ጠ/ሚ ዐቢይ ከትናንት ጀምሮ በግንባር አመራር እየሰጡ ነው

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከትላንት ጀምሮ ወደ ግንባር በመዝመት እዛው ሆነው አመራር እየሰጡ መሆኑን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫ እየሰጡ ነው።
ዶ/ር ለገሰ ፥ ” ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ከትናንትና ጀምሮ በግንባር አመራር እየሰጡ ነው ” ብለዋል። ሌሎችም አመራሮች የህልውና ዘመቻውን በመቀላቀል ወደ ግንባር መዝመታቸውን አሳውቀዋል።
መደበኛ ሥራዎች እንዳይስተጓጎሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን እየተመራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መዝመታቸው በርካቶችን ያነቃቃና በርካቶች እንዲከተሏቸው አድርጓል ሲሉም ዶ/ር ለገሰ እየሰጡት ባለው መግለጫ ተናግረዋል።
May be an image of 1 person and outdoors

May be an image of car, road, sky and tree