Home › View all posts by Addis Admas
Blog Archives
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ሃላፊዎች በሙስናና በሃብት ምዝበራ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ።በቁጥጥር ስር ከዋሉት ሃላፊዎች መካከል የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ እና ምክትል ፕሬዚዳንቱ ዶ/ር ታምራት ታገሰ ይገኙበታል።የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ለአንድ የዩኒቨርስቲው የፋይናንስ ቡድን መሪ የ790 ቀናት አበል እንዲሁም ለሌላኛው የፋይናንስ የቡድን መሪ ደግሞ በስድስት ወራት ውስጥ ብቻ የ1...
የህወሓት ሊቀ መንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል፤ “የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ለመጓተቱ የፌደራል መንግስትን ተጠያቂ አድርገዋል። ባለፈው ሰኞ ሃምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም ከራዲዮ ፍራንስ ኢንተርናሽናል (RFI) ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ዶ/ር ደብረፅዮን፤ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከተፈረመ ሁለት ዓመት ቢቆጠርም፣ አፈጻጸሙ ግን አዝጋሚ መሆኑን ገልጸዋል። ስምምነቱ በተፈረመ የመ...
“ነዋሪው ቅሬታውን የሚሰማው አካል የለም”- የከተማ አስተዳደሩ ነገ በጉዳዩ ዙሪያ ነዋሪውን ያወያያልበአማራ ክልል፣ አዊ ዞን፣ አንከሻ ጓጉሳ ወረዳ፣ ግምጃ ቤት ከተማ በቡድን የተደራጀ የዘረፋ ድርጊት መስፋፋቱን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ይኸው የዘረፋ ድርጊት የሚፈጸመው የጦር መሳሪያ በመጠቀም መሆኑንም አክለው ተናግረዋል።ለደህንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የግምጃ ቤት ከተማ ነዋሪ ለአ...
የትጥቅ ትግል ተፋላሚዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ በምክክሩ ላይ እንዲሳተፉ የሚያስችል አቅም እንዳለው የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ባለፈው ረቡዕ ሐምሌ 10 ቀን 2016 ዓ.ም በጽሕፈት ቤታቸው ከሌሎች ኮሚሽነሮች ጋር በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ለተፋላሚዎቹ አስቻይ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ መንግስትንና ሌሎች አካላትን ኮሚሽኑ እየጠየቀ መሆኑን ተ...
በሱዳን አሁንም በቀጠለው የእርስ በርስ ጦርነት ሳቢያ የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ደህንነት አደጋ ላይ እንደወደቀ ሂዩማን ራይትስዎች አስታውቋል። ስደተኞቹ በሱዳን ጦር ሃይሎችና በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይሎች እንግልት እየተፈጸመባቸው መሆኑን ተቋሙ አመልክቷል።የተቋሙ የምስራቅ አፍሪካ ዋና ዳይሬክተር ላቲሺያ ባድር እንደጠቆሙት፤ በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ ጊዜ አንስቶ፣ በዋናነት ገዳሪፍ የሚ...
በአዲስ አበባ ከተማ የ2016 ዓ.ም. የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር መካሄዱ ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት አዳነች አቤቤ፣ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ የአዲስ አበባ ከተማ የብልጽግና ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አምባሳደሮች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች፣ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው...
- ነቢይ ተደራራቢ የጤና እክሎች ነበሩበት- “ነቢይ መኮንን ከሳቅ የተሰራ ሰው ነው“ከሁሉም በላይ ገጣሚ ነኝ” የሚለው ሁለገብ ከያኒ ነቢይ መኮንን፤ የጥበብ መክሊታቸውን አሟጠው ሳይጠቀሙ ህይወታቸውን በሞት ለሚነጠቁ የጥበብ ሰዎች “የዕድሜ ዕቁብ በኖረ” ሲል በግጥም ምኞቱን አስፍሯል።….”ምነው ለጥበብ ሰው ለበሳል ኪነት ሰው እቁብ በኖረ፣ ወይ የእድሜ ቀይ መስቀል የክፉ ቀን ደራሽ፣ አንድ ቀን የሚ...
ከግጭት ለመውጣት ሰላማዊ ውይይትየኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ከሃላፊነታቸው መነሳታቸው ተገልጿል። ኮሚሽነሩ ከሃላፊነታቸው የተነሱት በትናንትናው ዕለት ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ነበር።በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ታገሰ ጫፎ ፅሕፈት ቤት ተገኝተው ይፋዊ ስንብት የተደረገላቸው ዶ/ር ዳንኤል፣ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ሆነው የተሾሙት ሰኔ 25 ቀን 20...
በኢትዮጵያ በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞችና ገጠራማ አካባቢዎች ተጠልለው የሚገኙ 4 ነጥብ 5 ሚሊየን የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መኖራቸው ተገልጿል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) ባወጣው ሪፖርት መሰረት፣ አብዛኛዎቹ ተፈናቃዮች የሚገኙት በሶስት ክልሎች ውስጥ “ነው” ተብሏል። እነዚህም ክልሎች ሶማሊያ፣ ኦሮምያና ትግራይ እንደሆነ ተነግሯል። አብዛኛዎቹ ቀያ...
ገጣሚ፣ ደራሲና ተርጓሚ ነቢይ መኮንን፣ ከአባቱ ከአቶ መኮንን ወንድም እና ከእናቱ ከወይዘሮ በለጤ በድሉ፣ በነሐሴ ወር 1946 ዓ.ም፣ በቀድሞዋ ናዝሬት፣ በአሁኑ አዳማ ከተማ ተወለደ፡፡ ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከመግባቱ አስቀድሞ፣ መምህር ተከስተ ጋር የቄስ ትምህርቱን የተከታተለ ሲሆን፤ እዚያም ሳለ ዳዊትን በቃሉ በመሸምደድ የማስታወስ ችሎታውን አዳበረ፡፡ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት...
አንዳንድ ጊዜና ሁኔታዎች አሉ፤ መሀሉን ትታችሁ ውጤቱን ብቻ የምትናገሩበት። ብቻ ግን ከቻላችሁ ደግ ተግባር ስሩ ፤ ከቻላችሁ። እኔ ሁሌም መልካምነት የልብ መሻቴ ነው። በተግባር ግን እንደ ልቤ አይደለሁም። ክፉም ባልሆን ደግ ግን አይደለሁም። መልካምነት የእውቀት ሳይሆን የመሰጠት ጉዳይ ነው። አሁን ይኸው ሁለቱም (አሰፋም ፣ ነቢይም) በሕይወት የሉም። አሰፋ ጎሳዬ ( የ"አዲስ አድማስ" ጋዜጣ ባለ...
ሰው ካልሞተ አይመሰገንም የሚሉት ብሂል ትክክል መሆኑን ዛሬ በተጨባጭ አረጋገጥኩኝ፡፡ ለምን እስከዛሬ ስለ ቅርብ ወዳጄ ነቢይ መኮንን የማውቀውን በጎነትና መልካምነት አልመሰከርኩም ብዬ ራሴን ስጠይቅ፣ በተደጋጋሚ ያገኘሁት ምላሽ፣ ”ንፉግነት” የሚል ሆኖ አገኘሁት፡፡ በዚህም ራሴን ክፉኛ ወቀስኩት፡፡ በጸጸት ተቃጠልኩ፡፡ በራሴም አፍሬ የምገባበት ጠፋኝ፡፡ የሰው ልጅ ኖሮ ኖሮ ማለፉ እንደማይቀር እያ...
ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ የሆነውና በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት የሚጠቀሰው ገጣሚ፣ ተርጓሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን፣ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ስንገልጽ፣ በጥልቅ ሃዘን ውስጥ ሆነን ነው፡፡ ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ፣ ድንገት ያረፈው ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ነው፡፡የአዲስ አድማስ ዝግጅት ክፍል...
• ተቃዋሚዎች “ፕሬዚዳንቱ ከሥልጣን ይልቀቁ“ እያሉ ነው የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የኑሮ ውድነትን እንዲያሻቅብ ያደርገዋል የተባለውንና ላለፉት ሁለት ሳምንታት ለተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ ሰበብ የሆነውን የፋይናንስ ረቂቅ በፊርማዬ አላጸድቅም ብለው ወደ ፓርላማ ቢመልሱትም፣ ተቃውሞው አሁንም አልበረደም፡፡ በዛሬው ዕለት በናይሮቢና በሌሎች ከተሞች ለተቃውሞ የወጡ ኬንያውያን ፕሬዚዳንቱ ...
ጊዜያዊ አስተዳደሩ እርምጃ ባለውሰድ ተወቅሷል በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ አራት ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ በትግራይ ሴቶች ላይ የሚደርሱ የፆታ ጥቃቶች በአስቸኳይ እንዲገቱና የመፍትሔ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠይቀዋል። ፓርቲዎቹ ባለፈው ሰኞ ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ.ም. መቐለ ከተማ በሚገኘው የሳልሳይ ወያነ ፓርቲ ጽሕፈት ቤት በሰጡት የጋራ መግለጫ፤ በክልሉ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች መነሻ...
“ጎረቤትህ ሲታማ ለእኔ ብለህ ስማ” ከሰሞኑ በኬንያ የተቀጣጠለው ሕዝባዊ ተቃውሞ አልበረደም። ይህ ተቃውሞ ረቂቅ ዓዋጅን ከማሰረዝ አንስቶ የተጓዘባቸው ሂደቶች አነጋጋሪ ሆነዋል። ለተቃውሞው መቀስቀስ እንደ አጣዳፊ ምክንያት የሚጠቀሰው፣ ለኬንያ ምክር ቤት የቀረበው የፋይናንስ ረቂቅ ዓዋጅ ሲሆን፤ በሂደት ግን ወደ ሌላ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። ተቃዋሚዎች ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ስልጣ...
ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ፣ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ግጭት በማገርሸቱ ሳቢያ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የሕክምና አገልግሎት እያገኙ አለመሆኑን አስታውቋል። በኢትዮጵያ የኮሚቴው ቡድን መሪ ኒኮላስ ቮን አርክስ እንደተናገሩት፣ ኮሚቴው በግጭቱ ቀጥተኛ ተሳታፊ ከሆኑ ሃይሎች ጋር በመገናኘት ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ሕጎችን እንዲያከብሩ በተደጋጋሚ እየወተወተ ይገኛል።ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር...
የደቡብ ጎንደር ዞን፣ ታች ጋይንት ወረዳ፣ የእናት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ዲበኩሉ፣ በጸጥታ ሃይሎች መታሰራቸውን ፓርቲው አስታውቋል። ”የአባላቱ እስራት የፖለቲካ ስብራታችን አንድ ማሳያ ነው” ብሏል፤ እናት።ፓርቲው ሰሞኑን በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ባሰራጨው መረጃ፤ አቶ ሰለሞን ዲበኩሉ በጸጥታ ሃይሎች ተይዘው የታሰሩት ግንቦት 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ነበር። በአሁኑ ወቅት ሰብሳቢው በላይ ጋይንት ...
ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ፣ በርበራ ወደብ በኩል ነዳጅ ለማስገባት መስማማቷን የበርበራ ከተማ ከንቲባ አብዲሽኩር መሃሙድ ሃሰን ተናግረዋል። ከንቲባው ይህንን የተናገሩት የሶማሌላንድ የነጻነት በዓል በአዲስ አበባ የሶማሌላንድ ኤምባሲ በተከበረበት ወቅት ነው።አብዲሽኩር፤ ኢትዮጵያ የነዳጅ ምርት የምታስመጣበትን ወደብ ወደ በርበራ እንደምትቀይር ያብራሩ ሲሆን፣ የገቢ ምርቶቿንም ለማስገባት ወደቡ ዝግጁ መሆኑን...
በምስራቅ ሐረርጌ ዞን “ጫት አምራች” የተባሉ አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ በመወሰኑ ሳቢያ፣ ጫት አምራች ገበሬዎችና ነጋዴዎች ለስደት መዳረጋቸው ተሰምቷል፡፡ በጫት ምርት ላይ የተጣለው ከፍተኛ ቀረጥ በጫት ንግድ ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳድሩ ዜጎች የዕለት ጉርሳቸውን እንኳን ለማግኘት ተፈታትኗቸዋል ነው የተባለው፡፡
ከሁለት ዓመታት ወዲህ ተወስኗል የተባለው ከፍተኛ የጫት ቀረጥ ባስከተለው ...
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ስልጤ ዞን፣ ስልጢ ወረዳ የበልግ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ ከ130 በላይ አባወራዎች ከመኖሪያ ቤታቸው መፈናቀላቸው ተነግሯል። ለበልግና ለመኸር የተዘጋጀ የእርሻ መሬት በጎርፍ እንደተያዘም ተገልጿል።የዞኑ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ወሲላ አሰፋ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፣ ከመደበኛው መጠን በላይ እየጣለ በሚገኘው የበልግ ዝናብ ሳቢያ ጎፍለላ ቀ...
በአገራዊ ምክክሩ የሚሳተፈው የሙስሊሙ ቁጥር አናሳ መሆኑን የገለፀው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሳታፊዎች ልየታ በድጋሚ እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል። በሙስሊሙ በኩል የቀረቡ አጀንዳዎች በምክክሩ ውስጥ እንዲካተቱም ጠይቋል።“የሙስሊሞች ተሳትፎ በሕዝባችን ቁጥር ልክ መሆን አለበት” ያለው ም/ቤቱ”፤ የተሳታፊዎችና የአወያዮች ቁጥር በኮሚሽኑ የአካታችነት መርህ አማካይነት ...
በትግራይ ክልል፣ ምስራቃዊ ዞን፣ ሃውዜን ከተማ የሚገኝ በርካታ ዓመታትን ያስቆጠረ ቅርስ መዘረፉ ተሰምቷል። ቅርሱ በከተማዋ በሚገኘው እንዳ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ይገኝ እንደነበረ ተገልጿል።ይኸው ቅርስ ከወርቅና በከፊል ከብር የተሰራ መስቀል መሆኑን አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የቤተ ክርስቲያኑ አገልጋይ ለአዲስ አድማስ ጠቁመዋል።ከ125 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው ይህ መስቀል፣ በ...
በ1966 ዓ.ም ዘመኑ በተማሪዎችና ምሁራን የተቀጣጠለው የኢትዮጵያ አብዮት 50ኛ ዓመት አስመልክቶ በግልም በቡድንም በተለያዩ ኹነቶች እየተዘከረ ይገኛል፡፡ ሰሞኑን የኢትዮጵያ አብዮት 50ኛ ዓመትን የሚዘክር ሴሚናር በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ራስ መኮንን አዳራሽ ተካሂዷል። ከትናንት በስቲያ በተካሄደው ሴሚናር ላይ አምስት የአብዮቱ ዘመን ምሁራን የተሳተፉ ሲሆን፣ ከአብዮቱ ጋር የተገናኙ በር...
ባለፉት 50 ዓመታት ከ8ሚ. በላይ ዜጎችን መድረስ ችሏል በአሁኑ ወቅት 700ሺ ዜጎች የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ናቸው ትልቅ የሀገር ሃብት ነውና መከበርና መጠበቅ አለበት ተብሏልላለፉት አምስት አሰርት ዓመታት የቤተሰባቸውን እንክብካቤ ያጡና የቤተሰባቸውን እንክብካቤ ለማጣት በአደጋ ላይ ያሉ ህፃናትን የቤተሰብ እንክብካቤና ጥበቃ አግኝተው እንዲያድጉ ለሁለንተናዊ ዕድገታቸው የሚያስፈልጋቸውን ...
ባለፉት 50 ዓመታት ከ8ሚ. በላይ ዜጎችን መድረስ ችሏል በአሁኑ ወቅት 700ሺ ዜጎች የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ናቸው ትልቅ የሀገር ሃብት ነውና መከበርና መጠበቅ አለበት ተብሏልላለፉት አምስት አሰርት ዓመታት የቤተሰባቸውን እንክብካቤ ያጡና የቤተሰባቸውን እንክብካቤ ለማጣት በአደጋ ላይ ያሉ ህፃናትን የቤተሰብ እንክብካቤና ጥበቃ አግኝተው እንዲያድጉ ለሁለንተናዊ ዕድገታቸው የሚያስፈልጋቸውን ...
ነዋሪነታቸውን በአሜሪካ ያደረጉት አቶ ጥበበ እሸቱ ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የቁሳቁስ ድጋፍና ለ7ሺ500 አረጋውያን ሙሉ ወጪውን በመሸፈን የምሣ ማብላት መርሃ ግብር አከናውነዋል፡፡ አቶ ጥበበ ትላንት ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም በመቄዶንያ ማዕከል በመገኘት አረጋውያኑን ምሣ ያበሉ ሲሆን፤ በርካታ ብርድልብሶችንና ጫማዎችንም ...
የፍየል ዋጋ አይቀመስም - የበግ ቅናሽ አሳይቷልየትንሳኤ በዓል የገበያ ዋጋ ከገና በዓል የገበያ ዋጋ አንፃር መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱን ነጋዴዎችና ሸማቾች ተናገሩ፡፡ የአዲስ አድማስ ሪፖርተሮች በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ትልልቅ የገበያ ቦታዎችን ከቃኙ በኋላ ባገኙት መረጃ ነው የበዓል ግባቶች የዋጋ ሁኔታ መጠነኛ መረጋጋት ማሳየቱን ማረጋገጥ የቻሉት። ነጋዴዎችና ሸማቾች እንደገለፁት፤ ...
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች መካከል፣ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ዙሪያ፣ “ሰላም ፈላጊ እና ጦርነት ፈላጊ አለ” በሚል እየተፈጠረ ያለው የልዩነት ትርክት ስህተት ነው፤ ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ጄነራል ታደሰ ወረደ ተናገሩ፡፡ ጄነራሉ ባለፈው ረቡዕ ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ለትግራይ ክልል መገናኛ ብዙኃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የፕሪቶ...
በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ላይ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።ለዚህ የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን ይዘው ወደ አሜሪካ የተጓዙት የኢትዮ ሮቦ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል መሥራችና ዋና ሃላፊ አቶ ሰናይክሪም መኮንን ናቸው። በአሜሪካው ውድድር ላይ ለመሳተፍ የተመረጡት ተማሪዎች በቅርቡ እዚህ አዲ...
የፖለቲካ ሹመኞች በሙያተኞች ላይ በሚያሳድሩት ጫና የመንግሥት ሥራ እየተደናቀፈ ነው ሲሉ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎቹ ለአዲስ አድማስ ተናገሩ። በብዙዎቹ የመንግስት መ/ቤቶች ሃላፊዎች ሥልጣን ላይ የሚቀመጡት በፖለቲካ ታማኝነት እንጂ በዕውቀትና በብቃት ባለመሆኑ በሙያተኞች ላይ የሚያሳድሩት ጫና ሥራውንም ባለሙያውንም እየጎዳው መሆኑንም ያስረዳሉ። እየጎዳው ነው ተብሏል፡፡በአ...
ብልፅግና “የሚዲያ ሠራዊት” አደረጃጀት የለም ሲል አስተባበለበገዢው ብልፅግና ፓርቲ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስር የሚንቀሳቀሱና ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የፓርቲው አባላት፤ መንግሥትን በሚተቹና በሚቃወሙ ግለሰቦች ላይ ሐሰተኛ መረጃ የማሰራጨት ዘመቻ ሥርጫትላይ መሳተፋቸውን ቢቢሲ ባደረገው ምርመራ ማረጋገጡን አመለከተ።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወ...
(ከእስራኤል ምክትል አምባሳደር ጋር የተደረገ ልዩ ቃለ መጠይቅ)ኢራን ባለፈው ቅዳሜ ሚያዝያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት ከ300 በላይ የድሮኖችና የሚሳኤሎች ጥቃት በእስራኤል ላይ ያደረሰች ሲሆን፤ እስራኤል አሜሪካና እንግሊዝን ጨምሮ ከአጋሮቿ ጋር በመተባበር ከተወነጨፉት ድሮኖችና ሚሳኤሎች ውስጥ 99 በመቶውን ከአየር ክልሏ ውጭ ማምከን መቻሏን አስታውቃለች፡፡ ኢራን የፈጸመችው ጥቃት የዛሬ 20...
የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት፣ በፑንትላንድ ዋና ከተማ ጋሮዌ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ እንዲዘጋ ያስተላለፈውን ትዕዛዝ እንደማትቀበል ፑንትላንድ አስታወቀች።የሶማሊያ መንግሥት የኢትዮጵያ መንግሥት በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ እየገባ ነው በሚል በሞቃዲሾ የኢትዮጵያ አምባሳደር አገሪቱን ለቀው እንዲወጡና በከፊል ራስ ገዟ ፑንትላንድና ነጻነቷን ባወጀችው ሶማሊላንድ ያሉት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች እንዲ...
ጠ/ሚኒስትሩ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሰብሰብ ብለው እንዲታገሉ ጥሪ አቀረቡ”60 ፓርቲዎች ሆናችሁ ልንደግፋችሁ ይቸግረናል“ለሁለት ወር ግድም ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ያደረጉት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ ባለፈው ሰኞ መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም በመቶዎች ከሚቆጠሩ የተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የፓርቲ አመራሮቹ በውይይቱ ላይ ለጠ/...
ጥበበ ተርፋ ማመጫ፤ በሐረር ከተማ በ1941 ዓ.ም ተወለዱ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሐረር መድኃኒዓለም ት/ቤት እንዳጠናቀቁ ወደ አዲስ አበባ ሥነ ጥበብ ት/ቤት (በአሁኑ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አለ የሥነ ጥበብና ዲዛይን ት/ቤት) በመግባት ተመርቀዋል።በኢትዮጵያ ዘመናዊ የሥነጥበብ ልምምድ ውስጥ ተዋጽዖአቸው ከፍ ያለ ሥፍራ የሚሰጠው ነበረ:: የሥዕል ሥራቸውን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ለ...
አማራ ባንክ ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ አክሲዮን ለመግዛት የሚያስችለውን ስምምነት የፈጸመ ሲሆን፤ የ10% አክሲዮን ድርሻ ገዝቷል፡፡ የአማራ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ተወያይቶ ባፀደቀው መሠረት፣ ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ በመመደብ የአክሲዮን ድርሻ የገዛው ባንኩ፤ ሲሆን፤ ይህም በገንዘብ ሲተመን 90.6 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ተገልጿል።አማራ ባንክ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገትና ለህዝብ ኑሮ መሻ...
• ”የቢጂአይ ኢትዮጵያ አመራር፣ ያሰርነውን ውልና የፍ/ቤት ትዕዛዝ ጥሷል” • ”የበለጸጉና የተደራጁ ኤጀንቶችን በአዳዲስ መተካት የሚል አዲስ ስትራቴጂ መጥቷል“ከተመሰረተ 14 ዓመት ገደማ ማስቆጠሩ የተነገረለት ቢጂአይ ኢትዮጵያ ኃ. የተ. የግል ወኪል አከፋፋይ አሰሪ ማህበር፤ በቢጂአይ ኢትዮጵያ አመራሮች ደረሱብኝ ያላቸውን በደሎች ለጋዜጠኞች በተሰጠው መግለጫ ላይ አብራርቷል፡፡ ማህበሩ በ...
- ባለፈው ዓመት 7 ሺህ የሚጠጉ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ተደርገዋልኢትዮጵያ ለሳይበር ጥቃት ተጋላጭነታቸው ከፍ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነችና የሳይበር ጥቃቶቹ የፋይናንስና የፀጥታ ተቋማትን፣ ባንኮችን፣ እንደ ቴሌኮምና መብራት ሃይል ያሉ ተቋማትን፣ መሰረተ ልማቶችንና ቁልፍ የመንግስት ተቋማትን ኢላማ ያደረጉ እንደሆኑ ታዋቂው የሳይበር ደህንነት ተቋም ሲዮን ገልጿል። ተቋሙ ከ...
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባጋጠመው የሲስተም ችግር ወቅት ገንዘብ የወሰዱ ወይም ያስተላለፉ ግለሰቦች እስከ መጪው ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ካልመለሱ ፎቷቸውንና ማንነታቸውን በመገናኛ ብዙኃን ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ።ባንኩ ገንዘቡን ተመላሽ በማያደርጉ ሰዎች ላይ በሕጋዊ ሂደቱ ተገቢ ውሳኔ እስኪገኝ ድረስ ፎቶግራፋቸውንና ዝርዝር ማንነታቸውን የሚገልጹ መረጃዎች “ባንኩ በመረጠው የ...
ኢትዮ - ሮቦ ሮቦቲክስ፤ በነገው ዕለት ሐሙስ፣ የ2024 የአፍሪካ ሮቦቲክስ ቻምፒዮንሺፕ ውድድሩን በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል የሚጀምር ሲሆን፤ ቅዳሜ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡ መርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄድ ዓመታዊ የሮቦቲክስ ወድድር መሆኑን የኢትዮ-ሮቦ ሮቦቲክስ መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰናይ መኮንን ገልጸዋል፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠ...
መልዕክተኛው የፕሪቶሪያው ስምምነት አፈጻፀምን ይገመግማሉ ተብሏልየአሜሪካ መንግሥት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የተከሰቱ ግጭቶች በድርድር እንዲፈቱ ለማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮችና በመንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰው ስምምነት አፈጻጸም ግምገማ ዙሪያ በአዲስ አበባ እየመከሩ ነው ። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መግለጫ ላይ እንደ...
በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ ለሕዝብ ቀርቦ ዜጎች ውይይት እንዲያደርጉበትና እንዲተች የሚጠይቅ ምክረሃሳብ ለፍትህ ሚኒስቴር ቀረበ ። ”ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ“ የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት፣ ከሌሎች በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሚሠሩ አገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር፣ ለረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ግብዓት የሚኾኑ ሀሳ...
በቢጂአይ ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ ኢትዮጵያ ዋና መሥሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር፣ ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡ ተገልጧል፡፡ቢጂአይ ኢትዮጵያ ትላንት ባሰራጨው መግለጫ፣ የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎትና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ነው፤ ብሏል።ፐርፐዝ ...
የፒያሳ ነዋሪዎች በ3 ወራት ጊዜ ውስጥ አካባቢውን እንዲለቁ ተነግሯቸዋልበአዲስ አበባ አስተዳደር አራዳ ክፍለ ከተማ፣ የፒያሳና አራት ኪሎ ነዋሪዎች ለልማት ከመኖሪያቸው እንደሚነሱ የክፍለ ከተማው አስተዳደር ገልጿል።አስተዳደሩ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ እንዳስታወቀው፤ ሁለቱን አካባቢዎች መልሶ በማልማትና ነዋሪዎችን በማስነሳት ዙሪያ ሰሞኑን ከነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርጓል። ውይይቱ፣ በንግድ ...
የፌደራል መንግስትና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ አደራዳሪዎች በተገኙበት በቀጣይ ሳምንታት በፕሪቶርያው ስምምነት ዙሪያ ዳግም ለውይይት ሊቀመጡ ነው ተባለ። የካቲት 18 እና 19 ቀን 2016 ዓ.ም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መሰብሰቡንና የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ረዳኢ ሀለፎም ከትግራይ ቴሊቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገልጸዋ...
የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ ”የሥራ መልቀቂያ አስገቡ“ በሚል የተሰራጨው መረጃ ሃሰተኛ መሆኑን የባንኩ ባለድርሻ አካላት ገለጹ፡፡የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን የሚገልጹ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች መሰራጨታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ሆኖም መረጃው ሙሉ በሙሉ ሃሰተኛ ነው ብለዋል - ለባንኩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች፡፡የባ...
ባለ አራት ኮከቡ ዘጠነኛው ኃይሌ ሆቴል ወላይታ በዛሬው ዕለት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አብስሯል፡፡ ሆቴሉ ትልቁን ዳሞታ ተራራን ተንተርሶ በኮረብታማዋ ወላይታ ሶዶ ከተማ እምብርት ላይ የተገነባ ነው። ሆቴሉ ተሰርቶ ለመጠናቀቅ አራት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን፤ እስካሁን 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ወጥቶበታል ብሏል፤ በሆቴሉ ዳሞታ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ። ሆቴሉ...
ም/ቤቱ ሁለቱ አገራት አለመግባባታቸውን በንግግር እንዲፈቱ መክሯልየሶማሊያ ባለሥልጣናት ጦርነት ቀስቃሽ ዛቻዎችን መሰንዘር ቀጥለዋልየአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ባለፈው ረቡዕ ጥር 8 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን ውጥረት አስመልክቶ ውይይት ያደረገ ሲሆን፤ የውጭ ሃይሎች በሁለቱ አገራት መካከል ጣልቃ ከመግባት እንዲቆጠቡ አሳስቧል። ምክር ቤቱ የቀድሞው...
የአንጋፋው ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈፀመጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ባደረበት ህመም በአሜሪካ ሕክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ባለፈው ሳምንት ሕይወቱ ማለፉ ይታወቃል፡፡በሚሊኒየም አዳራሽም የስንብት መርሐግብር ከተካሄደ በኋላ በመንበረ ጸባኦት ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ቤተሰቦቹ፣ የሙያ አድናቂዎቹ፣ የስራ ባልደረቦቹ በተገኙበት የፍትሃት እና የቀብር ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዝግ...
የኢትዮጵያና የሶማሊላንድ መሪዎች፣ ኢትዮጵያን ለ50 ዓመታት የባህር ጠረፍ ተጠቃሚ የሚያደርግ የመግባቢያ ሰነድ መፈረማቸውን ተከትሎ፣ በቀጠናው አዲስ የጂኦ ፖለቲካ ውዝግብ መፈጠሩ እየተነገረ ነው። እስካሁን ድረስ በሱማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል በህግ የሚፀና ስምምነት ባይካሄድም እንኳንም በቀጠናው ውዝግብ ማስከተሉ አልቀረም ። በሁለቱም መንግሥስታት መካከል የተፈረመው ለመግባቢያ ሰነድ የሚሆን...
• ኢትዮጵያውያን፣ ለልደት በዓልን ወደ እስራኤል ተጉዘዋል በብጹዕ አቡነ አብርሃም የተመራው የልዑካን ቡድን፣ በእስራኤል ኢየሩሳሌምን ጨምሮ በርካታ ታሪካዊና ቅዱሳን ሥፍራዎችን ለ5 ቀናት ጎብኝቶ፣ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰ ሲሆን፤ ሁሉም የጉብኝት ሥፍራዎች ሰላማዊና ምንም ዓይነት ሥጋት እንደሌለባቸው ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡በእስራኤል የሚገኙ ቅዱሳንና ...
• ከእስራኤል የተመለሰው የልኡክ ቡድን፤ የጉብኝት ሥፍራዎች ሰላማዊና አስተማማኝ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል• ሁለተኛው የልኡክ ቡድን፣ ለልደት በዓል ወደ እስራኤል ይጓዛል በብጹዕ አቡነ አብርሃም የተመራው የልዑካን ቡድን፣ በእስራኤል ኢየሩሳሌምን ጨምሮ በርካታ ታሪካዊና ቅዱሳን ሥፍራዎችን ለ5 ቀናት ጎብኝቶ፣ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰ ሲሆን፤ ሁሉም የጉብኝት ሥፍራዎች ሰላማዊና ምንም...
(የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጋዜጣዊ መግለጫ) የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣በጉራጌ ዞንና በቀቤና ልዩ ወረዳ መካከል የነበረውን አለመግባባት ተከትሎ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስና ያስከተለውን ጉዳት ከአካባቢው ነዋሪዎች በቀረበለት አቤቱታ መነሻነት ከጥቅምት 20 እስከ 25 ቀን 2016 ዓ.ም....
2ኛው ሀገር አቀፍ የህገወጥ ንግድ መከላከል ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩ ላይ ህገወጥ የቁም እንስሳ ንግድ ከፍተኛ ኪሳራ ማስከተሉ ተጠቁሟል፡፡በጉባኤው ላይ በቁም እንስሳት፤ በመድኃኒትና ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ በሚታይ ህገወጥ ንግድ ላይ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጓል፡፡ በንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ስርዓትና ፈቃድ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፍሰሀ ይ...
‘Fly Now Pay Later’ ዳሽን ባንክና የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ደንበኞች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን ‘ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል’ የሚል አዲስ የክፍያ አማራጭ በዛሬው ዕለት አስተዋወቁ። የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን አቶ ዮሐንስ መኮንን እንደገለጹት፤ ‘ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል’ የተሰኘው አዲሱ የክፍያ አማራጭ ...
ግጭቶቹ በዚሁ ከቀጠሉ አገሪቱ ከባድ አደጋ ላይ ትወድቃለች ተብሏል በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት 5300 ግጭቶች መከሰታቸውንና በዚህም በሺዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን መሞታቸውን ብሔራዊ የግጭት ክስተት ልየታ ጥናት ይፋ አደረገ። ጥናቱ ከ2010 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ዓመታት በአገሪቱ እጅግ ከባድ ግጭት የተከሰተባቸው ዓመታ...
የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እንደሚችል አስጠንቅቋል መንግስት በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ አለም አቀፍ ተቋማትና በዲፕሎማሲያዊ ማህበረሰብ አባላት ላይ እየወሰደ ያለው ተገቢ ያልሆነና አለማቀፋዊ ህጎችን የጣሰ ድርጊት ከፍተኛ ዋጋ ሊያስከፍልው እንደሚችል የፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዳዮች ምህሩ ዶክተር አንተነህ ተስፋዬ ገለፁ። የአፍሪካ ልማት...
በሃዋሳ ከተማ በምሥራቅ ክፍለ ከተማ በ280 ሚሊዮን ብር ወጪ በ700 ካ.ሜ ቦታ ላይ የተገነባው ባለ 3 ኮከቡ ፌኔት ሆቴል፣ በዛሬው ዕለት የክልሉ የሥራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመረቀ፡፡የዕለቱ የክብር እንግዳ የሲዳማ ክልል ፕሬዚዳንት አማካሪ አቶ ተሰማ ዲማ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "ሃዋሳ የቱሪዝም ከተማ እንደመሆኗ ሆቴሉ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል...
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ የሥራ ሀላፊዎች ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በዛሬው ዕለት በመሐል ሐዋሳ ፒያሳ ላይ አስገንብቶ ያስመረቀውን ሁለገብ ሕንጻ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ከጉብኙቱ በኋላ ባደረጉት ንግግር፤ ''ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በሲዳማ ክልልም ሆነ በሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ማስፋፋት...
በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው ነው የተባለለት የአንጎል የደም ስር ክሊፒንግ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።ይህ ህክምና የተደረገላት ታካሚ ከአዲስ አበባ በጥቂት ርቀት ላይ የምትኖር ሲሆን፤ ድንገት በዕለት ሥራዋ ላይ ሳለች ከፍተኛ የራስ ህመም ይሰማት እንደጀመረና ከዚያም እራስዋን ስታ መውደቋን ታሪኳ ያስረዳል።ህክምና ተቋም እንደደረሰችም በተደረገላት ምርመራ በአንጎልዋ ውስጥ ...
በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ኢንጅነር) ስለኢንስቲትዩቱ ሥራዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡ በውይይቱ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን ለማልማት በኢንስቲትዩቱ የሚሰሩ የምርምር ተግባራት ለሀገር የሚበጁ መሆናቸውን እንደተገነዘቡ ተመራማሪዉ ተናግረዋል።ሳይንቲስቱ የሰዉሰራሽ አስተዉሎት ቴክኖሎጂ ለሰዉ ልጅ የሚያበረክተውን ሚና እንዲሁም በጠፈር ምርምር የቴክኖሎጂዉ አበርክቶ ጉ...
ፈተናውን ማለፍ ያልቻሉ መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏልየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስሩ ለሚገኙትና አዲስ የመዋቅራዊ ማሻሻያ አደረጃጀት ጥናት ባደረጉ ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ ሁሉም ሠራተኞችና የስራ ኃላፊዎች የብቃት መመዘኛ ፈተና ሊሰጥ ነው ተባለ። ፈተናውን ያላለፉ ሰራተኞች መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏል።ከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ዘርፎች ለሰራኞቹ የብቃት ምዘና ፈተ...
ድሮኖቹ በሠላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየወሰዱ ነው ተብሏልየተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ለኢትዮጵያ መንግስት እያደረገች ያለው የሰው አልባ አውሮፕላን ‘የድሮን’ አቅርቦት በአስቸኳይ እንድታቆም በሰሜን አሜሪካ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅች ጠየቁ። ድርጅቶቹ ድሮኖቹ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየወሰዱ ናቸው ብለዋል።በኢትዮጵያ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረው የድሮን ጥቃት በእጅጉ አሳ...
”አርቲስት ሀናን እንደምትጠቅመን አምነንበታል” -ድርጅቱ-አርቲስት ሀናን ታሪክ፤ ድሪመር ፉድ ማኑፋክቸሪንግ ከተሰኘ ታዋቂና ግዙፍ የቻይና ኩባንያ ጋር የብራንድ አምባሳደር ለመሆን በዛሬው ዕለት በስካይላይት ሆቴል ከስምምነት ላይ የደረሰች ሲሆን፤ ለድርጅቱ የሁለት ዓመት የብራንድ አምባሳደር ለመሆን 10 ሚሊዮን ብር ተከፍሏታል፡፡ ኩባንያው በኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ኢንቨስትመንት የምግብ ማቀነባበ...
• በትግራይ የተከሰተው ድርቅ ከ77ቱ የከፋ ነው ተባለ • 25 ህፃናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ ሞተዋል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ ከ2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለረሃብ መጋለጡን ያስታወቀ ሲሆን፤ እስካሁንም 23 ህጻናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ መሞታቸውን ጠቁሟል፡፡በክልሉ ያጋጠመውን የድርቅ አደጋ ለመከላከል ያለመ፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 22 አባላት ያ...
በመንግስትና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት መካከል በዳሬ ሰላም ሲካሄድ የነበረው ድርድር እንዳይሳካ የተደረገው በመንግስት ነው ሲሉ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደኦ ገለፁ፡፡ መንግስት በሁለቱ ወገኖች መካከል የተፈጠረውን ችግር በውይይት ለመፍታት ፍላጎት የለውምሲሉም ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ ተናግረዋል፡፡
የሰላም ሚኒስትር ዴኤታና የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ) አባል የሆኑት...
መንግስት ለዜጎች ደህንነት ጥበቃ እንዲያደርግ ጠይቋልበአማራ፣ በኦሮሚያና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በዜጎች ላይ የሚፈጸሙ አሰቃቂ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተባብሰው መቀጠላቸውንና መንግስት ለሰብአዊ መብቶች ጥሰትና ለጥቃት ተጋላጭ ለሆኑ አካባቢዎችና ነዋሪዎች የተሟላ ጥበቃ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ። ኮሚሽኑ በሶስቱ ክልሎች በሲቪል ሰዎች ላይ የሚፈፀሙ ግድያዎች፣...
የዐማራ ባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን አቶ ኄኖክ አበበ ታደሰንና የኮርፖሬት አገልግሎት ዋና መኰንኑን አቶ ክንዴ አበበን፣ በአፈጻጸም ድክመት ከሓላፊነታቸው አነሣ።የባንኩ ቦርድ ውሳኔውን ያሳለፈው፣ ዛሬ ዐርብ፣ ኅዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ሲኾን፣ ኹለቱም ከፍተኛ ሓላፊዎች፣ ከተሾሙበት ዕለት ጀምሮ፣ በየጊዜው በሚሳዩት የሥራ አፈጻጸም ድክመት፣ የባንኩን ስትራቴጂያዊ ግቦች እና ቁ...
መቀመጫውን በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያደረገው በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ርዕሰ መዲናይቱን አዲስ አበባን ፊንፊኔ ሲል መጥራቱን ሃያሁለት የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶች ተቃወሙት። ማህበራቱ ተቃውሞአቸውን በመግለፅ ለአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ቢሊንከን ደብዳቤ ልከዋል።ኤምባሲው የሚሰጣቸውን የቪዛና ሌሎች አገልግሎቶችን አስመልክቶ ከትናት በስቲያ በማህራዊ ት...
- ከ150 አገራት የተውጣጡ 300 የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እገዳው እንዲነሳ ጠይቀዋል - የእገዳ ተግባሩ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት በኢትዮጵያ የከፋ ነው ተብሏል በአማራ ክልል የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎ በመንግስት የተወሰደውን የኢንተርኔት እገዳ እርምጃ በመቃወም መንግስት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እገዳውን እንዲያነሳና መደበኛ የኢንተርኔት አግልግሎት መስጠቱን...
የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ፍላጎት የለውም ተብሏል የአሜሪካ ህግ አውጭ ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ መክሯል የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልክዕክተኛ ማይክ ሐመር የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጪ ጉዳይ ኮሚቴ የአፍሪካ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ሲመክር ውሏል፡፡ ምክር ቤቱ በቀጥታ በሚተላለፈው ...
• ማዕከሉ በ25 ሚ. ብር ወጪ የማስፋፊያ ስራዎችን ማከናወኑን ገለጸ 33ኛው የገና የንግድ ትርዒት ፣ ባዛርና ፌስቲቫል ከታህሳስ 6 - 27 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡የፌስቲቫሉ አዘጋጅ ሴንቸሪ ፕሮሞሽንና ኤቨንትስ በዛሬው ዕለት ረፋዱ ላይ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት አዳራሽ በሰጠው መግለጫ፤ በዚህ የገና የንግድ ትርዒት...
በቅርቡ አፍሮ ባሮሜትር በተባለው ታዋቂ የምርምር ተቋም ይፋ የተደረገውን የሕገ- መንግስቱ ማሻሻያ አስፈላጊነት፤ “ጊዜውን ያልጠበቀና ግልፅነት የጎደለው ነው” ሲሉ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር አጣጣሉት። ተቋሙ የጥናቱ ውጤቱን ባለፈው ህዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም በኢንተር ሌግዥሪ ሆቴል ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።ሕገ መንግስቱ የፖለቲካና የሕግ ሰነድ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል ያሉት...
ድርድሩ ያለ ስምምነት መጠናቀቁ የአካባቢውን ሰላም ይበልጥ ያደፈርሰዋል ተብሏልበመንግሥትና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነስ ) ብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን መካከል በታንዛኒያ ዳሬሰላም ከተማ ለቀናት ሲካሄድ የሰነበተው የሠላም ድርድር፤ ያለ ሥምምነት መቋጨቱ በእጅጉ እንዳሳዘናቸውና ተስፋ እንዳስቆረጣቸው የአምቦ ከተማና የምስራቅ ወለጋ ዞን የተለያዩ አካባቢ ነዋሪዎች ለአዲስ አድማስ ገለፁ።...
• ስፖርቱ መስፋፋቱ በሥነ ምግባር የታነፁ ዜጎችን ለማፍራትጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ተብሏልየኢትዮጵያ ሌጀንድ ኢንተርናሽና ፕሮ ቴኳንዶ ፌደሬሽን፣ የቴኳንዶና የማርሻል አርት ስፖርትን በት/ቤቶችና በመዝናኛ ቦታዎች ለማስፋፋትና ለማጠናከር የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ከአሴቅ ዲኮርና ኢቨንት ኦርጋናይዜሽን ጋር ትላንት ተፈራረመ፡፡ የስምምነቱ ዋና ዓላማ፤ የቴኳንዶና የማርሻል አርት ስፖርትን በት...
• ማህበሩ 70 ቢሊዮን ብር ለብድር ማቅረቡ ተነግሯልየኢትዮጵያ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ማህበር የተመሰረተበትን የ25ኛ ዓመት የኢዮቤልዩ ክብረ በዓል በመጪው ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚያከብር ተገለፀ፡፡ በዝግጅቱ ላይ በአገሪቱ በልማቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና የ25 ዓመታት እድሜ ያስቆጠረው የማይክሮፋይናንስ ዘርፍ ኅዳር 18ን “የኢትዮጵያ የብድርና ቁጠባ ቀን” በማለት እንደሚ...
• ጉምሩክ 237 ተሽከርካሪዎችን በሃራጅ ለመሸጥ የጀመረውን እንቅስቀሴ መንግሥት እንዲያስቆምላቸው ጠይቀዋል• ገንዘብ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ለሚኒስትሮች ም/ቤት ያቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ተጥሷል ብለዋል• ቅሬታ አቅራቢዎቹ አቤቱታቸውን በተደጋጋሚ ለመንግሥት አካላት ማቅረባቸውን ተናግረዋል ከስደት ተመላሾችና ያገለገሉ ተሽከርካሪ አስመጪዎች፣ ጉምሩክ፣ የመንግሥት ውሳኔን በመጣስ፣ ከውጭ ...
የ“ፍትሕ መጽሔት” ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ዛሬ ኅዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም. በጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከጠበቆቹ ጋር ቀርቧል።ፍርድ ቤቱ በዛሬው ዕለት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፣ በባለፈው ቀጠሮ ፣ የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጠበቆች፤ “የጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት፣ የዐቃቤ ሕግን የይግባኝ ቅሬታና የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ሲሰጠን ገጽ አጉድሎ ስለሆነ የተሟላ ...
የባንኩ የሃብት መጠን 83 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል ሕብረት ባንክ የ25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ ክብረ በዓሉን በዛሬው ዕለት በይፋ ያበሰረ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት የባንኩ የሃብት መጠን 83 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል። አጠቃላይ ካፒታሉ 9. 3 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም 60 ቢሊዮን ብር ብድር እና 64 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ እንዳለው የገለጸው ባንኩ፤ በየዓመቱ ከ25 እስከ...
*ኩባንያው በቅርቡ በ3 የአፍሪካ አገራት የዳታ ማዕከሎቹን ይከፍታል በሰባት የአፍሪካ አገራት የሚንቀሳቀሰው ራክሲዮ የዳታ ማዕከል ኩባንያ፣ በአዲስ አበባ አይሲቲ ፓርክ የገነባው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የዳታ ማዕከሉ በይፋ ሥራ መጀመሩን አበሰረ፡፡በዓይነቱ ልዩ መሆኑ የተነገረለት የራክሲዮ ኢትዮጵያ የዳታ ማዕከል፣ በይፋ ሥራ መጀመሩን የማብሰሪያ ሥነስርዓት ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ በአይሲቲ ፓ...
• የሦስተኛ ወገን ኢንሹራንስን ዲጂታላይዝ የሚያደርጉ መላዎችንም አስጀምሯልኢትዮ ቴሌኮም፤ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ከነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣንና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ጋር በመተባበር፣ የነዳጅ አቅርቦት የአሰራር ስርዓትንና የነዳጅ ኩፖንን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚያስችል እንዲሁም ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርና ከመንገድ ደህንነትና ኢንሹራንስ ፈንድ አገልግሎት ጋር የተ...
በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በ14 .5 ሚሊዬን ዶላር የተገነባ ዘመናዊ የፕላስቲክ ቧንቧና መገጣጠሚያ ማማረቻ ፋብሪካ የፊታችን ቅዳሜ ይመረቃል፡፡
ፋብሪካውን “ኢ ዜድ ኤም ትሬድ እና ኢንቨስትመንት” የተሰኘው ኢትዮጵያዊ የንግድ ኩባንያና የቻይናው ዓለም አቀፍ ድርጅት ሪፎ በጋራ እንደገነቡት ተገልጿል፡፡
የፋብሪካውን ምርቃት አስመልክቶ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽንና የኩ...
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለኩባንያው አዲስ ሥራ አስፈፃሚ መሾሙን አስታወቀሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ በቅርቡ ለቅቀዋል ሲባል የነበሩትን የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በመተካት፣ ለኩባንያው አዲስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እንደተሾመለት አስታወቀ፡፡ቤልጂየማዊው አዲሱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዊልያም ቫንሀለፑተን፣ የቀድሞውን ሥራ አስፈፃሚ አንዋር ሶሳን በመተካት የተሾሙ መሆናቸውን ኩባንያው በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙ...
በአሜሪካው ተራድኮ ድርጅትና በአለም ምግብ ፕሮግራም ይሰጥ የነበረው ተቋርጦ የነበረው የቆየው የምግብ እርዳታ ዳግም መጀመር የመኖር ተስፋን እንዳሳያቸው ተረጂዎች ገለፁ፡፡ እርዳታው በተገቢው መንገድ ለተረጂዎች የሚደረስበትን መንገድ በማመቻቸቱ ረገድ እርዳታ አቅራቢ ድርጅቶቹ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባልም ብለዋል፡፡የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤይድ) እና የአለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ባ...
ኢትዮጵያ ወደከፋና የለየለት የእርስበርስ ጦርነት እንዳትገባ፣ በአገሪቱ ሰላም ለማስፈን የሚቻልበትን መንገድ በማፈላለግ፣ ከከፋ አደጋ ትታደጋት ዘንድ ለአሜሪካ ጥሪ ቀረበ። ጥሪውን ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ያቀረቡት በአሜሪካ የሚገኙ የኢትዮ-አሜሪካን ሲቪል ማህበራት ናቸው።ማህበራቱ በአሁኑ ወቅት ደብዳቤውን ለፕሬዚዳንት ባይደን ለመፃፍ የተነሳሱበትን ምክንያት ሲያስረዱም፤ በአገሪቱ በአሁኑ ወቅት እየተካሄ...
ቄራው በቀን 300 አህዮችን ያርዳል የቻይና ኩባንያዎች ከፍተኛ በጀት መድበው ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል በቻይናውያን ኩባንያዎች የተቋቋሙና አህዮችን እያረዱ ቆዳዎቻቸውን ወደ ቻይና የሚልኩ ድርጅቶች የአህዮቹን ህልውና አደጋ ላይ መጣላቸው ተገለፀ፡፡ ቄራዎቹ አሁን ባለው የእርድ መጠን ከቀጠሉ ከ20 ዓመታት በኋላ በአገሪቱ የአህዮች ህልውና ለከፍተኛ አደጋ የ...
በድርድሩ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ዋና አዛዥ ኩምሣ ድሪባ (ጃል መሮ)ተሳትፏል በመንግስትና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ኦነሰ) መካከል ከማክሰኞ ጀምሮ በታንዛኒያ ዳሬሰላም ሲካሄድ የሰነበተው የሰላም ድርድር ዛሬ ይጠነቃል ተብሎ ይጠናቀቃል። ድርድሩ ሁለቱን ወገኖች ወደ ሰላም በማምጣት አካባቢውን ለማረጋጋት ያስችላል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል።የፌደራል መን...
ሉላ ገዙ፣ የሮያል ፎምና ፈርኒቸር ብራንድ አምባሳደር ሆነች የኢቢኤስ ፕሮግራም አቅራቢዋና የማስታወቂያ ባለሙያዋ ሉላ ገዙ፤ የሮያል ፎምና ፈርኒቸር ብራንድ አምባሳደር ሆና ተመረጠች፡፡ ሉላ ገዙ፤ ለቀጣዮቹ 4 ዓመታት የሮያል ፎምና ፈርኒቸር ብራንድ አምባሳደር ሆና ለመሥራት በዛሬው ዕለት ከሮያል ግሩፕ አመራሮች ጋር በይፋ ተፈራርማለች።...
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን የተኩስ አቁሙ ትክክለኛ እና በቀጣናው የሚፈለገውን መሻሻል ለማምጣት ሚናው ከፍተኛ ነው ሲሉ አወድሰዋል፡፡የተሰኩስ አቁሙ በዋናነት በሥፍራው የሚገኙ ንጹሃን ዜጎችን ከአካባቢው እንዲሸሱ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡ከዚህ ባለፈም በቦታው ችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች አስፈላጊውን የሰብዓዊ እርዳታ ለማድረሰ እንደሚያስችል ተመላክቷል፡፡የእስራኤል ጦር ከዚህ በፊት...
የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስትር እና የዩኔስኮ ብሄራዊ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከዩኔስኮ አጠቃላይ ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ከአለም አቀፍ የትምህርት ቢሮ (UNESCO-IBE) ቦርድ ፕሬዝዳንት ስቪን ኦስትቬት ጋር በፈረንሳይ በሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መስሪያቤት የጎንዮሽ ውይይት አካሂደዋል።
በውይይታቸውም ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን የትምህርት ሥርዓት ለማሻሻል እና ለማዘመን ያከናወናቸውንና በመ...
የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጎበኙ። መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ከተማ ላደረጉ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች በጉባ ጉብኝታቸው፤ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል። ውሃው ተርባይኑን መትቶ ወደ ተፈጥሮአዊ ፍሰቱ የሚመለስና በአባይ ወንዝ ተፋሰስ ሀገራት የሚያመጣው ችግር እንደሌለ መመልከታቸውንም ወታደራዊ...
ኢትዮ ቴሌኮምና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከትላንት በስቲያ የተፈራረሙት ስምምነት፣ የሚኒስቴር መ/ቤቱን የኦፕሬሽንና አገልግሎት አሰጣጥን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በማስቻል፣ የውሃና ኢነርጂ ሃብቶችንና መሰረተ-ልማቶችን በዘመናዊና ቀልጣፋ ቴክኖሎጂ በማገዝ ውጤታማነትን የሚያሳድግ አሰራር በጋራ ለመተግበር ያስችላል ተብሏል።
ይህ ስትራቴጂያዊ ስምምነት፣ በዋናነት የኢትዮ ቴሌኮምን ዘመናዊ የክላውድ ...
*በሶማሊያ ክልል፣ ጎርፍ ብዙ ሺዎችን አፈናቅሏል፤3ሺ የቁም እንስሳትን ገድሏልየኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር፣ ሳምንታዊ የቁርስ ላይ ስብሰባውን ዛሬ ጠዋት በሂልተን ሆቴል ያካሄደ ሲሆን፤ የእለቱ የውይይት ርእሰ ጉዳይም፤ "The Role of Media in Climate Change Communications፡ Why should Editors Care?" የሚል ነበር፡፡ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ለውይይት መነሻ የሚሆ...
• ተቋሙ በአፍሪካ የአይቲ ማዕከል ለመሆን እየሰራ መሆኑ ተጠቁሟልበአፍሪካ የአይቲ ማዕከል ለመሆን ራዕይ ሰንቆ በአዲስ መልክ እየተዋቀረና እየተደራጀ መሆኑ የተነገረለት የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽን፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ በይፋ ሥራ እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡ በአይቲ ፓርኩ፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የግል የዳታ ማዕከል አገልግሎት መስጠት መጀመሩም ተጠቁሟል፡፡ ይህ ይፋ የተደረገው በዛሬው ዕለ...
ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል ወደ 1 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎቹን ያስመርቃል የናሽናል ኢንቨስትመንት ግሩፕ አባልና የናሽናል አየር መንገድ እህት ኩባንያ የሆነው ናሽናል አቪየሽን ኮሌጅ በግል አየር መንገድ ዘርፍ የመጀመሪያ የሆነውን የአውሮፕላን ጠጋኝነት ሥልጠና እንዲሰጥና ተማሪዎችን ተቀብሎ እንዲያስተምር ፈቃድ ማግኘቱን አስታወቀ።ኮሌጁ ዛሬ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ስካይላይት ...
የ”ኢስት ሲሚንቶ ፋብሪካ” ሠራተኞች ናቸው ተብሏል በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በዳጋም ወረዳ ከሀምቢሶ ከተማ በ5 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው ኢስት ሲሚንቶ ፉብሪካ ሰራተኞች የሆኑ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ቻይናውያን፣ በሸኔ ታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸው ተጠቆመ። ራሱን “የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት” እያለ የሚጠራውና መንግስት “ሸኔ” ብሎ የሚ...