የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት የዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ

የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት በዛሬው መግለጫ ምን አለ ? (ሙሉ ቪዲዮ ከታች ያገኙታል)

የትግራይ መልሶ ማቋቃም ጤና ዘርፍ :

ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከተናገሩት ፦

– 52 ከመቶ ሆስፒታሎች መደበኛ ስራ ጀምረዋል።

– ባለፈው ሳምንት ከነበረው ሪፖርት አኳያ አሁን ላይ በክልሉ 55 ከመቶ ሆስፒታሎች እና 52 ከመቶ የጤና ማዕከላት ስራ ጀምረዋል።

– አገልግሎት በተጀመረባቸው የጤና ፋሲሊዎች 85 ከመቶ በላይ የጤና ባለሞያዎች የእለት ተለት ስራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ።

– በተቀሩ የጤና ተቋማት ላይ የደረሰው ጉዳት ተገምግሟል። የፌዴራል መንግስት ባቀረበው በጀት በ14 ሆስፒታሎች እና 58 የጤና ማዕከላት አገልግሎት እንዲጀመር ይደረጋል።

– ለ40 የጤና ማዕከላት ኪትስ ተልኳል።

– የጤና ቁሳቁስ ከተላከባቸው አካባቢዎች መካከል መቀሌ፤ ኩይሃ ፤አቢ አዲ፤እና ሽሬ ይገኙበታል።

– የክልሉን የጤና አገልግሎት ለማስጀመር እስካሁን 310.8 ሚሊዮን በላይ የሚያወጣ መድሃኒት እና የህክምና መሳሪያ ወደ ክልሉ ተልኳል።

– የትግራይ ክልል ጤና መልሶ መቋቋም እንቅስቃሴ ምላሽ በማገዝ ሂደት የጤና ሚኒስቴርም ከአጋር አካላት ጋር በመሆን 215 በላይ ሚሊዮን ብር የሚገመት ገንዘብ ለክልሉ ተላልፏል።

– የጤና አገልግሎት ባልተጀመረባቸው አካባቢዎች ተንቀሳቃሽ ቡድኖችን በመጠቀም ህብረተሰቡን ተደራሽ የማድረግ ስራ በመከናወን ላይ ነው።

ሰብዓዊ ድጋፍ በተመለከተ :

የብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ ከተናገሩት ፦

– ከ5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ወይም 135 ሚሊዮን ዶላር በላይ ግምት ያለው ምግብ ሸቀጥ ተሰራጭቷል።

– በመጀመሪያ ዙር 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሰዎች ተጠቃሚ ተደርገዋል። በሁለተኛና በሶስተኛ ዙር 5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሰዎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።

– 170 ሺህ 798 ሜትሪክ ቶን ምግብ ቀርቧል። ለዚህም ከ5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል።

– በ1ኛና በ2ኛ ዙር የተሰራጨው የሰብዓዊ ድጋፍ ወጪ 70 በመቶ በመንግስት እንዲሁም ቀሪው 30 በመቶ በአጋሮች የተሸፈነ ነው። በ3ኛ ዙር ድጋፍ መንግስትን ጨምሮ 6 አካላት ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ።

– የዓለም የምግብ ፕሮግራም፣ ወርልድ ቪዥን፣ ኬር ኢንተርናሽናል፣ የትግራይ መልሶ ማቋቋም ድርጅት እና ፉድ ፎር ሀንግሪ በክልሉ የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎች ላይ እየሰሩ ነው።

– መንግስት እየተደረገ ያለውን ድጋፍ እየተቆጣጠረ እንደሚገኝ ገልጸው፤ የእርዳታ አሰጣጥ ሂደቱ እንዲሳካ ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ ነው።

ምንጭ፦ ኢዜአ