በፓትርያርኩ መመሪያ: የገርጂ ጊዮርጊሱ ዘራፊ ጽጌ ከበረ ወደ ደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት ተዛወረ፤ የተሐድሶው ቃል አቀባይ ግርማይ ሓዲስ የሀ/ስብከቱ ሒሳብና በጀት ሓላፊ ኾነ

ጎሠኝነትን የሚከተለውና የሕግ ተጠያቂነትን፣ ሃይማኖተኝነትንና ሞያዊነትን ሰለባ ያደረገው ምደባ፣ የሀገረ ስብከቱን ዕጣ ፈንታ ለስጋት ዳርጎታል፤ ትላንት ወደ ቁልቢ የተጓዙት ፓትርያርኩ በሌሉበት፣ ዛሬ ተሰብስበው በጉዳዩ የመከሩበት የቋሚ ሲኖዶስ አባላት፣ ሲመለሱ ሊሞግቷቸው ወስነዋል፤ ******** ‘ሊቀ ማእምራን’ ጽጌ ከበረ 104ሺሕ152 ካሬ ሜትር ይዞታውን በካሬ 7 ብር ከ3 እስከ 9 ዓመት እያከራየ መዝብሯል፤ ለመናፍቃን አሳልፎ ሰጥቷል፤ በርካታ እናቶችንና እኅቶችን …