰላም የለም። እንዴት ልሸውድ የሚል የፉገራ ፖለቲካ ሊቆም ይገባል። ፖሊሲዎች ሲሻሻሉ፣ ሚኒስትሮች ከሃሰት ሪፖርት ሲወጡ፣ ካድሬዎች ብልጽግና እና ብልግናን ሲለዩ፣ ህግና ደንብ ሲከበር፣ ባለስልጣናት ከማናለብኝነት ሲላቀቁ፣ በህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ ሲኖር፣ ኢኮኖሚውን መንግስት በህዝብ ልክ ሲሰራው፣ የተማሩና አደርባይ ያልሆኑ ምሁራን የመንግስት አማካሪ ሲሆኑ ፣ ካድሬዎች ለተግባራዊ ስራ፣ ለልማትና ሰላም ሲሰማሩ፣ በዘፈቀደ እስርና መገፋት ሲቆም፣ የህግ የበላይነት ሲሰፍንና ፖለቲካው ከፍትሕ ስርዐቱ ላይ እጁን ሲያነሳ፣ መንግስትከፖለቲካ ንግድና ከማምታታት ሲወጣ…. የመሳሰሉት ሲከወን ……. …… ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ከዚህ በኋላ ከጥቃቅን አጀንዳ እርስ በእርስ ከመበላላት ፤ከእርስ በእርስ ሽኩቻዎች ወጥተን ተደምረን ተሰባስበን እንደ ህዳሴ ኢትዮጵያን እንድንሰራ ፤ ከመናቆር ከማያስፈልግ ከተንኮል ፖለቲካ እንድንወጣና ፤በይቅርታ ልብ በጋራ እንድንቆም ፤ተባብረን ሃገራችንን እንድናለማ ለሁላችንም በጎና ቅን መንገድ ይከፍታል። ይህ የሚተገበረው ጠቅላዩ መጀመሪያ እንደ ገዢ ፓርቲ ራሳቸውንና ፓርቲያቸውን መለወጥ ሲችሉ ብቻ ነው። ይህ ሊሆን የሚችለው በቅድሚያ መንግስት ራሱን ሲፈትሽ፣ ዜጎች በሰላም ደሕንነታቸው ተጠብቆ በነጻነት መኖር ሲችሉ ነው። ይህ ባሌለበት ባለስልጣናት በማናለብኝነት በሕዝብ ላይ ሲደነፉና የህዝብን መብት እየጣሱ ባለበት ሂደት ህዝብ በዝምታ ውስጥ ይሆናል ዝምታው የፈነዳ እለት ደግሞ መሪዎቹን
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ደመቀ መኮንን እና ቡድኑ በስልጣን ለመቆየት አማራውን የጦስ ዶሮ እያደረጉት ነው።

ደመቀ መኮንን እና ቡድኑ በስልጣን ለመቆየት አማራውን የጦስ ዶሮ እያደረጉት ነው። – ምንሊክ ሳልሳዊ ሕወሓት ላይ እጁን እየጠቆመ የሕወሓትን ፖሊሲ የሚያስፈጽመው ደመቀ መኮንን እና ቡድኑ ለስልጣን ሽኩቻና ለፖለቲካ ሴራ እንጂ ለአማራ ህዝብ ዋጋ አይሰጥም። በኦሮሚያ ክልል በተለይ በወለጋ በሸዋ የሚገደሉ አማሮች ትኩረት እንዳያገኙ ከኦህዴድ ብልጽግና ይልቅ በደመቀ መኮንን የሚመራው የብአዴን ብልጽግና ከፍተኛ ጥረት በማድረግ የአማራውን ድምጽ ለማፈን ይሯሯጣል። በወለጋ በከፍተኛ ሰቆቃ ውስጥ ያሉ፣ በኦነግ ሸኔ ታፍነው የተወሰዱ፣ በከበባ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ማዳን በየካምፑ ተፈናቅለው ያሉትን መርዳትና ዜጎች ለነገ ዋስትና እንዲያገኙ መስራት ሲገባ ሆን ብሎ እያስጠቃ ፣……… ሆን ተብሎ በአማራው ጭፍጨፋ ላይ የደመቀ መኮንን ቡድን በእጅ አዙር አማራን እያጠቃ ነው። በለውጡ ውስጥ ያልሰራውን ታሪክ እንደሰራ አድርጎ የሚያወራውና የሚያስወራው ደመቀ መኮንን ስሙን ለመገንባት በርካታ ገንዘብ እያፈሰሰ ነው። ገዱ አንዳርጋቸውንና ቡድኑን ከስልጣን ለማባረር ደፋ ቀና የሚለው ቡድኑ በኦሮሚያ ክልል ለሚጨፈጨፉና ለሚፈናቀሉ አማሮች መብት ደፋ ቀና ቢል ኖሮ ስንት ንፁሃን ዜጎችን ባዳነ ነበር። የደመቀ መኮንን ቡድን ከሕወሓት ዘመን ጀምሮ በተላላኪነት ማገልገሉ ካለተላላኪነት መኖር እንደማይቻል አምኖ ተቀምጦ አማራን በማስጨፍጨፍ የግል ምቾቱን እየጠበቀ ነው። የሃገር ገንዘብ ዘርፎ ለመሸሽ ሲያሟሙቅ የነበረው የደመቀ መኮንን ቡድን ሕወሓት ላይ እጁን እየጠቆመ የሕወሓትን ፖሊሲ እያስፈጸመ ይገኛል። ይህ ቡድን ለአማራው ምንም የማይጠቅም የዜጎችን መብት ለማስከበርም ምንም የማይፈይድ ወራዳ ቡድን ነው። ይህ ቡድን በመላው አማራ ክልል የኦሕዴድ ብልፅግና ደህንነቶች እንዲሰማሩ በመፍቀድ እንዲሁም የመሳሪያ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በመንግስት መዋቅር ሙሉ ድጋፍ የሚደረግለት የኦነግ ጦር በወለጋ፣ ሸዋና ጉጂ ብቻ ሳይሆን በቤንሻንጉል ጉምዝ ሳይቀር የማሰልጠኛና የማደራጃ ካምፕ አለው።

እውነታው ይህ ነው ! ወለጋ ዛሬ ሌሊትም 13 የአማራ ተወላጆች ተገድለው አድረዋል ከተገደሉት 13 ሰዎች አራቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው:: በኦሮሚያ የሚፈጸሙ ወንጀሎችና የሽብር ድርጊቶች የሚመራው የኦሮሚያ ብልጽግና ነው። የኦነግ ጦር መንግስት ሸኔ የሚለው በቤንሻንጉል ጉምዝ ሳይቀር የማሰልጠኛና የማደራጃ ካምፕ አለው። የመንግስት ሚዲያዎች በተለመደው የቅጥፈት ዘገባቸው ሰንቀሌና ቀልቀልቲ ማሰልጠኛ እንደተደመሰሰ ነግረውናል። ቅጥፈት የማይሰለቸው መንግስት ምንም አልሰራም እንዳይባል ራሱ በሚያዘጋጀው ድራማ ጥይቶችንና የጦር መሳሪያዎችን በቁጥጥር ስር እንዳዋለ አድርጎ ይሰብከናል። በወለጋ የሚገኙ የኦነግ ጦር ማሰልጠኛዎች እንዲሁም በሸዋና በቤንሻንጉል የሚገኙ ማሰልጠኛዎችና ማደራጃዎች ምንም አይነት ውድመትም ይሁን ጉዳት አልደረሰባቸውም። ጭራሽ ሮኬቶችንና የተለያዩ ከባባድ መሳሪያዎች እንዲታጠቅ ዝግጅቱ ተጠናቆ በአዲስ መልክ የሎጀስቲክ ስራው ሊጀመር ነው። ይሕን በቅርብ ካሉ የኦነግ ጦር ሰዎች ማረጋገጥ ተችሏል። ይህ በተቀናጀ መልኩ የሎጀስቲክ ድጋፍ የሚያገኘው የኦነግ ጦር ከበታች የኦሮሚያ ብልጽግና አመራሮች ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የኦሮሚያ ብልጽግና አመራሮች ድረስ የጦር ጄኔራሎች ሳይቀሩ በተቀናጀ መልኩ በቂ ድጋፍ ይደረግለታል። በኦሮሚያ ክልል በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ እንደ ዜጋ በገዛ አገራቸው እንዳይኖሩ ከፍተኛ ስራ በመስራትና በማስገደል ላይ የተሰማራው በኢትዮጵያ ስም እየነገደ ተግባሩ ኝ ኢትዮጵያን ማጥፋት የሆነው የኦሮሚያ ብልጽግና ለሚሰራው የተንኮልና የደባ ስራው የሕወሓትን ጦርነት መክፈት እንደ ሽፋን ተጠቅሞበታል። አገር እንዳትፈርስ፣ ሃገር ለማፍረስ፣ ሃገር ልትፈርስ ነው ወዘተረፈ በሚል ፕሮፓጋንዳ በመርጨት በተግባር ግን አገር እያፈረሰ ያለው የኦሮሚያ ብልልፅግና የሚባለው አደገኛ ቡድን ነው። የኦነግ ጦር በጉጂ፣ በወለጋ። በሸዋና በቤንሻንጉል የሚፈጽመው
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኢ-መደበኛ አደረጃጀት ችግር ከሆነ ኢ-ህገ መንግሥታዊው የክልሎች ልዩ ሀይል ይፍረስ !

ኢ-ሕገመንግስታዊ የክልሎች ልዩ ኃይል አደራጅቶ አሰልጥኖና አስታጥቆ የሚንቀሳቀሰው መንግስት ስለ ኢ-መደበኛ አደረጃጀት ወይንም ስለ ፋኖ የማውራት ሞራል የለውም። እስከመቼ ነው በአማራ ክልል የሚደረጉ ሕዝባዊ ጉዳዮች ሁሉ ወንጀል ተደርገው የሚፈረጁት ? መቼ ነውስ ይህ ፍረጃ የሚቆመው ? በሃገሪቱ ህዝብ ላይ ሰቆቃን የፈጸሙና የሃገሪቱን ንብረት ያወደሙ ኃይሎች ጋር እየተደራደረ ሃገርን ከወራሪ ለማዳን የዘመቱ ኃይሎችን ለማስወገድ አቅጣጫ አስቀመጥኩ የሚለው ….. ? ለራስዋ ያላወቀች ለቅዱስ ገብሬል መድሃኒት ጠየቀች ! – ምንሊክ ሳልሳዊ ለመደበኛ አደረጃጀት ጠንካራ ስራዎች መስራት የሚጠበቅበት መንግስት ለኢመደበኛ አደረጃጀት መድሃኒት ፍለጋ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ሲራወጥ ማየትን የመሰለ አስገራሚ ነገር የለም። መንግስት ኢመደበኛና መደበኛ አደረጃጀት ብሎ ስም ከመለጣጠፉ በፊት ለሃገራችን አስጊ ናቸው ብሎ የፈረጃቸውን አሸባሪ ኃይሎች ያላቸውን ሕወሓትን እና ኦነግ ሸኔን አስወግዶ ያሳየን። በሃገሪቱ ህዝብ ላይ ሰቆቃን የፈጸሙና የሃገሪቱን ንብረት ያወደሙ ኃይሎች ጋር እየተደራደረ ሃገርን ከወራሪ ለማዳን የዘመቱ ኃይሎችን ለማስወገድ አቅጣጫ አስቀመጥኩ የሚለው ወሬ ተቀባይነት የለውም። ካሁን ቀደም በተደጋጋሚ በየአቅጣጫው እንደተባለው የኦሕዴድ ሸኔ አገዛዝ ከሕወሓት ጋር ያለውን ጦርነት ወደ ማብቃቱ ሲደርስ በአማራውና በፋኖው ላይ እጁን ማንሳቱ አይቀርም ተብሎ ተነግሯል። ይህን ነገር አሁን ማየት ችለናል። በኢመደበኛ አደረጃጀት ስም አማራውን ለማኮላሸት የሚኬድበት መንገድ እጅግ አሳፋሪ ነው። መንግስት በሕወሓት ስጋት ውስጥ ሆኖ መከላከያው ወደ ኃላ ሲያፈገፍግ ደጋፊና ረዳት ከሆኑ በዋናነት የአማራና የአፋር ኃይሎች ተጠቃሽ ናቸው። በኢመደበኛ አደረጃጀት ሰበብ በመፍጠር አማራውን ለማዳከም የሚቆፈረው ጉድጓድ እጅግ አደጋው የከፋ ነው
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከፍተኛ የኢኮኖሚ ውድቀትና ድሕነት ባለበት አዲስ አበባ ብቻ ለግንባታ መንግስት ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አደርጓል

የሕዝብን ሕይወት በማይለውጡ፣ የህዝብን የኑሮ እድገት በማያረጋግጡ፣ የኑሮ ውድነትንና የኢኮኖሚ ድቀትን በማያሻሽሉ ግንባታዎች ላይ መንግስት ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አደርጓል። ይህ በጦርነት በተደቆሰች ኢትዮጵያ ላይ ቢሊዮኖችን በግንባታ ላይ ማፍሰስ ምንም ዋጋ የማይሰጥ ነው። ባለፉት አራት አመታት ብቻ የህዝብን ህይወት በሚቀይሩ ድህነትን በሚቀርፉ መሰረታዊ በሚባሉ ነገሮች ላይ መንግስት ቢሊዮኖችን ገንዘቡን ፈሰስ ቢያደርግ በርካታ የኢኮኖሚ ለውጦችን ማድረግ በቻለ ነበር።በአዲስ አበባ ሕዝብ ምን ያሕል ተቸግሮ እንደሚኖር ለማወቅ በየዳቦ ቤቶቹ ደጃፍ ያለውን ሰልፍ ማየት በቂ ነው። ባለፉት ሶስት አመታት በአዲስ አበባ  የተደረጉ ትላልቅ የፓርክ ግንባታዎች የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት እድሳትን ጨምሮ ወደ 21.75 ቢሊየን ብር ወጪ ተደርጓል። ይህ ወጪ ለመሰረታዊ የህዝብ አገልግሎቶች ቢውሉ ትልቅ ስራ ይሰሩ ነበር። ለምሳሌ የቀዳማዊ እመቤት ቢሮ ለአዲስ አበባ የዳቦና ዱቄት ፋብሪካ በ217 ሚሊዮን ብር ሰርቶ አስረክቧል። ይህ ማለት የማዘጋጃ ቤት እድሳት ወጣ የተባለው ገንዘብ 2.2 ቢሊዮን ብር ቢያንስ ስምንት የዳቦና የዱቄት ፋብሪካዎችን መገንባት ይችላል። ወደ ሌሎቹ የትልልቅ ፓርኮች ግንባታ ሂሳብ ውስጥም ስንገባ ቅድሚያ ለህዝብ አገልግሎትና መሰረታዊ ነገሮች ላይ ቢውሉ የበርካቶችን ሕይወት ይለውጡ ነበር። በርካታ ስራ አጦችን ድሆችን ብሎም የድሃ ድሆችን ባቀፈች ከተማ ላይ ለግንባታ ብቻ የሚፈሱ ቢሊዮኖች እንዲሁም ከግ ንባታ ውጪ ጋር የማይመጣጠኑ ገንዘቦች ጥያቄ ያስነሳሉ። የሕዝብን ፍላጎት ያላሟላ አስተዳደር በቢሮ ግንባታና እድሳት ላይ ቢሰማራ ከራሱ ምቾት በስተቀር ለሕዝብ የሚፈይደው ነገር የለም። የህዝብ መሰረታዊ ፍላጎቶች ባልተሟሉበት ከተማ ላይ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አቦይ ስብሃት ተንደላቆ እንደገና ሊኖር ቤተሰብ ያጡ ህፃናት ግን ጎዳና ላይ ወድቀው ሊቀሩ ? – ሕዝብን የጦርነት ሰለባ ማድረግ ለምን ተፈለገ ?

የብልጽግናው ጠቅላይ ሚኒስትርና ባለስልጣኖቻቸው ማብራሪያ ሊሰጡ ይገባል ! አቦይ ስብሃት ተንደላቆ እንደገና ሊኖር ቤተሰብ ያጡ ህፃናት ግን ጎዳና ላይ ወድቀው ሊቀሩ ?????? …………… በመጨረሻም ፌልትማን ስራውን በኢትዮጵያ በተሳካ ሁኔታ አከናውኗል ! እውነትን የማሰብና የመናገር ሞራል ሊኖረን ይገባል ። ይህ ሁሉ ውድመት ግድያ እስር ከመከሰቱ በፊት መንግስት በስሜት ሲነዳ ህዝብንም ሲነዳ ተው ያላለው ዛሬ ድንገት ተነስቶ በስሜት አንነዳ እያለን ነው። ሕወሓትን አምርረን እስከታገልነው ድረስ የነስብሃት መፈታትና ድርድሩን ፖለቲካዊ ስሌቱን የብልጽግናው ጠቅላይ ሚኒስትርና ባለስልጣኖቻቸው ማብራሪያ ሊሰጡ ይገባል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲህ ብለውን ነበርኮ ! ተጭነው ይመልከቱት ሕዝብን የጦርነት ሰለባ ማድረግ ለምን ተፈለገ ? ወሎና ትግራይን ማውደም ለምን ተፈለገ ? የሕወሓት ወንጀለኞች ለምን ተፈቱ ? የሕወሓት አመራሮችን ንብረትና የዘረፉትን ገንዘብ መመለስ ለምን አስፈለገ ? ለዚህ ሁሉ ወንጀል ተጠያቂ ማነው ? ለማይረባ ፖለቲካ ህዝብ ጭዳ እንዲሆን ለምን ተፈለገ ? ቀጣዩ ምስጢራዊ ድርድር ምንድነው ? ……. አብይና ፖለቲከኞቹ ነገስ ምን ያደርጋሉ ብሎ መዘጋጀት መጠንቀቅ ነው። – የጦር አመራሩና የፖለቲካ አመራሩ ተጠያቂ ናቸው። ችግሩን ለመፍታት መንግስት እያደረገ ያለው ግልፅ አይደለም። የተገደሉት ወገኖቻችን ደም አሁንም ይጮሀል። ፍትህ ስጡኝ እያለ። ንብረቱና ከተማው ወድሞ ባዶ አገር እንዲታቀፍ ለተፈረደበት የወሎ ሕዝብ ካሳ ማን ሊከፍለው ነው? ህዝብ ይጠይቃል። ለፈሰሰው የንፁሀን ደም ተጠያቂ ማነው ? ለአማራና ለአፋር ሕዝቦች ጉዳት ተጠያቂው ማነው ? ከመጀመሪያው ለምን ይህ አልተደረገም ? ይህ ሁሉ ጥፋት እንዲደርስ ለምን ተፈለገ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

“ጠላት ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበታል፤ የወገንን ምት ሊቋቋም አልቻለም”፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ተበታትኖ የወጣውን የጠላት ኃይል እየተከተልን ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ኮምቦልቻ፣ ደሴ እና ባቲ ሙሉ ለሙሉ በመለቀቁ ለመላው ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ከግንባር አስተላልፈዋል። – ሸዋ በሙሉ፣ ወሎ በከፊል የአፋር ክልልም ሙሉ ለሙሉ ነፃ መውጣቱን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶበታል፤ የወገንን ምት ሊቋቋም አልቻለም ብለዋል። – ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እስካሁን የተገኘው ድል ከፍተኛ ድል ነው፤ ኢትዮጵያ አትሸነፍም፣ በድል የምትታወቅ አገር ናት፣ ለማመንም የሚከብድ ድል ነው ብለዋል። – ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠላት ይመታል፣ ድሉም ይቀጥላል ብለዋል። –  
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በሐሰት ፕሮፓጋንዳ ሽብር መንዛቱን ቀጥሏል ።

አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ዛሬን ጨምሮ ሰሞኑን በተከታታይ በሚያወጣቸው መግለጫዎች በሐሰት ፕሮፓጋንዳ በመፍጠር በሕዝብ ላይ ሽብር መንዛቱን ቀጥሏል። ራሳቸው አሜሪካኖቹ በኢትዮጵያ ውስጥ የሽብር ጥቃት እስካልፈጸሙ ድረስ አዲስ አበባ ሰላም መሆኗን መንግስት በተከታታይ የሚያወጣቸው መረጃዎች የገለጸ ሲሆን አዲስ አበባ መስተዳደር በበኩሉ ዲፕሎማቶችን በመሰብሰብ ገለፃ ማድረጉን የመንግስት ሚዲያዎች ተናግረዋል። የአሜሪካን ኤምባሲ ዛሬ በለቀቀ መግለጫ እንደገለጸው በኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለው የሽብር ጥቃት ሊደርስ እንደሚችል አስታውሷል። አሸባሪዎች ዲፕሎማሲያዊ ተቋማትን፣ የቱሪስት ቦታዎችን፣ የመጓጓዣ ማዕከሎችን፣ የገበያ ማዕከሎችን፣ የገበያ ማዕከሎችን፣ የምዕራብ ንግዶችን፣ ሬስቶራንቶችን፣ ሪዞርቶችን፣ የአካባቢ የመንግስት ተቋማትን እና ሌሎች የህዝብ ቦታዎችን በማነጣጠር በትንሽ ወይም ያለ ምንም ማስጠንቀቂያ ሊያጠቁ ይችላሉ። የአሜሪካ ዜጎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና በባዕድ አገር ዜጎች የሚዘወተሩ ቦታዎችን እንዲያስወግዱ በጥብቅ ይበረታታሉ። ሲል ሊፈፅምና ሊያስፈጽም ያሰበውን የሽብር ጥቃት ገልጻል ። ይህ የአሜሪካ ኤምባሲ መግለጫ በሃገሪቱ ሰላም እንዳሌለ በማስመሰል የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በመርጨት ሰላምን ለማደፍረስ ያቀደው እቅድ እንዳለ አመላካች ነው። ካሁን ቀደም አሜሪካ በተለያዩ ሃገራት እንደምትፈፅመው አይነት የሽብር ድርጊቶችን በመፈጸም የሃገራችንን ሰላም ለማደፍረስ ማሰቧን ያስታውቃል። የኢትዮጵያ መንግስት በተከታታይ እንዳሳወቀው የሰላም ጉዳይ ከሕብረተሰቡ ጋር በቅንጅት በመስራት ያረጋገጠው ጉዳይ መሆኑን ገልጿል። የህወሓት የሽብር ቡድን በአዲስ አበባ እና በዙሪያው ለሽብር ተግባር ያሰማራቸው ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። በከተሞች በህብረተሰቡ ውስጥ በተለያዩ መንገዶች በመመሳሰል እንዲገቡ በማድረግ አዲስ አበባ እና በዙሪያው ተልእኮ ሰጥቶ በማስገባት ለሽብር ተግባር እየተንቀሳቀሱ መሆኑን እንደተደረሰበት የፌዴራል
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የመንግስት የዛሬ ውሳኔዎች ለፌልትማን ሰርግና ምላሽ ነው !

የመንግስት የዛሬ ውሳኔዎች ለፌልትማን ሰርግና ምላሽ ነው ! ምንሊክ ሳልሳዊ የውጪ ኃይሎች እንቅስቃሴ በውስጥ ጉዳያችን ላይ ተጠናክሮ መቀጠሉና ጫናው ውጤት እያስገኘላቸው መምጣቱ በቀጣይነት ስጋትን ያስጭራል። ለሰላዮቻቸው በርን ከፍቶ ኑና ድፈሩን አስደፍሩን የሚል ውሳኔ መሰጠቱ የማያቋርጥ ዋጋ እንዳያስከፍለን መንግስት ጠንካራ እጅግ ጠንካራ የሆነ ቁጥጥር በነጮቹና በውስጥ ቅጥረኞቻቸው ላይ ሊያደርግ ይገባል። የአሚሪካኖቹ እንቅስቃሴና የኬንያ ኢትዮጵያን ማንቆለጳጰስ ለሕወሓት ጥንካሬ እንዳይሰጥ መንግስት መጠንቀቅ አለበት ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ካሁን ቀደም በዕርዳታ ስም በኢትዮጵያ ለነበሩት የረድኤት ድርጅቶች የፈቀደው የበረራ ፈቃድ ብዙ መዘዝ ይዞ ከመምጣቱም በላይ ለሕወሓት ግስጋሴ በር ከፍቷል። የረድኤት ድርጅቶች በረራውን ተከትሎ ከውስጥ ቅጥረኞቻቸው ጋር ተቀናጅተው ለሕወሓት በርካታ ጠቀሜታ ያላቸውን ጉዳዮች አስፈፅመዋል። ካለፈው ሂደት መንግስት መማር አለመቻሉና ሌላ ብልሐት ለመፍጠር አለመሞከሩ ዋጋ እንዳያስከፍለን አሁንም ስጋት አለን። ብሊንከን ኬንያን ተጠቅሞ የሚሰራውን አሻጥር መቀጠሉ ጥርጣሬ ያሳድራል። የኬንያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የሰጡት መግለጫ በውስጡ በርካታ መርዞች የያዙ መሆኑን የዲፕሎማሲ ቋንቋው ሲሰነጠቅ ግልጽ ነው። ብሊንከን ወደ ናይጄሪያ ሲያቀኑ የመፈንቅለ መንግስቱና የብጥብጥ ኤክስፐርት የሆነው ፊልትማን ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ከደመቀ መኮንን ቢሮ ተከስቷል። ይህ የተንኮል ጉዞ ለሐገራችን አደጋ ይዞ እንዳይመጣ ፈጥኖ ሊታሰብበት ይገባል። መንግስት በኮምቦልቻና በላሊበላ ለሰብአዊ ርዳታ የሚውሉ በረራዎች መፍቀዱና ወደ ትግራይም 369 ርዳታ የጫኑ መኪናዎች እንዲገቡ መፈቀዱን አቶ ደመቀ ለፊልትማን ነግረዋቸዋል። ይህ ማለት ለአሜሪካ ሰርግና ምላሽ ነው። የምትፈልገውን ነገር ሁሉ ለሕወሓት ወደ ኮምቦልቻና ላሊበላ በማድረስ ደጀን በመሆን ኃይሉ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የካድሬዎች ልፍስፍስ ወሬና የባለስልጣናት ብስለት የጎደለው ንግግር

የካድሬዎች ልፍስፍስ ወሬና የባለስልጣናት ብስለት የጎደለው ንግግር ለነገ አደጋ ነው!  ምንሊክ ሳልሳዊ መንግስት የካድሬዎችን አፍ ያሲዝ ፤ ባለስልጣናቱን አደብ ያስገዛ ፤ ጊዜው የፖለቲካ ብስለትና የዲፕሎማሲ ብልሐት የሚፈለግበት ወቅት ነው። ከስሜት ፖለቲካ በመውጣት አጉል ባለስልጣናትን ከማሞጋገስ በመውጣት ሐገራችንን ከወራሪ ሕዝባችንን ከአሸባሪ ልንታደገው ይገባል። ካድሬ ነን ባዮች እከካም ፍየል ባለስልጣናት ጉማሬ ሆነዋል። በተገኘ አጋጣሚ ሁሉ ጦርነቱ ላይ እሳት ማርከፍከፍ ህዝብን በጥላቻ መግፋትና ማሸበር ሊቆም ይገባል። የአብዛኛው ችግሮች ምንጫቸው የካድሬዎች ልፍስፍስ ወሬና የባለስልጣናት ብስለት የጎደለው ንግግር ነው። እንደፈለጉ መናገር ከባለስልጣናት አይጠበቅም። ሕግን ሽፋን አድርጎ ሕዝብ ላይ የሚወረወሩ የፖለቲካ ቦምቦች ዋጋ ያስከፍላሉ። ስለሐገርና ስለሕዝብ ሲነገር ኃላፊነትና ተጠያቂነት ያስፈልጋል። ጥንቃቄ ያስፈልጋል። መንግስት ጦርነቱን እጅግ ብልሐት በሞላበት መንገድ መጨረስ አለበት ። በመንግስት ደረጃ ያሉ ሰዎች በመንግስት ጉያ ተወሽቀው በርካታ እንቅፋቶችን እየፈጠሩ ስለሆነ መንግስት የራሱን መፍትሄ በመፈለግ የውስጥ መዥገሮችን ጉዟቸውን ሊገታ ይገባል። ባለስልጣናት የፖለቲካ ምላሶቻቸው ፕርቶኮልንና ዲፕሎማሲን ያማከለ ሊሆን ይገባል። በባለስልጣናት ሌላ ድንገት ሮጠው ካድሬ የሆኑ የዘር ፖለቲካው ሮቦትነትን ለራሳቸው ያጎናጸፉ የለውጥ አጥቢያ ካድሬዎች ሲሆኑ እንደ እከካም ፍየል ከብልጽግና ጋር እየተሻሹ የተጋቱትን ተጽፎ የተሰታቸውን በየማሕበራዊ ሚዲያ ላይ እየተፉ በሕዝብና በመንግስት መካከል መተማመን እንዳይኖር ሕዝብ እንዲሸበር የሚያደርጉ ስለሆነ መንግስት እነዚህን ካድሬዎች የመንግስት ሚዲያዎች የገደል ማሚቱ ብቻ እንዲሆኑ እንደለመዱት በኮፒ ፔስት ስራ ላይ ያሰማራቸው ስንል እንጠቁማለን። መንግስት የካድሬዎችን አፍ ያሲዝ ፤ ባለስልጣናቱን አደብ ያስገዛ መልዕክታችን ነው። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኦባሳንጆ – ለራሷ ያላወቀች ለቅዱስ ገብርኤል መድኃኒት ጠየቀች !

ለራሷ ያላወቀች ለቅዱስ ገብርኤል መድኃኒት ጠየቀች ! ምንሊክ ሳልሳዊ ኦባሳንጆ በካርተር ዘመን ለአሜሪካ የስለላ ድርጅት እንዲሰራ የታጨ ናይጄሪያዊ ነው። አሁንም ያው የአሜሪካንን ሚና ለመወጣት በአፍሪካ ሽፋን በየላኩት ቦታ ይጓዛል። የአፍሪካ ሕብረትን በጀት ምዕራባውያን ስለሚሸፍኑ ሕብረቱ በታዘዘው መሰረት የነአሜሪካ አስፈጻሚ አካል ነው። የቦኮሃራምን ችግር ያልፈታ ሰውዬ ለኢትዮጵያ መድኃኒት ሆኖ ሲመጣ እጅ በአፍ ያስጭናል። በመንግሥት በኩል የሚደበቅ ምንም ነገር የለም ….. ኦባሳንጆ እውነትን እንዲያፈላልጉና መረጃ እንዲሰበስቡ የመቀሌውን ጉዞ አመቻችተናል ! ብሏል የኢትዮጵያ መንግስት፤ ኦባሳንጆ ከመቀሌ ተመልሷል ፤ ዛሬ አማራና አፋር ክልል ያሉ ባለስልጣናትን ሊያናግር ይበራል። አዲስ አበባ ያሉትን ማናገሩን ነግሮናል። መንግስት የኦባሳንጆን የመፍትሔ ሀሳብ በጉጉት እንደሚጠብቅም ነግሮናል። በሁለቱም ወገን በኩል የእሳቸው የማደራደር ጥረት ተቀባይነት አግኝቷል። ለማሸማገል እየሞከሩ ካሉት የፌደራል መንግሥት ወይም የህወሓት አመራሮች ዘንድ ሸምግልናውን አልቀበልም ያለ ወገን አለ? ተብለው የተጠየቁት ኦባሳንጆ፤ “የአፍሪካ ሕብረት ሰላም ለማምጣት፣ ንግግርን ለማስጀመር እና ደኅንነትን ለማስጠበቅ ልዩ መልዕክተኛ መሰየሙን ሁሉም ወገን በበጎ ነው የተቀበሉት” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ድርድር ጥሩ ነው፤ ተደራድሮ መስማማትም ይበል የሚያሰኝ ነው። ድርድርን በተመለከተ የሕወሓት የኃላ ታሪክ ስናጤነው ግን ድርድር ከሕወሓት ጋር ለመጪው ጊዜ አደጋ ከመፍጠር ውጪ ምንም ፋይዳ የለውም። መንግስት መደራደሩን ስንደግፍ ከሕወሓት ጋር ያለው የድርድር ሂደት ኝ ውጤቱ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ይገባል። ደግሜ ለማስታወስ ያሕል ሕወሓት የድርድር ታሪኩ በራሱ ተንኮል የቆሸሸ ነው። አሜሪካኖቹም ቢሆኑ እያየነው ያለነው ነገር ለሕወሓት እያደሉ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መንግስት በመስታወት ራሷን ነብር አድርጋ የምታይ ደካም ድመት ከመሆን ይውጣ። (ምንሊክ ሳልሳዊ )

የሆነ ያላየነው ጎዶሎ ነገር አለ !  ምንሊክ ሳልሳዊ መንግስት ራሱን ይፈትሽ ! ….. የካድሬው ጩኸት ያስቁመው። መንግስት በመስታወት ራሷን ነብር አድርጋ የምታይ ደካም ድመት ከመሆን ይውጣ። ዳይ ወደ ተጀመረው ድርድር ………….. የሆነ ያላየነው ጎዶሎ ነገር አለ። መንግስት ከጠነከረ ድክመቶቹን ካስወገደ እኮ ሕወሓት ተራ ጉዳይ ነች፤ ውስጡን ሊፈትሽ ይገባል፤ ሕወሓት እየሮእጠች ደሴ ደጃፍ የደረሰችው እኮ በውስጥ ድክመት ነው። መንግስት ድክመቱን እንዲያስወግድ ጫና ማድረግ አለብን። መንግስት ድክመቱን ላለማመን ሲግደረደር ሕወሃት የጀመረውን ሀገር የማውደምና የማፍረስ ተልዕኮ በመደበኛ ወታደራዊ አደረጃጀት ብቻ መቀልበስና መቅበር አይቻልም ሲል በመግለጫው ነግሮናል ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትግራዩን ጦርነት መለማመጃችን ነው ብለው ነበር፤ መለማመድ አይደለም ሕወሓት እየገፋ ደሴና ኮምቦልቻ በስማቸው እየፎከረ ደብረብርሃን ላይ እየዛተ ነው። በመደበኛ ወታደራዊ አደረጃጀት ብቻ መቀልበስና መቅበር አይቻልም ማለት ግን ተስፋቢስነትን ያሳያል። መንግስት በመስታወት ራሷን ነብር አድርጋ የምታይ ደካም ድመት ነው የመሰለኝ። በየመግለጫዎቹ ሲፎክር ከርሞ ዛሬ ላይ ሌላ የዝመቱ ጥሪ እያስተላለፈ ነው። ይህ ሁሉ ችግር የመነጨው መንግስት መረጃዎችን በመደበቅ ራሱን ከፍ አድርጎ ከመጀመሪያው ማውራቱ ሲሆን ሌላው ደግሞ መቀሌን ለቆ ሲወጣ ራያ ላይ በተጠንቀቅ መቆም ሲገባው የዛሬውን ጥሪ የዛኔ ማቅረብ ሲገባው እያፈገፈገ ድክመቱን ማሳየቱ ነው። ዳይ ወደ ድርድር ….. ሰሞኑን ሕወሓትና ኦነግ ሸኔም ስለ ድርድር መግለጫዎችን እያወጡ ነው። ለጥቂቶች ድክመት ተብሎ ሕዝብ ማለቅ የለበትም። መንግስት የጦርነት ሸክሙ ከብዶታል። ካድሬዎቹን አደብ ያሲዛቸውና ወደ ድርድር ይዝለቅ በቃ ድክመቱን መሸፋፈን አያስፈልግም።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ወደ መቀሌ የሚሄድ የአለም የምግብ ድርጅት ትራንስፖርት በአፋር ሕዝብ ቁጣ ቆመ

የአፋር ሕዝብ ጀግንነት ቀጥሏል! ወደ መቀሌ የሚሄድ የአለም የምግብ ድርጅት ትራንስፖርት በአፋር ሕዝብ ቁጣ ቆመ! ሕወሓት በአፋር ላይ የሚያደርገው ወረራ ካላቆመ አንዳች ምግብ በአፋር በኩል ሊያልፍ አይገባም። – የክልሉ ህዝብ የወሰደው እርምጃ ተገቢና ትክክለኛ ውሰኔ ነው። ምክንያቱም የአፋር ህዝብ በገፍ በየቀኑ በመድፍና በታንክ እየተገደለም ቢሆንም የትግራይ ወንድሙ እንዳይቸገር እየሞተም በሩን ክፍት አድርጎ የጎርብትናው ሐቅ በመወጣት በተግባር አሳይተዋል። – ይሁን እንጂ ህፃናት በገፍ በህወሓት አረመኔያዊ ቡዱን ስገደሉ ፣ ስፈናቀሉ ስወረሩ የትግራይ ኤሊቶች እና አክቲቪስቶች ምንም እንዳልተፈጠረ አድርገው ወንበዴ በርታ አይነት ሆነዎ ስያልፉ ተስተውለዋል። በንፁሃን ደም የሰከረው አረመኔ ህወሃት ግን ያለፈው ሳይበቃልው ትናንት በጭፍራ ግንባር ላይ 30 የሚሆኑ ንፁሃን በመግደል ጭካኔውን በተግባር አሳይቷል። – ስለዚህ ህወሃት አፋርን እየጨፈጨፈ የወሎ ገበሬዎችን ከቤት ንብረቱ እያፈናቀለ በዋነኝነት ለሽብር የሚጠቀምበትን WFP በአፋር ስንቅ መንገድ አድርጎ በጦርነት መግፋቱ የፍርሃት አድርጎ የተመለከተው ይመስላል። ዛሬ ግን እነዚህ የጁንታ የጥፋት ተልዕኮ አስፈፃሚዎች የሚልኩት እርዳታ ወደመቀሌ ጉዞ ። ከአፋር ጠቅልሎ እስካልወጣ ብሎም በአፋር ላይ የሚያደርገው ወረራ ካላቆመ አንዳች ምግብ በአፋር አድርጎ ልያፍ አይገባል። እርምጃው ተገቢ ነው።  
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የመንግስት ካድሬዎች – ስንጥቅ ቅሎች ውሃ ብትጨምርባቸው ሲያፈሱ ይውላሉ ። – ምንሊክ ሳልሳዊ

ምንሊክ ሳልሳዊ – ኢትዮጵያና ሕዝቧ ሶስት ጠላቶች አሏቸው፤ ጠላቶቻቸው ለሐገርም ለወገንም የማይበጁ ውሸታም፣ አስመሳዮች፣ አደርባዮች፣ አማሳኞች፣ ራስ ወዳዶች፣ ሰባራ ቅሎች፣ አሾክሻኪውች …… የመሳሰሉት ናቸው፣ የኢትዮጵያና የሕዝቧ ጠላቶች ፦ አንደኛ – ሕወሓትና የዘር ፖለቲካው ጀሌዎቹ ሁለተኛ – ኦነግ እና ግድያ አስፈጻሚዎቹ ሶስተኛ – የመንግስት ካድሬዎች ( በተለይ ነባር ካድሬዎቹ PC/ Parasite Cadres/ ጥገኞች የሚሏቸው ወዶገብ አዳዲስ ካድሬዎች) ጠላትማ ምንጊዜም ጠላት ነው አስቀድሞ መግደል አሾክሻኪውን ነው ! የተሰነጠቀ ቅልን ለማወቅ ውሃ ጨምርበት! በየማሕበራዊ ሚዲያ የተኮለኮሉ የመንግስት ካድሬዎች በማይረባ ነገር ያሞጋግሱሃል በማይረባ ነገርም ይዘረጥጡሃል፤ ለሕዝብና ለመንግስት የሚጠቅሙ መረጃዎችንና ግለሰቦችን ሲያጣጥሉ ይውላሉ። ለነሱ ጭፍን ድጋፍና ጭብጨባ ትልቁ መናኸሪያቸው ነው። ለነሱ ከባለስልጣናት ጋር ማውራት ባለስልጣናትን ማወቅ የጉራቸው ዋና መሰረት ነው። ከባለስልጣናት ጋር ፎቶ መነሳትማ መኮፈእሻቸው ነው። ስንጥቅ ቅሎች ውሃ ብትጨምርባቸው ሲያፈሱ ይውላሉ ። አንደኛውና ሁለተኛው ላይ የተጠቀሱት ጠላቶች በከፍተኛ ደረጃ ጠላትነታቸው የተረጋገጠና በግልጽ ሽብርን የሚፈጽሙ አሸባሪ ድርጅቶች ናቸው። በሶስተኛ ደረጃ የሚገኙ ማሰቢያቸው በጥቅም የተደፈነ በራሳቸው የማይተማመኑና በመደገፍ ብቻ መኖር ይቻላል የሚሉ ጭፍን አስተሳሰብ ያላቸው ናቸው፤ ወዶ ገብ ካድሬዎች መልካምና ክፉን መለየት ስለማይችሉ ልክ የሐሰት ወሬና የከረፋ ሪፖርት እንደሚያሰራጩት የመንግስት ሚዲያዎች ለሐገርና ለሕዝብ አደገኛ ናቸው። በግልጽ የምታውቀውን ጠላትህን ትዋጋዋለህ፤ አስመሳዩን፣ ውሸታሙን ተሽሎክላኪውን፣ አደርባዩም ካድሬ ደግሞ እየተጣጠፈ አንዳያመልጥህ ልትጠነቀቅ ይገባል። ጠላትማ ምንጊዜም ጠላት ነው አስቀድሞ መግደል አሾክሻኪውን ነው ! ትላንት ለዲሞክራሲና ለነጻነት ነው ስንታገል የነበረን ሲሉ የነበሩ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ስልጣን በዕውቀት ላይ ሲመሰረት ለሐገር እድገት በበለጠም ለዜጎች ደሕንነትና ሰላም ዋስትና አለው።

ምንሊክ ሳልሳዊ ፤ ስልጣን በዕውቀት ላይ ሲመሰረት ለሐገር እድገት በበለጠም ለዜጎች ደሕንነትና ሰላም ዋስትና አለው። ድጋፍና ተቃውሞም በዕውቀት ላይ ሲመሰረት ይገባል። ከትርምስ፣ ከሴራ ፖለቲካ፣ ስልጣን ከማሯሯጥ መውጣት አለብን ። የነእከሌን ብሔር ሊከፋው ይችላል፣ የነእከሌን ሐይማኖት ሊያስኮርፍ ይችላል፣ የነከሌን ፓርቲ ለንቦጭ ያስጥላል፤ እነእከሌ የፖለቲካ ታማኛችን ናቸው፣ እነእከሌ መረጃ ሲሰጡን ነበር ወዘተረፈ እየተባሉ በዕውቀት ሳይሆን በእከክልኝ ልከክልህ የሚሰጡ ሹመቶች ለዕድገትና ለሰላም እንቅፋት ሲሆኑ ትልቅ የፖሊሲና የስትራቴጂ ክፍተት ስለሚፈጥሩ አደጋው የከፋ ነው። አሰልቺና በብድር ላይ ብቻ የተመሰረተ እቅድ እያቀደ ካለአቅሙ የሚኮፈሰው የአፈጻጸም ሸለምጥማጥ የሆነብን ካለ ዕውቀቱ የተሾመው ባለስልጣን ነው። ካለፈው ልንማር ይገባል ብለን ደጋግመን የምንናገረው ለዚሁ ነው። ላለፉት አስርት አመታቶች በዘር ፖሊሲ ላይ በተመሰረተ ሕገመንግስት ላይ በሚሰጡ የብሔርና የሃይማኖት ተዋፅዎን መሰረት ያደረጉ ሹመቶች በሐገር የፖለቲካና የኢኮኖሚ እድገት ላይ ውድቀትን በማህበራዊው መስክም ሰላምን እያሳጡን መሆናቸውን ዛሬ ድረስ እያየን ነው። ካለዕውቀት የሚሰጡ ሹመቶች ባንዳዎችንና ቅጥረኞችን ለመፍጠር መንገድ ይከፍታሉ። በዚህም የተነሳ የፖለቲካና የኢኮኖሚ አሻጥሮችም ይስፋፋሉ። ስልጣንን መከታ አድርገው የዜጎችን ሰላምና ደሕንነት የሚያበላሹ በርካቶቹ በዕውቀት ላይ ባላቸው ችሎታ የተሾሙ ሳይሆን በብሔራቸው፣ በሐይማኖታቸው አሊያም በፖለቲካ ታማኝነታቸው የተሾሙ ናቸው ። በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ሹመት ካለ የመንግስትን ፕሮጀክትንም ይሁን ጥናት ወደ ተግባል ለውጦ የሚያሳካ የሰው ሐይል ከመፍጠርም በተጨማሪም ካሁን ቀደም መንግስት የሚያለቃቅስበትን የአፈፃፀም ችግርን ይቀርፋል። በመንግስት ያፈፃፀም ሂደት ላይ ጋሬጣ በመሆን ለከፍተኛ ውድቀትና ለሙስና መስፋፋት አስታውፆ ያበረከቱት ካለዕውቀታቸው የተሾሙ አመራሮች
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጥብቅ መረጃዎችን በያዘው የፍትሕ መጽሔት የምርመራ ሪፖርት መደናገጡ ተሰምቷል።

ባለፈው ቅዳሜ የወጣቸው የፍትሕ መጽሔት የኢትዮጵያ አየር መንገድን አስመልክታ ይፋ ባደረገችው አንድ Dollar ብቻ ! በሚለው ጥብቅ መረጃዎችን የያዘው የተመስገን ደሳለኝ የምርመራ ሪፖርት ላይ እየር መንገዱ የተደናገጠ ምላሽ ማስፈሩ አነጋጋሪ ሆኗል ። አየር መንገዱ የመጽሔቱን መውጣት ተከትሎ በሕግ ስም ለማስፈራራት መሞከሩና መደናገጡ በይፋ ያወጣው መግለጫው አሳብቆበታል። ፍትሕ መጽሔት በዚህ ተጠየቅም፣ ከባድ የሳይበር ጥቃት ስለመፈጸሙ፣ አውሮፕላን በአንድ ዶላር ስለመከራየቱ፣ ቁጥራቸው የበዛ ተጋሩ ሠራተኞች ስለመኮብለላቸው… በምርመራ ዘገባ የተጠናከሩትን ጨርፋ ለማየት ሞክራለች ። በሪፖርቱም ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ረዳት አብራሪው ፍፁም እሸቱ አሰቃቂ ታሪክን ጨምሮ በአየር መንገዱ ውስጥ የሚፈፀሙ አስተዳደራዊ በደሎችን በመጽሔቷ ላይ በወጣው ምርምራዊ ሪፖርት ተዳሷል። ይህን ሪፖርት ተከትሎ ሌላው የራሱን አስተያየት የሰጠው Ethiopian Airlines Group Basic Trade Union  ፍፁም ለምን ሞተ!!!!??? በሚል ርዕስ በፍትህ መፅሔት ታትሞ የቀረበው ተምርመራ ሪፖርት ፤ ከሁለት አመታት በፊት ራሱን ከደንበል ህንፃ ላይ በመወርወር ራሱን ያጠፋውን የውዱን ባለደረባችንን የረዳት አብራሪ ፍፁምን አሟሟት ምክንያቶች ራሱን ከማጥፋቱ በፊት ከፃፈው ጋር አጋልጧል። ሲል የአየር መንገዱን አስተዳደራዊ በደሎችና ጫናዎች ይፋ አድርጓል ። የአየር መንገዱ የሰራተኞች ማሕበር ( EAGBTU )በዚሁ መግለጫው አብራሪ ፍፁም ፤ ረሱን ያጠፋበት ምክንያት ራሱን እንደ ሁለተኛ መንግስት በሚያየው በአየር መንገዱ አምባገነን ፣ ህገወጥ እና ጋጠወጥ አስተዳደር በደረሰበት በደል እንደሆነ ምርመራው አረጋግጧል። በኢትዮጲያ አየር መንገድ ውስጥ ያለው ግፍ ፣ በደል እና በስልጣን መባለግ ያለፈው ፖለቲካ ተቀጥላ ሆኖ አሁንም ቀጥሏል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መንግስት ከሕወሓት ጋር በከፊል ድርድር መጀመሩ ምን ያሕል አዋጪ ነው ? ( ምንሊክ ሳልሳዊ )

መንግስት በከፊል ድርድር መጀመሩ ምን ያሕል አዋጪ ነው ? ሕወሓት ምን ያሕል ለፖለቲካ ታማኝ ነው ? ድርድር ለሕወሓት ጊዜ መግዣና የማዘናጊያ ስልት ነው ! ( ምንሊክ ሳልሳዊ ) May be an image of 2 peopleወደ ዕውነታው ስንመጣ ፦ ለሰላም ሲባል የማይከፈል መስዕዋትነት የለም። ጦርነት ለማቆምም መደራደር፣ በከፊል ለትግራይ የተለቀቁ መብራትና ኢንተርኔትን በሙሉ ለመልቀቅ መደራደር በጥቅሉ ድርድር በተለይ ከሕወሓት ጋር ማድረጉ ምን ያሕል አዋጪ ነው ? እንደ ሕዝብ መንግስትን ለመጠየቅ እንገደዳለን። ግፋ ዝመት ታጠቅ ተኩስ በለው ሲሉ የነበሩ ከፍተኛ ሚኒስትሮች ሰሞኑን ስለ ሰላምና ድርድር በየማሕበራዊ ድረገፆች ሲጽፉ እያስተዋልን ነው፤ ሰላምን የሚጠላ የለም፤ ከሕወሓት ተፈጥሮ አንጻር ግን መመዘን ግድ ይላል ። ሕወሓት በተፈጥሮው በድርድር ላይ ያለው አቋምም ይሁን ድርድርን ተከትሎ በተግባራዊነቱ ላይ ያለው አሻጥር የሚታወቅና በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው። ሕወሓት ለሕዝብ በሚያደሉ ፖለቲካዎች ላይ ታማኝ አይደለም። ለጊዜው ለማዘናጊያና ጊዜ ለመግዣ የሚጠቀምበት ስልት ነው። ሕወሓትን የሚያውቁ ሰዎች የምንስማማበትና ሕወሓት በጉያው ሆነውም የነበሩ ተጎጂዎች እንደሚመሰክሩት የሕወሓትን ታሪክ ወደ ኋላ ዞር ብሎ ማየቱ ተገቢ ነው፡፡ ድርጅቱ በታሪኩ ይህ ነው የሚባል በሰጥቶ መቀበል ላይ የተመሠረተ የድርድር ታሪክ የለውም፡፡ ሕወሓት በድርድር የፈታው ችግር ኖሮ አያውቅም፡፡ ድርጅቱ ወደ በረሃ ከወረደ 47 ዓመታት አለፈዋል፡፡ እስከዛሬ ግን በድርድር የፈታው ምንም ዓይነት ችግር የለም፡፡ በረሃ እያሉ ኢዲኅ፣ ጥራናፌት፣ ኢሕአፓ ወዘተ… ከሚባሉ ድርጁቶች ጋር ተገዳድለው ተላልቀው ነው የጨረሱት፡፡ ከዚያም ቀጥሎ የኦነግ ኀይል ጋር፤ ከሻዕቢያ ጋር ልዩነቶቻቸውን የፈቱት በመሣሪያ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያ አሜሪካን ሲቪክ ካውንስል የሲኤንኤን ዘገባ በመቃወም ግምገማና የሕግ ምርመራ እንዲደረግበት ይጠይቃል ተባለ

The Ethiopian American Civic Council የኢትዮጵያ መንግስት ባለሥልጣናት በትግራይ ተወላጆች ላይ የዘር ማጽዳት ድርጊቶችን ፈጽመዋል በሚል ሲኤንኤን ያስተላለፈው ዘገባ ራሱን የቻለ ግምገማና የሕግ ምርመራ እንዲደረግለት የኢትዮጵያ አሜሪካ ሲቪክ ካውንስል ጥሪ እያቀረበ ነው። አሜሪካ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይህንን መዘዝ እና ብዙ ኢትዮጵያውያን ያላቸውን ፍርሃት አቅልለው ማየት የለባቸውም ያለው መግለጫው ካውንስሉ ለሲኤንኤን ኦፊሴላዊ ደብዳቤ መላኩን ጠቁሞ የካውንስሉን የበላይ ዮሴፍ ተፈሪን ጠቅሶእንዳለው ዘገባው የማያስተማምንና ምንም ማረጋገጫ የሌለው ግምታዊ ነው ብሏል። በዘገባው በሱዳን ተገኙ የተባሉት አስከሬኖች እውነታውን የሚያረጋግጥ የፎረንሲክ ባለሙያዎች ስም ዝርዝርም ይሁን በቂ አሳማኝ ማስረጃዎች ባልተዘረዘሩበትየሕግ ባለሙያዎች ያላረጋገጡት ስለሆነ የሕግ ምርመራ እንዲደረግስራ መጀመሩ ታውቋል። የኢትዮጵያ አሜሪካን ሲቪክ ካውንስል እና አድቮከሲ ኔትወርክ ሰሞኑን CNN የተባለው ሚዲያ ያወጣውን የሀሰት ዘገባ በመቃወም በመላ አለም ለሚገኙ ጋዜጦች ዘገባው እውነትን ያላማከለ እንዴውም በዘገባው ላይ የህወሃት አባል የሆነን ሰው በማቅረብ የጋዜጠኝነት ሙያን አንድ የሽብርተኛ ቡድን ለማገዝ ሲባል አራክሰዉታል ሲል ተቃውሞውን አሰምቶል። በዚህም ዝም ሳይል ይቅርታ ካልጠየቀ ካውንስሉ ያገኘውን መረጃ ይዞ በህግ አግባብ የሚጠይቅ መሆኑን አስስቧል። ካውንስሉ ያወጣውን መግለጫ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ያገኙታል። https://miniliksalsawi.medium.com/ethiopian-diaspora-calls-for-independent-review-of-cnn-report-bbdb769a75b6  
Posted in Amharic News, Ethiopian News

እስክንድር ነጋ ….. እውነትን መካድ ፍትሕን መካድ ነው ! – – -ሁላችንም ስለ እውነት ልንቆም ይገባል!

እውነትን መካድ ፍትሕን መካድ ነው ! – – -ሁላችንም ስለ እውነት ልንቆም ይገባል! ያልደፈረሰ ነጭ እውነት …. !!!  – ምንሊክ ሳልሳዊ ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ እውነት እያወራን ነው ። ….. ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ ፍትህ እያወራን ነው ። …. ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ እምነት እያወራን ነው። ….. ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ ዲሞክራሲ እያወራን ነው ። ….. ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ ፕሬስ ነጻነት እያወራን ነው። ….. ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ ሰብዐዊ መብት እያወራን ነው። ….. ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ ነፃነት እያወራን ነው ። ….. ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ ፅናት እያወራን ነው ። ….. ስለ እስክንድር ነጋ ስናወራ ስለ ኢትዮጵያ እያወራን ነው ። ዛሬ ላይ ለቆምንበት ነፃነትና ለውጥ የእስክንድር ነጋ ትግሎች የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ። እስክንድር ነጋ በግፍ ነው የታሰረው የዘረኞች ወንጀል ማመጣጠኛ ነው የምንለውም ለዚህ ነው። ትላንትና ለቆመለት ሕዝባዊ አላማ ዛሬም ላይ ሳይዛነፍ የቆመ ሰው ቢኖር እስክንድር ነጋ ነው። ከሴራና ከአሻጥር ፖለቲካ የፀዳ የተለየ ሰው ቢኖር የትውልዱ የነጻነትና የብርሐን ቀንዲል ቢኖር እስክንድር ነጋ ነው። ካለወንጀሉ ከነባልደረቦቹ በወሕኒ የሚማቅቀው እስክንድር ምንም አይነት ወንጀል የሌለበትና በዘረኞች ሴራ የታሰረ ንጹህ ኢትዮጵያዊ ነው። ድንጋይ ሳይወረውሩ፣ ጠበንጃ ሳያነሱ፣ ሰላማዊ ትግል ስለታገሉ ብቻ መንግስት የዐይናቸው ከለር ስላስጠላው የባልደራስ መሪዎችን ወደ ወሕኒ መወርወሩ የታሪክ ተወቃሽ ሆኗል። ትዝብትን አትርፏል ። መንግስት ካለአግባብ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ወለጋ የደም መሬት – የመንግሥታዊ መዋቅር ሽፋን ያለው የዘር ማጥፋት

ሰሞኑን ኦነግ ሸኔና የሚረዳው የመንግስት መዋቅር አማራውን ለመጨፍጨፍ እንደ ዘዴ መጠቀም የያዙት የአማራ ልዩ ኃይል ወለጋ ገብቷል የሚል ሐሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ነው። ድርጊቱ የተፈፀመው ሟቾቹ ራሳቸውን መከላከል በማይችሉበት ሁኔታ ሲሆን አሁን ድረስ የት እንደገቡ ያልታወቁ መኖራቸውንና ይህንን ጥቃት ለሸሹ ሰዎችም የደረሰላቸው እንደሌለ ከቦታው የሸሹ የአይን እማኞች ይናገራሉ። ምንሊክ ሳልሳዊ – ወለጋ የደም መሬት – የንፁሃን መጨፍጨፊያ ማእከል – በማንነቱ አማራ ተለይቶ የሚጨፈጨፍበት አኬልዳማ ……. ጭፍጨፋው በታቀደ መልኩ አንድን ማንነትና ሐይማኖት የለየና በሁለት ቤተክርስቲያናት ሥርዓተ ጸሎት በማድረስ ላይ በነበሩ ሰዎች ላይ የተፈጸመ ነው። ግድያው በኢትዮጵያ ውስጥ የዘር ፍጅት እየተካሄደ መሆኑን ያረጋግጣል። የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የፈጸሙትን ጭፍጨፋ ፌዴራል መንግስቱን ለማስጠላት ያቀደ የመንግሥታዊ መዋቅር ሽፋን ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው። May be an image of candle, fire and textኢትዮጵያዊ ሁሉ ትኩረቱ ሁሉ ሰሜን ኢትዮጵያ ላይ በሆነበት ሰዓት በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ወለጋ ፤ በኪረሙ ወረዳ ህፃናት ፣ ሴቶች ፣ ካህናት ፣ መነኮሳት ፣ አረጋዊያን ፣ ሙሉ የቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ባጠቃላይ 300 (ሦስት መቶ) የሚሆኑ አማሮችን እጅግ በሚዘገንን እና አረመኔያዊ በሆነ መንገድ በቤታቸው ውስጥ በማቃጠል ፣ በማረድ በዚሁ አካባቢ የሚንቀሳቀሰው ታጣቂ የኦሮሞ ኃይል ድርጊቱን መፈጸሙ ታውቋል። ከነዚህም ውስጥ 72ቱን መቅበር የተቻለ ሲሆን ሌሎች በየጫካው ያልተነሱ አስከሬኖች እንዳሉ ፤ በመቶች የሚቆጠሩ የቆሰሉና ህክምና ያላገኙ ፤ ከ10,000 በላይ የሚሆኑ የተሰደዱ ፤ ቤቶችና ቤተክርስቲያናት እንደተቃጠሉ ፤ በአጠቃላይ በአካባቢው ባለው አማራ ላይ ከፍተኛ የዘር ፍጅት እየተፈፀመበት እንዳለ ከአካባቢው
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአሜሪካ ፖለቲከኞችን ማመን ቀብሮ ነው፤ በተለይ ዲሞክራቶችን !

የአሜሪካ ፖለቲከኞችን ማመን ቀብሮ ነው፤ በተለይ ዲሞክራቶችን ! በአደባባይ የተጋለጠው የአሜሪካ የእርዳታ ድርጅት ለሕወሓት አለመገብኩም ሲል ለማስተባበል ሞክሯል። አሜሪካኖች ካሁን ቀደም በተለያዩ አገራት በእርዳታ ሰበብ ታጣቂዎችን ሲያደራጁና ሲረዱ እንደነበር እሙን ነው፤ ለማስረጃ ያሕል በደርግ ዘመን በወርልድ ቪዥን አማካኝነት ወያኔን በስፋት ሲያስታጥቁና ረHእብንና ግጭትን ተገን አድርገው በርካታ ወንጀሎችን ሲፈፅሙ እንደነበር እይረስም፤ ይህም ያሁኑ የአሜሪካ እርዳታ የዚሁ በእርዳታ ስም የሚደረግ የሕወHአት የሽብር ድርጊትን የማጠናከር አንዱና ዋነኛው አካል ነው። አሜሪካኖች አይተኙልንም፣ እድገታችንን አይፈልጉትም፣ ጉዟችንን በአጭሩ ለመቅጨት ወደኃላ አይሉም ፤ ለዚህ ደግሞ የውስጥ ብጥብጣችንን ሊጠቀሙና የበለጠ አደህይተውን የነሱ ጥገኛ እንድንሆን ይፈልጋሉ። አብዛኛውን መንገድ የሚተቀሙት ሕዝብን ለመርዳት ሳይሆን ክልሉን ለማተራመስ ለሚፈልግ አሸባሪ ቡድን ተሽቀዳድመው ያደርሳሉ። እያየን ያለነውም ይህንን ነው። በተደጋጋሚ እንደምንናገረው ድርጅቱ የተቋቋመውም ግጭት ባለባቸው አከባቢዎች ሰርጎ በመግባት በእርዳታ ስም ግጭቱን ማስፋፋትና ከፍተኛ መዋለ ንዋይ በማፍሰስ ለአሜሪካ ጥቅም የሚሰሩ እርጉም አምባገነኖችን ስልጣን ላይ ማውጣት ነው። የድርጅቱ ባለስልታናት በሰብዐዊ ድጋፍ ስም ኢትዮጵያ ሲመጡ የሚሰሩትና ደርሰው ወደ ዋና ቢሯቸው ሲመለሱ የሚሰሩት ስራ የተለያይ የሚናገሩትም ንግግር አዘናጊና የማጭበርበር መንፈስ ያለው አደገኛነትን የተላበሰ ነው። ሰሞኑን ሳማንዛ ፓውር ምን ያህል እየተገለባበጠች ልታዘናጋንና ልታጭበረብረን መሞከሯ የትዊተር ገፆቿ ምስክሮች ናቸው። የአሜሪካ የእርዳታ ድርጅት እየረዳ ያለው ምስኪኑን የትግራይ ሕዝብ ሳይሆን የሕወሓትን የሽብር ቡድን ነው። የኢትዮጵያ መንግስትን በመወንጀል የሽብር ቡድኑን ያበረታታሉ። ሕዝብን የወደዱ መስለው ሕዝብን ያስገድላሉ። በቅርቡ በውጊያ ላይ ከተማረኩ አሸባሪዎች የተገኙ የምግብ ቁሳቁሶች
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ፊልትማን የኢትዮጵያን ሉዓላዊትን የሚያከብር የዲፕሎማሲ ጥበብ እንዲከተሉ እንመክራለን።

ፊልትማን የኢትዮጵያን ሉዓላዊትን የሚያከብር የዲፕሎማሲ ጥበብ እንዲከተሉ እንመክራለን። የጆ ባይደን ልዩ መልዕክተኛ በኢትዮጵያ ጦርነቱን ለማስቆም እንደለመዱት አይነት ታክቲክ ለመጠቀም ቢሞክሩ ከኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት እንደሚቀያየሙና እንደለመዱት አኩርፈው እንደሚመለሱ ሊያውቁት ይገባል። ፊልትማን ዲፕሎማሲያዊ መንገድን በመጠቀም እንዲሁም የኢትዮጵያና የአሜሪካን ታሪካዊ ግንኙነትና የመንግስትን መመሪያና ደንቦች ባገናዘበ መልኩ በዲፕሎማሲ መስመር ከኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት ጋር ስምምነት ላይ መድረስ ይገባቸዋል፤ ልዩ ልዑኩ በማስፈራራት፣ በማዕቀብ ወይንም በወታደራዊ ጣልቃ ገብነት አሊያም በየመንና በሊቢያ እንዳደረጉት ኢመደበኛ ጦርን ለመርዳትና ለማሰማራት መሞከርም፣ ማሰብም እንደማይችሉ ልናሳውቃቸው እንፈልጋለን። የአሜሪካ መንግስት ጉዳዩን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ካለምንም ጣልቃ ገብነት ለመጨረስ ብቁ መሆኑን ከማረጋገጥ ውጪ በጅቡቲ አሊያም በሱዳን የጦር መሳሪያም ይሁን ወታደሮችን ለማስገባት የሚያደርገውን ሐሳብ ሊያቆም ይገባል። የሕወሓት የሽብር ቡድን መሪዎችን ለማግኘትም ወደ መቀሌ ካልተጓዝኩ ብሎ የመንግስት ባለስልጣናትን ማስቸገር እንደማይቻል ማወቅ አለበት። ፊልትማን ካሁን ቀደም በአፍጋኒስታን፣ በሶሪያ፣ በየመንና በሊቢያ የሰሩትን ስሕተት ኢትዮጵያ ላይ ለመድገም ማሰብ ሞኝነት ነው፤ ካለፉት ጣልቃ ገብተው ከበጠበጡት ሐገራት ትምሕርት ሊወስዱ ይገባል። በሶሪያ፣ ኢራቅ፣ ሊቢያ፣ ሊባኖስ፣ የመን፣ ሶማሊያ ወዘተ አሜሪካ ጣልቃ ገብታ ስርዐት አልበኝነትን ከማስፈን ውጪ የተረጋጋ መንግስትን አልመሰረተችም፣ ሕግን ስታስከብር ይሁን ስምምነት ስታመጣ ካለመታየቷም በላይ አልቃይዳ፣ አይሲስና አልሸባብ ተዋልደው እንዲራቡ እንዲስፋፉ ከማድረግ ውጪ ምንም አልፈየደችም። አሜሪካ በአፍጋኒስታን በሶማሊያና ጣልቃ በገባችባቸው አገሮች የገጠማትን ውርደትና ሽንፈት ልታጤነው ልትማርበት ይገባል። ኢትዮጵያ የባህር ኃይል እንዳይኖራት ፈረንሳይን ብድር እንድጸርዝ ያግባባችው አሜሪካ በጅቡቲ በኩል ጦሯን ለማስገባት እሞክራለሁ ብትል አሊያም ተዘዋዋሪ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አሜሪካ ወያኔን ዳግም ወደ ስልጣን ለመመለስ የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ መቀጠሏዋን የፌልትማን ወደ ቀጠናው የሚያደርጉት ዳግም ጉዞ ምስክር ነው።

አሜሪካ አሁንም አልተኛችልንም ፤ አሜሪካንን ማኮላሸት የምንችለው በጋራ ተባብረን ስንቆም ብቻ ነው። አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምታደርገውን ጫናና ተፅዕኖ ስራዬ ብላ ተያይዛዋለች፤ ከውስጥ ጠላቶቻችን ጋር ተባብራ ተላላኪና ሲጠሩት አቤት ሲልኩት ወዴት የሚል መንግስት ለማቆም እንዲሁም የሕዳሴው ግድብ ስም ብቻ ሆኖ እንዲቀር ለማድረግ የውስጥ ፖለቲካችንን እንደመሳሪያ ተጠቅማ እየሰራችብን ነው። የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ጄፍሪ ፌልትማንን በድጋሚ ወደኢትዮጵያ ሊልኳቸው መሆኑ ተሰምትዋል። ባለፈው ግንቦት መጥቶ አኩሩፎ የሄደው ፌልትማን ተመልሶ ሊመጣ መሆኑንና ጅቡቲንና ኢምሬትን ሊጎበኝ መሆኑ ታውቋል ። ጅቡቲንና ኢምሬትን የሚጎበኘው በኢትዮጵያ ጉዳይ መሆኑን ነጋሪ አያስፈልገንም። ፕሬዝዳንቱ ልዩ መልዕክተኛ ፌልትማን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ በዚህ ወሳኝ ወቅት ጥያቄ ማቅረባቸው ያለምክንያት አይደለም። ጅቡቲን የፈለጉት በሱዳን በኩል ብዙም አልመች ያላቸውን ጉዳይ በጅቡቲ በኩል ለመፈጸም ያላቸውን ፍላጎት እንዲሁም በሶማሌና አፋር መካከል ያለውን ግጭት ኢትዮጵያን ለመበጥበጥ የሚያመቻቸውን ስልት ለመስራትና ጅቡቲ ለሕወሓት አስፈላውን ትብብር የምታደርግበትንና አሜሪካንን የምትታዘዝበትን መንገድ ለመቀየስ ሲሆን የፕሬዝዳንቱ ልዩ መልዕክተኛ ፌልትማን ከዚህ ቀደም በተለያዩ አገሮች የፈጸመው ደባና ወንጀል በቂ ምስክር ነው። ፌልትማን ከሁን ቀደም በኢምሬት ባደረጉት ቆይታ የኢትዮጵያ ጦር ከትግራይ እንዲወጣና አሁን ላይ የተከሰተው የሰሜን ኢትዮጵያ ቀውስ በተለይ አማራና አፋር ላይ እየተደረገ ያለው ግጭት እንዲመጣ የራሱን ሚና ተጫውቷል።ፌልትማን የኢትዮጵያ ወዳጅ በሆኑ በኢምሬት ባለስልጣናት በኩል ኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር ያደረጉት ሙከራ ስለተሳካላቸው በድጋሚ ድርድር ለሚለው ጉዳይ ሌላ ጫና እንዲፈጠር ወደ ኢምሬት አጋሮቻቸው ይሄዳሉ። ሁሉም ወገኖች ወደ ድርድር ጠረጴዛ በአስቸኳይ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አብነት ገብረመስቀል ሚድሮክ የተሰኘውን ድርጅት መልቀቃቸው ተሰምቷል።

Abinet Gebremeskel Departs MIDROC, “Sacked” or “Resigned” ከሶስት አስርተ አመታት በላይ ሼህ አላሙዲን ቀኝ እጅ የነበሩት እና ሚድሮክን በበላይነት ያስተዳደሩ የነበሩ የሼሁ እምባ ጠባቂ የነበሩ የቅርብ ሰው አብነት ገብረመስቀል ሚድሮክ የተሰኘውን ድርጅት መልቀቃቸው ተሰምቷል። አቶ አብነት ገብረመስቀል ከስራ ይባረሩ አሊያም በገዛፍቃዳቸው ስልጣናቸውን ይልቀቁ በግልፅ ባይታወቅም ከሚድሮክ ስራቸው ግን መለያየታቸው ታውቋል። አቶ አብነት ስልጣናቸውን ከሁለት ሳምንት በፊት ያጡ ሲሆን በምትካቸው አቶ ጀማል አኅመድ መተካታቸው ተሰምቷል። በምትካቸው የተተኩት አቶ ጀማል እንደሚሉት አቶ አብነት በሼህ አላሙዲን ከስልጣን ተባረዋል፡ ከስልጣን የተባበሩትም ኃላፊነታቸውን በ አግባቡ ባለመወጣታቸው መሆኑ ተናግረዋል። አቶ አብነት ስልታን የተረከቡት የቀድሞ የሚድሮክ ስራ አስኪያጅ ዶክተር አረጋ ይርዳው በሼህ አላሙዲን ከስልጣን መባረራቸውን ተከትሎ ነበር። Abinet Gebremeskel, a close confidant of Mohammed Hussein Al-Amoudi (Sheikh) for over three decades, has left the MIDROC Ethiopia Group in all but clear circumstances. Abinet says he had resigned from his respo… Click To Read more
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከጅቡቲ በተነሱ ታጣቂ ኃይሎች በአፋር ክልል የሚገኙ ሱማለኛ ተናጋሪዎች ላይ ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል።

አዲስ ትኩሳት በጅቡቲ በኩል …………. ሳይቃጠል በቅጠል !!! ምንሊክ ሳልሳዊ – የጅቡቲ መንግስት የሚረዳቸውና የአፋርና በሶማሌ ክልል መካከል ያለውን የድንበር ውዝግብ ተንተርሰው ሽብር ለመፍጠር የሚሰሩ ታጣቂ ሃይሎች በአፋር ክልል ላይ ጥቃት መክፈታቸውን ሰምተናል። በአፋር ክልል የሚገኙ ሱማለኛ ተናጋሪዎች ላይ ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል። የውስጥ ቀውሳችንን ተገን አድርገው ሌላ ትኩሳት ለመፍጠር የሚተጉ ሃይሎችን መንግስት አፋጣኝ እርምጃዎችን ሊወስድባቸው ይገባል፤ ሳይቃጠል በቅጠል። ከፍተኛ ቁጥር ያለው የጦር መሳሪያ ለሕወሓት የሚሻገሩ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን የሚያሳይ ምስጢራዊ መረጃዎች ከወደ ጁቡቲ ተሰምተዋል። ይህን ሴራ ለማክሸፍ የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከጁቡቲ የሚወጡ የጭነት መኪኖች በሙሉ መፈተሽና ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ጀምረዋል። የህወሃት ቁንጮ አመራሮች እና የጅቡቲ ባለስልጣናት ለ27 አመታት የኢትዮጵያ ሐብት በመዝረፍ የአፈና ስርዓት በመዘርጋት በሽርክና ሲሰሩ የኖሩ የኢትዮጵያ ቀንደኛ ጠላቶች ናቸው። የህወሓት አሸባሪ ሐይል በአፋር መሃል ገብቶ ወረራ ከፈፀመበት እለት አንስቶ በጎረቤት ጁቡቲ ከፍተኛ ደስታና ፈንጠዝያ ሲሰማ ከርሟዋል። የአፋር ክልል ሙሉ በሙሉ በህወሓት ሐይሎች እጅ ገብታለች ፣ የክልሉ መሪ ሐጅ አወል አርባ በቁጥጥር ስር ውለዋል አፋር ተይዛለች ፣ ኢትዮጵያ ልትፈርስ ነው የሚለው ፕሮፓገንዳ በጅቡቲ ውስጥ ከመነዛቱም አልፎ በድንበር እከባቢዎች ዘልቀው ገብተው ቀውስ ለመፍጠር ለሚፈልጉ ለጅቡቲ ባለስልጣናትና ለታጣቂዎቻቸው አስደሳች የድል ዜና ሆኖ ሰንብቷል። የሰሞነኛ የጁቡቲ መንግስት ፈንጠዝያ እና ወደ ኢትዮጵያ አፋር አዋሳኞች ጦር የማከማቸት ሂደት ሌላ ሴራ ሊኖር ስለሚችል መንግስት ጉዳዩን በፍጥነት ሊቀጨው ይገባል። የአፋር ክልል በሰሜን በሕወሓት የተከፈበትን ጥቃት ለማክሸፍ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጠላት ለሊቱን ተጉዞ ቀን ያስለቀቅነው ቦታ ይዞ እናገኘዋለን።ከጠላት ፊት ተፋጠን እንደር ስንል ከአለቆቻችን ፈቃድ አጣን። – የአማራ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ

ኮረም ግንባር ከነበሩት የሰማሁት። በአብዛኛው የቢቸና፣የማቸከል፣የደብረ ማርቆስ እና የውጫሌ ሚሊሻዎች በሁለት ዋና ዋና ጎራ ተከፍለን በኮረሙ ግንባር ተሰልፍን ነበር ይላሉ። በዚህ ግንባር ጠላት በእየቀኑ ይመጣል ከባህሩ አሻግረን ስናሳዳቸው ተመለሱ እንባላለን እንመለሳለን።(ባህር የሚሉት አሼንጌ ሐይቅን ነው። እኛ ትዕዛዝ ተቀብለን ወደ ካንፕ እንገባለን ጠላት ለሊቱን ተጉዞ ቀን ያስለቀቅነው ቦታ ይዞ እናገኘዋለን።ከጠላት ፊት ተፋጠን እንደር ስንል ከአለቆቻችን ፈቃድ አጣን። – ሳምንቱን እንዲህ ከሰነበትን በኋላ ቅዳሜ ጠላት ጠንከር ብሎ መግጠም ጀመረ።ግን ብዙም ሳይቆይ ከረፋዱ ላይ ሸሼ።እሁድ በማንሰማው ቋንቋ በመገናኛ የሚያወሩ አካላት ሲዋጉን ዋሉ።ጥቃት ስንሰነዝር ተው ወገን ነው እያለን ዋልን። – ሰኞ ቦታ ቦታ ይዘን ተቀምጠን እያለ የመከላከያ ሰዎች መጡና ውጡ አሉን አንወጣም ስንላቸው ከመኪና እየገቡ ወጡ። የመከላከያ ሰዎች እንደወጡ ቅንቡላ ካለንበት አካባቢ እያረፈ መፈንዳት ጀመረ።ልበሙሉው ባለመነፀሩ አዋጊያችን ቦታ እንድንቀይር አዘዝን ቀየርን።ቅንቡላው እኛ ወዳለንበት ዳገት ተከትሎ መፈንዳት ጀመረ።አዋጊያችን አካባቢውን ሲቃኝ ካለንበት ዳገት ጫፍ አርሶ አደር መስለው የተቀመጡ ሰዎችን ጠረጠራቸው መሰል የተወሰኑ ሰዎች ወደ ዳገቱ ጫፍ ላከ በዚህ ግዜ ቅንቡላው ይባሱኑ መዝነብ ጀመረ ግን ከዳገቱ ጫፍ ያሉትን ማዳን አልቻለም። አሁንም በትዕዛዝ ቦታ ቀየርን ቅንቡላው ግን ቀድሞ የነበርንበትን ተራራ መደብደቡን ቀጠለ። – በዚህ ሁኔታ እያለን ከእኛ በስተፀሐይ መግቢያ(ምዕራብ መሆኑነው) የነበሩ አብረውን የዘመቱ ጓዶች ወንድሞቻችነን ትተን አንሄድም ብለው ኑ ወጡ ወጡ ተብናል አሉን።ማነው ውጡ ያላችሁ የበላይ አካል ነው ተብሏል። ከዚያ በኋላ ወደ ካንፓችን ተመልሰን የነበሩነኑ ጓዞች(እቃ ማለት ነው)
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሕወሓት መቀሌ ሲገባ አዲስ አበባ ሃርመኒና ካሌብ ሆቴሎች ውስጥ የኢትዮጵያ ባንዲራ ተቃጥሏል ።

ሕወሓት መቀሌ ሲገባ አዲስ አበባ ሃርመኒና ካሌብ ሆቴሎች ውስጥ ደግሞ ዊስኪ እየተቀዳ የኢትዮጵያ ባንዲራ ተቃጥሏል ። – መከላከያ ሰራዊታችን መቀሌን ለቆ የወጣ ቀን ፡ በአዲስ አበባ 22 እና ቦሌ መድሃኒያለም አካባቢ ፡ ጭፈራው ቀልጦ ነበር ። ሃርመኒና ካሌብ ሆቴሎች ውስጥ ደግሞ ዊስኪ እየተቀዳ የኢትዮጵያ ባንዲራ ተቃጥሏል ። ስንቱ ነብሱን የሚሰጥለትን ሰንደቃችንን መሬት ላይ አንጥፈው ረጋግጠውታል ። – ህወሃት ሰሜን እዝን ካጠቃ በኋላ የተዘፈኑ የሽብርና መከላከያን የሚሰድቡ የትግርኛ ዘፈኖች ተከፍተው ሌሊቱን ሲጨፍሩ ነው ያደሩት ። እነዚህ በቪዲዮ የተቀረፁ አስነዋሪ ድርጊቶችን ሲፈፀምባቸው ያደሩት ካሌብና ሃርመኒ ሆቴሎችን ጨምሮ ሌሎች የድርጊቱ ፈፃሚ የሆኑ ቤቶች የተዘጉ ቢሆንም ። አሁንም ሰወቹ ሊረዱ የሚገባው ነገር አለ ። – ይህ አዲስ አበባ ነው ። ህወሃትን መደገፍ ፈፅሞ የማይቻልበት ሃገር ነው ። ህወሃትን መደገፍና መከላከያን የሚሰድቡ ዘፈኖችን ከፍተህ መጨፈር ከፈለክ መቀሌ መሄድ ይኖርብሃል ።  #MinilikSalsawi – Read More – https://addisfortune.news/addis-abeba-hotels-closed-temporarily-over-inciting-music/
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የደቡብ ሱዳን መግለጫ ለኢትዮጵያ እና ወንዙን በፍትሀዊነት ለመጠቀም ለሚፈልጉ ለሌሎች ሀገራት ሁሉ መልካም አጋጣሚ ነው

ነጭ አባይ ምንሊክ ሳልሳዊ – የደቡብ ሱዳን ነጭ አባይ ይገደባል መግለጫ የውሀ አጠቃቀም ፍትሐዊነትን ለማስፈን ትልቅ ጠቀሜታ አለው። ነጭ አባይ ይገደባል መባሉ ጥቁር አባይን እንደሚጎዳው አድርገው የሚመለከቱ ጭፍኖች እየተፈለፈሉ መሆኑን ስናይ ሕዝብ ለማሳሳት የሚኬድበት መንገድ ይታሰብበት እንላለን። ነጭ አባይና ጥቁር አባይ በፍጹም የማይገናኙ ወንዞች መሆናቸውን ልናውቅ ይገባል። – የደቡብ ሱዳን መግለጫ ለኢትዮጵያ እና ወንዙን በፍትሀዊነት ለመጠቀም ለሚፈልጉ ለሌሎች ሀገራት ሁሉ መልካም አጋጣሚ ነው፤ ለቀጠናው የጂኦ ፖለቲካም ይሁን ኢኮኖሚ ትልቅ ጠቀሜታ አለው። ደቡብ ሱዳን ነጭ አባይን እገድባለሁ ማለቱ አንዳንድ የፖለቲካ ደናቁርትን ማደናቆሩን እያየን ነው። ደቡብ ሱዳን ነጭ አባይን ልትገድብ ማሰቧ እጅግ ጠቃሚ እንጂ ኢትዮጵያን የሚነካውም የሚያሳስበውም የፖለቲካ እደምታም ይሁን የኢኮኖሚ ጉዳት በፍጹም የለም። – ደቡብ ሱዳን ነጭ አባይን እገድባለሁ ማለቷ ለኢትዮጵያ ያለው አንዱ ጠቀሜታ በቀጠናው በናይል ወንዝ ዙሪያ የባለቤትነትና የይገባኛል መብትን የሚያነሱ አገራት ለግብፅ የራስ ምታት መሆናቸው ነው። መረጃዎች እንደሚተቁሙት ከግብጽ መሪዎች ጀምሮ የተለያዩ ባለስልጣናት ወደ ደቡብ ሱዳን በመመላለስ ደቡብ ሱዳንንን ለመሸንገል ያደረጉት ሙከራ በተለያይ ጊዜ አለመሳካቱን ነው። – ነጭ አባይና ጥቁር አባይ በፍጹም የማይገናኙ ሱዳን ላይ የሚገጥሙ ወንዞች መሆናቸውን ልናውቅ ይገባል። ግብፅ እና ሱዳን ለዘመናት አይነኬ የግል ሀብታቸው እንደሆነ ሲቆጥሩት የነበረውን ወንዝ ሌሎች የተፋሰሱ ሀገራትም የእኔ ማለት መጀመራቸው ለፍትሀዊ አጠቃቀም በጎ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፣ የሁለት ሀገራት ያልተገባ የበላይነት ተንሰራፍቶ ስለቆየ እሱን ለመስበርም ያገለግላል። ደቡብ ሱዳን ነጭ አባይን መገደብ ከፈለገች ልንረዳትና ልናግዛት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የፖለቲካ ደናቁርት እንደ አሸን በፈሉባት ኢትዮጵያ ሁሉም ነገር ጥንቃቄ ይጠይቃል ፤ ብስለት !

ጫፍ ይዞ ጉዞ ስሜትን እንጂ ስልትን አይወልድም ! ሮጦ ከመለጠፍ ብስለት ይቅደም ! – መደገፍም መቃወምም የሰው ልጆች መሠረታዊ የዲሞክራሲ መብቶች ናቸው ፤ ጭፍንነትና ምክንያታዊነት መጥኖ መደቆስና መንገኝነት ለየቅል ናቸው ፤ መደገፍ የሚፈልግ መብቱ እንደሆነ ሁሉ መቃወም የሚፈልግም መብቱ ነው። በዚህ ሁሉ መንገድ ውስጥ አስተዋይነትና ሰከን ማለት ያስፈልጋል፤ ይህ ማለት አደርባይነትና ሪችት በተተኮሰበት ማጨብጨብ ማለት አይደለም። የፖለቲካ ደናቁርት እንደ አሸን በፈሉባት ኢትዮጵያ ሁሉም ነገር ጥንቃቄ ይጠይቃል፤ ብስለት። – የጋራ አይኖች ሊኖሩን ይገባል። አንድን አይነት ነገር ላንዱ ኩነኔ ላንዱ ፃድቅ አድርጎ የመባረክ ስልጣን የለንም። የኛ ነገር ታጥቦ ጭቃ ነው ። ቁም ነገር ከመስራት ይልቅ የጭቃ ጅራፋችንን ማስጮህ ስራ ብለን ይዘናል ። የሕወሓት እኩይ አገር የመበጣጠስ አላማና ግብ ያወቀ ትውልድ እርስ በርሱ አይናከስም። – አስመሳይነት፣ ያልሆኑትን መለፍለፍ፣ የፖለቲካ ማባበል፣ ከትላንት ታሪክ አለመማር ፣ አደርባይነት፣ የፖለቲካ መሽኮርመም፣ አቋም አልባነት፣ በሽቆ ማብሸቅ ፣ ማድበስበስ፣ ማዘናጋት፣ ሕይወት አልባ የፖለቲካ ክሕደት፣እያባበሉ አድፍጦ መግደል፣ ለስልጣን መስገብገብና ያለሙትን ማጣት ወዘተረፈ እርግማን ነው ። – ላለፉት ረዥም አመታት ስንታገል ስንጮህ የነበረው ያለውም የሰው ልጅ ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት እንዲከበር ነው ፤ ይህ ማለት መጀመሪያ የደጋፊንም የተቃዋሚንም ሐሳብና ነፃነት ማክበር ያለብን ለመብቶች የምንታገል አክቲቪስቶች መሆን አለብን ፤ ጭፍን ድጋፍ ወይም ጭፍን ተቃውሞ የሆነ መንገኝነት ተወግዶ ምክንያታዊ የሆነ ተግባር ሥራ ላይ እንዲውል የሁላችንም ርብርብ ይጠይቃል ። – ዩጎዝላቪያን ያየ በእሳት አይጫወትም
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ብልጽግና ከአባቱ ኢሕአዴግ የወረሰው ማናለብኝነት

ከዛሬ ጀምሮ የምርጫ ቅስቀሳ አይካሄድም ቢባልም…. የጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዓርብ የተቀጠረው የፋና ኢንተርቪው በራሱ የምርጫ ቅስቀሳ ነው። ምርጫው ካለፈ በኃላ የማይቀርብበት ምክንያቱ ምንድነው ??? ብልጽግና ከአባቱ ኢሕአዴግ የወረሰው ማናለብኝነት – ምንሊክ ሳልሳዊ – ከዛሬ ጀምሮ የምርጫ ቅስቀሳ አይካሄድም ቢባልም ብልጽግና በመንግስት ሚዲያዎች ቅስቀሳውን ቀጥሏል። ብልጽግና የመንግስት ሚዲያዎችን ተጠቅሞ በተወዳዳሪ ፓርቲዎች ላይ ከምርጫ ጣቢያዎች ጀምሮ እስከ በሕዝብ ግብር እስከሚተዳደሩ የመንግስት ሚዲያዎች ከፍተኛ ጫና ሲፈጥር የከረመ ቢሆንም ምርጫ ቦርድ ሊያስቆመው ሳይችል የተቋሙን ተዓማኒነት አጠያያቂ እንዲሆን አድርጎታል። – የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፋና ኢንተርቪው በራሱ የምርጫ ቅስቀሳ ነው። ምርጫው ካለፈ በኃላ የማይቀርብበት ምክንያቱ ምንድነው ? – ብልጽግና በምርቃት በመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥ በሪቫን ቆረጣ ስም የመንግስትን ኃላፊነት ተገን በማድረግ የልማት ስራ ተሰራ በዉጤታማ ፖሊሲ ወዘተ በማለት የምርጫ ተወዳዳሪዎችን በሚዲያ በማቅረብ ቅስቀሳውን ቀጥሏል። – ይህ ሕግን አለማክበር ብልጽግና ከአባቱ ኢሕአዴግ የወረሰው ማናለብኝነትን ምርጫ ቦርድ ሊያስቆመው ይገባል። #MinilikSalsawi
Posted in Amharic News, Ethiopian News