በብሄራቸው ምክንያት ስለታሰሩ የትግራይ ተወላጆች የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ ለዓለምቀፍ ማኅበረሰብ የሚቀርብ ፊርማ እየተሰበሰበ ነው

VOA : ዓለምቀፍ የትግራይ ተወላጆች ንቅናቄ ለፖለቲካ እስረኞች ተብሎ የተቋቋመ እንቅስቃሴ ለዓለምቀፍ ማኅበረሰብ የሚቀርብ ፊርማ እያሰባሰበ መሆኑ አስታወቀ፡፡

እንቅስቃሴው ከ20 ሺ በላይ ፊርማ በማሰባሰብ “በብሄራቸው ምክንያት ስለታሰሩ የትግራይ ተወላጆች የፖለቲካ እስረኞች” ያለውን ጉዳይ ለተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እንደሚያቀርብ አስታውቋል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤሕግ በበኩሉ በፖለቲካና ብሄር ምክንያት ክስ የተመሰረተበት የትግራይ ተወላጅ የለም ብለዋል፡፡

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።