Home › View all posts by DW Amharic
Blog Archives
ህወሓት ሊያደርገው ያቀደው ጉባኤ በፓርቲው ቁጥጥር ኮምሽን ተቃውሞ ገጥሞታል። የህወሓት ቁጥጥር ኮምሽን ባወጣው መግለጫ 14ተኛ የህወሓት ጉባኤ ለማድረግ የሚደረገው እንቅስቃሴ በማውገዝ ተወካዮቹ ከጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ ራሳቸው ማግለላቸው አስታውቋል።...
«የሩጫ ዉድድር ለኢትዮጵያዉያን ባህል ነዉ። ከሻንበል አበበ ቢቂላ የሮማ ኦሎምፒክ የማራቶን ድል ወዲህ በስፖርቱ መንደር የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ከፍ ብሎ እንዲዉለበለብ ያደረገ ነዉ። አትሌቲክስ የኢትዮጵያ መታወቅያ ነዉ።»...
በጎርጎሪዮሳዊው 1950 በርካታ የአፍሪቃ ሃገራት ከቅኝ ተገዢነት ነጻ ወጥተው ሉዓላዊነታቸውን አግኝተዋል። ደቡብ ሱዳን፤ ኤርትራና ናሚቢያ ከአፍሪቃ ሃገራት ተጽዕኖ ተላቀው ነጻ መንግሥታት ሆነዋል። እንዲያም ሆኖ ግን የአፍሪቃ ሃገራት ነጻ መንግሥታት መሆን የኤኮኖሚም ብልጽግናም ሆነ የአካባቢ መረጋጋትን ሊያመጣ እንዳልቻለ ነው ተንታኞች የሚገልጹት።...
ደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኘው ጎፋ ዞን በተከሰተው የመሬት ናዳ ክፉኛ ለተጎዱ ዜጎች መሠረታዊ የሰብአዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ለዶቼ ቬለ ገለፁ።...
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በኮምፒዉተር ሳይን እና ተያያዥ የትምህርት መስኮች የተማሩ ኢትዮጵያዉያን ወጣቶችን እያደኑ በኦንላይን የገንዘብ ምንተፋ ተግባር የሚያሰማሩ እንደ ታይላንድ ፣ ማይናማር እና ላኦስን በመሳሰሉ ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ኩባንያዎች ተበራክተዋል።...
ፕሬዚዳንቱ ትላንት ምሽት ከነጩ ቤተመንግስት ጽሕፈት ቤታቸው ባደረጉት ንግግር፣ለዲሞክራቲክ ፓርቲው ፕሬዚዳንታዊ ዕጩነት የደገፏቸው ካማላ ሃሪስን፣" ደፋርና ራዕይ ያላት መሪ" ሲሉ አወድሰዋቸዋል። ጆሴፍ ባይደን፣ድጋሚ የመመረጥ ፉክክራቸውን የማቆም ውሳኔያቸው፣የሃገሪቱን ዴሞክራሲ ለመከላከል የተወሰደ እርምጃ እንደሆነ አመልክተዋል።...
ባለፈው በቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ላይ ከተካሄደ የግድያ ሙከራ ጋር በተያያዘ ከሃላፊነታቸው በለቀቁት በቺትል ምትክ የመስሪያ ቤቱ ምክትል ሃላፊ ሮናልድ ሮዌ ለጊዜው በተጠባባቂነት የቺትል ስራ ተረክበዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በትራምፕ ላይ ስለተፈጸመው የግድያ ሙከራ የሚካሄደው ምርመራ እንደቀጠለ ነው።...
በመሬት መንሸራተት አደጋው ህይወታቸው ያለፈ ቀሪ ሰዎችን የመፈለጉ ሂደት አሁንም መቀጠሉን የገዜ ጎፋ ወረዳው ባለሥልጣናት አስታውቀዋል ፡፡ በአሁኑ ወቅትም ከ40 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ከአፈር በታች ይገኛሉ የሚል ጥርጣሬ መኖሩን የወረዳ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ማስረሻ ማንአየ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል ፡፡...
አቶ ታየ ደንደኣ ለችሎቱ ባቀረቡት ጥያቄ ሁለት የእጅ ስልኮቻቸው፣ አንድ ላፕቶፕ ኮምፒዩተር እና «መደመር ሲመረመር» የሚል ረቂቅ ጽሁፍ እንዲመለሱላቸው ጠይቀው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ማስተላለፉ የሚታወስ ነው፡፡ አቶ ታዬ ደንደኣ ልጆቻቸውና ቤተሰቦቻቸው ሲኖሩበት ከነበረው ቤት ያለ አግባብ መበተናቸውን በቅሬታቸው አክለዋል፡፡...
አንድ የአላማጣ ከተማ ነዋሪ ተፈናቃዮቹ ከትግራይ ተመልሰው ወደ አላማጣ መኖሪያቸው የገቡ ቢሆንም ተዋጊ የነበሩና የታጠቁ አካላት አሁንም በየትምህርት ቤቶች ሰፍረዋል ብለዋል፣ በአካባቢው ያለው የመከላከያ ሰራዊት እነኚህ አካላት የከተማዋ ቀደምት ነዋሪ ካልሆኑ እንዲወጡ ይደረጋል የሚል ተስፋ እንደሰጣቸውም አስተያየት ሰጪው ገልጠዋል፡፡...
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ ትኩረት እና ሰፊ ጥናቶች እየተደረገበት የሚገኘው «ስፓሩሊና» ውሃ ውስጥ የሚገኝ ወደ ሰማያዊ የሚያደላ አረንጓዴ ቀለም ያለው የአልጌ አይነት ነው። ባለሙያዎች እንደሚሉት ስፓሩሊና በአንድ ህዋስ ውስጥ ፕሮቲን፣ ቫይታሚን፣ ስብ፣ ማዕድናት እና ካርቦሃይድሬትን በመያዝ ብቸኛው ማይክሮ አልጌ ነው።...
ጆ ባይደን ከፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ራሳቸውን ሲያገልሉ ዴሞክራቶች የመነቃቃት አዝማሚያ አሳይተዋል። በንግድ ሥራ የተሰማሩ ኩባንያዎች በአንጻሩ ካማላ ሐሪስ የመጀመሪያዋ ሴት የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነው ቢመረጡ በኤኮኖሚው ረገድ ምን ለውጥ እንደሚኖር እርግጠኞች አይደሉም። በርካታ ኩባንያዎች ግብር ለመቀነስ ቃል የገቡት ዶናልድ ትራምፕ እንዲመረጡ ይደግፋሉ።...
በትግራይ «ሕግ ማስከበር» ያለው ዘመቻ መጀመሩን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ። በዚህ ዘመቻ በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ የማዕድናት ምዝበራ፣ መሬት ወረራ እና ሌሎች ወንጀሎች ተሳትፎ ያላቸው አካላት በቁጥጥር ስር እንደሚውሉ የአስተዳደደሩ ምክትል ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ተናግረዋል።...
“የሠው ልጅ እንደ ድንች ከመሬት እየተቆፈረ ሲወጣ አይቼ አለቀስኩ» ይላሉ በጎፋ ዞን ስለደረሰው አሰቃቂ የመሬት መንሸራተት አደጋ ለዶቼ ቬለ የገለጹ አንድ የዐይን እማኝ። እስካሁን በተደረገ ቁፋሮ ከ229 በላይ አስክሬን ሲወጣ ሰባት ሰዎች ከአንገት በታች በአፈር ተቀብረው በሕይወት መገኘታቸውን የዞኑ ባለሥልጣናት ገልጸዋል።...
ኦርባን በጉብኝቶቻቸው በግልጽ የአውሮጳ ኅብረትን እወክላለሁ ባይሉም አንዳንዶች እንደሚሉት ግን የዚያ አይነት ስሜት ለማሳደር ሞክረዋል። የሩስያ ዩክሬን ጦርነት እንዲያበቃ አንድ ነገር መደረግ አለበት በሚለው አቋማቸው አሁን ወደፊት ገፍተዋል። በተአምር ጦርነቱ ያበቃል ብለን መጠበቅ የለብንም ብለዋል። ኅብረቱ ግን እርምጃቸውን ውድቅ አድርጓል ።...
ባሳለፍነው ሳምንት የመጨረሻ ቀናት በርካቶቹ የደቡብ አውሮጳ ሃገራት 40 ዲግሪ ከደረሰ ኃይለኛ ሙቀት ሲታገሉ፤ በአንጻሩ ኔዘርላንድ ገና መሞቅ የጀመረውን የበጋ ወራት ማጣጣም መጀመሯ ተሰምቷል። በምህረት የለሹ የሰሜን አትላንቲክ በረዷማ የክረምት ወራት የሚኮማተረው ሰውነት በጋውን ብዙም ሳያጣጥመው ነው ዘንድሮ ኃይለኛ ሙቀት የተከሰተው።...
ሳዑዲ አረቢያ ባለፉት ስድስት ወራት 100 ሰዎችን በሞት ከቀጣች በኋላ በሀገሪቱ የሞት ቅጣት በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን በአውሮጳ የሳዑዲ አረቢያ የሰብአዊ መብቶች ተመልካች ድርጅት አስታወቀ። ድርጅቱ ከሰሞኑ በመግለጫ እንዳለው ሃገሪቱ በያዝነው ዓመት የተፈጸመው የሞት ቅጣት ካለፈው የ2023 ጋር ሲነጻጸር የ42 ከመቶ ብልጫ አሳይቷል።...
የአውሮጳ ኅብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የአውሮጳውያኑን የበጋ ወቅት የመጀመሪያ ስብሰባቸውን ትናንት በብራስልስ አካሂደዋል። በዚህም ወቅት በበርካታ ዓለም አቀፍ ጉዳዮች በተለይም በዩክሬንና የመካከለኛው ምሥራቅ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎች አሳልፈዋል።...
በኦሮሚያ ክልል በታጠቁ አካላት ተነጣጥሮ ነበር የተባለ አገር የማፍረስ ልዩ ልዩ ሙከራ መንግስት መቀልበሱን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ፡፡ ሽመልስ እየተካሄደ ባለው የክልሉ ምክር ቤተ መደበኛ ጉባኤ ላይ እንደተናገሩት፤ በሺዎች የሚቆጠሩ አማጺያን ታህድሶ ስልጣና ወስደው ከህብረተሰቡ ጋር መቀላቀላቸዉን ተናግረዋል።...
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃድያ ዞን የሾኔ የመጀመሪ ደረጃ ሆስፒታል ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማ መቱ፡፡ የሁለት ወራት ደሞዛችን ይከፈለን የሚለው ጥያቄ የአድማው መነሾ ምክንያት ነው ተብሏል ፡ ሠራተኞቹ ሥራ መቆማቸውን ለዶቼ ቬለ ያረጋገጡት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር የሠራተኞቹን ጥያቄ ለዞንና ለክልል መስተዳድሮች ማሳወቃቸውን ተናግረዋል ፡፡...
ጆ ባይደን ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ፉክክር ራሳቸውን ማግለላቸውን ተከትሎ፣ ምክትላቸው ካማላ ሃሪስ ከዲሞክራቶች ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ እየተቸራቸው ነው። ባይደን፣ፕሬዚዳንታዊ ዕጩ ሆነው መመረጣቸውን ላለመቀበልና ሙሉ ኃይላቸውን በቀሪው የፕሬዚዳንትነት ጊዜያቸው በሚሰጡት አገልግሎት ላይ ለማዋል መወሰናቸውን ያስታወቁት በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው ነዉ።...
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት የሟቾች ቀጥር ከ55 በላይ መድረሱን የአካባቢው አስተዳደር አስታወቀ። ከሟቾቹ መካከል ሴቶች፣ ሕጻናት እና አደጋ የደረሰባቸውን ለመታደግ ወደ ቦታው ያቀኑ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ፖሊሶች ይገኙበታል።...
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን በሚገኙ ስደተኞች ላይ ልታወቁ ታጣቂዎች በወሰዱት ጥቃት ሁለት ሱዳናውን ስደተኞች መገደላቸውንና ሌሎች 10 መቁሰላቸውን ስደተኞችና የተ.መ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን (UNHCR) አስታወቁ፡፡ ከመጠለያው ከወጡ ስደተኞች መካከል ከ560 በላይ የሆኑት “አፍጥጥ” ወደተባለ አዲስ መጠለያ መዛወራቸው ተመልክtቷል።...
ኢትዮጵያውያን አንጋፋ አትሌቶች የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አትሌቶች በሚል ስማቸው በዓለም መድረክ ጎልቶ ተጠርቷል ። የፓሪስ ኦሎምፒክ ሊጀመር አራት ቀናት ብቻ ቀርተውታል ። ከፀጥታ ጥበቃው አንስቶ ፓሪስ ዛሬ ምን ትመስላለች? አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪቃዊ ስፖርተኛ ተባለ ።...
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር በጽ/ቤታቸው ተወያዩ። በውይይቱ የተሳተፉ አንድ ፖለቲከኛ የሰላም፣ የፀጥታ፣ የሕገ መንግሥት፣ የኢኮኖሚ እና ሌሎች ጉዳዮች እንዲሁም አስቸኳይ ውይይት እና ድርድር እንዲጀመር፣ ለታጣቂዎች ግልጽ ጥሪ እንዲደረግ እና የፖለቲካ እሥረኞች እንዲፈቱ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበው ነበር ብለዋል።...
አሁን አሁን ግጭት ጦርነት በሚደረግባቸውም ይሁን አንጻራዊ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች ለዜጎች የየዕለት ስጋት ሆኖ የቀጠለው እና ምናልባትም ችግሩ በዚህ ከቀጠለ በሀገር ህልውና ላይ የሚያስከትለው መዘዝ አሳሳቢ እየሆነ የመጣው የሰላማዊ ሰዎች ዕገታ ጉዳይ ነው ።...
የህክምና ስራ እያከናወኑ ያሉ ባለሙያ በሽታው እንዳይስፋፋና ተጨማሪ ጉዳት በህብረተሰቡ ላይ እንዳያደርስ የመከላከልና የህክምና ስራ እያከናወኑ ቢሆንም የበሽታው ስርጭት በሌሎች ቀበሌዎች በፍጥነት እየተዛመተ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡...
ሴኔጋል ባለፈው ሰኔ ወር በባሕር ዳርቻ የሚገኘው የድፍድፍ ነዳጅ ማውጣት እንቅስቃሴዋን ከተጀመረ በኋላ የአፍሪቃ የነዳጅ ዘይት አምራች ሃገራት ዝርዝር ውስጥ መግባቷን በደስታ እያከበረች ነው። ሀገሪቱ የጀመረችው የነዳጅ ዘይትና ጋዝ ኢንደስትሪዋ ለኤኮኖሚ እድገቷ እንደ ወሳኝ ትመለከተዋለች።...
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ ትናንት የፈተናውን መጠናቀቅ አስመልክተው ለብዙሐን መገናኛ በሰጡት መግለጫ ለፈተና ከተመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ9ሺህ በላይ የአማራ ክልል ተማሪዎች ፈተናውን አልወሰዱም ብለዋል፡፡...
የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በያዝነው ሳምንት ሁለት የምዕራብ አፍሪቃ ሃገራትን ጎብኝተዋል። ቅድሚያ ወደ ሴኔጋል ከዚያም ወደ ቡርኪናፋሶ ያመሩት አናሌና ቤርቦክ ዋነኛ ትኩረታቸው የጸጥታ ትብብር ጉዳይ ነበር።...
«አልሚ ልቦች ለኢትዮጵያ» ከቅርብ አመታት ወዲህ ጀርመን ውስጥ የተመሰረተ ማህበር ነው። ማህበሩ በጀርመን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ስለ ጀርመን ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ እና ማኅበራዊ ኑሮ ማስተማር አንዱ አላማው አድርጎ እየሰራ እንደሆነ ይናገራል።...
በሱዳኑ ከባድ ውጊያ፣ በጦር ቀጣና ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውን ስደተኞች ከሀገሪቱ በአስቸኳይ የሚወጡበት ሁኔታ እንዲመቻችላቸው ጥሪ አቀረቡ። የስደተኞቹ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ለዶይቸ ቨለ እንደገለጹት፣በሱዳን በሚካሄደው ጦርነት ምክንያት፣ ብዙ ኢትዮጵያውያን የተገደሉ ሲሆን የተቀሩት በረሃብ፣በመድኃኒት እጦትና በጭንቀት ከፍተኛ ስቃይ ላይ ይገኛሉ።...
በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞችና ገጠሮች የወንጀል ድርጊቶች እየተበራከቱ መምጣታቸው አሳሳቢ ሆኗል ። ዶናልድ ትራምፕ ላይ ባለፈው ቅዳሜ የ20 ዓመቱ ወጣት እንዴት በቅርብ ርቀት የመግደል ሙከራ ሊያደርግ ቻለ? የበርካቶች ጥያቄ ነው ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳ ልየታ ጉዳይም አነጋግሯል ። አስተያየቶችን አሰባስበናል ።...
ከኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተፈናቅለው በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሰፈሩ ተፈናቃዮች የእርዳታ እህል በወቅቱ አልደረሰንም አሉ፣ የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ኮሚሽን ደግሞ “አንዳንዴ መዘግየቶች ቢኖሩም የእርዳታ እህል ወደተፈናቃዮች ማጓጓዝ ጀምሪያለሁ” ብሏል፡፡...
በአፋር እና ሶማሌ የኢሳ ጎሳ መካከል ለዘመናት የዘለቀውን ግጭት ያስነሳው የሶስት ቀበሌያት አስተዳደር ውዝግብ ዘላቂ እልባት እንዲያገኝ በፌዴራል መንግስት አመቻችነት የሁለቱ ክልሎች አስተዳደሮች ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ፡፡ ይሁንና በግጭቱ መደጋገም የተሰላቹት የአከባቢው ነዋሪዎች ስምምነት የመጨረሻው ስለመሆኑ በጉልህ ይጠራጠራሉ።...
በፖሊሲ ራዕያቸው ላይም ትኩረታቸውን በግብር ቅነሳ፣ በስደተኞች ጉዳይ፣ በውጪ ጉዳይና በኢኮኖሚ ፖሊሲወች ላይ አድርገዋል። የውጪ ግንኙነትን በተመለከተ ዶናልድ ትራምፕ፣አሜሪካ በማያገባት ቦታ ሁሉ እየዘለለች የማትገባበት፣ የግብር ከፋዩዋን ገንዘብ በየሃገሩ የማታፈስበት፣ ይልቁንም በራሷ የውስጥ ጉዳይ ላይ አተኩራ የምትሰራበት ፖሊሲ ነው ያስቀመጡት።...
ኢትዮጵያዊዉ ሰዓሊ ተስፋዬ ኡርጌሳ "ቅድመ ግምትና አብሮ መኖር" በሚል ርዕስ ቬኒስያ ዓዉደ ርዕይ ላይ ያቀረበዉ የስዕል ትርዒት በጣም መነጋገርያ ከነበሩ ትርዒቶች መካከል አንዱ ነው። የኢትዮጵያን የአሳሳል ጥበብ በመጠቀም ተስፋዬ ያቀረባቸዉ ስዕሎች በዘር ሃረግና ማንነት ላይ ያጠነጥናሉ። ኢትዮጵያ በቬኪስያ ስትቀርብ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ነዉ።...
ከተመሠረተ ዓመታትን ያስቆጠረው የመጫና ቱለማ የልማትና መረዳጃ ማሕበር 60ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ባለፈው እሑድ አዲስ አበባ ላይ አከበረ። ማሕበሩ በዚህ የ60 ዓመት ጉዞው ተከፍቶ ሠራውን ከሠራበት ይልቅ ግን ተዘግቶ ያሳለፈበት ጊዜ እንደሚበልጥ ይነገራል።...
በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከራያ አላማጣ ተፈናቅለው በትግራይ የተለያዩ የመጠለያ ጣቢያዎች የነበሩ ወገኖች ወደ ራያ አላማጣ መመለስ መጀመራቸውን የትግራይ ክልል መንግሥት አስታውቋል። ከጦርነቱ በኋላ በአማራ ክልል ስር ያለው የራያ አላማጣ ጊዜያዊ አስተዳደር ደግሞ ወደ አካባቢው እየተመለሱ ያሉት ታጣቂዎችና ነዋሪ ያልነበሩ ናቸው ሲል ይከስሳል።...
የአውሮጳ የእግር ኳስ ሻምፒዮና በስፔን አሸናፊነት ተጠናቋል። አዘጋጅ ሃገር ጀርመን፤ ወደ ግማሽ ፍፃሜ ለማለፍ ባትችልም፤ ሃገሪቱ የእግርኳስ እንግዶቿን ጋብዛ በማስተናገድዋ፤ በሃገሪቱ የሚታዩ የተለያዩ ያልተጠበቁ ችግሮች በኳስ ዝግጅቱ ምክንያት ፋታ ሰጥተው ነዉ የሰነበቱት። 17 ኛዉ የአውሮጳ የእግርኳስ ሻንፒዮና አመርቂ ነበር?...
ደቡብ ሱዳን የናይል/የዓባይ/ ወንዝ ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ (CFA) የተባለውን ስምምነት ሰሞኑን ማጽደቋ ኢትዮጵያን አስደስቷል። የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሱዳንን ውሳኔ «ይህ ዲፕሎማሲያዊ እመርታ በናይል ተፋሰስ ቀጣናዊ ትብብር ለማድረግ ባለን የጋራ ምኞት ጉልህ እርምጃ ነው» በማለት፣ እርምጃውንም «ታሪካዊ» ብለውታል።...
በጦርነቱ ምክንያት ከቀዬአቸው ተፈናቅለው የነበሩ ዜጎች ወደ አላማጣ እና ሌሎች አካባቢዎች መመለስ መጀመራቸው ተገለፀ። ትናንት ከ10 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች ወደ አላማጣ ከተማ መመለሳቸውን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አስታውቋል። ተመላሾቹ ደህንነታቸውን ከማስጠበቅ በተጨማሪ ሰብአዊ ድጋፍም እንዲቀርብላቸው ጥሪ ያቀርባሉ።...
የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የ2016 በጀት ዓመት 227 የውጭ ሀገር ባለሀብቶችን ያካተተ በአጠቃላይ 329 አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን ዋና ኮሚሽነር ሃና አርአያ ሥላሴ አመለከቱ። ከአማራ፣ ከኦሮምያ እና ከድሬደዋ ፕሬዝደንት ጽሕፈት ቤቶች ጋር ለውጭ መዋዕለ ንዋይ ምቹ እና የተለየ ጥበቃ ለማመቻቸት መወያየታቸውንም ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል።...
በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆኑን በተለያዩ ተቋማት የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። በሌላ በኩል ለሰብዓዊ መብት የሚታገሉ እና ችግሩ መፍትሄ እንዲያገኝ የሚወተውቱ በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችም በስራቸው ሳቢያ ከመንግስት ጫና እና እንግልት እየጠነከረባቸው መምጣቱን እየገለፁ ነው።...
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ ወይም ዲጅታል ገንዘብ ለማግኘት ወጣቶች ብዙ ጊዚያቸውን በተንቀሳቃሽ ስልኮቻቸው ላይ ያሳልፋሉ።ይህንኑ ዲጅታል ገንዘብ ለማግኘት በተለይ «ታብታብ» የሚባለው ዲጅታል መድረክ በአሁኑ ወቅት እየተለመደ ነው።ለመሆኑ ይህ ዲጅታል መድረክ ገንዘብ ያስገኛል ወይ? ጥቅም እና ጉዳቱስ? ሕጋዊነቱስ?...
በአዲስ አበባ ከተማ ከተለያዩ ተቋማትና ከኢንዱስትሪዎች ከደረጃ በላይ የሚወጣውን የድምፅ ብክለት ለመቆጣጠር ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሄ እየተፈለገ መሆኑ ተገለጸ።...
ኢትዮጵያ ውስጥ እውቅና ያገኙ ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ሥራ መቀጠር የሚችሉበት እና ፍቃድ አውጥተው በንግድ ሥራ መሰማራት የሚችሉበት መመሪያ ተዘጋጀ።
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን በግብርና ልማት የተሰማሩ ባለሀብቶች የክልሉ የሰላም ሁኔታ በፈጠረው ጫና ምርት ወደ ተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውሮ ለመሸጥ አመቻላቸውን አመለከቱ። የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ ችግሮች ቢኖሩም ምርቱ ወደ ገበያ ማዕከል ደርሶ መሸጡን ይናገራል።...
በአሶሳ፣ ቤጊና ጊዳሚ ወረዳዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ከተቋረጠ 2 ሳምንት ሆኖታል ።በአሶሳና አካባቢው እንዲሁም በምዕራብ ወለጋ ዞን ሁለት ወረዳዎች ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ከተቋረጠ ሁለት ሳምንት አስቆጥሯል ።...
«በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች በቅርቡ እና ተከታታይ እገታዎች» መከሰታቸው እንዳሳሰበው አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ትናንት ዐሳውቋል ። ፖለቲከኞች፦ ለትጥቅ ግጭት ምክንያት የሆኑ ፖለቲካዊ ሁናቴዎች ቶሎ እልባት አለማግኘታቸው ለተገባበት የደህንነት ምስቅልቅል መነሻ ምክንያት ነው ብለዋል፡፡...
በአማራ ክልል የወባ በሽታ ከጊዜ ወደጊዜ እየተስፋፋ መምጣቱን የጤና ባለሞያዎች እና ነዋሪዎች አመልክተዋል ። ባለፈው አንድ ዓመት ከ1 ሚሊዮን 400 ሺህ በላይ ሰዎች በወባ ሲጠቁ፤ ከነኚህ ውስጥ 26ቱ ሕይወታቸው ማለፉን የጤና ባለሥልጣናት ተናግረዋል ።...
58ኛ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው የተመረጡት ሰር ኪየር ስታርመር በአገሪቱ ፖለቲካ የገነነ ስም የላቸውም ። እንዲያም ሆኖ ግን ወደ ከፍተኛ ሥልጣን ማማ ላይ መውጣታቸው ብዙዎችን አስገርሟል። ለመሆኑ ኪየር ስታርመር ማን ናቸው?...
መጤ አረሞች በተለያዩ ጊዜያት ወደ ሀገር ይገባሉ። ጣናን ጨምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ የውኃ አካላትን የወረረው እንቦጭ በቅርብ ጊዜ ብዙ ከተባለላቸው መጤ አረሞች አንዱ ነው። ለማደግ ብዙም ውኃ የማይፈልገው ደረቅ አካባቢ ተንሰፋርቶ የሚባዛው ፕሮሶፒስ በአፋር ክልል ሰፊ መሬትን መያዙ አርብቶ አደሩን ኅብረተሰብ የግጦሽ መሬት እንዳሳጣው ይነገራል።...
ባለፈው እሁድ የተካሄደው የፈረንሳይ ሁለተኛ ዙር ምክር ቤታዊ ምርጫ በግራዎች ጥምረት አሸናፊነት መጠናቀቅ የቀኝ ጽንፈኞችን ተጠናክሮ የመውጣት ስጋት አስቀርቷል። ይሁንና ከተወዳዳሪዎቹ አንዳቸውም ከ50 በመቶ በላይ ድምጽ አለማሸነፋቸው ግን የወደፊቱን የሀገሪቱን አቅጣጫ በእርግጠኛነት ለማወቅ አስቸግሯል።...
ባለፈው ሳምንት እረቡ ጠዋት ከአማራ ክልል ተነስተው ወደ አዲስ አበባ ስጓዙ የነበሩ ቁጥራቸው ከ 100 በላይ ይሆናል የተባሉ ተማሪዎች ኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገርበ ጉራቻ አካባቢ በታጣቂዎች ከታገቱ በኋላ የተማሪዎቹ ቤሰተቦች በጭንቀት ላይ ወድቀዋል፡፡ ከእገታው ሁለት ቀናት በኋላ ከአጋቾች ገንዘብ መጠየቃቸውን ቤተሰቦች ገልፀዋል።...
ከሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ፕሪምየር ሊግ ባደገበት ዓመት የሊጉ ሻምፒዮና ሆኗል። የኢትዮጵያ ቡና ደግሞ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል። የአዲስ አበባ ስቴዲየምም ከአራት አመታት ዓመታት ገደማ በኋላ ዳግም በአዲስ ገጽታ ውድድር አስተናግዷል። 17ኛው የአውሮጳ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ ሃገራትን ለይቶ አሳውቋል።...
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት"የኢትዮጵያ መንግሥት ትናንት የመልካም ጉርብትና እና ዓለም አቀፍ ሕግ መርህን ጥሷል፣ ዛሬ ደግሞ ሕገ ወጥ በሆነ አቋሙ ፀንቷል" ሲሉ ኢትዮጵያ ከራስ ገዝ ሶማሊላንድ ጋር ያደረገችውን የመግባቢያ ስምምነት በማንሳት ወቀሱ። ጎረቤታሞቹ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ውዝግባቸው ቀጥሏል።...
ፕሬዚዳንት ማክሮ ካቢኔያቸዉን በትነዉ ለዳግም ለሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምርጫ፤ መጥራታቸዉን ተከትሎ በተካሄደዉ ሁለተኛ ዙር ምርጫ አብላጫ ወንበሮችን ያገኙ እና መንግሥት ለመመስረት በቂ ዉጤት ያላገኙ ፓርቲዎች በጥምረት ለመስራት ለድርድር እና ለስልጣን ክፍፍል ተስማምተዉ መቀመጥ እንዳለባቸዉ ተመልክቷል። የምርጫዉ ዉጤት ያልተጠበቀ ተብሏል።...
ጆ ባይደን 35 ዓመታት በሴናተርነት፣ 8 ዓመት በምክትል ፕሬዝደንትነት፣ አራት ዓመት በፕሬዝደንትነት እየሰሩ ነዉ።47 ዓመት።ፈጣሪ ረጅም ዕድሜ ከጤና፣ ከሕዝብ ድጋፍና ስልጣን ጋር ሥለሰጣቸዉ አመስግነዉት ይሆን-ይሆናል፣ባለፈዉ ቅዳሜ እንዳሉት ግን ገና ፈጣሪን እየጠበቁ ነዉ።...
በትግራይ እየተፈፀሙ ላሉ ሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች የአስተዳደሩ የፀጥታ እና ፍትህ ተቋማት ተገቢው ምላሽ እየሰጡ አይደለም በማለት በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ሲቪል ተቋማት ተቹ። እነዚህ በተለይም በሴቶች ጉዳይ ላይ የሚሰሩ ተቋማት በጋራ በሰጡት መግለጫ በትግራይ አሳሳቢ የሆነው ፆታ መሰረት ያደረገ ጥቃት እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።...
የክልሉ መንግስት በርካታ ጊዜ የሰላም ጥሪዎችን አስተላልፏል። አሁን በቅርቡ በተካሄደ የሰላም ኮንፈረንስም የሰላም ድምጾች ተሰምቷል። ኮንፈረንሱ ያስተላለፋቸውን ውሳኔዎችን ተከትሎም የሰላም አመቻች ኮሚቴ ተቋቁሞ አሁንም የሰላም ጥሪውን አስተላልፏል።...
በትግራይ በወባ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በ60 በመቶ መጨመሩን የክልሉ የጤና ቢሮ አስታወቀ። በ20 ገደማ ወረዳዎች ወባ በከፍተኛ ሁኔታ መስፋፋቱን የገለጹት በትግራይ ጤና ቢሮ የበሽታዎች ቁጥጥር እና መከላከል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አረጋይ ገብረመድህን አስር የሚሆኑት ወረዳዎች “በወረርሽኝ ደረጃ የሚታይባቸው” መሆናቸውን ገልጸዋል።...
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በአፋር እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ለዘጠኝ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች በተካሔደው ምርጫ ሰባቱን አሸነፈ። የጉምዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ እና የቦሮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እያንዳንዳቸው አንድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ ማሸነፋቸውን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።...
በኢትዮጵያ እየዳሸቀ ነው የተባለውን የንባብ ልማድ ባህል ለማድረግ ያለመ የንባብ ፌስቲቫል ተሰኘ መርሃግብር አዲስ አበባ ውስጥ ተከፈተ፡፡ መሰል መርሃግብር ስካሄድ ዘንድሮ ለዘጠነኛ ጊዜ ነው የተባለለት መርሃግበሩ የማህበረሰብን የማንበብ ፍላጎት ለማነሳሳት ያለመ ነው ተብሎለታል፡፡...
«እናቴንና አክስቴን ሊተኩስባቸው ሽጉጡን ጥይት ሞላበትና አክስቴ ላይ ተኮሰ ። ሆኖም አክስቴ ከጥይቱ አመለጠች። እኔም ከርስዋ ይልቅ እኔን ተኩስብኝ አልኩት።አንቺን አልገልሽም ፤ ውጭ ያሉትን ወንድሞችሽን ነው የምገለው አለ። እኔንም በአለንጋ በዱላና በኮዳ ከደበደበኝ በኋላ አልጋ ላይ ወርውሮኝ ይደፍረኝ ጀመር።» ሀሊማ፣የሱዳን የወሲብ ጥቃት ሰለባ...
«መንግሥት በኤም 23 የተያዙትን ግዛቶች ለማስመለስ ምንም ሲያደርግ አናይም።ለምሳሌ ቡናጋና በኤም 23 እጅ ከገባች ወደ ሁለት ዓመት ይሆናታል። ብዙዎች መንግሥት ኪሩምባን መልሶ መቆጣጠሩ ቀላል አይሆንለትም ይላሉ።እንደ አነስተኛ ቡድን የተነሳው የኤም 23 ቡድን ከአቅም በላይ እንደሆነ ነው የምናየው። በዚህ የተነሳም ህዝቡ ተጨንቋል።»የኪሩምባ ነዋሪ...
የአፍሪቃ ልማት ባንክ መረጃ እንደሚያሳየው አፍሪቃ ካላት ከ420 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች ውስጥ ከሶስት አንዱ ስራ አጥ ናቸው። ባንኩ በቀጣዩ የጎርጎርሳዉያን 2025 የስራ አጦቹን ቁጥር ከ263 ሚሊዮን በላይ ያደርሰዋል። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ተደራራቢ ግጭት እና ጦርነት ውስጥ ላሉ ሃገራት አሃዙ ምን ያህል እንደሆነ በግልጽ የተቀመጠ መረጃ የለም።...
ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት፣ ሑዩማን ራይትስ ዋች በያዝነዉ ሳምንት ባሰራጨዉ ዘገባዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባልደረቦች በአማራ ክልል፣ «መጠነ ሰፊ» ጥሰት አድርሰዋል ይላል።ድርጅቱ በተለይ በጤና ተቋማት፣ ባለሙያዎችና ሕሙማንና ላይ ደረሰ ያለዉን ግፍ «ከጦር ወንጀል እኩል የሚቆጠር« ብሎታልም...
የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ጦርነት ለማስቆም እርምጃው እንዲወስድ ጥሪ ቀረበ። የኢትዮጵያ አሜሪካውያን ሲቪክ ማኀበራት ምክር ቤት አባላት ይህን ጥያቄ ያቀረቡት፣፣ከዩናይትድ ስቴትስ ህግ መወሰኛ ምክር ቤት/ሴኔት/ አባላት ጋር፣ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ባደረጉት ውይይት ላይ ነው።...
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ከሱዳን አዋሳኝ አካባቢዎች ያሉ በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች በተለምዶ “ፈላታ” እየተባሉ በሚጠሩ የናይጀሪያ ተዘዋዋሪ አርብቶ አደሮች ተፅዕኖ እየደረሰባቸው እንደሆነ ባለሀብቶቹ ተናገሩ ። የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ ችግሩ ቢኖርም ተፅዕኖው ቀላል ነው ብሏል፡፡...
በጥንታዊቱና ታሪካዊቱ ሽቱትጋርት ከተማ ጀርመን እና ስፔን ከጥቂት ሰአታት በኋላ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ለመግባት ይፋለማሉ ። የጀርመን እና የስፔን ብሔራዊ የእግር ኳስ ደጋፊዎች ከወዲሁ የተሟሟቁ ይመስላል ። በተለይ የጀርመን ደጋፊዎች በኮይኒግ ሽትራሰ ተሰባስበው እጅግ በደመቀ ሁኔታ ድጋፋቸውን ከወዲሁ እየገለጡ ነው ።...
ሱዳን መጠለያዎች እንደሚገኙት ከ30 ሺህ ገደማ የትግራዩ ጦርነት ተፈናቃዮች ከጦርነቱ በፊት በትግራይ ምዕራባዊ ዞን ራውያን አካባቢ ከልጆቻቸውጋር ይኖሩ የነበሩት እናት ወይዘሮ ጊቱ አለፈ፥ ከሕዳር 2013 ዓም ወዲህ ኑሮአቸው በሱዳን መጠልያ ነው። ሱዳን ወደ እርስ በርስ ግጭት በማምራትዋ በሺዎች የሚቆጠር ስደተኞች ለአደጋ መጋለጣቸውን ያነሳሉ።...
በኢትዮጵያ በሃይማኖት ተቋሚነት ሕጋዊ እውቅና የተሰጠው የዋቀፈና ሃይማኖት ተቋም የመረጃና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ በዪ ለዶቼ ቬለ በሰጡት አስተያየት፤ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ የሃማኖቱ ተከታዮች ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓ.ም. በቁጥጥር ስር የዋሉት ከምሽቱ ሶስት ሰዓት በኋላ ነበር፡፡...
ባለስልጣኑ እነዚህ ግለሰቦች በጦር መሳሪያ የታገዘ ዝርፊያ እና ግድ ሲፈጽሙ እንደቆዩም አስረድተዋል፡፡ በተለያዩ ጊዜ ፖሊስና የመንግስት ባለስልጣናት፣ ነጋዴዎችና የከተማው ነዋሪዎች ላይ የግድያ እርምጃ ስወስዱ እንደነበርም ነው የሚገለጸው፡፡ ባለሃቶችን በማስፈራራት ያሻቸውን በሚሊየን የሚቆጠር ብርም ስያስከፍሉ መኖራቸውን ነው የገለጹት፡፡...
በአውሮፓ ፓርላማ ምርጫ የተገኘው ያክራሪና ብሂረተኖች ድል፤ ያባል ገሮችን ፖለቲክንም ማናወጥ ይዟል። በቤልጅየም መንግስት አፈርሷል፤ በፈረንሳይ አስቸኳይ ምርጫ እንዲደረግ አስገድዷል።...
ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በብዙ የአማራ ክልል ከተሞች ባልታጠቁ ዜጎች ላይ የጅምላ ግድያ ተፈጽሟል፣ መንግሥት የሕሊና እሥረኞችን ለመፍታት፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለማቆም ምን ወስኗል የሚል ጥያቄም ቀርቦ ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግሥታቸው ጅምላ ግድያ እንዳልፈፀመ ገልፀዋል።...
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በማርቆ ልዩ ወረዳ እና በምሥራቅ መስቃን አዋሳኝ ሥፍራ ላይ ትናንት ታጣቂዎች እናትና ልጅን ጨምሮ ሦስት ሰዎችን ገድለው ሌሎች ሁለት አቆሰሉ ። የአካባቢው ነዋሪዎች ግድያው በታጠቁ ቡድኖች ትናንት ምሽት የተፈጸመው በማረቆ ልዩ ወረዳና በምሥራቅ መስቃን ወረዳ መካከል በምትገኘው ኢንሴኖ ከተማ አቅራቢያ ነው ብለዋል፡፡...
በኢትዮጵያ አማካኝ ወርሀዊ ደመወዝ 3000 ብር እንደሆነ ዓለም አቀፉ የሠራተኞች ድርጅት (ILO) ይፋ አድርጓል። ይኸ ለመሠረታዊ ፍላጎቶች ከሚያስፈልገው መኖሪያ ደመወዝ (Living Wage) እጅግ ያነሰ ነው። ኢትዮጵያ እንደ ጎረቤቶቿ ኤርትራ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ካልደነገጉ የመጨረሻዎቹ የአፍሪካ ሀገራት አንዷ ናት።...
ኢትዮጵያም ከጠቅላላው ህዝብ ከሩብ በታች ወይም ወደ 30 ሚሊዮን ለሚጠጋው ህዝብ ብቻ በይነመረብ ተደራሽ በማድረግ፤ አነስተኛ የበይነመረብ ተጠቃሚ ከሆኑ ሀገራት ውስጥ አንዷ ነች።የመብቶች እና ዲሞክራሲ እድገት ማዕከል በቅርቡ ይፋ ባደረገው አንድ ጥናት ደግሞ በኢትዮጵያ ከኢንተርኔት ተደራሽነት በተጨማሪ የፍትሃዊነት ችግር መኖሩን አመልክቷል።...
ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍረቃ ኅብረት ቅርንጫፍ የሂሳብ ቁጥር አስመስሎ በተሰናዳ ሐሰተኛ ሰነድ ገንዘብ ለማውጣት ሞክረዋል በሚል ክስ የቀረበባቸው የእነ ቀሲስ በላይ የክስ መዝገብ ላይ ዛሬ የአቃቤ ሕግ ምስክሮች ሲሰማ ዋለ ።...
በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር አበርገሌ ወረዳ የተለያዩ ቀበሌዎች ተፈናቅለው በወረዳው ማዕከል "ኒሯቅ” ከተማ የተጠለሉ አቤቱታ አቅራቢዎች ወደ ቀያችን እንዳንመለስ የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (አዴን) እንቅፋት ሆኖብናል አሉ ። የንቅናቄው ሊቀመንበር በበኩላቸው ስምታው ሐሰት ነው ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል ።...
ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ተፈናቅለው በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ በተለያዩ የአገር ውስጥ መጠለያ ጣቢዎች ከቆዩ በኋላ በዚሁ ዓመት ሚያዝያ ወር ወዲህ ወደ ቀዬያቸው እንዲመለሱ የተደረጉ ተፈናቃዮች የተሟላላቸው መሰረታዊ ጉዳይ አለመኖሩን ገልጸው መንግስትን ወቅሰዋል ።...
በአማራ ክልል በሚገኙ አንዳንድ ታላላቅ ከተሞች ዝርፊያ እና ነጠቃ ኅብረተሰቡን እያማረረ እንደሆነ ነዋሪዎቹ ተናገሩ ። ዘራፊዎቹ የተለያዩ ባለ ድምፅና ድምፅ አልባ መሣሪያ በመያዝ ቀንም ሌሊትም ኅብረተሰቡን መግቢያ መውጫ እንዳሳጡት ነው ነዋሪዎቹ ገልጠዋል ።...
አንድ የምክር ቤት አባል ከበጀቱ ጋር በተያያዘ "የሕዝብና ቤት ቆጠራ ለምን አይካሄድም" የሚል ጥያቄ መቅረቡን ጠቅሰው ከተለመደው ውጭ የግል መገናኛ ብዙኃን እንዳይገቡ የሚያደርግ ጉዳይ ነበር ብለው እንደማያምኑ ተናግረዋል።...
በፈረንሳይ የተፈራው ደርሷል።በሀገሪቱ የምርጫ ታሪክ ሆኖ የማያውቅ የተባለው እሁድ የተካሄደው የመጀመሪያው ዙር የምክር ቤት ምርጫ ውጤት አሳስቧል። RN በ2ተኛው ዙር ምርጫ እዳያሸንፍ የማድረግ ጥረቶች ቀጥለዋል።ሆኖም በመጀመሪያው ዙር ምርጫ ያሸነፉ የእነለፔን እጩ ተወዳዳሪዎች ብዙ በመሆናቸውው ምናልባት ከማክሮን ጋር አብረው ሊሰሩ ይችሉ ይሆናል።...
የኢትዮጵያ ደረጃ መዳቢ ድርጅት አንዱ አካል ሆኖ በቅርቡ በአዲስ መስሪያ ቤትነት የተመሰረተው የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዛሬ ለሜድሮክ ወርቅ ማውጫ ኩባንያ የሰጠው ሴርቲፊኬሽን በኢንቫይሮሜንታል ማነጅመንት ሲስተም (የአከባቢ ጥበቃ ስርዓት) በ- ISO 14001 በሚባል የዓለማቀፍ ስርዓት መስፈርት መሆኑን አስረድቷል...
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቡና አቅራቢዎች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ዳንኤል ሚጃኔ በሀዋሳው አውደ ርዕይ ከተሳተፉት መካከል አንዱ ናቸው ፡፡ አቶ ዳንኤል ይህን መሰሉ አውደርዕይ አምራቾች፣ አቅራቢዎች እና ላኪዎችን በቀጥታ እርስ በእርስ ለማገናኘት እንደሚረዳ ተናግረዋል ፡፡...
ኢጣሊያና ፈረንሳይ ዉስጥ በሚደረገዉ የዘንድሮዉ የቱር ደ ፍራንስ የብስክሌት ፉክክር ትናንት በተደረገዉ የሶስተኛ ቀን ዉድድር ኤርትራዊዉ ብስክሌት ጋላቢ ቢንያም ግርማይ አሸንፋል።ዘንድሮ የሚደረገዉ የቱር ደ ፍራንስ የብስክሌት ዉድድር ለ111ኛ ጊዜ ነዉ።...
የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የባህልና ስፖርት ትርዒት አትላንታ ጆርጂያ ውስጥ እየተካኼደ ነው። የፌዴሬሽኑ የስራ ኃላፊዎች ለዶይቸ ቨለ እንዳስታወቁት፣ በዘንድሮ 41 ዓመት ትርዒት፣32 ቡድኖች ይሳተፉበታል። በአትላንታ በከፍተኛ ድምቀት በተከፈተው 41ኛው ዓመት የፌዴሬሽኑ ዝግጅት በአጭር ጊዜ የተሰናዳ ነዉ።...
የአርቲስቱ አራተኛ ዓመት የሙት መታሰቢያ እና በአርቲስቱ ስም በተመሰረተው ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን አዘጋጅነት ለሦስተኛ ጊዜ በተሰናዳው መድረክ የአርቲስቱ ባለቤት ወ/ሮ ፋንቱ ደምሰው የሃጫሉ አገዳደል እውነታ እንዲወጣ ጠየቁ፡፡ ወ/ሮ ፋንቱ “አርቲስቱ የተገደለው ለፖለቲካ እቅድ ማስፈጸሚያ” መሆኑን ጠቁመዋል፡፡...
የኢትየጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ሶማሊ፣አፋር እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሰኔ 16/2016 የተካሄደው ቀሪና ድጋሚ ምርጫ የሰብአዊ መብቶችን ባከበረ መልኩ እንዲካሄድ ክትትል ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ በዚህም 31 ባለሙያዎችን መድቦ በ201 ምርጫ ጣቢያዎችን ምልታ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡...
በተለያዩ የትግራይ ከተሞች በሚገኙ ግዚያዊ መጠልያዎች አድርገው ከነበሩ ተፈናቃዮች መካከል የተወሰኑት፥ ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ወደቀዬአቸው መመለስ ጀምረዋል። ተፈናቃዮች ወደቀዬአቸው መመለስ መጀመራቸው በበርካቶች ዘንድ ተስፋ የፈጠረ ቢሆንም፥ የፀጥታና ድህነት ስጋቶች ትኩረት እንዲሰጣቸው ተመላሾቹ ይጠይቃሉ።...
የአዉሮጳ ህብረት ምርጫ ውጤትን ተከትሎ በፈረንሳይ ትናንት በተካሄደዉ የመጀመርያ ዙር የምክር ቤት ምርጫ ናሽናል ራሊ» የተባለዉ ቀኝ ጽንፈኛ ፓርቲ አሸነፈ። ስደተኛ ጠሉ የቀኝ አክራሪዉ ፓርቲ አንዱ አመራር “ፈረንሳይዊያን ድምጻቸውን ከሰጡን የሁሉም ፈረንሳዊ ጠ/ሚ እሆናለሁ” ብለዋል።...
የፕሬዝደንትነቱን ሥልጣን ሲይዙ መጀመሪያ ከተሰነዘረላቸዉ ጥያቄዎች አንዱ የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት የሚመለከት ነበር።«ኢትዮጵያ ዉስጥ ምንም ነገር ቢሆን ኬንያን ይነካል» መለሱ ዶክተር ዊሊያም ሩቶ።ብዙም አልቆዩ የቀድሞ አለቃቸዉን በልዩ አደራዳሪነት ሾሙ።...
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ መንግስታት፣ ድርጅቶችና ሕዝብ ከ«ከስደተኞች ጋር እንዲተባበሩ በሚቀሰቅስበት ወቅት ታጣቂዎች አማራ ክልል የሠፈሩ የሱዳን ስደተኞችን መዝረፍ፣ቢያንስ አንዷን መግደላቸዉ ተዘግቧል።የትግራዩ ተፈናቃዮች ወደቀያቸዉ በየከተሞቹ አደባባዮች ተሰልፈዉ ነበር። አማራ ክልል የሠፈሩ ዜጎች ደግሞ ርዳታ እንዲደረግላቸዉ እየጠየቁ ነዉ...
"ዋናው የጉባዔያችን ራስ ገዝ ዳንካሊያ ውስጥ ደንካሊያ የሚባል ዘጠኝ ወይም ስምንት ቦታ ይከፈላል የኤርትራ ክልሎች ማለት ነው። የራሳችንን መብት ራሳችን የምናስከብርበት ራስ ገዝ በሚባል ቦታ ላይ እንድናገኝ በሚል ጉባኤ ላይ ይህን ጉባኤ ያደረግንበት ዋናው ይሄ ነው።"...
” ፍትህ እንዲረጋገጥ እሻለሁ ” – ወ/ሮ ፋንቱ ደምሴ
ትላንት አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ የተገደለበት 4ኛው የሙት ዓመት መታሰቢያ እና 3ኛው ዓመት ” የሃጫሉ አዋርድ ” የሽልማት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች እውቅና አግኝተዋል፡፡
![](https://mereja.com/amharic/v2/wp-content/uploads/2018/08/DiKnwkwX4AEV4R3.jpg)
በዚሁ መድረክ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ባለቤት እና የሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን የበላይ ኃላፊ ወ/ሮ ፋንቱ ደምሴ ንግግር አድርገው ነበር።
ወ/ሮ ፋንቱ ፤ ” ፍትህ እንዲረጋገጥ እሻለሁ ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የሃጫሉ ባለቤት አሁንም ድረስ ትልቁ መሻታቸው የግድያው እውነታ ከምንጩ እንዲመረመር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
” አርቲስቱ የተገደለው ለፖለቲካ እቅድ ማስፈጸሚያ ” መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
” ህዝብን ተስፋ እናስቆርጣለን ያሉ በራሳቸው ተስፋ ቆርጠው ሃጫሉን በሚሊዮኖች ልብ ውስጥ አኖሩት ” በማለት ገልጸዋል።
” እውነት ተደብቋል ” ያሉት ወ/ሮ ፋንቱ የአርቲስቱ ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ መናገር እና መጠየቅ እንደማያቆሙም አስረድተዋል፡፡
” የምታውቁት እያላችሁ ምንም እንደማያውቁ አትሁኑ ” ያሉት ወ/ሮ ፋንቱ መንግስትም ሆነ ከመንግስት ውጪ ያሉ ያሏቸው የአርቲስቱን እውነተኛ የአገዳደል ሚስጥር የሚያውቁ ” እውነታው ወጥቶ ” ፍትህ እንዲረጋገጥ ስሉ ጥሪ አቅርበዋል።
” ገዳይና አስገዳዩን ለህግ አቅርቡልን ” በማለትም ማንም በዚህ ንጽህናውን እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል፡፡
አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ/ም አዲስ አበባ ውስጥ በተለምዶ ገላን ኮንዶሚኒየም ተብሎ በሚታወቅ አከባቢ ተገድሎ መገኘቱ ይታወሳል፡፡
ግድያውን ተከትሎም በማግስቱ በመላው ኦሮሚያ ክልል በተቀሰቀሰው ከፍተኛ አመጽ
ህዝባዊ ወያነ ርነት ትግራይ (ህወሓት) «ኃይልን መሠረት ያደረገ የአመጽ ተግባሩን በማቆም፤ ሕገ መንግሥታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን አክብሮ ለመንቀሳቀስ የተስማማ በመሆኑ በልዩ ሁኔታ» መመዝገብ እንዲችል ፍትሕ ሚኒስቴር ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ጠየቀ። "በልዩ ሁኔታ የፖለቲካ ፓርቲ ምዝገባን ይመለከታል" የሚለዉ ደብዳቤ ለቦርዱ መድረሱ ተመልክቷል።...
ኃይማኖታዊ እና ሌሎች ባህላዊ ተጽዕኖዎች በወጣቶች የአለባበስም ሆነ ሁለንተናዊ ስብዕና ላይ ብርቱ ተጽዕኖ በሚያሳድርበት ማህበረሰብ ውስጥ ዉበት ፣ ፋሽን ፣ አለባበስ እና ሌሎች በራስ መተማመንን ለማጎልበት የሚያግዝ ትምህርት መስጠት ምን ያህል ፈታኝ እንደሚሆን አይጠረጠርም።...
የአውሮጳ ህብረትን የሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ስታራቴጂክ አጀንዳዎች ለማጽደቅና የህብረቱን ተቋማት የሚመሩ ባለስልጣናትን ለመስየምና ለመምረጥ ለሁለት ቀናት የተጠራው የ27ቱ የህብረቱ መሪዎች ጉባኤ፤ መሪዎቹን መርጦ፤ በአጀንዳዎቹ ላይ ተወያይቶና ወስኖ ከተያዘው ፕሮግራም ቀደም ብሎ ትናንት ዕከለ ሌሊት ላይ ተጠናቋል።...