Blog Archives
የእንግሊዝ ዶክተሮች የ4% የክፍያ ጭማሪ ቢያገኙም አነሰ በሚል ለተቃውሞ ድምፅ እያሰባሰቡ ነው።
ባለፈው ሳምንት እንግሊዝ ለአስተማሪዎች እና ዶክተሮች ጭማሪ መደረጉን ብትገልፅም የብሪትሽ የሃኪሞች ማህበር በቂ ባለመሆኑ ሃኪሞች እንዲያምፁ እየጠየቀ ነው።
ማህበሩ የክፍያ ጭማሪው በቂ ባለመሆኑ የተነሳ የስራ ማቆም አድማ ለማድረግ ለመወሰን እንዲያስችል እስከ መጪው ሐምሌ 7 ድምፅ ይስጡ ብሏል።
በአዲሱ ጭማሪ መሰረት ለሪዝደንት ሃኪሞች 750 ፓውንድ ክፍያ ሲጨመርላቸው የሃኪሞቹ ማህበር ግን ትክክለኛ ገቢያችን ከ2008 ጀምሮ በ23 በመቶ በመቀነሱ የተደረገው ጭማሪ በቂ አይደለም ብሏል።
ማህበሩ ሃኪሞች በአድማው ላይ የይሁንታ ድምፅ ይስጡ ሲል መንግስት ክፍያዎችን ማስተካከል ያለበት ዛሬ ነው ብሏል።
በእንግሊዝ የሬዚደንት ሃኪም ከደሞዙ በተጨማሪ 37 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ለምሽት ስራዎች እና ሌሎችም ጥቅማጥቅሞችን ያገኛል።
በፋውንዴሽን ትሬኒንግ(F1) ያሉ ዶክተሮች መሰረታዊ የሚባል ከ36,616 እስከ 42,008 ፓውንድ በአመት ሲያገኙ የስፔሻሊስት ስልጠና የጀመሩ ደግሞ ከ49,909 እክከ 70,425 ፓውንድ ያገኛሉ።
የስፔሻሊቲ ዶክተር ከ59,175 ፓውንድ እስከ 95,400 ፓውንድ ሲያገኝ ሃኪሞቹ የስራ ጫናችን ባልቀነሰበት ሁኔታ ትክክለኛው ገቢያችን መቀነሱ አሳስቦናል ብለዋል።
በ2023 እና 2024 ዶክተሮቹ ተመሳሳይ ውሳኔ ውስጥ ገብተው የነበረ ቢሆንም በሁለት አመታት ውስጥ ክፍያቸው በ22 በመቶ ይጨምራል ከተባለ በኋላ ውሳኔያቸውን ቀልብሰው ነበር።
በአዲሱ ማሻሻያ የአንድ የሙሉ ሬዚደንት ዶክተር ክፍያ ከ38,800 ፓውንድ የሚጀምር ሲሆን ከ2023 አንፃር የ9500 ፓውንድ ጭማሪ አለው።
ማህበሩ ዶክተሮቹ በቂ ክፍያ ካልተከፈላቸው ከሃገር ወጥተው ይሰራሉ ያለ ሲሆን በ2023 ከ4000 በላይ ዶክተሮች ከሃገር ወጥተው ለመስራት ወስነዋል ወይም
የብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ፣ የመንግሥት ቀጣይ ዕቅድ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውንና ገበያ-መሩን የውጭ ምንዛሬ ገበያ “ይበልጥ ሥር እንዲሰድ” ማድረግ እንደኾነ ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት የአፍሪካ ክፍል ሃላፊ አበበ አዕምሮሥላሴ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ ተናግረዋል። ድርጅቱ ዛሬ ያሠራጨው ቃለ ምልልስ የተደረገው፣ በቅርቡ ዋሽንግተን ላይ ከተካሄደው የዓለም ባንክና ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት የጋራ ስብሰባ በተጓዳኝ እንደነበር ተገልጧል። ማሞ፣ ለአገሪቱ አስተማማኝ የዕድገት መሠረት ለመጣል “የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባቶችን ለማስተካከል” የሚያስችሉ ሥራዎችን መስራት ሌላኛው የመንግሥት ቀጣይ ዕቅድ መኾኑን ገልጸዋል። ገበያ-መሩ የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲ “አመርቂ ውጤት አስገኝቷል” ያሉት ማሞ፣ የብሄራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችትም በሦስት እጥፍ ማደጉንና የዋጋ ግሽበት ወደ 13 በመቶ ማሽቆልቆሉን ጠቅሰዋል። የአገሪቱ የወጪ ንግድም በእጥፍ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ማሞ ጠቁመዋል።
የሥራ ማቆም አድማ የመቱ የጤና ባለሙያዎች ተወካዮች ግንቦት 15 ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር መወያየታቸውን ከተወካዮቹ መስማቱን ቢቢሲ ዘግቧል። ኢሰመኮ በጉዳዪ ገለልተኛ አደራዳሪ ለመኾን ጥያቄ ማቅረቡንና በዚህ ዙሪያ “ቅድመ ውይይት” እየተደረገ መኾኑን ተወካዮቹ መናገራቸውንም ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም በጤና ባለሙያዎች ላይ እስሩ፣ ዛቻውና ማስፈራሪያው አለመቆሙን በመጥቀስ፣ መንግሥት ለድርድር ባለው ቁርጠኝነት ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ተወካዮቹ ገልጸዋል ተብሏል። ከ320 ሺሕ በላይ ከሚገመቱት የአገሪቱ የጤና ባለሙያዎች፣ ከ65 እስከ 75 በመቶ ያህሉ በንቅናቄው እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተወካዮቹ መጥቀሳቸውንም ዘገባው አመልክቷል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሥራ ማቆም አድማ ጋር በተያያዘ ያሠራቸውን የጤና ባለሙያዎች “ባስቸኳይ” እና “ያለምንም ቅድመ ኹኔታ” እንዲፈታ በድጋሚ ጠይቋል። አምነስቲ፣ መንግሥት በአድማ ላይ ከሚገኙት የጤና ባለሙያዎች ጋር ንግግር እንዲጀምርና የተቃውሞ ድምጾችን ማፈን እንዲያቆምም አሳስቧል። አምነስቲ ይህን ያለው፣ ትናንት ዘጠኝ የጤና ባለሙያዎች በከፍተኛው የፌደራሉ ፍርድ ቤት መቅረባቸውን አስመልክቶ ባወጣው አጭር መግለጫ ነው። ፍርድ ቤቱ፣ በትናንቱ ችሎቱ ለመርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ ስምንት የምርመራ ቀናት መፍቀዱ ይታወሳል።
የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ለተረጂዎች የምሠጠውን ዕርዳታ ከእስካኹኑ ይበልጥ ለመቀነስ እገደዳለሁ በማለት ሰሞኑን ባሠራጨው መረጃ አስጠንቅቋል። በገንዘብ እጥረት ሳቢያ፣ በሚያዝያ ወር ለተረጂዎች የሠጠው የምግብ ዕርዳታ ከመደበኛው ኮታ 65 በመቶውን ብቻ እንደኾነና በተያዘው ወር ለስደተኞች የሚሠጠው የምግብ ኮታም ከመደበኛው 50 በመቶውን ብቻ እንደኾነም ድርጅቱ ገልጧል። ድርጅቱ፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የቀጠሉ ግጭቶች የደኅንነት ስጋት እንደደቀኑበት፣ ለሰብዓዊ ዕርዳታ የሚያወጣቸውን ወጪዎች እንደጨመሩበትና የምግብ ዕርዳታን ለተረጂዎች ደኅንነቱ በተጠበቀ ኹኔታና በጊዜ እንዳያቀርብ እንቅፋት እንደፈጠሩበትም ጠቅሷል።
አሜሪካ በዜጎቿ እና በነዋሪዎቿ ላይ የሶሻል ሚድያ እቀባ የሚያደርጉ መንግስታት ሀላፊዎችን ቪዛ ልትከለክል መሆኑ ተሰማ
– “የውጭ ሀገራት መንግስታት በአሜሪካ ምድር ላይ ተኹኖ ለተፃፈ የሶሻል ሚድያ ፅሁፍ ማስፈራርያ ወይም የእስር ትእዛዝ ማቅረብ አይቻላቸውም”- ማርኮ ሩቢዮ
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/cf6?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
ህወሓት የግንቦት 20ን 34ኛ አመት እያከበረ ነዉ
በቅርቡ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁለተኛ ጊዜ የተሰረዘዉ ህወሓት የግንቦት 20ን 34ኛ በዓል እያከበረ ይገኛል።

በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገጹ እንዳሳወቀዉ ማለዳ ላይ የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት ጀነራል ጻድቃን በሰማዕታት ሀዉልት የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። በስነስርዓቱ ላይም ዶ/ር ደብረጽዮን ተገኝተዋል።
በሌላ ዜና ግንቦት 20ን በማስመልከት የአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት በአሜሪካ መንግስት ስም ለ34ኛው የነፃነት ቀናቹ እንኳን አደረሳችሁ ብሏል
የስቴት ዲፓርትመንት መግለጫ “ዩናይትድ ስቴትስ ከመቶ አመት በላይ የቆየውን የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታችንን ታደንቃለች ተጨማሪ የብዙ አመታት ትብብር እና ጓደኝነትንም በጉጉት ትጠብቃለች” ብሏል። ዩናይትድ ስቴትስ መንግስት በንግድና ኢንቨስትመንት የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስተዋወቅና ሰላምን ለማራመድ በሚደረገውን ጥረት ጨምሮ በሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ ከኢትዮጵያ ጋር ለመስራት ዝግጁ ነች ሲልም አክሏል።
ግንቦት 20 ብሄራዊ በዓል ሆኖ ከመከበር መሰረዙ ይታወቃል። https://www.state.gov/releases/office-of-the-spokesperson/2025/05/ethiopia-national-day/
የደቡብ ሱዳን የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በፈጸሙት “የደፈጣ ተኩስ ጥቃት” ስድስት ሰዎች ተገደሉ
ከደቡብ ሱዳን የመጡ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች፤ በጋምቤላ ክልል፣ በአኙዋሃ ዞን፣ ዲማ ወረዳ በሚገኝ ቦታ ላይ በከፈቱት “የደፈጣ ተኩስ ጥቃት” ስድስት ሰዎች መገደላቸውን የወረዳው የአስተዳደር እና የፖሊስ ኃላፊዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። በትላንትናው ዕለት ጠዋት በተፈጸመው በዚህ ጥቃት፤ በዘጠኝ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን መመልከታቸውን በአካባቢው የሚገኙ የህክምና ባለሙያ ገልጸዋል።
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ጥቃቱን የሰነዘሩት፤ ከዲማ ወረዳ 39 ሰዎች አሳፍሮ ወደ ጎግ ወረዳ ሲጓዝ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ላይ እንደሆነ የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር ኡታክ ሜዶ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሱ የደፈጣ ጥቃት የተሰነዘረበት፤ ከዲማ ከተማ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ተጉዞ አቻኛ እና 45 በተባሉ ቀበሌዎች መካከል በደረሰበት ወቅት እንደሆነ የፖሊስ አዛዡ አስረድተዋል።
ታጣቂዎቹ በአውቶብሱ ላይ ተኩስ በከፈቱበት ወቅት “መሳሪያ የያዘ ተሳፋሪ” መልሶ በመተኮስ አጸፋውን መመለሱን ረዳት ኢንስፔክተር ኡታክ አመልክተዋል። በተኩስ ልውውጡ አንድ ታጣቂ መገደሉንም የፖሊስ አዛዡ ጠቁመዋል። በታጣቂዎቹ የደፈጣ ጥቃት የአውቶብሱን ሹፌር ጨምሮ የስድስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በስድስት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱንም ጨምረው ገልጸዋል።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16005/
ኢትዮጵያ ውስጥ በዝንጀሮ ፈንጣጣ (Mpox) የተያዘ ሰው ተገኘ።
በMpox የተያዘ ሰው የተገኘው ሞያሌ ከተማ ነው።
ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት Mpoxን አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም ኢኒስቲትዩቱ በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ በህመሙ መያዛቸው ከተጠረጠሩ ታማሚዎች በወሰደው ናሙና በMpox ቫይረስ የተያዘ ሰው ማግኘቱን እንዳረጋገጠ ይፋ ተደርጓል።
ቫይረሱ እንደተገኘበት የተረጋገጠው የ21 ቀን እድሜ ያለው ህፃን ልጅ ሲሆን እናቱም በተደረገው ቀጣይ ምርመራ ለቫይረሱ እንደተጋለጠች ለማረጋገጥ መቻሉ ተገልጿል።
የህፃኑ አባትም ወደ ጎረቤት ሀገር ሄዶ የነበረ መሆኑ መታወቁና የሄደባቸውን አካባቢዎች እንዲሁም ከግለሰቡ ጋር የቅርብ ንክኪ የነበራቸው ግለሰቦችን የመለየትና ክትትል የማድረግ ስራ እንደተጀመረ ይፍ ተደርጓል።
ታማሚው ህፃን እና እናቱ፣ አስቀድሞ በተዘጋጀው የለይቶ ማከሚያ፣ ተገቢው የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን፣ እስካሁን ባለው ሁኔታ የከፋ የጤና እክል አልገጠማቸውም ተብሏል።
የMpox በሽታ ቫይረሱ ካለባቸው ግለሰቦች ጋር ንክኪ ያለው ሰው የሚከተሉት ምልክቶች በሚታዩበት ወቅት ማለትም ፦
– ሽፍታ
– ሳል
– ትኩሳት
– የራስ ምታት
– ድካም እና የጀርባ ህመም ሲያስተውል በአፋጣኝ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ተገቢውን የምርመራና ህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ጥሪ ቀርቧል።
እንዲሁም የግል እና የእጅ ንፅህና በመጠበቅና ከላይ የተገለፁት ምልክቶች ባሉባቸው ታማሚዎች አካባቢ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛዎችን በመጠቀም ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ተብሏል።
በአሁኑ ወቅት ይህ በሽታ በተወሰነ ቦታ ብቻ የታየ በመሆኑ ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ የተለመደውን አኗኗር መቀጠል ይችላል ያሉት ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
በአማራ ክልል በመቶዎች የሚቆጠሩ የባንክ ጥበቃዎች እየታሰሩ ነው፣ ምክንያቱ ምን ይሆን?
(መሠረት ሚድያ)- በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ አንዳንድ ከተሞች ውስጥ የባንክ ጥበቃ በመሆን እያገለገሉ ያሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች ከባለፈው ሁለት ሳምንት ወዲህ አፈሳ በሚመስል መልኩ እየታሰሩ ይገኛሉ።
መሠረት ሚድያ ‘ጉዳዩ ምን ይሆን?’ በሚል ማጣራት አድርጓል።
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/9de?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
የኤርትራው ፕሬዝደንት በትናንት ምሽት ብዙዎችን ባስደመመ ንግግራቸው ስለ ኢትዮጵያ ምን አሉ?
– “የውጭ ሀይሎች በብልፅግና ወኪላቸው አማካኝነት የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ላለፉት አምስት አመታት ያወጁት ጦርነት ምን ያህል ተስፋ እንደቆረጡ ያሳያል”
– “ሊያቀርቡ የሚፈልጓቸው ምክንያቶች; ናይል እና ቀይ ባህር፣ የባህር በር ማግኘት፣ የኦሮሞ ህዝብን የማይወክል የኦሮሙማ አስተሳሰብ፣ የኩሽ እና የሴም ግጭት… ናቸው”
– “የኢትዮጵያ ህዝብ የራሱን ምርጫ መርጧል፣ ተቃውሞውን ለማጠንከር እየተዘጋጀ ነው”
ሙሉ ዜናውን ያንብቡ፣ የሚድያችን ቤተሰብ ይሁኑ ⤵️
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/3bf?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
የአሜሪካ ኢምባሲ፣ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መንግሥት የድሮን ጥቃቶችን “በራሱ ሕዝብ ላይ” መፈጸምን “በአፋጣኝ እንዲያቆም” በጠየቁበት የዛሬው መልዕክታቸው ላይ ማሻሻያ አድርጓል። በተሻሻለው መልዕክት፣ ይህ መልዕክት ተነስቶ በምትኩ መንግሥት ለግጭቶች “ከኃይል ውጪ ያሉ ሰላማዊ አማራጮችን” መፈለግ እንዲቀጥልና “የዜጎቹን ደኅንነት እንዲያስቀድም” አምባሳደሩ መጠየቃቸው ብቻ ተጠቅሷል። የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የኦሮሚያው ግጭት እንዲያበቃ የሰላም ድርድሩን እንዲቀጥል፣ የፋኖ ቡድንም “ተጨባጭ” እና “ሰላማዊ የኾኑ” ግቦችን እንዲይዝና “በትጥቅ ትግል ስም የሚካሄድ ሕገወጥነት እንዲያበቃ” አምባሳደሩ በቀደመውም ኾነ በተሻሻለው መልዕክታቸው ጠይቀዋል። ኢምባሲው፣ የአምባሳደሩ መልዕክት በምን ምክንያት እንደተሻሻለ አላብራራም። https://www.facebook.com/profile.php?id=100007836377373
አንዳንድ ምግባረ ብልሹ የፀጥታ አካላት በመዲናዋ ነዋሪዎች ላይ በግልፅ ዝርፊያ መፈፀም እንደጀመሩ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- የፀጥታ አካላት በአቅራቢያችን ሲገኙ ደህንነት ይሰማናል፣ ከሌላው ግዜ በተለየ ህግ አስከባሪ እንዳለ ተሰምቶን ሰላም ይታየናል። ይህ የተለመደ ስሜት ግን በቅርብ ግዜያት በተለይ በመዲናዋ አዲስ አበባ እየጠፋ ይገኛል፣ ለዚህ ደግሞ እየበዙ የመጡት ምግባረ ብልሹ የፀጥታ አካላት ናቸው።
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/0be?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
አሜሪካ ምን አለች ?
➡️ ” ፋኖ ተጨባጭ እና ሰላማዊ የሆነ ዓላማ ይዞ ይምጣ። ”
➡️ ” የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) በኦሮሚያ ያለውን ግጭት ለማስቆም ድርድሩን ይቀጥል። ”
➡️ ” የፌዴራል መንግሥት በራሱ ዜጎች ላይ የሚያደርገውን የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ ያቁም። ”

አሜሪካ ዛሬ አዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ በኩል ለፌዴራል መንግሥት እና ለታጣቂዎች መልዕክት አስተላልፋለች።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ዛሬ ባስተላለፉት መልዕክት በመላው ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለጉዳት የዳረጉ ግጭቶች ሰላማዊና ትክክለኛ መፍትሔ እንዲፈለግላቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
አምባሳደሩ፥ ለታጣቂ ኃይሎች እና ለፌደራል መንግስት ባስተላለፉት መልዕክት ህዝብን እንዲያስቀድሙ ጥሪ አቅርበዋል።
” ጦርነቱን ማቆም፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ መርዳት እና ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ እና የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ ነው ” ሲሉ አስገንዝበዋል።
” በትጥቅ ትግል ስም የሚፈጸሙ ህገወጥ እና የኃይል እርምጃዎች ሊቆሙ ይገባል ” ብለዋል።
አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በመልዕክታቸው ለፋኖ ፣ ለኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) እና ለፌደራል መንግስት የተናጠል መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዚህም ፥
– ፋኖ ተጨባጭ የሆነ እና ሰላማዊ የሆነ ዓላማ/ግብ ይዞ እንዲመጣ፤
– የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) ደግሞ በኦሮሚያ ያለውን ግጭት ለማስቆም ድርድሩን እንዲቀጥል፡
– የፌደራል መንግስት በራሱ ዜጎች ላይ የሚያደርገውን የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ እንዲያቆምና ረጅም እርምጃ ወደ ለሰላም በመምጣት መፍትሄዎችን እንዲያመቻች ጥሪ አቅርበዋል።
አምባሳደሩ በመልዕክታቸው ማጠናቀቂያ ” ሰላምና መረጋጋት የምንመርጥበት ጊዜ አሁን ነው ” ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር እንደ ጎርጎሮሳዊያኑ ከ2001 እስከ 2023 የኢትዮጵያ ጠቅላላ አገራዊ ምርትና ምርቱ ለዜጎች የሚያስገኘው የነብስ ወከፍ ገቢ እየቀነሰ እንደሄደ በጥናት ማረጋገጡን መግለጡን ሸገር ዘግቧል። ማኅበሩ በተለይ ከአውሮፓዊያኑ ከአውሮፓዊያኑ 2016 ጀምሮ የነብስ ወከፍ ገቢ እየቀነሰ መምጣቱንና በአንጻሩ የዋጋ ግሽበት እየጨመረ መሄዱንና እንደገለጠ ዘገባው ጠቅሷል። የማዳበሪያ አጠቃቀም ከዓለማቀፍ መስፈርት አንጻር ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ የግብርናው ዘርፍ ያገኘው ብድር 7 ነጥብ 8 ከመቶ ብቻ መኾኑንም ተቋሙ ገልጧል ተብሏል። የጥሬ እቃ እጥረት፣ የኤሌክትሪክ ኃይልና የውሃ አቅርቦት እጥረትም ለአምራቹ ዘርፍ ፈተና እንደኾነ ተገልጧል። ግጭቶችም ኦኮኖሚው እንዲቀዛቀዝና ኢንቨስትመንት እንዲዳከም ምክንያት ሆነዋል ተብሏል።
“ የተገደሉት ሰዎች ብዛት 17 ነው። ከሟቾች መካከል 12 ህፃናት ናቸው ” – የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አባል
በካማሺ ዞን ምዥጋ ወረዳ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት ንጹሐን ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የክልሉ ምክር ቤት አባል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ነዋሪዎቹ፣ “የሸኔ ታጣቂዎች ጥቃት ፈጽመዋል” ብለው፤ ከ10 በላይ ንጹሐን እንደተገደሉ፣ አብዛኛዎቹ ሟቾች ህፃናት እንደሆኑ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለ ጥቃቱ የጠየቃቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ም/ቤት አባልና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ለሜሳ ኔኖ፣ “ ትክክል ነው። ንጹሐን ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ግድያ ነው የተፈጸመው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የክልሉ ምክር ቤት አባል በሰጡን ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
“ በካማሽ ዞን ምዥጋ ወረዳ አንገር ሜጢ የሚባል ታዳጊ ማዘጋጃ ቀበሌ ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ/ም ንጋት 12 ሰዓት ጅምሮ የሸኔ ቡድን ጥቃት ፈጽሟል።
በዚሁ ጥቃት 16 ሰዎች እዛው ነው የሞቱት። አንደኛው ሰው ደግሞ ለህክምና ከሄደ በኋላ ነው የሞተው። የተገደሉት ሰዎች ብዛት 17 ነው። ከሟቾች መካከል 12 ህፃናት ናቸው። ቀሪዎቹ አዋቂ ናቸው።
ቡድኑ በተለያዩ ጊዚያቶች ጥቃት ሰንዝሯል። እስካሁን በተፈጸሙ ሦስት ጥቃቶች 27 ሰዎች ናቸው የተገደሉት።
የትላንቱ ጥቃት የተፈጸመበት ቦታ ለኦሮሚያ ክልል አንድ ቀበሌ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ነው የሚገኘው። ጥቃቱ በወረዳው ከሚያዚያ ወዲህ ለሦስተኛ ጊዜ የተፈጸመ ነው ” ብለዋል።
ምክንያቱና መፍትሄው ምንድን ነው ?
የታጣቂዎቹ ፍላጎታቸው ምንድን ነው ? መፍትሄውስ ? በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ
” በደብረብርሃን ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች ላልተፈለገ እርግዝና እና በአባላዘር በሽታ እየተጠቁ ነው ” የተፈናቃይ ሴት ወጣት ተወካዮች
⚫ ” የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት ይሰጡ የነበሩ ድርጅቶች አሁን ላይ ሁሉም ወጥተዋል ” የቻይና ካምፕ ተፈናቃይ አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ
በደብረብርሃን መጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚሰጠው የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት ጥራቱን ያልጠበቀ በመሆኑ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን የተፈናቃዮቾ ሴት ወጣት ተወካዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
በህክምና ባለሙያዎች ዘንድም ሚስጥር ጠባቂ አለመሆን አገልግሎት ለማግኘት በምንሄድበት ወቅት የማሸማቀቂያ ቃላቶችን የሚጠቀሙ በመሆኑ አገልግሎቱን ማግኘት ከብዶናል ብለዋል።
“የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት እየሰጠ ያለው ዩኒሴፍ ብቻ ነው፣ አገልግሎት የሚሰጠውም ግቢ ውስጥ ቢሆንም ሴት ልጅ ስትገባ የእንትና ልጅ የወሊድ መቆጣጠሪያ ልትጠቀም ገበች ይላሉ፣ ስንወጣ ደግሞ ወጣት ወንዶች ይጠብቁና ያሸማቅቁናል” ሲሉ ችግራቸውን ይገልጻሉ።
በተጨማሪም ” የህክምና ባለሙያው ወንድ ነው፣ ይህ ደግሞ ሴቶች በነፃነት የሚፈልጉት እንዳይናገሩ አድርጓል፣ በከተማው ጤና ጣቢያዎች ስንሄድም በነፃ ስለሆነ የሚሰጠው ምን ልታደርጊ ትመጫለሽ ውጪ ይላሉ። እነሱ የሚፈልጉት ብር የሚከፍለውን ሰው ብቻ ነው” ሲሉ አክለዋል።
ወጣት ሴቶችም በየፋርማሲው መድሀኒት እየገዙ ይውጣሉ፣ አብዛኞቹም ለህመም እየተዳረጉ ነው ብለዋል።
በስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት እጥረት በርካታ ወጣቶች ላልተፈለገ እርግዝና፣ ለአባላዘር እና ለመሳሰሉ ተላላፊ በሽታዎች መጋለጣቸውንም አስረድተዋል።
“በተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ ውስጥ ያሉ ወጣት ወንዶች ተስፋ እየቆረጡ አልኮል እየጠጡ ሴት ልጆችንን አስገድደው እየደፈሩን ነው፣ ስንጠይቅም በቸልተኝነት ሁሉም ይስተካከላል ይላሉ” ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርቧል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቻይና ካምፕ የተፈናቃይ ኮሚቴ
ከሚሰራበት ባንክ ውስጥ በፀጥታ አካላት የተወሰደው ወጣት ያለበት ሳይታወቅ አራት ወር እንደሞላው ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- ጥር 9/2017 ዓ/ም ከሚሰራበት ባንክ ውስጥ በፀጥታ አካላት ታፍኖ ተወሰደው ወጣት ያለበት ቦታ ሳይታወቅ አራት ወር እንዳለፈው ታወቀ።
https://open.substack.com/pub/meseretmedia/p/954?utm_source=share&utm_medium=android&r=bb7g
በመቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች፤ ከደህንነት ስጋት ጋር በተያያዘ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ካልተመለሱ የጀመሩትን የስራ ማቆም እንደሚቀጥሉ ገለጹ
በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች በትላንትናው ዕለት የጀመሩትን የስራ ማቆም ዛሬም በመቀጠላቸው በከተማይቱ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች ተዘግተው ዋሉ። ዳኞቹ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ያቀረቧቸው ጥያቄዎች እስኪፈቱ ድረስ የስራ ማቆማቸውን እንደሚቀጥሉ የትግራይ ዳኞች ማህበር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጿል።
በመቐለ ከተማ የሚገኙ ዳኞች ስራቸውን ለማቆማቸው በዋነኛነት የጠቀሱት ምክንያት “የደህንነት ችግር አለብን” የሚል ነው። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትላንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫም፤ በመቐለ ሰባት ክፍለ ከተሞች ባሉ ፍርድ ቤቶች እና በከተማይቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚሰሩ ዳኞች “በደህንነት ስጋት” ምክንያት ስራ እንዳቆሙ ማሳወቃቸውን አረጋግጧል።
የትግራይ ዳኞች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ዳዊት ሃይለስላሴ፤ ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ያቀረቧቸው አምስት ጥያቄዎች ከዳኞች ደህንነት ጋር የተያያዙ መሆናቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የዳኞቹ የመጀመሪያ ጥያቄ በችሎት የሚመደቡ የጸጥታ አስከባሪዎችን የሚመለከት ነው።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15997/
የሕክምና ማስተማሪያ ሆስፒታሎች ያሏቸው በርካታ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አዲስ የጤና ባለሙያዎችን ለመቅጠር ማስታወቂያ በማውጣት ላይ እንደኾኑ የጤና ባለሙያዎች የሥራ ማቆም አድማ አስተባባሪዎች ገልጸዋል። አለርት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ 50 ጠቅላላ ሐኪሞችን፣ 120 ነርሶችንና 100 ሚድዋይፈሮችን ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣቱን አስተባባሪዎቹ ያጋሩት መረጃ ያሳያል። የካቲት 12 ሆስፒታል ሬዚደንት ሐኪሞች እስከ ዓርብ ግንቦት 15 ወደ ሥራና የትምህርት ገበታቸው ካልተመለሱ አካዳሚያዊ ርምጃ እንደሚወስድ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሲያወጣ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በበኩሉ እስከ ነገ እኩለ ቀን ወደ ሥራቸውና ትምህርታቸው ያልተመለሱ ረዚደንት ሐኪሞች ጥቁር ከዩኒቨርስቲው እንዲለቁ አሳስቧል።
የጤና ሚንስትር ደኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ፣ የሥራ ማቆም አድማ ያደረጉ የጤና ባለሙያዎች ባስቸኳይ ወደ ሥራቸው ካልተመለሱ የሙያ ፍቃዳቸውን ሊነጠቁ እንደሚችሉ ለመንግሥታዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል አስጠንቅቀዋል። በአድማው ሳቢያ የተወሰነ የሆስፒታሎች አገልግሎት መስተጓጎል መኖሩን ያመኑት ሚንስትር ደኤታው፣ ከድንገተኛ እና ከእናቶችና ሕጻናት ሕክምና ክፍሎች ጥለው የወጡ የሕክምና ባለሙያዎች መኖራቸውን እናውቃለን ብለዋል። የአድማው ዋነኛ ተሳታፊዎች፣ ሬዚደንት ሐኪሞች እንደኾኑም ዶ/ር ደረጀ ጠቅሰዋል። የጤና ባለሙያዎች ሙሉ የሥራ ማቆም አድማ ዛሬ ሦስተኛ ቀኑን ይዟል።
(መሠረት ሚድያ)- በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር (space) የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ ከቅርብ አመታት ግን ጥቂት ሰዎች ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል የዝቅተኛው ንፍቀ ክበብ የጠፈር ጉብኝት አድርገዋል።
መሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበርካታ ቀናት ሲያሰባስበው የነበረው መረጃ እንደሚጠቁመው በአለም ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የአንድ የሀገር መሪ ወደ ጠፈር ሊጓዝ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፣ መንገደኛውም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ናቸው።
በኤምሬቶች የሚገኙ ምንጮቻችን እንዳረጋገጡልን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የመጓዛቸው አላማ በርካታ ግቦችን አካቷል፣ ከእነዚህም መሀል የሰላም እና የአንድነት መልዕክት ለአለም ብሎም ለኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ እንዲሁም ወጣቶች ወደ ቴክኖሎጂው ዘርፍ እንዲሳቡ እና እንዲነሳሱ ለማድሩግ ታስቧል።
“ውይይቱ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተባበሩት ኤምሬቶች በኩል በስፋት ንግግር እየተደረገበት ነው” ያሉት አንዱ በዱባይ የሚገኝ የመረጃ ምንጭ በተለይ ከጠፈር ላይ ሆኖ ለአለም ህዝብ መልዕክት ማስተላለፍ የእቅዱ ዋና ግብ ነው ብለዋል።
‘Project X’ የሚል ስም ተሰጥቶት እየተሰራበት እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጠፈር ጉዞ ወጪው በተባበሩት ኤምሬቶች የሚሸፈን መሆኑን አንድ ሌላ እዛው ዱባይ የሚገኝ ምንጭ ለሚድያችን ተናግሯል።
ለመዳሰስ የሞከርናቸው ፅሁፎች እንደሚጠቁሙት ወደ ጠፈር የሚደረግ ጉዞ ለአንድ ሰው ከትንሹ 250 ሺህ ዶላር እስከ ከፍተኛው 55 ሚልዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ይጠቁማሉ።
ለምሳሌ ‘Blue Origin’ እና ‘Virgin Galactic’ የተባሉት መንኩራኩሮች ከንፍቀ ክበብ በታች ለሚደረግ እና ርካሽ የተባለ ጉዞ ከ200 ሺህ ዶላር
ኢሰመኮ፣ በርካታ የጤና ባለሙያዎች ከሥራ ማቆም አድማው ጋር በተያያዘ እየታሠሩ፣ ማስፈራሪያ እየደረሰባቸውና ከማስተማሪያ ሆስፒታሎች በግዳጅ እንዲወጡ እየተደረጉ መኾኑን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ኢሰመኮ፣ በአዲስ አበባ፣ ጂማ፣ ባሕርዳር፣ ሀዋሳ እና ጎንደር በርካታ ሬዚደንትና ተለማማጅ ሐኪሞችን ጨምሮ በርካታ የጤና ባለሙያዎች እንደታሠሩና በግዳጅ ከማስተማሪያና የሥራ ቦታቸው ከኾኑ ሆስፒታሎች እንዲወጡ እንደተደረጉ ገልጧል። ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ፣ በጤና ባለሙያዎች ላይ የሚወሰዱ ሕጋዊና አስተዳደራዊ ርምጃዎች የሰብዓዊ መብቶች መርኾዎችን የተከተሉ መኾን እንዳለባቸው አሳስበዋል። ችግሩን ለመፍታት ውይይት እንዲደረግና ተጠያቂነት እንዲሠፍን የጠየቀው ኢሰመኮ፣ አፈና አዋጭ መንገድ አይደለም ብሏል።
የተቀደሰው ቀጠሮ – የፋኖዎችን ጉዞ የሚያስቃኘው ዶክመንታሪ ፊልም ተለቀቀ – ጸሃፊ – ፋኖ ባየ ደስታው
የአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ፣ ዛሬ ወደ ትግራይ አቅንተው ከሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል፣ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አማኑኤል አሠፋና ከጸጥታ ኃይሎች ከፍተኛ አዛዦች ጋር በጸጥታ፣ ፖለቲካዊ፣ በሰብዓዊ ጉዳዮች፣ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አተገባበርና በቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል። አምባሳደሩ የሽሬውን የተፈናቃዮች መጠለያ የጎበኙ ሲኾን፣ ለተፈናቃዮች ዕርዳታ መስጠት ዘላቂ መፍትሄ ሊሆን እንደማይችልና መፍትሄው ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው መመለስ እንደኾነ መናገራቸውን የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። አምባሳደሩ፣ ተፈናቃዮቹ ወደ ቀያቸው ተመልሰው ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ከተፈናቃዮቹ ጋር ካደረጉት ውይይት ተረድቻለሁ ተብሏል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ተማሪዎች አንድነት፣ የዘንድሮው የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፣ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ላይ በሚስተዋሉ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ አላተኮረም በማለት ተችቷል። ማኅበሩ፣ በትግራይ የሚገኙ አሕጉረ ስብከቶች ከሲኖዶሱ ከተለዩ በኋላ በተስተዋሉ ጥፋቶች ዙሪያ ያዘጋጀውን ሰነድ ለቋሚ ሲኖዶስና ለፓትርያርኩ ማቅረቦ ምላሽ አለማግኘቱን ጠቅሷል። መምሪያው፣ በኦሮሚያ ክልል በአስተዳደራዊ ችግሮች ቤተክርስቲያናት እየተዘጉ፣ ካህናትና ተከታይ ምዕመናንም እየፈለሱ መሆኑን ገልጧል። የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅነትና የአሕጉረ ስብከት ጽሕፈት ቤቶች የአስተዳደር ዘርፍ ከሊቃነ ጳጳሳት ውጪ በብቁ ባለሙያዎች እንዲመሩ የጠየቀው መምሪያው፣ የቤተክርስቲያኗ ተቋማት ለምዝበራ ተጋልጠዋል ብሏል።
” መንግስታት ውጤት አልባ ከሆነ የIMF የበጀት መቀነስና ዕዳ መክፈል ፖሊሲ ወጥተው ትኩረታቸውን ዜጎቻቸው ላይ ማድረግ አለባቸው ” – አክሽን ኤድ
በአፍሪካ ስድስት ሃገራት በጤና እና ትምህርት ዘርፉ በጀት በመቀነሱ ሰራተኞች የከፋ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን አዲስ ጥናት (https://actionaid.org/sites/default/files/publications/The%20Human%20Cost%20of%20Public%20Cuts%20May%202025.pdf) አመላከተ።
ጥናቱን አክሽን ኤድ የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት የሰራው ሲሆን ፦
– በኢትዮጵያ
– በጋና
– በኬንያ
– በላይቤሪያ
– በማላዊ
– በናይጄሪያ 600 የጤና ባለሙያዎች፣ መምህራንና የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ ነው ተብሏል።
በጥናቱ ከተሳተፉት መሃል 97 በመቶ የሚሆኑት የጤና ባለሙያዎች የሚያገኙት ደመወዝ መሰረታዊ የሚባለውን ወጪያቸውን ለመሸፈን እንደማያስችላቸው ተናግረዋል።
97 በመቶ የሚሆኑት የጤና ባለሙያዎች በደመወዛቸው የቤት ኪራይ መክፈል፣ የምግብ እና ሌሎች ወጪዎችን መሸፈን እንዳልቻሉ አንስተዋል።
በጥናቱ በ6ቱ ሀገራት የሚገኙ የጤና ተቋማት ተገልጋዮች በሃኪሞች እጥረት እና በዋጋ መጨመር ደስተኛ አይደሉም ሲል ያስቀመጠ ሲሆን መንግስታት ውጤት አልባ ከሆነ የIMF የበጀት መቀነስና ዕዳ መክፈል ፖሊሲ ወጥተው ትኩረታቸውን ዜጎቻቸው ላይ ማድረግ አለባቸው ብሏል።
ህመምተኞች ወደ ጤና ተቋማት ለመሄድ ረጅም መንገዶችን እንደሚጓዙ፤ የወባ መድኃኒትም በ10 እጥፍ ዋጋው መጨመሩ በጥናቱ የተካተተ ነው።
ለአብነትም በኢትዮጵያ ሙያከላ ቀበሌ የምትኖር ሴትን በመጥቀስ ከ5 አመት በፊት የወባ መድሃኒት በ50 ብር ትገዛ እንደነበር እና አሁን ግን ከግል ተቋማት በ500 ብር እንደሚገዛ መናገሯን ገልጿል።
በሌላ በኩል ፥ በጥናቱ ከተሳተፉት 87 በመቶ የሚሆኑት መምህራን የክፍል ውስጥ ቁሳቁሶች /የማስተማሪያ ቁሳቁሶች እንዳልተሟሉላቸው ሲገልፁ ፤ 73 በመቶ ያህሉ የትምህርት ማስተማሪያ
Posted in
News,
አፍሪቃ,
ኢትዮጵያ
የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችላቸው አዋጅ “ጊዜውን የጠበቀ አይደለም” በሚል ተተቸ
የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የማይንቀሳቅስ ንብረት ባለቤት እና ባለይዞታ እንዲሆኑ የሚያስችላቸው አዋጅ “ጊዜውን የጠበቀ አይደለም” በሚል በፓርላማ አባላት ተተቸ። ትችቱ የቀረበው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 12፤ 2017 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው።
በአራት ክፍሎች እና በ20 አንቀጾች የተከፋፈለው የአዋጅ ረቂቅ፤ የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤት ወይም ባለይዞታ ለመሆን ማሟላት ስለሚጠበቅባቸው ቅድመ ሁኔታዎች፣ የፈቃድ አሰራሮች፣ ገደቦች፣ መብቶች እና ግዴታዎች አካትቶ ይዟል። የህግ ረቂቁ በዝርዝር እንዲታይ ለተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ከመመራቱ አስቀድሞ በተደረገ ውይይት ላይ፤ ሁለት የፓርላማ አባላት ትችት አዘል ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል።
የአዋጁ ዋና ዓላማ “የውጭ ካፒታል ወደ ሀገር ውስጥ ማምጫ” እና “የውጭ ምንዛሬ ማግኛ እንደሆነ” መገንዘባቸውን የገለጹት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካዩ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፤ በህግ ረቂቁ ላይ ያላቸውን ስጋቶች እና አስተያየቶች በዝርዝር አቅርበዋል። የፓርላማ አባሉ ለስጋታቸው በምክንያትነት ካስቀመጧቸው ጉዳዮች አንዱ የሀገሪቱ የነፍስ ወከፍ ገቢ እና ደመወዝ በአለም አቀፍ ደረጃ ካለው ሲነጻጸር ያለውን ልዩነት ነው።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15990/
🔴 የፓርላማ አባላቱን አስተያየት ለማድመጥ ➡️ https://youtu.be/0WW5cfnTOJc