Blog Archives
ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በዶይቼ ቬለ ዘጠኝ ዘጋቢዎች ላይ የጣለውን ጊዜያዊ እገዳ ባስቸኳይ እንዲያነሳ ትናንት ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። ፌዴሬሽኑ፣ ውሳኔው ጣቢያውን “ዝም ለማሠኘት” እና “በአማራ ክልል ስለሚካሄደው ግጭት ኢትዮጵያዊያን ገለልተኛ መረጃ እንዳያገኙ ለመገደብ” ያለመ ነው በማለት ተችቷል። ዶይቼ ቬለ፣ ባለሥልጣኑ የእገዳውን ምክንያት በዝርዝር ማስረጃ እንዲያስደግፍ እና ጊዜያዊውን እገዳ እንዲነሳ ከቀናት በፊት መጠየቁ ይታወሳል።
መኢአድን፣ እናት ፓርቲንና ኢሕአፓን ጨምሮ አምስት ፓርቲዎች የመሠረቱት ጥምረት፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄዱ “ማንነት” እና ኃይማኖት-ተኮር” ጥቃቶች መንግሥታዊ መዋቅሮችን የተከተሉ ስለመኾናቸው ምርመራ እንዲያደርግ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጥሪ አድርጓል። በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን በሚገኙ ወረዳዎች ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በንጹሃን ላይ የተፈጸሙ ግድያዎችን ያወገዘው ጥምረቱ፣ የኃይማኖት አባቶች የጅምላ ግድያዎች እንዲቆሙ በመንግሥትና ዓለማቀፉ ማኅበረሰብ ላይ ጫና እንዲፈጥሩ ጠይቋል። ጥምረቱ፣ ጥቃቶች እንዲፈጸሙ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ኾነው ይሠራሉ ላላቸው ባለሥልጣናት፣ ጥቃቶችን “በቸልታ” ያልፋሉ ላላቸው የጸጥታ አካላት እንዲኹም ጥቃቶችን አይዘግቡም ላላቸው የመንግሥት መገናኛ ብዙኀን ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ ወደፊት ከተጠያቂነት አታመልጡም የሚል መልዕክት በዚኹ መግለጫው ላይ አስተላልፏል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሲቪል ሠርቪስ ቢሮ፣ መንግሥት ከመስከረም ጀምሮ ለኹሉም መንግሥት ሠራተኞች በፈቀደው የደመወዝ ማሻሻያ መሠረት ገንዘብ ሚንስቴር የፈቀደው የ10 ወር የደመወዝ በጀት ከክልሉ ሠራተኞች ቁጥር አንጻር ሲታይ በቂ እንዳልኾነ አስታውቋል። ቢሮው፣ በክልሉ ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ በጀት ላይ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ጉድለት እንደተፈጠረ ገልጧል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ቤንሻንጉል ጉሙዝን ጨምሮ በብዙ ክልሎች የመረጃ ክፍተት የተፈጠረው በክልሎች ወይስ በፌደራል ደረጃ ስለመኾኑ ተጣርቶ ለውሳኔ እንዲቀርብ በቅርቡ መመሪያ መስጠታቸውን የጠቀሠው ቢሮው፣ የክልሉ የፋይናንስ ቢሮም ይህንኑ የማጣራት ሥራ ጀምሯል ብሏል። ይሄው የማጣራት ሥራ ተጠናቆ መንግሥት ውሳኔ እስኪሠጥ ድረስ፣ ሠራተኞች በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ለሚናፈሱ “አሉባልታዎች” ጆሮ እንዳይሠጡ አሳስቧል።
ኤርትራ፣ የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት ለመግታት የመከላከያ ኃይሏን በማጠናከርና ቀጠናዊ ተጽዕኖዎችን በመፍጠር ላይ መኾኗን የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚንስቴር ዛሬ ለኤርትራ ሕዝብ በትግሬኛ ባሠራጨው ጽሁፍ ላይ አስታውቋል። ተጽዕኖ ፈጣሪ አገራትና ዓለማቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያን አካሄድ እንዲያወግዙና ኢትዮጵያ ቀጠናዊ ግጭት ከመቀስቀስ እንድትቆጠብ ግፊት እንዲያደርጉ የጠየቀው ሚንስቴሩ፣ ኤርትራ ከቀይ ባሕር አዋሳኝ አገራት ጋር የኹለትዮሽ ትብብሯን ለማጠናከር ጥረት እያደረገች መኾኗን ገልጧል። ሚንስቴሩ፣ ኤርትራ ለኢትዮጵያ የባሕር በር አልባነት ተጠያቂ እንዳልኾነች ኹሉ የኢትዮጵያን የባሕር በር ሕልም እውን የማድረግ ግዴታም የለባትም ብሏል። የኢትዮጵያ መንግሥት ኢትዮጵያ “የጅዖፖለቲካ በደል” እንደተፈጸመባትና የችግሮቿ ምንጭ “የባሕር በር አልባነት” እንደኾነ በመስበክ፣ ሕዝቡ “በቁጭት እንዲነሳሳ” በመቀስቀስ ላይ ነው በማለትም ሚንስቴሩ ወቅሷል።

ግብፅ የኤርትራን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በፅኑ ትደግፋለች – አል ሲሲ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መንግሥት “የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት እንዲያረጋግጥ” ጠየቀች
ሕወሃት፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላይ ባደረጉት ንግግር የትግራዩ ጦርነት የሁለት ወራት ጦርነት ነበር በማለት፣ በትግራይ ላይ ላለፉት አምስት ዓመታት የቀጠለውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ አቅልለው ለማቅረብ ሞክረዋል በማለት ከሷል። ሕወሃት፣ የዐቢይ ንግግር በትግራይ ሕዝብ ሞት እና ስቃይ ምን ያህል እያፌዙ እንደሆነ እና ለቀድሞ ጥፋታቸው ንስሃ እንደማይገቡ ያሳያል በማለት ተችቷል። የግጭት ማቆም ስምምነቱ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አሁን አደጋ ላይ መውደቁን ዓለማቀፉ ማኅበረሰብ ማወቅ አለበት ያለው ሕወሃት፣ የአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪ አካል ኹኔታውን ለመገምገም አስቸኳይ ስብሰባ እንዲቀመጥ ጠይቋል።
የተቃውሞ ትችት ኃላፊነትን መወጣት እንጂ ባንዳነት አይሆንም!ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ በፓርላማ ያቀረብኳቸው ጥያቄዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ሕይወት የሚመለከቱ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ናቸው። እኔ እንደ ሕዝብ ተወካይና ተቃዋሚ ፖለቲከኛነቴ፣ የመንግሥትን ሥራ መተቸትና ለሕዝብ ጥቅም መቆም ስራየም፣ ግዴታዬም ጭምር ነው።የምመራባቸው ብቸኛ መርሆዎች የአማራ ሕዝብ ህልውናና የኢትዮጵያ ዘላቂ ብሔራዊ ጥቅሞች ናቸው። ከዚህ በመነሳት ማክሰኞ ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረብኳቸው ጥያቄዎች ላይ የገዢው ፓርቲ የማህበራዊ ሚዲያ ሰራዊት እና ወዶ ገብ መሸጦ “ተቃዋሚዎች” ላቀረቡት ሦስት ክሶች ግልጽ ምላሽ እሰጣለሁ። ይሄን የማደርገው የተነሱት ክሶች ክብደት ምላሽ የሚገባቸው በመሆናቸው ሳይሆን አጋጣሚውን በመጠቀም ባቀረብኋቸው በርካታ የፖሊሲና የትግበራ ጉዳዮች ላይ የበለጠ ግንዛቤ እንዲፈጠር ውይይት እንዲካሄድባቸው ምልከታዎቼን በተብራራ ሁኔታ ለማጋራት ነው።ክስ አንድ፦ የአስመራ መንግሥት ወኪል፣ አገልጋይና ባንዳ ነህይህ ክስ መሰረተ-ቢስ፣ ተራ ስም ማጥፋት ነው። የፖለቲካ ትችትን በባንዳነትና በክህደት ስም ለመምታት የሚደረግ አሳፋሪ ሙከራም ነው። የቤተሰቤ ታሪክ የጀግንነት ታሪክ፣ በላብና በጥረት ሰርቶ የማደር እንጂ በመሸጦነት እና በባንዳነት የማደር አንዳችም ነገር የለበትም። አባቴ ወታደር ጫኔ ዳኜው በዘውዳዊ ስርዓቱ፣ ወንድሜ መቶ አለቃ አያሌው ጫኔ (የሀረር ጦር ት/ቤት ምሩቅ እና የነብሮ ክፍለ ጦር መኮንን) በወታደራዊ ደርግ ዘመን፣ እንዲሁም ሌላው ወንድሜ ተስፋሚካኤል ጫኔ (የሁርሶ ወታደራዊ ት/ቤት አሠልጣኝ) በኢሕአዴግ ዘመን፣ ሶስቱም ኢትዮጵያን በከፍተኛ ጀግንነት እና ብቃት ያገለገሉ ወታደሮች ናቸው። ቅድመ አያቶቼም በሁለቱም በኩል እነ ቀኛዝማች ደስታ ብሩ እና ብላታ ጥሩነህ ኪዳኑ እንደአብዛኛው የጎጃም፣ አማራ ገበሬ

፡
ለዝርዝሩ ይህን ይጫኑ ፡ በአርሲው ጥቃት እናት እና ሦስት ልጆችን ጨምሮ ስምንት ሰዎች የተገደሉበት ቤተሰብ
ከ 30 ደቂቃዎች በፊ

ተጨማሪ ለማንበብ ፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ንግግር “ቅዠት” ያለችው ኤርትራ መሪዋ ወደ ግብፅ አቀኑ

ለዝርዝሩ ይህን ይጫኑ ፡ የአማራ ክልል ግጭት፡ “ልጆቼ እንደ እኔ ሳይማሩ እንዳይቀሩ ነበር ስታገል የነበረው፤ መላም የለው”

በፆታዊ ትንኮሳ ተፈርዶበት ከዩኬ ወደ ኢትዮጵያ የተባረረውን ግለሰብ መልቀቁን ፌደራል ፖሊስ ገለጸ
የኤርትራ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግብፅን ለ5 ቀናት ለመጎብኘት ዛሬ ከአስመራ ወደ ካይሮ ተጉዘዋል። የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረመስቀል በX ገፃቸዉ ዛሬ (ሐሙስ ጥቅምት 20 ቀን፣ 2018 ዓ.ም) እንደዘገቡት ፕሬዝደንት ኢሳያስ ግብፅን የሚጎበኙት የግብፅ ፕሬዝደንት አብዱልፈታሕ አል ሲሲ ባደረጉላቸዉ ግብዣ ነዉ። ሁለቱ መሪዎች የሁለቱን ሐገራት ግንኙነት ይበልጥ «ለማጠናከርና ለሁለቱ ሐገራት በሚጠቅሙ አካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች» ላይ ይወያያሉ ተብሏል። ፕሬዝደንት ኢሳያስ በቅርቡ የተገነባዉ የግብፅ ታላቅ ቤተ-መዘክር (ሙዚየም) በመጪዉ ቅዳሜ በሚመረቅበት ድግስ ላይም ይገኛሉ ተብሏል። የሁለቱ ሐገራት መሪዎች «በጋራና አካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ» ይነጋገራሉ የተባለዉ ሁለቱም መንግሥታት ይሳተፉበታል የሚባለዉ የሱዳን ጦርነት በናረበት ወቅት መሆኑ ነዉ። በግብፅ፣ በኤርትራና በሌሎችም የአካባቢዉ ሐገራት ይደገፋል የሚባለዉ የሱዳን መከላከያ ኃይል፣ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ይደገፋል በሚባለዉ በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር (RSF) ጠላቱ ባለፈዉ ሳምንት ማብቂያ ዳርፉር ዉስጥ ሽንፈት ገጥሞታል።
ከዚህም በተጨማሪ የፕሬዚደንቱ ጉብኝት ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ ሰበብ ከግብፅ፣ በወደብ ጉዳይ ደግሞ ከኤርትራ ጋር የገጠመችዉ እሰጥ አገባ ባየለበት ወቅትም ነዉ። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ባለፈዉ ማክሰኞ ከሐገሪቱ ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት መልስና ማብራሪያ ለኢትዮጵያ “የቀይ ባሕር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው” ብለዋል።
ባለፈዉ መጋቢት የግብፅ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር በድር አብድላትይ ከፕሬዝደንት አብዱልፈታሕ አል ሲሲ የተላከ መልዕክት ለፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈርቂ ለማድረስ በሚል አስመራን ጎብኝተዉ ነበር። ጉብኝቱና መልዕክቱ በግብፅ፣ በኤርትራና በሶማሊያ መካከል «የአካባቢዉን ሠላም የማጠናከር የትብብር

” ታዳጊዎቹ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ነው ሞተው የተገኙት። ፖሊስ ምርመራ እያደረገ ነው ” – በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያዊያን ተወካይ
ነዋሪነታቸዉን በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ ያደረጉ ዲቦራ መንግስቴ እና ኦፕራ መንግስቴ የተባሉ ሁለት እህታማማቾች በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ሞተው መገኘታቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያዊያን ማህበረሰብ ተወካይ ኮሚቴዎች መካከል አቶ ዓለማየሁ ቲጁማ አሳውቀዋል።
በሁለቱ እህትማማቾች አሟሟት ዙሪያ ፖሊስ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ያነሱት አቶ ዓለማየሁ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ” በካምፓስ /ዩኒቨርሲቲ/ውስጥ ሞተው ተገኙ ” በሚል የተሰራጩ መረጃዎች የተሳሳቱና ከእውነታዉ የራቁ ናቸው ብለዋል።
አስክሬናቸው በደቡብ አፍሪካ ሕዝባዊ ሽኝት ተደርጎ ነገ ዐርብ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚላክም ገልፀዋል።
መሠረት ሚድያ)- በአርሲ ሀገረ ስብከት ውስጥ ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ ብቻ በታጣቂዎች በተፈፀሙ ሶስት የተለያዩ ጥቃቶች 22 ሰዎች መገደላቸው ታውቋል።
ማኀበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዛሬ እንደዘገበው በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሌ ዋቤ ወረዳ በቀቅሳ ቀበሌ ትናንት ጥቅምት 18 ለ19 አጥቢያ ከምሽቱ 4፡00 ላይ አምስት ምእመናን በታጣቂዎች መገደላቸው በአካባቢው ያሉ ምእመናንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

የጥቃቱ ሰለባ ከሆኑት መካከል የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ሁለት ወንድማማቾች እና ሁለት እህትማማቾች የሚገኙ ሲሆን በተጨማሪም አንድ የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታይ ከቤተሰቡ አባላት ጋር መገደሉ ታውቋል።
ከዚህም በተጨማሪ በወረዳው በሚገኘው በቀቅሳ ቀበሌ የእግዚአብሄር አብ ቤተክርስቲያን አገልጋይ ታግተው መወሰዳቸው ታውቋል። በአካባቢው የሚኖሩ ምዕመናን በአሁኑ ሰዓት የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ይገኛሉ።

በተመሳሳይ ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከለሊቱ 4 ሰዓት አካባቢ በምሥራቅ አርሲ ሽርካ ወረዳ ሄላ ዘባባ ቀበሌ አርሴማ አጥቢያ የሚኖሩ ምእመናን በታጠቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ ሦስቱ መገደላቸው እና አራቱ ደግሞ መታገታቸው ተገልጿል።
ከተገደሉት ምእመናን ውስጥ የአንዱ ሟች አባትና ወንድም መታገታቸው በመረጃው የተገለጸ ሲሆን ታፍነው የተወሰዱት ምእመናን ስለሚገኙበት ሁኔታ አይታወቅም ተብሏል፡፡
በመረጃው እንደተነገረው የሞቱት ሦስቱ ግለሰቦች ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል፡፡
በሶስተኛነት በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ 14 ምዕመናን ከለሊቱ 6 ሰዓት አካባቢ በዕለተ ረቡዕ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ለ14 አጥቢያ ከተኙበት ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሲሆን ስድስቱ
ኢትዮጵያ በሕግ የበላይነት ምዘና ከ143 የዓለም አገራት 132ኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች። ከ34 የአፍሪካ አገራት መካከል ደሞ ኢትዮጵያ አራት አገራትን ብቻ በመብለጥ 30ኛ ደረጃ አግኝታለች። ዓለማቀፉ የፍትሕ ፕሮጀክት ባወጣው ሪፖርት፣ በተያዘው የአውሮፓዊያን ዓመት የኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት ደረጃ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ2 ነጥብ 4 በመቶ ቀንሷል ብሏል። ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው 16 አገራት መካከል ደሞ፣ ኢትዮጵያ 13ኛ ደረጃ ነው ያገኘችው። በአገሪቱ ለ5 ተከታታይ ዓመታት ተቋማት እየተዳከሙ፣ የሲቪክ ምኅዳሩ እየጠበበና የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እየጨመረ መሄዱንም ሪፖርቱ ጠቅሷል። ኢትዮጵያ፣ በተለይ ሃሳብን በነጻነት በመግለጽ፣ በመሰብሰብ ነጻነት እና በሲቪክ ተሳትፎ መስኮች እጅግ ዝቅተኛውን ውጤት አስመዝግባለች።
አገዛዙ በአዲስ አበባ ከተማ የወጣቶችን አፈሳ አጠናክሮ ቀጥሏል ሲሉ ኗሪዎች ተናገሩ።
ዛሬ ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም በአዲስአበባ ከተማ በርካታ ወጣቶች ታፍሰዉ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መወሰዳቸዉ ታዉቋል።
በ11 ክፍለከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ታፍሰዉ በሶስት መሰረታዊ ዉትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መወሰዳቸዉን ከአዲስአበባ ከተማ ኗሪዎች ተናግረዋል።
በተለይ እድሚያቸው ከ18 አመት በታች የሆኑ ታዳጊ ወጣቶች ከቤተሰቦቻቸው ተነጥለዉ ስለመወሰዳቸዉ ጭምር ኗሪዎች ተናግረዋል።
አፈሳው በናዝሬት፣በደብረዘይት፣በሞጆ፣በሀዋሳ፣በይርጋለም፣በኦሮሚያ ክልል በሁሉም አካባቢዎች እንዲሁም በጋሞ እና ወላይታ ብዛት ያላቸዉ ወጣቶች ታፍስዉ በእየ አዳራሹ ታጉረዉ ይገኛሉ።
በተለይ በኦሮሚያ ክልል የሚታፈሱ ወጣቶች ቁጥር ከወትሮው በተለየ መልኩ መጨመሩ የተገለፀ ሲሆን የብልግና ኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ የኦሮሞን ስልጣን እንጠብቅ እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነትን ሊያጠፉ ነዉ በሚል ስብከት ወጣቱ እየታፈሰ ነዉ ተብሏል።
በአርሲ ሀገረ ስብከት በኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
EOTCMK TV …. በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን መገዳላቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያሳያል።
በደረሰን መረጃ መሠረት በቀበሌው የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን ከለሊቱ 6:00 ሰዓት አካባቢ በዕለተ ረቡዕ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ለ14 አጥቢያ ከተኙበት ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉ ሲሆን ስድስቱ ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፈት ቀድመው ታፍነው ተወስደው ነበር ተብሏል።
የተገደሉት ምእመናን የዕድሜ ክልላቸው ከ2 ዓመት ጀምሮ እስከ 76 ዓመት አዛውንት እንደሚገኙበት መረጃው ይገልጻል።
በተጨማሪም ሁለት ሰዎች በጥቃቱ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው ለተሻለ ሕክምና ወደ አቦምሳ ከተማ ሪፈር መሄዳቸውን በመረጃው ተያይዞ ተነግሯል፡፡
ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ በቀበሌው ውስጥ የሚኖሩ 8 ኦርቶዶክሳውያን ሌሊት ላይ ከቤታቸው አስወጥተው የታጠቁ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን በደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል።
ከተገደሉት ምእመናን ውስጥ 6ቱ በገገሌ በዓለወልድ ቤተ ክርስቲያን፣አንድ ደግሞ በሞዬ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን እና ቀሪ ሟቾች ባሉበት አካባቢያቸው ሥርዓተ ቀብራቸው መፈጸሙ ተገልጿል።
በመረጃው እንደተመላከተው በቀበሌው ባለ ከፍተኛ ስጋት በቀጣይ የባሰ ችግር እንዳይፈጠር በሀገረ ስብከት ደረጃ ከመንግሥት ጋር በጋራ መሥራት ይገባል ተብሏል።
በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ሁኔታዎችን ለማረረጋት የሀገር መከላከያ በስፍራው እንደሚገኝ በመረጃው ተጠቅሷል።
ኢዜማ፣ ብልጽግና ፓርቲ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የመንግሥት ሠራተኞችን የራሱ አባላት ለማድረግ የተለያዩ “ጫናዎች” እያሣደረ ይገኛል በማለት ከሷል። ኢዜማ፣ ገዢው ፓርቲ መንግሥታዊ መዋቅሮችን ለራሱ መጠቀሚያ ማድረጉን ባስቸኳይ እንዲያቆምም ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል።
ኢዜማ፣ የገዥውን ፓርቲ ድርጊት የመገናኛ ብዙኃን እንዲያጋልጡ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንና እንባ ጠባቂ ተቋም እንዲያወግዙትና ዜጎች በጋራ እንዲቃወሙት ጥሪ አድርጓል። ይህ ካልሆነ ግን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመፍጠር ጉዳይ “የሕልም እንጀራ” ኾኖ ይቀራል በማለት ኢዜማ አስጠንቅቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ሕወሃት መሣሪያ እንዲደብቅና ተዋጊ እንዲያሠለጥን አይፈቅድም በማላት ዛሬ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሠጡት ምላሽና ማብራሪያ ላይ ተናግረዋል። ዐቢይ፣ መሣሪያ ደብቆ ማስቀመጥም ሆነ በኮንትሮባንድ ማስገባት በስምምነቱ ላይ የለም በማለት የሕወሓት አመራሮች ስምምነቱን እየጣሱ መኾኑን በመግለጽ ወንጅለዋል። ከውጭ አገራት ጋር ግንኙነት ማድረግ የፌደራል መንግሥቱ ሥልጣን ብቻ ሆኖ ሳለ፣ የሕወሓት ሰዎች ግን ከውጭ መንግሥታት ጋር ምን እየሠሩ ነው? በማለትም ዐቢይ ጠይቀዋል። ዐቢይ፣ ትግራይ እና አማራ ክልሎች የሚወዛገቡባቸው አካባቢዎች እጣ ፋንታ “በሕዝበ ውሳኔ” መወሰን እንዳለበትም ገልጸዋል።
“እንደ ሀገር ስንት ትውልድ በጦርነት እየበላን እንቀጥላለን” ሲሉ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠየቁ!
ዶክተር ደሳለኝ “10 ድስት ጥዶ አንዱንም ሳያማስል ሁሉንም የማሳረር ተግባር እየፈፀመ ነው” ሲሉም አገዛዙ የውስጥ ችግሩን ሳይፈታ ቀይ ባህርና መሰል የማጭበርበሪያ አጀንዳ መምዘዙን በፅኑ ተችተዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፅ ይሆኑኛል ብሎ የመረጣቸው የፓርላማ አባላት፡ ለመረጣቸው ሕዝብ ሳይሆን ነውረኛው ዐብይ አህመድ ያስቀመጣቸው ካድሬዎች እስኪመስሉ ድረስ “ዐብይ ሺ ከመት ንገስ” የሚል ይዘት ያለው የመወድስ አይነት ሲያቀርቡ በዋለበት በዚህ የፓርላማ ውሎ፡ መራር የሆኑ እውነታዎችን ያዘሉ ጥያቄዎች ደግሞ በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ መነሳታቸውን መረብ ሚዲያ ተመልክቷል።
እነዚህ ጥያቄዎች ምንም እንኳን መላሽና ምላሽ ባይኖራቸውም ነገር ግን ዶ/ሩ የጠየቁት ጥያቄዎች የሚከተሉት ናቸው።
1ኛ፦ መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ የህዝቡን ጥያቄ ማቅረብ ተስፈኛነት እንጂ ጨለምተኛነት አይደለም ያለው ዶክተሩ፡ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የተቀሰቀሱ ግጭቶች ተባብሰው ቀጥለዋል፡፡ በእነዚህ ግጭቶች የተጎዱ ንጹሀን ነዋሪዎች እና የንጹሀን መሰረተ_ልማት ጉዳቶች ቁጥር በግልጽ ሊነግሩን ይችላሉ ወይ ?
2፦ መንግስት ችግሮችን ለመፍታት ጽንፈኛ እና አሸባሪ የሚሏቸውን ቡድኖች ከመውጋት ባለፈ ለሁለቱ ክልሎች ከወታደራዊ አማራጮች ውጪ ያሉ ፖለቲካዊ መፍትሄዎችን ለመስጠት ለምን አይሰራም?
3ኛ፦ የኢትዮጵያ ህዝብ ተንቀሳቅሶ በሰላም ሰርቶ መኖር አቅቶታል፡፡ የሰላም እጦት ሰልችቶታል፡፡ሀገራችን እንደ ኮሎምብያ ከውስጥ ታጣቂዎች ጋር ለ 50 አመታት ስትዋጋ አትኖርም፡፡ በህግ ማስከበር ስም የሚወሰድ የዘፈቀደ እስር ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ የፖለቲካ
የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን፣ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ወደ ድሬደዋ አሥተዳደር፣ ምዕራብ ሐረርጌ ዞን እና ሶማሌ ክልል ገብተው እንደነበር አስታውቋል። ፖሊስ ከቡድኑ ጀርባ የነበሩ 34 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን መግለጡን የዘገበው የድሬዳዋ አስተዳደር ቴሌቪዥን ነው። ጸጥታ ኃይሎች ሰሞኑን በወሰዱት ርምጃ 43 ታጣቂዎች መገደላቸውንም ጣቢያው ጠቅሷል። ቡድኑ፣ በአሥተዳደሩና በአጎራባች ክልሎች፣ በመሠረተ ልማቶችና ኢንዱስትሪዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ ተዘጋጅቶ ነበር ተብሏል።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
============
(ጥቅምት፲፯/፳፻፲፰ ዓ.ም)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
+++++++
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
“ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ …
የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 – ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡
ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
1. ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018
ብልፅግናዎች በጦርነት አላልቅ ያላቸውን ሕዝብ በፕሮፓጋንዳቸው እየቀለዱበት ነው ………… የአብይ ሚኒስትር የሆነችው ፍፁም የተባለች ፈጣሪን የማትፈራ ሴት በኢኮኖሚ በደቀቀው በድህነት በተዘፈቀው የኢኮኖሚ ሉዓላዊነቱ ለምዕራባውያን የፋይናንስ ተቋማት የተሸጠበት የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ በሃሰት የቁጥር ቁልል እያሾፈችበት ይገኛል። … በጦርነት ሰብሉ እየወደ ያለው ገበሬ ምርቱ 400 ፐርሰንት አደገ ብለው በንቀት እየተሳለቁ ነው …. ከትምህርት ቤት ምገባ ጀምሮ በርካታ ሥራዎች አሉን ብለው ያሾፋሉ፤ ዜጎች ሰርተው ቤተሰባቸውን የሚመግቡበት የስራ ፖሊሲ ከመቅረጽ ይልቅ የድህነት አካል የሆነው የምገባ ፕሮግራም እያካሄዱ ይኮፈሱብናል። የእድገት ፖሊስን ቀርፆ በተግባር ላይ ማዋል እንጂ ተማሪን መመገብ የድህነት ቅነሳ አይደለም። …… ሴትየዋ ፈጣሪን ሳትፈራ የአቅመ ደካማ ቤቶች የማደስ እንዲሁም የገጠር እና የከተማ ኮሪደር ፕሮጀክቶች ያስገኟቸው ትሩፋቶች የዜጎችን ሕይወት ከማሻሻል አኳያ ትልቅ ሚና አላቸው ትላለች። በጣት የሚቆተሩ ቤቶችን ለፎቶ ፖለቲካና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ አድሶ ራስን ከፍ ማድረግ አሳፋሪ ነው፤ የኮሪደር ልማቱም ቢሆን በመቶ ሺዎችን ከቤታቸውና ከንግዳቸው አፈናቅሎ ተመጽዋች እና ስራፈት ደሃ አድርጓቸዋል። …. የኮሪደር ልማቱ የቆመው እኮ በእነ አሜሪካ ጫና እንደሆነ በደንብ ይታወቃል፤ የምዕራባውያን ኤምባሲዎች የተጫወቱት ሚና ተፈናቃይና ተመፅዋች እንዲቆም አድርጎታል ….. ውሸት ሲደራረብ እውነት ይሆንልናል የሚሉት የብልጽግና ሰዎች …. የአለም ባንክ የኢትዮጵያ የድህነት መጠን ወደ 43 ከመቶ ከፍ ይላል የአመታት ለውጥን ወደኃላ ይቀለብሳል ብሎ የተናገረበት መግለጫ አድምጠን ሳንጨርስ ….. ኢትዮጵያ የከፋ የብድር አዘቅት ውስጥ ትገኛለች የሚለውን መረጃ አንብበን ሳናጠናቅቅ …… የተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ኢትዮጵያ ደካማ
የፌዴራል ዋና ኦዲተር የተሟላ አስተዳደራዊና የፋይናንስ ነፃነት እንደሌለው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥናት አመለከተ
ኦዲተሩ በሚያጋልጣቸው የፋይናንስና የሕግ ጥሰቶች ላይ ተጠያቂነት አልተረጋገጠም ብሏል ኦዲተሩን የሚቆጣጠረው የፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ ገለልተኛ አለመሆኑ ተጠቅሷል የፌዴራል ዋና ኦዲተር በመንግሥት ጣልቃ ገብነት የተነሳ አስተዳደራዊ ነፃነቱ መገደቡንና የፋይናንስ ነፃነቱም የተጓደለ መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥናት አመለከተ። የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ከ2001 እስከ 2015 ዓ.ም. ባካሄዳቸው የፋይናንስና የሥራ አፈጻጸም ኦዲትና ግኝቶቹን መነሻ… https://ethiopianreporter.com/147032/
“የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
የቅዱስነታቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ መልእክት ከዚህ እንደሚከተለው ይቀርባል።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
• ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
• ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ቅዱስ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፤
የጎደለብንን እየሞላ አገልግሎታችንን እያቃና ከዚህ ላደረሰን፣ ይህንን ዓመታዊና ሐዋርያዊ ጉባኤያችንን ለማካሄድም ለሰበሰበን ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቀርባለን፡፡
“ወእፌጽም ታሕጻጸ ሕማሙ ለክርስቶስ በሥጋየ በእንተ ሥጋሁ እንተ ይእቲ ቤተ ክርስቲያኑ፡- ስለ አካሉ ማለትም ስለ ቤተክርስቲያኑ ስል በሥጋዬ በክርስቶስ መከራ የጎደለውን እፈጽማለሁ” (ቈላ.፩÷፳፬)
ያለንበት ዓለም በሁሉም ነገር በጉድለቱ የሚታወቅ ነው፤ ጉድለት ባይኖርና ሁሉም የሞላለት ቢሆን ኖሮ ፍጥረት እርስ በርስ የሚተረማመስበት ሁኔታ አይኖርም ነበር ወይም አሁን ባለበት ደረጃ የከፋ አይሆንም ነበር፡፡
እግዚአብሔር ሁሉንም አሟልቶ መፍጠር ወይም መስጠት የሚችል ከሃሊ አምላክ ቢሆንም፣ እሱ ባወቀ ፍጥረትን ሁሉ ጉድለት ያለበት አድርጎ ፈጥሮታል፤ በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ጉድለቱን ለመሙላት በሚያደርገው ፍትጊያ እየተጋጨ እርስ በርስ ሲተረማመስ ማየቱ የተለመደ ነው፡፡ ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያንም በጐዶሎው ዓለም እስካለች ድረስ ከሚመጣው ፈተና አታመልጥም፤ ይህም በመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ ለቈላስይስ ሰዎች “የጎደለውን እፈጽማለሁ” በማለት ሲጽፍ እናስተውላለን፡፡
• ብፁዓን አበው
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ‘ፅንፈኛ’ የተባሉ ታጣቂዎች ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ንጹሃንን ገደሉ፡፡
DW : የንጹሃን ግድያ ተደጋግሞ በተሰማበት በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ እሁድ ምሽት በግምት ሁለት ሰዓት ግድም የታጠቁ አካላት ባደረሱት ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች ወዲያው መገደላቸውን ተጎጂዎች እና የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡
ጥቃቱ ከትናንት በስቲያ እሁድ ጥቅምት 09 ቀን 2018 ዓ.ም. ማምሻውን አገር ሰላም ብለው እንደወትሮው ወደ ቤታቸው በገቡ ንጹሃን የኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ ነው የተወሰደው ያሉት አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ አንድ የአከባቢው ነዋሪ፤ በአጎራባች የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ወረዳዎች የሚንቀሳቀሱ ያሏቸው ታጣቂዎቹ ወሰን ተሻግረው ባደረሱት ጥቃት የአከባቢው ሰላማዊ ዜጎች ላይ ዘግናኝ ያሉትን ግድያ መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡ “ጥቃቱን ያደረሱት በአከባቢው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ የተባሉ ታጣቂዎች ናቸው” ያሉት አስተያየት ሰጪው፤ በእሁድ ምሽቱ ድንገተኛ ጥቃት 22 ሰዎች ወዲያው መገደላቸውን አመልክተዋል፡፡ በኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዳርጌ በሚባል ስፍራ እሁድ ምሽት ከአንድ እስከ ሁለት ሰዓት ግድም በተወሰደው በዚህ ጥቃት ህጻናት እና ሴቶች በስፋት ተጠቂ መሆናቸውን አስረድተዋልም፡፡
ቤተሰቦቻቸው የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን የነገሩን ነገር ግን አለብን ባሉት የደህንነት ስጋት ስማቸውን ከመግለጽ የተቆጠቡት ሌላው የአከባቢው ነዋሪ፤ “ሰላማዊ ዜጎችን በጭለማ ገብተው ነው የፈጁዋቸው፡፡ አሁን በእሁድ ምሽቱ በዚህ ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 29 ደርሰዋል፡፡ 22 ሰዎች ወዲያው መገደላቸው ሲረጋገጥ ቀሪዎቹ አስከሬናቸው በየጥሻው የወደቁና በሆስፒታል ህይወታቸው ያለፉ ናቸው” ብለዋል፡፡ የተገደሉትን ለመለየት ትናንት እስከ
በአፋር ክልል ገዋኔ ወረዳ ትናንት ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለ 8 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ያሉና የመንግስት ሰራተኞች የመጠጥ ውኃ በአግባቡ እየቀረበ አይደለም የሚሉ የወረዳው ነዋሪዎች የኢትዮጵያ ጅቡቲን አውራ ጎዳና መንገድ ለሰዓታትበመዝጋት ተቃውሟቸውን ማሰማታቸው ተነገረ፡፡ ለተቃውሞወደ አደባባይ የወጡ የገዋኔ ነዋሪዎች እንደገለፁት በወረዳውየሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች በተገቢው መንገድ ደመወዝ እየደረሰን አይደለም ይላሉ፡፡ ‹‹ደመወዝ ከነጭማሪው ወደ 8 ወራት አልተከፈለንም፡፡ በ2017 ዓ.ም ግማሽ አለ፡፡ ከ2018 ዓ.ም ያልተከፈለ የደመወዝ ጉዳዩን ማን ይስማ፡፡›› ተጨማሪ https://www.dw.com/am/