ኤርትራውያን ስደተኞች በድንበር በኩል ምዝገባ ተከልክለናል አሉ

ሠሞኑን በድንበር አካባቢ የተሰማውና ተግባራዊ እየሆነ ያለው የኤርትራ ስደተኞችን ያለመመዝገብ ሂደት ቢቢሲ ያነጋገራቸው ስደተኞችን አስጨንቋል።