በአዳማ ከተማ አንድ ግለሰብ በኮሮና ቫይረስ መያዙ ተገለጸ

በአዳማ ከተማ አንድ ግለሰብ በኮሮና ቫይረስ መያዙ ተገለጸ
በኦሮሚያ ክልል የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ኃይል በአዳማ ከተማ በቫይረሱ የተያዘ አንድ ግለሰብ መገኘቱን ገልጿል።
ግብረ ኃይሉ ዛሬ በሰጠው መግለጫ፣ ከግለሰቡ ጋር ግንኙነት የነበራቸው 24 ሰዎች በለይቶ ማቆያ ስፍራ ተነጥለው እንዲቆዩ መደረጉንም አስታውቋል።
የቫይረሱን ስርጭት በክልል ደረጃ ለመከላከል የተቋቋመው ይህ ግብረ ኃይል የቫይረሱን ስርጭትን ለመከላከል በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።