የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ከድርጅት ህገ-ደንብ እና አሰራር ውጭ በመሆን አፍራሽ ድርጊቶችንና የዲሲፕሊን ጥሰቶችን በፈፀሙ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ላይ ያስተላለፋቸው የእርምት ውሳኔዎች፡፡
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በ29/08/2014 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ በፓርቲው መዋቅር የተለያዩ የሃላፊነት እርከኖች ውስጥ እየተከሰቱ ያሉ የዲሲፕሊን እና ድርጅታዊ መርህ ጥሰቶችን በተመለከተ በጥልቀት ተወያይቶ የድርጅቱን መተዳደሪያ ደንብ የተለያዩ ድንጋጌዎችን መሰረት በማድረግ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡
ሀ. የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው የንቅናቄያችን የስራ አስፈጻሚ አባል በተመለከተ
አቶ ክርስቲያን ታደለ ፀጋዬ የንቅናቄው ከፍተኛ አመራር ሆነው ሳለ ፣ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ሃላፊነት ወደ ጎን በመተው በተለያዩ አፍራሽ ድርጊቶች ላይ የተሳተፉ ሲሆን ፣ ከዚህ ቀደም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ሁለት ጊዜ የቃል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡
ይሁን እንጂ አሁንም በንቅናቄው ሥራ አስፈፃሚነታቸውም ሆነ በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው በጋራ ለሚወሰኑ ውሳኔዎች ተገዥ ባለመሆን እና ንቅናቄውን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ አንጃኞች ጋር ሕብረት በመፍጠርና ፣ ንቅናቄው የሃሳብና የተግባር አንድነት እንዳይኖረው በሚያደርጉ ተግባራት ላይ ተሰማርተው ስተለገኙ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንዲሰጣቸው ተወስኗል፡፡
ለ. ከድርጅት ማገድ
በፓርቲው መዋቅር ውስጥ በተለያየ የሃላፊነት ደረጃ ላይ የሚገኙ የንቅናቄው መካከለኛ አመራሮችና አባላት የሆኑት:-
1. አቶ አንተነህ ስለሺ መርዕድ ፣
2. አቶ እሱባለው ሙላት ዘለቀ ፣
3. አቶ ንጉሥ ይልቃል ያለው ፣
4. አቶ ዓለሙ ወልዴ አከለ ፣
5. ዶ/ር ጌታሁን ሣህሌ ወልዴ /የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል/ ፣
6. አቶ የማነ ብርሃን ሙጬ ፣
7. አቶ ጓዴ ካሴ