Home › View all posts by DW Amharic
Blog Archives
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ-መስተዳደር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ትናንት መሾማቸው የተገለጠው አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ የትግራይ ክልል ግዛታዊ አንድነትን ለማስጠበቅ እንደሚሠሩ ተናገሩ ። የተፈናቀሉ ያሏቸውን መልሶ ወደ ቀዬአቸው የመመለስ ተግባራት እና ሌሎች ቀዳሚ አጀንዳዎችን እንደሚሠራባቸውም ዐስታውቀዋል ።...
ቤልጂየም ብራስል ውስጥ ለሁለት ቀናት በዘቀው የአውሮጳ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ አባል ሃገራቱ ኢኮኖሚና የኑሮ ውድነት፤ የስደተኞች ጉዳይና የውጭ ግንኙነት እንዲሁም የዩክሬን ጉዳይ ላይ ተወያይተው ውሳኔ አሳልፈዋል ። ኅብረቱ ዩክሬን የሩስያ ጦርን እንድትመክት በአንድ ዓመት 1 ሚሊዮን የመድፍ ጥይቶችን ለማቀበል መስማማቱን ትናንት ይፋ አድርጓል ።...
የረዥም አመታት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ የነበረው ኤርሚያስ አየለ ባለፈው እሁድ በጣሊያን ዋና ከተማ ሮም በተካሄደው የማራቶን ውድድር በባዶ እግሩ ሮጦ አጠናቋል። ይህንን ያደረገው ለዝነኛው አበበ ቢቂላ ክብር እና ለሀገር ገጽታ ግንባታ ነው ይላል።...
በዘንድሮ የምርት ዘመን የተሻለ ምርት የተሰበሰበቤት ወቅት እንደነበር የክልሉ ግብርና ቢሮ ከዚህ ቀደም ይፋ አድርገዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸርም የአራት ሚሊዩን ኩንታል ብልጫ እንዳለው ተጠቁሟል፡፡ ሆኖም በክልሉ አሶሳ ከተማና አሶሳ ዞን ውስጥ በቆሎን ጨምሮ የምርት ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል፡፡...
በህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ውሳኔ የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደርን አቶ ጌታቸው ረዳ እንደሚመሩት የተናገሩት የህወሓቱ ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትም ለአቶ ጌታቸው ሹመቱ ስለመስጠቱ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ህወሐት ከአሸባሪነት መዝገብ መሰረዙ የግዚያዊ አስተዳደሩ ስራ ለማስጀመር ምቹ ሁኔታ የፈጠረ መሆኑ ተገልጧል።...
ዲንካ ሙሉ በሙሉ ከቀርከሃ የሚሰራ ሲሆን ድምጽ በሚወጣበት ጫፉ የሚዳቋ ቀንድ ይገጠምለታል። ዲንካ በብሔረሰቡ የተለያዩ የደስታ በአላት ዋና ማድመቂያ እንደሆነ ባለሙያው ነግረውናል።...
"የዚህ ጦርነት ተሳታፊዎች ብዙ ናቸው። ዓላማቸውም እንደዚሁ በጣም የተለያየ ነው። ትግራይ ላይ ወይም ሕወሓት ላይ ተመሳሳይ አቋም የነበራቸው አካላት አብረው ተሰልፈዋል እና ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል እነዚህን አካላት አሁንም አንድ ላይ አስተባብሮ ወደ ሰላም ስምምነቱ ማስገባት እና ተገዢ ለማድረግ አስቸጋሪ እንደሚሆን ይገባኛል"...
የቻይናው ፕሬዝደንት ጂፒንግ በሞስኮ ያደረጉትን የ2 ቀናት ጉብኝት አጠናቀው ዛሬ ወደ አገራችው ተመልሰዋል። ፕሬዝድንት ጂፒንግ ወደ ሞስኮ ያቀኑት ቀደም ሲል ፕሬዝዳንት ፑቲን ባቀረቡላቸው ግብዣ ሲሆን፤ ሁለቱ መሪዎች ባደረጓቸው ውይይቶችም በሁለትዮሽና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች በጋራ ለመስራትና ወዳጅነታቸውን ለማጠናከር የተስማማሙ መሆኑ ተገልጿል።...
ዶክተር ተወልደ ብርሀን ገብረእግዚአብሔር የብዝሀ ሕይወት ጉዳይ የሚገዳቸው፤ በዓለም አቀፍ መድረኮች በማደግ ላይ የሚገኙ 134 አገራትን ወክለው የተደራደሩ ሳይንቲስት ነበሩ። በዚህ ሣምንት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ዶክተር ተወልደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና አስመራ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት በሙያቸው አገልግለዋል።...
የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ አባል እና የክልሉ አስተዳደር የሕግ ጉዳዮች አማካሪ አቶ አማኑኤል አሰፋ፥ «መጀመርያውኑም ህወሓትን በአሸባሪነት መፈረጅ አስፈላጊ አልነበረም» ያሉ ሲሆን፣ አሁን የኢትዮጵያ ፓርላማ እዚህ ውሳኔ ላይ መድረሱ ግን መልካም እርምጃ ነው ብለውታል።...
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ መጋቢት 13 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው አንደኛ ልዩ ስብሰባ በአሸባሪነት ፈርጆት የነበረውን የሕዝባዊ ወያነ ኃርነት ትግራይ ( ሕወሓት) ን የአሸባሪነት ፍረጃ በአብላጫ ድምጽ አነሳ።...
ቲክ ቶክ በአሁኑ ወቅት ተወዳጅ ከሆኑት የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች መካከል አንዱ ነው።ያም ሆኖ የተለያዩ ሀገራት ባለሥልጣናትን እያወዛገበ ነው።አሜሪካ፣ካናዳ እና ብሪታንያን ጨምሮ በርከት ያሉ ሀገራት ቲኪቶክ ከመንግስት ተንቀሳቃሽ የኤለክትሮኒክ መሳሪያዎች ላይ መታገዱን በቅርቡ አስታውቀዋል።ለመሆኑ ቲክ ቶክ በባለስልጣናት ዘንድ ለምን ስጋት አሳደረ?...
የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች የ2016ን በጀት ሲያዘጋጁ "ከውጭ ሊገኝ የሚችልን ዕርዳታ እና ብድር በማሰብ" ሊሆን እንደማይገባ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ አሳስበዋል። የፕሪቶሪያ የሰላም ሥምምነት እና የሽግግር ፍትኅ አተገባበር ምዕራባውያን የከለከሉትን እርዳታ እና ብድር ለመፍቀድ ቅድመ-ሁኔታ አድርገዋል።...
በጎርጎሪዮስ የዘመን ቀመር መጋቢት ወር የሴቶች ታሪክ የሚወሳበት እንደመሆኑ የጤና እና አካባቢ መሰናዶ ዓይነስውርነት ካለመችው ስኬት ያላስቀራትን የኮሌጅ መምህርት ያስተዋውቀናል።...
ብሪታንያ ያረቀቀችው አዲስ ሕግ በሕገ ወጥ መንገድ የገቡ ስደተኞችን ከብሪታንያ አባሮ ወደ ሩዋንዳ ወይም ወደ ሌላ ደኅንነቱ የተጠበቀ ሦስተኛ ሀገር እንዲላኩ የሚያደርግ ነው።ብሪታንያ በተለይ በጀልባ የሚመጡ ስደተኞችን አስገድዳ ከሀገርዋ ለማባረር የምታደርገው ዝግጅት በስደተኞችና በሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በእጅጉ መተቸቱ ቀጥሏል።...
ብሊንከን በዚሕ አለበቁም።ከአራቱ ኃይላት የትግራይ ነፃ አዉጪን አስቀርተዉ የተቀሩት ሶስቱን ወይም አባሎቻቸዉን በሰብአዊነት ላይ «ወንጀል ፈፅመዋል» ብለዋል።ከሶስቱ ደግሞ የአማራ ኃይላት አባላት ያሏቸዉን ለብቻ ነጥለዉ «በዘር ማፅዳት» ወንጅለዋቸዋል...
በኢትዮጵያ በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች የተከሰተውን ከባድ ድርቅ ተከትሎ በተለያዩ ዞኖች በተስተዋለው የኮሌራ ወረርሽኝ እስካሁን 44 ሰዎች ሕይወት አልፏል። አዲስ አበባ ላይ የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ ደግሞ መኖሪያ ቤቶችን ሰብሮ አራት ሰዎችን ገድሏል፣ በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን ከባድ ዝናብ የጎርፍ የ13 ሰዎችን ሕይወት ነጥቋል።...
ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ ዞኖች በየአካባቢዎች በነበሩ ግጭቶች ምክንያት በተለያዩ ጊዜዎች ተፈናቅለው በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ጃራ የመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች በቂ ድጋፍ አላገኘንም አሉ። የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ችግሩ መኖሩን አረጋግጧል።...
የኬንያ ፖሊስ በሃገሪቱ የሚታየዉን የኑሮ ዉድነት በመቃወም በተጠራ ሰልፍ ቢያንስ አንድ ሰዉ ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት መገደሉ ተሰማ ። ፖሊስ ሰልፉን በአስለቃሽ ጢስ እና ዉኃ በመርጨት በትኗል። ኦዲንጋ የኑሮ ዉድነትና፤ «በተሰረቀ የምርጫ ዉጤት» ስልጣን ላይ የሚገኙትን ፕሬዚዳንት ሩቶን በመቃወም ዜጎች ተቃዉሞዋቸዉን እንዲቀጥሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።...
በዓለም ዙርያ በተከሰተዉ የውኃ ብክለት እና እጥረት ብሎም የአየር ንብረት ለውጥ በደቀነዉ አደጋ ምክንያት ወደ 190 ሚልዮን የሚሆኑ ሕፃናት ላይ አደጋ ተደቅኗል ሲል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስጠነቀቀ። በየቀኑ ከ1000 የሚበልጡ ሕፃናት የተበከለ ውኃ በሚያስከትለው መዘዝ ተጠቂ መሆናቸዉን ዩኒሴፍ አስታዉቋል።...
ዢ ጂንፒንግ ለሦስት ቀናት ጉብኝት ዛሬ ጠዋት ሞስኮ ገቡ። የሩስያ የመንግሥት የዜና ወኪል «ሪያ ኖቮስቲ» ዢ ጂንፒንግን የያዘዉ አዉሮፕላን ሞስኮ ቭኑኮቫ ዓለም አቀፍ አዉሮፕላን ማረፍያ መድረሱን የሚያሳይ ፎቶግራፍ አሰራጭቷል። የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዢ ጂንፒንግ ወደ የሩስያ ጉዞን "የሰላም ጉብኝት" በማለት ገልጾታል።...
በሐሰት ዉንጀላ ሐገር ያጠፋዉ ጦር ከ4ሺሕ በላይ ጓዶቹን ሕይወት ገብሯል።የአሜሪካ ግብር ከፋይ በትሪሊዮን የሚቆጠር ዶላር ከስክሷል።የጦሩ ፊት አዉራሪዎች ግን በመዋሸታቸዉ፣ሐገር በማጥፋታቸዉ፣ ሕዝብ በማስፈጀታቸዉም፣ ወታደሮቻቸዉን በማስገደላቸዉም፣ ገንዘብ በማጥፋታቸዉ ወይም የዓለምን ሕግ በመጣሳቸዉ ባንዱም፣አንዳቸዉም፣ አንዴም ተጠያቂ አልሆኑም።...
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ማካሄድ ተጀመረ። ለጉባኤው ባለፉት ሰባት ወራት በኑሮ ውድነት ቅነሳ እና በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱ ተገልጿል።...
የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና ህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ «ህወሓት» ለሁለት ዓመት ያደረጉት ጦርነት ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም ደቡብ አፍሪቃ ፕሪቶርያ ላይ በሰላም ስምምነት ከተቋጨ አራት ወር ሆኖታል። ይህ አስከፊ ሰብዓዊ መብት ጥሰት የተፈፀመበት ጦርነት ቢያበቃም ብዙዎች የፕሪቶርያዉ የሰላም ስምምነት ተግባራዊነቱ አጠያያቂ ሆንዋል ሲሉ አስተያየት ይሰጣሉ። አንዳንዶች የፕሪቶርያዉ ስምምነት ከርዕስነት ወጥቷል ብለዉ የሚያስቡ እንዳሉ ሁሉ አንዳንዶች ስምምነቱ በከፊል ነዉ የተሟላዉ ብለዉ ያምናሉ።
በዚህ ሳምንት ለሁለት ቀናት ኢትዮጵያን የጎበኙት የአሜሪካዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ፕሪቶርያ ላይ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ግጭትን በዘላቂነት በማስቆም አፈሙዝን ጸጥ የተደረገበትን ሂደት አድንቀዋል። ለዚህም አገራቸው አሜሪካ ድጋፏን እንደምትቀጥል ነዉ ቃል የገቡት። ሆኖም በትግራይ ተከስቶ ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በተዛመተው የእርስ በርስ ጦርነት ተሳታፊ በሆኑ አካላት በተፈጸሙ ጥሰቶች ዙሪያ ተጠያቂነት ሊኖር እንደሚገባ የአሜሪካዉ የዉች ጉዳይ ሚኒስትር አሳስበዋል።
በሌላ በኩል መንግሥት ተለስላስሷል፤ የፕሪቶርያዉን የሰላም ስምምነት እያስፈጸመ አይደለም፤ የሚሉ እንዳሉ ሁሉ ህወሓት እየሄደበት ያለዉ መንገድ ትክክል አይደለም፤ እንደ ስምምነቱ ሁሉን አካታች የሆነ ሽግግር መንግሥት በትግራይ መመስረት አልቻለም፤ ስልጣንን የማካፈል ፍላጎት የለዉም የሚሉ ብዙዎች ናቸዉ። የፌደራሉ መንግሥት ከህወሓት ጋር ደቡብ ኢትዮጵያ ላይ ሲገናኝ በምን ጉዳይ ላይ እንደተነጋገረ እና እንደተስማማ የታወቀ ነገር የለም የሚሉ ትችቶችም ይሰማሉ። የፕሪቶርያዉ ስምምነት ምን ያህል ተግባራዊ ሆንዋል ተብሎ ይታመናል? ወደፊትስ ምን ያህል ተግባራዊ ይደረጋል ?
በእነዚህ ነጥቦች ላይ ሃሳቦቻቸዉን ያካፈሉን የዉይይቱ ተሳታፊዎች፤
አቶ ግርማ ሰይፉ፤
ፕሪቶርያ ላይ በሰላም ስምምነት ከተቋጨ አራት ወር የሆነዉና አስከፊ ሰብዓዊ መብት ጥሰት የተፈፀመበት የሰሜን ኢትዮጵያዉ ጦርነት ቢያበቃም ብዙዎች በሰላም ስምምነቱ አፈፃፀም ላይ ጥርጣሬ አላቸዉ። መንግሥት ስምምነቱን እያስፈጸመ አይደለም፤ የሚሉ እንዳሉ ሁሉ ህወሓት ሁሉን አካታች የሆነ ሽግግር መንግሥት ለመመስረት አልቻለም፤ የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም።...
ለጀርመኑ ሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ ቅርበት ያለው የፍሬድሪሽ ኤበርት ተቋም የአፍሪቃ ክፍል ያካሄደው ጥናት እንደሚያሳየው ከሰሀራ በረሀ በታች በሚገኙ የአፍሪቃ ሀገራት ስራ አጥነት እጅግ ተባብሷል። በተቋሙ የአፍሪቃ ጉዳዮች አጥኚ ሮበርት ካፔል እንደሚሉት በየዓመቱ 20 ሚሊዮን ሰዎች በገጠርም ሆነ በከተሞች የሌሉ ስራዎች ፍለጋ ላይ ናቸው።...
ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ ትላንት ባወጣው መግለጫ "ቅቡልነት እና ሕጋዊነት ያጣ ግዚያዊ አስተዳደር ፍትህና ዴሞክራሲ ሊያረጋግጥ አይችልም" ብሎታል።...
አንቶኒ ብሊንከን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ "መርዛማ ቅራኔዎችን እና የጎሳ መከፋፈልን ማስወገድ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉትን ብሔር ተኮር ግጭቶችን ለማስወገድ ብቸኛው መንገድ ነው" ብለው ነበር።...
ሌሽማንያሲስ ወይም በአማረኛው ቁንጭር በመባል የሚታወቀው ደዌ ከአሩራማ ተላላፊ የበሽታ አይነቶች መካከል አንዱ መሆኑ ይነገራል ፡፡ በትንኝ አማካኝነት የሚተላለፈውና የሰውነት ክፍሎችን በማቁሰልና በማሳበጥ ለሞት የሚዳረገው በሽታ ሥርጭት አሁን ላይ በደቡብ ክልል እየጨመረ መምጣቱን ከክልሉ ህብረተሰብ ጤና ተቋም የተገኘው መረጃ ያመለክታል ፡፡...
በፓርቲው ስም ሲንቀሰቃሱ የነበሩ ወደ 3 ሺ የሚደርሱ ታጣቂዎችም ከክልሉ መንግስት ጋር ስምምነት ላይ ከተደረሰ ወዲህ ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉደታ ተናግረዋል፡፡...
በዘንድሮ ዓመት እንደ ኦሮሚያ በሁሉም ዘርፍ የተሻለ የምርት ውጤት መኖሩን ያመለከቱት ባለስልጣኑ ሰሞኑን በገቢያ ላይ የምርት እጥረት ተከስቶ የህዝብን ምሬት ማስከተለውን ተከትሎ፤ የፖለቲካ ትርፍ የሚፈልጉ ያሏቸውና በስም ያልጠቀሳቸው ምርት በመደበቅ ህዝብን ያስመርራሉ ብለዋል...
ብሩክታዊት ሐብታሙ በአሁኑ ሰዓት ሚስ ካልቸር ኢንተርናሽናል በሚል ዓለም አቀፍ ባህላዊ የቁንጅና ውድድር ላይ ተሳታፊ ናት። ኢትዮጵያን ወክላ ለመወዳደር የበቃችውም «ሚስ ካልቸር ኢትዮጵያ» ተብላ ኢትዮጵያ ውስጥ የተካሄደውን ውድድር በማሸነፏ ነው። ብሩክታዊት ለዚህ ምን ያህል ዝግጁ ናት? ሰዎችስ ለምን ለእሷ ድምጫቸውን ይስጡ?...
ሁለት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዳያከናውኑ በመንግሥት የፀጥታ ኃይላት መከልከላቸውና አንድ ፓርቲም የጀመረውን ጉባኤ ዳር እንዳያደርስ አባላቱ ለወከባ፣ ለእንግልት እና ለእሥር መዳረጋቸው ፍፁም ተቀባይነት እንደሌለውና ቦርዱ በሕግ የተሰጠውን ኃላፊነት እንዳይወጣ ከፍተኛ ጫና የሚያመጣበት መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።...
በትግራይ ጤና ቢሮ ገለፃ መሠረት ሙሉ በሙሉ ከወደሙ የጤና ተቋማት ውጭ የተቀሩትን ወደ መደበኛ የጤና አገልግሎት ለመመለስ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።በመድኃኒትና የሕክምና ቁሳቁስ አቅርቦት በኩል መሻሻሎች ቢኖሩም ከፍላጎት አንፃር ግን አሁንም ብዙ እንደሚቀር የክልሉ ጤና ቢሮ ይገልፃል። አሁንም ቢሆን የሕክምና ግብአቶች አቅርቦት ውሱንነት አለ ይላል።...
አሜሪካ ከሳዑዲ አረቢያና የባህረ ሰላጤው አገሮች ጋር ካላት የቆየና የጠበቀ የንግድ፣ የፖለቲካና ወታደራዊ ግንኑነት አንጻር ተፎካክሪዋ ቻይና በወዳጆቿ ሰፈር ያልተጠበቀና የተሳካ ሽምግልና ማክሄዷ ለሁሉም አነጋጋሪ ሆኗል።ዲፕሎማሲይዊ ክስተቱ፤ አለም ዓቀፍ ግንኙነቱ እየተለወጠና አዳዲስ የኃይል አሰላለፎች እይታዩ መሆኑን የሚያመለክት ነው ተብሏል።...
የሶማሌ ሂሳ ብሄረሰብ ህጉን መሰረት በማድረግ የብሄረሰቡ ባህላዊ ፣ መንፈሳዊ እና ፖለቲካዊ መሪ አድርጎ የመረጣቸው ዑጋዝ ሙስጠፋ መሀመድን ጨምሮ ከጅቡቲ እና ከሶማሌላንድ የመጡ ተወካዮች እና ባለስልጣናት በውይይቱ ተገኝተዋል። የብሄረሰቡ መገኛ የሆኑት ኢትዮጵያ ፣ ጅቡቲ እና ሶማሌላንድ በጋራ ጥያቄውን ያቀርባሉ ተብሏል።...
ኢትዮጵያውያን እርቅን እና ተጠያቂነትን ያልተወ አካታችና ሁሉን ያቀፋ የሽግግር ፍትሕ ሥርዓትን ለመተግበር የያዙትን ቁርጠኛ አቋም እንዲያስቀጥሉ የጠየቁት ብሊንከን "መርዛማ ቅራኔዎችንና የጎሳ መከፋፈልን ማስወገድ፣በሰሜን ኢትዮጵያ ፣ በኦሮሚያም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች ያለውን ብሔር ተኮር ግጭቶችን ለማስቆም ብቸኛው መንገድ ነው" ሲሉም አሳስበዋል።...
በአፋር ሕዝብ ዘንድ ሲወርድ ሲዋረድ በመጣው ባሕላዊ የዳኝነት ሥርዓት የአንድ ሰው ነፍስን ያጠፋ ግለሰብ ሲዳኝ ካሳ የሚከፍለውግመልን በመስጠት ነው። ይህ የሚያሳየውደግሞ የአፋር ማኅበረሰብ ግመልንእንደ ሰው ህይወት ማየቱ ነዉ።...
በአዲስ አበባ የጤፍ ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ሸማቾች፣ ነጋዴዎች እና የወፍጮ ቤት ባለቤቶች ይናገራሉ። አንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ ጤፍ "የትም ቦታ ላይ ጨምሯል ነው እንጂ ቀንሷል የሚባል ነገር የለም" ሲሉ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። የነዋሪዎችን አቅም ከተፈታተነው የዋጋ ጭማሪ ባሻገር በገበያው የተከሰተው የጤፍ እጥረትም ሌላ ችግር ነው።...
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፒያሳ አከባቢ ከራስ መኮንን ድልድይ ጀምሮ በተለምዶ እሪ በከንቱ እስከሚባለው ሰፈር ሰሞኑን የሚከናወነው የቤቶች ፈረሳ በርካቶቻችንን ደጅ ያስቀረን ነው ሲሉ ቅሬታ አቅራቢዎች ገለጹ።...
የጀርመን ፌደራል የሥራና ሠራተኛ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንደሚለው በአሁኑ ጊዜ ጀርመን በዓመት 400 ሺህ የውጭ ሠራተኛ ኃይል ያስፈልጓታል። ይሁንና በጎርጎሮሳዊው 2021 ወደ ጀርመን የገባው የውጭ ሠራተኛ 40 ሺህ ብቻ ነው። ይህን ለመለወጥ የጀርመን መንግሥት በዚህ ዓመት የተሻሻለ የፍልሰት ሕግ ለማውጣት በዝግጅት ላይ ይገኛል።...
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ትናንት ምሽቱን አዲስ አበባ ገብተዋል። ብሊንከን ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በበርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸው ተሰምቷል።...
ዶክተር ብርሀኑ ቡልቻ በአሜሪካው የጠፈር ምርምር ናሳ ፤ ጨረቃ ላይ ውሃ የሚፈልግ መሳሪያ የሰሩ ሳይንቲስት ናቸው።ባለቤታቸው ዶክተር ፀጋ ሰለሞን ደግሞ የክትባት እና የመድሃኒት ተመራማሪ ናቸው።ጥንዶቹ ኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ተማሪዎች በተለያዩ ዘርፎች ስልጠና የሚሰጥ ብሩህ ትውልድ/Brighter Generation/የተሰኘ መርሃግብር መስርተዋል።...
የኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)የሰላም ስምምነት ከመፈራረማቸው ከሳምንት በፊት የኤርትራ ወታደሮች አድዋ አካባቢ በምትገኘው በማርያም ሸዊቶ መንደር በትንሹ 300 ሰዎች መገደላቸዉን አንዲት የመንደርዋ ነዋሪ ተናገሩ። ወይዘሮዋ የ 70 ዓመቱ ባለቤታቸዉና የ28 ዓመቱ ልጃቸዉ በኤርትራ ወታደሮች ተገድለዉባቸዋል።...
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን፣ ከዛሬ መጋቢት አምስት እስከ መጋቢት ስምንት ቀን 2015 ድረስ ወደ ኢትዮጵያና ኒጀር እንደሚያቀኑ መስሪያ ቤታቸው ያወጣው መግለጫ ያመለክታል።
አንቶኒ ብሊንከን፣ በአዲስ አበባ በሚያደርጉት ጉብኝት በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭትን ለማስቆም የተደረሰው የሰላም ስምምነት አተገባበር እና የሽግግር ፍትህ ጉዳይ ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል።
የኢትዮጵያንና የአሜሪካን ፖለቲካዊ ጉዳዮች በቅርበት የሚከታተሉት፣ልጅ ነቢያት አክሊሉ እንደሚሉት፣ብሊንከን በዚህ ጉብኝታቸው፣ በሰሜን ኢትዮጵያ የተደረሰዉ ስምምነት መሬት ላይ ወርዶ በትክክል ተፈጻሚ የመሆን ያለመሆኑን ጉዳይ እንደሚገመግሙ ይጠበቃል።
https://radiodownloaddw-a.akamaihd.net/downloads/Events/dwelle/dira/mp3/amh/74090138_2.mp3
“በኢትዮጵያ መንግስትና በህወሓት መካከል የተፈረመውን የሰላም ውል ባግባቡ መሬት በአግባቡ መሬት ላይ ወርዶ ተግባራዊ ስለመሆን አለመሆኑ ያንን ለማረጋገጥና በመንግስትና መሬት ላይ ባሉትም የፖለቲካ ኃይላት ተጽዕኖ ለመፍጠር እና ሰላምና መረጋጋት እንዲመለስ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማድረግ የሄዱ ይመስለኛል።”

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ከዚህ ቀዳም ባወጡት መግለጫ፣ ከሰሜን ኢትዮጵያ በተጨማሪ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ ክልል ያለው የጸጥታ ችግርና የፖለቲካ አለመረጋጋት ስጋት እየፈጠረ መሆኑን አንስተው ነበር።
በመሆኑም በዚህ ጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እንዲሁም ከሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በሚያደርጉት ውይይት፣ የአገሪቱን አጠቃላይ የፖለቲካ አለመረጋጋትና የጸጥታ ችግር አንስተው ይወያዩበታል ብለው እንደሚጠብቁ የፖለቲካ ተንታኙ ይናገራሉ።
“ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለውን፣በጸጥታውም አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለመገምገም እና የትግራዩን ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያውያን በንፁሃን ዜጎች ላይ እየተወሰደ ያለው የጅምላ ጥቃትና ጭፍጨፋ ዘርን መሰረት ያደረገ ጨፍጨፋ፣ ለማስቆም መንግስት ላይ ተጽዕኖ የሚፈጥሩ ይመስለኛል።”
,
በዚህ
የኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)የሰላም ስምምነት ከመፈራረማቸው ከሳምንት በፊት የኤርትራ ወታደሮች አድዋ አካባቢ በምትገኘው በማርያም ሸዊቶ መንደር በትንሹ 300 ሰዎች መገደላቸዉን አንዲት የመንደርዋ ነዋሪ ተናገሩ። በዚች ትንሽ መንደር የሚኖሩት የ63 ዓመቷ አዛውንት ወ/ሮ አብረኸት ሀጎስ በወቅቱ ስለነበረው ሁኔታ እንዲሁም በቤተሰባቸው ላይ ስለደረሰባቸው ጥቃት ለዶቼ ቬሌ የእንሊዘኛ ክፍል በምስል በተደገፈ ማስረጃ ተናግረዋል ።

ወ/ሮ አብረኸት ሀጎስ መኖርያ ቤታቸዉ በኤርትራ ወታደሮች በጥይት እንደተደበደበ ያሳያሉ
በ2012 ዓ.ም ጥቅምት ወር መጨረሻ ቀናት የኤርትራ ወታደሮች አዛዉንቷ ወ/ሮ አብረኸት ሃጎስ ከአድዋ ከተማ ወጣ ብሎ የሚኖርባት መንደርን እንደተቆጣጠሩ እና ሰዎች እየተገደሉ በወሬ ደረጃ እንደሰሙ መኖርያ ቤታቸዉን ለቀው ለመሸሽ ከቤተሰባቸው ጋር ቢያስቡም በወቅቱ መሸሸጊያ ቦታ ባለማግኘታቸዉ ምሽት ላይ ከመኖሪያቸው ወጣ ብሎ ባለ ቦታ ተሸሸጉ። እረፋድ ላይ ግን ይላሉ የ 63 ዓመት እድሜ ባለፀጋዋ ወ/ሮ አብረኸት «የቤት ውስጥ የነበሩት እንስሶቻችን ያልተለመደ ድምጽ ማሰማት ጀመሩ። በዚህ ግዜ የ 70 ዓመቱ ባለቤታቸዉ እና የ28 ዓመቱ ጎልማሳ ልጄ ምን እንደተፈጠረ ለማየት ወደ መኖርያ ቤታችን ሄዱ። በዚህ ግዜ ነበር በኤርትራ ወታደሮች እጅ ውስጥ ወድቀዉ ሁለቱም የተገደሉት። የመኖርያ ቤቱ ግድግዳ በአምስት ወይንም ስድስት ጥይት ተበሳስቷል። ልጄ ቤት ዉስጥ ተደብቆ ከሞት ለማምለጥ ከወታደሮቹ ለመሸሸግ ሞክሮ ነበር። ወ/ሮ አብረኸት እና ሴት ልጃቸዉ ከተሸሸጉበት ወጥተዉ መኖርያ ቤታቸዉ ሲደርሱ ባለቤታቸዉ እና ወንዱ ልጃቸዉ በደም ተነክረዉ ወድቀዉ አገኝዋቸዉ።
«ውይ !ብዬ ሴት ልጄን አባትሽ ሞቱ አልኩ፤ ከዛ
"ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለውን፣በጸጥታውም አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለመገምገም እና የትግራዩን ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያውያን በንፁሃን ዜጎች ላይ እየተወሰደ ያለው የጅምላ ጥቃትና ጭፍጨፋ ዘርን መሰረት ያደረገ ጨፍጨፋ፣ ለማስቆም መንግስት ላይ ተጽዕኖ የሚፈጥሩ ይመስለኛል።"...
ህገወጥ የዓሳ ማስገር ሀብቱን እያመናመነው መሆኑን የጣና ሐይቅ አካባቢ ነዋሪዎችና ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ ያልተፈቀዱ የዓሳ ማስገሪያ መሳሪያዎችን መጠቀምና ወቅቱን ያልጠበቀ ማስገር ዋናዎቹ የችግሩ ምንጮች ናቸውም ተብሏል፡፡ በጣና ሐይቅ ላይ ብቻ ከ5000 በላይ አስጋሪዎች እንዳሉ የአማራ ክልል የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ጽ/ቤት አመልክቷል፡፡...

ኢትዮጵያን እያናወጣት ነው ካለው አደገኛ የፖለቲካ ቀውስ ለመውጣት የዕልውና ትግል ጥሪ ማቅረቡን ራዕይ ለኢትዮጵያ አስታወቀ።
ተቀማጭነቱን በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው ራዕይ ለኢትዮጵያ፣ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባወጣው አስቸኳይ መገለጫ፣በዘር ማጥፋት፣በታሪክ ክለሳ፣በባህልና ኃይማኖት ብረዛ በሃብት ዝርፊያና በርስት ቅሚያ ሃገሪቱ እየተናወጠች ትገኛለች ብሏል።
በቅርቡ በእስልምና ኃይማኖት ተከታዮችና በኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሲኖዶስ ላይ የተነጣጠረ የከፋፍሎ ማዳከምና የማፈራረስ ዘመቻ፣ሃገሪቱን እንደ ድርና ማግ ያስተሳሰሯት እሴቶች በተቀነባበረ ስልት እየተተበጣጠሱ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል።
የጥቁር ሕዝብ ነጻነት መንጸባረቂያና መመኪያ የሆነው የዐድዋ ድል በአግባቡ እንዳይከበር መደረጉን ያወሳው ራዕይ ለኢትዮጵያ፣ይባስ ብሎም በቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ በአማኞችና በአድዋ ድል አክባሪዎች ላይ ፋሽታዊ ያለውን ዕርምጃ በመውሰድ፣ አስከፊ የታሪክ ጥቁር ነጥብ መመዝገቡን አስረድቷል።
በወለጋ፣ሰሜን ሸዋና ሌሎች አካባቢዎች የሚኖሩ የዐማራ ተወላጆች ከመገደላቸውና ከመፈናቀላቸው በተጨማሪ፣አሁን ደግሞ በጉራጌና ሌሎች ወገኖች ላይ ተመሳሳይ ወንጀል እየተፈጸመባቸው እንደሚገኝ ቪዥን ኢትዮጵያ ያወጣው መግለጫ አትቷል።
ስለሆነም፤ሕዝቡን ከከፋ ችግርና ዕልቂት ለመታደግና ሃገሪቱን ከተደቀነባት አደገኛ የፖለቲካ ቀውስ ለማዳን፣ቪዥን ኢትዮጵያ የህልውና ትግል ጥሪ ማቅረቡን፣የአትላንታው ወኪላችን ታሪኩ ኃይሉ የላከልን ዘገባ ያመለክታል።
በደቡብ ክልል በኦሞ ስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኙ ከ337 ሺህ በላይ አርብቶ አደሮች በከባድ የምግብ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ በዝናብ እጥረት ምክንያት በአካባቢው የሚገኙ ወንዞች ሙሉ በሙሉ በመድረቃቸው የተነሳ እንስሳት እየሞቱ ፣ ሰዎችም በምግብ እጥረት ለጉዳት እየተዳረጉ እንደሚገኙ ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል።...
በትግራይ ይቋቋማል የተባለው ጊዜያዊ አስተዳደር እስካሁን ድረስ እውን ባለመሆኑ የአስተዳደር ክፍተት መፈጠሩ እና ህዝቡ ለችግር መዳረጉ ተገለፀ። ተቃዋሚው ዓረና ትግራይ ፓርቲ በትግራይ ጊዜያዊ የሽግግር አስተዳደር በአፋጣኝ እንዳይቋቋም በማደናቀፍ ህወሓትን ከሷል።...
የጀመሪያዉ ከሰሜን ሩሲያዊቱ የወደብ ከተማ ቭይቦርግ፣ ሁለተኛዉ ከኡስት-ሉግ ተነስተዉ የቦልቲክ ባሕር ዉስጥ-ለዉስጥ ተጉዘዉ ሰሜናዊቱ የጀርመን ከተማ ሉብሚን ብቅ ይላሉ።1200 ኪሎ ሜትር ይርዘማል።በ2021 ብቻ 59 ቢሊዮን ኪዩብኪ ሜትር የሩሲያ ጋዝ ወደ ጀርመን ተንቆርቁሮበታል...

የምስረታ ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ ያካሄደው ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ጎጎት የሚል ስያሜ ያለው አገር አቀፍ የፖለቲካ ድርጅት ” የምርጫ አስፈፃሚዎች እና አስተባባሪዎች ከያዙት ሰነድ ጋር ዛሬ በፖሊስ ታፍነው ተወሰዱ ሲል የፓርቲው ጊዜያዊ አደራጅ ኮሚቴ አስታወቀ ። የኮሚቴው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ጀሚል ሳኒ ሰዎቹ የተያዙት ስብሰባው ከተካሄደበት ሆቴል አድረው ሲወጡ መሆኑን ለዶቼቬለ ተናግረዋል።
«ምርጫው እስከ ለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ነው የሄደው።ከ9 ሰዓት በኋላ ወደ ቤታቸርው መሄድ ስለማይችሉ እዛው በጉባኤተኛ የተመረጡ የምርጫ አስፈጻሚዎችና የእለቱን ጉባኤ ሲያስተባብሩ የነበሩ ቆጠራ ላይ የነበሩ ወደ አምስት ሰዎች የምርጫ አስፈጻሚ ሶስት አጠቃላይ የምርጫ አስፈጻሚ 8 አካባቢ አጠቃላይ 10 ልጆች ነበሩ።እዚያው ዋቢሸበሌ አድረው ሲወጡ ከያዙት የጉባኤው ሰነድ ጋር ጭምር አንድ ላይ በፖሊስታፍነው ተወስደዋል።»
ድርጅቱ ከሦስት ወራት በፊት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ ማግኘቱን ያስታወቁት አቶ ጀሚል ሳኒ ትናንት እሁድ እስከ ሌሊት ባካሄዱት ስብሰባ የኦዲት እና የቁጥጥር አባላትን ጨምሮ 29 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት እና 7 ተጠባባቂዎች ተመርጠው ዝርዝሩ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተልኳል፤ ውጤቱም በአጭር ጊዜ ይታወቃል ብለዋል።ውጤቱ ከታወቀ በኋላ የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚዎች ተለይተው ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግም ገልፀዋል።
አቶ ጀሚል ፓርቲው የተመሠረተው “ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጉራጌ ሕዝብ ላይ ሕገ – መንግሥታዊ ያሉት ጥያቄ ስለተጠየቀ ብቻ አቃፊ ድርጅት ባለመኖሩ መንግሥት ጠያቂዎችን “መደበኛ ያልሆኑ አደረጃጀቶች” በሚል እየፈረጀ እና እያሰረ መሆኑ፣ ሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶች ለዚህ የማህበረሰቡ ጥያቄ
ኢትዮጵያ ውስጥ ዓመታትን የተሻገረው የፖለቲካ አለመረጋጋት በህዝቡ ላይ ያስከተለው ስጋት ከዕለት ወደ ዕለት እየጠናበት በመሄድ ላይ ነው። በአወዛጋቢ ፖለቲካዊ ትርክትና ግልጽ ባልሆነው የፖለቲካ መርህ በየጊዜው ቅርጻቸውን የሚቀያይሩት ሀገራዊና አካባቢያዊ ጉዳዮች በሚቀሰቅሱት ውዝግብ ሕይወት እየተቀጠፈ፤ በርካቶች ለጉዳት እና እስር እየተዳረጉ ነው።...
ባለፈዉ የካቲት 14 ያደረጉት ንግግር ከሕዝብ የገጠማቸዉን ተደጋጋሚ ተቃዉሞ «አቅጣጫ ለማሳት» ያለመ ነዉ ።በርግጥም ሰዉዬዉ ጥቁር አፍሪቃዉያን የቱኒዚያን ሕዝብ ማንነት ይቀይራሉ፣ የሐገሪቱን ምጣኔ ሐብትም ያራቁታሉ፣ ወንጀለኝነት አስፋፋትዋል እያሉ የነዙት መርዝ ላጭር ጊዜም ቢሆን የበርካታ ቱኒዚያዊያንን ድጋፍ አግኝቷል።...
ሰሞኑን በአዲስ አበባ በተዘጋጀው የአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራችና ላኪዎች ኤክስፖ በርካታ የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ተሳትፈዋል። ኤክስፖው አትክልትና ፍራፍሬ አምርተው ለኢትዮጵያና ለዓለም ገበያ የሚያቀርቡ ኩባንያዎች ምርቶቻቸውን የሚያስተዋውቁበት ነው። ኤክስፖውን የጎበኘው የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ የሚገጥሟቸውን ተግዳዳሮቶች ጠይቋል።...
የኢትዮጵያውያን ካናዳውያን ኔትወርክ ለማህበራዊ ድጋፍና በአሜሪካ የሰዎች ለሰዎች ድርጅት በቦረና ዞኑ ድርቅ ለተጎዱ የሚውል ድጋፍ በማሰባሰብ ላይ ናቸው።ድርጅቶቹ "የቦረና ወገኖቻችንን ማትረፍ የዛሬ ዓድዋችን ነው" በሚል መሪ ቃል በጀመሩት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር እስካሁን አራት ሚሊዮን ብር የሚደርስ አስቸኳይ የዕርዳታ ገንዘብ አሰባስበዋል።...
የኢትዮጵያ መንግሥት በማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ላይ የጣለውን ገደብ በአስቸኳይ እንዲያነሳ ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል አሳሰበ። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ እንዳለው የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ቲክቶክ እና ዩቱብ የተሰኙ የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን ከዘጉ አንድ ወር ሊሆናቸው እንደሆነ አስታውሷል።...
የአውሮጳ ህብረት ስደተኖችና ፈላሳያን ወደ ኅብረቱ እንዳይገቡ ደንበር ላይ የሚያደርገው ቁጥጥር ኢሰብዓዊና ህገወጥ እንደሆነ ነው በብዙዎች ዘንድ የሚነገረው። በአስቸጋሪ ሁኔታና በባህር ጭምር ወደ ህብረቱ የባህር ዳርቻ የሚደርሱትን ሳይቀር ማረፊያ የሚከለክሉ መሆኑን የሰብዓዊና የስደተኖች መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች ይናገራሉ።...
ማስተር አብነት ከበደ ሰሞኑን በተለይ ቦረና ውስጥ ከተከሰተው ድርቅ እና ርሀብ ጋር በተያያዘ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ በተደጋጋሚ ስሙ እየተነሳ ይገኛል። ወጣቱ ቦታው ድረስ በመሄድ ርዳታ ሲለግስ እና ሲያሰባስብ ተስተውሏል።...
ሳልሳይ ወያነ ትግራይ በምህጻሩ ሳወት አስቀድሞ በትግራይ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም ሲወተውት እንደነበር ያስታውሳል። ያኔ ግን ባንዳ የሚል ስም እንደተሰጣቸው የገለጹልን የድርጅቱ የውጭ ጉዳይ ክፍል ኃላፊ አቶ ኃይሉ ከበደ ከሰላም ስምምነቱ እስከ ሽግግር መንግሥቱ ምስረታ አቃፊና አሳታፊ አይደለም ይላሉ።...
የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር አንቶኒዮ ብሊንከን በቅርቡ "በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል" ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። ጉብኝቱ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ግንኙነት ለማጠናከር እድል የሚሰጥ ነው ያሉት የሚኒስቴሩ ቃል ዐቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ባለስልጣኑ መቼ እንደሚመጡ ግን አልገለፁም።...
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለረጅም ጊዜ የሥነ ጽሑፍ መምህር፣ ሐያሲና ተመራማሪ የነበሩት ረዳት ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው ከትናንት በስተያ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል። የስነጽሑፍ ምሁሩን ሥራዎች በቅርብ የሚያውቁ ወገኖች «የኢትዮጵያ የሥነ ጽሑፍ ዋርካ ነው የወደቀው» ይላሉ።...
«በአለማችን በተለያዩ ቦታዎች የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ይፈጸማሉ እነዚ ከባባድ ወንጀሎች በህግ የማይታዩ ከሆነ እና በተለያዩ ምክንያቶች የሚተላለፉ ከሆነ ህገ ወጥነት ህግ እየሆነ ይቀጥላል»...
በቡታጅራ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ እስር ላይ ለሚገኙ ሰዎች መፍትሔ ለመሻት ጠበቆች ጥረት እያደረጉ ነው። ከጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ የታሰሩ ቡታጅራ ተወስደዋል። የመንግሥት እርምጃ የዞኑን ነዋሪዎች ለሐዘን ዳርጓል። የታሰሩት የዞኑ ምክር ቤት አባል ወይዘሮ ጠጄ ደነቀ ወንድም "በብሔር እየተለየ የምንመታበት አገር ሆኗል" ይላሉ...
የተመሰረተው ዞን እንደማይቀለበስ፤ ነገር ግን ስያሜውን ሦስቱ ጎሳዎች ተመካክረው መቀየር ይችላሉ
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ያደርጋል በማለት ምስራቅ ቦረና በሚል የመሰረተው የክልሉ 21ኛ ዞን ኢፍትሃዊ ነው በማለት የጉጂ ህዝብ መቃወሙን ተከትሎ የዞኑ ተወካዮች ቅሬታቸውን ለፌዴራልና ለክልሉ መንግስታት አቀረቡ፡፡ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ በዚሁ ቅሬታ ላይ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የጉጂ የሀገር ሽማግሌዎች ከመንግስት የተመሰረተው ዞን እንደማይቀለበስ፤ ነገር ግን ስያሜውን ሶስቱ ጎሳዎች ተመካክረው መቀየር እንደሚችሉ ተነግሮናል ብለዋል፡፡
ጥያቄያችን ምስራቅ ቦረና በሚል የተሰየመውን ዞን ስሙን ከመቀየርም በላይ ነው ያሉት የጉጂ አባገዳዎችና የሀገር ሽማግሌዎቹ በመንግስት ምላሽ አለመርካታቸውን ገልጸው፤ ውሳኔው የህዝብ በመሆኑ ህዝብ ግን እናወያይበታለን ብለዋል፡፡

የጉጂ ዞን ተወካዮች ቅሬታቸውን ለፌዴራልና ለክልሉ መንግስታት አቀረቡ
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ከአንድ ሳምንት በፊት ሰኞ የካቲት 20 ቀን 2015 ዓ.ም. አደረኩ ባለው 6ኛ የስራ ዘምን 2ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ምስራቅ ቦረና የተባለውን 21ኛ ዞን ከቦረና ሞያሌ፣ ጉቺ እና ዋችሌ ወረዳዎችን፤ ከጉጂ ጉሚ የልደሎ እና ሊበን ወረዳዎች እንዲሁም ነጌሌ ቦረና ከተማን፤ እንዲሁም ከባሌ ዞን መደወላቡ፣ ኦቦርሶ እና ሀረና ቡሉቅ ወረዳዎችን በማካተት መሰረትኩ ብሏል፡፡ በውሳኔው መሰረት ከዚህ በፊት የጉጂ ዞን ዋና ከተማ ሆና ስታገለግል የነበረችው ነገሌ፤ ነጌሌ ቦረና በሚል መጠሪያ የምስራቅ ቦረና ዞን መቀመጫ ትሆናለች፡፡ አዶላ ሬዴ ደግሞ የጉጂ ዞን ዋና ከተማ እንድትሆን መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ይህንኑን ተከትሎም ተቃውሞና አለመረጋጋት በሁለቱ የጉጂ ዞኖች ባለፉት
የጉራጌ ዞን ምክር ቤት አባል የሆኑት ወይዘሮ ጠጄ ደነቀን ጨምሮ በቡታጅራ ከተማ በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎች ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ አሊያም እንዲፈቱ የሕግ ባለሙያዎች ግፊት እያደረጉ ነው። ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ እስር ላይ ከቆዩ 21 ግለሰቦች መካከል የቀድሞ የዞኑ አመራሮች፣ ወጣቶች፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እንደሚገኙበት ለተጠርጣሪዎቹ ጥብቅና ለመቆም ጥያቄ ካቀረቡ የሕግ ባለሙያዎች አንዱ የሆኑት አቶ ቀኙ ሙሉ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።
“ጥብቅና ልንቆምላቸው የሔድን ሰዎች በቅርብ ጊዜ የታሰሩት ቁጥራቸው 21 ነው። በተጠረጠሩበት ወንጀል ፍርድ ቤት መቅረብ ነበረባቸው። ፍርድ ቤት አልቀረቡም” የሚሉት አቶ ቀኙ ተጠርጣሪዎቹ በታሰሩበት ቦታ ለሕግ ባለሙያዎች ውክልና እንዲሰጡ ባይፈቀድላቸውም አራት ጠበቆች ለጉራጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረባቸውን ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል።
https://radiodownloaddw-a.akamaihd.net/downloads/Events/dwelle/dira/mp3/amh/261059B9_2.mp3
“ፍርድ ቤት የማይቀርቡ ከሆነ የኢትዮጵያ ሕግ በሚፈቅደው መሠረት አካልን ነጻ ማውጣት የሚባል ሥነ-ሥርዓት አለ። በዚያ ሥነ-ሥርዓት መሠረት ፍርድ ቤት እነዚህ ሰዎች የተያዙበት መንገድ አግባብ ስላልሆነ፤ ፍርድ ቤትም ስላልቀረቡ የሚፈቱበትን ትዕዛዝ እንዲሰጥ ለመጠየቅ ለመወከል ነው ያሰብንው” ሲሉ ጠበቃው ተናግረዋል።
በቡታጅራ ከተማ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በእስር ላይ ከነበሩት 21 ሰዎች መካከል ሁለቱ ባለፈው ማክሰኞ እና ረቡዕ ተፈተዋል። የጉራጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የደቡብ ፖሊስ ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ ጉዳይ ላይ ምላሽ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን ጉዳዩ ለመጋቢት 6 ቀን 2015 ተቀጥሯል።

በቡታጅራ፣ ወልቂጤ፣ ቋንጤ እና እና አዲስ አበባ የታሰሩ ሰዎች የጉራጌ ዞን ክልል እንዲሆን ከሚደረገው ግፊት ጋር በተያያዘ በቁጥጥር የዋሉ ናቸው።
በቡታጅራ በእስር
የሶማሌ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱቃድር ረሺድ ለዶይቼ ቬሌ በስልክ በሰጡት መረጃ ዳዋ ፣ አፍዴር እና ሊበን ዞኖች በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ተናግረዋል። በድርቁ ምክንያት ሶስት ነጥብ ስምንት ሚሊየን ህዝብ በምግብ እጥረት ውስጥ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።...
የዘንድሮው የጎርጎሮሳዊው ዓመት "ዓለምአቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት" አሸናፊ የሆነችው መዓዛ፣"ሮሃ"በማለት በሰየመችው የዩቲዩብ ቴሌቪዥን ጣቢያ መስራችና ባለቤት በመሆን በጋዜጠኝነት ትሰራለች...
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ አምስት የደቡብ ክልል ምክር ቤት እንደራሴዎችን ጨምሮ አለአግባብ ታሥረውብኛል ያላቸውን ስድስት የፓርቲውን አባላት መንግሥት በአስቸኳይ እንዲፈታ ጠየቀ፡፡ ፓርቲው እንዳለው በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን የሚገኙ ስድስት አባላቱ ከህገ ውጪ ከታሠሩ ከሳምንት በላይ ቢሆናቸውም እስከአሁን ግን ፍርድ ቤት አልቀረቡም።...
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት "በትንሹ ያደጉ" የሚባሉ 46 ደሐ አገሮች ጉባኤ በቃጣር በመካሔድ ላይ ይገኛል። የድሆቹ አገራት መሪዎች እና ባለሥልጣናት በቃጣሩ ስብሰባ ሮሯቸውን እያሰሙ ነው። ይኸ ቡድን ከተመሠረተ አምስት አስርት ዓመታት ቢሻገርም ይኸ ነው የሚባል ለውጥ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ነዋሪዎች ላሏቸው አገራት አልታየም።...
ይህ መተግበሪያ ስራ ፈላጊን ከቀጣሪ ጋር ለማገናኜት የሚያገለግል ሲሆን፤ በተለይ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ሴቶች ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ያደርጋል።የመተግበሪያው ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ትግስት አፈወርቅ እንደሚሉት በዲጅታል መድረኩ በብዛት የሚፈለጉ ሴት ሰራተኞች ቢሆኑም እስካሁን ተጠቃሚ የሆኑት ግን 30 በመቶ ብቻ ናቸው ።...
በአፍሪቃው ቀንድ አካባቢ የሚደጋገመው ድርቅ ባለፉት ሦስት ዓመታት ደግሞ ተጠናክሮ በሰውም በእንስሳትም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ቀጥሏል። ቆላማውን አካባቢ በተቀናጀ ስልት በድርቅ ተደጋግሞ ከመጎዳት መከላከል እንደሚቻል የደን እና የተፈጥሮ አካባቢ ተመራማሪዎች ይናገራሉ።...
ኢትዮጵያ ዉስጥ መንግስታት ቢፈራረቁም የድርቅና የረሐቡ ድግግሞሽ ከ10 ወደ አምስት፣ ከአምስት ወደ 3 ዓመታት እየፈጠነ፣ በቅርቡ ደግሞ ከዓመት ዓመት እየቀጠለ፣ለረሐብ የሚጋለጠዉ ሕዝብ ብዛትም በ20 ሚሊዮኖች ይቆጠር ይዟል።...
ጀርመን በተለይም ከፍተኛ ክህሎት ያላቸውን የውጭ ዜጎች ለማስገባት ሕጎችን ብታወጣም መስፈርቶቹ የሂደቱ ውስብስብነትና አዝጋሚነት ብዙዎችን ሊስብ አልቻለም። ሚኒስትር ኃይል በዚህ ረገድ ችግሮች መኖራቸውን አምነው የትምህርት ማስረጃዎች እውቅና አሰጣጥ ፣ የቪዛ መጓተትና የመሳሰሉት ከተስተካከሉ ሁሉም ወገን ተጠቃሚ ይሆናል የሚል ተስፋ ሰጥተዋል።...
ይህ የህዝብ ቁጣ መንገድ በመዝጋት ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን አስተጓጉሏል፡፡ በተነሳው አመጽም እስካሁን ከቦሬ ሦስት ከአዶላ አንድ ሰው ህይወታቸው አልፈዋል፡፡...
«ቃል ሁልግዜም ይገባል ለምሳሌ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወይም ድህነትን ለማስወገድ፣ ክትባቶችን ለማምረት ሊሆን ይችላል። ግን ተግባራዊ ለማደረግ ቁርጠኘነት አይታይም።»...
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ያደርጋል በማለት ምሥራቅ ቦረና በሚል የመሰረተው የክልሉ 21ኛ ዞን አሁንም ማወዛገቡን እንደቀጠለ ነው፡፡
የጉጂ ዞን በመሆን ለዓመታት ያገለገለችውን ነገሌ ከተማ ነገሌ ቦረና በሚል ስያሜ ይመሰረታል ለተባለው ለአዲሱ ዞን ማስረከቡ በጉጂ ዞን በዋናነት ቁጣውን የቀሰቀሰ ዐቢይ ጉዳይ ሆኗል፡፡
የክልሉ መንግሥት ምክር ቤት አደረኩ ባለው 6ኛ የሥራ ዘመን 2ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ምሥራቅ ቦረና የተባለውን 21ኛ ዞን ከቦረና፣ ጉጂ እና ባሌ ዞኖች የተወሰኑ ወረዳዎችን በማገኛነት መሰረትኩ ማለቱ በተለይም በጉጂ ዞን ባስነሳው ተቃውሞ ቢያንስ እስካሁን የአራት ሰው ህይወት ጠፍቷል፡
https://radiodownloaddw-a.akamaihd.net/downloads/Events/dwelle/dira/mp3/amh/23994A20_2.mp3
አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ ነዋሪዎች ውሳኔው ካልተቀለበሰ ለአከባቢው ሰላምና ፀጥታ አስቸጋሪ ያሉትን ስጋት ሊያስከትል እንደሚችልም አመልክተዋል፡፡
«ሰሞኑን በመንግሥት አንድ ውሳኔ ተላልፏል፡፡ ይህ ውሳኔም ለ20 ዓመታት ገደማ የጉጂ ዞን ሆና ስታገለግል የነበረችወን ነገሌ ከተማን ነገሌ ቦረና በሚል ስም ከጉጂ ዞን አስወጥቶ ምሥራቅ ቦረና በሚል ስያሜ ለተመሰረተው አዲስ ዞን መዋቅር ይሰጣል ነው የተባለው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ይህ ዞን ከጉጂ ሊበን እና ጉሚ የልደሎ የተባሉ ሁለት ወረዳዎች እና ከባሌ ሦስት ወረዳዎችን ቆርሶ ለምሥራቅ ቦረና ዞን የሚሰጥ ነው ተብሏል፡፡ አሁን በከፍተኛ የድርቅ ችግር ውስጥ ላለው ህዝብ ሌላ እራስ ምታት ባልተገባው ነበር፡፡ ውሳኔው እንደተባለው ለመልካም አስተዳደር የተደረገ የሚመስል አይደለም፡፡»

ይህን አስተያየት የሰጡን የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የአዲስ ዞን ምስረታ ቅሬታ የገባቸው የጉጂ ዞን ቦሬ ወረዳ ነዋሪ ናቸው፡፡ ሌላው በመምህርነት ሙያ የተሰማሩት የሰባ
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ነሰቦ ወረዳ በደረሰ ጥቃት በትንሹ 12 ሰዎች ተገደሉ ፡፡

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ነሰቦ ወረዳ በደረሰ ጥቃት በትንሹ 12 ሰዎች ተገደሉ ፡፡ ነዋሪዎች እንዳሉት ጥቃቱ ባለፈው ዓርብ የተፈጸመው በወረዳው ቦጬሳ በተባለ ቀበሌ ውስጥ ነው ፡፡ ከሟቾቹ አብዛኞቹ የሲዳማ ብሄር ተወላጅ አርሶአደሮች መሆናቸውን በሥፍራው ነበርን ያሉ አይን አማኞች ለዶቼ ቬለ/DW/ ተናግረዋል ፡፡ ግድያው የተፈጸመው ለስብሰባ ትፈለጋላችሁ በሚል በቀበሌው መስተዳድር ጥሪ ከተደረገላቸው በኋላ መሆኑን ነዋሪዎቹ አክለዋል፡፡
በተሰበሰበው ነዋሪ ላይ ከተለያዩ አቅጣጫዎች በተከፈተው ተኩስ ሦስት ሰዎች ወዲያው መገደላቸውንና የተቀሩት አሥር ሰዎች ደግሞ በመሸሽ ላይ እንዳሉ በጥይት ተመትተው መሞታቸውን ነው ከዓይን አማኞቹ አንዱ ለዶቼ ቬለ DW የገለጹት፡፡ በጥቃቱ ቡርቃ ቡታሮ እና ሳሙኤል ቡታሮ የተባሉ ሁለት ወንድሞቻቸው እንደተገደሉባቸው ለዶቼ ቬለ የገለጹት ቴሶ ቡታሮ የተባሉ አንድ የአካባቢው ነዋሪ በበኩላቸው « ጥቃቱ የግፍ አገዳደል ፤ ሁኔታውም የዘር ጭፍጨፋ ይመስላል»’ ብለዋል ፡፡
በጥቃቱ በጥይት ተመተው የቆሰሉ በርካታ ሰዎች በአጎራባች የሲዳማ ክልል በሚገኘው የጭሪ ወረዳ ጤና ጣቢያ መወሰዳቸውን የዓይን አማኞቹ ገልጸዋል ፡፡ የሐዋሳው ወኪላችን ሽዋንግዛው ወጋዩሁ ስለጥቃቱ በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ አርሲ ዞን መስተዳድር እና የሲዳማ ክልል የፀጥታ ኃላፊዎችን ለማነጋገር ጥረት አድርጓል ፡፡ ይሁንእንጂ በሁለቱም በኩል የሚገኙ የሥራ ሃላፊዎች «ሁኔታውን እያጣራን እንገኛለን» የሚል አጭር ምላሽ በመስጠታቸው እስከአሁን ሥለጥቃቱ ዝርዝር መረጃ ማግኘት አልተቻለም ፡፡ ያም ሆኖ አንድ ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ በሲዳማ ክልል የጭሪ ወረዳ ጤና
አዲስ የተመሠረተው የሸገር ከተማ ባለሥልጣናት “ህገወጥ” የተባሉ መኖሪያ ቤቶች ማፍረሳቸው ነዋሪዎችን ለማህበራዊ ቀውስ እየዳረገ ነው፡፡ ቤት የፈረሰባቸው ከነልጆቻቸው በዘመድ ግቢ በሸራ ለመኖር መገደዳቸውን፤ በዋጋ ውድነት መከራየት መቸገራቸውን ይናገራሉ። የሸገር ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ተሾመ አዱኛ እየተወሰደ ያለው እርምጃ በፈጠረው ቀውስ አይስማሙም።...

ኢትዮጵያ ከ1960ዎቹ ጀምሮ እንደኖረችበት አምናና ዘንድሮም ጦርነት፣ግጭትና ዉዝግብ አልበቃ ያላት ይመስል በረሐብና ድርቅ የዓለም ርዕስ ሆናለች።በ1965 እና 66 የቀድሞዉን የንጉሰ ነገስት አፄ ኃይለስላሴን ዙፋናዊ አገዛዝ ለማስወገድ ተቃዋሚዎቻቸዉ እንደዋና መሳሪያ ከተጠቀሙባዎቸዉ ችግሮች አንዱ በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ሕዝብ በረሐብ መሰቃየቱ ነበር።በ1977ና 78 ኢትዮጵያን በመታዉ ድርቅ 5 ሚሊዮን ያክል ሕዝብ ለረሐብ መጋለጡ ዓለምን ጉድ አሰኝቶ፣ የደርግን መንግስት ለማሳጣት ዋና መሳሪያ ነበር።
ኢትዮጵያ ዉስጥ መንግስታት ቢፈራረቁም የድርቅና የረሐቡ ድግግሞሽ ከ10 ወደ አምስት፣ ከአምስት ወደ 3 ዓመታት እየፈጠነ፣ በቅርቡ ደግሞ ከዓመት ዓመት እየቀጠለ፣ለረሐብ የሚጋለጠዉ ሕዝብ ብዛትም በ20 ሚሊዮኖች ይቆጠር ይዟል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ የርዳታ ድርጅቶች እንዳስታወቁት ባለፉት ተከታታይ አራት ዓመታት ዝናብ በመሳቱ ከ25 ሚሊዮን የሚበልጥ ኢትዮጵያዊ ለምግብ እጥረት ተጋልጧል።

በተለይ ኑሮዉን በከብት ርባታ ላይ ያደረገዉ ከ12 ሚሊዮን የሚበልጥ የቦረና፣ የጉጂ፣ የደቡብ ኦሞ ዞኖችና የሶማሌ ክልል ነዋሪ ረሐብ ከየቀየዉ እያፈናቀለዉ፣አለያም በያለበት እያሰቃየዉ ነዉ።ለሕፃናት መብት የሚሟገተዉ ሴቭ ዘ ችልድረን ባለፈዉ ጥር እንዳስታወቀዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወደ አራት ሚሊዮን የሚጠጉ ሕፃናት በቂ ምግብ አያገኙም።የጀርመኑ ግብረ ሰናይ ድርጅት ቬልት ሑንገር ሒልፈ እንዳለዉ ደግሞ በተከታታይ በድርቅ በተመቱ እንደ ቦረና፣ሐመርና ኦጋዴንን በመሳሰሉ አካባቢዎች የሕዝቡ ዋና መተዳደሪያ የነበሩ ከ3.5 ሚሊዮን የሚበልጡ የቤት እንስሰዎች አልቀዋል።
ዝናብ የለም።ምርት የለም።ከብት የለም።ምግብ የለም-ኢትዮጵያ።ለመሆኑ ሌላዉ ኢትዮጵያዊ ይኸ ሁሉ ወገኑ መፅዋቾችን ሲማፀን ምን እያለ ምንስ እያደረገ ይሆን? የብዙ ወንዞች መፍለቂያ፣ የለም አፈር ባለቤቲቱ ኢትዮጵያ ድርቅና ረሐብ እንደተጣባት፣አስከሬንና አፅም
ማህበራዊ ቀውስን ፈጥሯል የተባለው የሸገር ከተማ ቤቶች ፈረሳ እና የመንግስት ምላሽ
አዲስ የተመሠረተው የሸገር ከተማ ባለሥልጣናት “ህገወጥ” የተባሉ መኖሪያ ቤቶች ማፍረሳቸው ነዋሪዎችን ለማህበራዊ ቀውስ እየዳረገ ነው፡፡ ቤት የፈረሰባቸው ከነልጆቻቸው በዘመድ ግቢ በሸራ ለመኖር መገደዳቸውን፤ በዋጋ ውድነት መከራየት መቸገራቸውን ይናገራሉ። የሸገር ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ተሾመ አዱኛ እየተወሰደ ያለው እርምጃ በፈጠረው ቀውስ አይስማሙም።

የሁለት ልጆች አባት እና የአራት ቤተሰብ አባላት አስተዳዳሪው አቶ ልጃለም አበበ አዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው ለገጣፎ ለገዳዲ ከስምንት ኣመታት በፊት ከአርሶ አደር ከገዙት መሬት ገዝተው የገነቡት እና ለስድስት ዓመታት የኖሩበት ቤት ፈርሶባቸዋል። “አንድ ዘመድ ጋ ግቢ ውስጥ ተጠልዬ ዕቃዬን ዝናብ እና ጸሐይ ይፈራረቅበታል” የሚሉት አቶ ልጃለም “ልጆቼን ሸራ ውስጥ አድርጌ ነው የምኖረው” ሲሉ ያሉበትን ሁኔታ ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል።
ያለምንም ማስጠንቂቃ የመኖሪያ ቤታቸው እንደፈረሰባቸው የገለጹት አቶ ልጃለም “እኛ አካባቢ ብቻ 460 ገደማ ቤት በአንድ ቀን ውድም ያደረጉት” ሲሉ ተናግረዋል። “ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነን እንዲህ አይነት ግፍ መፈጸሙ በጣም ከባድ ነው” የሚሉት ልጃለም “እንደዚህ አይነት ታሪክ ይፈጠራል” ብለው እንዳልጠበቁ ያስረዳሉ።
ብሔር ተኮር ትንኩሳ ይደርስብናል የሚሉት እኚህ ተፈናቃይ በተለያዩ ቦታዎች መጠለያም ጠይቀው እስካሁን አለመሳካቱን ገልጸዋል፡፡ “ይህ መሬታችን ነው አገራችሁ ግቡ እንባላለን። ደብረብርሃን ከተማም መጠለያ እንዲሰጠን ቅሬታ አስገብተን እስካሁን ምላሽ አላገኘንም፡፡ እዚህ በሸራ ተጠልለን ልጆቻችን በጅብ እንዳይበሉብን ነው አሁን ስጋታችን። መዳረሻችን ጠፍቶ መንግስት እንዲደርስልን ነው የምንጠይቀው” ሲሉ አቤቱታቸውን ለዶይቼ ቬለ ገልጸዋል።
በአዲስ
``እንዲህ ያለው ስልጠና ቀደም ብሎ ለአዳጊዎች በትምህርት ቤት ደረጀ መሰጠት ቢጀመር ኖሮ የአስተዳደር እና የአመራር ብቃት ያለው ትውልድ ማፍራት ይቻላል``
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የክልሉን ሕዝብ ተጠቃሚ ያደርጋል ያለውን አስተዳደራዊ አደረጃጀቶችን እና አሠራሮችን በመዘርጋት ላይ መሆኑን በማስረዳት 21ኛ የክልሉ ዞን እንዲመሰረት ውሳኔ ማሳለፉ የተሰማው በዚሁ ሳምንት ነበር ። ይህንን ውሳኔ ተከትሎ በጉጂ ዞን በዚህ ሳምንት የሰው ሕይወትም ያለፈበት የተቃውሞ ሰልፍም መደረጉ ይታወሳል፡፡...
ትናንት አዲስ አበባ ምኒልክ አደባባይ ላይ በተከበረው 127ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ ክብረ በዓል ላይ የጸጥታ ኃይሎች በፈጸሙት ከልክ ያለፈ የኃይል አጠቃቀም አንድ ሰው መገደሉንና ሌሎች የበዓሉ ታዳሚዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ ።...
ኒቆዲሞስ ኤሊያስ ገና ሚኒስትሪ ፈተና እንኳን አልተፈተነም። ነገር ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ የፕሮግራሚንግ ባለሙያ ሊሆን ችሏል። የ 14 ዓመቱ አዳጊ ወጣት እንደ ኔትፊሊክስ እና አማዞን የመሳሰሉ የተለያዩ ድረ ገጾችን አስመስሎ ሊሰራ ችሏል።...
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ ቡድን ሥራ እንዲቋረጥ ያቀረበችውን ጥያቄ በርካታ ዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ተቃወሙት ። ተቋማቱ ያሳሰባቸው ምንድን ነው?...
አድዋ ሲዘከር የአጼ ምኒሊክ እና የጦር አበጋዞቻቸው ተክለ ስብዕና ዘመን ተሻግሮ ያወዛግባል። ከ127 ዓመታት በፊት ለነጻነታቸው ቀናዒ በነበሩ ኢትዮጵያውያን የተገኘው ድል ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ ዜጎች የተሳተፉበት ነው። ታዲያ የአድዋ ዝክር ለምን ያወዛግባል? ወደፊትስ እንዴት ይዘከር?...
127 ኛውን የአድዋ ድል በአል አስመልክቶ «አድዋ ፓን አፍሪቃ ፎረ» ም በሚል ወጣቶች እና ቢዝነስን ማዕከል ያደረገ የፓናል ውይይት በ አዲስ አበባ እና በደቡብ አፍሪቃ ኬፕታውን ከተማ ትናንት ተካሄድዋል።...
127 ኛውን የአድዋ ድል በአል አስመልክቶ «አድዋ ፓን አፍሪቃ ፎረ» ም በሚል ወጣቶች እና ቢዝነስን ማዕከል ያደረገ የፓናል ውይይት በ አዲስ አበባ እና በደቡብ አፍሪቃ ኬፕታውን ከተማ ትናንት ተካሄድዋል።...
በዎላይታ ዞን የሚንቀሳቀሱ ሁለት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዎላይታ በተካሄደው ህዝበ ውሳኔን ላይ ያሳለፈው ውሳኔ «ተገቢና ታሪካዊ» ነው አሉ። ቦርዱ ህዝበ ውሳኔው ማጭበርበር ታይቶበታል ሲል በድጋሚ እንዲካሄድ መወሰኑን የደገፉት የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ ዎብን እና የዎላይታ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ዎህዴግ ናቸው።...
127 ኛው የአድዋ ድል ክብረ በዓል በብሔራዊ ደረጃ «አንድነት፣ ጀግንነት እና ጽናት» በሚሉ መሪ ሀሳቦች ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ተከብሯል። ሆኖም በበዓሉ አክባሪዎች እና በሥነ ሥርዓት አስከባሪ ፖሊሶች መካከል ፍጥጫ መፈጠሩ ተሰምቷል። ፖሊሶችም የበዓሉን ታዳሚ ለመበተን አስለቃሽ ጢስ ሲተኩሱና ድብደባ ሲፈጽሙ ታይተዋል።...
ወጣት ኡስማን በላይ የ12ኛ ክፍል ትምህርቱን በጥሩ ውጤት አጠናቆ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ለመግባት በመጠባበቅ ላይ የሚገኝ የ18 ዓመት አዳጊ ሲሆን፤ መንገድ ላይ ተፈላጊ ወንጀለኛን የሚለይ ቴክኖሎጅን ጨምር ከ20 በላይ የፈጠራ ስራዎችም አሉት። ወጣቱ ለወደፊቱም ከሀገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ወደ ውጭ የሚላክ የቴክኖሎጅ ውጤት የማልማት ህልም አለው።...
የቡድን 20 አገራት የገንዘብ ሚኒስትሮች እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በሣምንቱ መጨረሻ የኢትዮጵያ የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ “በፍጥነት እንዲጠናቀቅ” ጥሪ አቅርበዋል። ወደ 27 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ዕዳ ያለበት የኢትዮጵያ መንግሥት በአከፋፈል ረገድ ሽግሽግ ለማድረግ ጥያቄ ያቀረበው በሐምሌ 2013 ቢሆንም እስካሁን ድርድሩ ፈቅ አላለም...
በአባል ሀገራት መካከል የስራ ቅጥር እና የሰራተኞች ነጻ እንቅስቃሴ ላይ የተነጋገረውየ 2015 የ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለሥልጣን (ኢጋድ)ስብሰባ የአባል ሀገራት ሰራተኛ ዜጎች በቀጠናው ያለምንም ችግር በነጻነት ተንቀሳቅሰው የሚሰሩበትን መንገድ እንደዚሁም ሕጋዊ የስራ ፈቃድ የሚያገኙበት ሕግ እና አሰራር ላይ ተወያይቷል።...
በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ 130ሺህ የሚሆን የአበርገሌና ፃግብጂ ወረዳ ተፈናቃይና በህወሓት ቁጥጥር ስር ያሉ ነዋሪዎች ችግሮች በአፋጣኝ የማይፈታ ከሆነ በሰላማዊ ሰልፍ ችግሩን ለዓለም ማህበረሰብ አሳውቃለሁ ሲል አስጠንቅቋል። ነዋሪዎቹ ለከፍተኛ ሰብዓዊ ችግሮች ተዳርገዋል ይላል አስተዳደሩ።...
በትግራዩ ጦርነት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እንዲመርምር በተመድ የተቋቋመው የባለሙያዎች ቡድን ስራ እንዲቋረጥ ኢትዮጵያ ጥረት እያደረገች ነው። አምነስቲ ጥያቄው በሌሎች አገሮች ጭምር አሉታዊ ተጽእኖ ሊያሳድር የሚችል፣ የሰብዓዊ ምክርቤቱንም ተዓማኒንነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባና ለመብት ጥሰት ሰለባዎች ፍትህን የሚነሳ ነው ሲል ተቃውሟል።...