በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ረብሻ ለማስነሳት የሞከሩ 27 ተማሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

Image may contain: 1 person, smiling, standing and hat

ዛሬ ከሰዐት በኃላ ከአ.አ ዩኒቨርስቲ 6 ኪሎ ካምፓስ በየመግለጫዉ የማይጠፋ ኦብሳ የተባለ ነውጠኛ የጃዋር ቄሮ በግቢው ውስጥ ነውጥ ለማስነሳት ሲንቀሳቀስ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውሎ ከግቢዉ አንጠልጥለዉ ወስደዉታል፡፡ 27 ሰዎች ታስረዋል።

የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት/ባልደራስ በተደጋጋሚ ጊዜ የጠራቸውን ጋዜጣዊ መግለጫ እና ስብሰባዎችን ሲረብሽ የነበረው ወጣት ኦብሳ በዛሬው ዕለት መታሰሩ ተገልጿል።

ኦብሳ የተባለው ይህ ወጣት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ግቢ ተማሪ ሲሆን በዛሬው ዕለት የታሰረው አመንቴ ከሚባለው ጓደኛው ጋር አብሮ በመሆን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ረብሻ ለማስነሳት ሲሞክር መሆኑን የመረጃ ምንጮች አስረድተዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 6 ኪሎ ግቢ ከጠዋት ጀምሮ የፀጥታ ችግር መኖሩ ተማሪዎችም ስጋት ላይ በመሆን ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ ሆነው መዋላቸውና በኃላም እንደተረጋጋ በማህበራዊ ሚዲያ ሲሰራጭ መዋሉ ይታወሳል።

Image may contain: one or more people, people walking, people standing and outdoor