ቋሚ ሲኖዶስ: በአ/አበባ የፓትርያርኩ ረዳት ጳጳስንና ሥራ አስኪያጁን ጨምሮ 3 ሓላፊዎችን አነሣ፤ በሒሳብና በጀት ሓላፊውና በኮሌጁ ጉዳይ እየተነጋገረ ነው

ቋሚ ሲኖዶሱ፣ ዛሬ ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 23 ቀን 2011 ዓ.ም. ሲያካሒድ በዋለው መደበኛ ስብሰባው፥ብልሹ አሠራርንና ምዝበራን እንዲያስወግዱና ሀገረ ስብከቱን አረጋግተው እንዲመሩ የተሰጣቸውን ሓላፊነት መወጣት አልቻሉም ያላቸው፦ ረዳቱ ብፁዕ አቡነ አረጋዊ፣ ሥራ አስኪያጁ መ/ር ይቅርባይ እንዳለ እና የሰው ኃይል አስተዳደር ዋና ሓላፊው መጋቤ ጥበባት ሲያምር ተክለ ማርያም እንዲነሡ ወስኗል፡፡ *** ለመንበረ ፓትርያርኩ እና ለመንግሥት፣ ለሳምንታት አቤቱታ ሲቀርብ …