Home › View all posts by DW Amharic
Blog Archives
በምርጫው ውጤትና በፑቲን ድል ላይ የቻይና፣ ኢራን ቤላሩስና ጥቂት የማይባሉ የላቲን አሜሪካ አገሮች መሪዎች ፈጥነው የደስታ መልእክት አስተላለፈዋል። ቀድሞውንም የምርጫውን ሂደት የተቹትና ፑቲንንም በአምባገንነት የሚወነጅሉት የአሜሪካና አውሮጳ መሪዎች ግን ውጤቱን ፕሬዝድንት ፑቲን ብቻቸውን ተወዳድረው ያሸነፉበት ቲያትር በማለት ተሳልቀውበታል።...
የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት መጋቢት 05 ቀን 2016 ዓ.ም. የተፈቱበትን ውሳኔ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አጣጥሎ ነቀፈ። ኦነግ በመግለጫው በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በግፍ አፈናቅለዋል ያላቸው የቀድሞ ክልላዊ ፕሬዝዳንቱ ሲለቀቁ ክስ እንኳ ያልተመሰረተባቸው አመራሮቼ በእስር ላይ ይገኛሉም ሲል ውሳኔውን ተቃውሞታል፡፡...
በምዕራባዉያን የሚደረገፉት የማይደን አደባባይ አብዮተኞች ኪቭ ላይ ሲቦርቁ፣ ከ60 ዓመት በፊት ዋና ፀሐፊ ኽርሾቭ በጋዜጣ ቀላጤ ለዩክሬን የሰጧትን ግዛት ፑቲን በቀላሉ ግን በ«ሕዝበ ዉሳኔ» ከሩሲያ ቀየጧት።...
በእገታ ላይ ይገኛሉ የተባሉትን 272 ሰዎች ተረክቦ ያጓጓዘው ኒኮትካ ኮንስትራክሽን የተባለ የግል ኩባንያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ አለነ« ኩባንያው ችግሩ ወደተፈጠረበት አካባቢ በመሄድ ሠራተኞቹ በታጣቂዎቹ እጅ እንደሚገኙ አረጋግጧል ፡፡ ሠራተኞቹን በሰላም ለማስለቀቅ ጉዳዩን በባህላዊ የአገር ሽማግሌዎች ይዘን እንገኛለን » ብለዋል ፡፡...
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት "የሲስተም ችግር" እንዳጋጠመው ገልጾ ነበር። በዚሁ ዕለት በተለይ በውስን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ቁጥራቸው በውል ያልተለየ ተማሪዎች በፈጣን የገንዘብ መክፈያ መሣሪያ (ATM) በሒሳብ ቁጥራቸው እንኳን የሌለውን ያህል የገንዘብ መጠን ያለ አግባብ መመንተፋቸው ተነግሯል።...
አፈራራሚዎቹ በግጭቱ የተጎዱትን መልሶ ማቋቋምን ጨምሮ ተጎጂዎችን ያማከለ የሽግግር የፍትሕ ሂደት እና ተጠያቂነትን ለማስፈን የስምምነቱ ፈራሚዎች መገናኘታቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አድርገዋል።እነዚህ የበለፀጉ እንዲሁም በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተከሰቱት ቀውሶች በተመሳሳይ ቁርጠኝነት ችግሩ እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል።...
“ብሔራዊ መግባባት በገለልተኛ አካል ነው መመራት ያለበት፡፡ ሁሉም የውይይቱ ተካፋዮች የሚያምኑበት መሆን ይገባል” ያሉት ፕሮፌሰር መረራ በኢትዮጵያ የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ የተቋቋመውን አገራዊ ኮሚሽን የገለልተኝነት እና አቃፊነት ሁኔታን ነቅፈዋል፡፡...
በእነ ዶ/ር ወንድወሰን አሠፋ መዝገብ ስር ከተካተቱት 53 ተከሳሾች መካከል 21ዱን በተመለከተ ዛሬ ፍርድ ቤት ሦስት ውሳኔዎችን አሳለፈ ። ከ21ዱ ውጪ ቀሪ ተከሳሾች በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው መወሰኑንም ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ሰለሞን ገዛኸኝ ዛሬ ለዶይቸ ቬለ በስልክ ተናግረዋል ።...
በስላም ተጀምረዉ የሚጠናቀቁ የኢትዮጵያ ሀይማኖታዊና ህዝባዊ የአደባባይ በዓላት ከቅርብ ግዜ ወዲህ የመንግስት የፀጥታ ችግር እየሆኑ መጥተዋል፤ በዓላቱን ከሚታደሙት ታዳሚውን የሚጠብቁት እየበለጡ፤ የከተማው መንገድ እየተዘጋ በአብዛኛው አንዳንዴ ከበዓሉ 2 ቀናት በፊት ጭምር እየተዘጋ ለእንቅስቃሴ ፈተና የሚሆንበት ግዜ እየጨመረ መጥቷል ተባለ።...
ለሥራ ማስኬጅያ ከመንግሥት የተሰጠውን 2.7 ሚሊዮን ብር ከታለመለት ዓላማ ውጪ ማዋሉ እና ከፍተኛ ገንዘብ ለፓርቲው አመራሮች እና ሌሎች አባላት የግል ጥቅም አውሏል የተባለው አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የወንጀል ምርመራ እንዲደረግበት ተጠየቀ። ፓርቲው እና አመራሮቹ እንዲታገዱ መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።...
ለአንድ ሳምንት ያህል የዘለቀው እና ሩሲያ የተካሄደው የዓለም ወጣቶች ፌስቲቫል ባለፈው ሳምንት ሀሙስ ተጠናቋል። በዚህ ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያን ወክለው 70 የሚሆኑ ወጣት ኢትዮጵያውያን ተካፍለው ነበር።ስለ ፌስቲቫሉ እና ተሞክሯቸው ጠይቀናል።...
በጎርጎርሳውያኑ 1870 ዎቹ እና 80 ዎቹ ውስጥ ለሞቃታማ አካባቢዎች የሕክምና ምርምር ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረበት ጊዜ ነበር። ጊዜው ደግሞ የአውሮጳ ሃገራት መላው አፍሪቃን ለመቀራመት የሚሯሯጡበት ወቅትም ነበር።...
የቻጋ ሕዝብ በአፍሪቃ እጅግ ታዋቂ እና ትልቁ በሆነው የኪሊማንጃሮ ተራራ ተዳፋታማ አካባቢ የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው ። ህዝቡ የተራራውን አናት ኪቦ ብለው ይጠሩታል።
ነገር ግን በዘመናዊው ታሪክ ታንዛንያውያን ተማሪዎች የኪሊማንጃሮ ተራራ በጀርመን ሚሺነሪ ዮሃንስ ሬብማን አማካኝነት በ1848 እንደተገኘ ያስባሉ ።...
የራይንሽ ተልዕኮ ቤተክርስትያን የተባለችው የጀርመን ቤተክርስታያን ከሄሬሮ ህዝቦች ጋር ጥሩ ግንኙነት ፈጥራ እንደነበር ይነገርላታል። ጀርመኖቹ በኦካሃንጃ፣ ኦትጂምቢንግዌ እና በዊንድሆክ በስምምነት አብረው መኖር የጀመሩበት አጋጣሚም ነበር ። በዚህም በርካታ ሄሬሮዎችም ወደ ክርስትና እምነት እንዲመጡ መንገድ ከፍቶላቸዋል።...
በአዲስ አበባ በጎዳናና በወሲብ ንግድ የሚተዳደሩ ብሎም ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የተዳረጉ ሴቶችን ተጠቃሚ ያደርጋል የተባለው የሴቶች የተሀድሶና የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ዛሬ ተመርቋል፡፡ማዕከሉ በዋነኛነት በሴተኛ-አዳሪነት የተሰማሩትን በመቀበል ሙያዊና ስነ ልቦናዊ ድጋፍና ስልጠናዎችን በመስጠት ወደ ስራ ያሰማራልም ነው የተባለው፡፡...
ፓርቲው የዜጎች ግዲያ መበራከትና ፍትህ አለመስፈን በክልሉ በሰኔ ይካሄዳል በተባለው ምርጫ ላይ ተጽእኖ ሊያሳድር ይችላል የሚል ስጋቱን ገልጿል። የከፍተኛ ፖሊስ መኮንን ጨምሮ በግለሰቦች ላይ በመተከል ዞን እና አሶሳ ዞን ግድያ የፈጸሙ ወደ ህግ አለመቅረባቸው ስጋት የፈጠረና የፍትህ አካላትን ተአማኒነትንም ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ድርጊት ነው ብሏል፡፡...
ህወሓት ከተፈረመ 16 ወራት ያለፈው ውል በከፊል መፈፀሙን፣ በርካታ የስምምነቱ ይዘቶች ደግሞ አሁንም በእንጥልጥል እንዳሉ በውይይቱ መነሳቱን ገልጿል።ህወሓት በስምምነቱ መሰረት ከመከላከያ ሰራዊት ውጭ የሆኑ ሐይሎች አሁንም ከትግራይ አለመውጣቸውን፣ 40 በመቶ የትግራይ ግዛት አሁንም ወደ ክልሉ አስተዳደር እንዳልገባ ማንሳቱን በመግለጫው ጠቁሟል።...
የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ ለማስፈታት፣ ለመበተን እና ወደ ማህበረሰቡ መልሶ ለማዋሃድ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ የገለፁት የበለፀጉ ሀገራት በአማራ በኦሮሚያና በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተከሰቱት ቀውሶች በተመሳሳይ ቁርጠኝነት ችግራቸው እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል። ሁለቱ ወገኖች በቂት ወራት ተመሳሳይ ውይይት ለማድረግ ስለመወሰናቸውም ተነግሯል።...
የክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በክልሉ የመምህራንን ደሞዝን ጨምሮ ሌሎች የፋይናንስ ውጪዎችን ለማሟላት ያልተቻለው የገቢ አሰባሰብ በሚፈለገው መጠን ባለመሠራቱ መሆኑን ተናግረዋል ። በቀጣይ የፋይናንስና የገቢ ሰብሳቢ ተቋማትን አቅም በማጠናከር የደሞዝ ክፍያን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ጥረት እንደሚደረግ ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል ፡፡...
ጀርመናዊትዋ የፊልም ተዋናይ ሳንድራ ሁለር በምርጥ ዘርፍ ተዋናይት ኦስካር ባታሸንፍም፤ የሚሊዮኖችን ልብ በተወነችበት ፊልም አግኝታለች። ቀደም ሲል አዉሮጳ ላይ ሽልማትዋን እንድትወስድ ወደ መድረክ ስትጠራ፤ በአዳራሹ የነበረዉን ህዝብ ለዓለም ሰላም በፀጥታ መልክት እንዲያስተላልፍ ለሰላም እንዲቆም ጠይቃ ነበር።...
በትግራይ ክልል የሚገኙ ተፈናቃዮች አሁንም ወደ መኖሪያችን ባለመመለሳችን ለከፋ ሁኔታ ተዳርገናል ሲሉ ገለጡ ። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከሰላም ስምምነቱ በኋላም ጭምር መፈናቀሉ መቀጠሉን ገልጧል ።...
በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች በእስር ላይ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች የሆኑ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከእስር እንዲለቀቁ ቤተሰቦቻቸው እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጠየቁ ።...
በቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ እና በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ ውስጥ በሚስተዋለው የፀጥታ ችግር በንግድ እንቅስቃሴ ላይ ተጽእኖ ማሳደሩን የአካባቢው ነዋሪዎኢትዮጵያች አስታወቁ ። አልፎ አልፎ በታጣቂዎች እና ጸጥታ ኃይላት መካከል በሚከሰቱ ግጭቶች ምክንያት በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ አሁንም ጉዳት እየደረሰ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡...
በሀረሪ ክልል በተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ እስከትናንት ድረስ ቢያንስ ሦስት ሰዎች መሞታቸው ተገልጧል ። ከሰባ በላይ ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ ዐስታውቋል ። 31 ሰዎች ታክመው ወደ ቤታቸውመ መመለሳቸውም ተገልጧል ።...
የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የመንግሥት ተቋማት ከውጭ ከሚገቡ ሸቀጦች ይልቅ ለሀገር ውስጥ ምርት ቅድሚያ እንዲሰጡ ግፊት እያደረጉ ነው። የማምረቻ ኢንዱስትሪው የሀገሪቱ የጸጥታ ሁኔታ ፋይናንስ እና የውጭ ምንዛሪ እጦትን የመሳሰሉ ችግሮች ይፈታተኑታል። ባለፈው አንድ ዓመት 450 የሚሆኑ ኢንዱስትሪዎች ሥራ አቁመዋል። የባለሥልጣናቱ ግፊት ምን ይፈይዳል?...
በኦሮሚያ ክልል «የአቡነ ጴጥሮስ መንበር መስርተናል» በማለታቸው የታሰሩ የተባሉ ሦስት የሃይማኖት አባቶች እና አብረዋቸው የነበሩ ተጨማሪ ሰባት ሰዎች ከ7 ሳምንታት ገደማ እስራት በኋላ ትናንት አመሻሹን ከታሰሩበት ተለቀዋል ።...
አውሮጳውያን ከግዛታቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጠውን የአፍሪቃ አህጉር ቅኝ የገዙበት መንገድ አስገራሚ ነው ። እያንዳንዱ ሀገር ወደ አፍሪቃ እግሩን ያስገባበት የታሪክ አጋጣሚም እንዲሁ አስገራሚ ነው። በዚህ ረገድ ጀርመን በርካታ የአፍሪቃ ሃገራትን ቅኝ የገዛችበት አጋጣሚ በግለሰቦች ፍላጎት ላይ የተመሰረተ እንደነበር ሲታሰብ በእርግጥ ያስገርማል።...
የህብረቱ ውሳኔ የኢትዮጵያ ቡና አመራረት ሂደቱ እስኪጣራም ቢሆን ተጽእኖው እየታዬ ነው ብሏል፡፡ በሌላ በኩል በቀይ ባህር አከባቢ እየተስተዋለ ያለው አለመረጋጋት የወደብና መርከብ እንቅስቃሴን በጉልህ ማቀዛቀዙም የቡና ማህበሩን በእጅጉ አሳስቧል፡፡...
ግልፅነትን፣ ፍትሓዊነትን እና ቀልጣፋ የመሬት አስተዳደርን በማስፈን ኢንቨስትመንትን እና የኢኮኖሚ ልማትን የሚያበረታታ ግልፅና ወጥነት ያለው ፖሊሲ መዘርጋት እንዱ ለመንግሥት ከቀረቡ ሀሳቦች መካከል ነው።...
በኢትዮጵያ ሞያሌ በኩል ዛሬ ወደ አገራቸው የተመለሱት ከሦስት መቶ በላይ ፍልሰተኞች ከስድስት ወራት እስከ አንድ ዓመት በእሥር መቆየታቸውን በማዕካላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሃድያ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የፍልሰተኞች ባለሙያ አቶ አወል ጀማል ገልጸዋል...
የተመድ በጎርጎሪዮሳዊው 2030 ዓ,ም ሊያሳካ ካቀዳቸው ዘላቂ የልማት ግቦች አንዱ የሴቶችን መብቶች በማክበር ኑሯቸው ማሻሻልን ይመለከታል። ሆኖም የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ አንቶንዮ ጉተሬሽ እንደተናገሩት ከ340 ሚሊየን በላይ አዋቂና አዳጊ ሴቶች እጅግ በከፋ ድህነት ኑሯቸውን ይገፋሉ። «የሴቶችን ቀን እያሰብን በተግባር ለሴቶች ምን ተደርጓል?»...
ባለፉት አምስት ዓመታት የአውሮጳ ሀገራት የጦር መሣሪያ ግዢ በእጅጉ ጨምሯል። በአውሮጳ የጦር መሣሪያ ክምችት የጨመረበት አንዱ ምክንያት የዩክሬን ጦርነት ቢሆንም ሌላው ምክንያት ደግሞ የአውሮጳ ሀገራት ራሳቸውን ለመከላከል የሚያደርጉት ዝግጅት ነው። በጦር መሣሪያ ሽያጭ ፈረንሳይ አሁን ሩስያን ተክታ ሁለተኛው ደረጃ ላይ ትገኛለች።...
የጎርጎረሳዉያን 2023 ዓመት የዓለም የጦር መሳርያ ዝዉዉርና ሽያጭን በተመለከተ፤ በዓለማችን የጦር መሳርያ ንግድ ዩናይትድ ስቴትስ አንደኛ፤ በሁለተኛ ፈረንሳይ ፤ ሦስተኛ ሩስያ፤ አራተኛ ቻይና፤ አምስተኛ ጀርመን ስድስተኛ ጣልያን ፤ ሰባተኛ ኢጣልያ ፤ እንዲሁም ስምንተኛ ታላቅዋ ብሪታንያ መሆናቸዉ ዓለም አቀፉ ተቆጣጣሪ ተቋም አስታወቀ።...
አስተያየት ሰጪው በእለቱ በሶስቱ ቀበሌያት ከቆሰሉት በተጨማሪ ብያንስ የ11 ሰዎች ህይወት ህልፈት መሰማቱን አስረድተዋልም፡፡ ከነዚህም ስድስቱን በስም እንደሚያውቃቸው በማስገንዘብ፡ ከቆሰሉት ደግሞ የ11 ዓመት ታዳጊ ሴት እና አበራ መኮንን የሚባሉ የ60 ዓመት አዛውንት ተመልክቻለሁ” ብለዋል አስተያየት ሰጪው፡፡...
ዐማራው በአሁኑ ጊዜ ከሁሉም የከፋ ጥቃት እየረሰበት ነው ያሉት ሊቀመንበሩ፣ዓለም አቀፉ ማኀበረስብ ግን ለዚህ በደል ትኩረት አለመስጠቱን አመልከተዋል። በዚህ ላይም ውይይት መካሄዱንም አመልክተዋል።የመጀመሪያ የዐማራ አጠቃላይ ጉባኤ የዛሬ ዓመት ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ ዘንድሮ ደግሞ በዐማራ ማኀበር አስተናጋጅነት በአትላንታ ጆርጅያ ተካሄዷል።...
በአሁኑ ወቅት በርካታ የአገሪቱ ክፍሎች በማያባራ ግጭት ውስጥ መሆናቸውን የጠቀሱት ድርጅቶቹ መንግሥት ሕግና ሥርዓት የማስከበር ግዴታውን በአግባቡ ካልተወጣ በስተቀር የሽግግር ፍትሕን ተግባራዊ ለማድረግ በጣም አዳጋች እንደሚሆን አመላክተዋል፡፡ቀውሱ ለሽግግር ፍትሕ አፈጻጸምም እንቅፋት እንዳይሆኑ፣ መንግሥት የሕግ የበላይነትን እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል።...
ምክንያቱ ምንም ሆነ ምን የአዲስ አበባና የመቀሌ መሪዎች ኃላፊነት እንደሚሰማዉ ፖለቲከኛ ትግራይ፣ አማራ ይሁን ኦሮሚያ ክልሎች የሚያልቀዉን ሰዉ ሕይወት ማደን አይደለም ዉዝግባቸዉን እንኳን ራሳቸዉ ማስወገድ አቅቷቸዉ እንደሚያዉቁና እንደለመዱት የአሜሪካ-አዉሮጳና አፍሪቃን ሽምግልና እየተማጸኑ ነዉ።...
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዛሬ ሰኞ የጀመረዉን የረመዳን ጾምን በማስመልከት በእስራኤል-ሀማስ መካከል ጋዛ ሰርጥ ዉስጥ የሚካሄደዉ ጦርነት ብሎም በሱዳን የሚታየዉ ግጭት እንዲቆም እና እርቅ እንዲወርድ ጥሪ አስተላለፉ። ጉቴሬዝ በሃማስ የተያዙ የእስራኤል ታጋቾች እንዲፈቱም ጠይቀዋል።...
የተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች፣የመብት ተሟጋቾች፣የርዳታ ድርጅት ሠራተኞች ከሁሉም በላይ የየአካባቢዉ ነዋሪዎች እንደሚሉት በየግጭት፣ ዉጊያ ጥቃቶቹ የሚያልቅ፣ የሚቆስል፣የሚፈናቀለዉ ሕዝብና የምትደፈረዉ ሴት ቁጥር እየጨመረ ነዉ።...
ቤተልሔም አካሉ ትባላለች፡፡ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪየሽን ዩኒቨርሲቲ የፓይለት ስልጠና ትምህርት ቤት እጩ አብራሪ ናት፡፡ ካፕቴን (ፓይለት) ሆና ግዙፍ አውሮፕላኖችን በተለያዩ ዓለማት ማብረርን ህልሟ አድርጋ እየተጋች ያለች ወጣት ናት፡፡...
በኦሮሚያ ክልል ከምዕራብ ጉጂ ዞን በመቶዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞች፣ የቀበሌ አመራሮች እና ሚሊሺያዎች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወደሚገኘው ኮሬ ዞን መሸሻቸውን የዐይን እማኞች ተናገሩ። ሰዎቹ የሸሹት ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላት በገላና ወረዳ የምትገኘውን መጠሪ ቀበሌ ከተቆጣጠሩ በኋላ ነው።...
በአማራ ክልል ከታቀዱ 214 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች የተጀመሩት 92 ብቻ መሆናቸውን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ። በመንግሥት የጸጥታ አስከባሪዎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተካሔደ የሚገኘው ግጭት የታቀዱ የመስኖ ሥራዎች ግንባታ ላይ ተጽዕኖ እንዳሳደረ የአማራ ክልል የመስኖ እና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ ኃላፊ ዳኝነት ፈንታው ተናግረዋል...
የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪቃ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር የፕሪቶሪያ ግጭትን የማስወገድ ዉልን ገቢራዊነት በሚገመግመዉ ስብሰባ ላይ ተካፍለዋል ።የልዩ መልእክተኛው ጉብኝትና ዉይይት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ያስገኝ ይሆን?...
ዛሬ ዓለማቀፉ የሴቶች ቀን በመላው ዓለም ስከበር ውሏል፡፡ እለቱ ሴቶች በተለያዩ ዘርፎች እኩልነትና ተጠቃሚነታቸው ተረጋግጦ ምቹ የኑሮ አውድ እንዲኖራቸው ማስገንዘብና መወትወት ላይ ያተኩራል፡፡
በኢትዮጵያ በግጭት ፈተና ለመፈናቀል ተዳርገው አስከፊውን ኑሮ ሚገፉ እናቶች ግን ከዚህም የላቀ ትኩረትን ይሻሉ፡፡...
ሰሞኑን በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የነበሩ ብርቱ ውጊያዎች ጋብ ማለታቸው ተገለጠ ። በባሕርዳር ከተማ ትናንት ምሽት ቦንብ ፈንድቶ የተኩስ ድምፅም ለተወሰኑ ደቂቃዎች ይሰማ እንደነበር ታውቋል ።...
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በስድስት ወራት ውስጥ ለ188 አዳዲስ ባለሀብቶች በግብርና ዘርፍ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የክልሉ መንግስት አስታወቀ። ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዙ የኢንቨስትመንት ስራ ቀንሶ እንደነበር ገልጸው በተለያዩ አካባቢዎች ሰላም እየሰፈነ በመሆኑ ባለሀብቶች ወደ ስራ እየገቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል።...
"ወረፋ ከያዙት ባጃጆች በአንዱ ለመሳፈር ስንፈልግ ከወረፋ ውጭ የነበረ ባለባጃጅ እኔ ጋር ካልገባችሁ ብሎ በግድ ወተወተን። እኔ ሰውነቴ ቅፍፍ እያለኝ ነበር የገባሁት። ትንሽ እንደተጓዝን ሾፌሩ ዘሎ በመውረድ እኛን ከአንድ ሞተር ብስክሌት ጋር አጋጨን"...
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን፤ ስርዓታችን በዋነኝነት አባታዊ ስርዓት ነዉ። ሴቶቹም ብንሆን አባታዊ ስርዓት የፈጠረን ነን። ስለዚህ በራስ መተማመናችን፤ ለራሳችን ያለን ግምት ከወንዶቹ እኩል አይደለም። የሄድንበት ስርዓት ራሱ አንቺ አትችይም፤ እየተባለ እየተመረጠልን ነዉ ያደግነዉ። አሁንም ሴቶች ከፍርሃትና ከመሸማቀቅ አልወጣንም ብሎ መናገር ይቻላል።...
አሜሪካና ብሪታኒያ በሁቲዎቹ ላይ በከፈቱት ጥቃት አቅማቸውን እንዳዳከሙትና የማጥቃት ብቃታቸውን ቀንሰናል ቢሉም ሁቲዎቹን እንዳይተኩሱ ሊይደርጉ የንግድ መስመሩን ደህንነትም ሊያስጠብቁ እንዳልቻሉ ነው የሚነገረው።የአሜሪካና ብሪታኒያ ሚሳይሎች የሁቲዎቹን ጥቃት ሙሉ በሙሉ በማስቆም የቀይ ባህርን ደህንነት ማረጋገጥ መቻላቸውን ብዙዎች ይጠራጠራሉ።...
የአሜሪካ ኢትዮጵያ የሕዝብ ጉዳዮች ኮሚቴ የሚያካሂደው ይኸው ጥረት፣የኢትዮጵያ አሜሪካ ወጣቶችን በዩናይትድስቴትስ ኮንግረስ እና ሴኔት ድረስ የማስመረጥ ግብ እንዳለው፣ የመድረኩ አስተባባሪ አቶ ነብዩ አስፋው ይናገራሉ። በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉት ወጣቶች፣ በአሜሪካ ተወልደው ያደጉና በህፃንነታቸው አሜሪካን መጥተው ያደጉ ናቸው።...
በኢትዮጵያ የማህፀን በር መከላከያ ክትባት ለታዳጊ ሲቶች መስጠት ከተጀመረ 5ኛ ዓመቱን ይዟል። ባለሞያዎች ክትባቱ ከ90 ክመቶ በላይ በሽታውን ለመከላክል ያስችላል ይላሉ።
ክትባቱ በዚህ ሳምንት በተከታታይ ለ5 ቅናት ለ14 አመት ታዳጊ ሲቶቸ በመሰጠት ላይ ነው።ሁለት ጊዜ ይሰጥ የነበረው ክትባቱ ተሻሽሎ አሁን አንድ ግዜ ብቻ ነው የሚሰጠው።...
ኢትዮጵያ የሚገኙ ሁሉም ባንኮች በትግራይ ለሚገኙ ደምበኞቻቸው ከጦርነቱ በፊትላበደሩት ገንዘብ ባንኮች የጦርነቱን ጊዜ ጨምሮ ወለድ እንዲከፍሉ መጠየቃቸው ለከፍተኛ ችግር እንዳጋልጣቸው ነጋዴዎች ተናግረዋል። ያነጋገርናቸው በመቐለ በንግድ ዘርፍ ተሰማርተው የሚሰሩ ባለሐብቶች ሁሉም ባንኮች ብድራቸውን ከወለዱ ጋር እንዲከፍሉ እየጠየቋቁን ነው ብለዋል።...
ዛሬ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ያደረገው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት "የጋዜጠኞችን ደኅንነት በማስጠበቅ ሥራቸውን ከፍርሃት ነፃ ሆነው" የሚሠሩበት እድል እንዲኖር ውትወታ ከማድረግ ባለፈ ከሚመለከታቸው ጋር ውይይት ማድረጉን ቢገልጽም ጋዜጠኝነት አሁን ላይ ፈተና ላይ ስለመውደቁ ይታመናል።...
በኢትዮጵያ መንግስትና በትግራይ ክልል ኃይሎች መካከል ለሁለት ዓመታት የቆየውን ደም አፋሳሽ ጦርነት ያስቆመውን የፕሪቶሪያ ስምምነት ገቢራዊነት ላይ አሸማጋዩ የአፍሪካ ህብረት አፈጻጸሙን አዲስ አበባ ውስጥ ሲገመግም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፣ የአውሮጳ ኅብረት፣ ኢጋድ እና ዩናይትድ ስቴትስ በታዛቢነት ሂደቱን ይከታተላሉ ተብሏል፡፡...
ኢትዮጵያ እና ጀርመንን ጨምሮ የስድስት ሀገራት የንግድ ሥራ መሪዎች የሚሳተፉበት ዓመታዊ መርሐ-ግብር ማመልከቻዎች እየተቀበለ ነው። ለአራተኛ ጊዜ የሚካሔደው መርሐ-ግብር ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በታች የሆነ 40 ወጣት የንግድ ሥራ መሪዎችን በበርሊን ከተማ ያገናኛል። በመርሐ-ግብሩ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን በዕድሉ ጠቃሚ ግንኙነት እንዳበጁ ተናግረዋል።...
በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ አዲስ ከተገነባው የዐድዋ ሙዚየም ፊት ለፊት ያሉ ቤቶች «የፒያሳ እና አራት ኪሎ አካባቢ መልሶ ማልማት» እቅድ ውስጥ የተካተቱ በመሆናቸው ነዋሪዎች በጥቂት ወራት ውስጥ ከሥፍራው እንደሚነሱ የከተማ አስተዳደሩ በቅርቡ አስታውቋል። ጉዳዩ የብዙ ሰው መነጋገሪያ መሆኑን ታዝበናል።...
በአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ባይደን እና የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅድመ ምርጫው አሸንፈው ለዋናው ምርጫ ተመልሰው እንደሚገናኙ ይጠበቃል። ትናንት ማክሰኞ በተካኼደው፣«የሱፐር ቱይስዴይ» ቅድመ ምርጫ፣ እስካሁን በታወቀው ውጤት ሁለቱም የሚያስፈልጋቸውን የተወካዮች ድምጽ ማግኘታቸው ታውቋል።...
በኤርትራ ሠራዊት የተያዙ ቀሪ አካባቢዎች ለመለየት እና መፍትሔ ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴሩ ዶክተር አብርሃም በላይ ተናገሩ። ሚኒስትሩ ለመንግሥት ቴሌቪዢን ጋር በትግሪኛ ቋንቋ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባደረጉት ቃለመጠይቅ አወዛጋቢ ካሏቸው አካባቢዎች የመንግሥት ያልሆነ ታጣቂዎችን የማስወጣት ሥራ እየተሠራ ነው ብለዋል።...
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እቅድ ከ5 ዓመታት በፊት ይፋ የተደረገ ዕቅድ ሲሆን፤ የበይነመረብ አገልግሎትን እንደ መሳሪያ በመጠቀም የዜጎችን የዲጅታል ቴክኖሎጂ አቅም የማጎልበት እና በ2025 አካታች የሆነ ዲጅታል ኢኮኖሚን የመገንባት ዓላማ ያለው መሆኑን የዚህ ዕቅድ ሰነድ ያሳያል።...
አክራሪ ጽንፈኞች እና የሩሲያ ድብቅ ፍላጎት ከሰሃራ በታች ባሉ የሳህል አካባቢ አፍሪቃ ሀገራት ላይ ስጋት ደቅነዋል ሲሉ የጀርመን ልማት ሚኒስትር ስቬንያ ሹልዘ አስጠነቀቁ። ሚኒስትሯ ይህን የተናገሩት በያዝነዉ ሳምንት ሰኞ ለፖለቲካዊ ዉይይት ወደ ቡርኪናፋሶ እና ቤኒን ከማቅናታቸዉ በፊት ነዉ።...
በአማራ ክልል፤ ደቡብ ወሎ ዞን፤ ተሁለደሬ ወረዳ፤ «ቱርክ» በተባለ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮች «ለከፍተኛ ረሀብ ተጋልጠናል» አሉ ። በረሀብ ሰዎች መሞታቸውንም ተፈናቃይ አስተያየት ሰጪዎች ለዶይቸ ቬለ (DW) አመልክተዋል ።...
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር (ERCS) እና የዓለማቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) ለቀጣይ ሦስት ዓመታት አብሮ ለመሥራት የሚስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ ። ከ207 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚደርግም ተገልጿል ።...
ትውልዱ እንዴት የሚገለጽ ነው? የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤታ ክርስትያን ቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ «ያለንበት ዘመን ለእግዚአብሔር ክብርን የነሣ፤ ከፍቅርና ከአንድነት የራቀ፣ ራስ ወዳድነትና በቃኝ አለማለት የወረረው፤ በዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ የተዋጠ ትውልድ የታየበት ዘመን ነው» ብለዋል ።...
በተለያዩ የአውሮጳ ሃገራት ገበሬዎች ለተቃውሞ አደባባይ መውጣታቸው ቀጥሏል። ገበሬዎቹን ለተቃውሞ ያነሳሳው ጉዳይ ከሀገር ሀገር ቢለያይም በአሁኑ ጊዜ አብዛኞቹ ለአእምሮ ጤና ችግር መጋለጣቸውን መረጃዎች እየወጡ ነው።...
የአውሮጳ ኅብረት ባለፈው ታኅሳስ ቀኝ ጽንፈኞች የመራጩን ድምጽ ለማግኘት አጀንዳ ለሚያደርጉት ሕገ-ወጥ ለሚሉት ስደት መፍትሄ ይሆናል ባሉት የስደት ሕግ ማሻሻያ ተስማምተዋል። ይሁንና በጉዳዩ ላይ በቅርቡ በተካሄደ የዳሰሳ ጥናት መሠረት በሰኔው የአውሮጳ ኅብረት ምክር ቤት ምርጫ ቀኝ ጽንፈኞች ከፍተኛ ድምጽ ያገኛሉ የሚል ስጋት አለ።...
በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በመንግሥት ጦር ሰራዊትና የፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚካሄደዉ ጦርነት እንደቀጠለ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተናገሩ። በሰሜን ሸዋ፤ ሸዋሮቢት ከተማ ከሦስት ቀናት በፊት ጀምሮ የታየዉ ጦርነት ዛሬ ጋብ ያለ ይመስላል፤ ይሁንና ነዋሪዎች ስጋትና ጭንቀት ላይ ናቸዉ። መርዓዊ ከተማ እና ዙርያዋ ከባድ ዉግያ አለ ተብሏል።...
የኤርትራ ጦር በኃይል ከያዘው የኢትዮጵያ ግዛት እንዲወጣ፥ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት «ኃላፊነቱ ሊወጣ ይገባል» ሲል የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ጥሪ አቀረበ። የኤርትራ መንግሥት በበኩሉ፥ የያዘው የኢትዮጵያ ሉአላዊ ግዛት እንደሌለ ይገልፃል።...
የኃይማኖት መሪዎች ሰላም እንዲወርድ ፈጣሪያቸዉን ይማፀናሉ፣ ኃይለኞችን ያባብላሉ።የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ትናንት ለተከታዮቻቸዉ እንደነገሩት ከፀሎት-ምሕላ-ተማፅኗቸዉ ጋር ራሳቸዉ-ለራሳቸዉ ያነሱት ጥያቄም አላቸዉ። በዚሕ መንገድ የተሻለ ዓለም ዓለም መገንባት ይቻላል? የሚል መሠረታዊ ጥያቄ።...
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ፓትርያርክ ብፁዕ ዐቡነ ማትያስ በ11ኛው ዓመት ሲመተ በዓላቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት "በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ ጣልቃ እየገቡ የግል ፍላጎትና ዓላማ ለማስፈጸም መሞከር ፍጹም ስሕተት እና ተቀባይነት የሌለው ነው" ሲሉ አሳሰቡ።...
"ነጮች በዘራቸው ንጹህ ስለሆኑ፣ ከሰው ሁሉ በላይ ናቸው፣ ማንም ነጭ ያልሆነ ነጭን ሊያሽንፍ አይችልም የሚል እምነት ለ500 ዓመታት፣ አሜሪካ ከተቆረቆረች ጊዜ ጀምሮ ያራምዱ ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ ነጭን በከፍተኛ ደረጃ ያዋረደ ሰው ቢኖር ሚኒሊክ ነው ብሎ አንድ እንግሊዛዊ ጽፏል። " የታሪክ ሙሁር ፕሮፌሰር ሃይሌ ላሬቦ...
የጦርነቱ ጠባሳ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ ግድም በኋላም በጉልኅ ይታያል ። ባለፉት ሳምንታት በትግራይ እና አማራ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ ታጣቂዎች መካከል ለአጭር ጊዜያት የቆዩ ግጭቶች ከአንዴም ሁለት ጊዜ መከሰታቸው ነዋሪዎችን እጅግ አስግቷል ።...
በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተከስቷል በተባለ የኮሌራ በሽታ ሳቢያ ከአራት መቶ የማያንሱ ተማሪዎች መያዛቸውን በዩኒቨርሲቲው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል ።...
128 ኛው ዓመት የዓድዋ ድል መታሰቢያ ክብረ በዓል በአዲስ አበባ በቅርቡ በተመረቀው የዓድዋ ሙዚየም ውስጥ በመንግሥት ደረጃ ተከበረ።
ለወትሮው ፒያሳ ምኒልክ አደባባይ እና በዙሪያእ በዓሉን ያከብር የነበረው ብዙ ቁጥር የነበረው ሕዝብ በዚህኛው ዓመት በሥፍራው በዓሉን እንዳያከብር በፀጥታ አካላት ክልከላ ተደርጎበታል።...
በውሳኔ ዐሳቡ ሰነድ ላይ እንደተመለከተው፣ ሴቶች ህጻናትና አዛንቶችን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው የዐማራ ንጹሃን ዜጎች፣ በመንግስት ኃይሎች በድሮንና ሌሎች ከባድ መሳሪያዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል።የመንግስት የፀጥታ ኃይሎችና ሌሎች ታጣቂዎች፣ በሴቶችና ልጃገረዶች ላይ ጾታዊና ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶችን መፈጸማቸውንም ገልጿል።...
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚከሰተው የመኪና አደጋ መባባስ፤ የፈረንሳዊው ጋዜጠኛ እስር እንዲሁም የሶማሊላንድን የሀገርነት ጥረት በሚመለከቱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በማኅበራዊ መገናኛው ከተሰጡ አስተያየቶች ሚዛናዊ ያልናቸውን መራርጠናል።...
ከኢትዮጵያውያን አልፎ የጥቁር ህዝብ ድል ተደርጎ የሚነሳው የአድዋ ድል በዓል በአንድነት እና በህብረት እንዲከበር አስተያየት ሰጪዎች ጠየቁ፡፡ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸዉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ እየጎላ የመጣው ውዝግብ መወገድ አለበት...
ዛሬ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ረፋድ 4 ሰዓት አካባቢ የዘለቀ የተኩስ ልውውጥ በባሕርዳር ከተማ ሲደረግ አርፍዷል፣ በተኩስ ለውውጡ የከባድ መሳሪያዎች ድምፅም ይሰማ ነበር፡፡ የተኩስ ልውውጡን ተከትሎ ነዋሪዎቹ ከቤታቸው ሳይወጡ ሁኔታዎችን ሲከታተሉ ማርፈዳቸውን ዶይቼ ቬሌ ተመልክቷል፡፡...
በተለይ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ፣ የተፈናቀለ ሕዝብ የሚገኝበት ቢሆንም ክልሉ አሁን ድረስ ባልተመረጠ ምክር ቤት የሚተዳደር በመሆኑ ምርጫው ይደረግ የሚለውን ሲጠይቁት የቆዩት ጉዳይ መሆኑን በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ጠቅሰዋል።...
ሰዎች ይፋቀራሉ፣ ሲልም ትዳር ይመሰርታሉ። አንዳንዶች የትዳር አጋራቸውን የሚፈልጉት በዘመናዊው መንገድ - ኦንላይን ላይ ነው። «ጥሩና ጊዜ ቆጣቢ ነው» የሚሉ እንዳሉ ሁሉ መጥፎ ጎኑ የሚያመዝንባቸውም አሉ። የሀገር ውስጥም ይሁኑ የውጭ ሀገር የፍቅረኛ ማገናኛ መተግበሪያዎች መሠረታዊ የሆኑ መረጃዎችን ይጠይቃሉ። ይሁንና ሁሉም ሰው ሀቀኛ አይደለም።...
ደሞዝ ባለመከፈሉ የትምህርትና የጤና ሥራዎች ተስተጓጉለዋል ያሉት የምክር ቤት አባላቱ« የመንግሥት ሠራተኞችን ደሞዝ የሚያሳጣ መዋቅር መኖር የለበትም። ማዳበሪያን በተመለከተ አሁን ላይ በመንግሥትና በማህበራት እጅ 4ሺህ ብር የነበረው አንድ ኬሻ ማዳበሪያ በነጋዴዎች እስከ 20 ሺህ ብር እየተሸጠ ይገኛል ይህ ለምን ይሆናል? በማለት ጠይቀዋል ፡፡...
በአማራ ክልል በመከላከያ ሰራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚደረገውን ውጊያ ተከትሎ በክልሉ በተለይ በምዕራብ ጎጃም ዞን ፈረስቤት በተባለ ቦታ ንፁሃን መገደላቸውን የአይን እማኝ ለዶቼ ቬለ ገልፀዋል። በክልሉ በሚደረገው ውጊያ በከተሞች መደበኛ እንቅስቃሴ በመገታቱ ለችግር መጋለጣቸውንም በአዊ ብሄረሰብ ዞን አንድ የእንጅባሪ ነዋሪ ተናግረዋል።...
ሶማሊያ በቅርቡ ከቱርክ ጋር የገባችው ስምምነት ከኢትዮጵያ ጋር የቀጠለውን የባህር ውዝግብ ከፍ አድርጎታል። ሁለቱ ሀገራት ያደረጉት የፀጥታ ስምምነት ባልተረጋጋው የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ከፍተኛ ስጋት ይፈጥራል ሲሉ ባለሙያዎች ይናገራሉ።አንዳንዶች ደግሞ ስምምነቱ ለንግግር በር ሊከፍት ይችላል ይላሉ።...
አንድ ኩንታል ጤፍ እስከ 15 ሺህ ብር መድረሱን የነገሩን ነዋሪ ዘይትም 5ቱ ሊትር ከአንድ ሺህ ብር በላይ መድረሱን፣ጤፍ በኩንታል 11 ሺህ የነበረው አሁን 14 ሺህ፣ 15 ሺህ መድረሱን፣ ስኳር አንዱ ኪሎ አሁን 130 ብር እንደሚሸጥ፣ ዘይት 5 ሊትር ወደ 850 ብር የነበረው ዛሬ ላይ እስከ 900 ብር፣ እስከ 1 ሺህ ብር ደርሷል ብለዋል።...
የአየር ካርጎ አገልገሎቱ ወደ ኢ-ኮሜርስ አገልግሎት ማደግ አለበት ያሉት አቶ መስፍን ጣሰው ዛሬ ግንባታው ተጠናቆ የተመረቀው የካርኮ መጋዘን ከተለመደው የሚለየው፤ ትናንሽ እቃዎች በጥቅል መጥተው ግን እዚህ ተበትነው ለደንበኞች የሚደርሱበት አሰራር የሚዘረጋ በመሆኑ ነው በማለት አየር መንገዱ ዘርፉን መቀላቀሉን አረጋግጠዋል።...
«ስለ ሥነ-ጥበብ ካወራን ፤ ወደ ሰላም ወደ ፍቅር ወደ አንድነት የሚልከን ጎዳ ነዉ። በአሁን ወቅት በተለያዩ ጉዳዮች የተወጠረ ዓለም ላይ ነዉ የምንገኘዉ። ይህን በሥነ-ጥበብ በኪነ-ጥበብ ማስተንፈስ ያስፈልጋል። በጎ ነገራችንን ማሰብ አለብን። በዓዉደ ርዕዩ ላይ የቀረቡት ስዕሎች ላይ እንደተመለከተዉ፤...
"የአስራ ስምንት ወር የጡረታ አበላችን ይከፈለን" ፣ "ፍትሕ ለጡረተኞች" የሚሉና ሌሎች መፈክሮች ያሰሙ የነበሩት እነዚህ ከተለያየ የመንግስት ስራ መስክ በጡረታ ተገለው፥ በሚሰጣቸው ወርሓዊ የጡረታ አበል የሚተዳደሩ የዕድሜ ባለፀጎች፥ በሰልፍና በተደጋጋሚ ለሚመለከተው የመንግስት አካል ያቀረቡት አቤቱታ እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱን በማንሳት ይወቅሳሉ...
በኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዐሥር ወራት ርዳታ ለማቅረብ 3.2 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ መንግሥት እና አጋሮቹ ለለጋሾች ያዘጋጁት ዕቅድ አሳይቷል። ዕቅዱ ግጭት፣ የከባቢ አየር ለውጥ ዳፋ እና ወረርሽኞች በተደራረቡባት ኢትዮጵያ ርዳታ በአፋጣኝ እና በዘላቂነት ካልቀረበ ሰብአዊ ቀውስ ሊቀሰቀስ እንደሚችል የሚያስጠነቅቅ ነው።...
በሳምንቱ መጀመሪያ ሰኞ ዕለት ፓሪስ ፈረንሳይ ላይ 20 የሚሆኑ የአውሮጳ ሃገራት መሪዎች ጋር የተወያዩት ፕሬዝደንት ኢማኑዌል ማክሮ ለዩክሬን የሚደረገውን ድጋፍ በወታደር ኃይልም የማጠናከር ሃሳብ አቅርበዋል። ሆኖም ካልነጠፈው የጦር መሣሪያ ድጋፍ ጎን ለጎን ወደ ዩክሬን እግረኛ ጦር ስለመላክ በቀረበው ሃሳብ ተባባሪዎቹ ሃገራት አልተስማሙም።...
አዲስ አበባ ውስጥ በፀጥታ ኃይሎች የተያዘው ፈረንሳዊ ጋዜጠኛ አሁንም በምርመራ ላይ እንደሚገኝ የሚሠራበት የዜና ተቋም ከፓሪስ ለዶቼ ቬለ አስታወቀ። አፍሪካን ኢንተለጀንስ የተሰኘው ድረ ገጽ ዘጋቢ ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንትዋን ጋራንዶ ባለፈው ሳምንት በሥራ ላይ እንዳለ በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለጸው።...
ኢትዮጵያ በጎርጎሮሳዊው 2024 ለሰብዓዊ ዕርዳታ 3.2 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋት የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ባወጣው ዘገባ ይፋ አደረገ። የተቋሙ የኢትዮጵያ ጽሕፈት ቤት እንዳለው በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ 21.4 ሚሊዮን ዜጎች ሰብዓዊ እርዳታ ፈላጊ ሲሆኑ 16 ሚሊዮኑ የምግብ ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል።...
ባለፈው ዓርብ የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ወደአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን ከሚሴ ሲጓዙ የነበሩ መምህራንና ሌሎች ሰዎች ከህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ወርደው መገደላቸው ተሰምቷል። የእረፍት ጊዜያቸውን ከቤተሰቦቻቸው ጋር አሳልፈው የትምህርት መጀመርን ተከትሎ ወደ ከሚሴ ሲጓዙ ከተገደሉ አንዱ መምህር ኤፍሬም እንዳሉ ናቸው።...
።ፀሐይ በኢትዮጵያ የተሰራች የመጀመሪያዋ አውሮፕላን ስትሆን፤ የተገጣጠመችው በጎርጎሪያኑ 1935 ዓ/ም የፀደይ ወቅት በጀርመናዊው አብራሪ ሉድቪሽ ቬበር እና በወቅቱ በነበሩ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎችች ነበር። ለመሆኑ የነበራት ቴክኒካዊ ይዘት እና የዚያን ዘመኑ የአቬሽን ቴክኖሎጅ ምን ይመስል ነበር?...
በተለያዩ የአውሮጳ ሀገራት ለዩክሬን ስደተኞች የሚደረገው አቀባበል ይለያያል። ከአንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሰላሳ ሺህ በላይ ዩክሬናውያንን ሀገርዋ ያስገባችው ጀርመን ስደተኞቹን በመንከባከብ ተወዳዳሪ የላትም ። መንግሥት ለዩክሬን ስደተኞች የሚወጣው ገንዘብ በቢሊዮኖች ዩሮ የሚቆጠር ነው።...
ማህበረሰባዊ የጸባይ ለውጥ በህብረተሰቡ ውስጥ ያሉትን መልካም ልማዶች እያበረታቱ ጎጂዎችን በሌላ መተካት ነው የሚሉት የጥናትና ምርምር ባለሙያ፤ አሁን አሁን በኢትዮጵያ ማህበረሰባዊ የጸባይ ለውጥን የመፍጠሩ አስፈላጊነት ጉልህ እንደሆነም ያምናሉ፡...
ሀብትና ንበረት ወደ አፈራንበት ዴቻ ወረዳ በመመለሰ እንደሚያቋቁሙን በተደጋጋሚ ገልጸውልን ነበር የሚሉት አርሶአደሮቹ “ ነገር ግን የተገባው ቃል አሁን ድረስ ተግባራዊ ሊሆን አልቻለም ፡፡ ይልቁንም የክልሉ መንግሥት የአርሻ መሬታችንን ለባለሀብቶችና ግለሰቦች መሰጠቱን መረጃ አግኝተናል ይላሉ።...
ተፈናቃዮችን ወደ ቀድሞ አካባቢያቸው መመለስ ቢጀመርም አሁንም ግን የፀጥታ ስጋት እንዳለ ተመላሾቹ ለDW ተናግረዋል። በአካባቢው የፀጥታ ስጋት በመኖሩም ወደ ቀድሞው ቀያቸው እስከአሁን ሳይሄዱ በወረዳ ከተማ በተዘጋጀው መጠለያ ውስጥ እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡...
ስድስተኛው የተመድ የአካባቢ ጥበቃ ጉባኤ በናይሮቢ ኬንያ ትናንት ተጀምሯል። በርካታ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሮች እና በሺህዎች የሚገመቱ ተሳታፊዎች የሚገኙት ይህ ጉባኤ የአየር ንብረት ለውጥ ስላስከተለው ቀውስ፤ የተፈጥሮ ይዞታ እና እየጠፋ ስላለው ብዝሃ ሕይወት ከትናንት አንስቶ እስከ ፊታችን ዓርብ ድረስ እንደሚወያይ ተገልጿል።...
በሆስፒታሉ ሕክምና እና የምግብ ድጋፍ የሚደረግለት ህፃኑ ሀፍቱ ንጉሱ አሁን በጥቂትም ቢሆን መሻሻል እያሳየ ነው። ባለፈው ክረምት ዝናብ ባለመዝነቡ ምንም ዓይነት ምርት ያላገኙት አርሶአደሮቹ የህፃኑ ወላጆች፥ አሁን ላይ መላ ቤተሰብ ለረሃብ ተጋልጠው ይገኛሉ። ለተእግዚሄር እና ልጆችዋ ካለፈው ጥቅምት ወር ወዲህ በከተሞች በልመና ተሰማርተዋል።...
አንድ ነዋሪ በኦሮሚያ በተለይም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በተለይም አራት ወረዳዎች፤ ቶሌ፣ በቾ፣ ሰዴን ሶዶ እና ሶዶ ዳጪ በሚባሉ ወረዳዎች በየጊዜው በሚፈጠረው ግጭት ሰው ያልቃል፤የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በሌሊት ሲንቀሳቀሱ እገታ በመፈጸም ከመንግስት ጋር ናችሁ ይላል፤ቀን የመንግስት ጦር ከታጣቂዎቹ ጋር ትሰራላችሁ በሚል ህዝቡ ተሰቃይቷል”ብለዋል፡፡...
የደብረብርሀን ከተማ ነዋሪ በመንገዱ መዘጋት በርካታ ሰዎች በደብረብርሀን አውቶቡስ መናኸሪያ ለእንግልት መዳረጋቸውን ተናግረዋል።፡“ወደ አዲስ አበባም እንዳይኬድ፣ ተዘግቷል፣ ከጫጫ ጀምሮ ወደ አዲስ አበባም መሄድ አይቻልም፣ ወደ ጅሩም መጓዝ አይቻልም፣ ዋና መንገዱ ስለተዘጋ ሁሉም ቦታ መሄድ አይቻልም፣የደብረብርሀን መናኸሪያ ዝግ ነው»ብለዋል...