በቅ/ሥላሴ ካቴድራል ሓላፊዎች ላይ የተላለፈው የቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ተፈጻሚ እንዲኾን ካህናትና ምእመናን ጠየቁ፤ ፓትርያርኩ በአቋማቸው እንደጸኑ ነው

በውሳኔው አፈጻጸም ላይ ቋሚ ሲኖዶሱ እና ፓትርያርኩ የተለያየ አቋም ይዘዋል፤ አጣሪ ኮሚቴ በሀገረ ስብከቱ ቢመደብም የአባላቱ መቀያየር ጥርጣሬ አስነሥቷል፤ “የዘር ጥቃት ነው” በሚል ለማዳፈን የሚደረገው ምክር በጥንቃቄ ሊታይ ይገባል፤ ከምእመናን አንዱ በፖሊስ ተወስዶና ታስሮ ቢውልም፣ በአባቶች ጥያቄ ተፈቷል፤ የፓትርያርክ አቡነ ማትያስ 7ኛ ዓመት በዓለ ሢመት እሑድ በካቴድራሉ ይከበራል፤ “ሁከት ፈጣሪ በሚል እንድንታሰር ስማችንን ለፖሊስ አስተላልፈዋል፤”/ምእመናኑ/ …