የሃይማኖት መሪዎችና የአገር ሽማግሌዎች መቐለ በዝግ እየመከሩ ነው – መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

DW : የሃይማኖት መሪዎችና የአገር ሽማግሌዎች መቐለ በዝግ እየመከሩ ነው

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤና የሀገር ሽማግሌዎች በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥትና ትግራይ ክልል መንግስት መካከል ያለው መልካም ያልኾነ ግንኙነት በንግግር እንዲፈታ ጥረት ለማድረግ ዛሬ መቐለ ገብተው በዝግ እየመከሩ ነው፡፡

የኢትዮጵያ የተለያዩ ሃይማኖት ተቋማት መሪዎችና ታዋቂ ግለሰቦችን ያካተተው ይኽ ቡድን ዛሬ ጠዋት መቐለ ደርሶ በአኹኑ ወቅት ከትግራይ ክልል መንግስትና ህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዝግ እየመከረ ነው።

ከሽማግሌዎቹና የትግራይ ክልል መንግስት አመራሮች ውይይት በኋላ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።