Home › View all posts by Addis Admas
Blog Archives
የፍየል ዋጋ አይቀመስም - የበግ ቅናሽ አሳይቷልየትንሳኤ በዓል የገበያ ዋጋ ከገና በዓል የገበያ ዋጋ አንፃር መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱን ነጋዴዎችና ሸማቾች ተናገሩ፡፡ የአዲስ አድማስ ሪፖርተሮች በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ትልልቅ የገበያ ቦታዎችን ከቃኙ በኋላ ባገኙት መረጃ ነው የበዓል ግባቶች የዋጋ ሁኔታ መጠነኛ መረጋጋት ማሳየቱን ማረጋገጥ የቻሉት። ነጋዴዎችና ሸማቾች እንደገለፁት፤ ...
በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ላይ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።ለዚህ የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን ይዘው ወደ አሜሪካ የተጓዙት የኢትዮ ሮቦ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል መሥራችና ዋና ሃላፊ አቶ ሰናይክሪም መኮንን ናቸው። በአሜሪካው ውድድር ላይ ለመሳተፍ የተመረጡት ተማሪዎች በቅርቡ እዚህ አዲ...
የፖለቲካ ሹመኞች በሙያተኞች ላይ በሚያሳድሩት ጫና የመንግሥት ሥራ እየተደናቀፈ ነው ሲሉ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎቹ ለአዲስ አድማስ ተናገሩ። በብዙዎቹ የመንግስት መ/ቤቶች ሃላፊዎች ሥልጣን ላይ የሚቀመጡት በፖለቲካ ታማኝነት እንጂ በዕውቀትና በብቃት ባለመሆኑ በሙያተኞች ላይ የሚያሳድሩት ጫና ሥራውንም ባለሙያውንም እየጎዳው መሆኑንም ያስረዳሉ። እየጎዳው ነው ተብሏል፡፡በአ...
ብልፅግና “የሚዲያ ሠራዊት” አደረጃጀት የለም ሲል አስተባበለበገዢው ብልፅግና ፓርቲ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስር የሚንቀሳቀሱና ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የፓርቲው አባላት፤ መንግሥትን በሚተቹና በሚቃወሙ ግለሰቦች ላይ ሐሰተኛ መረጃ የማሰራጨት ዘመቻ ሥርጫትላይ መሳተፋቸውን ቢቢሲ ባደረገው ምርመራ ማረጋገጡን አመለከተ።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወ...
(ከእስራኤል ምክትል አምባሳደር ጋር የተደረገ ልዩ ቃለ መጠይቅ)ኢራን ባለፈው ቅዳሜ ሚያዝያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት ከ300 በላይ የድሮኖችና የሚሳኤሎች ጥቃት በእስራኤል ላይ ያደረሰች ሲሆን፤ እስራኤል አሜሪካና እንግሊዝን ጨምሮ ከአጋሮቿ ጋር በመተባበር ከተወነጨፉት ድሮኖችና ሚሳኤሎች ውስጥ 99 በመቶውን ከአየር ክልሏ ውጭ ማምከን መቻሏን አስታውቃለች፡፡ ኢራን የፈጸመችው ጥቃት የዛሬ 20...
የሶማሊያ ፌደራል መንግሥት፣ በፑንትላንድ ዋና ከተማ ጋሮዌ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ እንዲዘጋ ያስተላለፈውን ትዕዛዝ እንደማትቀበል ፑንትላንድ አስታወቀች።የሶማሊያ መንግሥት የኢትዮጵያ መንግሥት በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ እየገባ ነው በሚል በሞቃዲሾ የኢትዮጵያ አምባሳደር አገሪቱን ለቀው እንዲወጡና በከፊል ራስ ገዟ ፑንትላንድና ነጻነቷን ባወጀችው ሶማሊላንድ ያሉት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች እንዲ...
ጠ/ሚኒስትሩ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሰብሰብ ብለው እንዲታገሉ ጥሪ አቀረቡ”60 ፓርቲዎች ሆናችሁ ልንደግፋችሁ ይቸግረናል“ለሁለት ወር ግድም ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ያደረጉት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ ባለፈው ሰኞ መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም በመቶዎች ከሚቆጠሩ የተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የፓርቲ አመራሮቹ በውይይቱ ላይ ለጠ/...
ጥበበ ተርፋ ማመጫ፤ በሐረር ከተማ በ1941 ዓ.ም ተወለዱ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሐረር መድኃኒዓለም ት/ቤት እንዳጠናቀቁ ወደ አዲስ አበባ ሥነ ጥበብ ት/ቤት (በአሁኑ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አለ የሥነ ጥበብና ዲዛይን ት/ቤት) በመግባት ተመርቀዋል።በኢትዮጵያ ዘመናዊ የሥነጥበብ ልምምድ ውስጥ ተዋጽዖአቸው ከፍ ያለ ሥፍራ የሚሰጠው ነበረ:: የሥዕል ሥራቸውን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ለ...
አማራ ባንክ ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ አክሲዮን ለመግዛት የሚያስችለውን ስምምነት የፈጸመ ሲሆን፤ የ10% አክሲዮን ድርሻ ገዝቷል፡፡ የአማራ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ተወያይቶ ባፀደቀው መሠረት፣ ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ በመመደብ የአክሲዮን ድርሻ የገዛው ባንኩ፤ ሲሆን፤ ይህም በገንዘብ ሲተመን 90.6 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ተገልጿል።አማራ ባንክ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገትና ለህዝብ ኑሮ መሻ...
• ”የቢጂአይ ኢትዮጵያ አመራር፣ ያሰርነውን ውልና የፍ/ቤት ትዕዛዝ ጥሷል” • ”የበለጸጉና የተደራጁ ኤጀንቶችን በአዳዲስ መተካት የሚል አዲስ ስትራቴጂ መጥቷል“ከተመሰረተ 14 ዓመት ገደማ ማስቆጠሩ የተነገረለት ቢጂአይ ኢትዮጵያ ኃ. የተ. የግል ወኪል አከፋፋይ አሰሪ ማህበር፤ በቢጂአይ ኢትዮጵያ አመራሮች ደረሱብኝ ያላቸውን በደሎች ለጋዜጠኞች በተሰጠው መግለጫ ላይ አብራርቷል፡፡ ማህበሩ በ...
- ባለፈው ዓመት 7 ሺህ የሚጠጉ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ተደርገዋልኢትዮጵያ ለሳይበር ጥቃት ተጋላጭነታቸው ከፍ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነችና የሳይበር ጥቃቶቹ የፋይናንስና የፀጥታ ተቋማትን፣ ባንኮችን፣ እንደ ቴሌኮምና መብራት ሃይል ያሉ ተቋማትን፣ መሰረተ ልማቶችንና ቁልፍ የመንግስት ተቋማትን ኢላማ ያደረጉ እንደሆኑ ታዋቂው የሳይበር ደህንነት ተቋም ሲዮን ገልጿል። ተቋሙ ከ...
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባጋጠመው የሲስተም ችግር ወቅት ገንዘብ የወሰዱ ወይም ያስተላለፉ ግለሰቦች እስከ መጪው ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ካልመለሱ ፎቷቸውንና ማንነታቸውን በመገናኛ ብዙኃን ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ።ባንኩ ገንዘቡን ተመላሽ በማያደርጉ ሰዎች ላይ በሕጋዊ ሂደቱ ተገቢ ውሳኔ እስኪገኝ ድረስ ፎቶግራፋቸውንና ዝርዝር ማንነታቸውን የሚገልጹ መረጃዎች “ባንኩ በመረጠው የ...
ኢትዮ - ሮቦ ሮቦቲክስ፤ በነገው ዕለት ሐሙስ፣ የ2024 የአፍሪካ ሮቦቲክስ ቻምፒዮንሺፕ ውድድሩን በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል የሚጀምር ሲሆን፤ ቅዳሜ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡ መርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄድ ዓመታዊ የሮቦቲክስ ወድድር መሆኑን የኢትዮ-ሮቦ ሮቦቲክስ መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰናይ መኮንን ገልጸዋል፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠ...
መልዕክተኛው የፕሪቶሪያው ስምምነት አፈጻፀምን ይገመግማሉ ተብሏልየአሜሪካ መንግሥት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የተከሰቱ ግጭቶች በድርድር እንዲፈቱ ለማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮችና በመንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰው ስምምነት አፈጻጸም ግምገማ ዙሪያ በአዲስ አበባ እየመከሩ ነው ። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መግለጫ ላይ እንደ...
በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ ለሕዝብ ቀርቦ ዜጎች ውይይት እንዲያደርጉበትና እንዲተች የሚጠይቅ ምክረሃሳብ ለፍትህ ሚኒስቴር ቀረበ ። ”ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ“ የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት፣ ከሌሎች በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሚሠሩ አገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር፣ ለረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ግብዓት የሚኾኑ ሀሳ...
በቢጂአይ ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ ኢትዮጵያ ዋና መሥሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር፣ ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡ ተገልጧል፡፡ቢጂአይ ኢትዮጵያ ትላንት ባሰራጨው መግለጫ፣ የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎትና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ነው፤ ብሏል።ፐርፐዝ ...
የፒያሳ ነዋሪዎች በ3 ወራት ጊዜ ውስጥ አካባቢውን እንዲለቁ ተነግሯቸዋልበአዲስ አበባ አስተዳደር አራዳ ክፍለ ከተማ፣ የፒያሳና አራት ኪሎ ነዋሪዎች ለልማት ከመኖሪያቸው እንደሚነሱ የክፍለ ከተማው አስተዳደር ገልጿል።አስተዳደሩ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ እንዳስታወቀው፤ ሁለቱን አካባቢዎች መልሶ በማልማትና ነዋሪዎችን በማስነሳት ዙሪያ ሰሞኑን ከነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርጓል። ውይይቱ፣ በንግድ ...
የፌደራል መንግስትና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ አደራዳሪዎች በተገኙበት በቀጣይ ሳምንታት በፕሪቶርያው ስምምነት ዙሪያ ዳግም ለውይይት ሊቀመጡ ነው ተባለ። የካቲት 18 እና 19 ቀን 2016 ዓ.ም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መሰብሰቡንና የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ረዳኢ ሀለፎም ከትግራይ ቴሊቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገልጸዋ...
የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ ”የሥራ መልቀቂያ አስገቡ“ በሚል የተሰራጨው መረጃ ሃሰተኛ መሆኑን የባንኩ ባለድርሻ አካላት ገለጹ፡፡የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን የሚገልጹ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች መሰራጨታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ሆኖም መረጃው ሙሉ በሙሉ ሃሰተኛ ነው ብለዋል - ለባንኩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች፡፡የባ...
ባለ አራት ኮከቡ ዘጠነኛው ኃይሌ ሆቴል ወላይታ በዛሬው ዕለት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አብስሯል፡፡ ሆቴሉ ትልቁን ዳሞታ ተራራን ተንተርሶ በኮረብታማዋ ወላይታ ሶዶ ከተማ እምብርት ላይ የተገነባ ነው። ሆቴሉ ተሰርቶ ለመጠናቀቅ አራት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን፤ እስካሁን 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ወጥቶበታል ብሏል፤ በሆቴሉ ዳሞታ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ። ሆቴሉ...
ም/ቤቱ ሁለቱ አገራት አለመግባባታቸውን በንግግር እንዲፈቱ መክሯልየሶማሊያ ባለሥልጣናት ጦርነት ቀስቃሽ ዛቻዎችን መሰንዘር ቀጥለዋልየአፍሪካ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት ባለፈው ረቡዕ ጥር 8 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን ውጥረት አስመልክቶ ውይይት ያደረገ ሲሆን፤ የውጭ ሃይሎች በሁለቱ አገራት መካከል ጣልቃ ከመግባት እንዲቆጠቡ አሳስቧል። ምክር ቤቱ የቀድሞው...
የአንጋፋው ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈፀመጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ባደረበት ህመም በአሜሪካ ሕክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ባለፈው ሳምንት ሕይወቱ ማለፉ ይታወቃል፡፡በሚሊኒየም አዳራሽም የስንብት መርሐግብር ከተካሄደ በኋላ በመንበረ ጸባኦት ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ቤተሰቦቹ፣ የሙያ አድናቂዎቹ፣ የስራ ባልደረቦቹ በተገኙበት የፍትሃት እና የቀብር ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዝግ...
የኢትዮጵያና የሶማሊላንድ መሪዎች፣ ኢትዮጵያን ለ50 ዓመታት የባህር ጠረፍ ተጠቃሚ የሚያደርግ የመግባቢያ ሰነድ መፈረማቸውን ተከትሎ፣ በቀጠናው አዲስ የጂኦ ፖለቲካ ውዝግብ መፈጠሩ እየተነገረ ነው። እስካሁን ድረስ በሱማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል በህግ የሚፀና ስምምነት ባይካሄድም እንኳንም በቀጠናው ውዝግብ ማስከተሉ አልቀረም ። በሁለቱም መንግሥስታት መካከል የተፈረመው ለመግባቢያ ሰነድ የሚሆን...
• ኢትዮጵያውያን፣ ለልደት በዓልን ወደ እስራኤል ተጉዘዋል በብጹዕ አቡነ አብርሃም የተመራው የልዑካን ቡድን፣ በእስራኤል ኢየሩሳሌምን ጨምሮ በርካታ ታሪካዊና ቅዱሳን ሥፍራዎችን ለ5 ቀናት ጎብኝቶ፣ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰ ሲሆን፤ ሁሉም የጉብኝት ሥፍራዎች ሰላማዊና ምንም ዓይነት ሥጋት እንደሌለባቸው ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡በእስራኤል የሚገኙ ቅዱሳንና ...
• ከእስራኤል የተመለሰው የልኡክ ቡድን፤ የጉብኝት ሥፍራዎች ሰላማዊና አስተማማኝ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል• ሁለተኛው የልኡክ ቡድን፣ ለልደት በዓል ወደ እስራኤል ይጓዛል በብጹዕ አቡነ አብርሃም የተመራው የልዑካን ቡድን፣ በእስራኤል ኢየሩሳሌምን ጨምሮ በርካታ ታሪካዊና ቅዱሳን ሥፍራዎችን ለ5 ቀናት ጎብኝቶ፣ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰ ሲሆን፤ ሁሉም የጉብኝት ሥፍራዎች ሰላማዊና ምንም...
(የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጋዜጣዊ መግለጫ) የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣በጉራጌ ዞንና በቀቤና ልዩ ወረዳ መካከል የነበረውን አለመግባባት ተከትሎ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስና ያስከተለውን ጉዳት ከአካባቢው ነዋሪዎች በቀረበለት አቤቱታ መነሻነት ከጥቅምት 20 እስከ 25 ቀን 2016 ዓ.ም....
2ኛው ሀገር አቀፍ የህገወጥ ንግድ መከላከል ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩ ላይ ህገወጥ የቁም እንስሳ ንግድ ከፍተኛ ኪሳራ ማስከተሉ ተጠቁሟል፡፡በጉባኤው ላይ በቁም እንስሳት፤ በመድኃኒትና ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ በሚታይ ህገወጥ ንግድ ላይ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጓል፡፡ በንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ስርዓትና ፈቃድ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፍሰሀ ይ...
‘Fly Now Pay Later’ ዳሽን ባንክና የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ደንበኞች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን ‘ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል’ የሚል አዲስ የክፍያ አማራጭ በዛሬው ዕለት አስተዋወቁ። የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን አቶ ዮሐንስ መኮንን እንደገለጹት፤ ‘ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል’ የተሰኘው አዲሱ የክፍያ አማራጭ ...
ግጭቶቹ በዚሁ ከቀጠሉ አገሪቱ ከባድ አደጋ ላይ ትወድቃለች ተብሏል በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት 5300 ግጭቶች መከሰታቸውንና በዚህም በሺዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን መሞታቸውን ብሔራዊ የግጭት ክስተት ልየታ ጥናት ይፋ አደረገ። ጥናቱ ከ2010 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ዓመታት በአገሪቱ እጅግ ከባድ ግጭት የተከሰተባቸው ዓመታ...
የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እንደሚችል አስጠንቅቋል መንግስት በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ አለም አቀፍ ተቋማትና በዲፕሎማሲያዊ ማህበረሰብ አባላት ላይ እየወሰደ ያለው ተገቢ ያልሆነና አለማቀፋዊ ህጎችን የጣሰ ድርጊት ከፍተኛ ዋጋ ሊያስከፍልው እንደሚችል የፖለቲካና ኢኮኖሚ ጉዳዳዮች ምህሩ ዶክተር አንተነህ ተስፋዬ ገለፁ። የአፍሪካ ልማት...
በሃዋሳ ከተማ በምሥራቅ ክፍለ ከተማ በ280 ሚሊዮን ብር ወጪ በ700 ካ.ሜ ቦታ ላይ የተገነባው ባለ 3 ኮከቡ ፌኔት ሆቴል፣ በዛሬው ዕለት የክልሉ የሥራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመረቀ፡፡የዕለቱ የክብር እንግዳ የሲዳማ ክልል ፕሬዚዳንት አማካሪ አቶ ተሰማ ዲማ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "ሃዋሳ የቱሪዝም ከተማ እንደመሆኗ ሆቴሉ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል...
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ የሥራ ሀላፊዎች ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በዛሬው ዕለት በመሐል ሐዋሳ ፒያሳ ላይ አስገንብቶ ያስመረቀውን ሁለገብ ሕንጻ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ከጉብኙቱ በኋላ ባደረጉት ንግግር፤ ''ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በሲዳማ ክልልም ሆነ በሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ማስፋፋት...
በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው ነው የተባለለት የአንጎል የደም ስር ክሊፒንግ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።ይህ ህክምና የተደረገላት ታካሚ ከአዲስ አበባ በጥቂት ርቀት ላይ የምትኖር ሲሆን፤ ድንገት በዕለት ሥራዋ ላይ ሳለች ከፍተኛ የራስ ህመም ይሰማት እንደጀመረና ከዚያም እራስዋን ስታ መውደቋን ታሪኳ ያስረዳል።ህክምና ተቋም እንደደረሰችም በተደረገላት ምርመራ በአንጎልዋ ውስጥ ...
በጉብኝቱ ወቅት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ኢንጅነር) ስለኢንስቲትዩቱ ሥራዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡ በውይይቱ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን ለማልማት በኢንስቲትዩቱ የሚሰሩ የምርምር ተግባራት ለሀገር የሚበጁ መሆናቸውን እንደተገነዘቡ ተመራማሪዉ ተናግረዋል።ሳይንቲስቱ የሰዉሰራሽ አስተዉሎት ቴክኖሎጂ ለሰዉ ልጅ የሚያበረክተውን ሚና እንዲሁም በጠፈር ምርምር የቴክኖሎጂዉ አበርክቶ ጉ...
ፈተናውን ማለፍ ያልቻሉ መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏልየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስሩ ለሚገኙትና አዲስ የመዋቅራዊ ማሻሻያ አደረጃጀት ጥናት ባደረጉ ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ ሁሉም ሠራተኞችና የስራ ኃላፊዎች የብቃት መመዘኛ ፈተና ሊሰጥ ነው ተባለ። ፈተናውን ያላለፉ ሰራተኞች መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏል።ከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ዘርፎች ለሰራኞቹ የብቃት ምዘና ፈተ...
ድሮኖቹ በሠላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየወሰዱ ነው ተብሏልየተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ለኢትዮጵያ መንግስት እያደረገች ያለው የሰው አልባ አውሮፕላን ‘የድሮን’ አቅርቦት በአስቸኳይ እንድታቆም በሰሜን አሜሪካ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅች ጠየቁ። ድርጅቶቹ ድሮኖቹ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየወሰዱ ናቸው ብለዋል።በኢትዮጵያ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረው የድሮን ጥቃት በእጅጉ አሳ...
”አርቲስት ሀናን እንደምትጠቅመን አምነንበታል” -ድርጅቱ-አርቲስት ሀናን ታሪክ፤ ድሪመር ፉድ ማኑፋክቸሪንግ ከተሰኘ ታዋቂና ግዙፍ የቻይና ኩባንያ ጋር የብራንድ አምባሳደር ለመሆን በዛሬው ዕለት በስካይላይት ሆቴል ከስምምነት ላይ የደረሰች ሲሆን፤ ለድርጅቱ የሁለት ዓመት የብራንድ አምባሳደር ለመሆን 10 ሚሊዮን ብር ተከፍሏታል፡፡ ኩባንያው በኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ኢንቨስትመንት የምግብ ማቀነባበ...
• በትግራይ የተከሰተው ድርቅ ከ77ቱ የከፋ ነው ተባለ • 25 ህፃናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ ሞተዋል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ ከ2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለረሃብ መጋለጡን ያስታወቀ ሲሆን፤ እስካሁንም 23 ህጻናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ መሞታቸውን ጠቁሟል፡፡በክልሉ ያጋጠመውን የድርቅ አደጋ ለመከላከል ያለመ፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 22 አባላት ያ...
በመንግስትና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት መካከል በዳሬ ሰላም ሲካሄድ የነበረው ድርድር እንዳይሳካ የተደረገው በመንግስት ነው ሲሉ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደኦ ገለፁ፡፡ መንግስት በሁለቱ ወገኖች መካከል የተፈጠረውን ችግር በውይይት ለመፍታት ፍላጎት የለውምሲሉም ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ ተናግረዋል፡፡
የሰላም ሚኒስትር ዴኤታና የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ) አባል የሆኑት...
መንግስት ለዜጎች ደህንነት ጥበቃ እንዲያደርግ ጠይቋልበአማራ፣ በኦሮሚያና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በዜጎች ላይ የሚፈጸሙ አሰቃቂ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተባብሰው መቀጠላቸውንና መንግስት ለሰብአዊ መብቶች ጥሰትና ለጥቃት ተጋላጭ ለሆኑ አካባቢዎችና ነዋሪዎች የተሟላ ጥበቃ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ። ኮሚሽኑ በሶስቱ ክልሎች በሲቪል ሰዎች ላይ የሚፈፀሙ ግድያዎች፣...
የዐማራ ባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን አቶ ኄኖክ አበበ ታደሰንና የኮርፖሬት አገልግሎት ዋና መኰንኑን አቶ ክንዴ አበበን፣ በአፈጻጸም ድክመት ከሓላፊነታቸው አነሣ።የባንኩ ቦርድ ውሳኔውን ያሳለፈው፣ ዛሬ ዐርብ፣ ኅዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ሲኾን፣ ኹለቱም ከፍተኛ ሓላፊዎች፣ ከተሾሙበት ዕለት ጀምሮ፣ በየጊዜው በሚሳዩት የሥራ አፈጻጸም ድክመት፣ የባንኩን ስትራቴጂያዊ ግቦች እና ቁ...
መቀመጫውን በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያደረገው በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ርዕሰ መዲናይቱን አዲስ አበባን ፊንፊኔ ሲል መጥራቱን ሃያሁለት የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶች ተቃወሙት። ማህበራቱ ተቃውሞአቸውን በመግለፅ ለአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ቢሊንከን ደብዳቤ ልከዋል።ኤምባሲው የሚሰጣቸውን የቪዛና ሌሎች አገልግሎቶችን አስመልክቶ ከትናት በስቲያ በማህራዊ ት...
- ከ150 አገራት የተውጣጡ 300 የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እገዳው እንዲነሳ ጠይቀዋል - የእገዳ ተግባሩ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት በኢትዮጵያ የከፋ ነው ተብሏል በአማራ ክልል የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎ በመንግስት የተወሰደውን የኢንተርኔት እገዳ እርምጃ በመቃወም መንግስት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እገዳውን እንዲያነሳና መደበኛ የኢንተርኔት አግልግሎት መስጠቱን...
የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ፍላጎት የለውም ተብሏል የአሜሪካ ህግ አውጭ ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ መክሯል የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልክዕክተኛ ማይክ ሐመር የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጪ ጉዳይ ኮሚቴ የአፍሪካ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ሲመክር ውሏል፡፡ ምክር ቤቱ በቀጥታ በሚተላለፈው ...
• ማዕከሉ በ25 ሚ. ብር ወጪ የማስፋፊያ ስራዎችን ማከናወኑን ገለጸ 33ኛው የገና የንግድ ትርዒት ፣ ባዛርና ፌስቲቫል ከታህሳስ 6 - 27 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡የፌስቲቫሉ አዘጋጅ ሴንቸሪ ፕሮሞሽንና ኤቨንትስ በዛሬው ዕለት ረፋዱ ላይ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት አዳራሽ በሰጠው መግለጫ፤ በዚህ የገና የንግድ ትርዒት...
በቅርቡ አፍሮ ባሮሜትር በተባለው ታዋቂ የምርምር ተቋም ይፋ የተደረገውን የሕገ- መንግስቱ ማሻሻያ አስፈላጊነት፤ “ጊዜውን ያልጠበቀና ግልፅነት የጎደለው ነው” ሲሉ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር አጣጣሉት። ተቋሙ የጥናቱ ውጤቱን ባለፈው ህዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም በኢንተር ሌግዥሪ ሆቴል ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።ሕገ መንግስቱ የፖለቲካና የሕግ ሰነድ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል ያሉት...
ድርድሩ ያለ ስምምነት መጠናቀቁ የአካባቢውን ሰላም ይበልጥ ያደፈርሰዋል ተብሏልበመንግሥትና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነስ ) ብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን መካከል በታንዛኒያ ዳሬሰላም ከተማ ለቀናት ሲካሄድ የሰነበተው የሠላም ድርድር፤ ያለ ሥምምነት መቋጨቱ በእጅጉ እንዳሳዘናቸውና ተስፋ እንዳስቆረጣቸው የአምቦ ከተማና የምስራቅ ወለጋ ዞን የተለያዩ አካባቢ ነዋሪዎች ለአዲስ አድማስ ገለፁ።...
• ስፖርቱ መስፋፋቱ በሥነ ምግባር የታነፁ ዜጎችን ለማፍራትጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ተብሏልየኢትዮጵያ ሌጀንድ ኢንተርናሽና ፕሮ ቴኳንዶ ፌደሬሽን፣ የቴኳንዶና የማርሻል አርት ስፖርትን በት/ቤቶችና በመዝናኛ ቦታዎች ለማስፋፋትና ለማጠናከር የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ከአሴቅ ዲኮርና ኢቨንት ኦርጋናይዜሽን ጋር ትላንት ተፈራረመ፡፡ የስምምነቱ ዋና ዓላማ፤ የቴኳንዶና የማርሻል አርት ስፖርትን በት...
• ማህበሩ 70 ቢሊዮን ብር ለብድር ማቅረቡ ተነግሯልየኢትዮጵያ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ማህበር የተመሰረተበትን የ25ኛ ዓመት የኢዮቤልዩ ክብረ በዓል በመጪው ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚያከብር ተገለፀ፡፡ በዝግጅቱ ላይ በአገሪቱ በልማቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና የ25 ዓመታት እድሜ ያስቆጠረው የማይክሮፋይናንስ ዘርፍ ኅዳር 18ን “የኢትዮጵያ የብድርና ቁጠባ ቀን” በማለት እንደሚ...
• ጉምሩክ 237 ተሽከርካሪዎችን በሃራጅ ለመሸጥ የጀመረውን እንቅስቀሴ መንግሥት እንዲያስቆምላቸው ጠይቀዋል• ገንዘብ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ለሚኒስትሮች ም/ቤት ያቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ተጥሷል ብለዋል• ቅሬታ አቅራቢዎቹ አቤቱታቸውን በተደጋጋሚ ለመንግሥት አካላት ማቅረባቸውን ተናግረዋል ከስደት ተመላሾችና ያገለገሉ ተሽከርካሪ አስመጪዎች፣ ጉምሩክ፣ የመንግሥት ውሳኔን በመጣስ፣ ከውጭ ...
የ“ፍትሕ መጽሔት” ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ዛሬ ኅዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም. በጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከጠበቆቹ ጋር ቀርቧል።ፍርድ ቤቱ በዛሬው ዕለት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፣ በባለፈው ቀጠሮ ፣ የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጠበቆች፤ “የጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት፣ የዐቃቤ ሕግን የይግባኝ ቅሬታና የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ሲሰጠን ገጽ አጉድሎ ስለሆነ የተሟላ ...
የባንኩ የሃብት መጠን 83 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል ሕብረት ባንክ የ25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ ክብረ በዓሉን በዛሬው ዕለት በይፋ ያበሰረ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት የባንኩ የሃብት መጠን 83 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል። አጠቃላይ ካፒታሉ 9. 3 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም 60 ቢሊዮን ብር ብድር እና 64 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ እንዳለው የገለጸው ባንኩ፤ በየዓመቱ ከ25 እስከ...
*ኩባንያው በቅርቡ በ3 የአፍሪካ አገራት የዳታ ማዕከሎቹን ይከፍታል በሰባት የአፍሪካ አገራት የሚንቀሳቀሰው ራክሲዮ የዳታ ማዕከል ኩባንያ፣ በአዲስ አበባ አይሲቲ ፓርክ የገነባው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የዳታ ማዕከሉ በይፋ ሥራ መጀመሩን አበሰረ፡፡በዓይነቱ ልዩ መሆኑ የተነገረለት የራክሲዮ ኢትዮጵያ የዳታ ማዕከል፣ በይፋ ሥራ መጀመሩን የማብሰሪያ ሥነስርዓት ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ በአይሲቲ ፓ...
• የሦስተኛ ወገን ኢንሹራንስን ዲጂታላይዝ የሚያደርጉ መላዎችንም አስጀምሯልኢትዮ ቴሌኮም፤ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ከነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣንና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ጋር በመተባበር፣ የነዳጅ አቅርቦት የአሰራር ስርዓትንና የነዳጅ ኩፖንን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚያስችል እንዲሁም ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርና ከመንገድ ደህንነትና ኢንሹራንስ ፈንድ አገልግሎት ጋር የተ...
በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በ14 .5 ሚሊዬን ዶላር የተገነባ ዘመናዊ የፕላስቲክ ቧንቧና መገጣጠሚያ ማማረቻ ፋብሪካ የፊታችን ቅዳሜ ይመረቃል፡፡
ፋብሪካውን “ኢ ዜድ ኤም ትሬድ እና ኢንቨስትመንት” የተሰኘው ኢትዮጵያዊ የንግድ ኩባንያና የቻይናው ዓለም አቀፍ ድርጅት ሪፎ በጋራ እንደገነቡት ተገልጿል፡፡
የፋብሪካውን ምርቃት አስመልክቶ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽንና የኩ...
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለኩባንያው አዲስ ሥራ አስፈፃሚ መሾሙን አስታወቀሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ በቅርቡ ለቅቀዋል ሲባል የነበሩትን የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በመተካት፣ ለኩባንያው አዲስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እንደተሾመለት አስታወቀ፡፡ቤልጂየማዊው አዲሱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዊልያም ቫንሀለፑተን፣ የቀድሞውን ሥራ አስፈፃሚ አንዋር ሶሳን በመተካት የተሾሙ መሆናቸውን ኩባንያው በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙ...
በአሜሪካው ተራድኮ ድርጅትና በአለም ምግብ ፕሮግራም ይሰጥ የነበረው ተቋርጦ የነበረው የቆየው የምግብ እርዳታ ዳግም መጀመር የመኖር ተስፋን እንዳሳያቸው ተረጂዎች ገለፁ፡፡ እርዳታው በተገቢው መንገድ ለተረጂዎች የሚደረስበትን መንገድ በማመቻቸቱ ረገድ እርዳታ አቅራቢ ድርጅቶቹ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባልም ብለዋል፡፡የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤይድ) እና የአለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ባ...
ኢትዮጵያ ወደከፋና የለየለት የእርስበርስ ጦርነት እንዳትገባ፣ በአገሪቱ ሰላም ለማስፈን የሚቻልበትን መንገድ በማፈላለግ፣ ከከፋ አደጋ ትታደጋት ዘንድ ለአሜሪካ ጥሪ ቀረበ። ጥሪውን ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ያቀረቡት በአሜሪካ የሚገኙ የኢትዮ-አሜሪካን ሲቪል ማህበራት ናቸው።ማህበራቱ በአሁኑ ወቅት ደብዳቤውን ለፕሬዚዳንት ባይደን ለመፃፍ የተነሳሱበትን ምክንያት ሲያስረዱም፤ በአገሪቱ በአሁኑ ወቅት እየተካሄ...
ቄራው በቀን 300 አህዮችን ያርዳል የቻይና ኩባንያዎች ከፍተኛ በጀት መድበው ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል በቻይናውያን ኩባንያዎች የተቋቋሙና አህዮችን እያረዱ ቆዳዎቻቸውን ወደ ቻይና የሚልኩ ድርጅቶች የአህዮቹን ህልውና አደጋ ላይ መጣላቸው ተገለፀ፡፡ ቄራዎቹ አሁን ባለው የእርድ መጠን ከቀጠሉ ከ20 ዓመታት በኋላ በአገሪቱ የአህዮች ህልውና ለከፍተኛ አደጋ የ...
በድርድሩ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ዋና አዛዥ ኩምሣ ድሪባ (ጃል መሮ)ተሳትፏል በመንግስትና የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (ኦነሰ) መካከል ከማክሰኞ ጀምሮ በታንዛኒያ ዳሬሰላም ሲካሄድ የሰነበተው የሰላም ድርድር ዛሬ ይጠነቃል ተብሎ ይጠናቀቃል። ድርድሩ ሁለቱን ወገኖች ወደ ሰላም በማምጣት አካባቢውን ለማረጋጋት ያስችላል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል።የፌደራል መን...
ሉላ ገዙ፣ የሮያል ፎምና ፈርኒቸር ብራንድ አምባሳደር ሆነች የኢቢኤስ ፕሮግራም አቅራቢዋና የማስታወቂያ ባለሙያዋ ሉላ ገዙ፤ የሮያል ፎምና ፈርኒቸር ብራንድ አምባሳደር ሆና ተመረጠች፡፡ ሉላ ገዙ፤ ለቀጣዮቹ 4 ዓመታት የሮያል ፎምና ፈርኒቸር ብራንድ አምባሳደር ሆና ለመሥራት በዛሬው ዕለት ከሮያል ግሩፕ አመራሮች ጋር በይፋ ተፈራርማለች።...
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን የተኩስ አቁሙ ትክክለኛ እና በቀጣናው የሚፈለገውን መሻሻል ለማምጣት ሚናው ከፍተኛ ነው ሲሉ አወድሰዋል፡፡የተሰኩስ አቁሙ በዋናነት በሥፍራው የሚገኙ ንጹሃን ዜጎችን ከአካባቢው እንዲሸሱ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡ከዚህ ባለፈም በቦታው ችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች አስፈላጊውን የሰብዓዊ እርዳታ ለማድረሰ እንደሚያስችል ተመላክቷል፡፡የእስራኤል ጦር ከዚህ በፊት...
የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስትር እና የዩኔስኮ ብሄራዊ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከዩኔስኮ አጠቃላይ ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ከአለም አቀፍ የትምህርት ቢሮ (UNESCO-IBE) ቦርድ ፕሬዝዳንት ስቪን ኦስትቬት ጋር በፈረንሳይ በሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መስሪያቤት የጎንዮሽ ውይይት አካሂደዋል።
በውይይታቸውም ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን የትምህርት ሥርዓት ለማሻሻል እና ለማዘመን ያከናወናቸውንና በመ...
የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጎበኙ። መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ከተማ ላደረጉ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ አታሼዎች በጉባ ጉብኝታቸው፤ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል። ውሃው ተርባይኑን መትቶ ወደ ተፈጥሮአዊ ፍሰቱ የሚመለስና በአባይ ወንዝ ተፋሰስ ሀገራት የሚያመጣው ችግር እንደሌለ መመልከታቸውንም ወታደራዊ...
ኢትዮ ቴሌኮምና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከትላንት በስቲያ የተፈራረሙት ስምምነት፣ የሚኒስቴር መ/ቤቱን የኦፕሬሽንና አገልግሎት አሰጣጥን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በማስቻል፣ የውሃና ኢነርጂ ሃብቶችንና መሰረተ-ልማቶችን በዘመናዊና ቀልጣፋ ቴክኖሎጂ በማገዝ ውጤታማነትን የሚያሳድግ አሰራር በጋራ ለመተግበር ያስችላል ተብሏል።
ይህ ስትራቴጂያዊ ስምምነት፣ በዋናነት የኢትዮ ቴሌኮምን ዘመናዊ የክላውድ ...
*በሶማሊያ ክልል፣ ጎርፍ ብዙ ሺዎችን አፈናቅሏል፤3ሺ የቁም እንስሳትን ገድሏልየኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር፣ ሳምንታዊ የቁርስ ላይ ስብሰባውን ዛሬ ጠዋት በሂልተን ሆቴል ያካሄደ ሲሆን፤ የእለቱ የውይይት ርእሰ ጉዳይም፤ "The Role of Media in Climate Change Communications፡ Why should Editors Care?" የሚል ነበር፡፡ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ለውይይት መነሻ የሚሆ...
• ተቋሙ በአፍሪካ የአይቲ ማዕከል ለመሆን እየሰራ መሆኑ ተጠቁሟልበአፍሪካ የአይቲ ማዕከል ለመሆን ራዕይ ሰንቆ በአዲስ መልክ እየተዋቀረና እየተደራጀ መሆኑ የተነገረለት የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽን፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ በይፋ ሥራ እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡ በአይቲ ፓርኩ፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የግል የዳታ ማዕከል አገልግሎት መስጠት መጀመሩም ተጠቁሟል፡፡ ይህ ይፋ የተደረገው በዛሬው ዕለ...
ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል ወደ 1 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎቹን ያስመርቃል የናሽናል ኢንቨስትመንት ግሩፕ አባልና የናሽናል አየር መንገድ እህት ኩባንያ የሆነው ናሽናል አቪየሽን ኮሌጅ በግል አየር መንገድ ዘርፍ የመጀመሪያ የሆነውን የአውሮፕላን ጠጋኝነት ሥልጠና እንዲሰጥና ተማሪዎችን ተቀብሎ እንዲያስተምር ፈቃድ ማግኘቱን አስታወቀ።ኮሌጁ ዛሬ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በኢትዮጵያ ስካይላይት ...
የ”ኢስት ሲሚንቶ ፋብሪካ” ሠራተኞች ናቸው ተብሏል በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በዳጋም ወረዳ ከሀምቢሶ ከተማ በ5 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው ኢስት ሲሚንቶ ፉብሪካ ሰራተኞች የሆኑ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ቻይናውያን፣ በሸኔ ታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸው ተጠቆመ። ራሱን “የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት” እያለ የሚጠራውና መንግስት “ሸኔ” ብሎ የሚ...
ዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ሽልማት በአዲስ አበባ ይካሄዳልዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ሽልማት ጉባዔ በአዲስ አበባ በሳይንስ ሙዚየም ከጥቅምት 14-16/2016 ይካሄዳል።በጉባዔው ከ300 በላይ አህጉርና አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ባለቤቶች ይወዳደራሉ። ጉባዔውን አስመልክተው የስራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።ሚኒስትሯ በመግለጫቸው ጉባዔው ከጥቅምት 14-...
የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID ) እና የአለም ምግብ ድርጅት (WFP)፤ በጦርነትና ሌሎች ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ምክንያት ከመኖሪያቸው ተሰደው በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ለተጠለሉ ስደተኞች የሚሰጡትን ሰብአዊ ርዳታ ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ መንግሥት ውጪ በሆኑ አካላት እንደሚያሰራጩ ተነገረ። ሁለቱ የእርዳታ ድርጅቶች የሚሰጡትን ሰብአዊ እርዳታ እስካለፈዉ ዓመት አጋማሽ ድረስ የሚያከፋፍለዉ...
ኬንያ በቅርቡ በወደብ ከተማዋ ላሙ ላይ ከተፈጸሙ ጥቃቶች ጀርባ እጁ አሉበት ያለችውን ጃንጋሌ ሁቴይባ የተሠኘውን ኢትዮጵያዊ እያደነች ነው ። የአልሸባብ አባል በመሆን ፈንጂዎች በተለያዩ የአገሪቱ መንገዶች ላይ በማጥመድ እና በላሙ-ዊቱ-ጋርሰን ጎዳና ላይ ሠላማዊ ሰዎችን በመግደል የሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ ከሚታደነው ኢትዮጵያዊ ሌላ 35 የተለያዩ አገራት ዜጎችም እየተፈለጉ ነው ።
የአገሪቱ መ...
“ጥያቄው አገሪቱ ከአጎራባቾቿ ጋር ያለትን የቆየ ቁርሾ እንደመቀስቀስ ይቆጠራል” ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ሰሞኑን ለጎረቤት ሀገራት ያቀረቡትን የወደብ ባለቤትነት ድርድር ጉዳዪ የሚመለከታቸው ሁሉም አገራት ውድቅ አደረጉት ። ኤርትራ ጅቡቲና ሱማሊያ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥያቄ እንደማይቀበሉ ይፋ አድርገዋል ። የወደብ ባ...
ካቻ የተሰኘ የዲጂታል ፋይናንሲንግ ሰርቪስ የግል ክፍያ ሰነድ አውጪ በመሆን አገልግሎቱን በይፋ አስጀምሯል። በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ነው የተባለው አገልግሎቱ ከብሔራዊ ባንክ የአገልግሎት ፈቃድ ያገኘ እና የሞባይል የገንዘብ ዝውውርና ሌሎች የፋይናንስ አገልግሎቶችን በተለያየ ደረጃና አማራጮች ያካተተ መሆኑ ታውቋል። ይህን ተከትሎ በካቻና በተለያዩ ባንኮች፣ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት እና ሌሎች ስትራቴ...
ሀበሻ ቪው 4ኛ ዙር የፊልም ፌስቲቫሉን በለንደን ከተማ ሊያካሂድ ነውሀበሻ ቪው 4ኛ ዙር የፊልም ፌስቲቫሉን በእንግሊዝ አገር ለንደን ከተማ በቅርቡ ሊያካሂድ ሲሆን፤ የቅድመ መክፈቻ ሥነሥርዓቱን ባለፈው ቅዳሜ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት በሃያት ሪጀንሲ ሆቴል አካሂዷል፡፡በዘንድሮው የለንደኑ የኢትዮጵያ ፊልም ፌስቲቫል ለዕይታ የተመረጡት “ጸጸት” እና “ዝምታዬ” የተሰኙት ሁለት የኢትዮጵያ ...
• በሃማስ ጥቃት የተገደሉ እስራኤላውያን ቁጥር 1300 የደረሰ ሲሆን፤ ከ3ሺ 300 በላይ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል፡፡• በእስራኤል የአየር ድብደባ የሞቱ ፍልስጤማውያን ቁጥር 1ሺ 500 የደረሰ ሲሆን፤ 5ሺ 600 ሰዎች ቆስለዋል፡፡ • በእስራኤልና ሃማስ ጦርነት 27 አሜሪካውያን ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፤ በሃማስ ከታገቱት ከ150 በላይ ሰዎች ውስጥ አሜሪካውያን ይገኙበታል፡፡• የእስራኤል የጦር ...
ግብፅና ደቡብ አፍሪካ የአሸማጋይነት ሚናን መርጠዋል፤ኢትዮጵያስ?ባለፈው ቅዳሜ መስከረም 26 ቀን 2016 ዓ.ም በአሜሪካና አጋሮቿ የሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ የተበየነው እስላማዊው የሃማስ ቡድን፣ በእስራኤል ላይ የፈፀመውን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ፣ በተቀሰቀሰው የእስራኤል-ሃማስ ጦርነት ዙሪያ የአፍሪካ መንግስታት የተለያዩ አቋሞችን አንፀባርቀዋል - አንዱን ደግፈው ሌላውን በማውገዝ፡፡ በእርግጥ ...
መንግስት የተመድ ባለሥልጣን መግለጫውን እንዲያስተባብሉ ጠይቋልበኢትዮጵያ አሁንም የዘር ማጥፋትና ተያያዥ አሰቃቂ ወንጀሎች ስጋት በከፍተኛ ሁኔታ መኖሩን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዘር ማጥፋት መከላከል ልዩ አማካሪ ዋይረሙ ንደሪቱ ገለፁ። አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን በኢትዮጵያ (ICHREE) ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርት፤ በኢትዮ...
“ሀዘኑ ሁሉም ቤት ስለገባ እርስ በርስ እንዳንፅናና አድርጎናል” ለሁለት ዓመታት በዘለቀው የሰሜኑ ጦርነት ከትግራይ ሃይሎች ጎን ተሰልፈው ሲዋጉ ህይወታቸውን ያጡ የቀድሞ ተዋጊዎች መርዶ ዛሬ በይፋ ይነገራል፡፡ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የመርዶ መንገሩን ሂደት ተከትሎ፣ ከዛሬ ጥቅምት 3 ቀን ጀምሮ እስከ ፊታችን ሰኞ ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የ3 ቀናት ሃዘን በክልሉ አውጇል፡፡በ...
* መገናኛ ብዙኃን ከችግር ፈጣሪነት ወጥተው ፖለቲካውን መምራት አለባቸው ተብሏል የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር፤ "Media Polarization; How Editorial Policy Counteracts Polarization in the News Media" በሚል ርዕስ፣ በመገናኛ ብዙኃን ዋልታ-ረገጥነት ዙሪያ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ሳምንታዊ የቁርስ ላይ ውይይቱን አካሄደ።የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖ...
በኢትዮጵያ በሰው ልጅ ላይ የሚፈጸሙ አስከፊ ወንጀሎች እየተባባሱ መቀጠላቸውና አገሪቱ በከፍተኛ ደረጃ አስጊ በሆነ የደኅንነት ስጋት ላይ እንደምትገኝ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ የባለሙያዎች ቡድን አስታወቀ። ቡድኑ ባወጣው አዲስ ሪፖርት፤ በተለይ በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያና በአፋር ክልሎች ያለው ሁኔታ በእጅጉ እንዳሰሰበው አመልክቷል። በተባበሩት መንግሥታት ድር...
- የአውሮፓ ህብረት፣ የመርማሪ ቡድኑ የሥራ ጊዜ እንዲራዘም የሚያስችል ረቂቅ ሃሳብ አለማቅረቡ ተኮንኗል በኢትዮጵያ የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን እንዲመረምር በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የተቋቋመው የባለሞያዎች ቡድን የምርመራ ጊዜ እንዲያራዝም በበርካታ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች በተደጋጋሚ ጥሪ ሲደረግ ቢቆይም፣ የመርማሪ ቡድኑ የስራ ጊዜ ሳይራዘም ቀርቷል...
በሰሜናዊው የአገሪቱ ክፍል በትግራይ ሀይሎችና በፌደራል መንግስቱ መካከል ተካሂዶ በነበረው ጦርነት ህይወታቸው ያለፉ ተዋጊዎችን ለመዘከር በትግራይ ክልል በጥቅምት ወር መጀመሪያ የሦስት ቀናት ሀዘን እንደሚታወጅ፣ የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ ጀኔራል ታደሠ ወረደ ሰሞኑን በክልሉ ለሚገኙ ጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። በክልሉ ለሶስት ቀናት ይደረጋል የተባለው ክልላዊ የሀዘን ...
ለስደተኞች ብቻ መስጠት ጀመረበኢትዮጵያ 20ሚ. ሰዎች እርዳታ ይፈልጋሉ ተብሏል በኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ሰብአዊ እርዳታዎችን በማቅረብ በቀዳሚነት የሚታወቀው የአሜሪካ ዓለማቀፍ ተራድዖ ድርጅት (ዩኤስአይዲ) ፤ ለተረጂዎች የታለመውን የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት ከታለመለት ዓላማ ውጪ ውሏል በማለት በመላ አገሪቱ ለወራት አቋርጦት የነበረውን የምግብ ዕርዳታ ለስደተኞች ብቻ መስጠት ጀመረ...
የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች ከሚያቀርቡ ታላላቅ የሞባይል አምራች ኩባንያዎች አንዱ የሆነው አይቴል ሞባይል፤ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸውን የተለያዩ የትምህርትና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ለሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበር አስረክቧል፡፡ አይቴል ሞባይል “ሁሌም ፍቅር” (Love Always) የሚል መርህ በማንገብ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የሚቀጥለውን ትውልድ በትምህርት...
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወዲህ በርካታ ግፎች በንፁሀን ላይ ተፈፅመዋል ተብሏልበኢትዮጵያ የጦር ወንጀሎችና በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ተባብሰው መቀጠላቸው ተገለፀ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀይል የተሞሉ ግጭቶች መበራከታቸውንና በተለይም በአማራና በትግራይ ክልሎች በንፁሃን ላይ የሚፈፀሙ ከፍተኛ በደሎች መኖራቸውም ተመልክቷል፡፡አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ኤክስፐርቶች በኢትዮጵያ (ICHREE) ለተ...
- ኢሰመኮ በክልሉ ገላን ከተማ ውስጥ በሚገኘው ጊዜያዊ የሰዎች ማቆያ ስፍራ በተላላፊ በሽታ ሰዎች እየሞቱ መሆናቸውን ገልጿል- የኦሮሚያ ክልል በበኩሉ በክልሉ ምንም አይነት የሰዎች ማቆያ ስፍራ የለም ብሏልበኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘው ጊዜያዊ የሰዎች ማቆያ ስፍራ ውስጥ በተቀሰቀሰ ተላላፊ በሽታ ሰዎች መሞታቸውንና ከ190 በላይ የሚሆኑ ደግሞ የህክምና ክትትል እየተደ...
ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የጦር ጉዳተኞች የሚገለገሉበት ማዕከል ተመርቆ ተከፍቷልበሁለት ዓመታቱ የሰሜኑ ጦርነት የሞቱ ታጋዮችን መርዶ ለቤተሰቦቻቸው ለመንገር ዝግጅት እየተደረገ ነው ተባለ። በጦርነቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጋዮች መሞታቸውና በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተገልጿል።የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በመቀሌ ከተማ የተገነባውንና በጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረ...
በጋምቤላ ክልል የባሮ ወንዝ ሞልቶ ባስከተለው ጎርፍ፣ በጋምቤላ ከተማና በዘጠኝ ወረዳዎች በርካታ ሰዎችን እንዳፈናቀለ፣ የክልሉ መንግሥት ባለፈው ማክሰኞ አስታውቋል፡፡ የጋምቤላ ከተማ ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የከንቲባው ተወካይ አቶ ሳይመን ቲያቺ፣ ባለፉት አራት ቀናት ውስጥ ስድስት ሺ የሚደርሱ ሰዎች ተፈናቅለው በትምህርት ቤቶችና በደረቃማ አካባቢ ላይ እንደሚገኙ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል።በደረሰ...
“ከፍተኛ ሙቀት፣ ድርቅና የጎርፍ አደጋ ዋነኛ ስጋቶቿ ናቸው” አዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የተፈጥሮ አደጋ ስጋት ያጠላባት ከተማ እንደሆነች ሰሞኑን ይፋ የተደረገ አንድ የጥናት ሪፖርት አመለከተ፡፡ ከፍተኛ ሙቀት፣ ድርቅና የጎርፍ አደጋ ዋነኛ የከተማዋ ስጋቶ ናቸው ተብሏል፡፡የውድ ዌል ክላይሜት ሪሰርች ሴንተርና የቱፍት ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በጋራ ባደረጉት ጥና...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ መስከረም 4 ቀን 2016ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን ሁኔታ የተመለከተ ዓመታዊ ባለ 29 ገጽ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የዘርፍ ሪፖርት፣ ኢሰመኮ ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔ...
- በክልሉ ከነሐሴ ጀምሮ የተወሰደው ኢንተርኔትን የማቋረጥ እርምጃ ዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ ነው ተብሏል - ባለፈው ዓመት ብቻ መንግስት በአገሪቱ ለ3 ጊዜያት ያህል ኢንተርኔት ማቋረጡም ተጠቁሟል፡፡ ከ105 አገራት የተውጣጡ ከ300 በላይ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፣ መንግስት በአማራ ክልል ላይ የጣለውን የኢንተርኔት እገዳ እንዲያነሳና በክልሉ የተቀሰቀሱ ግጭ...
ግብረሠዶማውያን ኢትዮጵያን እንጐበኛለን ማለታቸው ማህበረሰቡን ያስቆጣ ሲሆን የሀገሪቱ የሃይማኖት ተቋማት ግብረ ሰዶማውያን ኢትዮጵያን መርገጥ አይችሉም መንግስት ህግ ያስከብር አቋሙን ከወዲሁ ያሳውቅ ብለዋል፡፡ ጐብኚዎቹ ትኩረት ያደረጉበት የላሊበላ ቤተክርስቲያን አስተዳደር በበኩሉ በፈጣሪ ጽዩፍ የሆነውን ድርጊት ፈፃሚ ግብረሰዶማውያንን ተቀብሎ አላስተናግድም፤ ስለአካባቢው ለሚደርስባቸው ጉዳትም ከወ...
· “አቧራውን አልፈዋለሁ፤ አሻራዬን አኖራለሁ፤ ታሪኬንም እሠራለሁ” - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ · 56 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻዎች ማስዋብ - 29 ሚሊዮን ብር · የአድዋ ማዕከል የዋጋ ግምቱ ያልታወቀ · 3ሺ ሰው የሚይዝ ቤ/መፃህፍት - 1 ቢሊዮን ብር · የለገሃር የመኖሪያና ቢዝነስ ማዕከል -...
ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች አንድነታቸውንና ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ ያቀረቡት ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፤ የሃይማኖት አባቶች ለሠላም፣ ለፍቅርና ለእርቅ ተግተው እንዲሠሩ ጠይቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባልተለመደ መልኩ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን (አርክበ ካህናት) የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ መክፈቻ ላይ ሳይጠበቁ ድንገት መከሰታቸው ለፓትሪያሪኩና የሲኖዶሱ አባላት መደነቅን ፈ...
ሀገራቱ ለድርቅ ተጋላጭ ሆነዋል ተብሏል ኢትዮጵያን ጨምሮ በምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ከመጋቢት እስከ ሰኔ ባለው ጊዜ ውስጥ የሚጠበቀው ዝናብ አለመዝነቡ ከፍተኛ ሠብአዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት እንዳለው በተባበሩት መንግስታት የረሃብ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ተቋም አስታውቋል፡፡ በምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት፡- ኢትዮጵያ፣ ኡጋንዳ፣ ኬንያና ሶማሊያ፤ ከመጋቢት እስከ ሰኔ የሚፈለገው ለግብ...