ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስን በመንበረ ፓትርያርኩ ማረፊያቸው ጠየቁ፤ የዕርቀ ሰላሙ ብሥራት በክልል ከተሞች እንዲቀጥል አደራ አሉ

ቅዱስነታቸው፣ ከአሜሪካ የመልስ ጉዞ ወቅት፥“ትጠይቀኛለኽ ወይ? ሥራ ይበዛብሃል፤ ማን ይጠይቀኛል አኹን? እንዴት ትጠይቀኛለህ?” ሲሉ ጠ/ሚኒስትሩን ጠይቀዋቸው ነበር፤ ቅዱስነታቸው፥ ከመናገር አብዝተው ሲታቀቡ ቢስተዋልም ይነጋገራሉ፤ ከቅርብ ልዩ አገልጋይ(ረዳት) ጀምሮ በግል ሐኪምና ነርስ ክትትል ይደረግላቸዋል፤ እንደሚጠይቋቸው ቃል የገቡላቸው ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ዛሬ ከቀትር በኋላ በመንበረ ፓትርያርኩ ማረፊያቸው ተገኝተው አይተዋቸዋል፤ ቤተ ክርስቲያን፥ ለአገር የመጸለይና የማስታረቅ ሓላፊነቷን እንድትወጣ፤ በሰላም፣ በልማትና በማኅበራዊ …