የኮሮናቫይረስ መዛመት መባባሱን የዓለም የጤና ድርጅት ጠቆመ

በዓለም ዙሪያ የኮቪድ-19 ተጋላጮች ቁጥር ከሃምሳ አምስት ሚሊዮን ባለፈበት እና ታመው ለህልፈት የተዳረጉት ከአንድ ነጥብ ሦስት ሚሊዮን በሆነበት ባሁኑ ወቅት የቫይረሱን መዛመት መቆጣጠሩን ቸል የሚሉ ሃገሮች በእሳት እየተጫወቱ ነው ሲሉ የዓለምቀፍ የጤና ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖም አሳሰቡ።

ዶ/ር ቴድሮስ ትናንት በጄንኔቫ የድርጅቱ ዋና ጽህፈት ቤት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግ…