በኢትዮጵያ ካሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ “ከፍተኛ” የሚባለውን ደረጃ ያሟሉ፤ አራት ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

በኢትዮጵያ ካሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ “ከፍተኛ” የሚባለውን ደረጃ ያሟሉ፤ አራት ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ካሉ 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተፈላጊውን “ከፍተኛ ደረጃ” የሚያሟሉት አራቱ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ወላጆች፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና መምህራንን የሚያሳትፍ፤ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ያለመ ሀገር አቀፍ የትምህርት ዘመቻ በአንድ ወር ተኩል ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።

የትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 15፤ 2015 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው። ሪፖርቱን ለፓርላማ አባላት ያቀረቡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአጽንኦት ካነሷቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ፤ የትምህርት ቤቶችን ጥራት የሚመለከት ነው።

እርሳቸው የሚመሩት መስሪያ ቤት በሀገሪቱ አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ባሉ 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ግምገማ ማድረጉን የተናገሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ በተገኘው ውጤት ላይ ተመስርቶ ትምህርት ቤቶቹ በአራት ደረጃዎች እንደተመደቡ ገልጸዋል። ግምገማው የተደረገው፤ ትምህርት ቤቶች በሚጠቀሟቸው ግብዓቶች፣ በመማር ማስተማር ሂደቶቻቸው እንዲሁም ተማሪዎቻቸው በሚያስመዘግቧቸው ውጤቶች ላይ እንደነበር አመልክተዋል።

ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11020/