Home › View all posts by DW Amharic
Blog Archives
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስተኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ምርጫ እንደሚካሄድ አስታወቀ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አፋር፣ ሶማሌና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ በሚገኙ ምርጫ ክልሎች የምርጫ ማስፈጸሚያ ጊዜ ሴለዳ ቦርዱ ይፋ አድርጓል።...
የአፍሪቃ ሕብረት «የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው» በሚል የተሰራጨው መረጃ «የተሳሳተ» ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ።...
ሶማሊላንድ ከሶማሊያ እራሷን በመነጠል እራስ ገዝ ከሆነች ሦስት አስርት ዓመታት አለፉ። ዛሬም ግን ሶማሊላንድ እንደ ሀገር ዓለም አቀፍ እውቅና አላገኘችም።
በአፍሪቃ እየተስፋፋና እየተጠናከረ ነው የተባለውን የአሸባሪዎች ጥቃት ለመክላከል ብሎም ለማጥፋት በሚቻልበት ሁኔታ የመከረ የአፍርቃ የጸረ ሽብርና ደህንነት ከፍተኛ ጉባኤ በዚህ ሳምንት ሰኞና ማክሰኞ በናይጀሪያ ዋና ከተማ አቡጃ ተካሂዷል።...
አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ፍልስፍና ረዳት ፕሮፈሰር ሲሳይ አሰምሬ የኮሚሽኑን ገለጻ ለመረዳት መቸገራቸውን ይናገራሉ፡፡ “ኮሚሽኑ የታጠቁ አካላት መንግስት ያስረናል ይጮቅነናል በሚል ነው ትጥቅ አንግበው በራሳቸው መንገድ የሚታገሉት...
በዛሬው ችሎት ዐቃቤ ሕግ ክስ ማሻሻል ምስክሮችን ለጉዳት የሚዳርግ ነው በሚል ያንን ማድረግ እንደማይችል በጽሑፍ አቤቱታ አቅርቧል። የተከሳሽ ጠበቆችም በበኩላቸው በቃል ክርክር በማድረግ ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾችን ጥያቄ እንዲመልስ ተከራክረዋል።...
ትምህርት ቤቶቹ የተዘጉት ከባለፈው የመጋቢት ወር ጀምሮ ደሞዝ አልተከፈለንም ያሉ መምህራን ሥራ በማቆማቸው ነው ተብሏል ፡፡ የትምህርት ቤቶቹን መዘጋት ለዶቼ ቬለ ያረጋገጡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር ሊቀመንበር በበኩላቸው “ የመምህራኑን ጥያቄ ለመፍታት ማህበሩ ከዞን እና ከክልል ትምህርት ቢሮች እየተነጋገረ ይገኛል “ ብለዋል...
የጀርመን ፌዴራል ፕሬዝደንቶች በሥልጣን ላይ እያሉ መጽሐፍ መፃፍ ብዙ ጊዜ የተለመደ ባይሆንም፤ ከሰባት ዓመታት በላይ ጀርመንን በፕሬዚዳንትነት እየመሩ ያሉት ፍራንክ ዋልተር ሽታይንማየር ይህንን አድርገዋል።ሽታይንማየር በቅርቡ ባወጡት «እኛ» በተሰኘው አዲሱ መጽሃፉቸው በብዝሃነት ውስጥ አንድነትን ይፈልጋሉ።...
የሰላም ጥሪ ምንጊዜም ተቀባይነት ያለው ሀሳብ መሆኑን የገለፁ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች፤ ይልቁንም ፓርቲዎች መሰል ጥሪ ሲያደርጉ መቆየታቸውን በመግለጽ ሰሚ እንዳላገኙ ገልፀዋል። ይህ የመንግሥት ጥሪ እውነተኛ እና ለዘላቂ መፍትሔ ታምኖበት የተደረገ ስለመሆኑ ጥርጣሬ እንዳላቸውም አብራርተዋል።...
የምስራቅ ሀገሪቱ የአገልግሎት እና የኢንዱስትሪ ማዕከል በሆነችው ድሬደዋ የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት ሽፋን የፍላጎቱን ሃምሳ በመቶ እንኳን እንደማይደርስ የሚያነሳው የመስተዳድሩ ውሀ እና ፍሳሽ ባለስልጣን "ፍላጎት እና አቅርቦት አለመጣጣም" ህብረተሰቡ ለገጠመው ችግር ዋንኛ ምክንያት መሆኑን ገልጿል...
የ25 ዓመት ፎዝያ ጀማል ሳዉዲአረብያ ስትኖር አምስት ዓመት ሆኗታል። የማዳም ቤት ገጣሚ ነኝ፤ የደሴ ልጅ ወሎዬ ስትል ራስዋን ታስተዋዉቃለች። በቲክቶክ የመጽሐፍት አንባብያንና ገጣምያን መድረክ ላይ ግጥሞችዋን በማቅረብም ትታወቃለች። በቅርቡ ቲክታክ ላይ በነበረ የሥነ-ግጥም ዉድድርም አሸናፊ ሆናለች። የግጥም መድብሏ በቅርቡአንባብያን እጅ ይደርሳል።...
ኢኒሼቲቭ ፎር ቼንጅ በተባለው ድርጅት ውስጥ የሚሰሩት አቶ ገረሱ ቱፋ የሰሞኑን የኦሮሚያ ሁኔታ በተስፋም በስጋትም እንደሚመለከቱት ያስረዳሉ።የፖለቲካ ሳይንስ ምሁርና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፖለቲከኛ መረራ ጉዲና አሁን በኦሮሚያም ይሁን በመላ አገሪቱ ግጭቶች የመባባስ እንጂ የመርገብ ምልክት አላሳዩም ብለዋል፡፡...
በትግራይ ለ2 ዓመት በተካሄደው ጦርነት ለደረሰው ሰብዓዊ ችግር ለመድረስ "እኛ ለትግራይ ዓለም ነን" የተሰኘ ዓለም አቀፍ የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ተጀመረ።አስተባባሪው ኘሮፌሰር ሙሉጌታ ገብረእግዚአብሄር ለዶይቸ ቨለ እንደገለጹት፣በትግራይ ከተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት በኃላ የደረሰው ሰብዓዊ ቀውስ ፣አስቸኳይ እርምጃ ያስፈልገዋል።...
በዓለም አቀፉ የሰላም ጥናት ተቋም መግለጫ መሠረት በ2023 ዓ.ም. ዩናይትድ ስቴትስ ቻይናና ሩስያ ዋነኛዎቹ የጦር መሣሪያ ሻጭ አገራት ናቸው። የሩስያ ወታደራዊ ወጪ በ24 በመቶ ማለትም በ109 ቢሊዮን ዶላር አድጓል።ዩክሬን ለጦር መሣሪያ ግዥ ያወጣችውና ከውጭ ያገኘችው ወታደራዊ እርዳታ በአጠቃላይ ከሩስያ ወታደራዊ ወጭ 91 በመቶው ያህል ሆኗል።...
አዲሱ ጥናት እንዳረጋገጠው አረቢካ የቡና ዝርያ የተገኘው ከ610,000 እስከ አንድ ሚሊዮን ዓመታት በፊት ባለው ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ደኖች ውስጥ ነው። ይህ የቡና ዝርያ ከዛሬ 300,000 ዓመታት በፊት በአፍሪካ ከነበረው ዘመናዊ የሰው ዝርያ /Homo sapiens/ በዕድሜ ቀደምት ነው።...
ከብልፅግና ጋር የሚያገናኘው የጋራ አጀንዳው የፕሪቶርያው ውል መሆኑን የገለጸው ህወሓት ውሉ በሙሉ እንዲተገበር አጋዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብልፅግና ፓርቲና ህወሓት በመቐለና አዲስአበባ መወያየታቸውን አስታውቋል። ከዚህ ውጭ ህወሓትና ብልፅግና ፓርቲ በመገናኛ ብዙሐን እንደተባለው የጀመሩት ወደ ውህደት የሚመራ ውይይት የለም ሲል አስተባብሏል።...
በአማራና ትግራይ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች በተከሰተ ግጭት ከ50 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ያለፈው ሰኞ አስታውቋል። እንደ ድርጅቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፤ በተለይ ሴቶችና ህጻናት የሚገኙበት ሁኔታም አሳሳቢ ነው።...
በዚህ የመንግሥት ውሳኔ መሠረት የውጭ ባለሃብቶች ቡናና የቅባት እህሎችን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ምርቶችን እና የቁም እንስሳትን ወደ ውጪ እንዲልኩ ፣ ከነዳጅ እና ማዳበሪያ በስተቀር በሁሉም ገቢ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ይፈቀድላቸዋል።...
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የምስራቅ ሀረርጌ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ መልዓከ ገነት ቀሲስ ንጋቱ ደሣለኝ ለዶይቼ ቬለ በስልክ በሰጡት መረጃ በሀረር ከተማ የቤተ ክርስትያኒቱ ንብረት የነበረና በደርግ መንግስት ተውርሶ ለማስመለስ በፍርድ ቤት ሂደት ላይ የሚገኝ ይዞታ እንዲፈርስ መደረጉን ገልፀዋል ።...
አጣዳፊ የተቅማጥና ትውከት (አተት) በሽታ ከመጋቢት 27/2016 ዓ ም ጀምሮ በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር መከሰቱን የወረዳው ጤና ጽ/ቤት የባቲ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የጥራት ቁጥጥር ባለሙያ አቶ ፉአድ ቶፊቅ በባቲ ወረዳ 5 ቀበሌዎች 86 ሰዎች በበሽታው ተይዘው ህክምና እየተከታተሉ እንደሆነ አመልተዋል፡፡...
መረጃውን ያጋራው ግለሰብ የቤተሰባቸው አባል የሚገኙበት ዘጠን ሰዎች በምዕራብ አርሲ ዞን አዳባ ወረዳ ወሻ እና ቡቢሳ በተባሉ ቀበሌያት ተገድለው ተጥለው ቢገኙም አንስተው ለመቅበር እንኳ እድሉን መነፈጋቸውን ጠቅሰው ለማን እንንገር በማለት አስተያየታቸውን በሀዘን አጋርተዋል፡፡...
በትግራይ፣ዕድሜአቸው ከ15 እስከ 29 የሆኑ ወጣቶች ቁጥር 2 ነጥብ 9 ሚልዮን ይገመታል።የሁለት ዓመቱ ጦርነት ዋነኛ ሰለባዎች መሆናቸው የሚገለፅላቸው እነዚህ ወጣቶች ከጦርነቱ በኃላ ባለው ግዜም በስራ እጦት፣ ተስፋ ማጣት እና ሌላ ግጭት ስጋት እግራቸው ወደመራቸው መሰደድ፣ ለተለያዩ ሱሶች እና ወንጀሎች መጋለጥ በስፋት እየታየባቸው መሆኑ ይገለፃል።...
በአሁኑ ጊዜ ለኦቲዝም የተጋለጡ ልጆች ቁጥር እየጨመረ መሄዱን የአሜሪካው የበሽታዎች መቆጣጠሪያን መከታተያ ማዕከል ይፋ ያደረጋቸው መረጃዎች ያመለክታሉ። የዓለም የጤና ድርጅት ከአንድ መቶ ልጆች ውስጥ ቢያንስ በአንዱ ላይ ኦቲዝም ሊያጋጥም እንደሚችል ይገልጻል።...
በዚህ ዓመት ከጥር እስከ ሚያዚያ እስራኤል ከጀርመን የገዛችው የጦር መሣሪያ 326.5 ሚሊዮን ዩሮ የወጣበት ነው።ይህም በ2022 ለጦር መሳሪያ ከወጣችው 32 ሚሊዮን ዩሮ በአስር እጅ ይበልጣል። በግዥው ከተካተቱ ውስጥ 20.1 ሚሊዮን ብር የወጣባቸው ፀረ-ታንክ መሣሪያዎች እና የአውቶማቲክና የመለስተኛ አውቶማቲክ ጠመንጃ ጥይቶች ይገኙበታል።...
ሰሞኑን በራያ አላማጣና አካባቢው ከተፈጠረው የሰላም መደፍረስ ጋር በተያያዘ የተፈናቀሉ ነዋሪዎች አሁንም ህብረተሰቡ ከሚያደርግላቸው ድጋፍ ውጪ ድጋፍ እንዳላገኙ አመለከቱ።...
ኢትዮጵያ ውስጥ የተወሳሰቡ የፖለቲካ እና የጸጥታ ቀውሶችን ለመፍታት ብሎም በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ብቸኛው መንገድ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ውይይት ማድረግ መሆኑን በኢትዮጵያ የሚገኙ የ 7 ሀገራት ኤምባሲዎች በጋራ ባወጡት መግለጫ ገለፁ።...
በጋምቤላ ክልል አኙዋ ብሔረሰብ ዞን ጆር ወረዳ ውስጥ መጋቢት 26/2016 ዓ.ም ከደቡብ ሱዳን የመጡ ታጣቂዎችና በክልሉ ውስጥ የሚገኙ ጸረ ሰላም የተባሉ ሀይሎች በመተባበር ባደረሱት ጥቃት 738 ቤቶች መቃጠላቸው ተገለጸ፡፡...
ባለፈው ሳምንት በአፍሪካ ኅብረት ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል በመቅረብና ከአፍሪካ ኅብረት የክፍያ ሰነድ ጋር ተመሳስለው የተዘጋጁ የተለያዩ ሐሰተኛ ሰነዶችን በመጠቀም፣ ከአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ ከስድስት ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማዘዋወር ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል።...
የገንዘብ ሚንሰትር አቶ አህመድ ሺዴን ጨምሮ ሌሎች ባለስልጣናት ሰሞኑን ከዓለም ባንክ (WB) እና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(IMF) ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በዩናይትድ ስቴትስ ተወያይተዋል።...
የኢራን እና የእስራኤልን ቁርቁስ በአንክሮ የሚከታተሉ ጉምቱ ዲፕሎማቶች እና ተንታኞች መካከለኛው ምሥራቅን የሚያዳርስ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ሰግተዋል። በደማስቆ የተፈጸመ ጥቃት የሁለቱን ሀገራት የበርካታ አስርት ዓመታት የእጅ አዙር ፍልሚያ ገሀድ ቢያወጣውም በመካከላቸው በቂ ቂም እና አለመተማመን አለ።...
ወደ ሳዑዲ አረብያ ለመሄድ ጉዞ የጀመሩ 38 ኢትዮጵያውያን ጅቡቲ ድንበር አቅራቢያ የተጫኑበት ጀልባ ሰጥሞ ባለፈው ሳምንት ሞተዋል። በዚሁ ሳምንት ነበር ሳዑዲ አረብያ ውስጥ ችግር ላይ የወደቁ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ጥረት የቀጠለው።በአሁኑ ጊዜ በአደገኛ ጉዞ መላልሰው ወደ መካከለኛው ምሥራቅና ወደ ደቡብ አፍሪቃ የሚሄዱ ጥቂት አይባሉም።...
በጀርመን የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ምዕምናን ፍራንክፈርት ከተማ ሰልፍ አካሔዱ። በተለያዩ የጀርመን ከተሞች የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት አባቶች እና ምዕምናን መሳተፋቸውን በጀርመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ካሕናት መራዊ ተበጀ ለዶይቼ ቬለ አስረድተዋል።...
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በሌላ መንገድ እየታገሉ ይገኛሉ ያላቸው አካላት ወደ ምክክር መድረኩ እንዲገቡ ጥሪ አቀርበ። በምክክሩ መድረኩ ለሚሳተፉ ለእነኝሁ አካላት ኮሚሽኑ ተገቢውን የጥበቃ ዋስትና እንደሚያመቻች አስታውቋል። የታጠቁ የሚባሉት ቡድኖች እስከአሁን በአገራዊ የምክክር ጉባዔው ሥለመሳተፍ አለመሳተፋቸው በይፋ ያሉት ነገር የለም።...
በደቡብ አፍሪቃ ከዐሥር ዓመት ወዲህ የተስፋፋው የኮሌራ ወረርሺኝ በዋናነት ዛምቢያ፤ ዚምባብዌ እና ማላዊን አጥቅቷል ። ወረርሺኙን ለመቅለበስ የነበረው የክትባት ክምችትም እየተሟጠጠ ነው ።...
ለቸኮሌት ምርት ዋነኛ ግብአት የሆነው የካካዎ ምርት ባለፉት ጥቂት ወራት ዋጋው በዓለም ዙሪያ በሦስት እጥፍ ጨምሯል ። ገበሬዎች ከፍተኛ ክፍያ እንዲፈጸምላቸውን እና ከድህነት እንዲወጡ ይሻሉ ። ሲታይ ቀላል የሚመስለው ጉዳይ ግን የዚያን ያህል ቀላል አይመስልም ።...
በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ የወባ በሽታ መስፋፋቱና ከ200 በላይ ሰዎች በወባ መታመማቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። በዚህ ቶሌ በተባለው አካባቢ የሚገኙ ዜጎች የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ ተፈናቅለው ወሎ እና ደብረብርሃን ቆይቶ በየካቲት ወር 2016 መጀመሪያ ላይ ወደቤታቸው የተመለሱ ናቸው።...
oይነሥውር መሆኑ የስፖርት ዘገባ ከመሥራት እንዳላገደው ይናገራል።ጋዜጠኛ መረጃዎችን አሰባስቦ እና ተንትኖ ለአድማጮቹ የሚያደርስ መሆኑን የጠቀሰው ሙሉቀን “ እኔ ይህንኑ የዘገባ ሥራ ለዛውም በስፖርት ዘርፍ እየሠራሁ እገኛለሁ, እይታን ከሚፈልጉ ከኮሜንታተርነት እና ከዳኝነት ሥራዎች በስተቀር አንድ አይነ ሥውር ስፖርትን መዘገብ ይችላል» ብሏል ፡፡...
ባለፈው ሳምንት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር በተገደሉበት ምሥራቅ ሸዋ ዞን መቂ ከተማ ከሰሞኑ በኅቡዕ ታወጀ ከተባለው የመጓጓዣ አገልግሎት እቀባ ጋር በተያያዘ ተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱ እየተነገረ ነው።...
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር የነበሩት ፖለቲከኛ በቴ ዑርጌሳ በአሰቃቂ ሁኔታ በትውልድ አካባቢያቸው መቂ ከተማ ተገድለው ከተገኙ 11 ቀናት አልፈዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥም በርካቶችን ያስቆጣው የፖለቲከኛው ግድያ በርካታ ሁነቶችን አስተናግዷል።...
በትግራይና አማራ አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንዳለባቸው ምሁራን አመለከቱ።
የአማራና የትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት መከሰቱ ለምን? ጠ/ሚ አቢይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ጋር እንዲወያዩ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት መጠየቁ፤ በኢትዮጵያ ለሚታየዉው የከፋ የሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት በመንግሥትና ዓለምአቀፍ አጋሮች በተጠራው የገንዘብ ማሰባሰብ 610 ሚሊዮን ዶላር መሰብሰቡ።...
በተለይም ከቅርብ ቀናት ወዲህ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭቶች እያገረሹ ይገኛሉ። በዚህም ሞትና መፈናቀል ተከስቷል። የሁለቱ ክልል አስተዳደሮችም እርስ በራሳቸው እየተወነጃጀሉ ይገኛሉ።...
በኢትዮጵያ ለተከሰተው የከፋ የሰብአዊ ቀውስ ድጋፍ ለማሰባሰብ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ውስጥ በተደረገው ዓለም አቀፍ ድጋፍ የማሰባሰብ ሥራ ከታቀደው እጅግ ዝቅ ያለ ገንዘብ ቃል መገባቱ ተገለጠ ። 3.24 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ታቅዶ ቃል የተገባው ግን 630 ሚሊዮን ዶላር መሆኑም ተጠቅሷል ።...
የወልቃይት፣ ጠገዴ ጠለምትና ራያ ጉዳይ በፖለቲካዊ ውሳኔ እንዲፈታ በአሜሪካ የሚገኙ 8 ኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅቶች ጥሪ አቀረቡ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን «እየተባባሰ መጥቷል» ባሉት ጠለፋ የተነሳ ሴት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ ። በዞኑ በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ አስተማሪ የሆነ ቅጣት ስለማይሰጥ አሁን ላይ ሴት ልጆች ወጥተው ለመግባት ሥጋት ውስጥ መውደቃቸውን ነው ነዋሪዎቹ ለዶቼ ቬለ የተናገሩት ።...
ለጥንታዊቷ ሀረር ከተማ ከወራት በፊት በዓለም አቀፉ የሳይንስ ፣ የትምህርት እና የባህል ድርጅት በእንግሊዝኛ ምኅፃሩ/ UNESCO ሁለተኛ ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው የሽዋልኢድ ዓመታዊ በዓል የከተማይቱን የቱሪስት መዳረሻነት እድል ይበልጥ ያሰፋል የሚል እምነት አሳድሯል።...
ረቡዕ ሚያዝያ 9 ቀን የጀመረው የ27ቱ የአውሮጳ ኅብረት አገሮች የመሪዎች ስብሰባ ዛሬ ከስአት በኋላ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቅቋል ። የጉባኤው አጀንዳ ምን ነበር? ትናንት እና ዛሬ የተከናወነው የኅብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ምንስ ውሳኔ አሳልፎ ተጠናቀቀ?...
የዓዉደ ርእዩ መጠርያ ንጹሕ ምንጭ ኢትዮጵያ ይሰኛል። ኢትዮጵያ ብዙ ንጹሕ ምንጮች አልዋት። ከነዚህ ንጹሕ ምንጮች መካከል፤ የራስዋን ድርሳናት፤ ሥነ- ነገር የከተበችባቸዉ ፊደላት የሚጠቀሱ ናቸዉ። እግዚቢሽኑን የሚመሰገን ፤ የወጣቶቹ ሥራ ለሃገሪዉ ሃገሩን፤ ነባር ባህሉን እና እዉቀቱን እንዲያዉቅ የሚያደርግ ብዙ ምንጮችንም የሚያሳይ ነዉ።...
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ያደረጉትን ተከታታይ ውይይት ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ጋርም እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ጠየቀ። ምክር ቤት የውይይት ጥያቄውን ከሦስት ሳምንት በፊት ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ማስገባቱን እና ምላሽም እየተጠባበቀ መሆኑን አስታውቋል።...
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከ1300 በላይ ባለሀብቶች መሬት የተረከቡ ቢሆንም የሚፈለገውን ያህል ውጤት ሳይገኝ መቆየቱ ተገለጸ። ባለሀብቶች የተሳተፉበት ክልል አቀፍ የግብርና ኢንቨስትመንት መድረክ ትናንት በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል።...
ባለፈው ሳምንት ዓርብ አዲስ አበባ ውስጥ የተገደሉት የፋኖ አባላት አስከሬን እስካሁን ለቤተሰብ አለመሰጠቱን የሟቾች ቤተሰቦች ተናገሩ። አስተያየታቸውን ለዶቼ ቬለ የሰጡ የቤተሰብ አባላት ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ከፌዴራል ፖሊስ እስከ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ቢመላለሱም የሟቾቹን አስከሬን ተረክበው ለመቅበር አለመቻላቸውን አስረድተዋል።...
የኢትዮጵያ መንግሥት የችርቻሮ ንግድ ለውጭ ባለወረቶች ሲፈቅድ ከ2 ሺሕ-10 ሺሕ ስኩዌር ሜትር የሚሰፉ ሱፐርማርኬቶች እንዲገነቡ ይፈልጋል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ መመሪያ በወጪ፣ ገቢ እና ጅምላ ንግድ ዘርፎች የውጭ ባለወረቶች እንዲሳተፉ የሚፈቅድ ነው። የመንግሥት ጉልህ ፖሊሲ ለውጥ ለአንዳንድ ባለሙያዎች ተስፋ ለሌሎች ሥጋት ያጫረ ሆኗል።...
ባለሙያዎች እንደሚሉት በተንቀሳቃሽ ስልኮች፣በታብሌት፣በቴሌቪዝን እና በሌሎች ዲጅታል መሳሪያዎች ላይ ረዘም ያለ ጊዜ የሚያሳልፉ ልጆች ለጭንቀት እና ለመረበሽ፣ ለትኩረት ማጣት፣ ለንግግር እና ለቋንቋ መዘግየት እንዲሁም ለግንዛቤ እድገት ውሱንነት ይዳረጋሉ። የሰዎችን ስሜት የመረዳት እና የመግባባት ችሎታቸውንም ይቀንሳል።...
በኢትዮጵያ በድርቅ፤ ጎርፍና ጦርነት ምክኒያት ለከፍተኛ ችግር የተዳረጉ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመርዳት የሚያስችል ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ ትናንት ሲዊዘርላንድ ጀኔቭ በተዘጋጀ መርሃ ግብር፤ ከለጋሾች 630 ሚሊዮን ዶላር መገኘቱ ተገለጸል።...
የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት «ህወሓትና ግብረ አበሮቹ» ያላቸው አካላት ሁለቱ ወገኖች የይገባኛል ጥያቄ ከሚያነሱባቸውና ሰሞኑን በኃይል ከያዟቸው አካባቢዎች በአስቸኳይ እንዲወጡ አሳሰበ። የአማራ ክልላዊ መንግሥት በመግለጫው የፕሪቶሪያው ስምምነት እንዲተገበርም ጠይቋል።...
በአውሮጳ ሻምፒዮንስ ሊግ ግጥሚያ ዛሬም ማታም ሁለት ወሳኝ ግጥሚያዎች ይኖራሉ ። በምሽቱ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ በሚደረጉ ግጥሚያዎች፦ የጀርመኑ ባዬርን ሙይንሽን ከእንግሊዙ አርሰናል ጋ ይፋጠጣል ። ሌላኛው የእንግሊዝ ቡድን ማንቸስተር ሲቲ ከስፔኑ ሪያል ማድሪድ ጋ ይፋለማል ።...
ኢትዮጵያ ውስጥ የተቃውሞ ፓርቲዎች ህልውና አነጋጋሪ ከሆነ ሰነባበተ። ለእንቅስቃሴያቸው መዳከም አብዛኞቹ የገዢውን ፓርቲ የተጠናከረ ጫና በዋናነት ሲገልጹ፤ የራሳቸው የፓርቲዎቹ እራስን እየተቹና እያረሙ የማደግ ድክመትም ለውጪው ጫና ተጋላጭ እንዳደረጋቸው በምክንያትነት የሚያነሱም አሉ።...
ፑቲን ቢቃወሙም ኔቶ መስፋፋቱን በመቀጠል ለቀድሞዎቹ የሶቭየት ኅብረት ግዛቶች ጆርጅያና ዩክሬን የኔቶ አባል እንዲሆኑ ቃል ገባላቸው። ያኔ ግን ፑቲን ስልታቸውን ቀየሩ። በጆርጅያ ላይ ጥቃት በመሰንዘር የተወሰነውን የጆርጅያ መሬት ያዙ። በ2014 የዩክሬንዋን የክሪምያ ልሳነ ምድር ገነጠሉ።በ2022 ሩስያ በዩክሬን ላይ ጦርነት ከፈተች።...
የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ጠላት የሆኑ ኃይሎች ግጭት ለመፍጠር እየጣሩ ነው ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከሰሱ።
የአጥንት መሳሳት ችግር በሁሉም ሰው ላይ ሊከሰት የሚችል እንደሆነ የዘርፉ የህክምና ባለሙያዎች ይገልጻሉ። ችግሩ በሚያጋጥሙ አደጋዎች አጥንት በቀላሉ እንዲሰበር ያደርጋል። አጥንት ጥንካሬ የሚረዳ ነገር ይኖር ይሆን?...
እስራኤል፦ የእሜሪካና የአውሮጳ ወዳጆቿ ሃገራትን ምክር ሰምታ ከኢራን ጋር ወደ ቀጥተኛ ግጭት ከመግባት ብትቆጠብ እንደሚሻል ተገለጠ ። የዊልሰን ማዕከል የመካከለኛው ምስራቅ ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ፕሮፌሠር ማሪና ኦታዌ ቀጥተኛ ግጭቱ አያዋጣም ብለዋል ።...
ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ እንደገና የተቀሰቀሰው የአማራና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት ነዋሪዎችን በገፍ ማፈናቀል መጀመሩ ተገለጠ ። ወደ 10ሺህ የሚሆኑ የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ተፈናቅለው ቆቦ ከተማ ደርሰዋል ተብሏል ።...
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ባለፈው ሳምንት በትውልድ አከባቢያቸው መቂ የተገደሉት የአቶ ቤቴ ዑርጌሳ የግድያ ምርምራ ላይ እምነነት እንደማኖረው ዐስታወቀ ። ኦነግ ይህን ያለው መንግስት 13 ሰዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጾ የሂደቱን መጀመር በይፋ ማሳወቁን ተከትሎ ነው ።...
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማኅማት ከ2009 ጀምሮ ከያዙት ሥልጣን በሚቀጥለው ዓመት ይለቃሉ። የኮሚሽኑ ቀጣይ ሊቀ-መንበር አስራ አራት ሀገራት ከሚገኙበት የምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ይመረጣል። እስካሁን ከሦስት የኢትዮጵያ ጎረቤቶች ዕጩዎች ለአፍሪካ ኮሚሽን ሊቀ-መንበርነት እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል።...
“ከትግራይ ክልል ተሻግረው የመጡ” ያሏቸው ታጣቂዎች ጥቃት እንዳደረሱባቸው የራያ አላማጣ ወረዳ ባለስልጣናትና ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬሌ ተናገሩ። ጉዳዩን አስመልክቶን ከትግራይ ክልል የመንግስት የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃአስተያየት ለማካተት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ የፕሪቶሪያው ስምምነት በህገመንግስቱ መሰረት እንደሚፈታ ዉሉ ያትታል፡፡...
የኢትዮጵያ መንግስት አገራዊ የአደጋ መከላከል ፖሊሲውን ለማሻሻል እያደረገ ያለው ጥረት አበረታች መሆኑን የተጠቆመው የማማክርቱ መግለጫ፣ በየደርጃው የማስፈጸም አቅምን ማጠናከርና ውጤታማ የተጠያቂነት ሥርዓት መዘጋት ያለውን ፋይዳ አስረድቷል። ድርቅን በብቃት ለመቆጣጠርና ረኃብን ለመከላከል፣ ሰላምና መረጋጋት ያለውን ጠቀሜታም አመልክቷል።...
በሐረር ፣ ሚዛን አማን እና ነገሌ ቦረና አካባቢ የሚኖሩ የሠራዊቱ አባላት ቤተሠቦች እንዳሉት፤ ቤተሰቤቻቸው "በጦርነቱ ሞተዋል" ተብለው በመንግሥት መርዶ ተነግሯቸው ነበር። ይሁንና ይህ ከሆነ በኋላ በቀይ መስቀል በኩል ከወታደር ቤተሰቦቻቸው ጋር በስልክ እንደተገናኙና አሁንም አልፍ አልፎ ስልክ እንደሚደውሉላቸው የወታደሮቹ ቤተሰቦች ተናግረዋል።...
የአውሮፓ ፓርላማ የህብረቱን የስደተኞች እና የጥገኝነት ደንቦችን የሚያጠናክር ማሻሻያ ትናንት አፅድቋል።አዲሱ ሕግ የጥገኝነት ሂደትን ለማፋጠን እና መደበኛ ያልሆኑ ስደተኞች ደግሞ ወደ አገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ ለማፋጠን ያለመ ሲሆን፤በጎርጎሪያኑ 2026 ተፈጻሚ ይሆናል። አዲሱ ህግ ምን አካቷል?የአውሮፓ መሪዎችስ ምን ምላሽ እየሰጡ ነው?...
አንድ የቤተሰብ አባል በአቶ ቤተ አስከሬን የተለያዩ የሰውነት አካል ላይ በርካታ ያሉት ቦታ ላይ በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን የሚያመላክት ብዙ ቁስሎች በአይናቸው መመልከታቸውንም አስረድተዋል። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የአቶ በቴ ግድያን ተከትሎ ተጠያቂነቱን ወደ መንግስት ለማድረግ የሚደረግ ያለው አሉባልታ ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቋል።፡...
ፕሬዚደንት ጆሴፍ ባይደንና ቀዳማዊት እመቤት ዶክተር ጂል ባይደን፣በያዝነው ዓመት በጆርጂያ የምርጫ ዘመቻ አካሄደዋል። ተቀናቃኛቸው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ትናንት እዚህ ጆርጂያ ተገኝተው የገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አካሄደዋል። አንድ የፖለቲካ ሳይንስ ፕሮፌሰር እንደሚሉት፣ጆርጂያ በዘንድሮው ምርጫ ቁልፍ ሚና ትጫወታለች።...
የስልጤ ህዝብ መጠሪያውን ያገኘው ከቀደምት የእስላማዊ ሱልጣኔቶች አመሰራረት ሲወርድ በመጣው ሂደት እንደሆነ ይነገርለታል። በተለይ ደግሞ ሀጂ አሊዬ ለልጃቸው ሌላ ሱልጣን (ሱልጣኔት) (ገዢ) የሚል ስም መስጠታቸውን ተከትሎ ስልጤ ለመጠሪያነት መዋሉን የስልጤ ዞን የባህል ጽ/ቤት ከድርሳናት ያገኘውን መረጃ አጋርቶናል።...
ሀጂ ሙስጠፋ አወል ይባላሉ፡፡ በሚከተሉት የእስልምና ሃይማኖት እና በስብእናቸው አንቱታን ያተረፉ በሚል የሚያውቃቸው ይመሰክራሉ፡፡ ዛሬ በቤታቸው ከነመላው ቤተሰቦቻቸው ቤሰተብን የሚያሰባስበው እና የመተሳሰብ የሚሰነውን የኢድ-አልፈጥር በዓልን ሲያከብሩ ዶቼ ቬለ በቤታቸው ተገኝቶ የበዓሉን ድባብ ቃኝቷል፡፡...
ጊዜ በማይሽራቸው የሙዚቃ ሥራወቹ የሚታወቀው ሙሉቀን መለሰ በትናንትናው እለት ጠዋት የረጅም ጊዜ የጤና ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ሙሉቀን በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ጉልህ አሻራቸውን ካሳረፉ ጥቂት ድምፃውያን ውስጥ አንዱ ነበር ።...
የሰውሰራሽ አስተውሎት በአሁኑ ወቅት የሰው ልጆችን የአኗኗር ዘይቬ በእጅጉ እየለወጠ ያለ እና በግለሰብም ይሁን በማህበረሰብ ደረጃ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያለው ቴክኖሎጅ ነው። ተፅዕኖው አወንታዊ ወይም አሉታዊ ሊሆን ይችላል።ከዚህ አኳያ በቴክኖሎጂው አጠቃቀም ላይ የህግ እና የፖሊሲ ማዕቀፎች ያስፈልጉታል የሚለው ግፊት እየተጠናከረ ነው።...
ከ48 ኢንቨስተሮች 1.5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያሰባሰበው የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የድርሻ ድልድል እያካሔደ ነው። በዚህ ሣምንት የሚጠናቀቀው ድልድል ባለድርሻዎች ምን ዓይነት መብት እንደሚኖራቸው ይወስናል። የናይጄሪያ ኤክስቼንጅ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚው የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የቦርድ አባል እንደሚሆኑ አስታውቋል።...
በሱዳን የቀድሞው ፕሬዝድንት ኦማር አልበሺር ታማኝ ጄነራሎች፤ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ አብደል ፋታህ አልቡርሀንና የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት አዛዥ ሞሃመድ ሀምዳን ዳጋሎ መካከል ጦርነት ከተጀመረ አንድ ዓመት ሊሞላው ቀናት ቀሩት።...
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሥልጣን የያዙበት ስድስተኛ ዓመት ደጋፊዎቻቸው በሰልፍ ተቃዋሚዎቻቸው በትችት አስበውታል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ጆን አሕመድ፣ ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ዶክተር ሙከርም ሚፍታህ፣ ከጁሐንስበርግ ዩኒቨርሲቲ ዶክተር ሰይፈ ታደለ የተሳተፉበት ውይይት ለመሆኑ ዐቢይ ምን አሳክተው ምን አጎደሉ? ሲል ያጠይቃል...
ራስ ገዟ ሶማሌ ላንድ እና ከፊል ራስ ገዟ ፑንትላንድ ፤ የሶማሊያ ፌዴራል ሪፐብሊክ ኢትዮጵያ በሁለቱም ግዛቶች የሚገኙ የቆንስላ ጽህፈት ቤቶቿ እንዲዘጉ ያስተላለፈችውን ዉሳኔ አንቀበልም ብለዋል። የኢትዮጵያውን አምባሳደር በ72 ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ተነግሯቸዋል።...
እሁድ መጋቢት 29 ቀን 2016 ዓ/ም በጎርጎርሳውያን የቀን ቀመር ኤፕሪል 7 ቀን ርዋንዳውያን በታሪካቸው የጨለማውን ጊዜ ይዘክራሉ ። አብዛኞቹ አናሳ የቱትሲ ጎሳ አባላት የሆኑ እና ከ1 ሚሊዮን በላይ ርዋንዳዊያን በማንነታቸው ብቻ እየተለዩ የዘር ጭፍጨፋ የተፈጸመባቸው ቀን ነው።...
ዛሬ የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ፊቼ ጫምበላላ በዓል ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በጉዱማሌ መሰብሰቢያ ሥፍራ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል ፡፡ በበዓሉ ላይ በሀዋሳ ከተማ እና ከሲዳማ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የመጡ በሺህዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ታድመዋል ፡፡...
በተደጋጋሚ የጡረታ አበላቸው እንዲከፈላቸው ሲጠይቁ ለነበሩ በትግራይ የሚገኙ ጡረተኞች የፌደራሉ መንግስት 1.6 ቢልዮን ብር መድቦ ክፍያቸውን መስጠት መጀመሩ ተገለፀ። ጡረተኞቹ የ17 ወር የጡረታ አበላቸው እንዲከፈል በተደጋጋሚ ሲጠይቁ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ሲያደርጉ ነበር።...
አዳጊ ሴቶች በሥነ ውበት ላይ ያላቸው ግንዛቤ ፣ ከፅንሰ ሀሳቡ ጀምሮ ሥለውበት አጠባበቅ ያላቸው እይታ እንደየአመለካከታቸው ሊለያይ ይቻላል ፡፡ በሀዋሳ ከተማ የ2ኛ ደረጃ ተማሪ የሆኑት የአብሥራ እና ሽታዬ በተመሳሳይ ዕድሜና የትምህርት ደረጃ ላይ የሚገኙ ቢሆንም ሥለውበት ያላቸው አመለካከት የተለያየ ነው፡፡...
በዞኑ ውስጥ አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች በሰው እና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሳቸውንና ከዚህ ቀደም የወደሙ ንብረታቸውም አለመጠገኑን ገልጸዋል፡፡ጊምቢም የተወሰኑ ሰዎች ወደ ተጠገኑ ቤቶች መግባታቸውን ነገር ግን ለተፈናቀሉ ዜጎች የእርሻ መሳሪያ አለመሰጠቱንና የተወሰኑት ሰዎች ደግሞ በአንድ ቦታ በዘተጋጀው መጠለያ እንደሚገኙም ገልጸዋል፡...
የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ትንቢያ እና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አሳምነው ተሾመ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩትም ባለፉት ሁለት ወራት የጣለው ከፍተኛ ዝናብ ባለፉት 30 ኣመታት ውስጥ በተመሳሳይ ወቅት ታይቶ የማይታወቅም ነው፡፡...
ለዩኒቨርሲቲው በተደጋጋሚ ቅሬታ ማቅረባቸው፥ ከዩኒቨርሲቲው ምላሽ ባለማግኘታቸው ደግሞ ቅሬታቻው ለማሰማት ሰልፍ መውጣታቸው ይገልፃሉ። ተማሪዎቹ ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ እያደረጉ ወደ የከተማው ማህል ክፍል ጉዞ ላይ በነበሩበት ወቅት ጥይት በመተኮስ፣ በድብደባ እና አፈሳ ፖሊስ ሰልፉን በሐይል መበተኑ ገልፀዋል።...
ተከሳሾቹ ከሳምንት በፊት እሥር ቤት ውስጥ ሆነው በፃፉት ደብዳቤ "ማንነትን መሠረት ያደረገ ስድብ፣ ዘለፋ ፣ ማስፈራራት፣ ዛቻ ፣ ድብደባ እና ዝርፊያ" እንደተፈፀመባቸው ገልፀው ነበር። በዛሬው ችሎት ላይም አቶ ክርስትያን ታደለ ደረሰብኝ ያሉትን የመብት ጥሰት ለፍርድ ቤቱ መግለጻቸውን ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ በስልክ ነግረውናል።...
የፕሮጀክት ጽህፈት ቤቱን መረጃ መሰረት በማድረግ ምክትል ዋና ዳይሬክተሯ እንደገለፁት ለግድቡ ግንባታ እስካሁን 193 ቢሊዮን ብር ወጪ ሆኗል፣ የግድቡ አፈፃፀም 95.8 ከመቶ መድረሱን የተናገሩት ወ/ሮ ፍቅርተ አንዳንድ ሚዲያዎች የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ 99.8 ከመቶ ደርሷል ብለው የሚዘግቡት ስህተት ነው ብለዋል፡፡...
የኢትዮጵያ የፀጥታ ኃይላት ጥር ወር በአማራ ክልል መርአዊ ከተማ ከታጣቂዎች ጋር ባደረጉት ውጊያ በርካታ ንጹሓን ዜጎችን ገድለዋል ሲል ሁዩማን ራይትስ ዎች ዛሬ ባወጣው ዘለግ ያለ ዘገባ አመለከተ።...
ግጭትና የጸጥታ ስጋት ባልተለየው የኦሮሚያ የክልል፤ የክልሉ መንግሥት የ30 ዓመታት ጉዞን የሚያሳይ ያለውን የሦስት ቀናት አውደ ርዕይ ከትናንት ጀምሮ እያካሄደ ነው። የክልሉ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አስተናብሮታል በተባለው በዚህ አውደ ርዕይ ላይ የክልሉ መንግሥት ሁሉም መዋቅሮች እንደየ ዘርፋቸው አሳክተናል ያሉትን ሥራዎቻቸውን ይዘው ቀርበዋል።...
የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት ኔቶ የተመሠረተበትን 75ኛ ዓመት አባል ሃገራት በተገኙበት ብራስልስ ቤልጂየም ላይ ዛሬ ተከበረ። አባል ሃገራቱ በተሰባሰቡበት በዋናነት የወቅቱ ስጋት ባሉት የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ተነጋግረዋል።...
የኢትዮጵያ ሰነድ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ 1.51 ቢሊየን ብር ማሰባሰቡን አስታወቀ። ካፒታል ገበያው ያሰባሰበው የገንዘብ መጠን ካቀደው 631 ሚሊዮን ብር በ240 እጥፍ ክፍያ ያለው እንደሆነም ተገልጿል።...
ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትርነት ከኃይለማርያም ደሳለኝ ከተረከቡ ስድስት ዓመታት ተቆጠሩ። ዐቢይ በእነዚህ ዓመታት የተከተሉት የአመራር ሥልት በፍቃዱ ኃይሉ “እየሰጡ መንሳት” የሚለው አባባል ይገልጸዋል የሚል አተያይ አለው።...
ጅቡቲ ላይ ዝናብ በመዝነቡ ኢትዮጵያ ውስጥ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን የሚገልፀው ምክንያት ኢትዮጵያ በጅቡቲ ላይ ምን ያህል ጥገኛ መሆኗን በግልጽ የሚያመለክት ብሎም ሀገሪቱ እንቅስቃሴዋ ምን ያህል በየብስ ማጓጓዣ ላይ የተመሠረተ ኢኮኖሚ ያላት መሆኑን ያመለክታል።...
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፈው መጋቢት መጀመሪያ አጋጥሞት የነበረውን ችግር በተመለከተ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ከባንኩ ጋር አደረኩት ባለው ማጣራት፤ የሞባይል ባንኪንግ የሲስተም ማሻሻያ በሚደረግበት ወቅት የፍሰት ስህተት በመፈጠሩ ነው ሲል በቅርቡ አስታውቋል። ለመሆኑ ተፈጠረ የተባለው የፍሰት ስህተት ምን ማለት ነው?...
የድርድሩ መክሸፍ ኢትዮጵያ የገጠማትን የኤኮኖሚ ችግር ለማቃለል ይረዳል የተባለዉን ብድር ከማዘግየቱ በተጨማሪ «የፓሪስ ክለብ» የተባለዉ የአበዳሪ መንግሥታት ስብስብ የሰጣትን ዕዳ የመክፈያ እፎይታ ሊያቋርጠዉ ይችላል የሚል ሥጋት አሳድሯል።...
ከጦርነቱ መቆም 17 ወራት በኃላ የቀድሞ ተዋጊዎቹ ትግራይን የሚመራው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ እና የሀገሪቱ ገዢ ፓርቲ ብልፅግና ፓርቲ ትላንት በመቐለ ቀጣይ ፖለቲካዊ ውይይት በሚያደርጉበት ጉዳይ ዙርያ በከፍተኛ አመራሮቻቸው በኩል ንግግር አድርገዋል።...
አቶ አበበ እና መምህር ሰለሞን አሁን ላይ እየተባባሰ ይገኛል ያሉትን ጥቃት ለማስቆም ለአካባቢው አስተዳደር ፣ ለፌዴራሉ መንግሥትና ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን / ኢሰመኮ/ አቤቱታቸውን ማቅረባቸውን ተናግረዋል።...
«የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ» የተሰኘው ሕግ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ ወጥነት እና ተገማችነት ያለው፣ የአከራይ እና ተከራይን መብት ሚዛናዊ በሆነ መልኩ ለማስተዳደርና ዘርፉን በሕግ ለመምራት ታስቦ መዘጋጀቱም ተነግሯል።...
የመጀመሪያውን የሙዓለ-ንዋይ አማካሪነት ፈቃድ የተረከበው ዴሎይት በኢትዮጵያ ገበያ ተስፋ ሰንቋል። ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ 900 ሚሊዮን ብር ዋጋ ካላቸው አክሲዮኖች ከአስር በላይ የግል ባንኮች እና የመድን ድርጅቶች ድርሻ ገዝተዋል። በምሥረታ ላይ የሚገኘው ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ በቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ሕንጻ ላይ ገበያ ያቆማል።...
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ. ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ። መንግሥት አዋጁ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት ፣ ወጥነት እና ተገማችነት ያለው እንዲሁም የአከራይ እና ተከራይን መብት ሚዛናዊዊ በሆነ መልኩ ለማስተዳደርና ዘርፉን በሕግ ለመምራት በሚል ማርቀቁን አስታውቋል።...