Home › View all posts by Konjit Sitotaw
Blog Archives
የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ በተያዘው ዓመት ምንም ስኳር አለማምረቱን የመንግሥት ዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ፋብሪካው ስኳር ያላመረተው፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ምንጩ የኾነው የቁንዝላ ኃይል ማመንጫ ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ብልሽት ስለገጠመውና በፋብሪካው ላይ የማሽን አቅርቦት እጥረት በመፈጠሩ እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል።
ፋብሪካው ዘንድሮ 183 ሺህ ኩንታል ስኳር እንዲያመርት ታቅዶ የነበረ ሲኾን፣ ከጅምሩ ሲገነባ ግን በቀን 12 ሺህ ቶን ስኳር የማምረት አቅም እንዳለው ተገልጦ ነበር።
በጋምቤላ ከተማ ሰሞኑን በጸጥታ ስጋት ሳቢያ የነዋሪዎች የዕለት’ተለት እንቅስቃሴ መገደቡንና ውጥረት መስፈኑን ዋዜማ ከምንጮች ሰምታለች።
በከተማዋ ውጥረት የተፈጠረው፣ አንድ የከተማዋ ትራፊክ ፖሊስ አባል ባልታወቁ ታጣቂዎች መገደላቸውን ተከትሎ እንደኾነ ምንጮች ተናግረዋል።
በከተማዋ ትናንት አንዳንድ የንግድ ተቋማት ተዘግተው እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል።
በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች የውሃ አቅርቦት ችግር እንዳለ የከተማዋ ነዋሪች ለአዲስ ማለዳ ቅሬታቸውን ተናግረዋል።
“መንግስት መጀመሪያ የሕዝቡን የውሃ አቅርቦት ችግር ሳይፈታ የመንገድ ላይ እና የፓርኮችን አትክልቶች በቀን ሶስት ጊዜ ሲያጠጡ መዋል አግባብነት የሌለው ነው” ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች ተመሳሳይ የሆነ የውሃ አቅርቦት ችግር እንዳለ እና ችግሩን ለማስተካከል እየተሰራ ያለ የሚታይ ጥረት አለመኖሩን አዲስ ማለዳ ካነጋገረቻቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተረድታለች።
በጉለሌ ክፍለ ከተማ በወረዳ 4፣5 እና 7 አካባቢዎች ከፍተኛ የውሃ ችግር እንዳለ እና በሳምንት አንድ ጊዜ የሚመጣው ውሃ በበቂ ሁኔታ ሳይዳረስ እና የሚመጣበትም ሰአት ለሊት በመሆኑ ለመቅዳት አስቸጋሪ በመሆኑ ከፍተኛ ችግር ላይ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
የነዋሪዎቹን ቅሬታ በመያዝ አዲስ ማለዳ የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣንን ለማነጋገር ባደረገችው ጥረት ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል። ነገር ግን በተለያዩ አካባቢዎች ውሃ በሳምንት አንድ ቀን እንደሚመጣና ኃይል የሌለው በመሆኑ አንድ ጀሪካን ለመሙላት ከ30 እስከ 40 ደቂቃ ይፈጃል ሲሉ ነዋሪዎች በምሬት ይናገራሉ።
“እሱን ሌሊት ስንቀዳ አድረን ጠዋት ተነስተን ስራ መግባት አልቻልንም። ከሳምንት ሳምንት መድረስም ከብዶናል” ሲሉም ጠቁመዋል።
በተወሰኑ አካባቢዎች ደግሞ የአካባቢው ሰው ገንዘብ በማዋጣት የታንከር ውሃ በመኪና እያስመጡ እየተጠቀሙ እንደሆነ እና ለተጨማሪ ወጪ መዳረጋቸውን እንዲሁም በመኪናው ለሚመጣው ውሃ የመክፈል አቅም የሌላቸው ሰዎች በእጅጉ እየተጎዱ መሆኑን ቅሬታቸውን አመላክተዋል።
እንዲሁም በልደታ ክፍለ ከተማ ልደታ መናፈሻ አካባቢ “ውሃ ከጠፋ አንድ ወር ሆኖታል”
በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የስነ ሕዝብ፣ ስደትና ፍልሰት ረዳት ሚንስትር ጁሌይታ ኖይስ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ኖይስ፣ ትናንት ከተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ሃላፊ ራሚዝ አላክባሮቭ እና ከሌሎች የተመድ ሃላፊዎች ጋር ተመድ ለተረጂዎች በሚያቀርባቸው ሰብዓዊ ድጋፎች ዙሪያ መወያየታቸውን በ”ኤክስ” ገጻቸው ገልጸዋል።
ረዳት ሚንስትሯ ዛሬና ነገ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትና ዓለማቀፍ አጋሮች ጋር ስደተኖችን በሦስተኛ አገራት በማስፈር፣ በሰብዓዊ ዕርዳታ፣ ረድዔት ሠራተኞችን ከጥቃት በመጠበቅና ኢትዮጵያ ባለፈው ታኅሳስ ጀኔቫ ላይ በገባቻቸው የስደተኞች ቃል ኪዳኖች ዙሪያ ይወያያሉ።
መንግስት ወደ ኦሮሚያ ክልል የመለሳቸው ተፈናቃዮች “የከፋ በመሆኑ” ወደ ደብረብርሃን እየተመለሱ ነው
ወደ ኦሮሚያ ክልል የተመለሱ ተፈናቃዮች ወደመጡበት ደብረ ብርሃን መልሱን የሚል ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑን አዲስ ማለዳ ሰምታለች።
ተመላሾቹ በኦሮሚያ ክልል ዞኖች የሚገኙበትን ሁኔታ ሲገልጹ “እንጨት እንኳን መስበር አንችልም። ለህይወታችን አስጊ ነው፤ ከመጠለያችን መውጣት አንችልም።
በዛ ላይ ከመንግስት ምንም አይነት ድጋፍ እየተደረገልን አይደለም” ብለዋል።
ደብረ ብርሃን የሚገኙትም የከፋ ችግር ውስጥ ሲሆኑ ተፈናቃዮቹ ወደ ኦሮሚያ ክልል እንዲመለሱ ሆን ተብሎ እንዲቸገሩ እየተደረገ ስለመሆኑና… https://addismaleda.com/archives/36342 የአዲስ ማለዳን ልዩ ዘገባ ሙሉ ያንብቡ
ዋዜማ- ቅዳሜ ዕለት በየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል መዋቅር ላይ የተከሰተውን ግድፈት ተጠቅመው ገንዘብ የወስዱ አካላትን ለማደን ግብረ ኀይል መቋቋሙን ዋዜማ ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች ሰምታለች።
ከብሔራዊ ባንክና ንግድ ባንክ ባለሙያዎች እንዲሁም የፀጥታ አካላት የተካተቱበት ይህ ግብረ ኀይል በስድስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ከባንኩ ያለ አግባብ ተወስዷል ያለውን ገንዘብ ለማመለስ ያለመ ነው። ባንኩ የተወሰደበትን የገንዘብ መጠን አላሳወቀም። ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ግን ከ66 ሺህ በላይ ደንበኞች አካውንት በችግሩ መታወኩን፣ ቅዳሜ ለስድስት ሰዓታት በቆየው መታወክ 25 ሺ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር መደረጉን እንዲሁም ሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊየን ብር ተንቀሳቅሷል። ባንኩ መረጃውን ማረጋገጥ አልፈለገም።
አንዳንድ የትምህርት ተቋማት ከወዲሁ ገንዘብ ከክፍያ ማሽኖች የወሰዱና በህገወጥ ዝውውሩ የተሳተፉ ተማሪዎች ገንዘቡን ለባንኩ እንዲመልሱና ራሳቸውን ከህግ ተጠየቂነት እንዲያተርፉ የሚያሳስብ ጥሪ አድርገዋል።
በባንኩ ላይ የደረሰው ችግር የሳይበር ጥቃት አለመሆኑንና ውስጣዊ ግድፈት መሆኑን ባንኩ አበክሮ ገልጿል።
የባንኩ የውስጥ ምንጮች ለዋዜማ እንደተናገሩት ግን ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የተከናወነ አንድ መንግስታዊ የባንክ ክፍያ (ከአንድ መቶ ሚሊየን ብር ያላነሰ) ከአንድ በላይ የከፋይ ወገን በዲጂታል ፊርማ ሊያፀድቀው ሲገባ በአንድ ሰው ፈራሚነት ወደ ተከፋይ መተላለፉ የባንኩን ሀላፊዎች አስደንግጦ ነበር። አርብ ዕለት ችግሩን ለማወቅና ለመፍታት ሙከራ ሲደረግ መዋሉንና የቅዳሜ ሌሊቱ ቀውስ መከተሉን ሰምተናል።
ባንኩ የሳይበር ጥቃት አለመፈፀሙን ይናገር እንጂ ክስተቱ በባንኩ ዲጂታል መዋቅር ላይ በውስጥ አዋቂ የተፈፀመ ጥቃት ሊሆን እንደሚችል የሳይበር ደህንነት ባለሙያዎች ይናገራሉ። ባንኩ ከተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ ጋር በተያያዘ
ዋዜማ- በአዲስ አበባ በተለያየ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች በማያውቁት ስልክ እየተደወለላቸው ገንዘብ እየተጠየቁ ፤ ገንዘቡን የማይሰጡ ከሆነም ለደህንነታቸው የሚያሰጋ ማስፈራርያ እየደረሰባቸው እንደሆነ ዋዜማ ካሰባሰበችው መረጃ ተረድታለች ።
አዳማና ባህርዳር ያሉ ባለሀብቶችም በታጣቂዎች ከአንድ ጊዜ በላይ ገንዘብ መጠየቃቸውን ነግረውናል።
እየደወሉ በማስፈራርያ ገንዘብ የሚጠይቁ ግለሰቦች ፤ ባለሀብት ነው ብለው ያሰቡትን ሰው ሙሉ አድራሻ ብቻ ሳይሆን ፤ በባንክ ውስጥ የሚያንቀሳቅሱትን ገንዘብ እና የባንክ መረጃቸውን የሚያውቁ መሆኑ ደግሞ በግለሰቦች ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ተረድተናል ።
ለዚህ ዘገባ ሲባል ጉዳያቸውን የተከታተልነው እና ለደህንነታቸው ስማቸው እና የኩባንያቸው ስም እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ ግለሰብ ፤ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ማምረቻ ፋብሪካ አሏቸው ሌሎች የንግድ ስራዎች ላይም ተሰማርተዋል ።
ሆኖም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በስልካቸው እየተደወለ መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ እየተጠየቁ ፤ ይህን ማድረግ የማይችሉ ከሆነ ዛቻ እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል።የሚደውሉላቸው ሰዎች ግለሰባዊ ጉዳዮቻቸውን ሳይቀር የሚያውቁበት ደረጃ ስላሰጋቸውም መጀመርያ ይኖሩበት ከነበረበት ቦታ ሁለት ግዜ የመኖርያ ሰፈር እንደቀየሩም መረዳት ችለናል።ሁኔታውን በስራ እና ኑሯቸው ላይ ስጋት እንደፈጠረባቸውም ገልጸዋል ።
ሌላው ባለሀብት እንዲሁ በአዲስ አበባ በንግድ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ፤ በተመሳሳይ በስልክ እየተደወላላቸው መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብን እየተጠየቁ እንደሆነ ያስረዳሉ። በዚሁ ሳቢያ የእጅ ስልካቸውን ለቤተሰብ አባላቸው ሰጥተው በሌላ ስልክ እንደሚጠቀሙ ይገልጻሉ ።ሆኖም ለቤተሰብም እንፈልጋቸዋለን እየተባለ እንደሚደወል ይናገራሉ ።
ለዚህ ዘገባ ጉዳያቸውን የተመለከትናችው ግለሰቦች ከሚደውሉላቸው ሰዎች ንግግር በመነሳት ገንዘብ ካላመጣችሁ ብለው
የኤርትራ መንግሥት፣ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ዋና ጸሃፊ ኤሊዜ ኪሪስ “ኤርትራ ሕግ የሌለባት አገር ናት” በማለት በተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በቅርቡ መናገራቸውን አጣጥሎታል።
የኤርትራ መንግሥት፣ ረዳት ዋና ጸሃፊዋ የኤርትራ ወታደሮች ትግራይ ውስጥ እንደሚገኙ መግለጣቸው፣ አውቀውም ኾነ ሳያውቁ የዓለማቀፉን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ አለመቀበላቸውን ያሳያል በማለት ተችቷል።
ሃላፊዋ ያወጡት መግለጫ፣ ያልተረጋገጡና ሐሰተኛ መረጃዎችን ያካተቱ እንደኾነም ኤርትራ ጠቅሳለች።
የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ዓለማቀፍ ወንጀል ፈጽማ የማታውቀውን ኤርትራ ለቀቅ አድርጎ፣ በሌሎች የዓለም ክፍሎች ለሚፈጸሙ ዓለማቀፍ የመብት ጥሰቶች ቅድሚያ ቢሰጥ ይሻላል በማለትም ኤርትራ መክራለች።
የአሜሪካ ዓለማቀፍ ተረድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ አይ ዲ) ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ትናንት በድጋሚ በመቀሌ ጉብኝት አድርጓል።
በሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ የዋና ዳይሬክተሯ ረዳት ሶናሊ ኮርዴ የመሩት ልዑካን ቡድን፣ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ሃላፊዎች ጋር በክልሉ በተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስና በወቅታዊ ኹኔታዎች ዙሪያ መክሯል።
ልዑካን ቡድኑ ወደ አፋር ክልልም አቅንቶ፣ የዕርዳታ ሥርጭት ሂደቱን ተመልክቷል።
ከጥር ወር ወዲህ፣ ድርጅቱ በትግራይ፣ አፋር፣ አማራ፣ ኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች ለ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ተረጂዎች አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ማቅረቡን ገልጧል።
የከተመን ማክተም፤ ድሃ ጠል የከተማ ዝመና ፖሊሲ ውጤት ነው ፟ ( ያሬድ ሃይለማርያም ፡ የሰብዐዊ መብት ተሟጋች )
+++++
“Eviction is a cause, not just a condition, of poverty.”
Matthew Desmond
የዛሬው የመልዕክተ ቅዳሜ ትኩረት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እና በዙሪያዋ እየታየ ያለው የጅምላ ቤት ፈረሳ እና የዜጎች ስቃይና እንግልት ላይ ነው። ለአብዛኛው የአገራችን ሕዝብ ትንሽ የምትባለውም ደሳሳ ጎጆ ሁሉ ነገሩን ያሳረፈባት ደሴቱ ነች። ያችን ደሴቱን ስታፈርስበት ልክ አውላላ ውቂያኖስ መሃል አንድ መዋኘት የማይችልን ሰው ከነቤተሰቡ ዋኝተህ ውጣ ብለህ ከጀልባ ላይ እንደወረወርከው ያህል ነው የሚቆጠረው። በዛሬዋ ኢትዮጵያ ሚሊዮን ዜጎች ይህ እጣ ፈንታ ገጥሟቸዋል። ልጆቻቸውን ይዘው፣ እቃቸውን በየሜዳው ላይ በትነው፣ ገሚሱም ተዘርፎባቸው በተንጣለለ ውቃኖስ መሃል የመጣል ያህል አደጋ ተጋርጦባቸዋል። በላዩ ላይ መቆሚያ ያጣው የኑሮና የገበያ ግሽፈት በውቂያኖሱ ላይ የሚጋልብ ማዕበል ነው። ሌሎች ሚሊዮኖች ደግሞ ይሄው እጣ ፈንታ ዛሬ ወይ ነገ ይገጥመናል በሚል አንድ አይናቸውን ጨፍነው ተኝተው እንድ አይናቸውን ገልጠው በሌሊት በተኙበት መጥተው በላያቸው ላይ ቤት የሚንዱና የሚያፈርሱ ሕገ ወጥ ግብረሃይሎችን ኮቴ ሲጠባበቁ ያድራሉ። ያገዛዝ ሥርዓቶቹ አንድ ያልተረዱት ነገር ቢኖር ከመሬቱና ከቤቱ በከተማ ዝመና ወይም በልማት ስም ያፈናቀልከው ሕዝብ ከልቡ ፈንቅሎ ይጥልሃል። ሕዝብ ከልቡ ያወጣው ሥርዓት ደግሞ አክራሞቱ በግጭት የተሞላ ብቻ ሳይሆን አወዳደቁ እጅግ የከፋና ዘግናኝ መሆኑን ነው።
የከተማ ዝመና እና ሰፋፊ የልማት ሥራዎች ሁሌም የሚነሳባቸው ጥያቄ ምን ያህል ሰዋዊ ገጽታ አላቸው
የአብይ ቀይ መስመር ለአባቶች – የእስክንድር ነጋ የቪዲዮ መልዕክት
!function(r,u,m,b,l,e){r._Rumble=b,r[b]||(r[b]=function(){(r[b]._=r[b]._||[]).push(arguments);if(r[b]._.length==1){l=u.createElement(m),e=u.getElementsByTagName(m)[0],l.async=1,l.src="https://rumble.com/embedJS/u4"+(arguments[1].video?'.'+arguments[1].video:'')+"/?url="+encodeURIComponent(location.href)+"&args="+encodeURIComponent(JSON.stringify([].slice.apply(arguments))),e.parentNode.insertBefore(l,e)}})}(window, document, "script", "Rumble");
Rumble("play", {"video":"v4gw84h","div":"rumble_v4gw84h"});
በአፋር ክልል በኢሳ እና አፋር ጎሳዎች መካከል ግጭት መቀጠሉ ተሰምቷል ።
ትናንት በአፋር ክልል ዞን 6 ወይም ማሂ ረሱ ዞን ውስጥ በሚገኘውና አፋር እና ሶማሌ ክልሎች በሚወዛገቡበት አዳዶ ወረዳ በኹለቱ ጎሳዎች መካከል ግጭት ማገርሸቱን ምንጮች ተናግረዋል።
በኹለቱ ጎሳዎች መካከል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተደጋጋሚ ግጭቶች የተከሰቱ ቢኾንም፣ ኹለቱ ክልሎች ግን ስለ ጎሳ ግጭቶች መግለጫ ሲያወጡ አይሰሙም።
የጎሳ ግጭቱ ትናንት በድጋሚ ያገረሸው፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስተባባሪነት የኸለቱ ክልሎች የጎሳ እና የአገር ሽማግሌዎች ተገናኝተው ከመከሩና ለግጭቶችና አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሄ ለመፍታት ጠቅላይ ምክር ቤቱ የሚመራው መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ካቋቋሙ ከጥቂት ቀናት በኋላ ነው።
ዋዜማ ራዲዮ
18 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በኬንያ ዋጅር ተያዙ
በኬንያ ዋጅር ካውንቲ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገሪቱ ገብተዋል የተባሉ 18 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የዋጅር ፖሊስ ገልጿል።
18ቱ ፍልስተኞች የተያዙት በዛሬው እለት ኮሮንዲሌ በሚባል የከተማይቱ አውራጃ በተደረገ ኦፕሬሽን መሆኑ ተነግሯል።
ፍልሰተኞቹ በኮሮንዲሌ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ ሲሆን በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኬንያ በመግባት ክስ እንዲመሰረትባቸው የሚያስችለውን ሂደት በመጠባበቅ ላይ እንዳሉ ተጠቁሟል።
በኬንያ በህገ-ወጥ መንገድ ገብተው የተገኙ የሌላ ሀገር ዜጎች የመባረር ወይም እስራት ሊገጥማቸው እንደሚችል ሲገለፅ በተጨማሪም፣ በኬንያ የኢሚግሬሽን ህጎች በተገለፀው መሰረት ቅጣት ሊጣልባቸው እንደሚችልም ነው የተገለፀው።
አሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የግጭትና መረጋጋት ረዳት ሚንስትር የኾኑት አን ዊትኮውስኪ ከመጋቢት 8 እስከ 17 በኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሞዛምቢክ ይፋዊ ጉብኝት ያደርጋሉ።
ረዳት ሚንስትሯ በኢትዮጵያ እና ኬንያ በሚኖራቸው ቆይታ፣ አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን ለቀጠናዊ ጥረቶች የምታደርጋቸውን ጥረቶች ለማጠናከር ያለመ ውይይት እንደሚያደርጉ መስሪያ ቤታቸው ዛሬ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።
ረዳት ሚንስትሯ፣ በሦስቱ አገራት ከመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከሲቪል ማኅበረሰብና ከዓለማቀፍ አጋሮች ተወካዮች ጋር የግጭት ተጎጂ ማኅበረሰቦችን መልሶ ለማቋቋም በማደረጉ ጥረቶች ዙሪያ ጭምር እንደሚወያዩና አሜሪካ በዚኹ መስክ ለሦስቱ አገራት እያደረገች ያለችውን ድጋፍ እንደሚገመግሙ ተገልጧል።
የአሜሪካ የላይኛው ምክር ቤት አባላት የባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ እንዲሰጥ ጠየቁ
የአሜሪካ የላይኛው ምክር ቤት አባላት ሴናተር ቲና ስሚዝ፣ ጄፍ ሜርክሌይ፣ ኤሚ ክሎቡቻር፣ ጆን ሂክንሎፐር፣ ክሪስ ቫን ሆለን፣ እና ቲም ኬይን፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ እንዲሱጡ ጠይቀዋል።
ሴናተሮቹ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አንቶኒ ብሊንከን እና የአሜሪካ አለማቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) ዋና ዳይሬክተር ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ በጦርነት እና ግጭት ምክንያት ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ ድጋፍ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጡ በፃፉት ደብዳቤ ጥሪ አቅርበዋል።
በኢትዮጵያ ያለው የእርስ በርስ ግጭትና የአየር ንብረት መዛባት በሀገሪቱ ያለውን አስከፊ ሰብዓዊ ቀውስ አባብሶታል ያሉት የምክር ቤት አባላቱ 4.4 ሚሊዮን ሰዎች በአገር ውስጥ እንደተፈናቀሉና ኢትዮጵያ ወደ 942,ሺ የሚጠጉ የጎረቤት ሀገራት ስደተኞችን አስጠልላ እንደምትገኝ ገልፀዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ 20.1 ሚሊዮን የሚገመቱ ሰዎች አፋጣኝ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ሴናተሮቹ የጠቆሙ ሲሆን በኢትዮጵያ በ2024 የሰብዓዊ እርዳታ እቅድ መሰረት ለዜጎች ድጋፍ ለማድረግ 3.24 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገውና ለ6.6 ሚሊዮን ሰዎች የምግብ እርዳታ ለማድረግ 500 ሚሊዮን ዶላር በአስቸኳይ የሚያስፈልግ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ሴናተሮቹ የባይደን አስተዳደር በሀገሪቱ የሚደረገውን ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማሳደግ ከሌሎች ለጋሽ አገራትና የተራድኦ ድርጅቶች ጋር እንዲተባበር የጠየቁ ሲሆን በተጨማሪም በሀገሪቱ ሰብአዊ ፍጡራን ላይ ተፅዕኖ የሚያደርጉ ግጭቶችን ለማስወገድ ግፊት እንዲደረግም ጠይቀዋል።
በአብይ አህመድ አገዛዝ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በር ላይ ታፍነው ከተወሰዱ ተማሪዎች መካከል፦
1 ,ጆን ተሻገር
2, ቃልኪዳን እያሱ
3, ቴዎድሮስ ይበልጣል እና
4, አራጋው ሞሳው ይገኙበታል።( ምስላቸው ከታች ይገኛል
ከተማሪዎቹ መካከል ሦስቱ የ4ኛ አመት እና አንደኛው ደግሞ የ3ኛ አመት የህግ ተማሪዎች መሆናቸውን ለማወቅ ችለናል። ተማሪዎቹም እስካሁኗ ሰዓት የት እንዳሉ እንደማይታወቅ ከቅርብ ጓደኞቻቸው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በአብይ አህመድ አረመኔአዊ አገዛዝ አማራ ከሆንክ የትም እና በምንም አይነት ሁኔታ ትታገታለህ፣ ትታፈናለህ፣ ትገደላለህ፣ ትፈናቀላለህ።
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ከእስር ተፈቱ
ላለፈው አንድ ወር ከ12 ቀን በእስር ላይ የቆዩት፤ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ዛሬ ከሰዓት መለቀቃቸውን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ)፣ የቀድሞው የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘውም “በምህረት” ከእስር እንደሚፈቱ ታማኝ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ዶ/ር ደሳለኝ “በዋስትና እንደሚለቀቁ” የተነገራቸው፤ ዛሬ ምሳ ሰዓት ገደማ መሆኑን በስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ገልጸዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ፤ ጥር 22፤ 2016 ምሽት በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ታስረው የቆዩት በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው የፌደራል የወንጀል ምርመራ የእስረኞች ማቆያ ስፍራ ነው።
ዶ/ር ደሳለኝ ከእስር ከመለቀቃቸው ከሰዓታት በፊት በተካሄደ የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ፤ ከፓርላማው “የምክር ቤት ጉዳዮች አማካሪ ኮሚቴ” አባልነታቸው ተነስተዋል። ይህ ኮሚቴ “የተወካዮች ምክር ቤት የሚወያይበትን ማንኛውም አጀንዳ የመቅረጽ” ኃላፊነት ያለበት ሲሆን የሚመራው በፓርላማው አፈ ጉባኤ ነው። በዛሬው ስብሰባ፤ ላለፉት ሰባት ወራት በእስር ላይ ያሉት ሌላኛው የአብን የፓርላማ ተወካይ አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት መነሳቱ ይታወሳል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አዲስ አበባን ጨምሮ ከተለያዩ ክልሎች ተወካዮች ጋር ተከታታይ ውይይቶች ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ወክለው በውይይቶቹ የተገኙ ግለሰቦች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በርካታ ጥያቄዎች አቅርበዋል፡፡ ከጥያቄዎቹ መካከል የልማትና የፀጥታ ጉዳዮች ሰፊ ትኩረት ያገኙ ነበሩ፡፡ የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ፣ የውኃ፣ የጤና፣ የትምህርትና መሰል መሠረተ ልማቶች ከኑሮ ውድነትና ተዛማጅ ጉዳዮች ጋር ተነስተው ነበር፡፡ በፀጥታ ጉዳይም በየአካባቢው በሚካሄዱ ግጭቶች ምክንያት እየደረሱ ያሉ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳቶች በስፋት ተዳሰዋል፡፡ ብዙዎቹ የተነሱት ጥያቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ በገዥው ፓርቲና በሚመሩት መንግሥት የሚታወቁ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ምላሽ ሲሰጡ ጥያቄዎቹን ተራ በተራ በማንሳት በማነፃፀሪያዎች እያስደገፉ ነበር፡፡ ሕዝብና መንግሥት በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ሊያግባባቸው የሚችል አማካይ እንዲኖር አንዳንድ መሠረታዊ ጉዳዮች መነሳት አለባቸው፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ ‹‹በወንዝ ዳር ፕሮጀክት›› እና ‹‹በመንገድ ኮሪደር ልማት›› መርሐ ግብሮች፣ ይዞታዎችን የማፍረስና አጥሮችን ወደ ውስጥ የማስገባት ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ነው፡፡ ‹‹ስማርት ሲቲ›› በተሰኘው ከተማን የመለወጥ ግዙፍ እንቅስቃሴ፣ የከተማዋን ገጽታ የሚለውጡ ተግባራት ሲከናወኑ በከተማ አስተዳደሩና በነዋሪዎች መካከል መግባባት መኖር አለበት፡፡ አገሩ ወይም ከተማው በልማትና በዕድገት ስትለወጥለት የሚጠላ ዜጋ ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ልማቱም ሆነ ዕድገቱ የጋራ ሲሆን፣ ከአንድ አካባቢ ተነስተው ወደ ሌላ የሚሠፍሩ ዜጎች፣ በተቻለ መጠን ከነበሩበት ያላነሰ ተስማሚ የመኖሪያና የመሥሪያ ቦታ ማግኘታቸው መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ በከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ እንደተነገረው ነዋሪዎች የተሻለ መኖሪያና መሥሪያ አግኝተው ከሆነ መልካም ነው፡፡ ነገር ግን የተባለውና እየተደረገ ያለው የማይመጣጠን ከሆነ ማስተካከያ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ ሐሙስ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም. በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካይ የሆኑትን የአቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት ሊያነሳ ነው።
አቶ ክርስቲያን ታደለ ፓርላማ የገቡት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ቋሪት ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)ን ወክለው ተወዳድረው ነው።
አቶ ክርስቲያን ፓርላማ ከገቡ በኋላ በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነዋል።
ሆኖም በአማራ ክልል የተፈጠረውን የፀጥታ መደፍረስ ተከትሎ ባለፈው ሐምሌ ወር በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ላላፉት ሰባት ወራት በእስር ላይ ይገኛሉ።
አቶ ክርስቲያን በቁጥጥር ስር ከዋሉ ከሰባት ወራት በኋላ ነው ምክር ቤቱ ያለመከሰስ መብታቸውን ነገ የሚያነሳው።
ቢቢሲ የተመለከተው እና ለፓርላማ አባላት የተላከው አጀንዳ የአንድ የምክር ቤት ያለመከሰስ መብት እንደሚነሳ ያትታል።
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የቢቢሲ ምንጮች ያለመከሰስ መብታቸው የሚነሳው የምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከአቶ ክርስቲያን በተጨማሪ ሌላኛው የአብን ተወካይ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔም ባለፈው ጥር መጨረሻ ላይ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወሳል።
ሆኖም ግን ምክር ቤቱ በአሁኑ ወቅት ያለመከሰስ መብት የሚያነሳው የአንድ የምክር ቤት አባልን ብቻ ነው።
የአገሪቱ ሕገ መንግሥት፤ “ማንኛውም የምክር ቤት አባል ከባድ ወንጀል ሲፈጽም እጅ ከፍንጅ ካልተያዘ በስተቀር ያለ ምክር ቤቱ ፈቃድ አይያዝም፤ በወንጀልም አይከሰስም” ሲል ይደነግጋል።
ነገ የአቶ ክርስቲያን ያለመከሰስ መብት የአባላትን አብላጫ ድምጽ አግኝቶ የሚነሳ ከሆነ በሥራ ላይ ባለው ምክር ቤት ያለመከሰስ
ዋዜማ- መንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅጥር ሲፈጽሙ ሀሰተኛ የትምህርት ሰነድን ያቀረቡ 220 ሰራተኞቹን ማበረሩን ዋዜማ ከባንኩ ምንጮች ሰምታለች።
ባንኩ ከሰሞኑ ሀሰተኛ የትምህርት ሰነድ አቅርበዋል በሚል ከስራ ያባረራቸው ሰራተኞቹ ባለፈው አመት ንግድ ባንኩ ባወጣው የስራ ማስታወቂያ ተወዳድረው በማለፍ በስራ ላይ የነበሩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፈው አመት በአንድ ቅጥር ክብረ ወሰን በተባለ ሁኔታ ወደ 12 ሺህ ሰራተኞችን መቅጠሩ ይታወሳል።ሆኖም ባንኩ እነዚህ ተቀጣሪዎች ፈተና አልፈው የስራ ቅጥር ውል ፈጽመው ወደ ስራ ከገቡ በሁዋላ ተመርቀንበታል በሚል ያስገቡትን የከፍተኛ ትምህርት ሰነድ ፣ በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በመላክ በጀመረው የማጣራት ስራ ከ200 ዋዜማ በላይ ሰራተኞች ያቀረቡት የትምህርት ሰነድ ሀሰተኛ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብሏል።
ተቀጣሪዎች የፈጸሙት የሰነድ ማጭበርበር ሁለት አይነት መልክ እንዳለው የተገለጸ ሲሆን ፣ የተወሰኑት ተቀጣሪዎቹ እንዳስገቡት ሰነድ የመጀመርያ ዲግሪ ያላቸው ቢሆንም ፣ ተወዳዳሪነታቸውን ከፍ ለማድረግ በማሰብ በትክክል ካመጡት የመመረቂያ ውጤት ላይ ከፍተኛ የሆነ የነጥብ ጭማሬ እንዳላቸው በማስመሰል ሀሰተኛ የትምህርት ሰነድ ማሰራታቸው ተረጋግጦባቸዋል።
ሌሎቹ ደግሞ ለባንኩ ለቅጥር ያስገቡት የከፍተኛ ትምህርት ሰነድ ፍጹም ሀሰተኛ መሆኑ በመረጋገጡ ከስራ እንዲሰናበቱ ተደርገዋል።ንግድ ባንኩ ጉዳዩን ወደ ህግ ይውሰደው አይውሰደው ለማወቅ ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።
ሆኖም ባለፈው አመት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀጠራቸው ሰራተኞች ላይ የጀመረው የትምህርት ሰነድ ማጣራት እስካሁን አለመጠናቀቁን ፤ ይህ የትምህርት ሰነድ ከአምና ተቀጣሪዎች ባለፈ ቀድሞ ተቋሙን በተቀላቀሉ ባልደረቦችም ላይ የትምህርት ሰነዶች ትክክለኝነትን በስፋት ወደ ማጣራት እንደሚገባም ሰምተናል።
በኢትዮጵያ የተለያዩ የመንግስት
” ፍርዱ ለሚዲያ 16 ዓመት ከተባለ በኃላ ወደ 10 ዓመት ዝቅ እንዳለ ሰምቻለሁ ” – ጸጋ በላቸው
” ጉዳዩ ለቢሮዉም ሆነ ለኔ አዲስ ነው ” – ወ/ሮ ወይንሸት ብርሀኑ
በሀዋሳ ከተማ የዳሽን ባንክ ሰራተኛ ከሆነችዉ ጸጋ በላቸዉ ጋር በተያያዘ በጠለፋና አስገድዶ መድፈር ወንጀል ተከሶ የነበረው ኮንስታብል የኃላመብራት ወ/ማርያም ” ለብዙዎች አስተማሪ ይሆናል ” በተባለ መልኩ የ16 አመት ጽኑ እስራት እንደተፈረደበት ይታወሳል።
ይሁንና ይህ ለሚዲያ የተገለጸው ፍትህ ከተበዳዩዋ እውቅና ውጭ በሆነ መልኩ የእስራት ፍርዱ ከ16 አመት ወደ 10 መቀነሱን እንደሰማች በሶሻል ሚዲያ ባስተላለፈችዉ በዕንባ የታጀበ ቅሬታ ገልጻለች።
ወይዘሪት ጸጋ ፤ ጉዳዩን ለማወቅ ብዙ ድካም እንደነበረዉና በመጨረሻ የሰማችዉ ጉዳይ እጅግ እንዳሳዘናት በመግለጽ አቤቱታዋን አሰምታለች።
ጸጋ ፤ ” የፍርድ ሂደቱ በጥሩ ሂደት ሄዶ ፍርድ ቤት 16 ዓመት ተፈርዶበታል በሚል ለኔ ውሳኔ ሰጥቶኝ ነበር ፤ አሁን ግን እኔ በማላውቅበት ሁኔታ የፍርዱ ውሳኔ ይግባኝ ብሎ #እንደተስተካከለ ሰምቻለሁ፤ ይህ ውሳኔ መቼ እንደተላለፈ አልተነገረኝም ለግል ጉዳዬ የውሳኔ ወረቀት እንዲሰጠኝ በተደጋጋሚ ወደ ፍርድ ቤት በምደውልበት ጊዜ ምላሽ እየተሰጠኝ አልነበረም ጉዳዩን አጥብቄ በተደጋጋሚ ስጠይቅ ውሳኔው በይግባኝ እንደተስተካከለ ተነገረኝ ” ስትል አስረድታለች።
ውሳኔው አሁን ላይ ወደ 10 ዓመት ዝቅ እንዳለ የገለፀችው ጸጋ ፤ በድርጊቱ እጅግ እንዳዘነችና ካሳለፈችው የስቃይ ሁኔታ ጋር በፍፁም እየሚገባ እንዳልሆነ በእምባ ታጅባ ገልጻለች።
ከዚህ ባለፈ ህዝብ የማያውቀው ብዙ ነገር እንደተፈፀመ ፤ ከጠለፋው እገታ ከተለቀቀች በኃላ በማታውቀው ምክንያት
ደቡብ አፍሪቃ ለመግባት በሚሞክሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የሞት አደጋ ተባብሷል
ወደ ደቡብ አፍሪቃ ለመግባት በሚሞክሩ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች ላይ የሚደርሰው የሞት አደጋ እየተባባሰ መምጣቱን ከኬኒያ እና ታንዛኒያ እሥር ቤቶች ተለቀው ዛሬ በኢትዮጵያ ሞያሌ በኩል ወደ አገራቸው የገቡ ተመላሽ የአይን እማኝ ፍልሰተኞች መመልከታቸውን ዶይቼ ቬለ ዘግቧል።
በስደት ጉዞና በእሥር ቆይታቸው አስቸጋሪ ፈተናዎችን ማለፋቸውን የተናጉሩት ከፍልሰት ተመላሾቹ ” ዜጎች በጉዞ ላይና በበረሃና በእሥር ቤቶች ለሞት ሲዳረጉ በርካቶች ሕይወታቸው ሲያጡ ተመልክተናል። አብዛኞቹ የሞት አደጋ የሚጋጥማቸው በጉዞ ላይ ሲሆን በበረሃ፣ እስር ቤቶች ውስጥ በረሃብና በበሽታ የሞቱ ሰዎችንም አይተናል” ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃድያ ዞን ነዋሪ የሆኑት ወጣት ታደሰ ተመስገን እና ብሩክ ግርማ በሞያሌ በኩል ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ከዓመት በፊት ጉዞ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ እነ ታደሰ የተስፋይቱ ምድር ብለው ጉዞ የጀመሩባት ደቡብ አፍሪካ እንዳሰቡት መድረስ አልቻሉም። ይልቁንም በተሽከርካሪ ኮንቴይነር ውስጥ ተደብቀው ከኬኒያ ሞምባሳ ወደ ታንዛኒያ በበረሃ በመጓዝ ላይ ሳሉ አየር ለመውሰድ በወጡበት በአገሬው ፖሊሶች ተይዘው ለእሥር መዳረጋቸውን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ ሞያሌ በኩል ዛሬ ወደ አገራቸው የተመለሱት ከሦስት መቶ በላይ ፍልሰተኞች ከስድስት ወራት እስከ አንድ ዓመት በእሥር መቆየታቸው ሲገለፅ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙት የሃድያና የከምባታ ዞኖች ወደ ደቡብ አፍሪካ ለሚደረገው ፍልሰት በመነሻነት የሚጠቀሱ መሆኑም ነው የተገለፀው።
ኦነግ፣ መንግሥት ያቋቋመው ሚስጢራዊ የጸጥታ ኮሚቴ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚፈጽማቸው ግድያዎች እንዲቆሙ ሕዝቡ፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል።
የጸጥታ ኮሚቴው አባላት ለፈጸሟቸው ተግባራት ተጠያቂ እንዲኾኑ እነዚኹ አካላት ጥረታቸውን እንዲቀጥሉም ኦነግ ጥሪ አድርጓል። ኦነግ ጨምሮም፣ በአብዛኞቹ የክልሉ ዞኖች ከፍርድ ውጭ የኾኑ ግድያዎች፣ የዘፈቀደ እስሮች፣ ስቃይ እና ምዝበራ እንደቀጠለ ነው ብሏል።
የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተካተቱበት ሚስጢራዊ የጸጥታ ኮሚቴ የሚያስፈጽማቸውን ከሕግ ውጭ የኾኑ ግድያዎች ሮይተርስ በጥልቅ ምርመራ በቅርቡ አጋልጧል ያለው ኦነግ፣ የሚስጢራዊው ኮሚቴ መዋቅር እስከ ዞን፣ ወረዳ፣ ከተማ እና ቀበሌ አስተዳደሮች ድረስ የተዘረጋ መኾኑን ጠቅሷል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት እና ዓለማቀፍ አጋሮች በተያዘው የአውሮፓዊያን ዓመት ለ15 ሚሊዮን ዕርዳታ ፈላጊዎች ዕርዳታ ለማቅረብ ማቀዳቸውን ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።
ቢሮው፣ ለ15 ሚሊዮን ሰዎች ዕርዳታ ለማቅረብ 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ በሪፖርቱ ላይ ገልጧል።
ከዚህ የዕርዳታ ገንዘብ ውስጥ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላሩ ለምግብ ዕርዳታ ብቻ እንዲውል መታቀዱን የገለጠው ቢሮው፣ ኾኖም ለምግብ ዕርዳታ ከታሰበው ገንዘብ ውስጥ እስካሁን የ527 ሚሊዮን ዶላር ክፍተት እንዳለ ጠቁሟል።
ከመጋቢት እስከ ቀጣዩ ዓመት መስከረም ብቻ 9 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተብሏል። የዓለም ምግብ ፕሮግራም በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ለ5 ሚሊዮን ሰዎች ዕርዳታ ለማቅረብ የሚበቃ ገንዘብ ከወዲሁ ማግኘቱም ተገልጧል።
አፍሪካ ኅብረት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሃት በፕሪቶሪያው ግጭት ማቆም ስምምነት ዙሪያ በኹለት ወራት ውስጥ ተመሳሳይ ግምገማ ለማድረግ እንደተስማሙ አስታውቋል።
በትግራይ ክልል ሰላም፣ ጸጥታና መረጋጋት አጠናክሮ ለማስቀጠል ኹለገብ ምክክሮችን ለማድረግ መስማማታቸውን ኅብረቱ ባወጣው መግለጫ ገልጧል።
ኹለቱ ወገኖች የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት ለመተግበር በድጋሚ ቁርጠኛነታቸውን ማረጋገጣቸውንና ተከታታይ ምክክሮችን ለማድረግ መስማማታቸውንም ኅብረቱ ጠቁሟል።
ኹለቱ ወገኖች፣ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ተጨማሪ ጥረት የሚጠይቁ ጉዳዮችንም ለይተዋል ተብሏል።
አፍሪካ ኅብረት ትናንት ባዘጋጀው የስምምነቱ አተገባበር ግምገማ ላይ፣ የፌደራል መንግሥት፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርና የሕወሃት ባለሥልጣናት እንዲኹም የኅብረቱ አሸማጋይ ቡድን አባላትና ታዛቢዎች ተገኝተዋል።
እኛን የመረረን ያንተን ድምጽ መስማት ነው
(ዘላለም ጸጋዬ)
ናፍቆቴ፣ምኞቴ…ወደ አገሬ መሄድ ሳስብ መጀመርያ ደስ ደስ የሚለኝ ነገር ቢኖር ጠዋት በማለዳ በተኛሁበት…ቅዳሴ እና አዛን መስማት ነው…ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድምጻችሁ እረበሸኝ፣ ቱሪስቶች ተረበሹ ያለበትን ቪድዮ ሥሰማው ስቅጥጥ ነው ያለኝ… የጠቅላይ ሚንስትር ሞልፋጣ።
እዚህ ላሉት ነጭ ጉዋደኞቼ እኮ ይሄ አገር ቦሪንግ ነው…የእንጀራ ነገር ሆኖብኝ ተዚህ መጥቼ እንጂ የኔ አገር ድምጽ አላት፣ውብ ናት እስትረስ አናውቅም እያልኩ ነው ዘወትር የማስቀናቸው።ከቅዳሴ እና አዛኑ ባሻገር ቦሌ ቦሌ ፒያሳ ፒያሳ የሚል የወያላ ጥሪ፣የአውራ ዶሮ ጩሀት፣የውሾች ጸብ፣የወፎች ዝማሬ፣የእረኞች ዋሽንት፣የጎረምሳ ፉጨት፣ የወንዞች ፉዋፉዋቴ… በቃ ምን ልበላችሁ የአገሬ ድምጹዋ ይናፍቀኛል።
እናማ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጮሀችሁብኝ ያሉት የያዛቸው ሰይጣን ደብሮት ነው እንጂ ስንት ሺ ዘመን ሲሰማው የኖረውን ህዝብ ወክለው አይደለም።ይልቅ የኢትዮጵያ ህዝብ መስማታ የሰለቸው ድምጽ ቢኖር የራሱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ነው።
በደቡብ ኦሞ የሚነገሩት የኦንጎታ እና የባጫ ቋንቋዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል ተባለ
Ongota and Bacha Language in Ethiopia
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በደቡብ ኦሞ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ባህልና ቋንቋዎች ላይ ያተኮረ ብሔራዊ የምክክር መድረክ በጂንካ ያካሄደ ሲሆን በደቡብ ኦሞ የሚነገሩት የኦንጎታ እና የባጫ ቋንቋዎች የመጥፋት አደጋ እንደተጋረጠባቸው በመድረኩ ተገልጿል።
በየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ካሉት 32 ብሔረሰቦች መካከል 16ቱ በአሪና ደቡብ ኦሞ የሚገኙ እንደሆኑ ሲገለፅ ኦንጎት ከአምስት በማይበልጡ የብራይሌ ብሔረሰብ አባላት ብቻ የሚነገር ሲሆን ፥ የባጫ ብሔረሰብ የሚናገሩት ቋንቋም የመጥፋት አደጋ ከተደቀነባቸው የደቡብ ኦሞ ቋንቋዎች ውስጥ አንዱ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመሆኑም ማህበረሰቡ የአፍ መፍቻ ቋንቋዎችን ለትውልዱ ለማስተላለፍ በቀዳሚነት ኃላፊነት እንዳለበት በማንሳት የመንግሥትና የትምህርት ተቋማትም ቋንቋዎች ተሰንደው እንዲያድጉ በጋራ መሥራት እንደሚያስፈልግም ነው የተለገለው።
የሱዳን ወታደራዊ መሪ በረመዳን የጾም ወር የቀረበውን የተኩስ አቁም ጥሪ ውድቅ አደረጉ
የሱዳን ጦር ሰራዊት ምክትል አዛዥ ሌተናል ጀነራል ያሲር አል አታ፣ በረመዳን የጾም ወር ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል (RSF) ጋር የሚያደርጉትን ግጭት እንዲያቆሙ የተኩስ አቁም ጥሪ ቢቀርብም የቀረበውን ጥሪ ውድቅ ማድረጋቸው ተነግሯል።
በሱዳን ካርቱም፣ ዳርፉር፣ ኮርዶፋን እና አልጃዚራ ለ11 ወራት በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉና በጦር ሰራዊቱ መሃከል የተደረገው እንዲሁም በሀገሪቱ በርካታ ሰብዓዊ ቀውስ ያስከተለውን ጦርነት እንዲቆም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ባለፈው አርብ ጥሪ አቅርቦ ነበር።
የሱዳን ጦር ሰራዊት ምክትል አዛዥ ሌተናል ጀነራል ያሲር አል አታ በቅዳሜ እለት በሀገሪቱ የፍትህ እና የእኩልነት ንቅናቄ (JEM) ሃይሎችን የማስመረቅ ስነስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር የተኩስ አቁም ጥያቄን እንደማይቀበሉ እና ወታደሩ እና ህዝቡ በሶስተኛ ወገን የሚቀርብን የእርቅ ሰላም ስምምነት ጥያቄ እንደማይቀበሉ ማሳወቃቸውን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል።
የፀጥታው ምክር ቤት ያቀረነበውን የእርቅ ጥሪ ተከትሎ፣ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ (RSF) ቅዳሜ በሰጠው መግለጫ፣ ” ለማድረግ የታቀደውን ሰብዓዊ የተኩስ አቁም በመቀበል፣ በጋራ ስምምነት ላይ ተመስርቶ የተደረሱ እርምጃዎችን ለመውሰድ ውይይቶች ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናችንን እንገልጻለን ” ማለታቸውን አልጀዚራ በዘገባው አመልክቷል።
የጦር ሰራዊቱ ምክትል አዛዥ አል አታ በሁለቱ ሀይሎች መሃከል ድርድር ሊደረግ የሚችለው ፥ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ወታደሮች በዳርፉርና በኮርዶፋን የያዙትን ከተሞች በመልቀቅ ከካርቱም መውጣታቸው ሲረጋገጥና ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ሲያስረክቡ እንደሆነ ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል ነው የተባለው።
በሀዋሳ ከተማ የህዝብ ትንራንስፖርት አገልግሎት (ታክሲ) የሚሰጡ አሽከርካሪዎች ፤ ” የነዳጅ ጉዳይ ስቃያችንን አበላን ፤ የመፍትሄ ያለህ !! ” ሲሉ ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የታክሲ አገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች ፤ “ሰርተን ከምንገባበት ለነዳጅ ሰልፍ ቆመን የምንውለበት እየበለጠ ነው ” ብለዋል።
የነዳጅ ችግሩ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ዛሬም ድረስ የቀጠለ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።
የቤተሰብ አስተዳዳሪ እንደሆኑም በመግለፅ ”
ካልሰራን ልጆቻን ምን ይብሉ ? ፤ እኛስ ምን በልተን እንደር ? ይህ ጉዳይ መፍትሄ ይፈልጋል ” ብለዋል።
ከሳምንታት በፊት በዚሁ በሀዋሳ ከተማ ያሉ አሽከርካሪዎች ፤ ” በረዣዥም ሰልፍችና በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ስራችን በአግባቡ መስራት አልቻልንም ” በሚል ምሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተው ነበር።
አሽከርካሪዎች ፤ ሁሉም ማደያዎች በአግባቡ አለመስራትና ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ መኪኖች ለነዳጅ ሰልፍ ተገፍተዉ ከመግባት ባለፈ ከፍተኛ መጠን ያለዉ ሳልቫቲዮ ገጥመዉ መምጣታቸው ቀኑን ሙሉ ተሰልፈዉ እንኳን መቅዳት እንዳይችሉ ምክኒያት እንደሆነባቸው ገልጸው ነበር።
በወቅቱ እየተነሳ ላለው ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ገበያ ልማት ቢሮ የስነልኬት ባለሙያው አቶ ሀብታሙ መኮንን ፤ ችግሩ መኖሩን አምነው ፤ ከጅቡቲ የሚመጣው ነዳጅ መዘግየቱን ተከትሎ የተፈጠረው ክፍተት ለችግሩ ምክንያት እንደሆነ ገልጸው ነበር።
ችግሩም ” ወደፊት ይቀረፋል ” የሚል ተስፋ እንዳላቸዉ ማመልከታቸው ይታወሳል።
የዓለማቀፉ ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ኮምንኬሽን ዳይሬክተር ጁሊ ኮዛክ፣ የድርጅቱ ልዑክ “በቀጣዮቹ ሳምንታት” በኢትዮጵያ የብድር ጥያቄ ዙሪያ ከባለሥልጣናት ጋር ለመነጋገር ወደ አዲስ አበባ እንደሚጓዝ ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
ኾኖም ልዑካን ቡድኑ መጋቢት ወር ከማለቁ በፊት ወደ ኢትዮጵያ ይጓዝ እንደኾነ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ሃላፊዋ ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል። የፓሪስ ክለብ አበዳሪ አገራት እስከ መጋቢት 23 ገደማ መንግሥት ከድርጅቱ ጋር አዲስ የብድር ስምምነት ላይ ካልደረሰ፣ ለአገሪቱ የሰጧትን የብድር መክፈያ እፎይታ እንደሚሰርዙ ቀደም ሲል ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
ኮዛክ፣ አሜሪካ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ ሰሞኑን ያነሳችው ስጋት በብድር ጥያቄው ላይ ሊኖረው ስለሚችለው ተጽዕኖም ተጠይቀው ነበር። ግጭቱ አሳሳቢ መኾኑን የጠቀሱት ሃላፊዋ፣ ድርጅቱ ኹኔታውን እየተከታተለ መኾኑን፣ የአሜሪካን ስጋት እንደሚገነዘብና ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ ይፈታል ብሎ እንደሚጠብቅ በመግለጽ ብቻ መልስ ሰጥተዋል።
ምንጭ ፡ https://www.imf.org/en/News/Articles/2024/03/07/tr030724-transcript-of-imf-press-briefing
ኢትዮጵያ በኤደን ባህረ ሰላጤ ላይ ልታገኝ ባሰበችው የባህር በር ምትክ ለሱማሊላንድ ልትሰጥ ያሰበችውን የሀገር እውቅና ለመተው እያሰበች እንደሆነ አለም አቀፍ ሚድያዎች እየዘገቡ ነው።
እኔም ከሰሞኑ በተካፈልኩበት አንድ የዲፕሎማቲክ አባላት መግለጫ ላይ ይህ ጉዳይ የተነሳ ሲሆን “አንድም ከአለም አቀፍ አጋሮች፣ ሀገራት እና ተቋሟት በተሰነዘረ አስተያየት እና በተደረገ ጫና…ሁለትም አሁናዊ አለም አቀፋዊ እና ቀጠናዊ ክስተቶችን ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሱማሌላንድ እውቅና መስጠት የሚለው ሀሳብ እንደማያስኬድ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ግንዛቤ እንደተወሰደ እናውቃለን” የሚል አስተያየት ተሰጥቷል።
በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ የመግባብያ ስምምነቱ ተግባራዊ ቢሆን የሁቲ አማፅያንን ጨምሮ በአካባቢው ያሉ የፀጥታ ችግሮችን ለመቅረፍ መፍትሄ እንደሆነ ተደጋግሞ የተነሳ እንደነበር፣ ይህም ከዩናይትድ ኪንግደም አቋም ጋር ቢመሳሰልም ዩኬ ሀሳቧን ወደ መሬት ለማስረገጥ እንዳልቻለች ይጠቅሳሉ።
በሱማሌላንድ በኩል በዚህ ዙርያ እስካሁን አስተያየት ያልተሰጠ ሲሆን ከዚህ ቀደም ግን ‘እውቅና ከሌለ ስምምነቱም የለም’ (No recognition, no deal!) ብለው ደጋግመው ተደምጠው ነበር።
Image via Bloomberg
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የጉራጌ ሕዝብ ይቅርታ እንዲጠይቃቸው ትዕዛዝ እንዳስተላለፉ ምንጮች ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይቅርታ ይጠይቁኝ ያሉት በመጋቢት ወር 2015 ዓ/ም ወደ ወልቂጤ በሄዱበት ወቅት “የወልቂጤ ነዋሪ ማሕበረሰብ ለምን በነቂስ ወጥቶ አልተቀበለኝም” በሚል ነው።
የወልቂጤ ሕዝብ ከክልልነት ጥያቄ ጋራ በተያያዘ በነበረው አመጽ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ብዙ መከራ ደርሶበት ሥለነበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ከተማው በመጡበት ወቅት ሕዝቡ ተቃውሞውን ለመግለጽ በአድማ ቤቱን ዘግቶ ተቀምጦ ነበረ። በዚህ የተቃውሞ ድርጊት የጉራጌ ተወላጅ የሆኑ የፌደራል እና የክልሉ የመንግሥት ሥልጣን ላይ ያሉ የብልጽግና ካድሬዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ በገጠማቸው ተቃውሞ ተቆጥተው እንደነበረ ተነግሯል። ይህንን ለማካካስ የጉራጌ የብልጽግና ፓርቲ ካድሬዎች የይቅርታ ኮሚቴ አዋቅረው በጉራጌ ሕዝብ ሥም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ይቅርታ ለመጠየቅ እየተዘጋጁ እንደሆነም ተገልጿል።
በጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር ዐቢይ ዘመነ መንግሥት የጉራጌ ሕዝብ ላይ ከብዙ በጥቂቱ የሚከተሉትን በደሎች ተፈጽሞበታል። ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕዝቡን ይቅርታ ሊጠይቁት ይገባል።
1/ በሀገሪቱ ሕገ መንግሥት በተደነገገው መሠረት የብልጽግና ፓርቲ አባላት የሆኑ የጉራጌ ዞን የሕዝብ ተወካዮች በአብላጫ ድምጽ ጉራጌ ክልል እንዲሆን ጥያቄ ለኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አስገብተው ነበረ።
** በኢትዮጵያ የብሔር ፌደራሊዝም መካለል እስካለ ድረሰ የጉራጌ ሕዝብ ራሱን የቻለ ክልል እንዲሆን ለረዥም ዓመታት ሲጠየቅ መቆየቱ ይታወቃል። ለሌሎች የኢትዮጵያ ማሕበረሰቦች የተሰጠውን ዕድል ጉራጌ ግን አላገኘም።
** በጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተዳደር ሌሎች የደቡብ ሕዝቦች ሪፍረንደም እንዲያካሄዱ እድል አግኝተዋል። ነገር ግን ጉራጌ ሪፍረንደም ሳይካሄድ በግድ “ማዕከላዊ ኢትዮጵያ” ወደተባለው ክልል እንዲጠቃላል ተወሰነ።
ትክክለኛው የአገር ፍቅር መገለጫ እና ዘላቂ ብሄራዊ ጥቅም ማስከበሪያ አስተሳሰብ የቱ ነው?
የአገር ፍቅር/የአገር ተቆርቋሪነት እና ዘላቂ ብሄራዊ ጥቅም መሬት ላይ ያለውን እውነታ በመካድ “ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ” በማለት ብቻ ሊረጋገጥ አይችልም። ከንቱ መፈክሮች ብቻቸውን በደመነፍስ ከሚደግፍና ከሚቃወመው Hooligan ጭብጨባ እና ሆይሆይታ ከማስገኘት ባለፈ የአገርን ጥቅም በተጨባጭ ሊያስከብሩ አይችልም።
እውነታውን ለመጋፈጥ ባለመዘጋጀት እና የችግሮችን ምንጭ በቅጡ መርምሮ ባለመረዳትና ችግር የወለዳቸውን ሁነቶችን ብቻ በመኮነንና ሰዎችንም በማጥላላትና በመፈረጅ የሚጠበቅ አገርም ሆነ አገራዊ ጥቅም የለም፣ የሚፈታ ችግርም አይኖርም።
ያረጀ ያፈጀ ጀብደኝነት እና ጠርዝ-ረገጥ አገራዊም ሆነ ማህበረሰባዊ ብሄርተኝነት ያገር ፍቅር ወይም የማህበረሰባዊ ወገንተኝነት መገለጫ አይሆኑም። ፖለቲከኞች አንዴ የአጉል አገራዊ ብሄርተኝነት ስሜቶችን በሌላ ጊዜ ደግሞ ጠርዝ-ረገጥ የማህበረሰባዊ ማንነት ስሜቶችን በመኮርኮር የፖለቲካ አላማቸውን ለማሳካት የሚጠቀሙበት ሆሊጋን መሆንም አይገባም።
የአገር ፍቅር የሚገለፀውና ዘላቂ ብሄራዊ ጥቅም የሚከበረው ከእውነታው ጋር በመታረቅ እና ተጨባጭ ካልሆነ ምዕናባዊ አገር ወደ እውነተኛዋ ኢትዮጵያ ስንመለስ ነው።
የማህበረስቡን ችግር የማስተባበያ ሰበብ ከመፍለግና ችግሩ በሃሳባቸው የማትስማማባቸው ሰዎች ስላነሱት ብቻ ችግሩን አቃሎና አራክሶ ከማየት ይልቅ ችግሩን በነፃ አዕምሮ በተጎጂዎች ጫማ ውስጥ ሆኖ ለመረዳት በመሞከርና በእነሱ ቦታ ብሆን ምን አይነት የተስፋና የመፍትሄ ሃሳብ ላመነጭ እችል ነበር ብሎ ማሰብ ሲቻል የአገር ጥቅም ይከበራል።
ወደ ተጨባጩ አለም ስንመጣ የአገራችንን ሁኔታ በውል የሚወስኑ ጉዳዮችን በአግባቡ ለመለየት አዕምሯችን ክፍት ይሆናል። በደፈናው የምንፈርጃቸውን ሰዎች ትክክለኛ የተግባራው እምጃ መነሻ ምክንያቶችንም ሆነ የራሳችንን ክፍተት ለመለየት እንላለን። መሬት
ኦብነግ፣ በሶማሌ ክልል ኦጋዴን አካባቢ የንጹሃን ደም እየፈሰሰ መኾኑን ዛሬ በ”ኤክስ” ገጹ ባወጣው አጭር መልዕክት አስታውቋል።
“ኦጋዴን ውስጥ በሚፈሰው ደም የሚደሰቱ አካላት ይኖራሉ” ያለው ኦብነግ፣ ኾኖም እነዚህ አካላት “አንድ ቀን የእኛ ጊዜ እንደሚመጣ መርሳት የለባቸውም” በማለት አስጠንቅቋል። ግንባሩ አያይዞም፣ በሕዝባችን ላይ ጉዳት የሚያደርሱ አካላትን ድርጊት መቼም ቢኾን አንረሳውም ብሏል።
ኦብነግ፣ በክልሉ ሕዝብ ወይም በኦጋዴን አካባቢ ሕዝብ ላይ ጉዳት ያደርሳሉ ወይም ደም ያፈሳሉ ያላቸውን አካላት ማንነት ግን በስም ለይቶ አልጠቀሰም። ግንባሩ ከሳምንት በፊትም፣ በክልሉ ውስጥ በሲቪል ተሽከርካሪዎች ላይ ይፈጸማሉ ያላቸው “ዒላማ ያልለዩ የመሳሪያ ጥቃቶች” እና “የአርብቶ አደሮችን እንስሳትና ንብረት የመውረስ ድርጊቶች” እንዲቆሙ ጠይቆ ነበር።
ከአምስት ዓመታት በፊት ከክልሉ መንግሥት ጋር የሰላም ስምምነት ተፈራርሞ ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የተመለሰው የቀድሞው አማጺ ኦብነግ፣ በተለያዩ ጊዜያት በክልሉ ጸጥታ ኃይሎች ላይ ቅሬታ ሲያሰማ መቆየቱ ይታወሳል።
“የማሳሳቻና የማደናገሪያ መረጃ በማውጣት የሚቆም ትግል የለም” የአማራ ፋኖ በጎጃም የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ማርሸት ፀሐው!
አማራ ጠሉ የአብይ አህመድ አገዛዝ በአማራ ፋኖ የደረሰበትን ሽንፈት ለማወራረድ አማራ ክልልን በከባድ መሳሪያ እየደበደበ መሠረተ ልማቶችን አውድሟል። ንፁኃንን ጨፍ*ጭፏል!
በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች እንደ እባብ እየተቀጠቀጠ ያለው ኦህዴድ መራሹ የብልፅግና ስርዓት በጢስ አባይ አካባቢ “የፋኖ ታጣቂዎች አሉ” በማለት በከባድ መሳሪያ ሲደበድብ ሰንብቷል። ስለሆነም ብዙ መሰረተ ልማቶችን አውድሟል፤ ንፁኃንን ጨፍ*ጭፏል። በዚህም ምክንያት መነሻውን ጢስ አባይ ያደረገውን የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ሳብስቴሽን አውድሞታል።
በውሸት ከክልሉ ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ለማሳመን ነጭ የውሸት መረጃዎችን እያሰራጨ ይገኛል። በተለይም የአገዛዙ አዳሪ የሆነው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በክልሉ በርካታ አካባቢዎች ከትላንት እኩለ ቀን ጀምሮ ለተቋረጠው የኤሌክትሪክ ኃይል፤ ምክንያቱ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በጦር መሳሪያ እንደተመታ ካሳወቀ በኋላ የኃይል ማስተላለፊያው በፋኖ ታጣቂዎች ነው የተመታው ሲል የተገላበጠ የውሸት መረጃውን አሳውቋል።
በትላንትናው ዕለት አብዛኛው የሰሜን ምስራቅ የኢትዮጵያ ክፍል የኤሌክትሪክ ኃይል እንደተቋረጠበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስታወቁን አዲስ ማለዳ ዘግባ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፤ እውነተኛ መረጃው ግን ተቋሙ ከባህር ዳር – በደብረታቦር – ንፋስ መውጫ – ጋሸና – አላማጣ የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በብልፅግና ሰራዊት በከባድ መሳሪያ በመደብደቡ ሙሉ ለሙሉ ወድሟል።
ማረጋገጥ የምንፈልገው ግን የአማራ ፋኖ ለመብራት ኃይል ሰራተኞች ልዩ ጥበቃ የሚያደርግ ይሆናል!
ፋሽስታዊው ፀረ-ህዝብ የአብይ አህመድ አገዛዝ በትግራይ ህዝብ ላይ እንዳደረገው፣ በአማራ ህዝብ ላይ
ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ስለ ወቅታዊው የፋኖ ትግል ጠንከር ያለ መልዕክት በማህበራዊ ሚዲያ አጋርተዋል ይመልከቱት
ታላቁ ስእል ላይ ማተኮር ነው እሱም : የፋኖ አንድነትና : የፋኖ ተናቦ መስራት ነው:: ይህ የእስክንድር ራእይ ነው::
ይህንንም የጀመረው ያስጀመረው: እዚህ ያደረሰው እስክንድርና የሚመራው ግንባሩ ነው::
አሁን ከገባንበት አዲስ ምእራፍ ተነስተን ወደ ዋናው ግባችን ለመድረስ እስክንድርና ዘመነ እንዲሁም በየክፍለሀገሩ ያሉ የእዝና የፋኖ እዛዦች አብረው ተናበው እንዲስሩ ማበረታትና ማገዝ እንጂ: አሁን ባለቀ ስአት እዚህ ተቀምጠን እነሱን የሚከፋፍል ንግግር : መግለጫ : ወሬ መንዛት ከአቢይ የበለጠ ታላቅ ጠላትነት ነው::
የዛሬ ስራችን ሀላፊነታችን: ሜዳ ያለውን ከልጅነት እስከእውቀት: አንድም ቀን ከአገሩ ከህዝቡ ጥቅም ውጭ ስርቶ የማያውቀውን እስክንድርን መኮነን ማኮሰስ : በህሊናም በባህልም በእምነትም በአገር ወዳድነት ሚዛንም ያስጠይቃል:: ስአቱ ጊዜው አይደለም:::
እዚህ ድረስ ከመጣን በሁዋላ መሪዎቻችንን ማንኳሰስ: ግልፅ ጠላትነት ነው:: ቅሬታችን ክሳችን እውነት ነው ብላችሁ ካስባችሁ ለምን አራት ኪሎ ከገባን በሁዋላ እንጠያየቅም? አላማው ሌላ ነዋ !! ይህንን የማይረዳ ማንም አዋቂ አእምሮ ሊኖር አይችልም::
በተንኮል የተመረዘ ወይም የታመመ አእምሮ ካልሆነ:: የአማራን ፋኖ የሚያቆመው ምንም ሀይል በአለም ውስጥ የለም:: መሪዎችን ማጥላላት እንቅፋት እንጂ ግድግዳ አይደለም:: የአራት ኪሎ መንገድ ግድግዳ ፈርሷል::: ወደፊት እንጂ ወደኋዋላ የለም::
አማራ ጠሉ የአብይ አህመድ ሰራዊት በሰሜን ሜጫ ወረዳ ብራቃት ቀበሌ ከ50 በላይ ንፁኃን መጨፍጨፋቸውን አሻራ ሚዲያ አረጋግጧል። የአገዛዙ ሰራዊት በደረሰባቸው አካባቢዎች በተለይምበብራቃትና አካባቢው ንፁኃን ተጨፍጭፈዋል።
የሃይማኖት አባቶች ገደል ቆፍረው ተረሽነዋል። በተለይም ላይ ጋፊት ገብርኤል በተባለው ቀበሌ 12 የአብነት ተማሪዎች ተጨፍጭፈዋል። የደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ደጋአረገ አሳዬና አብረዋቸው የነበሩ 4 የአካባቢው ሰዎች በመከላከያ ተይዘው ይዝማ ማርያም (አየለች)ከሚባል ቦታ ጉድጓድ አስቆፍረው ሁሉንም ሰዎች ረሽነዋቸዋል።
ፈለገ ብርሃን ቀበሌ ውስጥ በሚገኙት ጅባስራ ማርያም ውስጥ ሁለት ውንድማማቾችንእና ሁለት ልጆችን እንዲሁ ከዚሁ ንውስ ቀበሌ ታች ላሎ ጎጥ አንድ የ11ኛ ክፍል ተራራማ ከዚህ በስተጨማሪ ቢጢ ጊወርጊስ ንውስ ቀበሌ ውስጥ አንድ እርሶ አደር እናም በተመሳሳይ ይዝማ ማሪያም ፣ማሁዳ ቀበሌ፣ ዘንጋቸር ቀበሌ አንድ አርሶ አደር፣ ፍጣ ሚካኤል 6 ሰዎች፣ በርኳ ማርያም 4 ሰዎች ስንኳ ጊወርጊስ 2 ሰዎች ሲረሸኑ የ74 ዓመት ወንድ አዛውንት ግብረ ሰዶም በሰራዊቱ ተፈፅሞባቸዋል።
ይፌሳ ቀበሌ አንድ ሙዝ ሻጭ ልጃ ገረድ ለብዙ ሰራዊት ተደፍራ ወዲያውኑ ህይወቷ አልፎል። ይዝማ (አየለች) ገበያ የግል ክሊኒክ መድሀኒቶች በመከላከያ ተዘርፈዋል።
በተመሣሣይ ብጢ ጊወርጊስ አንድ ትንሽ ከተማ ውስጥ የነጋዴ ቤቶች ዕቃዎቻቸው በሙሉ በመከላከያ ሰራዊት ተዘርፈዋል ።በአጠቃላይ በሰሜን ሜጫ በብራቃት ቀጠና ውስጥ ከሱቅ እስከ ሆቴሎች እንዲሁም የአርሶ አደር ሰብሎች በአገዛዙ ዘቭ ጠባቂ ወታደሮች ተዘርፈዋል። ልጃገረዶችና አዛውንቶች ተደፍረዋል።
አሻራ ሚዲያ
የሂዩመን ራይትስ ዋች መግለጫ
የኢትዮጵያ መንግሥት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ቃል አቀባይ ባቴ ኡርጌሳንና ሌሎች የተቃዋሚ ፓርቲ ፖለቲከኞችን እያዋከበ ነው ሲል የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች አስታወቀ። ድርጅቱ «ማንም ሰው ከዘፈቀደ እስርና በቁጥጥር ስር ከመዋል የሚያመልጥ አይመስልም» ሲል ትናንት ባወጣው መግለጫ ከአስር ቀናት በፊት ከፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንቷን ጋሊንዶ ጋር አዲስ አበባ ውስጥ በቁጥጥር ስር የዋሉት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ቃል አቀባይ ባቴ ኡርጌሳ እስከ ነገ በእስር እንደሚቆዩ አቃቤ ሕግ ማሳወቁን ገልጿል። በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲለቀቅ ጥሪ የተደረገለት ጋዜጠኛ ጋሌንዶ ከተያዘበት ከቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ባለፈው ሐሙስ ተለቆ ወደ ሀገሩ መሄዱን ሂዩመን ራይትስ ዋች አስታዉቋል።
ይሁንና ከጋዜጠኛዉ ጋር አብረው የታሰሩት የኦሮሞ ነፃ አዉጪ ግንባር (ኦነግ) ቃል አቀባይ አቶ ባቴ ኡሮጌሳን ግን መንግሥት በአሸባሪነት ከፈረጀዉ ከኦሮሞ ነጻ አውጭ ጦር ጋር አላቸው በተባለው ግንኙነት ላይ ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን አቃቤ ሕግ ባለፈው አርብ ፍርድ ቤት በቀረቡበት ወቅት ማሳወቁንና እስከ የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ በቁጥጥር ስር እንዲቆዩ ወደ ተያዙበት ቦታ መመለሰቸውን የመብት ተማጋቹ ድርጅት ጽፏል። የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የፓርላማ አባሉን አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ መንግሥትን የሚተቹ 5 ሌሎች ፖለቲከኞችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ያስታወሰው ሂዩመን ራይትስ ዋች እነዚህ የቅርብ ጊዜ እስሮች በኢትዮጵያ ማንም ሰው ከዘፈቀ እስርና በቁጥጥር ስር መዋል እንደማያመልጥ የሚያሳይ ነው ብሏል። የኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ አጋሮችም እነዚህ «የተሳሳቱ» ያላቸውን እስሮች እንዲያወግዙና መንግሥት ሰላማዊ
ከሸዋ ሮቢትና ከሚሴ በስተቀር የሰሜን ምስራቅ የአገሪቱ አካባቢዎች፣ መቀሌ እና ሠመራ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል ተባለ
የኢትዮፕያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከባህር ዳር – ጋሸና – አላማጣ የተዘረጋው መስመር ተበጥሶ ኃይል መቋረጡን አስታወቀ።
ከባህር ዳር – በደብረታቦር – ንፋስ መውጫ – ጋሸና – አላማጣ የተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ በአካባቢዎቹ ኃይል ተቋርጧል የተባለ ሲሆን የመበጠሱ ምክንያት አልተገለጸም።
በተጨማሪም ከደብረ ብርሃን – ሸዋሮቢት – ኮምቦልቻ የተዘረጋው መስመር በሸዋ ሮቢት ከተማ አቅራቢያ በመበጠሱ ከሸዋ ሮቢትና ከሚሴ በስተቀር አብዛኛዎቹ የሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ መብራት የለም ተብሏል።
በዚህም ሳቢያ ከኮምቦልቻ በባቲ በኩል ኤሌክትሪክ ኃይል የሚደርሳቸው የአፋር ክልል መዲና ሠመራና የተለያዩ የክልሉ ዞኖችና ወረዳዎች እንዲሁም በወልዲያ አላማጣ መስመር ኃይል የሚያገኙት የትግራይ ክልል መዲና መቀሌን ጨምሮ አብዛኛዎቹ ከተሞች ኃይል እንደተቋረጠባቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያሳያል።
46ኛው የካራማራ ድል በአዲስ አበባ ተከበረ
ኢትዮጵያ በወራሪው የሶማሊያው የሲያድ ባሬ መንግሥት በ1969 የተቃጣባትን ጥቃት የመከተችበት የካራማራ ድል 46ኛው ዓመት የድል በዓል ዛሬ በድላችን ሐውልት ( ኢትዮ ኩባ የወዳጅነት ማዕከል ) ውስጥ ተከብሯል።
በዚህ ሥነ ሥርዓት ላይ በወቅቱ በጦርነቱ ላይ ጉልህ የጦር ጀብዱ የፈፀሙ ጀኔራል መኮንኖች ተገኝተዋል ። በበዓሉ ላይ በጦርነቱ ወቅት ከኢትዮጵያ ጎን ተሰልፈው የተዋጉ ኩባውያን ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ አምባሳደርራቸው ተወክለዋል ።
የታሪኩ ዘካሪዎች እና ወዳጆችም ተገኝተዋል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያ ( ከ 1969- 70) በተካሄደው በዚሁ ጦርነት) ከሶማሊያ ከተዘነዘረባት የግዛት ማስፋፋት ጥቃት በኢትዮጵያ የቀድሞው ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም መሪነት ጦርነቱን በማሸነፍ ዳር ድንበሯ የተከበረበት ድል በየ ዓመቱ እየተከበረ ይገኛል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ኤርቪን ማሲንጋ በፓትሪያርክ ብፁዕ አቡነ ማትያስ 11ኛ አመት በአለ ሲመታቸው አስመልክተው በኤምባሲው ድረገፅ ባስተላለፉት መለክት ላይ በዝቋላ አቦ የተፈጸመውን ግድያ አውግዘው በኦርቶዶክስ ምዕመናን እና በንጹሃን ላይ የሚደረገው ግድያ እንዲቆም ጠይቀዋል። የአሜሪካ መንግስት በሃይማኖት መሪዎች እና በመመናን ላይ የሚደረገውን ጭፍጨፋ ታወግዛለች ብለዋል። በአጠቃላይ በንጹሃን ላይ የሚደረገውን ጭፍቸፋ ሁሉ እናወግዛለን ሲሉ አምባሳደሩ በመልዕክታቸው ገልጸዋል።
የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ ኢትዮጵያና ሱማሊያ በመካከላቸው የተፈጠረውን ውጥረት እንዲያረግቡ ሰሞኑን ከመጋረጃ ጀርባ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማድረጋቸውን የኬንያ ጋዜጦች ዘግበዋል። የፕሬዝዳንት ሩቶን ጥረት ተከትሎ፣ ኹለቱ አገራት ከዚህ ሳምንት ጀምሮ የተካረሩ የቃላት ልውውጦችን ያለዝባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ጉዳዩን የሚያውቁ ዲፕሎማቶች መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። ኹለቱ አገራት ጉዳዩን ባደባባይ ከማራገብ ለመቆጠብ መስማማታቸውንም ዘገባው ጠቅሷል። ኬንያ፣ በጉዳዩ ዙሪያ በቅርቡ ከኹለቱ አገራት ጋር ውይይት ለማድረግ አቅዳለች ተብሏል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይና ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ባለፈው ሳምንት ናይሮቢ የነበሩ ቢኾንም፣ ፊት ለፊት ግን ተገናኝተው አልተነጋገሩም።
ኬንያ፣ ከላሙ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ የሚዘረጉ የመሠረተ ልማቶችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ መስማማቷን ዘ ኢስት አፍሪካን ጋዜጣ አስነብቧል። ኢትዮጵያ የላሙ ወደብን ለመጠቀም የወደቡ አገልግሎት ታሪፍ እንዲሻሻልላት መጠየቋን የጠቀሰው ዘገባው፣ የኬንያ ወደብ ባለሥልጣንም የታሪፍ ተመኑን እንደገና ለመፈተሽ መስማማቱን አመልክቷል። ዘገባው፣ ኢትዮጵያ የካርጎ ጭነቶችን በላሙ ወደብ በኩል ከውጭ ለማስገባት መስማማቷንና ኬንያም ከላሙ እስከ ሞያሌ ለኢትዮጵያ የካርጎ ደኅንነት ማረጋገጫ ሰጥታለች ብሏል። ኹለቱ አገሮች የላሙ ኮሪደር እስካኹን ጥቅም ላይ እንዳይውል ያጓተቱ ችግሮችን የሚያጠና የጋራ ኮሚቴ ለማቋቋምም ተስማምተዋል ተብሏል።
ፓስፖርት ፈልገው ወይም በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው።
የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል።
ወጣት፣ ሴት፣ ወንድ፣ ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም ” ፓስፖርት ፈልገው ነው ? ” እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ።
አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ አሠራር ዘርግቻለሁ ቢልም አሁንም በርካታ ተገልጋዮችን አገልግሎቱ ደጃፍ ላይ መመልከት አልቀረም።
ተገልጋዮች ዐሻራ ለመስጠት እና ፎቶ ለመነሳት በመ/ቤቱ መገኘት ግዴታቸው በመሆኑ ከተለያዩ አካባቢዎች መጥተው በወረፋው ምክንያት ላልተፈለገ እንግልት ይዳረጋሉ።
እንግልቱ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ከእንቅልፍ ተነስቶ ረዥም ሰልፍ ከመሰለፍ ይጀምራል።
በሌቦች መዘረፍም የሚያጋጥም ክስተት መሆኑን ተገልጋዮች በምሬት ይናገራሉ።
ለአላስፈላጊ እንግልት እና ወጪ ተዳርገናል የሚሉ ተገልጋዮች ሃሳባቸውን አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት በበይነ መረብ አማካኝነት ከተመዘገቡ ወራት እንዳለፋቸው ይገልጻሉ።
ተገልጋዮቹ አገልግሎቱ አካባቢ ወረፋ ለመያዝ ስንሞክር ” እኔ ቅድሚያ ወረፋ ልያዝላችሁ ክፈሉኝ ” በሚሉ ደላሎች እንዋከባለን ይላሉ።
እነሱ እንደሚሉት የመሥሪያ ቤቱን ሰልፍ አሰላፊዎች ወከባና ዱላ አልፎ ውስጥ መግባት መቻል መታደል ነው።
ተገልጋዮቹ በሌሊት ለመነሳት ሲሉ በአካባቢው ለአልጋ ኪራይ ከፍለው እንደሚያድሩና ለአላስፈላጊ ወጪም እንደሚዳረጉም ይገልጻሉ።
ሰልፉ ረዝሞ ወረፋ ሳይደርሳቸው ከቀረም ቅጣት እንደማይቀርላቸው ይናገራሉ።
በርካታ አገልግሎት ፈላጊ ሕዝብ በተገቢው መንገድ ከማስተናገድ ይልቅ በዱላ በመደብደብ ሥርዓት ለማስያዝ ሲሞከር ይታያል። ወደ መግቢያ በሩ ተጠግቶ መረጃ ማግኘት የማይታሰብ ነው።
የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ተስተካክሏል ይባል እንጂ አሁንም ችግሮቹ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ፣ ፖለቲከኞች ከሕገ መንግሥቱ በተቃራኒ በቤተ ክርስቲያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት “የግል ፍላጎትና ዓላማ ለማስፈጸም” መሞከራቸው “ስህተት” እና “ተቀባይነት የሌለው” ድርጊት ነው በማለት ተናግረዋል። አቡነ ማትያስ ትናንት በ11ኛ ዓመት በዓለ ሲመታቸው ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ቤተክርስቲያኗ እና የሐይማኖት አባቶች ግጭት ውስጥ ከሚገቡ ፖለቲከኞች አንዱን ወገን ደግፈው ሌላውን ከመንቀፍ መቆጠብ እንዳለባቸው አሳስበዋል። ቤተክርስቲያኗ ባኹኑ ወቅት ባስቸጋሪ ፈተና ላይ እንደምትገኝ የገለጡት ፓትርያርኩ፣ መንግሥት ለቤተክርስቲያኗ “የሕግ ከለላና ጥበቃ” እንዲያደርግም ጠይቀዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ዛሬ በበዓለ ሢመታቸው ላይ ያስተላለፉት ቃለ ምእዳንና ቡራኬ እንደሚከተለው ይነበባል፦
+++++
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
• ብፁዕ አቡነ አብርሃም፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
• ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤
• የተከበራችሁ የመንግሥት ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት፤
• የተከበራችሁ አምባሳደሮችና ኮር ዲኘሎማቶች፤
• የተከበራችሁ የቤተክርስቲያናችን የየመምሪያውና የየድርጅቱ ኃላፊዎች፤
• ክቡራን ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፤
• ክቡራን የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፤
• የሰንበት ት/ቤት ወጣት ልጆቻችን፤
• በአጠቃላይ በዚህ ዓውደ ምሕረት የተገኛችሁ ክቡራንና ክቡራት በሙሉ፤
ፈተናዎች ቢበዙብንም ምሕረቱን ከኛ ያላራቀ እግዚአብሔር እንኳን ለዐሥራ አንደኛው በዓለ ሢመተ ክህነት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
‹‹ወይእዜኒ ተመየጡ ኀቤየ ወአነሂ እትመየጠክሙ፡- ‹‹አሁንም ወደኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደናንተ እመለሳለሁ›› (ዘካ. ፩-፫)
ዋዜማ- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የብቃት መመዘኛ ፈተና በተሰጠባቸው ተቋሟት ለሚገኙ ሠራተኞቹ፣ አዲስ የሥራ ድልድል ይፋ ማድረጉን ዋዜማ ሰምታለች።
የብቃት መመዘኛው ፈተና ውጤትን ተከትሎ የተሰራው አዲሱ የሥራ ድልድል ይገለፃል ከተባለበት ቀን ኹለት ሳምንት ገደማ ዘግይቶ፣ በኹሉም ወረዳዎች እና ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በከተማ አስተዳደሩ ይፋ የተደረገው ከአንድ ሳምንት በፊት ነመሆኑን የዋዜማ ምንጮች ጠቅሰዋል። በአዲሱ የሥራ ድልድል መሰረት፣ የብቃት መመዘኛ ፈተናውን ወስደው ውጤት ካመጡት ሠራተኞች መካከል፣ በምርጫቸው የተመደቡ የመኖራቸውን ያህል፣ እስካሁንም ያልተመደቡ እንዳሉ ተረድተናል።
የማለፊያ ውጤት ቢያመጡም፣ በምደባው ያልተካተቱት ሠራተኞች ያልተመደቡባቸውን ምክንያቶች፣ የትምህርት ዝግጅታቸው ከመረጡት የሥራ መደብ ጋር የተራራቀ መሆን፣ በፈተናው ያገኙት የማለፊያ ነጥብ እና ከዚህ ቀደም በየስድስት ወሩ ይሰጣቸው የነበረው የብቃት መመዘኛ ውጤት ተደምሮ ዝቅተኛ መሆኑ፣ አግባብነት ያለው የሥራ ልምድ የላቸውም የሚሉ እና የብሔር ተዋፅዕ መጠበቅ አለበት የሚሉ እንደሆኑ የዋዜማ ምንጮች ይናገራሉ።
አንድ የክፍለ ከተማ የመሬት ልማት ጽኅፈት ቤት ሠራተኛ ለዋዜማ ሲናገሩ፣ “ከ70 በመቶ በላይ የሆነ የማለፊያ ነጥብ ባመጣም፣ የተመደብኩት ግን ከደረጃ 12 ወደ ደረጃ 9፣ ሦስት ደረጃ ዝቅ ተደርጌ ነው” ይላሉ። ይህም ከተቀመጠው የብቃት መመዘኛ መመሪያው አሰራር ውጭ መሆኑን የገለፁልን እኚሁ ሠራተኛ፣ ለሦስት የሥራ መደብ ብወዳደርም፣ አንዱን ቅድሚያ ለሴቶች፣ ኹለተኛውን ደግሞ ክፍት መሆን አለበት፣ እንዲሁም ሦስተኛው ቀጥተኛ የትምህርት ዝግጅት የለህም በሚሉ ምክንያቶች ተከልክያለሁ ብለውናል። ከ10 ዓመት በላይ የሥራ ልምድ ኖሯቸው ዜሮ ዓመት የሥራ ልምድ የሚጠይቅ የሥራ መደብ ላይ የተመደቡ ሠራተኞች
(ኢትዮ 360 -የካቲት 24/2016) በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ መዳሎ ቀበሌ ነባር ነዋሪ የሆኑ ከ295 በላይ የአማራ ተወላጆችን መሬት እየሸነሸነ ቄሮ ለሚባለው ህገወጥ ቡድን እያደለ ያለው ሰው በላ ሃይል የአማራ ተወላጆችን ለመጨፍጨፍ መዘጋጀቱን የአማራ ተወላጆቹ ለኢትዮ 360 ገለጹ።
የአማራ ተወላጆቹ ለዘመናት ግብር ሲከፍሉበትና በህጋዊ ነባር ነዋሪነት ተመዝግበው የኖሩበት መሬት መሸንሸን የተጀመረው አላግባብ ሰፊ መሬት ይዛችሁዋል በሚል ምክንያት መሆኑን ይናገራሉ።
ይሄ የመሬት ዝርፊያ ሲካሄድ ደግሞ ከከፍተኛው የገዳዩ ቡድን አመራሮች ጀምሮ የክልሉ ልዩ ሃይል ሚሊሻና የጸጥታ ሃይሉ ያሉበት ስብስብ በሙሉ ባለበት ሁኔታ ውስጥ መሆኑንም ሳይጠቁሙ አላለፉም።
ይሄ ሃይል ወደ አካባቢው የአማራ ተወላጆቹን መሬት ለመዝረፍ ሲመጣ ደግሞ በከባድ መሳሪያ በነታጀብ ጭምር መሆኑንም አስታውቀዋል።
ወደ አካባቢው መሬቱ ይሰጥሃል የተባለውን ጨምሮ የአማራ ተውላጆቹ ካንገራገሩ የሚጨፈጭፍ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰው በላ ስብስብም መግባቱን ተናግረዋል።
350 ሙሉ ባለ ሶስት እግር ተሽከካሪ ባጃጅ ፥200 ሞተሮችና በአካባቢ ያለና ገዳዩ ቡድንን ያጀበ ጽንፈኛ ቡድን ወደ አካባቢው ለዝርፊያና ለንጹሃን የአማራተወላጆች ጭፍጨፋ መግባቱንም አስታውቀዋል።
ካለፈው አርብ ጀምሮ አካባቢውን በወረረው በዚህ ዘራፊ ቡድን መሬቱ መሸንሸን የተጀመረው ከ295 በላይ የሚሆኑ ነባር የአማራ ተወላጆች መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
ነገር ግን ለጊዜው የእነዚህን የአማራ ተወላጅ የአማራ ተወላጆችን መሬት እየዘረፈ ያለው የሰው በላ ስብስብ ወደ ቀሪዎቹ ከ400 በላይ ወደሚሆኑት የአማራ ተውላጆች በቀጣይ የሚያልፍ መሆኑንም ገልጸዋል።
ከምንም በላይ የሚያስፈራው ግን ከመሬት ዝርፊያው በላይ የአማራ ተወላጆቹን ለመጨፍጨፍ መዘጋጀቱ ነው ሲሉ የድረሱልን
በኢትዮጵያ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት እንዲሁም 350 ሺ ነፍሰ ጡር እና የሚያጠቡ እናቶች ለከፋ የምግብ እጥረት ይጋለጣሉ ሲል ዩኒሴፍ አስጠነቀቀ።
በ2024 በኢትዮጵያ ወደ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት እና ወደ 350,000 ነፍሰ ጡር እንዲሁም የሚያጠቡ እናቶች ለከፋ የምግብ እጥረት የሚጋለጡ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) በትላንትናው እለት ባወጣው መግለጫ አስጠንቅቋል።
የዩኒሴፍ ምክትል ስራ አስፈፃሚ ቴድ ቻይባን በኢትዮጵያ ለ5 ቀናት ባደረጉት ጉብኝት በመላ ሀገሪቱ እየደረሰ ያለውን የከፋ ሰብአዊ አደጋ ለመከላከል አለም አቀፉ ማህበረሰብ ለህጻናት እና ቤተሰቦች የሚያደርገውን ድጋፍ በአፋጣኝ እንዲያጠናክር አሳስበዋል።
ቻይባን በድርቅ ከተጠቁት አካባቢዎች ውስጥ የትግራይ ክልልን የጎበኙ ሲሆን በክልሉ የምግብ ዋስትና ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ዜጎች ችግሩን ሊቋቋሙ የሚችሉበት መንገዶች መሟጠጣቸውንና በሀገሪቱ ውስጥ የኮሌራ፣ የኩፍኝ፣ የዴንጊ ትኩሳት እና የወባ ወረርሽኝ መከሰቱ የህብረተሰቡን የጤና ሁኔታ የበለጠ እንዳወሳሰበው ጠቁመዋል።
” ኢትዮጵያ በርካታ ቀውሶች ተጋርጠውባታል ያሉት ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚው ” በኤልኒኖ ምክንያት የተከሰተውና በሰሜን፣ በመካከለኛው እና በደቡብ ኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ በሚሊዮን በሚቆጠሩ ህጻናት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ነው” ብለዋል።
በዚህም በ 2024 ወደ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በከፍተኛ የምግብ እጥረት እንደሚሰቃዩ እና 350,000 የሚጠጉ ነፍሰ ጡር እና የሚያጠቡ እናቶች የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እንደሚገጥማቸው ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልፀው አለም አቀፉ ማህበረሰብ ለህጻናት እና ቤተሰቦች የሚያደርገውን ድጋፍ በአፋጣኝ እንዲያጠናክር አሳስበዋል።
የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሃመድ ሰሞኑን ቱርክ ባስተናገደችው የዲፕሎማሲ መድረክ ላይ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ኢትዮጵያ ውስጣዊ ችግሮቿን ውጫዊ ለማድረግ እየሞከረች ነው በማለት ከሰዋል።
ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ከመድረኩ በተጓዳኝ ዛሬ ከቱርኩ ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን ጋር ተገናኝተው በኹለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
ሱማሊያና ቱርክ ለ10 ዓመታት ይጸናል የተባለለትን የባሕር መከላከያ ስምምነት ከተፈራረሙ ወዲህ፣ ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ከፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ጋር ሲነጋገሩ የአኹኑ የመጀመሪያቸው ነው።
ኹለቱ አገራት የባሕር መከላከያ ስምምነቱን ዝርዝር ይዘት እስካኹን ይፋ ባያደርጉም፣ ቱርክ የሱማሊያን የባሕር ወሰን ከተለያዩ የውጭ ኃይሎች ሕገወጥ እንቅስቃሴዎች ለመከላከል መስማማቷን የአገራቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ሶማሊላንድ ግን፣ ስምምነቱ የባሕር ወሰኔ በምትለው የውቂያኖስ ዳርቻ ላይ ተፈጻሚ ሊኾን እንደማይችል በመግለጽ ላይ ናት።
የአድዋ ድል በዓልን ለማክበር ወጥተው በፖሊስ ታግተው የዋሉት 25 ጋዜጠኞች!
ነገሩ እንዲህ ነው፣ ዛሬ “አድዋን በባዶ ዕግር” በሚል መሪ ቃል ለ5ኛ ጊዜ ተገናኝተው በባዶ እግር ትንሽ ተጉዘው፣ ፎቶ ተነስተው ለመለያየት ከፋና፣ ከኢቢሲ፣ ከአዲስ ቲቪ፣ ከሀገሬ ቲቪ፣ ከኢዜአ እና ከመንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ የተውጣጡ 25 ጋዜጠኞች በጠዋቱ ይገናኛሉ።
ይሁንና ገና 6 ኪሎ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አጠገብ ተገናኝተው “አድዋ” የሚል ፅሁፍ ብቻ ያለበትን አረንጓዴ ቲሸርት ለብሰው ፎቶ ሲነሱ የጉለሌ ፖሊስ አባላት ከበዋቸው በመንገድ ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ ታክሲ አስቁመው በግድ ጫኗቸው።
ከጠዋቱ 1 ሰአት የታገቱት ጋዜጠኞቹ እስከ ምሽቱ 12 ሰአት ቆይተው ተይዘው ምንም በማያዉቁት እና ባላጠፉት ነገር በሰው ዋስ አስይዘው ወጥተዋል።
ይህ አንድ ማሳያ እንጂ እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በተለያዩ ስፍራዎች ተይዘው እንደተወሰዱ፣ ማምሻውን የተወሰኑት እንደተለቀቁ፣ ሌሎቹ ግን የት እንኳን እንደተወሰዱ ቤተሰቦቻቸው እንደማያውቁ የሚደርሱኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
እውነት ለመናገር አሁን አሁን በሀገራችን የምናያቸው ክስተቶች ጆርጅ ኦርዌል “1984” በተባለው መፅሀፉ ላይ ያሰፈረውን የ dystopia የማህበረሰብ አኗኗር ሁኔታን እየመሰለ መጥቷል።
@EliasMeseret
በ128ኛው የዓድዋ ድል በዓል”የተከለከለ ልብስ ለብሳችኋል” በሚል በርካቶች ወጣቶች እየታሠሩ ነው – አዲስ ማለዳ
128ኛው የዓድዋ ድል በዓል የአደረንጓዴ ቢጫና ቀይ፣ የምኒሊክ እና የእቴጌ ጣይቱ ምስል ያለበት ልብስ ለብሳችኋል በሚል በርካቶች ወጣቶች ታስረዋል።
እንዲሁም ከነዚህ ልብሶች በተጨማሪም “የፋኖ ልብስ ነው” የለበሳችሁት በሚል የታሰሩ መኖራቸውን ለአዲስ ማለዳ ከአንድ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ ሰዎች ሰምታለች።
ለ128ኛው የዓድዋ ድል በዓል ለማክበር የተሰበሰቡ ወጣቶች ወደ ምንሊክ አደባባይ ሲጓዙ “ትፈለጋላቹ” በሚል በፖሊስ ተይዘው በአዲሱ ገበያ ወረዳ ስምንት ፖሊስ ጣቢያ ተወስደዋል።
በአንድ ቦታ ላይ “ሀምሳ አካባቢ እንሆናለን። ዝም ብለው አስቀምጠውናል። አንድ በአንድ አስገብተው እየመረመሩ ነው” ሲል አንድ ወጣት ለአዲስ ማለዳ ገልጿል። ሌሎችንም እያመጡ እየጨመሩ ነውም ተብሏል።
ከአዲሱ ገበያ በተጨማሪ ጊዮርጊስ እና ሌሎች አካባቢዎች በሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎችም የታሰሩ መኖራቸውና እንዲሁም ይህ ዘገባ እስከወጣበት ሰዓት ድረስ እስር እንደቀጠለ ምንጮች ገልጸዋል።
ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን እንጂ ወደ ምንሊክ ሃውልት ማለፍ እንደማይቻል እና ወደ አደባባዩ የሚወስዱ መንገዶች ላይ የፀጥታ ኃይሎች ጥብቅ ፍተሻ እያደረጉ እንደነበር አዲስ ማለዳ በስፍራው ተገኝታ ተመልክታለች።
የድል በዓሉ ከዚህ ቀደም ይከበርበት ከነበር የምኒሊክ ሃውልት ጋር ሳይከበር በመቅረቱ በርካቶች ቅሬታቸውን ሲያንፀባርቁም አዲስ ማለዳ ታዝባለች።ለዚህም ከተለያየ አካባቢ በዓሉን ለመታደም በቡድን በመሆን ተመሳሳይ ልብስ በማሰራት በስፍራው ይገኙ የነበሩ ታዳሚዎች ቁጥር ከዚህ ቀደሙ መቀነሱ አይነተኛ ማሳያ ነው።
መከላከያ ሚንስቴር ያዘጋጀው የአድዋ ድል በዓል በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም የተከረ ሲሆን፤ በርካታ ታዳሚዎች
ዓድዋን ከፒያሳ ምኒሊክ አደባባይ ለማላቀቅ ስራዎች…
የዓድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ እንደ ከዚህ ቀደሙ በ “ምኒሊክ አደባባይ” በዓሉን ማክበር የሚፈልግ የአዲስ አበባ ነዋሪ ሁሉ ተሰብስቦ እንዲያከብር አልተደረገም የሚል ቅሬታ ያደረባቸው ወገኖች አስተያየታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
አንድ በጥዋት በዓሉን አከብራለሁ ብሎ ወደ ፒያሳ “ምኒሊክ አደባባይ” ያቀና የአዲስ አበባ ነዋሪ ምኒሊክ አደባባይ በከፍተኛ የፀጥታ ኃይሎች ጥበቃ ስር እንደነበር፣ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ብቻ ማለፍ እንደሚቻል፣ ጥብቅ የሆነ ፍተሻም እንደነበር ገልጿል።
በዓሉን ለማክበር ወደ ዓድዋ መታሰቢያም ፍቃድ ከተሰጠው ውጭ መግባት እንደማይቻል በዚህም በዓሉም ለማክበር እንዳልቻለ ጠቁሟል። ይህ የህዝብ በዓል በመሆኑ ህዝብ በመረጠው መንገድ ወይም ተካፋይ በሆነበት መንገድ ሊከበር ይገባ ነበር ሲል ያደረበትን ቅሬታ አጋርቷል።
ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ደግሞ ፤ “ዛሬ ከባለፈው ዓመት በበለጠ የዓድዋ በዓልን ለማክብር የመጣ ሰው ከቴዎድሮስ አደባባይ ጀምሮ መግባት ባለመቻሉ ሲመለስ ነበር። ፈረስ እና የተለያዩ የዓድዋ አልባሳትን የለበሱ ሰዎችም ሲመለሱ ነበር” ብሏል።
“በዓሉን ለማክበር ወደ ዓድዋ መታሰቢያ እየገቡ የነበሩትም በቀበሌ ይመስለኛል ባጅ የተሰጣቸው ብቻ ናቸው” ያለው ይኸው አስተያየት ሰጪ በዓሉ ሁሉም ለማክበር ባለመቻሉ እንዳደበዘዘው ጠቁሟል።
ይኸው አስተያየት ሰጪ “ካለፈው ሁለት ዓመት ጀምሮ ዓድዋን ከፒያሳ ምኒሊክ አደባባይ ለማላቀቅ ስራዎች የተሰሩ ይመስለኛል” ሲል ገልጾ “የኔ ጥያቄ የተገነባው ዓድዋ መታሰቢያ ከዚህ በኃላ ባለስልጣናት እና የሚፈልጉት ሰው ብቻ በብቸኝነት ለማክብረ ነው? ወይስ በዓሉን ማክበር የሚፈልግ ህዝብ ተሰብስቦ እንዲከበርበት ነው ?” ብሏል። መንግሥት የ128ኛው ዓድዋ
ያኔ ጥቁር ህዝቦች እንደእንስሣ ከመቆጠራቸው ብዛት የተነሳ “ጥቁሮችን ረግጦ መግዛት የነጮች እዳ ነው” ይባል ነበር። ኢትዮጵያውያን ይህንን የአለም ህግ አድዋ ላይ ሻሩት።
በ ይርጋ ገላው አዲስ ዘይቤ
የሃገራችን ህዝቦች መልካቸውም፣ ባህላቸውም፣ ሃይማኖታቸውም፣ ቋንቋቸውም፣ ታሪካቸውም፣ ፍላጎታቸውም፣ ስነልቦናቸውም…. ተመሳሳይ ነው። ተመሳሳይ ማለት “አንድ” ማለት አይደለም። ልክ ከአንድ ምድር ላይ እንደሚበቅሉ ልዩ ልዩ እጽዋት፣ ልክ ከአንድ የቤተሰብ ግንድ እንደሚመዘዙ የተለያዩ ልጆች፣ ምንጫቸው ላይ፣ የማንነታቸው ንጥረነገር ውስጥ አንድ የሚያደርጋቸው መሰረት አለ። አድዋ የዚህ የአንድነት መሰረት ገሃዳዊ መገለጫ ነው። አድዋ የሃገራችንን ልዩ ልዩ ህዝቦች አንድነት ያስመሰከረ ብቻ ሳይሆን፣ ሃገራችን ኢትዮጵያ ከወራሪ ቅኝ ገዢዎች ጋር ያላትን ልዩነት አንጥሮ ያወጣ የድል ቀን ነው።
የአድዋ ጦርነት አይቀሬ ነበር። ምክንያቱም የሃገራችን ህዝቦች ያላቸው ስነልቦና፣ ቋንቋ፣ አስተሳሰብ፣ እምነት፣ ባህል፣ ፍላጎት ሁሉ ጣልያን ከአውሮፓ ይዞት ከመጣው የተለየና ተቃራኒ ስለነበረ ነው። በመላው አለም “አውሮፓን የሚቃረን ማንነት ሁሉ ለአውሮፓ መገዛት ወይ መጥፋት አለበት” የሚል እምነት ገኖ ነበር። ስለዚህ በአድዋ የገጠሙት ኢትዮጵያዊነትና አውሮፓዊነት ነበሩ። የጦርነቱ ጎራ “ኢትዮጵያ ያለአውሮፓዊነት ሃገር ልትባል አይገባትም፣ ወደፊትም አትሆንም፤” በሚልና “ኢትዮጵያ ከአውሮፓ በፊት ሃገር ሆና ኖራለች፣ ወደፊትም ትኖራለች፤” በሚል የእምነት ልዩነት ላይ የተሰመረ ነበር። ጦርነቱ እአአ በ1884 በበርሊን ኮንፈረንስ በተወሰነው የአለማቀፍ የቅኝ አገዛዝ ህግና፣ኢትዮጵያውያን ለብዙ ሺህ አመታት ሃገር ሆነው በኖሩበት ህግ መካከል የተካሄደ ጦርነት ነበር።
ያኔ ጥቁር ህዝቦች እንደእንስሣ ከመቆጠራቸው ብዛት የተነሳ “ጥቁሮችን ረግጦ መግዛት የነጮች እዳ ነው” ይባል ነበር።
አራት ኪሎን እያተራመሰ ያለው የባህርዳሩ ኦፕሬሽን!
https://rumble.com/v4gn53c-ethio-360-zare-min-ale-friday-march-01-2024.html
ከሃያ በላይ የአብነት ተማሪዎች ከነመምህራቸው፤ መነኮሳትም ተገደሉ
+++
(አደባባይ ሚዲያ፤ ማርች 1/2024፤ የካቲት 22/2016 ዓ.ም):-
ሰሜን ሜጫ ብራቃት ከተማ ልዩ ቦታው ጋፊት ገብርኤል በሚባል ቦታ ከሃያ በላይ የአብነት ተማሪዎች ከነመምህራቸው በመንግሥት ወታደሮች መገደላቸውን ምንጮች ለአደባባይ ተናግረዋል።
የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ.ም ከሌሊቱ 6:30 እስከ 8:00 በተፈጸመው ግድያ ዕድሜያቸው ከ11 ዓመት እስከ 18 ዓመት ናቸው ያሉ የቤተ ክርስቲያን ተማሪዎች አረመኔነት በተሞላበት መልኩ የተገደሉ ሲሆን ከተገደሉት መካከል
1) ስብሐት
2) ገብረ ኢየሱስ
3) ዘርዓ ዳዊት
4) ናሁ ሠናይ
5) ቃለ ጽድቅ
6) በዕውቀት
7) እንዳልካቸው
8) ኤፍሬም
የሚባሉ ተማሪዎች ይገኙበታል ተብሏል። ከአካባቢው በመንግሥት ታጣቂዎች የተያዙ ካህናት እንዳሉም ታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ለመንበረ ፓትርያርኩ በጻፈው ደብዳቤ በሀገረ ስብከቱ ሥር በሚገኙ የተለያዩ አድባራትና ገዳማት ብዙ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን ገልጿል:: ታሕሣሥ 2/2016 ዓ.ም በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት በማቻከል ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር በሚገኘው የዋሻ አምባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም እመምኔት እማሆይ ወለተ ማርያም ገላው ታፍነው መወሰዳቸው ተገልጿል።
በተመሳሳይ መልኩም በአዋበል ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር በሚገኘው በመካነ ቅዱሳን ጣቢት ቅ/ጊዮርጊስ አንድነት ገዳም ላይ በተፈጸመ ጥቃት አባ ገ/ሥላሴ ታመነ የተባሉ አባት ሲገደሉ ዲ/ን ዮሐንስ ለማ ላይ ደግሞ ከፍተኛ የአካል ጉዳት መድረሱን ሀገረ ስብከቱ አስተውቋል። ከዚህም በተጨማሪ የተለያዩ ንብረቶች መዘረፋቸው ተገልጿል::
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየተፈጸሙ ባሉ የተቀናጁ ጥቃቶች ገዳማት፣ በየገዳማቱ ውስጥ ያሉ
የወልዲያ ከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ተገደሉ
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን የወልዲያ ከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ትናንት ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸውን የቅርብ ጓደኞቻቸው ተናገሩ፡፡
የወልዲያ ከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ዓለማየሁ ካሳሁን ትናንት ጠዋት 2 ሰዓት አካባቢ “ሆርማት” በተባለ የከተማው አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በጥይት ተመትተው መግደላቸውንና አጥቂዎቹ ሸሽተው ማምለጣቸውን ከሟቹ ጓደኞች አንዱ ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በባለሦስት እግር ተሸከርካሪ (ባጃጅ) ሆነው ጥቃቱን መፈፀማቸውንም አመልክተዋል፡፡
ሌላ የሟቹ ጓደኛ በበኩላቸው፣ በግለሰቡ መኖሪያ ቤት ላይ ከዚህ በፊትም ቦምብ ተወርውሮ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ማቹ ቀደም ሲል በወልዲያ ገቢዎች ጽ/ቤት ይሰሩ እንደነበር ያመለከቱት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ ግለሰቡ በነበረው የስራ ትጋት በክልል ደረጃ ተሸላሚ ነበርም ብለዋል፡፡
አቶ ዓለማየሁ የከተማ አስተዳደሩ አገልግሎት ኃላፊ ሆነው ሲሰሩም ከመሬት ወረራ ጋር በተያያዘ በርካታ ሥራዎችን ሲሰሩ እንደነበር የጠቆሙት አስተያየት ሰጪዎች፣ ግድውም ከዚህ ሥራቸው ጋር ሳይያያዝ ኤቀርም የሚል ግምት እንዳላቸው አመልክተዋል፡፡
በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባሕር ዳር ዛሬ አርብ የካቲት 22፤ 2016 ዓ/ም በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ መካሄዱን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ።
በከተማዋ ሦስት ቀበሌዎች ላይ አርብ ማለዳ 12፡00 ሰዓት ላይ ውጊያው መጀመሩን የተናገሩት አራት ነዋሪዎች፤ የከባድ መሳሪያ ድምጾችንም መስማታቸውን ተናግረዋል።
ለደህንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁት ነዋሪዎቹ በከተማዋ ቀበሌ 14 አቡነ ሃራ እና ልደታ በሚባሉ የመኖሪያ ሰፈሮች፤ እንዲሁም ቀበሌ 11 አባይ ማዶ እየተባለ በሚጠራ ሰፈር እና ቀበሌ 13 ባታ ቤተ ክርስቲያን ወይም ወይራሚት አካባቢ በሁለቱ ተዋጊዎች መካከል ውጊያ መደረጉን ተናግረዋል።
አንድ የከተማዋ ነዋሪ “. . . ከጠዋቱ 12፡20 ጀምሮ ውጊያ ነበር። የእጅ ለእጅ፤ የቅርብ ለቅርብ የሚመስል የክላሽ ድምጽ ነበር። እስከ 1፡30፤ 1፡40 አካባቢ ድረስ የቀጠለ [ነበር]። እየቀጠለ ግን የከባድ መሳሪያ፤ ትልልቅ መሳሪያዎች ድምጽ ይሰሙ ነበር” ብለዋል።
አባይ ማዶ በተባለው አካባቢ ከሦስት ቀናት በፊት ጀምሮ የተኩስ ልውውጦች እንደነበሩ የተናገሩት ሌላ ነዋሪ፤ አየር ጤና በተባለው ሰፈር “ሌሊቱን ሙሉ” በሁለቱ ወገኖች መሃል ውጊያ እንደነበር ተናግረዋል።
በመኖሪያ ሰፈሮች አካባቢ ተደርጓል የተባለው የዛሬው ውጊያ ለአንድ ሰዓት ያህል ተጋግሎ መደረጉንና ማለዳ 3፡00 ሰዓት አካባቢ መብረዱን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ረፋድ አካባቢም አልፎ አልፎ የተኩስ ድምጾች ይሰሙ ነበር ብለዋል።
ትናንት ሐሙስ ምሽት ላይ ‘ውጊያ ሊኖር ይችላል ተጠንቀቁ’ የሚል መረጃ እንደሰሙ የተናገሩት አንድ የመንግሥት ሰራተኛ ጥዋት 12፡00 ሰዓት አካባቢ የተኩስ ድምጽ መስማታቸውን ተናግረዋል።
የተኩስ ልውውጡ በተደረገበት አንደኛው ቀበሌ
“አድዋን ተዉት”- የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ለ’አድዋ ሩጫ’ አዘጋጆች
የአድዋ ድል በዓልን ለማክበር ‘አድዋ ሩጫ’ በሚል ስያሜ ሊካሄድ የነበረው አመት ሙሉ የተለፋበት የአደባባይ ሩጫ እንዳይካሄድ በከንቲባዋ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ተከለከለ
አዘጋጆቹ ‘አድዋ ሩጫ’ ለማካሄድ ከባለፈው ዓመት የካቲት 20 ቀን 2015 ጀምሮ ለአዲስ አበባ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከኪነ ጥበብ ዘርፍ ጋር በአጋርነት ለመስራት በመጠየቅ ህጋዊ ሂደት መጀመራቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ከሁነቱ በሚገኘው ከወጪ ቀሪ ገቢ ትርፍ ስልሳ በመቶው የአድዋ ድል ታሪክ እና የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ታሪክ በመፅሐፍ ሰንዶ ለህትመት የሚያበቃበት ዕቅድ የያዘ እንደነበርም መግለጫው አመልክቷል።
ቢሮውም ጥያቄውን ተቀብሎ የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ለስምንት ወራት በጋራ ሲሰሩ መቆየታቸውን አዲስ ማለዳ ከመርሃ ግብሩ አዘጋጆች ተረድታለች።
በሂደቱ የመከላከያ ሚኒስቴር ለአድዋ ሩጫ ፍቃድ መስጠቱን ለአዲስ አበባ ባህል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ በደብዳቤ ያሳወቀ ቢሆንም፤ የአዲስ አበባ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳው ስምምነቱን በድንገት እንዲቋረጥ አድርገዋል።
የጋራ ስምምነቱ የተቋረጠበትንም ምክንያት “ቢሮው ምንም አይነት ከአድዋ በዓል ጋር የተያያዘ ስራ አይሰራም፤ የሚሰራም ከሆነ በመከላከያ ወይም በከንቲባዋ ይህንን ስሩ የሚል ዝርዝር ትዕዛዝ ከተሰጠ ብቻ ነው” የሚል መሆኑን ከራሳቸው ከቢሮዋ ሃላፊ “የጋራ ስምምነቱ እንዲቀጥል ባናገርናቸው ወቅት በሰጡት መልስ መረዳት ችለናል” ሲሉ አዘጋጆቹ ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል። የሩጫው አዘጋጆች “በገጠሙን በርካታ ተግዳሮቶች እጅ ባለመስጠት በቀን ጥር 22 ቀን 2016 ለአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የአደባባይ ሩጫ ለማካሔድ ለከተማ አስተዳደሩ ደብዳቤ
ኮሜዲያን ያሬድ በ 1 ዓመት ቀላል እስራትና በ2 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወሰነ
ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም (ልጅ ያሬድ) በተከሰበት የወንጀል ክስ በአንድ አመት ቀላል እስራት እና በሁለት ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ውሳኔ ተላልፎበታል።
ተከሳሹ ጥፋተኛ ተብሎ ቅጣቱ የተላለፈበት በኮምፒዩተር የሚፈጸም ወንጀል ድንጋጌን መተላለፍ፣ የቤተክርስቲያንና የሰዎችን ክብርና መልካም ስም ማጉደፍ እንዲሁም የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት በሚሉ ተደራራቢ ክሶች ነው።
ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም የቀረበበት ክስ እንዲሻሻል የክስ መቃወሚያውን በጽሁፍ ያቀረበ ቢሆንም በዐቃቤ ሕግ በኩል ክሱ ሊሻሻል የሚችልበት የህግ አግባብ እንደሌለ ተጠቅሶ መልስ ሰጥቷል።
ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን መርምሮ ተከሳሹ ያቀረበው የክስ መቃወሚያ ጥያቄ የህግ አግባብነት የለውም በማለት ውድቅ አድርጎታል።
ተከሳሹ የመከላከያ ማስረጃ አለኝ ማለቱን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ያቀረባቸውን የሰው መከላከያ ማስረጃዎችን ቃል አዳምጧል።
ተከሳሹ የሰው የመከላከያ ማስረጃ ያቀረበ ቢሆንም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከል ባለመቻሉ እና በክስ ዝርዝሩ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት መፈጸሙ በፍርድ ቤቱ በመረጋገጡ በዛሬው ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ ተሰጥቶበታል።
የቅጣት ውሳኔውን የወሰነው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ህገመንግስታዊና በህገመንግስት ስርዓቱ ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከተው ችሎት ተከሳሹ ያቀረበውን አምስት የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶችን ይዟል።
ፍርድ ቤቱ በድርጊቱ የእርስ በእርስ ግጭት አለመፈጠሩንና ጉዳት አለመድረሱን ከግምት ውስጥ በማስገባት በዕርከን 6 መሰረት በአንድ ዓመት ቀላል እስራትና በሁለት ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል።
የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ተከሳሹ እጁ ከተያዘበት ከነሃሴ
በኢትዮጵያ በሰው ልጆች ላይ ከሞራል ያፈነገጠ ኢሰብዓዊ ተግባር እየተፈጸመ ነው = ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ
“ከእንግዲህ በኋላ ከፌደራል መንግስት ጋር በፕሪቶርያው ስምምነት ዙሪያ የማደርገው ውይይት በአፍሪካ ህብረት በኩል ነው” – የትግራይ ግዜያዊ አስተዳደር
የትግራይ ግዜያዊ አስተዳደር በፕሪቶርያው ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ ከፌደራል መንግስቱ ጋር የሚያደርገው ውይይት በአፍሪካ ህብረት በኩል ብቻ እንዲሆን መወሰኑን አስታወቀ።
ግዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ትላንት የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ አካሄድኩት ባለው ስብሰባ በፕሪቶርያው ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ ዝርዝር ውይይት ማድረጉን ገልጿል።
የፕሪቶርያው ስምምነት በተሟላ መንገድ እንዲተገበር ለማስቻል በተለያዩ ምክንያቶች ሲጓተት የነበረው “የአፍሪካ ህብረት ፓናል” በአስቸኳይ ስራ እንዲጀምር ሲል ጠይቋል።
ከፌደራል መንግስት ጋር በመወያየት ችግሮችን ለማቃለል፣ መተማመን ለመፍጠር በተወሰነ ደረጃ እየሰራሁ መጥቻለሁ ያለው ግዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ የትግራይ ህዝብ ጥያቄዎች በተሟላ መንገድ ለመመለስ እንዲያስችል በሚል የውይይት አካሄዱ በሁሉቱ አካላት በፌደራል መንግስቱ እና በግዜያዊ አስተዳደሩ መሆኑ ቀርቶ ቀጣይ ውይይቶች በአፍሪካ ህብረት ፓኔል በኩል እንዲሆን መወሰኑን አስታውቋል።
ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ህልውና በላይ የሚያስቀድመው አንዳች ነገር የሌለ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያናችን የገጠማትን ፈተና ለማለፍ የሚጠበቅበትን መንፈሳዊ ግዴታ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ዛሬ የካቲት 19/2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
ማኅበሩ በመግለጫው የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን መንፈሳዊ አንድነት የጠየቀ ሲሆን “ቤተ ክርስቲያንን በማይጠቅማት ጉዳይ የግል ፍላጎትንና ምድራዊ ዓላማን መሠረት አድርገው ከቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ውጭ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊን ለመተካት፣ ፓትርያርክ ለመሾምና የመሳሰሉትን ለመፈጸም” የሚንቀሳቀሱ ያላቸውን “አንዳንድ አባቶች” ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በማሳሰብ ጉዳዩንም በመከታተል መረጃውን ለምእመናን አደርሳለሁ ብሏል።፡፡
ይመለከታቸዋል ላላቸው ሌሎች የቤተ ክርስቲያን አካለትም ጥሪውን አስተላልፏል።
1. የተከበራችሁ አበው ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ሆይ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ “በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፡፡ እንዳለ በዚህ ታላቅ የፈተና ወቅት የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማስጠበቅ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጣችሁን ኃላፊነት ለመወጣት ምእመናንን አቅጣጫ በመስጠት የቀደሙ አባቶቻችሁን ፈለግ በመከተል ዛሬም በጽናት እንድትተጉ፤ ያከበረቻችሁን ቤተ ክርስቲያን በአንድነት ሆናችሁ እንድትጠብቁ በልጅነት መንፈስ በትሕትና እንጠይቃለን፡፡ በተጨማሪም የአባትነት የዋህ ልቦናችሁን በመጠቀም ያዘኑ፣ የጠቀሙ፣የተቆረቆሩ መስለው ቀርበው የግል ፍላጎታቸውን ለመፈጸም የሚጥሩ ስለሚኖሩ ሁሉንም በጥንቃቄ እንድትመረምሩ፤ቀኖች ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን በመዋጀት አንድነታችሁን እንድታጠነክሩና በቤተክርስቲያን ዙሪያ ስለሚፈጠሩ ችግሮች በጥልቀት እንድትወያዩና እንድትመካከሩ እናሳሰስባለን።
2. ከዚህ ውጭ ቤተ ክርስቲያንን በማይጠቅማት ጉዳይ የግል ፍላጎትንና ምድራዊ ዓላማን መሠረት አድርጋችሁ ከቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ውጭ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊን ለመተካት፣
የሎሳንጀለስ አማራ ማህበር ታሪክ ሰራ !!! https://rumble.com/v4g2ssl-268869189.html
የአምነስቲ ሪፖርት እና በአማራ ህዝብ እየተመዘገቡ ያሉ ድሎች!
https://rumble.com/v4g1g66-ethio-360-zare-min-ale-tuesday-feb-27-2024.html
በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚፈጸሙ እገታዎች እና ግድያዎች አፋጣኝ መፍትሄ ሊሰጣችው ይገባል!
የኢሰመጉ ጋዜጣዊ መግለጫ-የካቲት 19 /2016 ዓ.ም
“መሞታቸው ብቻ ሳይሆን አሟሟታቸውም ዘግናኝ ነበረ አስከሬናቸው እንኳ ተለቃቅሞ እንዲቀበር ነው የሆነው።”
መጋቤ ካህናት ቆሞስ አባ ሃብተ ጊዮርጊስ አስራት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የገዳማት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ በግፍ በተገደሉት የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አባቶች ዙሪያ ከተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ጋር ቆይታ አድርገዋል።
የመምሪያው ዋና ኃላፊ የሆኑት መጋቤ ካህናት ቆሞስ አባ ሃብተ ጊዮርጊስ ዓሥራት እንደተናገሩት ከጥቃቱ በፊትም በተደጋጋሚ የማስፈራሪያ ዛቻና ገዳሙን ለቃችሁ ውጡ የሚባሉ መልእክቶች ይደርሱ እንደነበር ገልጸዋል።
ከዚህ ክስተት ቀደም ብሎ የገዳሙ መጠበቂያ መሣሪያና የመናንያኑ እህል በኃይል ተወስዷል ያሉ ሲሆን የሚመለከተው አካል ለጉዳዩ ትኩረት ካልሰጠ ወደ ፊትም ከዚህ ያልተናነሰ ወንጀል በገዳሙ ሊፈጸም የማይችልበት ምክንያት አይኖርም ብለዋል።
ምንም እንኳ ለቤተክርስቲያን አባቶች መደብደብ መሰደድና መገደል የነበረ ቢሆንም የአሁኑ ግን መሞታቸው ብቻ ሳይሆን አሟሟታቸውም ዘግናኝ ነበረ አስከሬናቸው እንኳ ተለቃቅሞ እንዲቀበር ነው የሆነው ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳማትን መጠበቅ የቤተክርስቲያኗ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የመንግሥትም ኃላፊነት ነው መንግሥት ከፌደራል እስከ ክልል ባሉት የጸጥታ መዋቅሮቹ ገዳማትን እንደማንኛውም ተቋም ሊጠብቅ ይገባል በማለት አክለዋል።
በመጨረሻም በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ያሉ ምእመናን በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙት የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም መናንያን በገዳሙ ሕጋዊ አካውንት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000011282222 (የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም) ድጋፍ እናድርግ በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።
የአማራ ፋኖ በጎጃም (10)አስር ብርጌዶች ውጊያ ላይ ናቸው።ጠላት እየተወቀጠ ይገኛል።
~ ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም የአማራ ፋኖ በጎጃም
“ሳሙኤል አወቀ ብርጌድ” ግንደወይን፣
“ገረመው ወንድ አውክ ብርጌድ ” ቋሪት፣
“ቀኝ አዝማች ስሜነህ ብርጌድ” እንጅባራ ዙሪያ፣
“ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ” አዲስ ቅዳም፣
“ፊትአውራሪ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ” ዳንግላ፣
“ዘንገና ብርጌድ” ቲሊሊ፣ “ግዮን ብርጌድ” ሰከላ፣
“ደጋ ዳሞት ብርጌድ” ፈረስ ቤት ከፍተኛ ጦርነት እየተደረገ ይገኛል።
የአማራ ፋኖ በጎጃም!! መንገዶች ይዘጉ! GAR ይፋፋም!
©አስረስ ማረ ዳምጤ
የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ሀሙስ ዕለት በአስጨናቂ ሁኔታዎች በግፍ የታሰረውን ፈረንሳዊ ጋዜጠኛ አንትዋን ጋሊንዶን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፍታት አለባቸው ሲል የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ኮሚቴ CPJ ሰኞ አስታወቀ።
በፓሪስ ለሚገኘው አፍሪካ ኢንተለጀንስ የግል የዜና ድረ-ገጽ የሚዘግበው ጋሊንዶ፣ በመዲናይቱ አዲስ አበባ ውስጥ ሲቪል ልብስ ለብሶ በደህንነቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን Africa Intelligence በመግለጫው እና ታምሩ ወንድም አገኘሁ በተባለ ድርጅት ውስጥ የሚሰሩት ጠበቃው ለሲፒጄ በስልክ ተናግረዋል።
ጋሊንዶ በኢትዮጵያ ህጋዊ እውቅና ካለው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ መኮንን ባቴ ኡርጌሳ ጋር ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል ታስሮ እንደነበር ጠበቃው ተናግረዋል።
ሙሉ መረጃውን ይህን ተጭነው ያገኙታል ፡ https://cpj.org/2024/02/french-journalist-antoine-galindo-detained-in-ethiopia/
በአንድ ወቅት ያደገው የሪል ስቴት ገበያ ውድቀት ገጥሞታል፣ አልሚዎች ከፍላጎት መቀነስ እና የዋጋ መውደቅ ጋር እየታገሉ ነው።
The once-booming real estate market faces a downturn, with developers struggling with declining demand and falling prices.
READ MORE: https://addisfortune.news/dream-homes-deflate-in-downturn/
“በዝቋላ ገዳም አባቶች ላይ ለተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ከመንግሥት ፍትህን አንጠብቅም!”- እናት ፓርቲ
እናት ፓርቲ ዛሬ ባወጣው መግለጫ በዝቋላ ገዳም አባቶች ላይ ለተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ “ከመንግሥት ፍትህን አንጠብቅም” ሲል አስታወቀ።
“ብልጽግና መራሹ መንግሥት የእምነት ተቋማት በማይከበሩበት የሃይማኖት አባቶች እንደ ከብት በሚታረዱበት ወደፊት ታሪክ በጥቁር መዝገብ በሚጽፈው ዘመን ውስጥ የሕዝብን መከራ ማራዘሙን ተያይዞታል” ሲልም ፓርቲው ወቅሷል።
ዴሞክራሲያዊ እና ሰብዓዊ መብቶችን ማግኘት “እንደ ሰማይ እርቋል” የሚለው የእናት ፓርቲ መግለጫ ከሦስት አሥርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የአብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ፣ የክርስቲያኖችና የካህናት ግድያ ባለፉት አምስት ዓመታት “በተጠናከረና በተቀናጀ መልኩ” ቀጥሏልም ብሏል።
ፓርቲው ተጠናክሮ የቀጠለው የሃይማኖት አባቶቻችን አሰቃቂ ግድያ መሠረታዊ አገራዊ እሴቶቻችን ለመጣሳቸው ግልጽ ማሳያ ነው በመሆኑም በአብዛኛው መንግሥት እየመራው የሚገኘው የአገራችን ፖለቲካ “አሻጥርን የተከተለ” በመሆኑ መንግሥትን ተስፋ አድርገን የምንጠይቀው ፍትህ ባይኖርም፤ ለሁሉም ጊዜ አለውና የንጹሃን ደም ፍትሕ የሚያገኝበት ጊዜ እንደሚመጣ በእጅጉ ተስፋ እናደርጋለን ሲል ገልጿል።
ኦነግ፣ ባለፈው ሳምንት በምሥራቅ ሸዋ ዞን ዝቋላ ገዳም በአራት መነኮሳትና ካህናት ላይ የተፈጸመውን ግድያ አስመልክቶ ትናንት ባወጣው መግለጫ፣ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈጸሙ የዘፈቀደ ግድያዎች በገለልተኛ አካል እንዲጣሩ ጠይቋል።
የመንግሥት መዋቅሮች የዜጎችን ሕይወትና ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው ያለው ኦነግ፣ ለካህናቱና መነኮሳቱ ጅምላ ጭፍጨፋ የክልልና የፌደራል መንግሥታት ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው ብሏል።
ኦነግ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በግጭቶችና ኹከቶች ውስጥ እንደ ሰላም ፈጣሪ አካል የምትጫወተውን ሚና እንደገና እንድታጤን፣ እጆቿን ከፖለቲካ እንድታስወጣና በገዥው አካልና በተቃዋሚዎች ግጭት ከመግባት እንድትቆጠብም በመግለጫው ጠይቋል። !
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶክተር) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነነዌን ጾም በተመለከተ ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ያስተላለፉት መልዕክት ፦
+++
ለተወደዳችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቼ በሙሉ፣
ይህን መልእክት ስጽፍ በእንባ እየታጠብኩ ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ይጎዳል ብዬ በማሰብ መልካም ነገርን እንኳ ላለመናገር ወስኜ ነበር። ነገር ግን፣ የወገኖቼ መቸገር፣ ምግብ ሳይጠፋ መራብ፣ ወንዝ ዳር ተቀምጦ መጠማት፣ በትርጉም የለሽ ግጭቶች መሠቃየት የኅሊና እረፍት ሊሰጠኝ አልቻለም። መንፈሴ አሁንም “ኢትዮጵያ ለምን መፍትሔ አጣች? ኢትዮጵያ ለምን መፍትሔዋን እግዚአብሔርን እና መንገዱን ተወች? መቼስ ወደ እግዚአብሔር ዕረፍት ትመለሳለች?” በሚሉ ጥያቄዎች ይረበሻል። ብቻዬን ባለቅስም አልወጣልህ ስላለኝ የአምናው እንባና ጩኸታችሁን፣ ለእኛ የነበራችሁን እምነትና ሐዘኔታ እያሰብኩ ቢያንስ አብራችሁኝ ታለቅሱ ዘንድ ይህን ጻፍኩ። ከሁሉ አስቀድሞ ምሕረቱ ብዙ የሆነው አምላክ ባለፈው ዓመት ቤተ ክርስቲያን መከራ ደርሶባት በጾመ ነነዌ ከፊቱ ቀርባ ስታዝን ምሕረቱን ከእኛ ያላራቀብን እግዚአብሔር ከታላቅ ምሕረቱ የተነሣ ለዓመቱ አድርሶናልና ክብር ምሥጋና ይሁንለት! እንደምናስታውሰው አምና ቤተ ክርስቲያን ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ ችግር ብዙ ምእመናን ወገኖቻችን ተገድለዋል፤ ታሥረዋል፤ ቆስለዋል፤ ቀሪዎቹ እኛም የኅሊና ቁስላችንን እያስታመምን እነሆ ሌላ ጾመ ነነዌ ላይ ደርሰናል። ዘንድሮም እንደአምናው ከመንፈስ ልጆቼ ጋር በጋራ እንዳናለቅስና በእግዚእብሐር ፊት እንባችንን እንዳናፈስ ከ27 ዓመታት በኋላ እንደገና በአዲስ መልከ ለስደት ተዳርጌያለሁ።
“ነነዌ ኢትዮጵያ ናት!” ያልኩትን ጾም ቤተ ክርስቲያን የጣለችብኝን ኃላፊነት እየተወጣሁ፣ በኢትዮጵያ ካሉ ምእመናን
ከምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ የተላለፈ ጥብቅ ትዕዛዝ
የአማራ ፋኖ በተለያዩ አውደ ውጊያዎች አንፀባራቂ ድሎችን እየተጎናጠፈ ይገኛል። በዚህም አገዛዙ አለኝ የሚለውን “የመከላከያ ሰራዊት” ገሚሱን ደምስሰነዋል ቀሪውን ደግሞ እየደመሰስነው እንገኛለን፣ ገሚሱን ማርከነዋል ቀሪውን ደግሞ እያስከዳነው እንገኛለን። ከዚህ በፊት ያለውን ትተን ከሰሞኑ እንኳን ኮረኔሎችን ጭምር የፋኖን ትግል ደግፈውና ዓላማችን ገዝቷቸው ወደ እኛ የመጡ ሲሆን እኛም እነሱን የፋኖ አባል አድርገናል፣ በገባንበት አውደ ውጊያ ሁሉ በትንሽ መስዋዕትነት ከፍተኛ ድሎችን ተቀዳጅተናል።
በዚህ የተበሳጨው አገዛዝ ንጹሃንን ኢላማ ያደረገ ጥቃት በወሎ፣ በጎጃም፣ በጎንደር እና በሸዋ እየፈፀመ ይገኛል። በመሆኑም በፋኖ ጠንካራ በትር ሲመታ ንጹሃንን ኢላማ ያደረገ ጥቃት የተለመድ የአገዛዙ ባህሪው ነውና መላው የአማራ ፋኖ ከሰሞኑ ጠንካራ ኦፕሬሽኖችን እየፈፀምን ስለሆነ አገዛዙ በንጹሃን ላይ ሊያደርሰው የሚችለውን ጥቃት ለመቀነስ መላው የወሎ ጠቅላይ ግዛት መንገዶች ከየካቲት 17 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ቀን እንዲዘጉ የወሰን መሆኑን እየገለጽን ሕዝባችንም ለውሳኔያችን ተገዥ እንዲሆን ካለንበት ከበረሃ ሁነን ጥብቅ መልዕክታችን እናስተላልፋለን። ከዚህ ትዕዛዝ የሚወጣ ካለ ለሚደርሰው ማንኛውም ጉዳት ራሱ ኃላፊነቱን እንደሚወስድ እንገልጻለን።
ድል ለአማራ ፋኖ!
የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ
የካቲት 17 ቀን 2016 ዓ.ም
ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር
ከቢትወድድ መንገሻ ጀንበሬ ብርጌድ | ዳንግላ
ከቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ ብርጌድ በሁሉም የእድሜ ደረጃ ለሚገኝ የከተማችን ህዝብ የተላለፈ ጥብቅ መልዕክት!
እንደሚታዎቀው በህዝባችን ላይ የተቃጣውን ጥፋት ለመቀልበስ በፍፁም ፅኑነት እና ለህዝባችን ታማኝ በሆነ ሁኔታ የቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ የህዝብ ልጆች ከሌሎች የወገን አደረጃጀቶች ጋር በመተባበር እስከ ሞት መስዋዕትነት ትግል ላይ መሆናችን ይታዎቃል፡፡
በመሆኑም ለፋሽስቱ እና ፀረ አማራው ስርዓት ወንበር አስጠባቂ የሆኑ ጠላቶቻችንን ስርዓት ለማስያዝ እንዲሁም በግፍ ያለሃፂያታቸው ለሚጨፈጨፉ ንፁኃን ወገኖቻችን ደምን በደም የማጥራት ዘመቻ ከነገ ጀምሮ ለሚተገበረው እርምጃችን ህዝባችን አስፈላጊውን ሁሉ ቅድመ ዝግጅት ያደረግ ዘንድ ማሳዎቅ ግዴታ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ስለሆነም የግልም ሆን የመንግስት ትጥቅ የያዛችሁ የከተማችን ነዋሪዎች ከነገ ጀምሮ በሚደረገው ኦፕሬሽን ከታጋይ ወንድሞቻችሁ ጎን መቆም ግዴታ መሆኑን አውቃችሁ። ጥሪያችንን እንድትቀበሉ እያስገነዘብን እድሜያችሁ ለትግል የደረሰ የከተማችን ወጣቶች ደግሞ በቅርባችሁ ያገኛችሁትን ገጀራም ሆነ መጥረቢያ፤ አንካሴም ይሁን ቢላ ይዛችሁ በመውጣት ያለበደላችሁ ሊያጠፋችሁ የመጣውን ደም መጣጩ አረመኔ ጠላታችሁን ማርካችሁ ትታጠቁ ዘንድ ታሪካዊ የአርበኝነት ጥሪ ተደርጎላችኋል፡፡
ከዚህም ጋር በተያያዘ የአማራ ፋኖ በጎጃም ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሠረት አቅመ ደካሞች፤ ሴቶች እህቶቻችን እና እናቶች ደግሞ ከነገ ጀምሮ ከተማችን ላይ ምንም አይነት የትራንስፖርትም ሆነ የስራ እንቅስቃሴ አለመኖሩን አውቃችሁ አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ ከወዲሁ ታደርጉ ዘንድ ብርጌዱ ያሳውቃል፡፡
ድል ለጭቁኑ ህዝባችን!
ድል ለአማራ ፋኖ!
የቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ ብርጌድ!
በአብይ አገዛዝ በዳቦ ስሙ ኦነግ ሸኔ የሚባለው ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ንፁሃንን በመግደል የሚታወቀው በኦሮሚያ የሚንቀሳቀሰው ሃይል ባወጣው መግለጫ ፣ የፋኖ ታጣቂዎች ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል የኦሮሞ ልዩ የብሄረሰብ ዞን በመጓዝ ላይ የነበሩ ስምንት መምህራንን ሐሙስ’ለት “ጭካኔ በተሞላበት ኹኔታ ገድለዋል” በማለት በ”ኤክስ” ገጹ ላይ ባወጣው አጭር መግለጫ ከሷል።
ይህ የሃሰት ክስ የሽመልስ አብዲሳ የጨፌን ንግግር ተከትሎ የተፈበረከ ክስ እንደሆነ በርካቶች ይስማሙበታል። ፋኖን የሚወነጅሉበት ቢያጡ በራሳቸው ድርጊት በራሳቸው ወጀል ራሳቸው በሚፈፅሙት የንጹሃን ግድያ በሃስት የስም ማጥፋቱን የብልጽግ ና ተባባሪ ሆነዋል። ስምንቱ መምህራን የተገደሉት ሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ መኾኑን የገለጠው ከሳሹ ኦነግ ሸኔ ፣ ግድያውን “በጥብቅ አወግዛለኹ” ብሏል። ቡድኑ ተገደሉ ያላቸውን መምህራን ስም እና አድራሻ አልጠቀሰም። በሃሰት ክስ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚኬደው መስመር እንደማይሳካ ካሁን ቀደም ያየነው የሰማነው እውነታ ነው።
በግፍ የተገደሉት የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አባቶች ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጸመ።
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሚገኘው ጥታዊው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ራሱን ኦነግ ሸኔ ብሎ በሚጠራው ቡድን የገዳሙን መጋቢ ጨምሮ ዐራት አባቶችን መግደሉን ይታወቃል፡፡
መረጃውን በስልክ ያደረሱን አንድ የገዳሙ የሥራ ኃላፊ በግፍ የተገደሉት አባቶች አስክሬን ተረሽነው ከተቀበሩበት በረሀማው ጊዳ ተክለሃይማኖት አካባቢ ተነስቶ በገዳሙ በክብር ሥርዓተ ቀብራቸው ዛሬ የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ተፈጽሟል ብለዋል፡፡
የገዳሙ የሥራ ኃላፊ ለጊዜው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ለገዳሙ ጥበቃ እያደረገ ሲሆን ነገሮች እስኪረጋጉ ጥበቃው እንዲቀጥል ጠይቀዋል ሲል EOTC TV ዘግቧል።
አዳነች አቤቤ የዶክተር ካሳ ተሻገርን ያለመከሰስ መብት አነሳች፤ በታሰሩ የምክር ቤት አባላት ላይ በአቃቢ ሕግ ክስ ሊመሰረት ነው። የሰሞኑን በየክልል ምክር ቤቶች የአባላቱን ያለመከሰስ መብት እየተነሱ ሲሆን በቀጣይነት የነክርስቲያን ታደለ እና ደሳለኝ ጫኔ ያለመከሰስ መብት ተነስቶ በሚቀጥለው በጌዲዮን ጢሞቲዮስ የተዘጋጀው የሃሰት ክስ ያለመከሰስ መብታቸው በተነሳባቸው የሕዝብ እንደራሴዎች ላይ እንደሚከፈት ታውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤው፤ የአንድ የምክር ቤት አባልን ያለመከሰስ መብት ሊያነሳ ነው። የከተማይቱ ምክር ቤት የተወካዩን ያለመከሰስ መብት የሚያነሳው፤ ከፍትሕ ሚኒስቴር በቀረበለት ጥያቄ መሆኑን አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር በጉባኤው መክፈቻ ላይ ተናግረዋል።
አፈ አጉባኤዋ የጉባኤውን አጀንዳ በዘረዘሩበት ወቅት የተወካዩን ማንነት ሳይጠቅሱ አልፈዋል። የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር ካሳ ተሻገር ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ላለፉት አምስት ወራት በእስር ላይ መሆናቸው ይታወሳል። ዶ/ር ካሳ ያለመከሰስ መብታቸው ከተነሳ፤ አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ተመሳሳይ ውሳኔ የተላለፈባቸው ሶስተኛ የምክር ቤት ተመራጭ ይሆናሉ።
የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ ኦሮሚያ) ባለፈው ሰኞ ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ፤ የምክር ቤቱ አባል የሆኑት የአቶ ታዬ ደንደአን ያለመከሰስ መብት ማንሳቱ ይታወሳል። ከትላንት በስቲያ ሐሙስ መደበኛ ጉባኤውን ያካሄደው የአማራ ክልል ምክር ቤትም፤ የአቶ ዮሐንስ ቧያለውን ያለመከሰስ መብት በተመሳሳይ መልኩ አንስቷል። በቀጣይነት የፓርላማ አባላቱ የክርስቲያን ታደለ እና የደሳለኝ ጫኔ ያለመከሰስ መብት ይነሳል።
ሮይተርስ የዜና ወኪል አካሄድኩት ባለው ለወራት የዘለቀ ምርመራ በኦሮምያ በክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት የተቋቋመ እና በህቡዕ የተደራጀ ኮሚቴ፣ የጸጥታ ሀይሎች ከፍተኛ ወንጀሎችን እንዲፈጸሙ፣ ተቃማሚዎችን እንዲያጠፉ ትዕዛዝ ይሰጥ ነበር ሲል አስታወቀ። የህቡዕ አደረጃጀት አለው የተባለው ኮሚቴው ስያሜው “ኮሬ ነገኛ” ወይንም የጸጥታ ኮሚቴ መሆኑን እና ዶ/ር አብይ አህመድ ጠ/ሚኒስትር ሁነው በተሾሙ ወራት ውስጥ የተቋቋመ መሆኑን የዜና አውታሩ በሪፖርቱ ጠቁሟል።
በኮሚቴው በተላለፈ ትእዛዝ ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎች፣ “የጸጥታ ስጋቶች” ናቸው በሚል የተፈጸሙ ጅምላ እስሮች በዜና አውታሩ ሪፖርት ተካተዋል። በ2014 ዓ.ም በከረዩ አባገዳዎች ላይ የተፈጸመው ግድያ ጋር በተያያዘ ሮይተርስ በምርመራ ማለትም ከሚስጥራዊ ሰነዶች እና ቃለምምልሶች አገኘሁት ባለው መረጃ ከህቡዕ አደረጃጃቱ በተላለፈ ትእዛዝ እንዲገደሉ ተደርገዋል ብሏል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የኮሚቴውን መኖር አረጋግጠልኛል ያለው ሮይተርስ ከኮሚቴው ጋር በተያያዘ የተፈጸሙ ከህግ አግባብ ውጭ ግድያዎች፣ የዘፈቀደ ጅምላ እስሮች እና ግርፋቶች በኮሚሽኑ ማጠናቀሩን ጠቁሟል።
የሮይተርስን ሪፖርት ለመመልከት ፡ https://minilik-salsawi.blogspot.com/2024/02/in-ethiopia-secret-committee-orders.html
በቦሌ አየር ማረፊያ በፍተሻ እና ጥበቃ አካላት ተጓዦች ላይ የሚፈፀም ውንብድና እና ዝርፊያ! ( ጋዜጠኛ ኤሊያስ መሰረት )
ድርጊቱ የተፈፀመው ሰኞ እለት (የካቲት 11/2016) ምሽት ላይ ነበር። ስሟን የማልጠቅሳት ትውልደ ኢትዮጵያዊ፣ የአሜሪካ ዜግነት ያላት ተጓዥ ማታ 5 ሰአት ወደ አሜሪካ ላለባት ጉዞ ቀደም ብላ 2 ሰአት ቦሌ ኤርፖርት ትደርሳለች።
በፍተሻው ወቅት “ሻንጣሽን ከፍተሽ አሳዪን፣ ማሽኑ የሆነ ነገር ያሳየናል” በማለት ሻንጣዎቿን አስከፈቱ። በዚህ ወቅት የያዘችውን የግል መገልገያ ጌጣጌጥ እና በህጋዊ መንገድ የያዘችውን ዶላር ይመለከታሉ። ቀጥላም ሁኔታውም ስታስረዳኝ እንዲህ ብላለች:
“እነዚህ ለብዙ አመታት ያደርግኳቸው ከቤተሰቦቼ እንዲሁም ከባለቤቴ የተሰጡኝ ጌጣጌጦች ናቸው። የሌላ ሀገር ዜግነት ላለው ዶላር እስከ 10,000 በህጋዊ መንገድ ይፈቀዳል፣ እኔ የያዝኩት ከዚህ በጣም ያነሰ ነበር። ጌጣጌጥ ደግሞ ማስመስገብ እንዳለብኝ አላውቅም ነበር። ስለዚህ ፈታሿን ይቅርታ ከዚህ በሗላ አስመዘግባለሁ አልኳት፣ ከዛም በሊፍት አድርጋ ለብቻዬ የሆነ ቦታ ወሰደችኝ።”
“በዚህ ወቅት ሌሎች ሰራተኞች ‘በጥሺላት’ እና ‘በቃ ስጫት’ ይሉኝ ነበር። እኔም ግራ ገብቶኝ የእኔ መሆኑን ማረጋገጥ ከፈለጋችሁ ጌጣጌጡ የሚታይበት የድሮ ፎቶ ላሳያችሁ ብላቸውም ፈቃደኛ አልሆኑም። ከዛም ተለቅ ወዳለች ሌላ ሴትዮ ጋር ወሰደችኝ። የሴትዮዋ መልስ ደግሞ ‘የሀገሪቱን ሁኔታ አታውቂም? ሀገሪቷ እኮ ወርቅ ያስፈልጋታል!’ ነበር።”
“በዚህ ሁሉ መሀል ይቺ ትልቅ ሴትዮ ተስማሚ፣ ካልሆነ በሙሉ ይወረሳል አለችኝ። ምን ማለት ነው ስላት በግልፅ ወርቁን አካፍዪ አለችኝ። በዚህ ወቅት ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ። እንደማይለቁኝ ስለገባኝ፣ ስልክ እንዳወራም ስለከለኩሉኝ ብዙ ትዝታዬ ያለበትን ጌጣጌጤን
የአንጋፋው ድምጻዊ ጌታቸው ካሣ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ
የአንጋፋው ድምጻዊ ጌታቸው ካሣ ሥርዓተ-ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ ወዳጆች፣ የሙያ አጋሮቹ፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የሙያ አድናቂዎቹ በተገኙበት በዛሬው እለት ተፈፅማል።
አንጋፋው ድምጻዊ ጌታቸው ካሳ ግማሽ ምዕተ ዓመትን በተሻገረው የሙዚቃ ሥራው፤ ዘመን አይሽሬ ሙዚቃዎችን ለአድማጮች ያበረከተ ሲሆን ጌታቸው የኢትዮጵያን ሙዚቃ ካዘመኑ ባለሙያዎች አንዱና በሙያ ሥራው አንቱታን አትርፏል።
የአዲስ አበባ ከተማ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማኅበራት ኅብረት ጋር በጋራ በመሆን ለድምጻዊ ጌታቸው ካሳ የስንብት መርኃ ግብር ዛሬ በብሔራዊ ቲያትር አካሂዷል።
ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረ እግዚብሔር ከህወሓት አባልነታቸው ተባረሩ
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በትግራይ ጦርነት ወቅት በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ውለው ከነበሩት ከፍተኛ አመራሮቹ ውስጥ ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረ እግዚብሔርን ከማዕከላዊ ኮሚቴ እና ከፓርቲ አባልነታቸው ማባረሩን አስታወቀ።
በእስር ላይ ከነበሩ አመራሮች መካከል ዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ እና ዶ/ር አብርሃ ተከስተ በፓርቲው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ ውሳኔ አሳልፏል።
ህወሓት በከፍተኛ አመራሮቹ ላይ ይህን ውሳኔ ያሳለፈው፤ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ትላንት ሐሙስ የካቲት 15፤ 2016 ካደረገው ስብሰባ በኋላ መሆኑን ገልጿል። ህወሓት በጦርነቱ ወቅት “በጠላት እጅ ወድቀው ነበር” ያላቸውን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን በተመለከተ “ለረጅም ጊዜ ሲንጓተት” የቆየውን ያስተላለፈው ውሳኔ፤ የነበሩትን ሁኔታዎች በመገምገም እና የፓርቲውን ህገ ደንብ በመከተል መሆኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።
በዚህም መሰረት “እጃቸውን ለጠላት በመስጠት” እና “ምስጢር አሳልፈው በመስጠት” የተገመገሙት የቀድሞው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም እና የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሙሉ ገብረ እግዚብሔር፤ ከማዕከላዊ ኮሚቴ እና ከፓርቲ አባልነታቸው “መባረራቸውን” ህወሓት አስታውቋል።
በትላንቱ ሰብሰባ “ከባድ ጸጸት” እንደተሰማቸው መግለጻቸው የተነገረላቸው ሁለቱ ተባራሪዎች ፤ ወደፊት “በተሰማሩበት የስራ መስክ ህዝቡን ለመካስ እንደሚሰሩ” ቃል መግባታቸውን የፓርቲው መግለጫ ጠቅሷል።
በራያ አካባቢ ዛታ ኦፍላ በተባለ ወረዳ ትናንት እኩለ ቀን ላይ በትግራይ ኃይሎችና በአማራ ክልል ታጣቂዎች መካከል ላጭር ጊዜ የቆየ የተኩስ ልውውጥ እንደተካሄደ ዋዜማ ከምንጮች ሰምታለች።
አንድ ሰዓት ገደማ ቆይቷል የተባለው የተኩስ ልውውጥ የቆመው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ጣልቃ መግባታቸውን ተከትሎ እንደኾነ ምንጮች ተናግረዋል።
በኹለቱ ወገኖች መካከል ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የተኩስ ልውውጥ ሲካሄድ የትናንቱ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
በተኩስ ልውውጡ ስለደረሰው ጉዳት ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የዐማራ ክልል ኃይሎች ራያ አካባቢን በኃይል ተቆጣጥረው እንደሚገኙ በተደጋጋሚ ይገልጣል።
የቤተክርስቲያንና የሰዎችን ክብርና መልካም ስም ማጉደፍ የተከሰሰው ኮሜዲያን ያሬድ ዘለዓለም (ልጅ ያሬድ) የወንጀል ድርጊት መፈጸሙ በፍርድ ቤቱ በመረጋገጡ በዛሬው ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ ተሰጥቶበታል።
++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም በቅጽል ስሙ ልጅ ያሬድ በተከሰሰባቸው የወንጀል ክስ ጥፋተኛ ተባለ። የጥፋተኝነት ፍርዱን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ሕገመንግስታዊና በሕገመንግስት ሥርዓቱ ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከተው ችሎት ነው።
የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በኮሜዲያን ያሬድ ዘለዓለም ላይ ሶስት ክሶችን አቅርቦበት ነበር።
ከቀረቡበት ክሶች መካከል በኮምፒዩተር የሚፈጸም ወንጀል ድንጋጌን መተላለፍ፣ የቤተክርስቲያንና የሰዎችን ክብርና መልካም ስም ማጉደፍ እንዲሁም የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት የሚሉ ተደራራቢ ክሶች ይገኙበታል።
ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም የቀረበበት ክስ እንዲሻሻል የክስ መቃወሚያውን በጽሁፍ ያቀረበ ቢሆንም በዐቃቤ ሕግ በኩል ክሱ ሊሻሻል የሚችልበት የህግ አግባብ እንደሌለ ተጠቅሶ መልስ ተሰጥቷል።
ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን መርምሮ ተከሳሹ ያቀረበው የክስ መቃወሚያ ጥያቄ የህግ አግባብነት የለውም በማለት ውድቅ አድርጎታል።
ከዚህም በኋላ ተከሳሹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸሙን በመጥቀስ የዕምነት ክህደት ቃሉን በመስጠቱ ዐቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃውን አቅርቧል።
የቀረበውን ማስረጃ የመረመረው ችሎቱ ተከሳሹ የቀረቡበት ሶስት ክሶች ተጠቃለው በአዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 እና 7 መሠረት እንዲከላከል ብይን ተሰጥቷል።
ሶስቱም ክስ በአንድ እንዲጠቃለል የታዘዘው የወንጀል ድርጊቱ በሀሳብ፣ በጊዜና በቦታ ተመሳሳይ መሆኑን በምክንያትነት ተጠቅሶ ነበር።
ተከሳሹ የመከላከያ ማስረጃ አለኝ ማለቱን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ያቀረባቸውን የሰው
ሶማሊላንድ ከኢትዮጵያ ጋር የተፈራረመችውን የባሕር በር መግባቢያ ስምምነት ወደ ትግበራ ለማስገባት የተለያዩ ርምጃዎችን እየወሰደች እንደምትገኝ የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ አስታወቋል።
የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ መንግሥት፣ የስምምነቱን አፈጻጸም የሚከታተል የቴክኒክ ኮሚቴ፣ ዓለማቀፍ የሕግ ባለሞያዎች እና ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን ማቋቋሙን ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጧል።
የሶማሊላንድ ልዑክ በአዲስ አበባ በተካሄደው 37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ስለ መግባቢያ ስምምነቱ ለበርካታ አገራት ባለሥልጣናትና ተወካዮች ገለጻ ማድረጉንና መልካም የሚባል ምላሽ ማግኘቱን አስታውቋል።
በሌላ በኩል፣ በኅብረቱ ጉባዔ ላይ ተሳታፊ የነበሩት የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ጋር የገቡበት እሰጣገባ ዓለማቀፍ የዲፕሎማሲ አካሄድን ያልተከተለና አሳዛኝ ነው በማለት መስሪያ ቤቱ በመግለጫው ኮንኗል።
የዝቋላ አቦ አባቶች በጭካኔ ተገደሉ
+++++++++++++++++++++
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሚገኘው ጥታዊው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም እራሱን ኦነግ ሸኔ ብሎ በሚጠራው ቡድን የገዳሙን መጋቢ ጨምሮ አራት አባቶችን መግደሉን ገዳሙ አስታውቋል፡፡
ሰኞ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓመተ ምሕረት ታጣቂዎቹ ሦስት አባቶችን አግተው ወደ በረሃ ከወሰዱ በኋላ የታገቱትን ለማስለቀቅ ገዳሙ ጥረት በሚያርግበት ወቅት የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተጨማሪ አባቶችን በመያዝ፦
1. የገዳሙ መጋቢ አባተክለማርያም ዐሥራት
2. የገዳሙ ጸሐፊ አባ ኪዳነ ማርያም ጥላሁን
3. የገዳሙ የመጽሐፍ መምህርና ቀዳሽ አባ ገ/ማርያም አበበ
4. በአመክሮ የሚኖሩ መናኝ ኃይለማርያም ወልደሰንበት
የተባሉት የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች እንደተገደሉና አብረው ከነበሩት አንድ አባት ብቻ ማምለጥ መቻላቸውን እንደተረዱ የገዳሙ ኃላፊዎች ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) ገልጸዋል፡፡
የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች ቡድኑ ከዚህ ቀደም ገዳሙን በመዝረፍ ለከፋ ችግር አጋልጦት መቆየቱን አስታውሰው ገዳሜ ጸጥታውን የሚያስከብረበት መሣሪያች በቡድኑ በመወረሳቸው ለከፋ የጸጥታ ችግር መጋለጡን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ገዳማውያ በስጋት ላይ መሆናቸውንና የመንግሥት የጸጥታ አካላትን እገዛ እንደሚሹ አስታውቀው መረጃውንም በየደረጃው ለሚገኙ የሀገረ ስብከቱና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ማሳወቃቸውን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያና የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት EOTC TV በክሰተቱ ሕይወታቸው ላጡ ሰማዕታት አባቶች የተሰማውን ኃዘን ይገልጻል፡፡ ጉዳዩ አስመልክቶ ዝርዝር መረጃ እየተከታተለ የሚያቀርብ መሆኑን ያስታውቃል፡፡
(ምንጭ EOTC TV)
የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ አምባሳደር ማይክ ሐመር በመቀሌ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ እና ከሌሎች የአስተዳደሩ ባለሥልጣናት ጋር ባደረጉት ውይይት፣ አሜሪካ የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲኾን በርትታ እንደምትሠራ ማረጋገጣቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
ሐመር እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ የመሩት ልዑካን ቡድንና የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ባለሥልጣናት ከመከሩባቸው ዝርዝር ጉዳዮች መካከል፣ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው የሚመለሱበትን ኹኔታ፣ አንዳንድ ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮችን ከጦርነቱ በፊት ወደነበሩበት መመለስ፣ የቀድሞ ተዋጊዎችን መበተንና መልሶ ማቋቋምና ድርቁ ያስከተለው ሰብዓዊ ቀውስ እንደሚገኙበት የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ሞሊ ፊ፣ ሐመር እና አምባሳደር ማሲንጋ፣ ከጥቂት ቀናት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ ከርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ጋር በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አተገባበር ዙሪያ መወያየታቸው ይታወሳል።
ቀጥታ ስርጭት
https://www.youtube.com/live/Hl1Y4_UGzdw?si=HjS_IFnXkMIfgiZ0
የኑሮ ውድነት፣ የዋጋ ንረት እና የገንዘብ ግሽበት ከየት ወደየት?
የኢትዮጵያ መንግስት ብርን የማራከስ ሂደትን መግታት አለበት- ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ
(አዲስ ማለዳ)
📍አንዲት እናት የኑሮ ውድነትን የዓመታት ጫና ለአዲስ ማለዳ ሲገልጹ “ከዓመታት በፊት ለቤቴ አስፈጭ የነበረው ጤፍ 50 ኪሎ ነበር። ዋጋው ሲጨምር ግን 25 ኪሎ እና ከዛም ያነሰ ማስፈጨት ጀምርኩ። አሁን ጭራሹኑ ትቻለው እንጀራ እየገዛን ነው የምንኖረው” ብለዋል።
📍የኢትዮጵያ መንግስት ብርን የማራከስ ሂደትን መግታት አለበት ሲሉ ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።
📍አዲስ ማለዳ በተወሰኑ የሸቀጣ ሸቀጥ መደብሮች ይኼ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በተመለከተቻቸው ዋጋዎች ጤፍ በኪሎ ከ60 ብር ወደ 150 ብር፣ ዘይት ባለ5 ሊትር 360 ብር የነበረው አሁን እስከ 920 ብር፣ መኮሮኒ በኪሎ ከ16 ብር ወደ 110 ብር፣ ምስር ከ45 ብር ወደ 160 ብር፣ ሽንኩርት ከ25 ብር ወደ 140 ብር በጥቂት ዓመታት ውስጥ መጨመራቸውን ተረድታለች።
አዲስ ማለዳ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በመታዘብ፣ ነዋሪዎች፣ የሸቀጣ ሸቀጥ ነጋዴዎች፣ የምግብና መጠጥ አቅራቢዎች እንዲሁም የምጣኔ ሐብት ምሁር አነጋግራ ያዘጋቸውን ዝርዝር ዘገባ https://addismaleda.com/archives/36193 ያንብቡ።
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌደሬሽን (ኢሠማኮ) “ኮንቬንሽን 189″፣ “190”፣ “97” እና”143″ የተባሉትን ዓለማቀፍ ድንጋጌዎች ኢትዮጵያ እንድታጸድቅ ዛሬ አገር ዓቀፍ ዘመቻ ጀምሯል።
አራቱ የቤት ሠራተኞችን፣ ፍልሰተኛ ሠራተኞችንና በሥራ ላይ የሚፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶችን የሚመለከቱት ድንጋጌዎች፣ የዓለም የሥራ ድርጅት ያወጣቸው ድንጋጌዎች ናቸው። “ኮንቬንሽን 189” የተሰኘው ድንጋጌ የቤት ሠራተኞችን መሠረታዊ መብቶች የሚመለከት ሲኾን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በ2011 ዓ፣ም ያወጣው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ የቤት ሠራተኞችን ከወሰኑ ውጭ ያደረገና ያለ ሕግ ከለላ የተዋቸው መኾኑን ኢሠማኮ ገልጧል።
“ኮንቬንሽን 190” የተሰኘው ዓለማቀፍ ድንጋጌ በሥራ ቦታ ላይ የሚደርሱ የጾታና ጥቃቶችንና ትንኮሳዎችን የሚመለከት ሲኾን፣ “ኮንቬንሽን 97” እና “ኮንቬንሽን 143” ባንጻሩ በውጭ አገራት የተሠማሩ የቤት ውስጥ ሠራተኞችን መብቶች የሚመለከቱ ናቸው።
እናት ፓርቲ፣ መኢአድ፣ ኢሕአፓና አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ያበረታታል የተባለውንና የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ አገራት ከአውሮፓ ኅብረት ጋር የተፈራረሙት የሳሞአ የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ስምምነት እንዳያጸድቅ ዛሬ ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል።
ፓርቲዎቹ፣ ኢትዮጵያ የፈረመችውን ይሄንኑ ስምምነት “ትውልድ አምካኝ” እና “አገር እና ማንነትን አጥፊ” ብለውታል። ምክር ቤቱ የስምምነቱን መጽደቅ ማስቀረት ካልቻለ፣ ቢያንስ ከግብረ ሰዶም ጋር የተያያዙ አንቀጾች ከስምምነቱ “እንዲወገዱ” ወይም “እንዲታረሙ” እንዲያደርግ ፓርቲዎቹ ጠይቀዋል።
ስምምነቱ “ለግብረ ሰዶምና ግብረ ሰዶማዊነት በተዘዋዋሪ መልኩ ጥበቃ የሚያደርጉ፣ የሚደግፉና የሚያበረታቱ” አንቀጾችን አካቷል ያሉት ፓርቲዎቹ፣ ኢትዮጵያ ስምምነቱን እንዳታጸድቅ የኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በጋራና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በተናጥል ጭምር ያሰሙት ተቃውሞ በከንቱ ሊታለፍ እንደማይገባም አሳስበዋል።
ምክር ቤቱ የሳሞአ ስምምነትን ካጸደቀ ግን፣ “የታሪክ ተጠያቂነት ይከተለዋል” በማለት ፓርቲዎቹ አስጠንቅቀዋል። የኢትዮጵያ ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ የግብረ ሰዶማዊነት ተግባርን ወንጀል አድርጎ ደንግጓል።
በአማራ ክልል በምሥራቅ፣ ምዕራብና ሰሜን ጎጃም ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች በመንግሥት ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ግጭቶች እንደቀጠሉ መኾኑን ተሰምቷል።
በተመሳሳይ በደቡብ ጎንደር እንዲኹም በሰሜንና ደቡብ ወሎ ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች ሰሞኑን በኹለቱ ወገኖች መካከል ግጭቶች መካሄዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል።
በተለይ በደቡብ ወሎ ዞን፣ በአምባሰልና ውጫሌ ከተሞች አካባቢ በሚካሄደው ግጭት ሳቢያ፣ በደሴ እና ወልድያ ከተሞች መካከል የትራንስፖርት እንቅስቃሴ መስተጓጎሉን ምንጮች ገልጸዋል።
እውቁ ድምፃዊ ጌታቸው ካሳ አረፈ
በይበልጥ ” ሀገሬን አትንኳት ” ፣ ” ውብ አዲስ አበባ ” ፣ ” የከረመ ፍቅር ” በተሰኙት ዘመን አይሽሬ የሙዚቃ ስራዎች የሚታወቀው አንጋፋው ድምፃዊ ጌታቸው ካሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ድምፃዊ ጌታቸው ባደረበት ህመም የካቲት 12 ሆስፒታል ውስጥ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ሀገሬን አትንኳት …
” የብዙሃን እናት መጠጊያ የምንላት
እማማ ናትና ሀገሬን አትንኳት።
በዓድዋ በማይጨው ጀግኖች የሞቱላት
ህፃን ሽማግሌ የተሰየፈላት
ደመ መራራና ቁጡነት ያለባት
ጎጆዬ ናትና ኢትዮጵያን አትንኳት !
ዘርዓይ ደረስ ወንዱ በሮሞ የቆመላት
ጀግኖች በጦር ሜዳ ወጥተው የቀሩላት
እኔም በተጠንቀቅ አለሁሽ የምላት
ጥቁሯን አፍሪካዬን ኢትዮጵያን አትንኳት። ”
NB. አንፋጋው ድምፃዊ ጌታቸው የተጫወተው ‘ ሀገሬን አትንኳት ‘ የተሰኘው ዘመን አይሽሬ ስራ በአንጋፋው ደራሲና ገጣሚ ጋሽ አበራ ለማ የተፃፈ ነው።
° በኢትዮጵያ 10.8 ሚሊዮን ህጻናት አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
° በ2024 በኢትዮጵያ ለ 20 ሚሊዮን ዜጎች ለሚደረግ ሰብአዊ እርዳታ እና የተለያዩ ሰብዓዊ ቀውሶችን ለመከላከል 535 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልገኛል።
የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በኢትዮጵያ በ2024 በትንሹ 10.8 ሚሊዮን ህጻናትን ጨምሮ 20 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን አዲስ ባወጣው የኢትዮጵያ የሰብአዊ ሁኔታ ሪፖርት አስታውቋል።
ዩኒሴፍ በ2024 በኢትዮጵያ ተጋላጭ ማህበረሰቦች እያጋጠማቸው ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግሮች አሳሳቢ መሆናቸውን የገለፀ ሲሆን በሀገሪቱ እጨመሩ ያሉ ፈተናዎችን ለመቅረፍ እና በ2024 ይከሰታሉ ተብሎ የተገመቱትን ችግሮችና የሚያደርሱትን አስከፊ ቀውሶች ለመከላከል 535 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደሚያስፈልግ በሪፖርቱ አመልክቷል።
በተጠናቀቀው የፈረንጆቹ 2023 ዓመት ውስጥ ባሉት 12 ወራት በኢትዮጵያ የግጭት፣ ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋ እና የበሽታ ወረርሽኝ ወደ 31.4 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ለችግር ዳርጓል ያለው ዩኒሴፍ በተጨማሪም 7.6 ሚሊዮን ህጻናት ከትምህርት ገበታቸው ውጪ እንዲሆኑ እንዳደረጋቸውም ነው የጠቆመው።
ዩኒሴፍ በ2023 በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች ድጋፍ ሊያደርግ ካቀዳቸው ሰዎች ውስጥ 42 በመቶ ለሚሆኑት እርዳታ ያደረሰ መሆኑን ሲገልፅ በ2024 በሀገሪቱ በስድስት ክልሎች አዲስ እና ውስብስብ ችግሮች እየተከሰቱ በመሆኑና ነባር ችግሮችንም የሚያባብስ በመሆኑ በመላ ሀገሪቱ 10.8 ሚሊዮን ሕፃናትን ጨምሮ ቢያንስ 20 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ ሰብዓዊ ዕርዳታ ያስፈልጋቸዋል ሲል አሳስቧል።
የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ከኢትዮጵያ የተዘረፈውን ቅዱስ ታቦት ለመመለስ በመርህ ደረጃ ተስማማ
በእንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን የዌስትሚኒስተር ከተማ የሚገኘው የቀድሞው የቅዱስ ጴጥሮስ የአሁኑ ዌስት ሚኒስትር አቢ ቤተ ክርስቲያን ከኢትዮጵያ የተዘረፈውን ቅዱስ ታቦት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለመመለስ “በመርህ ደረጃ” መስማማቱን አስታውቋል፡፡
“የኢትዮጵያን ታቦት ወደ ኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መመለስ ተገቢ መሆኑን የቤተክርስቲያኑ ዲንና ቀሳውስት ማህበር በመርህ ደረጃ ወስኗል” ሲሉ የአቢ ቤተክርስቲያን ቃል አቀባይ ተናግረዋል።
ለስምምነቱ እንዲረዳ ” ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተወካዮች ጋር ቀጣይነት ያለው ንግግር እደረግን ነው” ያሉት ቃል አቀባዩ ጉዳዩ ውስብስብ ስለሆነ ውይይቱ ጊዜ ሊወስድ እንደሚችልም ገልፀዋል።
ታቦቱ በ1860 ዓ/ም በነበረው የመቅደላ ጦርነት ወቅት በእንግሊዝ ወታደሮች ከተዘረፈበት ጊዜ ጀምሮ በዌስትሚኒስትር አቢ ቤተክርስቲያን ውስጥ መቆየቱ ተጠቁሟል።
የእንግሊዝ ቤተክርስቲያን ቅርሱን ለመመለስ አቋሙን የቀየረበትን ምክንያት ባያሳውቅም ቀደም ሲል የተዘረፉ ቅርሶችን እንዳይመልስ ከሌሎች የአውሮፓ ተቋማት ጫና ሲደረግበት ቆይቷል ተብሏል።
የዌስትሚኒስትር አቢ ቤተ ክርስቲያን በንጉሠ ነገሥቱ ሥልጣን ስር የሚተዳደር በመሆኑ ለቅዱስ ታቦቱ መመለስ የንጉስ ቻርለስን ፍቃድ ይጠይቃል ሲል የዘገበው ዘ ጋርዲያን ነው።
የትግራይ ኃይል ታጣቂዎችን ያለበቂ ስልጠና ወደ ፖሊስና ማረሚያ ቤት ስራዎች ማስገባት ለእስረኞችና ተጠርጣሪዎች ስጋት ነው- ኢሰመኮ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን፣ ሰሜን ምዕራብ ዞን፣ ደቡብ ዞን፣ ደቡብ ምስራቅ ዞን እንዲሁም በመቀሌ ልዩ ዞን በሰብዓዊ ሁኔታዎች እና በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሰኔ 30 ቀን 2015 እስከ ሐምሌ 23 ቀን 2015 የተደረገ ክትትልን በ40 ገጽ ሪፖርት ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2016 ይፋ አድርጓል።
ኢሰመኮ በሪፖርቱ እንዳስታወቀው ከፕሪቶሪያው የሠላም ስምምነት በኋላም በትግራይ ክልል በኤርትራ መከላከያ ሠራዊት እና በአማራ ኃይል ቁጥጥር ስር ከሚገኙት አካባቢዎች የወጡ አንዳንድ ሰዎች የወሲባዊ እና ጾታዊ ጥቃት ደርሶባቸዋል ብሏል።
አብዛኛዎቹ የጥቃቶቹ ሰለባዎች በክልሉ የጤና ዘርፍ አጠቃላይ ሁኔታ የህክምና፣ የስነ-ልቦና፣ የህግ እና የመልሶ ማቋቋም አገልግሎቶች ወሳኝ እጥረት ያጋጠማቸው በመሆኑ አገልግሎት ለማግኘት መቸገራቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል። በተጨማሪም ከወሲባዊ እና ጾታዊ ጥቃት የተረፉ ሰዎች ከማህበረሰቡ ዘንድ መገለል ደርሶባቸዋል የተባለ ሲሆን ይህም ብዙዎች መሰል ጥሰቶችን ከማጋለጥ እንዲቆጠቡ እና ህክምና እንዳይፈልጉ ማድረጉን ኢሰመኮ አሳስቧል።
በትግራይ ክልል የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች በሚገኙባቸው አካባቢዎች የመጠለያ እና የጤና አገልግሎትን ጨምሮ ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች በጣም የጎደሉ እና የማይመጥኑ እንደሆኑ ሪፖርቱ አመላክቷል። ለዘጠኝ ወራት ገደማ ከዋና ዋና ደጋፊዎች ተቋርጦ የቆየው እርዳታ ችግሩን አባብሶታልም ሲል ኢሰመኮ ገልጿል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ በክልሉ እየታየ ያለው “የሰብዓዊ መብት ሁኔታ መሻሻልን” በደስታ ተቀብለው “ሰብዓዊ ስጋቱን ለመቅረፍ
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮችን “በግዳጅ ወደ ወለጋ እየተጓዙ” ነው ሲል ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አስታወቀ
(አዲስ ማለዳ) “በሽብርተኛው ሸኔና በኦሮሚያ ልዩ ኃይል” ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ተጠልለው የነበሩ የአማራ ተወላጅ ተፈናቃዮችን “የብልፅግና አገዛዝ በፖሊስ እያስገደደ ወደ ወለጋ አካባቢ እየጫኗቸው መሆኑን ተፋቃዮቹ” ነግረውኛል ሲል ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ገለጸ።
በደብረ ብርሃን ከተማ በተለያዩ የመጠለያ ጣቢያዎች ከተጠለሉ ተፈናቃዮች መካከል “ኦሮሚያ ክልል” መሬት ያላቸው የአማራ ተወላጆች ብቻ ወደ ተፈናቀሉበት ወለጋ አካባቢ በግዴታ እንዲመለሱ መደረጉንም ጠቁመዋል።
“ስማችሁ ከወለጋ የተላከ ነው “ በሚል የታጠቁ ኃይሎች በግዴታ ከመጠለያ ካምፕ አውጥተው ወደ ወለጋ እንደወሰዷቸው ከተፈናቃዮቹ አውቂያለው ሲልም ፓርቲው አስታውቋል፡፡
ባልደራስ ከተፈናቃዮች አገኘው ባለው መረጃ መሰረት “ያለምንም ዋስትና ለእልቂት ወደ ወለጋ አንሄድም በማለት በርካታ ተፈናቃዮች የመጠለያ ካምፑን ለቀው የጠፉ ሲሆን በርካቶች በፖሊስ ተገደው የካቲት 10 ቀን2016 ጀምሮ ወደ ወለጋ መጫናቸው” አመላክቷል።
በተጨማሪም አንድም ተፈናቃይ “በግዳጅ ወደ ወለጋ የተጫነ መሆኑን ለሚጠይቀው አካል መናገር እንደሌለበት ማስፈራሪያ እንደተሰጠ እና ተፈናቃዮችን ወደ ቦታቸው መልሰናል ለማለት የሚደረግ ሴራ መሆኑን መናገራቸውን” ፓርቲው ካወጣው ጽሁፍ አዲስ ማለዳ ተረድታለች።
የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ዛሬ በሱማሊያ ጉዳይ ላይ በዝግ ያመክራል።
የተመድ ዋና ጸሃፊና የአፍሪካ ኅብረት የሰላም የሽግግር ተልዕኮ ተወካዮች በአገሪቱ ጸጥታና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ይሰጣሉ። ጸጥታው ምክር ቤት፣ ኢትዮጵያና ሶማሊላንድ የተፈራረሙትን የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት በሱማሊያ ጥያቄ፣ ጥር 20 ቀን በዝግ ተወያይቶበት ነበር።
ኾኖም የምክር ቤቱ ተለዋጭ አባላት የኾኑት፣ አልጀሪያ፣ ሞዛምቢክ፣ ሴራሊዮንና ጉያና ጉዳዩን ቀጠናዊ ድርጅቶች ይዘውታል በማለታቸው፣ ምክር ቤቱ ሊያወጣው አስቦት የነበረውን መግለጫ መሰረዙን ከምክር ቤቱ የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል።
አራቱ ተለዋጭ አባላት፣ ባለፈው ሳምንት ዓርብ ጸጥታው ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ በድጋሚ ሊያካሂድ የነበረውን ሌላ ምክክርም፣ በቅድሚያ የአዲስ አበባው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ውጤት ይታወቅ የሚል አቋም በማንጸባራቃቸው ወደ ዛሬ መዛወሩ ተገልጧል።
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሺመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሞ ሕዝብና መንግሥት የመጀመሪያውም ኾነ የመጨረሻው ተልዕኮው ይህን መንግሥታዊ ሥርዓት መጠበቅ ነው በማለት መናገራቸውን የክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
ሺመልስ ትናንት በጨፌ ኦሮሚያ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የኦሮሞ ሕዝብ በሕይወት መስዋዕትነት ያገኘውን ድልና ነጻነት ሊያሳጡት ከውስጥም ከውጭም የሚያሴሩ አካላትን በንቃት ሊከታተል እንደሚገባ ማሳሰባቸው ተጠቅሷል።
ሥልጣን ባቋራጭ ለመያዝ የሚያልሙ ኃይሎች ሃሳባቸው በጭራሽ ሊሳካ አይችልም ያሉት ሺመልስ፣ በእነዚህ ኃይሎች ላይ መንግሥት የሚወስደው ርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸውን ቢሮው ገልጧል።
መንግሥት ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ጋር ችግሩን በውይይት ለመፍታት አኹንም በሩ ክፍት መኾኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል ተብሏል። ጨፌው በዛሬው ውሎው፣ እስር ላይ የሚገኙትን የምክር ቤት አባሉን ታዬ ደንደአን ያለመከሰስ መብት አንስቷል።
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዘርፍ ቢሮዎች እስከ ዞን አስተዳደሮች ድረስ በኹሉም መዋቅሮች የአመራር ለውጥ ሊያደረግ መኾኑን ዋዜማ ከኹነኛ ምንጮቿ ሰምታለች። የክልሉ ምክር ቤት ከትናንት ጀምሮ እያካሄደው በሚገኘው መደበኛ ስብሰባው፣ የአመራሮችን ምደባ መበወዝ አስፈላጊ መኾኑን አምኖበት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰኑን ዋዜማ አረጋግጣለች። የአመራር ለውጡ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር እና ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ያካትት እንደኾነ ዋዜማ ለጊዜው ማረጋገጥ አልቻለችም። ኾኖም በርካታ የክልሉ መዋቅሮች ላይ የአመራር ለውጥ እና ሽግሽግ እንደሚደረግ መረዳት ተችሏል፡ በተለይ በዞን መዋቅሮች ላይ አመራሮችን ከተወለዱበት አካባቢ ውጭ በአመራርነት እንዲመደቡ የማድረግ ዕቅድ እንዳለ ምንጮች ለዋዜማ ጠቁመዋል።ዝርዝሩን ያንብቡት- http://tinyurl.com/bdxn3chd
ዛሬም ኢትዮጵያ ውስጥ የፍትሕና የዴሞክራሲ ጥያቄ አለመመለሳቸው ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ እንደ ሀገር መቀጠልም አደጋ ላይ ወድቋል!
የዛሬ ሃምሳ ዓመት በዛሬዋ ዕለት መምህራን የሥራ ማቆም አድማ ጠሩ፣ የታክሲ ሹፌሮች ሥራ አቁመው የነዳጅ ማደያዎችን አገልግሎት እንዳይሰጡ አደረጉ እናም አብዮቱ ገሀድ ሆኖ በተግባር በአደባባይ የተገለፀበት ዕለት የካቲት 11/1966 ዓ.ም. ነው ቢባል ስህተት አይሆንም፡፡ የ66ቱ አብዮት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ምን ግዜም ሲታሰብ የሚኖርና ያለፉትን ሃምሳ ዓመታት የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ ምጣኔሃብታዊ እና ማኅበራዊ ህይወት የቀረጸ ዐቢይ ክስተት ነው። በተለምዶ አብዮቱ የፈነዳው ግብታዊ በሆነ መንገድ ነው እየተባለ ሲነገር የቆየ ቢሆንም፣ “የታህሳስ ግርግር” በመባል የሚታወቀው የነጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ እንቅስቃሴና የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴ የመሳሰሉ ክስተቶች የአብዮቱ አቀጣጣዮት ነበሩ ማለት ይቻላል።
በ1966 ወርሃ የካቲት ላይ የፈነዳው አብዮት የመሬት ላራሹን ጥያቄ፣ የትምህርት መዳረስና እኩልነት ጥያቄ፣ የኑሮ ልዩነት ጥያቄ፣ የሥልጣን መጋራት ጥያቄ፣ የእኩልነት ጥያቄ እና የመሳሰሉ የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱበት ቢሆንም ለዚህ አብዮት መምጣት ዋናውና ቁልፉ ጥያቄ ከላይ የተጠቀሱትን ጥያቄዎች ሁሉ አቅፎ የያዘው የፍትሕ ጥያቄ ነው። ይህንን ጥያቄ ለመመለስ ሁለት የተለያዩ መንግሥታት ተራ በተራ እየመጡ ሄደው ዛሬ ሶስተኛው መንግስት ኢትዮጵያን እያስተዳደረ ይገኛል።
ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ኢትዮጵያ የተጓዘችበትን ጠመዝማዛ መንገድ ስንመለከት ወለል ብሎ የሚታየን እያንዳንዱ አራት ኪሎን የተቆጣጠረ መንግሥት የኢትዮጵያ ሕዝብ የጠየቀውን የፍትሕ ጥያቄ ለመመለስ የማንም ዕርዳታና ምክር ሳያስፈልገው በራሱ መንገድ ሲጓዝ፣ አንዱ የገነባውን ሌላው ሲያፈርስ፣ ነጻ አውጪ ነኝ ባዩና ዴሞክራሲ አሰፍናለሁ ባዩ ጎራ