Home › View all posts by Konjit Sitotaw
Blog Archives

የተፈፀመው ጭፍጨፋ ዓለምአቀፋዊ ወንጀል ነው!
*****
በደብረ ኤልያስ አጼ መልክአ ሥላሴ ገዳም ባሉ ገዳማውያን መነኮሳት፣ ገዳሙ የሚያሳድጋቸው ሕፃናት እና መንፈሳዊ ፈውስን ፈልገው በገዳሙ በነበሩ ፀበልተኞች ላይ የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች የፈፀሙትን ከሕግ ውጭ የሆነ ጭካኔ የተሞላበት ግድያ በጽኑ አወግዛለሁ።
ራሱን «የጋራ የፀጥታ ግብረ ኃይል» እያለ የሚጠራው ቡድን የኢፌዴሪ ሕገመንግስትንና ኢትዮጵያ የፈረመቻቸውን ዓለምአቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎች በሚገረስስ መልኩ ባልተመጣጠነ፣ ያለ ልዩነት፣ ጭካኔ በተሞላበት አኳኋን እና ከሕግ ውጭ የፈፀማቸው ግድያዎች የ«ማንነት ተኮር ጅምላ ጭፍጨፋ» እና «ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት» ተብሎ የሚወሰድ ነው።
መላው ኢትዮጵያውያን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሰብአዊ መብት ተቋማት፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡና ሚዲያዎች ይህንን አስነዋሪ ድርጊት በጽኑ እንድታወግዙትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጫና ታደርጉ ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ታደለ
(አዲስ ማለዳ) በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር ዛሬ ማለዳ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ገብተዋል።
ልዩ መልዕክተኛው ወደ መቐለ ያቀኑት ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ለመነጋገር መሆኑም ተገልጿል።
ሐመር መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደረሱ በትግራይ ጊዜዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳን ጨምሮ በአስተዳደሩ የካቢኔ አባላት አቀባበል እንደተደረገላቸው የክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።
በትግራይ ቆይታቸውም በፕሪቶሪያ ስምምነት አፈፃፀም፣ በሽግግር ፍትሕና ተጠያቂነት እንዲሁም ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
አምባሳደሩ እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ትሬሲ አን ጃኮብሰን ከጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ ጋር መወያየታቸውም ተነግሯል።
ማይክ ሐመር ካሳለፍነው ረቡዕ ጀምሮ በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረጉ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸውም የሽግግር ፍትሕ እና የተጠያቂነት ጉዳይን እንዲሁም ትጥቅ ማስፈታትን፣ ተዋጊዎችን መበተን እና መልሶ ማቋቋምን ጨምሮ የስምምነቱ አተገባበር ሂደትን እና ቅድሚያ ሊሰጣቸው ስለሚገቡ ጉዳዮች እንደሚያነሱ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ማስታወቁ ይታወሳል።
አምባሳደሩ የኢትዮጲያ ቆይታቸውን ሲያጠናቅቁ ወደ ጂቡቲ የሚያቀኑ ሲሆን፤ በጂቡቲም በዩናይትድ ስቴትስ አፍሪካ ኮማንድ እና በአፍሪካ ቀንድ ጥምር ኃይል አዘጋጅነት በሚካሄደው የምሥራቅ አፍሪካ የደኅንነት ፎረም ላይ እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
በተጨማሪም ከጂቡቲ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው በኹለትዮሽ እና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ የተባለ ሲሆን፤ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅትን (ኢጋድ) የቅርብ ጊዜያት እንቅስቃሴዎችን ለመቃኘት ከተቋሙ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጋር እንደሚገናኙም ተጠቁሟል።
አምባሳደር ማይክ ሐመር ከጥቂት ሳምንታት በፊት በአሜሪካ ከሚገኙ የተለያዩ የኢትዮጵያ
ከአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ የተሰጠ ማብራሪያ!
ከግማሽ ምዕተ-ዓመት ወዲህ ባለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እንደ አማራ ህዝብ የመከራ ዶፍ የወረደበት ህዝብ በኢትዮጵያ ምድር የለም። በአለም ላይ በከፍተኛ ወንጀልነቱ የሚጠራው መንግስታዊ የዘር ማጥፋት እንኳን ሳይቀር በአማራ ህዝብ ላይ ለግማሽ ምዕተ-ዓመት ሙሉ ያለ ከልካይ ተፈጽሟል። ይህን አሰቃቂ ወንጀል የፈጸሙት የወያኔና የአሁኑ ኦነግ-ብልጽግና መንግስት ለዚህ ወንጀላቸው የጠየቃቸው የለም። እነዚህ በአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት፣ ዘር ማጽዳት እና ዘር ማሳሳትን የመሰሉ ከባድ ወንጀሎችን የፈጸሙ መንግስታት የማይጠይቁት የአማራ ህዝብን ሰቆቃ በሚመጥን መንገድ ከአማራው ሊሂቅ በኩል ኮስተረ ያለ ትግል ባለመደረጉ ነው። በዚህ ረገድ እሰከ ሞት ድረስ ቆርጠው ለአማራ ህዝብ የታገሉ እንደ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያሉ የአማራ ልጆችን ትግል በክብር የምናስታውሰው መሆኑን ማሳሰብ እንወዳለን፣ ሆኖም ከፕሮፌሰር አስራት ሞት ወዲህ የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የመኖር ያለመኖር ስጋት የሚመጥን ትግል ማድረግ አልተቻለም። የአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ የተመሰረተውም ይህን የትግል ክፍተት ለመሙላት ነው ።
የአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ ከሁለት አመት በፊት የአማራ ህዝብን ጥቃት መቀበል ባቃታቸው የአማራ ተወላጆች የተመሰረተ የአማራ ተቆርቋሪዎች ስብስብ ነው። ኮሚቴው ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል። ከነዚህ ውስጥ ዋንኛው የአማራ ህዝብን ትግል የሚያመክኑ አደናቃፊ ሁነቶችን መተንተንና ከአማራ ህዝብ የትግል መንገድ ላይ የሚወገዱበትን ስትራቴጂ መቅረጽ ነው። በተጨማሪም በአማራ ህዝብ ትግል ውስጥ የነበሩ ክፍተቶችን መርምሯል፤ የወቅታዊና መሰረታዊ የፖለቲካ ሁኔታዎችን ከጂኦ-ፖለቲካዊና ሀገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች አንጻር በመገምገም ከአማራ ህዝብ ትግል አኳያ የሚቃኝበትን መንገድ መትሯል።
የብልጽግና ፓርቲ አባላት ብዛት 13.5 ሚሊዮን መድረሱን ፕሬዝዳንቱ አስታወቁ
የገዢው ብልጽግና ፓርቲ አባላት ብዛት 13.5 ሚሊዮን መድረሱን የፓርቲው ፕሬዝዳንት የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ፓርቲው ባለፉት ወራት በመቶ ሺህ አባላቱ ላይ “የማጥራት” እርምጃ መውሰዱን የገለጹት አብይ፤ ወደፊትም ተመሳሳይ አካሄድ መከተል እንደሚያስፈልግ ጥቆማ ሰጥተዋል።
አብይ ይህን ያሉት ካለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ ስብሰባውን በማካሄድ ላይ ለሚገኘው የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በሰጡት ገለጻ ነው። አብይ ወቅታዊውን የፓርቲያቸውን አባላት ብዛት ጉዳይ የጠቀሱት፤ “የኢንተርፕሪዩነራል መንግስትን” የመፍጠር አስፈላጊነት ባስረዱበት የገለጻቸው ክፍል ላይ ነው።
ብልጽግና ፓርቲን “በአፍሪካ ትልቁ” ሲሉ የጠሩት የፓርቲው ፕሬዝዳንት፤ በአሁኑ ወቅት ፓርቲው 13.5 ሚሊዮን አባላት እንዳሉት በገለጻቸው አስታውቀዋል። ብልጽግና ፓርቲ አንደኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በመጋቢት 2014 ባካሄደበት ወቅት፤ ፓርቲው ያሉት አባላት ብዛት 11 ሚሊዮን እንደሆነ አብይ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ላይ ጠቅሰው ነበር። የአብይ የአሁኑ ገለጻ፤ 2.5 ሚሊዮን አዳዲስ አባላት ባለፈው አንድ ዓመት ገደማ ጊዜ ውስጥ ገዢውን ፓርቲ መቀላቀላቸውን ያመለከተ ሆኗል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11111/
መንግስት ሰብዓዊ መብቶችን የማክበር እና የማስከበር ሃላፊነቱን በአግባቡ ይወጣ
የኢሰመጉ አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ-ግንቦት 27/2015 ዓ.ም
–
ሙሉውን የኢሰመጉ ጋዜጣዊ መግለጫ ከቴሌግራም ቻናላችንን ላይ ማግኝት ይችላሉ።
https://t.me/ehrco/1799
–
የአስገድዶ መሰወር ወንጀልን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመከላከል ይረዳ ዘንድ፤ ሁሉንም ሰዎች ከአስገድዶ መሰወር ለመጠበቅ የተደረገውን ዓለም አቀፍ ስምምነት (International Convention for the Protection of All Persons from Enforced Disappearance) ኢትዮጵያ በአስቸኳይ ተቀብላ ልታጸድቅ ይገባል

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ/ኮሚሽኑ) በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ አካባቢዎች እየጨመረ የመጣውን የአስገድዶ መሰወር (Enforced Disappearance) እና ተይዘው የሚገኙበት ሁኔታ ሳይታወቅ በእስር ላይ የሚገኙ (Incommunicado Detention) ሰዎችን ጉዳይ ሲከታተል ቆይቷል።
በተለይም ይህ አሳሳቢ ሁኔታ በተከሰተባቸው የአዲስ አበባ ከተማ፣ የኦሮሚያ ክልል እና የአማራ ክልል ኮሚሽኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን መንግሥታዊ ኃላፊዎች በማነጋገር፣ በልዩ ልዩ የተጠርጣሪዎች ማቆያ ቦታዎች በመዘዋወር እና ከቤተሰቦችና ከሌሎች የመረጃ ምንጮች መረጃዎችን ሲያሰባስብ ቆይቷል።
ኢትዮጵያ ገና ያላጸደቀችው ቢሆንም ሁሉንም ሰዎች ከአስገድዶ መሰወር ለመጠበቅ በተደረገው ዓለም አቀፍ ስምምነት (International Convention for the Protection of All Persons from Enforced Disappearance) መሠረት አስገድዶ መሰወር ማለት ‘’በመንግሥት ወኪሎች ወይም ከመንግሥት ፈቃድ ወይም ድጋፍ በተሰጣቸው ሰዎች ወይም ቡድኖች ወይም በመንግሥት ስምምነት አንድን ሰው በማሰር፣ አፍኖ በመውሰድ፣ ወይም በሌላ በማናቸውም መንገድ ነጻነቱን በማጥፋትና፤ በቁጥጥር ስር መዋሉን በመካድ፣ በመደበቅ፣ የአለበትን ቦታ ባለማሳወቅ ወይም ደብዛውን በማጥፋት ፈጽሞ ከሕግ ጥበቃ ውጪ እንዲሆን ማድረግ’’ ነው።
በሌላ በኩል አንድን ሰው የሚገኝበትን ቦታና ሁኔታ ሳይታወቅ በእስር መያዝ (Incommunicado Detention) ማለት በተለይ በከባድ ወንጀል ተጠርጥሯል የተባለን ሰው ለወንጀል ምርመራ በሚል ምክንያት ከቤተሰብ እና ከጠበቃ እንዳይገናኝ አድርጎ በእስር
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሁመራ እና ማይካድራ ከተሞች ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል። ሰልፈኞቹ የወልቃይት እና የራያ አማራ ማንነት ጥያቄን የርእስት ማስመለስ ስም በመስጠት ወደ ኋላ መመለስ አይቻልም፣ ሀገር ርእስት ነዉ፣ ለርእስት መሞት ደግሞ ክብር ነዉ ብለዋል። በበጀት ክልከላ የሚጣል ማንነት፣ በፈተና ብዛት የሚዝል አማራነት የለም ሲሉም አስገንዝበዋል።
የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዲሱ ማለፊያዉ ለሰልፈኞቹ ባስተላለፉት መልእክት የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ሕዝብ አሁናዊ ኹኔታዉ ፈተና ያለበት መኾኑን ተናግረዋል። በተለይም ለረጂም ጊዜ የማንነት ጥያቄው መልስ ያልተሰጠው፣ በጀት እስካሁን ያልተለቀቀለት እንዲሁም በአካባቢዉ የፍትሕ ሥርዓት ያልተዘረጋለት መኾኑን አንስተዋል። እነዚህን መሰል ችግሮች እንዲፈቱም ጠይቀዋል። በሰልፉ ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘዉዱ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ከፍ ሲል ኢትዮጵያዊ ዝቅ ሲል አማራ ነዉ፤ የሕዝቡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄም በተገቢዉ መልኩ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።
የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ሕዝብ ጥያቄ በዋለ ባደረ ቁጥር ለሐሰት ፕሮፖጋንዳ፣ ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት አድሏዊ ፍርድ እየተጋለጠ መሆኑንም አንስተዋል። እንደ ኢትዮጵያዊነታችን በጀት፣ እንደ አማራነታችን ደግሞ ማንነታዊ እውቅና እንዲሰጥ በዚህ ሰልፍ እጠይቃለሁ ብለዋል። በሰልፉ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የከተማ አሥተዳደሮች እንዲሁም የዞን የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ከኦሮሚያ ክልል፣ ከአዲስ አበባ ዙሪያ እና ከአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ተፈናቅለው በደብረ ብርሃን ከሚገኙ ተፈናቃዮች ውስጥ በርካታ ወጣቶች ለሕገወጥ ስደት መዳረጋቸው ተገለጸ፡፡
በመጠለያ ጣቢያዎች “ቁጭ ብለው አማራጭ ያጡ በርካታ ወጣቶች በዋናነት ወደ አረብ አገር በብዛት እየተሰደዱ ነው።” ሲሉ፤ በከተማዋ የሚገኙ ተፈናቃዮች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡
“ቁጥራቸው በርካታ የሆነ ወጣቶች መንገድ ላይ መሞታቸውን ሰምተናል፣ ገብተናል ብለው የደወሉልንም አሉ” ያሉት ተፈናቃዮች፤ ቁጥራቸው የማይታወቅ ብዙ ወጣቶችም የደረሱበት እንደማይታወቅ ተናግረዋል፡፡
ወጣቶቹ ወደ አረብ አገራት የሚሄዱት በየመን በኩል አድርገው ነው የተባለ ሲሆን፤ አሁንም ብዙ ወጣቶች በሕገወጥ መንገድ ከአገር ስለመውጣት እንደሚያስቡ ተገልጿል፡፡
በከተማዋ 40 ሺሕ ገዳማ ተፈናቃዮች መኖራቸው በመጥቀስ፤ መንግሥት ከአራት ወራት አንድ ጊዜ የበቆሎ ዱቄት እና ዘይት እንደሚሰጣቸውም ተናግረዋል፡፡
በዚህም ሰሞኑን የበቆሎ ዱቄት እንደተሰጣቸው ገልጸው፤ “ይሁን እንጂ ጥራቱን የጠበቀ ባለመሆኑ እንጀራም ይሁን ገንፎም አድርገን ልንጠቀመው የማንችል ነው። ሲሉም ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡
በመጠለያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ረሃብ አለ የተባለ ሲሆን፣ ብዙ ቤተሰብ ያላቸው እናቶች እንዲሁም ሕጻናት ጎዳና ላይ ወጥተው እንደሚለምኑ ተጠቁሟል፡፡
እንዲሁም በቅርቡ ቻይና ካምፕ ተብሎ ወደሚጠራው መጠለያ ጣቢያ የገቡ ከ3 ሺሕ በላይ ሰዎች፤ “በመንግሥት አልተመዘገባችሁም” በሚል ምንም ዓይነት እርዳታ ስለማያገኙ ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸው ተገለልጿል፡፡
“መሄጃ ስለሌለን ቁጭ ብለናል።” የሚሉት ተፈናቃዮቹ፤ “ተፈናቅለን ከመጣንበት የወለጋ አካባቢዎች አሁንም ድረስ ሰዎች እየተገደሉ ስለሆነ ተመልሰን አንሄድም፡፡ መጨረሻችን ምን እንደሆነም የምናውቀው ነገር የለም” ሲሉም ተደምጠዋል፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር በዞኑ ከ70 ሺሕ
በአማራ ክልል በሚገኙ አምስት ዞኖች ሐሰተኛ ገንዘብ በብዛት እየተንቀሳቀሰ መሆኑንና ይህም በጎንደር፣ ምዕራብ ጎጃም፣ አዊ እና ሰሜን ሸዋ በዋናነት እየተስተዋለ እንደሚገኝ ተገለጸ።
የሐሰተኛ ገንዘብ ህትመቶቹ በብዛት የኹለት መቶ ብር ኖት እና የአሜሪካ ዶላር መሆናቸው ተገልጿል።
በዘንድሮው በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ብቻ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ሐሰተኛ የኢትዮጵያ ገንዘብ ኖት እና ከ14 ሺሕ በላይ የአሜሪካ ዶላር በቁጥጥር ሥር መዋሉን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ለአዲስ ማለዳ አስታውቋል።
የሐሰተኛ ገንዘብ ዝውውሩ በቁም እንስሳት ግብይት ላይ ጎልቶ መታየቱ የተገለጸ ሲሆን፤ ሰዎች ግብይታቸውን ለማሳለጥ ደፋ ቀና ሲሉ ያልጠበቁት ኪሳራ እያጋጠማቸው እንደሆነ ነው የተጠቆመው።
‹‹ተገልጋዮች ግብይታቸውን ጨርሰው ወደ ባንክ ቤት ሲሄዱ ሐሰተኛ ወይም ፎርጅድ ብር እየሆነ እየከሰሩ ናቸው። በድርጊቱ ሲሳተፉ የነበሩ ግለሰቦችንም ከብር ማተሚያ ማሽን ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋል የተቻለ ቢሆንም፤ ያልተደረሰባቸው በርካታ ሐሰተኛ ገንዘብ አዘዋዋሪዎች አሉ›› ሲልም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ለአዲስ ማለዳ ተናግሯል።
በገበያ አዳራሾች እና በቁም እንስሳት ግብይት በርካታ ሐሰተኛ ገንዘብ በየቀኑ እየተያዘ መሆኑን በመጠቆም፤ ዜጎች ግብይታቸውን በጥንቃቄ መከወን እንዳለባቸው ተመላክቷል።
በተያያዘ ዜና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በመዲናዋ በአዲስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው መርካቶ በረካ ምግብ ቤት አካባቢ ከ79 ሺሕ ብር በላይ ሐሰተኛ ባለ ኹለት መቶ ብር ኖት የያዘን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ማስታወቁ ይታወሳል። ግለሰቡ ከተያዘበት ቀንና ሰዓት ጀምሮ አስፈላጊውን ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ ተጠቅሷል።
ኮሚሽኑ ሐሰተኛ የገንዘብ ዝውውር በማኅበረሰቡ ብሎም በአገር
በራያ አላማጣ የሚገኙ ስድስት ወረዳዎች በዋናነት በጀት እንዲለቀቅላቸው የሚጠይቅና በፊርማ የተደገፈ አቤቱታ በቀጥታ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ሊያስገቡ መሆኑ ተገልጿል።
ለዚህም ከኹለት ሳምንት በፊት ተደርጓል የተባለው ፊርማ የማሰባሰብ ዘመቻ በዋግኽምራ ዞን ሥር ባሉ ኮረም፣ ዛታ፣ ወፍላ ወረዳዎች እንዲሁም፤ በሰሜን ወሎ ዞን ሥር በሚገኙ አላማጣ፣ ራያ አላማጣ እና ራያ ባላ ወረዳዎች መከናወኑን የኮረም ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ገብረእግዚአብሔር ደረጀ ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።
ኃላፊው አክለውም የወሰንና የማንነት ጥያቄ ከአራት ዓመት በፊት ለፌዴሬሽን ምክር ቤቱ መግባቱን ጠቅሰው፤ “አሁን የሚላከው አቤቱታ ዋና ዓላማው የአካባቢው በጀት ወደ ትግራይ ሳይሆን ወደ አማራ ክልል እንዲገባ ለመጠየቅ ነው።” ብለዋል።
“ከሕዝቡ የተሰበሰበው በፊርማ የታገዘ አቤቱታ ተደራጅቶ ወደ ምክር ቤቱ መላክ ነው የቀረው” ያሉት ኃላፊው፤ “በኮረም ከተማ የተደረገው ጥናት 74 በመቶ የሚሆኑት ወደ አማራ ክልል መካለል የሚፈልጉ መሆናቸውን አመላክቷል።” ሲሉ ተናግረዋል።
11 በመቶ የሚሆኑት መሀል ላይ የሚወላውሉ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ቀሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እንካለል ያሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
አላማጣ ላይ ደግሞ 90 በመቶ የሚሆኑ ነዋሪዎች በአማራ ክልል ሥር መጠቃለልን የሚፈልጉ መሆናቸውንም አስረድተዋል። ኃላፊው አቤቱታው በቅርቡ ለምክር ቤቱ እንደሚገባም አመላክተዋል።
“2010 ገደማ ያስገባነውን የማንነት ጥያቄ ምክር ቤቱ እያየው እንደሆነ እናምናለን፣ በአሁኑ አቤቱታ የምንጠይቀው በጀቱ ወደ አማራ ክልል ገብቶ ወደ ወረዳዎች እንዲተላለፍ፤ የባንክ፣ የቴሌኮሙኒኬሽን እና የኤሌክትሪክ አገልግሎት የአሰራር ሥርዓቱም ወደ አማራ ክልል እንዲዞር ነው።” ሲሉ ተደምጠዋል።
ኃላፊው በጀት ባለመለቀቁ ለመንግሥት ሠራተኞች በቂ

አርበኛ ዘመነ ካሴ በአሁኑ ሰአት ከማረሚያ ቤት ወጥቷል::
ከመስከረም ወር ጀምሮ በባህር ዳር ሰባታሚት ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የቆየው አርበኛ ዘመነ ካሴ ዛሬ ከማረሚያ ቤት ወጥቷል::
በተለያዩ ጊዜያት ፍርድ ቤት በመቅረብ ክርክር ሲያደርግ የቆየው አርበኛ ዘመነ ካሴ የአማራ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 25/2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት አርበኛውን በነጻ ማሰናበቱ ይታወሳል::
ሁኖም የፍርድ ቤቱን ትዛዝ በመተላለፍ በመንግስት አመራሮች ከማረሚያ ቤት ድጋሚ ለሁለት ቀናት የቆየው አርበኛ ዘመነ ዛሬ የባህር ዳርና አካባቢው ወጣቶች በተገኙበት ከሰባታሚት ማረሚያ ቤት ወጥቷል::
የባህር ዳርና አካባቢው ወጣቶች ትላንትም አርበኛው ሲለቀቅ ለመቀበል ማረሚያ ቤት በር ላይ ሲጠባበቁ መዋላቸው የሚታወስ ሲሆን ዛሬ አርበኛው ሲወጣ በደስታና በጭፈራ ተቀብለው ይዘውት ወጥተዋል::
አርበኛ ዘመነ ለ9 ወራት ያክል በግፍ እስር ላይ ቆይቷል::

በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ ደማቅ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።
በተካሄደዉ ህዝባዊ ስላማዊ ሰልፉ ላይ የአማራ ነን አልን እንጂ አማራ እንሁን አላልነም፤ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ የፍትህ ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ነዉ።
✔️- የማይገባን አልፈን አንጠይቅ፤ የራሳችንም አሳልፈን አንሰጥም። በማንነታችን/በአማራነታችን በርስታችን አንደራደርም የራሳችንም አሳልፈን አንሰጥም!!
✔️- የፖለቲካ ሴራ የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ለድጋሜ እልቂት እንጂ ሰለምን አያመጣም የሚሻለዉ መራራዉን ሀቅ መቀበል ብቻ ነዉ።
✔️-ለእንግዶሽ እንጂ ለወንጀለኞች ቦታ የለነም፣ በወልቃይት ጠገዴ የተፈጸሙ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፍትህ ካሳ ንፈልጋለን፣
✔️-ተበዳይ እንጂ በዳይ ተጨፍጫፊ እንጂ ጨፍጫፊ፣ተወራሪ እንጂ ወራሪ ተፈናቃይ እንጂ አፈናቃይ አይደለነም ፤
✔️አማራዊ ማንነታችን የወሰን አስተዳደር ግዛት በህግ አግባብ ይከበር!
✔️ወልቃይት ጠገዴ የከለዉ ልጅ የአማራ ዘር ግንድ መነሻ ነዉ!!
(ዳንሻ ከተማ ኮሙኒኬሽን)
ይህ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብ በአደባባይ ያሰማው ድምፅ ነው!
“አማራ ነን አልን እንጅ አማራ እንሁን ብለን አልጠየቅንም” ብሏል ህዝብ በነቂስ ወጥቶ።
ወንጀለኞች ለህግ ይቀርባሉ እንጅ በተፈናቃይ መልክ እናስፍር አይባልም!
ከትግራይ ጋር ደንበራችን ተከዜ ነው። ነፃ ወጥተናል። በህግ ይረጋገጥ።
ብሏል የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብ።ለትህነግ የሚሰሩ የውጭ የሰብአዊ ድርጅቶችን የቅጥፈት ሪፖርት አውግዟል።
ከትግራይ ህዝብ ጋር መልካም ጎረቤት ሆነን ለመቀጠል ችግር የለብንም ብሏል ህዝብ በአደባባይ።
መሪዎቻችንና ህዝብ ላይ የሚደረግን ስም ማጥፋት ወደበለጠ ትግል ያመራናል ብሏል።

“እስክንድር የሚያደርገው ትግል፣ ህዝብ ላይ የመጣውን አደጋ የማንቃትና የማሳወቅ እንጂ፣ ጦር አንስቶ አልተዋጋም። እየተዋጋም አይደለም!
“የአማራ ህዝብ በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ከየአብይ አገዛዝ የተቃጣበትን የዘር ማጥፋት እንዲከላከል የማንቃት ስራ ነው እየሰራ ያለው። ጦር አንስቶ እንደነጃልመሮ መንገድ እየዘጋ ሰላማዊ ህዝብን እየገደለ ባንክ እየዘረፈ አይደለም። ይህንን መንግስት ተብዬው ጠንቅቆ ያውቃል።
“እስክንድር ለስልጣን ወይም ለጥቅም አይደለም የሚንከራተተው። በኑሮው ምንም የጎደለበት ሰው አይደለም። እስክንድር ጭቆናን ይፀየፋል። የአማራ ህዝብና የኢትዮጵያ ህዝብ ልጅህን አሳሳፈህ ለሰው በላው መንግስት እንዳትሰጥ ጥሪ አቀርባለሁ። ልጅህን ጠብቀው። የአብይ ሰራዊት እነ እስክንድር ይገኙበታል ወደተባለው ስፍራ እንዳይደርሱ የምትችሉትን ሁሉ ታደርጉ ዘንድ እጠይቃለሁ።
“እስክንድር አንድ ነገር ቢሆን ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ክብርህ የሚገፈፈው ያንተ እንጅ የእሱ አይደለም። እሱ የጀግና ሞት ነው የሚሞተው። በጀርባው እንጅ ፣ በሆዱ አይወድቅም።
የአማራ ክልል ባለስልጣናት ወንድምህን አሳልፈህ እየሰጠህ ነገ ከማን ጋር እንደምትኖር ቆም ብላችሁ ልታስቡ ይገባል።”
ሠርክዓለም ፋሲል
አሳዛኝ ዜና!
በሸዋ ደራ ከሳላይሽ ከተማ ወደ ጉንደ መስቀል ከተማ በመኪና ይጓዙ የነበሩ ነዋሪዎች እና በቅዳሴ ላይ የነበሩ ካህናት በአሸባሪ እና ወራሪ ኦነጋዊያን እገታ ተፈጽሞባቸዋል።
በሸዋ ደራ ከሳላይሽ ከተማ ወደ ጉንደ መስቀል ከተማ በመኪና ይጓዙ የነበሩ ነዋሪዎች ላይ በአሸባሪ እና ወራሪ ኦነጋዊያን ግንቦት 26/2015 ረፋድ ላይ እገታ ስለመፈጸሙ አማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ) ከስፍራው አረጋግጧል።
የአሚማ ምንጮች እንደገለጹት ሙቀጭታ ከጉንደ መስቀል በ7 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ አካባቢ ነው።
በተመሳሳይ በቅዳሴ ላይ የነበሩ የሙቀጭታ ጊዮርጊስ ካህናትም ታግተው ተወስደዋል።
በአካባቢው ያለው የመከላከያ ሰራዊት ታጋቾችን ለማስለቀቅ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አላደረገም በሚል በነዋሪዎች እየተወቀሰ ነው።
በአንድ መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሳፍረው የነበሩ ከ30 ያላነሱ ሰዎች ታግተዋል ነው የተባለው ።
የአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ የሚመለከታቸው አካላት በአስቸኳይ ከእገታ በማስለቀቅ ህይወትን የማዳን ስራ እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል።
ዘገባው የአሚማ ነው ።

መሐመድ ሰይድ ይባላሉ። ኑሯቸውን በደቡብ ወሎ ዞን፣ ሐይቅ ከተማ አካባቢ በሚገኝ ቱርክ ካምፕ ተብሎ በሚጠራው የተፈናቃዮች መጠለያ ካደረጉ ሰባት ወራት ተቆጥረዋል።
መሐመድ የአምስት ልጆች አባት ናቸው። ባለቤታቸውን ጨምሮ ሰባቱ የቤተሰብ አባላት የተጠለሉት እዚሁ ካምፕ ውስጥ ነው።
በጊዜያዊ መጠለያው ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደሚገኙ የገለጹት አቶ መሐመድ፣ የሚደረግላቸው ድጋፍ ከተቋረጠ ሁለት ወራት መቆጠሩን ይናገራሉ።
“ምንም የሚላስ የሚቀመስ የለም። አሁንማ የምናደርገው ሲጠፋን ነፍሳችንን ለማቆየት ለመገልገያ የተሰጠንን ፍራሽ፣ ብረት ድስት እና ሌሎች እቃዎችን ሳይቀር እየሸጥን ነው” ይላሉ።
አስቸኳይ ድጋፍ የማይደረግላቸው ከሆነም በርካታ ሕጻናት እና እናቶች ሕይወታቸውን ሊያጡ ይችላሉ ብለው አቶ መሐመድ ይሰጋሉ።
ቀደም ብሎ በቂ ባይሆንም የዱቄት እና የስንዴ እርዳታ ይሰጣቸው እንደነበር የሚናገሩት እኚህ አባት፣ “አሁን ግን ድጋፍ የሚባል ጭራሽኑ የለም” ይላሉ።

እርሳቸው እንደሚሉት የተፈናቀቃዮቹ መጠለያው ከከተሞች የራቀ በመሆኑም ከአካባቢው ነዋሪዎች እርዳታ ለመጠየቅም ሆነ የተገኘውን የቀን ሥራ ለመስራት የማይቻል ሆኖባቸዋል።
ልጆች እንጀራ ለመለመን የአንድ ሰዓት የእግር መንገድ ለመጓዝ ተገደዋል።
“ሁሉም በረሃብ እየተሰቃየ ነው። ከሰሞኑ በረሃብ ምክንያት እናትዬዋ የምታጠባው አጥታ የአንዲት ሕጻን ሕይወት አልፏል” ብለዋል።
ሌላኛዋ እዚያው መጠለያ ውስጥ የሚገኙት ተፈናቃይ ወ/ሮ መሬማም ልጆቻቸውን ይዘው ነው ቤት ንብረት ያፈሩበትን አካባቢ ጥለው የወጡት።
ከዚያ ሕይወታቸውን ለማትረፍ ቢወጡም አሁንም የገጠማቸው ችግር ፈታኝ ነው ይላሉ።
“የምግብ ችግር አለብን ። እንጮኻለን…እንጮኻለን…ምግብ ግን የሚሰጠን የለም” በማለትም የሚደርስላቸው አካል እንዳላገኙ ተናግረዋል።
እኚህ እናት እንደሚሉት በጊዜያዊ መጠለያው ውስጥ በቆዩባቸው ሰባት ወራት
በጎጃም አንዳንድ አካባቢዎች የሥራ ማቆም አድማ እየተደረገ መሆኑ ተሰማ
(አዲስ ማለዳ) በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረኤሊያስ ገዳም ሰሞኑን በተሰማው ግጭት ምክንያት የሥራ ማቆም አድማ እያደረጉ መሆናቸውን በስፍራው የሚገኙ የአዲስ ማለዳ ምንጮች ገልጸዋል።
በምዕራብ ጎጃም ጅጋ ወረዳ እንዲሁም በምሥራቅ ጎጃም ደብረማርቆስ፣ ፍኖተ ሰላምና ቡሬ ከተማዎች የሥራ ማቆም አድማ እያደረጉ ናቸው ተብሏል።
በደብረ ኤሊያስ ገዳም ዙሪያ በተፈጠረው ግጭት በውል ያልታወቀ ብዛት ያለው የንፁሐን ሕይወት ጠፍቷል የሚሉት ነዋሪዎቹ፤ “ድርጊቱን ለማውገዝ የታሰበ አድማ ነው።” ሲሉ አመላክተዋል።
በምዕራብ ጎጃም ዞን ጅጋ፣ ደንበጫ፣ ፍኖተ ሰላም፣ ቡሬ እንዲሁም፤ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስን ጨምሮ ደብረኤሊያሰ ወረዳ በዙሪያው በሚገኙ ከተሞች የገበያ አዳራሾችና ሱቆች ተዘግተዋል ነው የተባለው።
አድማ እየተደረገ ባለባቸው ቦታዎች የባንክ አገልግሎት ክፍት ሆነው እንደሚታዩ የአዲስ ማለዳ ምንጮች የገለጹ ሲሆን፤ ደንበጫ አዲስ ዓለም ቀበሌ መንገድ መዘጋቱንም አክለዋል።
ሰሞኑን በደብረኤሊያስ ወረዳ በሚገኙ ገዳማት ዙሪያ ሽፍታ አለ በሚል የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ተኩስ መክፈቱ ይታወቃል። በተከፈተው ተኩስም በርካታ የአካባቢው ማኅበረሰቦች ከቀያቸው እንደተፈናቀሉ ተመላክቷል።
ከግንቦታ 18/2015 ጀምሮ በደብረኤሊያስ ወረዳ በሚገኙ ገዳማት ዙሪያ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የበርካታ ዜጎች ሕይወት መጥፋቱን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
በውጥረቱም በደብረኤሊያስ ገዳም ውስጥ የሚያገለግሉ እና በዙሪያው የሚገኙ የሥላሴ አንድነት ገዳም እና ተክለሃይማኖት ገዳም አገልጋዮችና ተገልጋዮች አካባቢውን ለቀው መሰደዳቸው የተነገረ ሲሆን፤ እስከአሁን ወደ ገዳሙ አለመመለሳቸው ተገልጿል።
በዐማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ደጎልማ ቀበሌ በሚገኘው፣ በደብረ ኤልያስ ብሔረ ብፁዓን መልክአ ሥላሴ አንድነት ገዳም ውስጥ እና አካባቢው በተፈጠረ ግጭት፣ ከሲቪሎችም ኾነ ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት መካከል፣ በመቶዎች የተቆጠሩ ሰዎች መጎዳታቸውን፣ ነዋሪዎች እና የሆስፒታል ምንጮች፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
የደብረ ኤልያስ ወረዳ የሰላም እና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት፣ ስለ ግጭቱ ባወጣው መግለጫ፣ ገዳሙ የታጣቂዎች መሸሸጊያ በመኾኑ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ በገዳሙ ውስጥ ልዩ ዘመቻ ማድረጉንና በገዳሙ ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልጿል።
ለጸበል በገዳሙ ውስጥ እንደነበርና “ውጊያ” ሲል በጠራው ግጭት በደረሰበት የጥይት ምት እግሩን መቆረጡን፣ በደንበጫ ከተማ በሕክምና እየተረዳ የሚገኝ አንድ ታካሚ ነግሮናል።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የደብረ ኤልያስ ሆስፒታል ሐኪም፣ ካለፈው ሳምንት ኀሙስ ጀምሮ፣ ከ200 የማያንሱ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ቆስለው ወደ ሆስፒታሉ መግባታቸውንና ከእነርሱም ውስጥ 10 ያህሉ ሕይወታቸው ማለፉን ገልጸውልናል።
በጉዳዩ ላይ፣ የአትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ፣ ትላንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ፣ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ፥ ጉዳዩን አጣርቶ በቅርብ ቀን ለምእመኑ ሙሉ መረጃ ለመስጠት እየሠራ እንደሚገኝ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።
በዐማራ ክልል በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ በደጎልማ ቀበሌ በሚገኘው፣ የደብረ ኤልያስ ብሔረ ብፁዓን መልክአ ሥላሴ አንድነት ገዳም ውስጥ፣ ከፍተኛ ግጭት መከሠቱ የተሰማው፣ ባለፈው ሳምንት ኀሙስ፣ ግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም. ነበር።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁን፣ የደብረ ኤልያስ የመጀመሪያ ሆስፒታል ሐኪም፣ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ ካለፈው ኀሙስ ጀምሮ እስከ
ዘመነ ካሴ ነፃ ነህ መባሉ ተሰማ
(አዲስ ማለዳ) መስከረም ወር 2015 በቁጥጥር ሥር የዋለው ዘመነ ካሴ፤ ዛሬ ግንቦት 25 /2015 በባህርዳር ከተማ እና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት “ነፃ ነህ” መባሉን የአዲስ ማለዳ ምንጮች ገልጸዋል።

ዘመነ ካሴ በመስከረም ወር በቁጥጥር ሥር ውሎ መስከረም 23/ 2015 በባህርዳር እና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርቦ የ7 ቀናት ቀጠሮ ተሰጥቶት እንደነበር የሚታወስ ነው።
ምርመራውን የያዘው የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የምርመራ ቡድን “በተሰጠኝ 10 ቀናት ውስጥ ምርመራዬን ማጠናቀቅ አልቻልኩም” በማለት ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል።
የዘመነ ካሴ ጠበቆችም ወንጀል የተባለውን ጉዳይ ለማጣራት በሚል ፖሊስ ላለፉት አራት ወራት ያጣራ በመሆኑ እና ፍርድ ቤቱ ባለፈው ችሎት ውሎ የፈቀደው 10 ቀናት በቂ መሆኑን እና ሌሎችን መከራከሪያዎች አቅርበዋል፡፡ ስለዚህም ”የጊዜ ቀጠሮ መስጠት አያስፈልግም“ በማለት ተከራክረው ዘመነ ካሴ በዋስ እንዲለቀቅ ለፍርድ ቤቱ ጠይቀዋል።
የምርመራ ቡድኑ ያቀረበው ምክንያት በቂ አይደለም ያለው ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ መርማሪ ቡድኑ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ የ7 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ በመስጠት ፖሊስ እስከ ጥቅምት 01/2015 ድረስ ምርመራውን እንዲያጠናቅቅ ትዕዛዝ ተሰጥቶት፤ ዘመነ ካሴም ወደ ባህርዳር ማረሚያ ቤት መመለሱን ከዚህ ቀደም አዲስ ማለዳ መዘገቧ ይታወሳል።
“በከባድ የሰው መግደል ወንጀል” ተከሶ የነበረው የዘመነ ካሴ ጠበቆች የክስ መቃወሚያ ማቅረባቸውን ተከትሎ፤ ዐቃቤ ሕግ መልስ ለመስጠት የክስ ችሎት ለማሰማት ጊዜ ይሰጠኝ ማለቱም አይዘነጋም።
ፍርድ ቤቱም ዐቃቤ ሕግ በጠየቀው መሠረት ለኅዳር 12/2015 ቀን ዘጠኝ
የኤርትራ ስደተኞች በአዲስ አበባ ከተማ ለእስርና እንግልት ተጋልጠዋል ተባለ
(አዲስ ማለዳ) በአዲስ አበባ የሚገኙ በተለይም ኤርትራዊያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስር መዳረጋቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።
ኢሰመኮ ለአዲስ ማለዳ በላከው መግለጫ፤ በቀረቡ አቤቱታዎች መሠረት ባደረገው ክትትል ስደተኞቹ “የማስረጃ ሰነድ የላችሁም” በሚል ምክንያት፤ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በመቶዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ጠቁሟል።
እንዲሁም ክስ ሳይመሠረትባቸው በእስር የቆዩ መኖራቸውን እና በተለያየ ጊዜ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ ከእስር የተለቀቁ መኖራቸውንም ኮሚሽኑ አመላክቷል።
ኢሰመኮ የእስሩ ሰለባ የሆኑ በርካታ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን በንፋስ ስልክ ላፍቶ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያዎች በመገኘት ክትትል ያደረገ ሲሆን፤ ግለሰቦቹ ከተያዙ በኋላ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ከ10 ቀናት በላይ በእስር ላይ መቆየታቸውን ነግረውኛል ብሏል።
በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉበት ምክንያትም “ስደተኛ መሆናችሁን የሚገልጽ የሰነድ ማስረጃ የላችሁም”፣ “ከካምፕ ለመውጣት ፈቃድ ሳይኖራችሁ ከተማ ውስጥ ተገኝታችኋል”፣ “የሥራ ፈቃድ ሳይኖራችሁ በሥራ ላይ ተሰማርታችኋል’’ በሚል መሆኑን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡
መንግሥት ዓለም አቀፍ እና በብሔራዊ ሕጎች ግዴታ የተጣለበት በመሆኑ በስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ላይ ያለ ሕግ አግባብ የሚደረግ እስር በነጻነት የመንቀሳቀስ መብታቸውን ከመገደቡ ባሻገር፤ ለስደተኞች የሚደረገውን ጥበቃ እና ከለላን ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት አደጋ ላይ እንደሚጥል ተመላክቷል፡፡
የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በመንግሥት የጸጥታ አካላት እና በስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት መካከል በተወሰነ መልኩ
ተኩስ መከፈት ሲጀምር አንድም የተቃውሞ ድምፅ አልነበረም። ሶላት ተሰግዶ ዱአ ማድረግ ሲጀምር የሪፑብሊካን ጋርዱ የጥይት እሩምታ በሰጋጆች ላይ ማውረድ የጀመረው።በርካቶች በጥይት ተመተዋል ።
፟የአንዋር መስጂድ የዛሬው ውሎ በቪዲዮ ( ይጫኑት )
ዛሬ በአዲስ አበባ ፤ ” አንዋር መስጂድ ” ከጁመአ ስግደት መጠናቀቅ በኃላ የፀጥታ ኃይሎች በተከፈቱት ተኩስ ጉዳት ስለመድረሱ በአካባቢው የሚገኙ ጠቁመዋል።

በአሁን ሰዓት የተጎዱ ሰዎች እርዳታ እንዲያገኙ ጥሪ አቅርበዋል።
በመስጂዱ በነበረው ሁኔታ የአደጋ ጊዜ አዛን መሰማቱ ተነግሯል።
ከዚሁ ጋር በተያየ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ፤ ” በታላቁ አንዋር መስጂድ የጁምዓ ሰላቱን ለመስገድ ከቤቱ የወጣን እና በመስጂድ ያለን ንፁሃን ህዝበ ሙስሊም ላይ ያለምንም ርህራሄ በጥይት የሀይል እርምጃ መውሰድ ኢ ሰብዓዊ ተግባር ነው ” ብለዋል።
” ባዶ እጁን ለሰላት በወጡ ንፁሀን ላይ እየተወሰደ ያለውን የኃይል እርምጃ የፀጥታ ኃይሎች ያቆሙ ዘንድ አሳስባለሁ ” ያሉቱ ኡስታዝ አቡበከር ” በመስጂዱ ተጠልለው የሚገኙ እና ያለህራሄ በጥይት ተመትተው በመስጂዱ ውስጥ እና ዙሪያውን ወድቀው የሚገኙት ወንድሞቻችን በአስቸኳይ ወደ ህክምና ቦታ ይወሰዱ ዘንድ አምቡላንስ ወደ ቦታው እንዲገባ መንገዱን ክፍት ልታደርጉ ይገባል ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ስለ ዛሬው የአንዋር መስጂድ ሁኔታ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እንዲሁም የአ/አ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሚሰጡት መረጃ/መግለጫ ካለ ተከታትለን እናሳውቃለን።
በተመሳሳይ በመንግስት / በከተማው አስተዳደር በኩል የሚሰጥ ማብራሪያ ካለ ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል።
ባለፈው ሳምንት በሸገር ከተማ እየተከናወነ ያለው የመስጂዶች ፈረሳ ተግባር
በአምስት ግለሰቦች ላይ አሰቃቂ ግድያ ሲፈጸም 12 ሰዎች ታግተው ተወስደዋል
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን፣ በጢዮ ወረዳ በጨፌ ሚሶማ ቀበሌ ገበሬ ማኀበር በዴራ አማኑኤል አጥቢያ ቤተክርስቲያን በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያ መፈጸሙን አዲስ ማለዳ ዘግባለች።
ግድያው እሁድ ግንቦት 20 ለ21/2015 አጥቢያ ከሌሊቱ 5 ሰዓት ጀምሮ መፈጸሙን እንደተፈፀመ ዘገባው የጠቀሰ ሲሆን ጥቃቱን ያደረሱት ራሳቸውን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በማለት የሚጠሩት፤ መንግሥት “ሸኔ” በማለት በአሸባሪነት የፈረጃቸው ታጣቂ ቡድኖች መሆናቸውንም ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
በታጣቂ ቡድኑ ግድያ ከተፈጸመባቸው ግለሰቦች መካከል የቤተክርስቲያኑ አገልጋይ አባቶች እና ጠበቂ ይገኙበታል።
በሌላ በኩል፤ ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ ታጣቂዎቹ 12 ሰዎችን አፍነው በመውሰድ ገንዘብ አምጡ ብለው በመደራደር ላይ ናቸው ያሉ ሲሆን፣ ይሄ ዘገባ እሰከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ግለሰቦቹ በታጣቂ ቡድኑ ቁጥጥር ሥር እንደሚገኙ ተጠቅሷል፡፡
በአካባቢው በተለይም በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ እና በብሔር አማራ በሆኑ ሰዎች ላይ በተደጋጋሚ ጥቃቶች ይከሰታሉ ያሉት ምንጮች፣ “የኦሮሚያ እና የብሔር ብሔረሰቦች ሲኖዶስ እንመሠርታለን” ያሉ አካላት ወደ ስፍራው ባቀኑበት ወቅትም ተመሳሳይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን አስታውሰዋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ
ወቅታዊ መልዕክት ለምዕመናን
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
የደብረ ኤልያስ ብሔረ ብፁዓን መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳምን በተመለከተ በበርካታ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችና የመገናኛ አውታሮች ልዩ ልዩ ዘገባዎች እየተላለፉ ይገኛሉ።
ይህን ተከትሎም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ገዳማት አስተዳደር መምሪያ ከሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ጋር በመገናኘት ተፈጸመ የተባለውን ችግር በተመለከተ በዝርዝር የማጣራት ሥራ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትም በማዕከል ደረጃ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ላይ ይገኛል።
ስለሆነም ዝርዝር ሁኔታው በሚገባ ተጣርቶ የተደረሰበት የማጣራት ውጤት እውነታውን በሚገባ በሚያሳይ መልኩ በቤተክርስቲያናችን ማዕከላዊ አስተዳደር የሚገለጽ ይሆናል።
በሌላ በኩል በአርሲ ሀገረ ስብከት በጢዮ ወረዳ በጨፌ ሚሶማ ቀበሌ ገበሬ ማኀበር በዴራ አማኑኤል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ግንቦት ፳ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ምሽት ላይ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ደረሰ ተብሎ በተለያዩ የመገናኛ አውታሮች የተገለጸውን ጥቃት በተመለከተ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የተሰማትን ጥልቅ ኃዘን እየገለጸች በሀገረ ስብከቱ በኩል ተጣርቶ በሚቀርቀው መረጃ መሰረት ጉዳዩን በሕግ አግባብ የምትከታተሐው መሆኑን ትገልጻለች።
ልዑል እግዚአብሔር የሟች ወገኖቻችንን ነፍስ በአብርሃም፣
በይስሐቅና በያዕቆብ ዘንድ እንዲያኖርልንም የቅድስት ቤተክርስቲያናችን የዘወትር ጸሎቷ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
ግንቦት ፳፬ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም
© የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
“ያልተሰራጨውን የአፈር ማዳበሪያ ፈጥኖ በማሰራጨት የአርሶ አደሩን ችግር እንፍታ። በየመጋዝኑ የአፈር ማዳበሪያ አስቀምጦ ህዝባዊ ቅሬታና ጭንቀት መፍጠር በምንም መለኪያ ትክክል አይሆንም” •~•~• ር/መስተ ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ሲል የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ልሳን ጽፏል።

የማዳበሪያ ግዥ የሚፈጸመው በፌደራል መንግሥት ነው ያሉት ዶክተር ኃይለ ማርያም የፍላጎት እቅዱ ግን ከላይ ወደ ታች ከቀበሌ ወረዳ፣ ከወረዳ ዞን እና ከዞን ክልል የተዘጋጀ ነው ይላሉ፡፡ ክልሉ 9 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል ለ2015/16 የምርት ዘመን ታቅዶ ለፌደራል መንግሥት ተልኳል፡፡ የፌደራል መንግሥት የክልሉን እቅድ ተቀብሎ 5 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል የማዳበሪያ ግዥ ፈጽሟል ነው ያሉት፡፡
ለአማራ ክልል የሚያስፈልገው የመዳበሪያ አይነት ዩፒኤስ እና ዩሪያ የተባሉ የማዳበሪያ ዓይነቶች ናቸው ያሉት የግብርና ቢሮ ኅላፊው ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ 2 ነጥብ 1 ሚሊየን ኩንታል ማዳበሪያ ተጓጉዞ ወደ ክልሉ ገብቷል ብለዋል፡፡
ካለፈው ዓመት የከረመ 299 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ እጃችን ላይ አለ የሚሉት ኅላፊው በጥቅሉ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ክልሉ ውስጥ አለ፡፡ ነገር ግን ይላሉ ዶክተር ኃይለ ማርያም እስከ አሁን ድረስ ለአርሶ አደሩ የተሰራጨው 41 በመቶ ብቻ ነው፤ ችግሩ ያለውም ከዚህ ላይ እንደኾነ ኅላፊው ያነሳሉ፡
ክልሉ ውስጥ ከከረመው እና በአዲስ ከገባው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 96 በመቶ የሚኾነው የአፈር ማዳበሪያ ከዩኔኖች ወደ መሠረታዊ የሕብረት ሥራ ማኀበራት ተጓጉዟል፡፡
“ያልተሰራጨውን የአፈር ማዳበሪያ ፈጥኖ በማሰራጨት የአርሶ አደሩን ችግር እንፍታ። በየመጋዝኑ የአፈር ማዳበሪያ አስቀምጦ

ፀጋ በላቸው ከእገታ ነጻ መውጣቷ ተሰማ
ከሰሞኑ እጅግ መነጋገሪያ የነበረችውና ለ10 ቀናት ያክል በሐዋሳ ከተማ ከንቲባ የግል ጠባቂ ኮንስታብል የኋላመብራት ወ/ማሪያም ታግታ የቆየችው ፀጋ በላቸው፤ ከአጋቿ ቁጥጥር ነጻ በመውጣት ወደ ሐዋሳ መመለሷን አዲስ ማለዳ ሰምታለች፡፡
በጉዳዩ ላይ በአሁኑ ሰዓት የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ እና የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሸን መግለጫ እየሰጡ ሲሆን፣ አዲስ ማለዳ በቦታው ካሉ ምንጯቿ ያገኘችው መረጃ እንደሚያመላክተው፤ ጸጋ ነጻ ብትወጣም እገታውን የፈጸመው የፖሊስ አባል አለመያዙ ታውቋል፡፡
ግንቦት 15/2015 የግል ተበዳይ ፀጋ በላቸው፤ ከሥራ ወጥታ ወደ ግል ጉዳይ በምታመራበት ወቅት በተለምዶው አሮጌው መነሃሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጠለፋው እንደተፈፀመባት በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የመነሐሪያ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለአዲስ ማለዳ መግለጹ ይታወሳል።
ጸጋ መታገቷ ከተሰማ በኋላ ፖሊስ ከፍተኛ ክትትል ሲዲርግ መቆየቱን የገለጸ ሲሆን፤ እሳካሁን ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የጠጠረጠሩ ስምንት ሰውች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተጠቁሟል፡፡
ምንጭ አዲስ ማለዳ
በራሱ ስሕተት እየተበጠበጠ ያለው ኢዜማ የስራ አስፈፃሚ አመራሩን ያባረረ ሲሆን ማስፈራሪያም ሰቷል።
በዐማራ ክልል፣ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት እና በሌሎች ግጭቶች ሳቢያ የደረሰውን ውድመት ተከትሎ፣ 12 ሚልዮን የሚጠጋ ሕዝብ፥ በከፋ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ፣ በክልሉ፣ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ፈንድ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
የጽ/ቤቱ ዋና ዲሬክተር ዶር. አባተ ጌታሁን፣ ዛሬ፣ ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ በነበራቸው ቆይታ፣ ከሁለተኛው ዙር የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በኋላ የተደረገውን ጥናት መነሻ በማድረግ፣ በቅርቡ በተደረገው የክለሳ ጥናት፣ ክልሉ፥ በጦርነቱ እና ከጦርነቱ ጋራ በተያያዙ ግጭቶች የወደሙ መሠረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባት እና ለማቋቋም፣ 522 ቢልዮን ብር እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል፡፡
ለመልሶ ግንባታ የተጠየቀው ገንዘብ፣ እጅግ ከፍተኛ በመኾኑ፣ መንግሥታዊም ኾኑ መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶች፣ የርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉ፣ የጽ/ቤቱ ዋና ዲሬክተር ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በኢትዮጵያ እንደሚያደርጉት የሚጠበቀው ጉብኝት፣ ላለፉት ሁለት ዓመታት፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈጠረውን የሐሳብ ልዩነት ለማጥበብ የሚደረግ ዲፕሎማሲ አካል መኾኑን፣ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።
የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም፣ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ፣ ስለ ጉብኝቱ አብራርተዋል፡፡
በኢትዮጵያ እና በጅቡቲ፣ ለአንድ ሳምንት ጉብኝት ያደርጋሉ የተባሉት ልዩ መልዕክተኛው፣ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት እና ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋራ እንደሚወያዩ ይጠበቃል፡፡
በሌላ ዜና፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል የተጀመረው የሰላም ውይይት እንደተቋረጠ መኾኑን፣ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ተናግረዋል፡፡ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ቃል አቀባይም እንዲሁ፣ “ከመንግሥት ጋራ የቀጠለም ኾነ የታቀደ ውይይት የለም፤” ብሏል፡፡ በሌላ በኩል፣ በሁለቱ አካላት መካከል ግጭቶች መቀጠላቸው ይታወቃል፡፡
በዩናይትድ ስቴትስ ቨርጂኒያ የሚገኙት የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ዓለም አቀፍ ቃል አቀባይ ኦዳ ተርቢም፣ ትላንት በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሠፈሩት ጽሑፍ፣ “እየተናፈሰ ካለው ወሬ በተፃራሪ፣ በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት እና በመንግሥት መካከል፣ የቀጠለም ኾነ የታቀደ ውይይት የለም፤” ብለዋል።
አቶ ኦዳ አክለውም፣ አሁን ላይ፣ ሁለተኛ ዙር ንግግር ባይዘጋጅም፣ ለሰላማዊ መፍትሔ ቁርጠኞች እንደኾኑና ወደፊት የሚደረግ ድርድር ወዲያውኑ ይፋ እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡
ችግሩ በውይይት እንዲፈታ፣ ከኅብረተሰቡ እና ከልዩ ልዩ ዓለም አቀፍ አካላት፣ ተደጋጋሚ ጥሪዎች እየቀረቡ ቢኾንም፣ ከመጀመሪያው ዙር ውይይት ወዲህ በቀጠሉት ግጭቶች ሳቢያ፣ ስለ ውይይቱ ቀጣይነት የሚጠቁሙ አዝማሚያዎች አልታዩም፡፡
በሌላ በኩል፣ በምዕራብ ኦሮሚያ በቀጠለው ግጭት ምክንያት፣ በአካባቢው
የኢትዮጵያ ሥርዓተ ትምህርት ችግር ፈቺ ያልሆነ፣ የሀገሪቱን ኑሮ እና ተጨባጭ ጉዳዮች የማይመለከት፣ ከውጪ የተገለበጠ መሆኑ በውጤትም ሆነ በጥራት ማሽቆልቆል እየታየበት መቀጠሉን የትምህርት ባለሙያዎች ተናገሩ። ባለሙያዎቹ የዚህ ጥሩ ማሳያ ያደረጉት በኢትዮጵያ አጠቃላይ ትምህርት ከሚሰጥባቸው 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በተሻለ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት በጣት የሚቆጠሩ ብቻ መሆናቸው ከሰሞኑ በትምህርት ሚኒስቴር መነገሩን ነው።
አስተማሪነት ከአመላመሉ ጀምሮ ዝቅተኛ ውጤት ያላቸው የሚገቡበት፤ እና ሙያው ለበረታ የኑሮ ጫና የተጋለጠ እየሆነ መምጣቱ የትምህርት ጥራት ለመጓደሉ ዋንኛ ችግር መሆኑን የገለፁት ባለሙያዎቹ የትምህርት ሥርዓት ለውጥ አለመኖሩንም እንደ ሌላ መሠረታዊ ችግር ይጠቅሳሉ።
ትምህርት ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ውስጥ ከጠቅላላ ትምህርት ሰጪ 47 ሺህ ገደማ ትምህርት ቤቶች ደረጃቸው የላቁት አራት ናቸው ማለቱ ተሰምቷል። ቀደም ብሎ ለዘንድሮው ዓመት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ለፈተና ከተቀመጡት 909 ሺህ ተማሪዎች ማለፊያ ያመጡት 30 ሺህ ያልሞሉ መሆናቸውን ሲገልጽ ድንጋጤ ፈጥሮ ነበር። የዚህ ችግር ሥረ መሠረቱ ምንድን ነው ብለን የጠየቅናቸው የትምህርት ባለሙያው ዶክተር ሰለሞን በላይ በዋናነት አስተማሪነት ላይ የተከሰተው ውድቀት ነው ይላሉ።
«መምህራን ካመላመላቸው ጀምር አሰለጣጠናቸው፣ እንደገና ደግሞ አመዳደባቸው እያሽቆለቆለ በመምጣቱ» መሆኑን ጠቅሰዋል። ዝቅተኛ ውጤት ያላቸው ሰዎች አስተማሪ እንዲሆኑ የሚያደርግ ምልመላ መኖሩ፣ መምህራን ዝቅተኛ ተከፋይ መሆናቸው፣ ወደ ሌሎች ሙያዎች ትኩረት ማድረግ እና አስተማሪ የመሆን ፍላጎት እያሽቆለቆለ መምጣት ግልጽ ምክንያት መሆናቸውን ገልፀዋል።ያነጋገርናቸው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪም ይህንኑ ምክንያት ይጋራሉ።
«አማራጭ ያጡ ሰዎች ናቸው መምህር እየሆኑ ያሉት» በማለት ያለውን ተጨባጭ
ሰሞኑን በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤሊያስ ወረዳ በተለያዩ ምክንቶች በተፈጠረ ግጭት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን እና ሌሎች መቁሰላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የህክምና ተቋማት አመለከቱ። በግጭቱ በአንድ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ የነበሩ ምዕመናን ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን በመንግሥት የፀጥታ አካላት ላይም የአካል ጉዳት መድረሱ ተነግሯል፡፡
እንደ ነዋሪዎቹ ካለፈው ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ ም ጀምሮ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤሊያስ ወረዳ ደገሎ ቀበሌ፣ ብሐረ ብፁዓን ሥላሴ መልከአ አንድነት ገዳም አካባቢ መነሻው በግልፅ ባልታወቀ ምክንያት በምዕመናን እና በፀጥታ ኃይሉ መካከል በተፈጠረ ግጭት በርካታዎቹ ምዕመናን በከባድ መሳሪያ በታገዘ ጥቃት ህይወታቸው ማለፉንና ሌሎቹ መበተናቸውን የዓይን እማኞች ተናግረዋል። ግጭቱ ለተከታታይ አምስት ቀናት ከተካሄደ በኋላ ትናንት እኩለ ቀን አካባቢ መቆሙን ተናግረዋል። በገዳሙ ከ600 በላይ ሰዎች ይኖሩ እንደነበረ የተናገሩት አስተያየት ሰጪው ከ95 ከመቶ በላይ ቆስለዋል፣ ተገድለዋል አሊያም ተበትነዋል ነው ያሉት፡፡
በነበረው ግጭት ከባድ የጦር መሣሪያዎች ጥቅም ላይ መዋላቸውን የሚናገሩት አስተያየት ሰጪው፣ ቤተክርስቲኑ ጉዳት እንደደረሰበትም አስረድተዋል። ሌላው የአካባቢ ነዋሪ የግጭቱ መነሻ የወረዳ አመራሩ እና የገዳሙ አባቶች በተከሰተ አለመግባባት ችግሩ እንደተፈጠረ ተናግረዋል። የተፈጠረውን አለመግባባት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ጥረት መደረጉን የሚናገሩት እኚሁ አስተያየት ሰጪ መግባባት አለመቻሉንም አመልክተዋል፡፡ አንድ የደብረ ኤሊያስ ሆስፒታል አስተያየት ሰጪ ሰሞኑን በነበረው ግጭት ከ200 በላይ የመንግሥት የፀጥታ አካላት ቆስለው በሆስፒታሉ መታከማቸውን ተናግረዋል፡፡ ከወራት በፊትም በዚሁ ገዳም አካባቢ በተፈጠረ ግጭት 10 ያህል ምዕመናን መገደላቸውን አንድ የሀገር ውስጥ

ደብረ ማርቆስ ሱቆቿን ዘግታ ትግሉን ተቀላቀለች
የደብረ ማርቆስ ህዝብ በደብረኤልያ የሚደረገው የሥላሳሴ ገዳም የከባድ መሳሪያ ድብደባ፣የመነኮሳት እና የፀበልተኞች ጭፍጨፈ ባስቸኳይ እንዲቆም ትግሉን ተቀላቅሏል።
ዕምነት የለሹ የዐብይ አህመድ ጨፍጫፊ የኦነግ ሠራዊት ከተቀደሰው የጎጃም ገደማት እና አካባቢዎች ባስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ህዝቡ በቁጣ እየጠየቀ ነው።የማይወጣ ከሆነ ግን ትግሉ አድማሱን አስፍቶ አቅጣጫውን ይቀይራል ብለዋል።
በተመሳሳይ በደጀን፣ቢቸና፣ሞጣ፣አማኑኤል፣ደንበጫ፣ፋኖተ ሠላም፣ቡሬ፣ደንግላ፣መራዊ እና ሌሎች የጎጃም አካባቢዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ህዘባዊ እምቢተኝነቱን ይቀላቀላሉ ተብሏል።
ማሳሰቢያ፡ ደብረማርቆስ አንድ አንድ የስርዓቱ አገልጋይ ሆቴሎች እና ተሽከርካሪዎች የህዝብን ጥሪ ባለመቀመበል የከፈታችሁ አላችሁ፤ባስቸኳይ እንድትዘጉ እንጠይቃለን።ካልሆነ ለሚደርስባችሁ ጉዳት ኃላፊነቱን እራሳችሁ ትወስዳላችሁ ሲል ህዝባዊ ኮሚቴው አስጠንቅቋል።
በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፣ በትግራይ ክልል ውስጥ፣ ከ3ሺሕ800 በላይ መምህራንና ተማሪዎች ሕይወት ማለፉን፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡ ተቋሙ፣ ጦርነቱ በክልሉ ስላደረሰው ጉዳት በአካሔደው የዳሰሳ ጥናት፣ በትምህርት ሥርዐቱም ላይ ከፍተኛ ውድመት መድረሱን አመልክቷል፡፡
የጉዳት መጠኑ፣ በቅርቡ በተጀመረው የመማር ማስተማር ሒደት ላይ ከፍተኛ እክል እንደፈጠረ በተቋሙ የተገለጸ ሲኾን፣ የክልሉ የትምህርት ቢሮ በበኩሉ፣ የሚመለከታቸው የፌዴራል አካላት እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ አለማድረጋቸውን በመጥቀስ ወቀሳ አሰምቷል፡፡
የተቋሙ ዋና እንባ ጠባቂ ዶ/ር እንዳለ ኃይሌ፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፥ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከማይቆጣጠራቸው 26 ወረዳዎች ውጪ ባሉት የክልሉ አካባቢዎች፣ እስከ ወርኀ ነሐሴ 2013 ዓ.ም. ድረስ ብቻ ያለውን የጦርነት ጉዳት ያካተተ ጥናት መደረጉን ገልጸዋል፡፡
በጦርነቱ፥ በሺሕዎች የሚቆጠሩ መምህራንና ተማሪዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ መረጋገጡን የጠቀሱት ዋና እንባ ጠባቂው፣ ውድመቱ፥ በመማር ማስተማር ሒደቱም ላይ፣ አሉታዊ ተጽእኖ መፍጠሩን አመልክተዋል፡፡
የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሓላፊ ዶር. ኪሮስ ጉዑሽ በበኩላቸው፣ በጥናቱ ከተጠቀሰው ከነሐሴ 2013 ዓ.ም. በኋላም፣ በክልሉ በተካሔደ ጦርነት፣ ብዙ ውድመት መድረሱን ተናግረዋል፡፡
የተቋሙ ጥናት እንደሚያሳየው፣ እስከ ነሐሴ 2013 ዓ.ም. ድረስ፣ 88 ከመቶ የሚኾኑት የመማሪያ ክፍሎች በሙሉ እና በከፊል ተጎድተዋል፤ 96 ከመቶ የሚኾኑት የተማሪዎች መቀመጫ ዴስኮች ወድመዋል፤ 95ነጥብ8 ከመቶ የመማሪያ ጥቁር ሰሌዳዎችም አልተገኙም፡፡
ይኸው የጉዳት መጠን፣ በቅርቡ በተጀመረው የመማር ማስተማር ሒደት ላይ እክል እንደፈጠረ፣ ዋና እንባ ጠባቂው ዶ/ር እንዳለ ኃይሌ ያስረዳሉ፡፡
በትግራይ ክልል የትምህርት ዘርፍ የደረሰው ውድመት፣ ግዙፍ እንደኾነ የሚናገሩት የቢሮ ሓላፊው
እስራኤል የኢትዮጵያውያን አይሁዶችን ችግር የሚፈታ ከፍተኛ ኮሚቴ ማቋቋሟ ተገለጸ
(አዲስ ማለዳ) እስራኤል ከኢትዮጵያ የሄዱ ቤተ እስራኤላውያንን ችግር የሚከታተል እና ምላሽ የሚያሰጥ በሚኒስትር ደረጃ የሚመራ ኮሚቴ ማቋቋሟ ተገለጸ፡፡
የኮሚቴውን መቋቋም ባሳለፍነው እሁድ በነበረው ሳምንታዊ የካቢኔ ስብሰባ ላይ ይፋ ያደረጉት የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔትንያሁ፤ ‹‹ከኢትዮጵያ የመጡ እህት ወንድሞቻችን ችግር እንዲፈታ የተቋቋመው ኮሚቴ ከሌሎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችም እግዛ ያገኛል፡፡›› ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
አክለውም፤ ‹‹ብዙ ችግሮች ሊኖሩ ይችላሉ፣ ሆኖም ኮሚቴው ኢትዮጵያውያን አይሁዶች ያሉባቸውን ችግሮች በሂደቱ እንዲፈቱ ይሠራል፡፡›› ነው ያሉት፡፡
በቅርቡ በእስራኤል የሚኖሩ ቤተእስራኤላውያን የአገሪቱ መንግሥት ኢትዮጵያ የቀሩ ቤተሰቦቻቸውን ለማምጣት በጀት እንዲመድብ እና ሌሎች የሚያነሷቸውንም ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጥ በአደባባይ የተቃውሞ ሰልፍ አሰምተዋል፡፡
በዚህ ወር ውስጥም ከኢትዮጵያ ወደ ተስፋይቱ ምድር ለመግባት ሲሞክሩ በመንገድ ላይ ሕይወታቸውን ላጡ በሺዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን፣ በእየሩሳሌም የመታሰቢያ ዝግጅት የተካሄደ ሲሆን፤ በርከት ያሉ የአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ዝግጅቱን ታድመዋል ተብሏል፡፡
ከ4 ሺሕ ያላነሱ ቤተ እስራኤላውያን ከ1970 እስከ 80ዎቹ ባሉት ዓመታት ከኢትዮጵያ ተነስተው ሱዳን ውስጥ ወደተዘጋጀው የመቀበያ ጣቢያ በእግር ለመግባት ሲሞክሩ በምግብ እጥረት እና በበሽታ መሞታቸውም ተጠቅሷል፡፡
90 ሺሕ ገደማ ቤተእስራኤላውያን በ1980 ወደ እስራኤል እንደገቡ እና በአሁኑ ወቅት ከአጠቃላይ አገሪቱ ሕዝብ 2 በመቶ የሚሆኑ 160 ሺሕ ገዳማ ቤተ እስራኤላውያን መኖራቸው ተመላክቷል፡፡
ሆኖም እስራኤል በሚኖሩ አትዮጵያውያን አይሁዶች የዘረኝነት ጥቃት እንደሚደርስባቸው እና ሌሎች ኢ-ፍትሐዊ የሆኑ አሰራሮች ሰለባ እንደሚሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ደብረ ኤሊያስ ገዳም በድሮን ሊደበደብ ነው ፤ ምስራቅ ጎጃም ደብረ ኤልያስ 118ቱን አጋድሙት!
ወደ ጎጃም የተላከው የኦህዴድ ጦርና የአማራ ህዝብ ምላሽ

በዛሬው ዕለት ለተከታታይ ሦስት ሰዓታት ያልተቋረጠ የከባድ መሳሪያ እና የቦንብ ድብደባ በደብረ ኤልያስ ስላሴ ገዳም ተፈፀመ!
ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ድብደባው አለመቆሙን የመረጃ መንጮቻችን አረጋግጠዋል።
በርካታ ፀብልተኞች እና መነኮሳት ተገድለዋል።
አሁንም የኦህዴድ/ኦነግ ሠራዊት በኦራል ተጭኖ በገፍ ወደ ገዳሙ እየገባ ነው ሲሉ የአካባቢው የመረጃ ምንጮች ገልፀዋል።
ገዳሙ ውስጥ ለሚደርሰው የንፁሃን ፀበልተኞች እልቂት ቀዳሚው ተጠያቂ የምስራቅ ጎጃም ዞን የብልፅግና አመራሮች እና የፀጥታ አካላት ናቸው ሲሉ አስረድተዋል።
ገዳሙ ባለፈው ሀሙስ ዕለት ከቀን 17/09/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ስድሰት ቀናት በኦህዴድ/ኦነግ ጦር መጠነ ሰፊ ድብደባ እና ጥፋት እየተፈፀመበት ነው።
ከተገደሉት 7 መነኮሳት ባሻገር ከፍተኛ ቁጥር ያለው ፀበልተኛ ተጎድቷል።
የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይዎቅ፤ ዛሬም አልቆመም።ህዝቡ ምን እንደሚጠብቅ አልታወቅም።

በሰሜን ኢትዮጵያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ ለመወያየት፤ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው
የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ባለፈው ጥቅምት ወር በተፈራረሙት የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ላይ ለመነጋገር፤ የአሜሪካ አፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር በድጋሚ ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው። ሐመር ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግስት እና ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር በአዲስ አበባ፤ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ደግሞ በመቐለ ከተማ በመጪዎቹ ቀናት እንደሚወያዩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል።
ማይክ ሐመር ከነገ ረቡዕ ግንቦት 23፤ 2015 ጀምሮ ለሰባት ቀናት በአፍሪካ ቀንድ የሚያደርጉት ቆይታ፤ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ጅቡቲንም ያካተተ መሆኑን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቃል አቃባይ ጽህፈት ቤት ገልጿል። አምባሳደር ሐመር ወደ ጀቡቲ የሚጓዙት ሀገሪቱ በምታስተናግደው የምስራቅ አፍሪካ የጸጥታ ፎረም ስብሰባ ላይ ለመገኘት መሆኑን የቃል አቃባይ ጽህፈት ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫው አመልክቷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
የቅንጦት ፕሮጀክቶች ጆሮውን የደፈኑት መንግስት

የህወሓት ሊቀ መንበር ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል በትግራይ ክልል ምርጫ ‘በአስቸኳይ’ እንዲካሄድ ጠየቁ።
በፕሪቶሪያው ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት መሠረት በትግራይ የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ክልሉን መምራት የሚችለው ከስድስት ወር እስከ አንድ ዓመት መሆኑን ዶ/ር ደብረጽዮን በህወሓት የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ግንቦት 21/ 2015 ዓ.ም በወጣው ጽሁፍ አስታውሰዋል።
“ራስን በራስ ማስተዳደርን መሠረት በማድረግ በአስቸኳይ ወደ ምርጫ መሄድ አለብን” ብለዋል የህወሓት ሊቀመንበር።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሥራውን አጠናቆ ቀሪውን ሥራ በሕዝብ ለሚመረጠው መስተዳደር ማስተላላፍም እንዳለበት መናገራቸውም በጽሁፉ ሰፍሯል።
“የነበረው አመራር ለሰላም ሲባል ፈርሷል” ያሉት ዶክተር ደብረ ጽዮን የትግራይ ሕዝብ በሚመረጣቸው አመራሮቹ ሊመራም እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
“ህወሓት ማስተዳደር የለበትም ቢባል እንኳን፣ የትግራይ ሕዝብ በሚመርጣቸው መሪዎቹ ሊተዳደር ይገባል” ሲሉም መናገራቸው ሰፍሯል።
የህወሓት ሊቀመንበር በሰጡት አስተያየት ላይ እስካሁን ከጊዜያዊው የክልሉ አስተዳደሩ የተሰጠ አስተያየት የለም።
በፌደራል መንግሥቱ እና በህወሓት መካከል ከወራት በፊት በፕሪቶሪያ በተደረሰው ስምምነት መሠረት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከሁለት ወራት በፊት መቋቋሙ ይታወሳል።
በተዋቀረው ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ የሚኖርን ውክልናን በተመለከተ 30 በመቶ ለህወሓት፣ 25 በመቶ ለትግራይ ሠራዊት፣ 15 በመቶ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ቀሪው ለምሁራን እና ለሲቪክ ማኅበራት እንደሚሰጥም ከዚህ ቀደም መገለጹ ይታወሳል።
በትግራይ ውስጥ የተካሄደውን ደም አፋሳሽ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ በሽብርተኛ ቡድንነት ተፈርጆ የነበረው ህወሓት፣ የሽብተኝነት ፍረጃው የተነሳለት ቢሆንም ከምርጫ ቦርድ ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባቱ ይታወቃል።
በአመጽ እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳትፏል

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በጋምቤላ ክልል መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች ላይ ከደቡብ ሱዳን ዘልቀው በገቡ ታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ ዘጠኝ ምዕመኖቿ እንደተገደሉ አስታወቀች።
ጥቃቱ የተፈጸመው ግንቦት 12/ 2015 ዓ.ም አመሻሽ አስራ አንድ ሰዓት ላይ ሲሆን፣ ከሟቾች ውስጥ የስድስት ዓመት ህጻን እና አንዲት የምታጠባ እናት እንደሚገኙበትም ቤተ ክርስቲያኗ ትናንት ግንቦት 21/ 2015 ዓ.ም ባወጣችው መግለጫ አስታውቃለች።
ይህ ጥቃት የደረሰው በምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ አገልግሎት ክልል ውስጥ በሚገኘው ማታራ በሚባል ቀበሌ ነው።
ጥቃቱን ያደረሱት ከደቡብ ሱዳን ዘልቀው የገቡ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች መሆናቸውን የገለጸችው ቤተ ክርስቲያኗ፣ ከሞቱት በተጨማሪ በርካቶች የመቁሰል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በሲኖዶሱ የሴቶች አገልግሎት ተዘጋጀ በተባለው ጉባኤ ከ2 ሺህ 700 በላይ የሚሆኑ ሴቶች፣ እናቶች እና ልጆቻቸው ተሳታፊ ነበሩ።
ተሳታፊዎቹ የቀኑን መርሃ ግብር አጠናቀው ለእራት በተቀመጡበት ወቅት ጊዜ ጥቃቱ መፈጸሙን ከቤተ ክርስቲያኗ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
ታጣቂዎቹ ህጻናቱን በኃይል አፍነው ሊወስዱ ሲሞክሩ እናቶች በመከላከላቸው ታጣቂዎች ተኩስ ከፍተዋል ብላለች ቤተ ክርስቲያኗ ባወጣችው መግለጫ።
ከሞቱት ውስጥ የስድስት ዓመት ህጻን የሆነችው ንያካካ ዊዩአል ኒኜት እና አንዲት የምታጠባ እናትም እንደሚገኙበትም መግለጫው ጠቅሷል።
በዚህ ጥቃት የቆሰሉ በርካታ እናቶች በጋምቤላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በህክምና እየተረዱ ናቸው ተብሏል።
ከእነዚህም ውስጥ ሁለቱ በአሳሳቢ ደረጃዎች ላይ እንደሚገኙ መረጃዎችን ዋቢ እድርጎ መግለጫው ጠቅሷል።
የምዕራብ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ መሪዎች ጥቃቱ በተፈጸመበት ቀበሌ ተገኝተው ድጋፍ ቢያደርጉም ጉዳት ለደረሰባቸው ቤተሰቦች ተጨማሪ አፋጣኝ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተጠቅሷል።
ጥቃቱ የደረሰበት

የትግራይ ኃይሎች የጦር አካል ጉዳተኞች እንክብካቤ እየተደረገልን አይደለም በማለት በመቐለ ከተማ ሰልፍ አካሄዱ። የጦር ጉዳተኞቹ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ለሁለተኛ ግዜ ባካሄዱት በዚህ ሰልፍ “አመራሮች ረስተዉናል፣ ከእኛ ይልቅ በግል ህይወታቸው ተጠምደዋል፣ ቀጣይ የጉዳተኞች ህይወት ተረስቷል” ሲሉ ተደምጠዋል።
በዛሬው እለት በተካሄደው ሰልፍ ላይ የተሳተፉት በመቶዎች የሚቆጠሩ የጦር አካል ጉዳተኞች “በቂ የህክምና አገልግሎት እና በቂ ምግብ ማግኘት አልቻልንም” በማለት ተቃውሞ ያሰሙ ሲሆን ለጦር ጉዳተኞች ተብሎ የሚሰበሰበውን ሃብት አመራሮች እያባከኑት ነው በማለትም ቅሬታ አሰምተዋል።
ከመቐለ ከተማ ምስራቅ አቅጣጫ ላይ ከምትገኘው አይናለም የተሰኘች መንደር፣ ከ10 ኪሎሜትር በላይ በእግር ተጉዘው በመምጣት በከተማዋ ጎዳናዎች ላይ ጥያቄያቸውን ያሰሙት ሰልፈኞች፣ በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ፅሕፈት ቤት ገብተው ጥያቄያቸውን ያቀረቡ ሲሆን፣ ከግዜያዊ አስተዳደሩ ፅሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋ ጋር ተወያይተዋል።
ከውይይቱ በኃላ አቶ አማኑኤል በሰጡት መልስ፣ የጦር አካል ጉዳተኞቹን ጥያቄ ለመመለስ “ግዝያዊ አስተዳደሩ ከጦር ጉዳተኞች ጋር በመተባበር ይሰራል” ብለዋል። ለተጎጂዎቹ የህክምና አገልግሎት፣ በተለይ የአጥንት ሕክምና ለመስጠት፣ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም የገለፁት ኃላፊው፣ በቀጣይ የጦር ጉዳተኞችን ህይወት ለማስተካከል በክልሉ የአርበኞች ኮምሽን ተቋቁማል በማለትም ምላሽ ሰጥተዋል።
የጦር አካል ጉዳተኞቹ ተመሳሳይ ሰልፍ ባለፈው መጋቢት ወር ላይም አካሂደው ነበር።

የዳሽን ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ ባልደረባ ፀጋ በላቸው በሐዋሳ ከንቲባ ፀጋዬ ቱኬ የግል ጠባቂ ኮንስታብል የኋላመብራት ወ/ማሪያም ተጠልፋ ከተወሰደች ከሳምንት በላይ ሆኗታል።
የተጎጂዋ ቤተሰቦች ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፤ የግል ተበዳይ በቤተ ክርስቲያን ደንብ መሰረት የጋብቻ ትምህርት ከወደፊት የትዳር አጋሯ ጋር ተምረው በማጠናቀቅ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ ለመጋባት ቀን ቆርጠው የቤት ዕቃዎችን በማሟላት ላይ ነበሩ። ይሁን እንጂ ጥቃት አድርሷል በሚል በፖሊስ የሚፈለገው ተጠርጣሪ የግል ተበዳይን በተደጋጋሚ ይዝትባት እና ያስፈራራት እንደነበር አዲስ ማለዳ ከጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ሰዎች መስማት ችላለች።
የግል ተበዳይ ቤተሰቦች ፀጋ ያለችበትን ባለማወቃቸው ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ከመሆናቸውም ባለፈ የተበዳይ አባት በጠና ታመው ሕክምና እየተከታተሉ ስለሚገኙ ጉዳዩ ቤተሰቡ ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩንም ጨምረው ገልጸዋል።

ግንቦት 12/2015 የግል ተበዳይ ፀጋ በላቸው፤ ከሥራ ወጥታ ወደ ግል ጉዳይ በምታመራበት ወቅት በተለምዶው አሮጌው መነሃሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጠለፋው እንደተፈፀመባት በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የመነሐሪያ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለአዲስ ማለዳ አስታውቋል።
ፖሊስ አያይዞም፤ የተበዳይን ሁኔታ በተመለከተ በአሁኑ ሰዓት በውል የሚታወቅ ባይሆንም ፖሊሳዊ ሥራዎችን በከፍተኛ ርብርብ እና ቅንጅት ከሌሎች አካላት ጋር በመሆን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጿል።
አዲስ ማለዳ ከፖሊስ ያገኘችው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ ተጠርጣሪው ተበዳይን ጠልፎ ከተሰወረ በኋላ ወደ ትውልድ መንደሩ እና ከሐዋሳ በቅርብ ርቀት ወደምትገኘው ሐገረ ሰላም ወደምትባል መንደር ይዞ እንደሄደ ለማወቅ ተችሏል። ይህንንም ተከትሎ ፖሊስ መረጃው እንደደረሰው ወደ አካባቢው በስውር ቢያቀናም ተጠርጣሪ መረጃው ቀድሞ ደርሶት ስለነበር ስፍራ እንደቀየረ ታውቋል። ግለሰቡ

በብዙ ስራዎቹ የምናውቀው አርቲስት ተሾመ አየለ (ባላገሩ ) በአፋኙ ቡድኑ መታፈኑ ተሰማ
ተሾመ አየለ(ባላገሩ) ትናንት ረፋድ ላይ 4ኪሎ ስላሴ ቤተክርስቲያን አካባቢ ሠሌዳ በሌለው ተሽከርካሪ ለጥያቄ ትፈለጋለህ በሚል እንደተወሰደ ቤተሰቦቹ ተናግረዋል።እስካሁን ያለበትን እንደማያውቁም አስረድተዋል።ተሾመ የባላገሩ አስጎብኝ ድርጅት ባለቤት ነው።
ባለገሩ ተሾመ ከአሁን በፊት ፋኖን ታሰለጥናለህ ተብሎ ሲጠየቅ እንዲህ ብሎ ብሎ ነበር። “እኔ የፋኖ መሪ ሳልሆን ፋኖ ነኝ ” የሚል መልስ ሰጥቷቸዋል።
…………
የሀገራችንን ባህልና ትውፊት ለረጅም አመታት በማስተዋወቅ እና 365 ቀን ባህላዊ ልብስ በመልበስ የሚታወቀው የሀገራችን የባህል አምባሳደር ባላገሩ ተሾመ አማራነቱ ቢያሳስረው በሀገራችን ተከስቶ በነበረው የህልውና ዘመቻ ጦርነት ላይ አብሮ ሲሳተፍ በቆየበት ወቅት ያየውንና የተመለከተውን “የሸዋ ተጋድሎ” በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን የ1:30 ዘጋቢ ፊልም በእምዬ ምኒሊክና በእቴጌ ጣይቱ የልደት ቀንን አስመልክቶ ነሀሴ 12/2014 ዓ/ም በደብረ ብርሀን/ደብረ ኤባ ከተማ በአጤ ምኒሊክ አዳራሽ ማስመረቁ ይታወሳል።
የሸዋ ተጋድሎ የተሰኘው ዘጋቢ ፊልም ተሾመ ከሽዋ ግንባር እስከ አፋር ከአፋር እስከ አበርገሌ ግንባር ላይ ሆኖ ሲንቀሳቀስ የተመለከተውን ምልከታና እይታ የጻፈው ነበር።
እኔ የፋኖ መሪ አይደለሁም ፋኖ ግን ነኝ ። ፋኖ ደረቱን ለጥይት ሰጥቶ ህይወቱን ለመገበር ለከፈለው መስዋዕትነትና ለሀገር በዋለው ውለታ መሸለም ሲገባው መሳደዱ እና መታሰሩ እጂግ ያሳዝናል። “
ከደብረኤልያስ ሕዝብ የቀረበ ጥሪ
አንገት ለአንገት ከፋሽቱ አገዛዝ ጋር እየተናናቀ ያለው የደብረኤልያስ እና አካባቢው ሕዝብ እንዲሁም ሕዝባዊ ኃይሉ ከደጀን እስከ ባህርዳር ያሉ መንገዶች እንዲዘጉ እና በቅርብ የሚገኘው የአማራ ሕዝባዊ ኃይል የተቃጠብንን ጥቃት በመመከቱ በኩል እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
በማንነቱ እና በሐይማኖቱ ጥቃት የተከፈተበት የደብረኤልያስ እና አካባቢው ሕዝብ፤ ሴት፣ ወንድ ሳይል ከህጻን እስከ አዋቂ ራሱን የመከላከል ክተት አውጆ ሊያጠፋው ከመጣው የፋሽስት አገዛዝ ጋር አንገት ለአንገት መተናነቁን ከቦታው በደረሰን መረጃ መሠረት ማረጋገጥ ችለናል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የደብረ ዔልያስ መነኮሳት በኦሮሞ ብልፅግና ሰራዊት ተጨፍጭፈዋል።
በአሁኑ ሰዓትም የገዳሙ መነኮሳት በኦሮሞ ብልፅግና ሰራዊት፣ በጎጃም አመራሮች ተላላኪነትና መንገድ መሪነት እየተጨፈጨፉ ነው። ገዳሙንም ወደ ፍርስራሽነት እየተቀየረ ይገኛል።
ለታሪክ ይቀመጥ ሼር በማድረግ የአለም ህዝብ ይወቀው ሲሉ የአካባቢው ሰዎች መልዕክት አስተልፈዋል።
አቶ ክርስቲያን ታደለ ለአቶ ታዬ ደንደአ መልዕክት ላኩ!
አቶ ክርስቲያን ታደለ እንዲህ ሲሉ ሃሳባቸውን ይጀምራሉ። ክቡር ሚኒስትር ዴኤታ Taye Dendea Aredo፣
በቅድሚያ በፋሽስታዊ አገዛዙ ላይ ለሰነዘሩት ድፍረት ለተሞላበት፥ ከሞላ ጎደል መሬት ላይ ያሉ መራራ እውነቶችን ለያዘው፥ ትችት አድናቆት መስጠት እፈልጋለሁ።
እርስዎም በጽሑፍዎ ደጋግመው እንዳነሱት የጠባብ ጥቅመኞች ስብስብ በብሔር ምሽግ ተደብቆ በሕዝብ በተለይም በአማራ ሕዝብ ላይ በሚወስዳቸው ዘር ተኮር ጥቃቶች እና የዘር ፍጅት ቅስቀሳዎች የተነሳ፥ አንዳችን ያንዳችንን ቁስል በወጉ እንዳንገናዘዘብ፤ ለጋራ ነገ በአንድነት እንዳንቆም፤ በሰብአዊነት ላይ በሚፈፀሙ በደሎችና ግፎች ላይ የተባበረ ድምጽ እንዳናሰማ መሆናችን እሙን ነው።
ይባስ ብሎም ይህ ጠባብ የጥቅም ቡድን ፋሽዝምን መንግስታዊ መመሪያው በማድረግ መሰል ነውሮችን በመቃወም ትችት በሚያቀርቡ የመብት ታጋዮች ላይ የኃይል እመቃና ጅምላ እስር በመፈፀም፤ አስገድዶ ሥወራዎችንና በሕዝብ ላይ የፀጥታ ኃይሉን ወረራ በሚመስል መልኩ በማሰማራት ወገናችን የየእለት ኑሮውን በሰቀቀን እንዲያሳልፍ አድርጎታል።
የሚፈፀሙ መሰል ወንጀሎችን በብሔር ምሽግ ለመደበቅ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን አይተናል። ከአንዴም ሁለቴ ሕዝብን የወንጀል ተጋሪ ለማድረግ መንግስታዊ ሰልፎችን ታዝበናል። ክቡርነትዎ እንደርስዎ ሁሉ ሌሎች የብሔሩ ልኂቃንም በስማችን ወንጀል አትሰሩ ማለት ይኖርባቸዋል። ሕዝቡም ከወንድሞቻችን ጋር አታጣሉን፤ በስማችን የድሃ ጎጆ አታፍርሱ፤ ምስኪኖችን አታስለቅሱ፤ የንፁኃንን ደም አታፍስሱ ብሎ መጠየቅ ይኖርበታል። ፍትኅ ወንጀሉንና ወንጀለኞችን በስማቸው ከመጥራት ይጀምራልና፥ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታ፥ እንደጀመሩ «ሌቦች» ያሏቸውን ፋሽስቶችና በሕዝባችን ላይ የሚያደርሱትን ሰቆቃም በስሙ እንዲጠሩት እጠይቅዎታለሁ። በቀደመው ጊዜ ለሰላም፣ ለነፃነት፣ ለፍትኅና እኩልነት ብለው ዋጋ ከፍለዋልና፤ እርስዎን ጨምሮ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ኢዜማ አባላቱ ራሳቸውን ማግለላቸውን ተከትሎ ፓርቲው ያዘጋጀው የአምስት አመት የፖለቲካ ሂደትን የሚገመግም ሰነድ ላይ ውይይት አያደረገ ነው። ይሁንና ተጨማሪ 41 የፓርቲው የምርጫ ወረዳ አመራርና መደበኛ አባላት ድርጅቱን ለቀው መውጣታቸውን ለዋዜማ በላኩት መግለጫ ገልፀዋል።በኢዜማ ውስጥ ፓርቲው ከገዥው ብልፅግና ፓርቲ ጋር ባለው ግንኙነት ዙሪያ የሰነበተ አለመግባባት እንደነበረ ሲነገር ቆይቷል። ባለፉት ቀናትም የቀድሞ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በተለያየ ደረጃ ያሉ አባላት ከፓርቲው ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታውቀዋል። በዛሬው ዕለትም በምርጫ ወረዳ 2/14 ያሉ 41 ብሄራዊ የስራ አሰፈፃሚ አባላትና መደበኛ አባላት ራሳቸውን አግለዋል። የኢዜማ መሪዎች በጉዳዩ ላይ ለዋዜማ ምላሽ ሰጥተዋል።
የኢዜማ አመራር ያለፉትን ሁለት ቀናት በአምስት ዓመቱ የፖለቲካ ሂደት ላይ ሰነድ አዘጋጅቶ ውይይት ማድረግ የጀመረ ሲሆን ውይይቱ ወደታችኛው የድርጅቱ መዋቅር እንደሚቀጥልም አስታውቋል። የውይይት ሰነዱን ይዘት ፓርቲው ይፋ አላደረገም። ይሁንና አሁንም በፓርቲው ውስጥ ያሉ አባላት በኢዜማና በመንግስት መካከል ስላለው ግንኙነት አንድ ወጥ አቋም እንደሌላቸው፣ ግን ደግሞ ልዩነቶቻቸውን ለመፍታት ትግል ላይ መሆናቸውን ለዋዜማ ተናግረዋል።
“ኢዜማ የህልውና አደጋ ተጋርጦበታል” ያሉን አንድ የፓርቲው አባል ችግሩን በቀጣይ ቀናት መፍታት ካልተቻለ ፓርቲው የሚፈለገውን የህዝብ ድጋፍ አግኝቶ መቀጠል የማይችልበት ደረጃ ላይ እየደረሰ ነው ብለውናል።
ከፓርቲው ራሳቸውን ያገለሉ ሌላ የቀድሞ ከፍተኛ አመራር በበኩላቸው “አሁን ሰነድ ተዘጋጅቶ እየተደረገ ያለው ውይይት ኢዜማ ከብልፅግና ጋር ያለውን ትብብር ቅቡልነት እንዲያገኝ ለማሳመን በተወሰኑ የፓርቲው አመራሮች ፍላጎት የተሰናዳ ሰነድ ነው” ብለው እንደሚያምኑ ያስረዳሉ።
ሰኞ ዕለት ከፓርቲው

የአማራ ገበሬዎች ተቃውሞ በባህር ዳር
በዛሬው ዕለት በባህር ዳር ከተማ ከተለያዩ ቦታዎች የተሰባሰቡ የአማራ አርሶአደሮች በአፈር ማዳበሪያ እጦት ምክንያት ማረስ አልቻልንም ፣እህል የምንዘራበት ወቅት አለፈብን እንዲሁም የአማራን ገበሬ ሆን ተብሎ እንዲዳከም እየተሰራ ነው በማለት ተቃውሟቸውን አሰምተዋል ።
የአማራ ወጣቶች ማህበር በአፈር ማዳበሪያ ላይ የሚሰራው ደባና ሸፍጥ አንዱ የአማራን ህዝብ የማዳከም ፣የማደኸየት እና ለማስገበር የሚደረግ መዋቅራዊ የሆነ እንቅስቃሴ ፤የስርዓቱ መገለጫ እንደሆነ ያምናል ።
የአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ ማህበራዊ እረፍት የሚያገኘው ስርዓታዊ እና መዋቅራዊ ለውጥ ሲመጣ ብቻ ነው ።

በምዕራብ ሸዋ ዞን ከ1 ሚሊየን አንድ ጊዜ ሊከሰት የሚችለው የበቅሎ መውለድ አጋጣሚ መከሰቱ ተነገረ
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ባኮ ቲቤ ወረዳ ከወትሮ በተለየ መልኩ አንዲት በቅሎ ከአምስት ቀናት በፊት መውለዷን የወረዳው ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ገልጿል።
የበቅሎዋ ባለቤት ብርሃኑ ተምትሜ፤ በ2014 የገዟትን በቅሎ ለጭነት አገልግሎት ሲጠቀሙባት መቆየታቸውን ተናግረዋል።
ነገር ግን የበቅሎዋ ሆድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን እንዳስተዋሉ የገለጹት ብርሃኑ፤ ግንቦት 15/2015 ከቀኑ 5፡30 ላይ ውርንጭላ መውለዷን ተናግረዋል።
የበቅሎዋ መውለድ ክስተት እንዳስገረማቸውም በመግለጽ፤ ውርንጭላው አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡
በባኮ ቲቤ ወረዳ ግብርና ጽ/ ቤት የእንስሳት ሐኪም የሆኑት ዶክተር ለማ አያላ፤ በቅሎ ሲወልድ አይተው እንደማያውቁ እና ክስተቱ እንግዳ እንደሆነባቸው ገልጸዋል፡፡
ባለሙያው በቅሎ አትወልድም የሚለው እሳቤ በሳይንስ እና በባህላዊ መንገድ የታመነበት ጉዳይ መሆኑን በመግለጽ፤ ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ ከአንድ ሚሊየን በቅሎዎች አንዳቸው ሊወልዱ እንደሚችሉ ጥናቶች ያሳያሉ ብለዋል።
‹‹የደረሰብንን ስቃይ ቃላት አይገልጹትም፤ በኤሌክትሪክ ቶርች ተደርገናል፣ ጥፍራችን ተነቅሏል፤ በቀዝቃዛ ውሃ እየተነከርን ተገርፈናል፤ አሁንም በአፍና በአፍንጫው ደም የሚፈሰሰው ታሳሪ አለ›› በፌደራል ፖሊስ የሚገኙ እስረኞች
የዚህ አፋኝ ቡድን ሰለባ የሆኑትን አማራዎች ከአዲስ አበባ ፌድራል ፖሊስ ኮሚሽን በሚገኘው እስር ቤት የኢትዮ 251 ሚዲያ ዘጋቢ በቦታው ተገኝቶ የደረሰባቸውን ሁሉ ጠይቆ ያጠናቀረው ዘገባ ነው።
ለኢትዮ 251 ሚዲያ አስተያየታቸውን የሰጡት ግፉኣን የሚከተለውን ብለውናል፡፡ እኛም ጥሬ ሃቆቹን እና ዘጋቢው የተመለከተውን ብቻ ወደ እናንተ አቅርበናል።
‹‹የደረሰብንን ስቃይ ቃላት አይገልጹትም፡፡ አሁን ስንታሰር ህዝቡ ሊጨነቅ ይችላል፡፡ ለእኛ ግን በማሰቃያ ቦታው የደረሰብንን ስንመለከት ይህ ፖሊስ ጣቢያ የቅንጦት ቤታችን ነው›› የአንደኛው አስተያየት፤
ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ደግሞ፤ ‹‹በደረሰብኝ ድብደባ መተንፈስ ተቸግሬያለሁ›› ሲል ተናግሯል፡፡ ዘጋቢያችን በአካል ተገኝቶም የኢንጂነሩን ስቃይ ተመልክቷል፡፡
በአይን እንደተመለከትነው አንዷ እህታችን እስካሁን በአፍና በአፍንጫዋ ደም እየፈሰሳት ነው።
በግርፋት ብዛት ራሳቸውን የሳቱና ምግብ መመገብ የማይችሉ አሉ፡፡ በኤሌክትሪክ ቶርች የተደረገ አለ፤ በቀዝቃዛ ውሃ እየተነከረ የተገረፈም አለ፣ ጥፍሩ የተነቀለም አለ፡፡ ይህን ሁሉ ግርፋት መቋቋም ያልቻሉ ወንድሞቻችን ምግብ መመገብም ሆነ ራሳቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው እላያቸው የሚጸዳዱም አሉ፡፡ “የእኛ ስቃይ የማይታያቸው ገራፊዎቻችን ሆን ብለው ህክምና ከልክለውናል”፡፡
በተጨማሪም፤ ‹‹28ታችን ወደ ፖሊስ ጣቢያ መጣን እንጂ አሁንም በማሰቃያ ቤቱ መከራቸውን እያዩ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ወንድሞቻችን አሉ፡፡ እነዚህ ወንድሞቻችን ከአጣዬ፣ ሽዋሮቢት፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ጎጃም፣ ጎንደር እና አዲስ አበባ በግፍ ታፍነው የተወሰዱ ናቸው፡፡
<<የሀይማኖት አባቶች፣ የሰብአዊ
በገላን የኦሮሚያ ልዩ ሃይል ካምፕ በሚገኝ ስውር ማሰቃያ ቦታና በፌደራል ወንጀል ምርመራ ከፍተኛ ቶርቸር እየተፈጸመ መሆኑን የሚያሳይ ጽሁፍ ከእስረኞቹ ደርሶናል። ጥፍር መንቀልን ጨምሮ እጅግ አሰቃቂ ድብደባና ማሰቃየት የደረሰባቸውን በተመለከተ :: አንከር ሚዲያ!
<<የቱለማን መሬት ሸጦ ሴተኛ አዳሪ በሚሊዮን የገዛ ቡድን ዛሬ በህግ ማስከበር ስም የደሃ ቤት እና ቤተ እምነት ማፍረስ ተገቢ አይደለም!!>> አቶ ታየ ደንደዓ
መከላከያ የመላው ህዝብ ሆኖ ሳለ በኦሮሚያ ብቻ ሰልፍ የሚደረገው ለምንድነው !? (ታዬ ደንደአ አሬዶ)
አቶ ታዬ ደንደዓ በአዲስ አበባ ዙሪያ ሸገር ከተማ የሚፈርሱ ቤቶች እና ቤተ እምነቶችን ተከትሎ የፃፉትን ፋስት መረጃ እንደሚከተለው ወደ አማርኛ ተርጉሞታል እንድታነቡት እንጋብዛለን!!

ቱለማዎች መፈናቀላቸው እውነት ነው። ቱለማን አፈናቅሎ ለማኝ እና ስደተኛ ያደረጋቸው ማነው? ሌላ ሃይል ቢኖርም አብዛኛውን ቱለማን ከቤታቸው ያፈናቀለው ሌቦቹ ናቸው። ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ ከተሞች የሆነውን ሀገር ያውቃል። በገበሬ ስም የአዲስ አበባን መሬት የዘረፈው ማነው? የአዲስ አበባን መሬት ቸብችቦ ሴተኛ አዳሪ በጨረታ የገዛው በሚሊየን ቲፕ የሰጠው ማነው? የሌባው ቡድን ነው።
ቀን ቀን የቱለማን ደሃ የሚያስለቅሰው፣ ማታ ውስኪ ቤት የሚጨፈረው፣ ይቅር የማይባል ወንጀል እየፈፀሙ ዛሬ ደግሞ የቱለማ ጠበቃ መሆን። በቱለማነት ተከልለው የራስን ወንጀል መደበቅ አይቻልም። ለቱለማ ብለን መስጂድ አፈረስን ማለት ምን ማለት ነው! የመስጂድ ማፍረስን ከቱለማ ጋር ማገናኘት ለግጭት መቀስቀሻ ነው።
ህግን ማክበር ትክክል ነው። የቤተ እምነት ግንባታ ጨምሮ ሁሉም ነገር በሕግና በሥርዓት መከናወን አለበት። ህገ ወጥ ግንባታን መከልከል ጉልበትና ሃብት ሳይባክን ነው መሆን ያለበት። የራስን መሬት ሸጦ፣ ቤት ሲሰራ ዝም ብሎ መብራትና ውሃ አስገብቶ፣ ከፍተኛ የሀገር ሀብት ከፈሰሰበት በኋላ በህግ ማስከበር ስም የደሃ ቤት እና ቤተ እምነት
በተከዜ አዋሳኝ የሚገኙ የጠለምት ነዋሪዎች በህወሓት ታጣቂዎች ትንኮሳ እየተፈፀመብን ነው አሉ
👉 ነዋሪዎቹ በሚደርስባቸው ትንኮሳ ከአካባቢያቸው እየተፈናቀሉ መሆኑን ገልጸዋል
(አዲስ ማለዳ) በተከዜ አዋሳኝ የሚገኙ የጠለምት አካባቢ ነዋሪዎች የህወሓት ታጣቂዎች ልምምድ እያደረጉ እና ትንኮሳ እየፈጸሙብን ነው ሲሉ ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።
በዚህም ትጥቅ ያልፈቱ የህወሓት ኃይሎች በጠለምት ሦስት ቀበሌዎችን በመቆጣጠራቸው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ተናግረዋል፡፡
በምስራቅ ጠለምት ወረዳ ሥር የሚገኙት ሜዳ፣ ምድረ አምሾ፣ እና ደገብራይ የሚባሉ ሦስት ቀበሌዎች በህወሓት ኃይሎች ቁጥጥር ሥር በመሆናቸው ሕብረተሰቡ ለከፋ ችግር ተጋልጧል ነው የተባለው።
በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት ትጥቅ ያልፈቱት የህወሓት ታጣቂዎች መድፍን ጨምሮ ሞርታር፣ ዙ-23 እና ሌሎች ከባድ መሳሪዎችን ይዘው እንደሚንቀሳቀሱም ተገልጿል፡፡
ታጣቂዎቹ በአካባቢው የጦር ልምምድ ሲያደርጉ ይስተዋላሉ የተባለ ሲሆን፤ ነዋሪዎቹ በሚደርስባቸው ትንኮሳ እየተፈናቀሉ መሆናቸው ተመላክቷል።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የሕወሓት ታጣቂ ኃይሎች መሳሪያ ማስረከብ የሚኖርባቸው ቢሆንም፤ ሙሉ በሙሉ አለማስረከባቸው እና በተለያዩ የድንበር አካባቢዎች ትንኮሳ እንደሚፈጽሙ ይገለጻል፡፡
በሌላ በኩል፤ በትናንትናው ዕለት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የሕወሓት ታጣቂ ኃይሎች መቀለ አቅራቢያ በሚገኘው ላጪ ተብሎ በሚጠራው ቦታ፣ የቡድን መሳሪያዎችን ለመከላከያ ሠራዊት ተወካዮች ማስረከባቸው መዘገቡ ይታወሳል፡፡
ርክክቡ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም ስምምነቱ ክትትል፣ ቁጥጥር እና ማረጋገጥ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት መከናወኑ የተገለጸ ሲሆን፤ በርክክቡም የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች በእጃቸው የነበረ የቡድን መሳሪያ ማለትም ዲሽቃ፣ አርፒጂ፣ መትረየስና ሞርታር የተባሉ የጦር መሳርያዎችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ማስረከባቸው ተነግሯል።
ኦህዴድ መራሹ ስርዓት በአማራ ክልል እያካሄደ ያለውን መንግስታዊ ሽብር አፈና እና የማገት ተግባር የሚያበረታታ መከላከያ ሰራዊትን እንደግፋለሁ የሚል የድጋፍ ሰልፍ በአዲስ አበባ ጠራ !
በደረሰን መረጃ መሰረት መንግስት በህግ ማስከበር ሰበብ በአማራ ክልል እያካሄደ ያለውን የሽብር ተግባር ፋኖን የማሳደድ : የጦር መኮንኖች እና ለአማራው ድምፅ የሆኑትን ጋዜጠኞችና ማህበራዊ አንቂዎች እንዲያስር እና የማሳደዱን ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥልበት የፊታችን ነገ እሁድ በአዲስ አበባ ከተማ በተላላኪዎቹ በኩል የድጋፍ ሰልፍ እንዲካሄድ ትእዛዝ ማስተላለፉን ነዋሪዎቹ ገልፀዋል::
በአዳነች አቤቤ በኩል የተጠራው የአብይ አህመድን የሽብር ተግባር የሚደግፍ ሰልፍ ብዙ የአማራ ተወላጆችን አስቆጡታል::
ዛሬ ቅዳሜ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን የአገዛዙ ስርዓት አስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት መስጂድ ፈረሰ፣ ቤተክርስቲያን ፈረሰ፣ ፋኖን አትንኩ የሚል ሃሳብ ፈፅሞ ከነዋሪው እንዳይነገር ቀጭን ትዕዛዝ አስተላልፏል።
አሻራ ባጣራው መረጃ መሠረት ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ከሆነ የትናንቱ የህዝበ ሞስሊሙ ተቃውሞ የአገዛዙን ስርዓት ክፉኛ ስላስደነገጠው በነገው ሰልፍ የማይወጣ የአዲስ አበባ ነዋሪ 5,000 ብር ቅጣ እና እስር እንደሚጠብቃቸው ተናግረዋል።
አሻራ ሚዲያ ፣
የፕሮፌሰሩ አዲስ ሰነድ ፡ ከመፈረካከስ ወደ መክሰም የተሸጋገረው ኢዜማ

ይህ እየተካሄደ ያለው የትዊትር ዘመቻ፤ በመጪዎቹ ሳምንታትና ወራት በሰላማዊና ህዝባዊ እምቢተንኝነት የትግል ማዕቀፍ ውስጥ ያሉ ተጨማሪ የትግል ዘርፎችን ይዞ የሚመጣ ይሆናል። እነዚህ የትግል ዘርፎች ተጨባጭ ህዝባዊ እምቢተኝነትንና ከዚህ ፍጹም ጨቋኝና ኢፍትሃዊ ከሆነው በኢትዮጵያ ካለው አገዛዝ ጋር ያለመተባበር ጥሪን ይጨምራል።
ይህ ዘመቻ የእንቅስቃሴያችን ጅማሮ ብቻ እንጂ ዋናው የትግሉ መዳረሻ ጉልላቶች ይሚከተሉት ናቸው፤
o የአብይ አህመድ መንግስት በአግባቡ ተጠያቂ ማድረግ፤
o በኢትዮጵያ መረን ያጣውን የጭቆናና የሰብዐዊ መብት ጥሰቶችን ማስቆም፤
o በ10ሸዎች በሚቆጠሩ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ኢሰብአዊ የሆነ የቤት ፈረሳና ማፈናቀልን ምግታት፤
o በአማራዎች፣ በጋዜጠኞችና በማህበራዊ አንቂዎች ላይ በስፋት እየተካሄደ የሚገኘውን ማንነትን ያማከለ እገታና ህገወጥ አፈሳና እስርን ማስቆም፤
ዘመቻው ክዚህም በተጨማሪ በአገዛዙ በከፍተኛ ባለስልጣኖችና ሸሪኮቻቸው ጥምረት እየተፈጸሙ ያሉ ግዙፍ፣ ሀገርን የሚያቆረቁዙ ዘረፋዎችንና የሙስና ወንጀሎች በገለልተኛ አካል እንዲጣሩ የማድረግ ዓላማ አንግቧል። በወለጋ በበርካታ ዙር በአማራዎች ላይ የተካሄደውን ማንነት ተኮር ጭፍጨፋና ማባሪያ ያጣውን ማፈናቀል በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ማድረግ፣ በአዲስ አበባና አካባቢው የተንሰራፋውን እና ስርአታዊ እየሆነ የመጣውን የማግለል፣ አድሎና የዜጎች መጎሳቆል ባግባቡ ማጣራትና መቋጫ መስጠት በዘመቻው እንደግብ ከተቀመጡት መሃከል ይገኙበታል።
ከዚህም ባለፈ በተለየ መልኩ ላለፉት 30 ዓመታት በጠላትነት ተፈርጆ፣ በሀገሩ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ይህ ነው የሚባል ተሳትፎና ሚና እንዳይኖረው በማግለል፣ በግላጭ የጥላቻና የጎሳ ፖለቲካ ሀ ሁ ማለማመጃ ተደርጎ ተዘርዝሮ ለማያልቅ ግፍ እና መከራ ሲዳረግ ለከረመው ሰፊው የአማራ ህዝብ፣ ከአምስት አመት ወዲህ ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያዊ
ባንኮች ከፍ ያለ ካሽ ገንዘብ ለማውጣት ለሚጠይቋቸው ደንበኞቻቸው አገልገሎቱን እየሰጡ አይደለም
የኢትዮጵያ ባንኮች ለምን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ገጠማቸው?
ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ባንኮች ለደንበኞቻቸው በተለይ መጠኑ ከፍ ያለ ካሽ ገንዘብ ለማውጣት ለሚጠይቋቸው ደንበኞቻቸው አገልገሎቱን እየሰጡ አይደለም።
አል ዐይን አማርኛ በአዲስ አበባ ተዘዋውሮ ቅኝት ባደረገባቸው የተለያዩ ባንክ ቅርንጫፎች በባንክ ባለሙያዎች እና ደንበኞች መካከል ንትርኮች መኖራቸውን ታዝበናል።
ከባንክ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች እና አገልገሎት ፈላጊዎች ጋር ባደረግነው ቆይታም ከጥቂት ባንኮች በስተቀር አብዛኞቹ ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት እንደገጠማቸው እና ብድር መስጠት በጊዜያዊነት ማቆማቸውን ነግረውናል።
አገልገሎት ፈልገው ወደ ባንኮች ያመሩ ተገልጋዮችም ከባንኮች በተለይም በርከት ያለ ጥሬ ገንዘብ ለማውጣት ሲጠይቁ ባንኮች እንደሚያጉሏሏቸው፣ ብድር ለመውሰድ ሲጠይቁም ብድር ለጊዜው መቆሙን እንደሚነግሯቸው ጠቅሰውልናል።
አል ዐይን አማርኛ አብዛኞቹ ባንኮች ለምን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ሊገጥማቸው ቻለ ብድርስ ለምን ሊከለክሉ ቻሉ ሲል የኢኮኖሚ ባለሙያዎችን አነጋግሯል።
አቶ ዋሲሁን ኢኮኖሚስት የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ናቸው፤ እሳቸው እንዳሉት ባንኮች ላጋጠማቸው የጥሬ ገንዘብ እጥረት እና ብድር ክልከላ አራት ቢሆኔዎችን ጠቅሰዋል።
እንደ አቶ ዋሲሁን አስተያየት ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት ሊያጋጥማቸው የሚችለው ወቅቱ የበጀት መዝጊያ እና አመታዊ ግብር የሚከፈልበት ወቅት በመሆኑ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ከግል ባንኮች ወደ መንግስታዊ ባንኮች ስለሚዞሩ ሊሆን ይችላል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ንረት በገበያው ውስጥ ባለው ከፍተኛ የጥሬ ገንዘብ መሰራጨት ምክንያት መሆኑን ብሔራዊ ባንክ በመረዳቱ እና ይህንን ለማስተካከል የተወሰደ እርምጃ ሊሆን ይችላል በሚል በባንኮች ላጋጠመው
በቦረና ዞን ለተከታታይ ሦስት ዓመታት በቆየው ድርቅ፣ ከ3ነጥብ3 ሚሊዮን በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸውን፣ የዞኑ የግብርና እና የእንስሳት ሀብት ጽሕፈት ቤት ገለጸ።
የዞኑ ጽሕፈት ቤት ምክትል ሓላፊ ዶክተር ቃሲም ግዩ፣ ለአምስት ተከታታይ የዝናም ወቅቶች በጸናው ድርቅ፣ 46 በመቶ የዞኑ የእንስሳት ሀብት መጥፋቱን፣ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል።
አሁን የድርቁ ወቅት ያለፈ ቢኾንም፣ ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ የወደፊት ኑሯቸው እንደሚያሳስባቸው ስጋታቸውን አመልክተዋል፡፡
ወይዘሮ ኤለማ ጀልዴሳ፣ የቦረና ዞን ዱብሉቅ ወረዳ፣ ላፍቶ ቀበሌ ማኅበር ነዋሪ ናት። የአምስት ልጆች እናት እንደኾነች የምትናገረው ወይዘሮ ኤለማ፣ ድርቁ ባዶ እጃቸውን ካስቀራቸው መካከል አንዷ ናት።
“ባለቤቴ እኔን ጨምሮ ሦስት ሚስቶች አሉት፡፡ ድርቁ ሳያራቁተን በፊት፣ ከበረት የምናሠማራቸው 50 የሚደርሱ ከብቶች ነበሩን፡፡ አሁን አንዲት ጥጃ እንኳን አልቀረችልንም፡፡ የእኛ ቤተሰብ፣ ከአማቻችንን ቤት ጋራ አራት ቤቶች አሉት፡፡ ከእኔ ብቻ አምስት ልጆች ተወልደዋል፡፡ የጣውንቶቼ ጨምሮ በአጠቃላይ ወደ ዐሥር ይኾናሉ። ከቤተሰባችን ሰው ቢታመም ወይም የኾነ እክል ቢገጥመው፣ የምንሰጠው ነገር የለንም፡፡ ይህ ፈጣሪ ያመጣው ነገር ነው።”
አቶ ገርብች ዳለቻም፣ በላፍቶ ቀበሌ ነዋሪ ሲኾኑ ፤ “ቀደም ሲል በባንክ የነበረኝን ተቀማጭ፣ ለከብቶቹ መኖ በመግዛት ነው የጨረስኹት፡፡ ኾኖም አሁን፣ ከ180 ከብቶች የቀሩኝ ሁለት ብቻ ናቸው፡፡ ከነበሩኝ ከ200 በላይ ፍየሎች፣ አሁን የተረፉት አምስት ብቻ ናቸው፡፡” ይላሉ።
አክለውም፤ “በጎቹ ደግሞ 150 ነበሩ፤ አሁን ያሉት ሰባቱ ብቻ ናቸው። ድርቁ ይህን ያህል ሀብት አውድሞብኛል፡፡ አብዛኞቹ ነዋሪዎችም፣ እንደ እኔ ያለ ጉዳት ነው የደረሰባቸው፡፡ ከእነርሱም፣ የቤት እንስሶቻቸው ያለቁባቸው ሰዎች
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶርያ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል በተደረገው የሰላም ስምምነት መሠረት፣ በትግራይ ክልል የሚገኙ ተዋጊዎች፣ 85 በመቶ የጦር መሣሪያቸውን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ማስረከባቸው ተገለጸ።
ዛሬ፣ በመቐለ ከተማ በተከናወነው ቀጣይ የርክክብ ሥነ ሥርዐት ላይ፣ የአፍሪካ ኅብረት ያቋቋመው፣ የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊነት ክትትል እና ቁጥጥር ቡድን በታዛቢነት ተገኝቷል።
በሰላም ስምምነቱ መሠረት፣ የትጥቅ ማስፈታቱን ተከትሎ የሚከናወነው፣ የተዋጊዎችን አደረጃጀት የማፍረስ ሒደት፣ በዛሬው ዕለት፣ በመቐለ ዙሪያ በምትገኘው ኵሓ መንደር፣ በታዛቢዎች ፊት በኦፊሴል መጀመሩ ተገልጿል፡፡

በፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 14 ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ አስታወቀ
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሚገኘው ፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ላይ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት፤ 11 የፋብሪካው ሰራተኞች እና ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደተገደሉ ማረጋገጡን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታወቀ። ፋብሪካው በተፈጸመበት በዚሁ ጥቃት እና ዘረፋ ምክንያት ስራ ማቋሙም ተገልጿል።
ከአዲስ አበባ በ350 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ላይ ጥቃቱ የተፈጸመው ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ግንቦት 12፤ 2015 መሆኑን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የህዝብ ግንኙነት እና ተሳትፎ ክፍል ኃላፊ አቶ ረታ ደመቀ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ፋብሪካው ባለፈው 2014 ዓ.ም እና በዚህ ዓመት ተመሳሳይ ጥቃቶችን ቢያስተናግድም፤ የአሁኑ ከዚህ ቀደም ከነበሩት “ከበድ ያለ” እንደሆነ ተነግሯል።
የፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ እና በስሩ ያለው የሸንኮራ አገዳ እርሻ፤ በአጠቃላይ በ67 ሺህ ሄክታር ይዞታ ላይ ያረፈ ነው። የቀደሙት ጥቃቶች ይበልጥኑ ኢላማ የሚያደርጉት የፋብሪካው እርሻ ላይ እንደነበር የሚናገሩት አቶ ረታ፤ ታጣቂዎቹ “የአገዳ እና የእርሻ ማሽነሪዎችን የማቃጠል” ድርጊት ይፈጽሙ እንደነበር ያስታውሳሉ። የአሁኑ ከዚህ ቀደም ከነበሩት የሚለየው፤ ታጣቂዎቹ ወደ ፋብሪካ ጭምር በመግባት ጥቃቶቹን በመፈጸማቸው እንደሆነ ያስረዳሉ።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11051/

የሸገር ከተማን መስጂድ ፈረሳ በመቃወም በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ
በአዲሱ የሸገር ከተማ አስተዳደር እየተፈጸመ የሚገኘውን መስጂድ የማፍረስ ተግባር በመቃወም ሙስሊሙ ማኀበረሰብ በአዲስ አበባ አንዋር መስጂድ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂዷል።
የሰልፉ ዋነኛ ዓላማም በአዲሱ የሸገር ከተማ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የመስጂድ ፈረሳዎች በአስቸኳይ እንዲቆም ማሳሰብ መሆኑ ታውቋል።
ይህንንም ተከትሎ የአዲስ አበባ ፖሊስ በአንዋር መስጂድ ላይ የተቃውሞ ሠልፍ እያደረገ ያለውን ህዝበ ሙስሊም እንዲበተን ማድረጉም ተነግሯል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጻፈው ደብዳቤ፤ በሸገር ከተማ እያፈረሱ ስላሉ መስጂዶች አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ መጠየቁ ይታወሳል።ት
የብልጽግና ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴዎች፤ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ መደበኛ ስብሰባዎቻቸውን ሊያካሄዱ ነው
የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴዎች፤ ከመጪው ሰኞ ግንቦት 21 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ገደማ የሚቆዩ ስብሰባዎችን ሊያካሄዱ ነው። በሁለቱ ኮሚቴዎች መደበኛ ስብሰባዎች፤ ወቅታዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ይነሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል።
ከመጪው ሰኞ እስከሚቀጥለው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት የሚቆዩት የብልጽግና ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴዎች መደበኛ ስብሰባዎች፤ የፓርቲው የስራ አፈጻጸም “በዋነኛነት የሚገመገምባቸው” እንደሆኑ የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አዳራሽ የሚደረጉት ስብሰባዎች በቅደም ተከተል የሚደረጉ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
በቅድሚያ የሚደረገው የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ ሲሆን፤ ሰኞ ግንቦት 21፤ 2015 ተጀምሮ በማግስቱ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህ ስብሰባ መጠናቀቅ አንድ ቀን በኋላ የሚጀመረው የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ እስከ ሚቀጥለው ሳምንት ማክሰኞ ግንቦት 29 ድረስ እንደሚቀጥል አቶ አዲሱ ተናግረዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11045/
የአባላቶቹ መልቀቅ ያስደነገጠው ኢዜማ የደበቀውን “ያለፉት አምስት ዓመታት የፖለቲካ ሁኔታዎች ግምገማ” ሰነድ ይፋ ሊያደርግ ነው።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ መጋቢት 02/2015 ዓ.ም. ባደረገው 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ የተጋረጠባትን የህልውና አደጋ በሥፋት ለማጥናት፣ በተጨማሪም እንደሀገር እየሄድንበት ያለውን የፖለቲካ አካሄድ እና በተደጋጋሚ እየተከሰቱ ያሉ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታን ቆም ብሎ በመገምገም ቀጣይ የትግል አቅጣጫዎቻችንን ማስመር እንዲቻል የጥናት ግብረ ኃይል እንዲቋቋም፣ ግኝቱንም በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ ውሳኔ ማሣለፉ ይታወሳል።
ግብረ ኃይሉ የሃገራችንን የአምስት ዓመት ጉዞ በስፋትና በጥልቀት በመፈተሽ እንደዚሁም ኢዜማ ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ ያለፈበትን አራት የትግል ዓመታት እንደሀገር አሁን ከደረስንበትና ከተደቀኑብን አደጋዎች አንፃር ሊሆኑ የሚችሉ ክስተቶችን በሰከነ መንፈስ ተንትኖ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን የሚያሣይ “ያለፉት አምስት ዓመታት የፖለቲካ ሁኔታዎች ግምገማ” ሰነድ አዘጋጅቶ ግንቦት 13/2015 ዓ.ም. በብሔራዊ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴው ጸድቋል።
ሰነዱ በተለያየ ደረጃ ካሉ አባላት ጋር ውይይት እንደሚደረግበት መገለፁ የሚታወስ ሲሆን ከነገ ግንቦት 19/2015 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ከፓርቲው የፓርላማ አባላት፣ የብሔራዊ ህግ ተርጓሚና አሥፈፃሚ ኮሚቴ፣ ኦዲት ኮሚቴ፣ በፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስር ከሚገኙ ቋሚ ኮሚቴ እና ሀገራዊ ምክክር ኮሚቴ አባላት ጋር በሰነዱ ላይ ውይይት ያደርጋል።
ይህ ውይይት በቀጣይ ሳምንታት ከዞን ምክርቤቶች እና ከምርጫ ክልሎች ከተውጣጡ አመራር እና አባላት ጋር የሚደረግ ይሆናል።

የዳያስፖራ አባላት የገንዘብ፣ ጉዞ እና መዋእለ ንዋይ እቀባ ዘመቻ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጀምረዋል!
ውጭ ሃገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሲቪል ማኅበራት «ግፈኛ አገዛዝ» ያሉት መንግሥት ላይ የገንዘብ ተጽእኖ ለማሳደር ዘመቻ ጀምረዋል። ማኅበራቱ ዘመቻቸው፦ ኢትዮጵያ ውስጥ በገዢው ብልጽግና መንግሥት ይፈጸማል ያሉትን ኢ-ፍትኃዊነትና ዘረኝነት በመቃወም፤ ትኩረቱ ፍትሕ ላይ ያተኮረ መሆኑንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራው ማኅበረሰብም ወደ ሀገር ቤት የሚልከውን ገንዘብ በባንኮች እንዳይጠቀም ጥሪ አስተላልፈዋል። ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ የሚያደረጓቸውን ጎዞዎች እንዲያቋርጡ እና መዋእለ ንዋይ ፍሰት (ኢንቨስትመንት) ለማደርግ የሚደረጉ ሂደቶች በአጠቃላይም መቋረጥ አለበት ብለዋል።
ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚንሥትር አህመድ ሽዴ ባቀረቡት ዘገባ፦ የፌድራል መንግሥት የበጀት ጉድለት እንደገጠመው ይፋ አድርገዋል።የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሀገሪቱ ኤኮኖሚ ላይ 28 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ኪሳራ ማድረሱን ዐሳውቀዋል ።
ሚንስትሩ ጉድለት ያሉትን ለመሸፈንም ከአገር ውስጥ 194.6 ቢሊዮን ብር በብድር መንግስት መውሰዱን ገልጸዋል። «ብድሩም የተገኘው ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀጥታ ብድር፣ ከትሬዠሪ ቦንድ እንዲሁም ከትሬዠሪ ቢል ነው።ካሉት የፋይናንስ ተቋማት 194.6 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለቱን ለመሸፈን ሬይዝ ተደርጓል»ም ብለዋል ። መንግስት ከፍተኛ የገንዘብ ችግር እንደገጠመው፤ የኑሮ ውድነቱም በከፍተኛ ደረጃ ማኅበረሰቡን እንዳማረረው የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ዋዜማ – በፓርቲ ንብረትነት ለሚታወቁት ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እና ለዋልታ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት ባልተለመደ መልኩ የፌደራሉ መንግስት በርካታ መጠን ያለው ገንዘብ ድጎማ እያደረገላቸው መሆኑን ዋዜማ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል።
የሚድያ ተቋማቱ ገንዘቡን ስራቸውን ለማስፋፊያ እንዲሁም ለሰራኞቻቸው ደሞዝ ጭማሪ እና ማሻሻያዎችን ለመተግበር ይጠሙበታል ተብሏል።
ሁለቱ ሚድያዎች በኢህአዴግ ጊዜ ከአራቱ እህት ድርጅቶች የቦርድ አባላት የሚሾሙላቸው ፣ እንዲሁም አመታዊ ትርፋቸውን በኢህአዴግ እህት ድርጅቶች ከሚተዳደሩ ኩባንያዎች ጋር የሚከፋፈሉት ነው። ገንዘብ ሲያስፈልጋቸውም ከባንኮች ይበደሩ ይሆናል እንጂ በቀጥታ በፌደራሉ መንግስት በኩል አይሰጣቸውም ነበር።
ዋዜማ ከምንጮቿ እንደሰማችው ዋልታ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት እስከ ሁለት ቢሊየን ብር ከመንግስት እንደሚያገኝ እንደሚያገኝ ታሳቢ አድርጎ ዕቅድ አውጥቷል። የገንዘቡን መጠን ፣ እንዲሁም ገንዘቡ የሚሰጠው በብድር ይሁን በልግስና ከተቋሙ አመራሮች ለማረጋገጥ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
ይሁንና የሚዲያ ተቋሙ አመራሮች ገንዘቡን ለማግኘት ከገንዘብ ሚኒስቴር ሰዎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ሲያደርጉ እንደነበር ተረድተናል።
ዋልታ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የቅርብ ሰው እንደሆኑ በሚነገርላቸው እና “ሰውዬው” የሚለውን መጽሀፍ በጻፉት መሀመድ ሀሰን በዋና ስራ አስፈፃሚነት እየመሩት ይገኛሉ።
ተቋሙን ሰፋፊ የፕሮግራም ማሻሻያዎችን ለማድረግ ፣ የህንፃና እና ስቱዲዮ ግንባታዎችን ለማከናወን እየተዘጋጀ መሆኑን ሰምተናል። እንዲሁም ለሰራተኞች የደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅም ማስተካከያ ባለፉት ቀናት አድርጓል።
ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በበኩሉ ድጎማን ለመቀበል ሰሞኑን ከገንዘብ ሚኒስቴር ምላሽ እየተጠባበቀ ይገኛል።
እነዚህ መገናኛ ብዙሀን ከመንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ ድጎማ ያገኙት በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት በሰላም ሚኒስቴር

ፋኖን ትጥቅ አስፈታለሁ በሚል ወደ ሸዋሮቢት ከተማ የገባው የብልፅግና ቡድን መከላከያ ሰራዊት፡ በህዝቡ ላይ ድብደባ እና ዘረፋ እየፈፀመ ነው ተባለ!
መሣሪያ ለመግፈፍ በሚል በከተማዋ ቤት ለቤት እየዞረ ፍተሻ እያካሄደ የሚገኘው የአብይ አህመድ መከላከያ ሰራዊት፡ ጥሬ ገንዘብን ጨምሮ የጣት ቀለበት እና የአንገት ሀብል እንዲሁም የጆሮ ጌጦችን እየዘረፈ መሆኑን ነው የአማራ ድምፅ ያነጋገራቸው የከተማዋ ኗሪዎች የገለፁት።
በተጨማሪም፡ መሣሪያ ያለውን ሰው ካልጠቆማችሁን እንዲሁም ፋኖ ያለበትን ቦታ ካላሳያችሁን በሚል በተፈፅመባቸው ድብደባ አረጋውያንን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተነግሯል።
በዚህም እየተፈፅመበት ያለውን ግፍና በደል ለመመከት ነፍጥ አንስቶ ወደ በርሃ የሚወርደው የከተማዋ ኗሪ ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ መምጣቱ ተገልጿል።
የተከፈተበትን ጥቃት ለመመከት ነፍጥ አንስቶ ፋኖዎችን የሚቀላቀለው ሰው ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ ያስደነገጠው የዞኑ ብልፅግና ፅ/ቤት፡ ተጨማሪ የገዢው መንግስት ወታደር ወደ ከተማዋ እንዲገባ እያስደረገ መሆኑንም የአማራ ድምፅ ካሰባሰበው መረጃ ለማረጋገጥ ችሏል።
ይሄው የብልፅግና ቡድን ወታደር፡ ከሸዋሮቢት ከተማ በተጨማሪ በሰሜን ወሎ ዞን ላሊበላ፣ ብልባላ፣ ጋሼና፣ እስታይሽ፣ ሀሙሲት፣ ቀበሮ ሜዳ፣ ሳንቃ፣ ጎብየ፣ ሮቢት፣ ቆቦ፣ ዞብል፣ ጋቲራ፣ ተኩለሽ እና በሌሎች አከባቢዎች ላይ ልጆቻችሁ ፋኖ ናቸው ያሉበትን ጠቁሙ በሚል አራስ እናቶችን ጨምሮ አረጋውያን እና ታዳጊዎች ላይ ከባድ ድብደባ እየፈፀመ መሆኑን የአማራ ድምፅ ከሰሞኑ መዘገቡ አይዘነጋም።
ዘገባው የአማራ ድምፅ ነው።
” … መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉት 10 የከባድ ውንብድና ፍርደኛ ታራሚዎች ናቸው ” – ቃሊቲ ማረሚያ ቤት
ከቃሊቲ ማረሚያ መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ነበሩ የተባሉ ታራሚዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰምቷል።
ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉር የከባድ ውንብድና ወንጀል ፍርደኛ ታራሚዎች መሆናቸው ተነግሯል።
ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ጥበቃና የደኅንነት አስተባባሪ ኢንስፔክተር ድሪባ ሰንበታ ለኤፍ ቢ ሲ የሰጡት ቃል ፦
” ትናንት ሌሊት 10 ሰዓት ከ30 ላይ መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉ 10 የከባድ ውንብድና ፍርደኛ ታራሚዎች ላይ ማረሚያ ቤቱ ባደረገው ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ለማምለጥ ሙከራ ካደረጉ ፍርደኞች መካከል ከዚህ በፊት #አምልጦ ከጣልያን ሀገር በኢንተርፖል ተይዞ የመጣ ታራሚ ይገኝበታል።
ሌሎችም በተደጋጋሚ ከጤና ጣቢያ ፣ከመኪና ላይ ጭምር ለማምለጥ ሞክረው የተያዙ ፍርደኞች አሉ።
ማረሚያ ቤቱ ዛሬ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ቀጠሮ የነበራቸው ታራሚዎችን አጅቦ በማቅረብ መደበኛ ስራውን ሲሰራ ውሏል።
ታራሚዎቹ ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠቡ ተገቢ የሆነ የክትትልና የቁጥጥር ስራው ይቀጥላል። “
ለሚመለከተው ሁሉ
ጉዳዩ፡- ከኢዜማ መለየታችንን ስለማሳወቅ!

ላለፉት 30 ዓመታት የኢትዮጵያ ሕዝብ የሥልጣን እና የሀገሩ ባለቤት እንዲሆን የአንድነት ኃይሉ አካላት የሆንን ሁሉ ከሕዝባችን ጋር ሆነን በሀገራችን ፖለቲካ ውስጥ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈልን እና እየከፈልን የቆየን መሆናችን አይካድም።
እኛም (ፓርቲውን በስራ አስፈጻሚ ደረጃ ስንመራ የነበርን) እንደ ሌላው አባል ሁሉ ባለፉት የትግል ዓመታት በተደረገው ትግል ውስጥ ተሳታፊ የነበርን የዚህ ትውልድ አካል የሆነው በሕዝብ መስዋዕትነት በተገኘው እና በተስፋ በቀረው የለውጥ ጅማሮ አንድ ትልቅ ሀገራዊ ፓርቲ እንደሚያስፈልግ አምነን ያለንን ሁሉ አዋጥተን “ኢዜማ” የሚባል ሁሉን አሰባስቦ የሚያቅፍ፣ ለአንድነት ኃይሉ መሰባሰቢያ ይሆናል ብለን በማለም ሀገር አቀፍ ፓርቲ እንዲሆን መመሥረታችን የሚታወስ ነው።
በጋራ በመሠረትነው ኢዜማ ፓርቲ ውስጥ በአንዳንዶቻችን መሀል መጠነኛ የአቋም ልዩነት ቢኖረንም በሂደት በውይይት እንዲሁም መሬት በረገጠ ሥራ ወቅት ልዩነቱ እየጠበበ እና እየተስተካከለ ይሄዳል በሚል ቅን እሳቤ፤ በወንድማማችነት መንፈስ አምነን ነበር የተቀበልነው፡፡ ሆኖም ብዙም ሳይቆይ የአቋም ልዩነቱ ላይ የአካሄድም ልዩነት ተጨምሮበት ትግላችን መስመር ስቶ ከፍተኛ በሆነ በውስጠ ፓርቲ ትግል ውስጥ ተጠልፈን እንድንቆይ አድርጎናል፡፡
የኢትዮጵያ አሁን ሕዝብ በታሪኩ ገጥሞት የማያውቅ እዚህ መከራ ውስጥ ከመግባቱ በፊት መንገዳችንን እንድናስተካክል በፓርቲው ውስጥም በብዙ ታግለናል፡፡ በፓርቲው ጉባኤዎች ሁሉ ሳይቀር ስህተቶች ይታረሙ ይሆናል በማለት የትግሉን መድረክ ለማስፋት ብንሞክርም በተለያዩ ውስጣዊ እና ውጫዊ ምክንያቶች ማሳካት አልተቻለም፡፡ ኢዜማን ጠግኖ ለማዳን ያደረግነው ትግልም ከንቱ ቀርቷል፡፡
አሁንም በግልፅ እየታየ እንደሚገኘው የኢዜማ ከፍተኛ አመራር ሀገርን ለመታደግ ሕዝብንና ፓርቲዎችን አስተባብሮ
ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ለማምለጥ በተደረገ ሙከራ፤ ቢያንስ አምስት ታራሚዎች ቆስለው መያዛቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ
በአዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኙ የተወሰኑ ታራሚዎች ትላንት ለሊት ለማምለጥ ባደረጉት ሙከራ፤ አንድ እስረኛ ሲገደል ቢያንስ አምስቱ መቁሰላቸውን እና አንዱ ሳያይዝ መቅረቱን የአይን እማኞች እና የአካባቢ ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ከቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የማምለጥ ሙከራ መደረጉን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያረጋገጠው የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ግን ያመለጠ እስረኛ “የለም” ብሏል።
ከአስር ዓመት እና ከዚያ በላይ የተፈረደባቸው እስረኞችን ከሚያስተናግደው ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት የማምለጥ ሙከራ የተደረገው፤ ለዛሬ አጥቢያ ትላንት ረቡዕ ግንቦት 16፤ 2015 ለሊት አስር ሰዓት ገደማ መሆኑን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው አንድ የአይን እማኝ እና አምስት የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። የማምለጥ ሙከራውን ያደረጉት እስረኞች ብዛት 11 መሆኑን ከማረሚያ ቤት ፖሊሶች መስማታቸውን ነዋሪዎቹ አክለዋል።
እንደ ነዋሪዎቹ ገለጻ እስረኞቹ ከማረሚያ ቤቱ አምልጠው መውጣታቸውን ተከትሎ፤ በትንሹ ለአንድ ሰዓት ያህል የቆየ ተኩስ በአካባቢው ሲሰማ ቆይቷል። ድርጊቱ በተፈጸመበት ሰዓት በስራ ምክንያት በአካባቢው እንደነበሩ የተናገሩ አንድ የዓይን እማኝ በበኩላቸው፤ ተኩሱ ይበልጥ ጎልቶ ይሰማ የነበረው በማረሚያ ቤቱ መግቢያ ላይ ባለው አስፓልት መንገድ ላይ እና ተሻግሮ ባሉት አካባቢዎች እንደነበር አስረድተዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11039/

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ከ35 በላይ የሚሆኑ ባለሙያዎች እንዲሁም 11 በላይ አመራሮች በህገ-ውጥ የመሬት ወረራ ተሳትፈው መገኘታቸውን አስታውቋል፡፡
ፍትህ ቢሮው ለጠቅላይ አቃቤ ህግ አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ መረጃ በማደራጀት መላኩን ኢትዮ ኤፍ ኤም ሰምቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ወንጀል መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብዮት ጅፋር ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቁት፣ በዚህ ድርጊት ላይ ከተያዙት ውስጥ አስተዳደራዊ እርምጃ የተወሰደባቸው ሲኖሩ ሌሎች ደግሞ ጉዳያቸው በወንጀል እየተጣራ ያለ እንዲሁም በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ መኖራቸውን አስታውቀዋል፡፡
እነዚህ አመራሮች እና ባለሙያዎች መሬት ባንክ የገባን መሬት ለግል ጥቅማቸው ለማዋል በማሰብ ከግለሰቦች ጋር በጋራ በመሆን ጥቅም ለማግኘት ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
በለሚ ኩራ፣በልደታ እና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ አንድ አንድ አመራሮች እና ባለሙያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡
Ethio FM

የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈ ወርቂ፣ “የዋሽንግተን ዲሲ ቡድን” ሲሉ በጠሩት አካል ላይ ክሥ አሰሙ። ፕሬዚዳንቱ ወቀሳውን ያሰሙት፣ ዛሬ በተከበረው 32ኛ ዓመት “የነፃነት በዓል” ላይ ነው።
ፕሬዚዳንቱ፣ የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር፣ በኤርትራ እና በሌሎች ሀገራት ላይ ያካሒደዋል ያሉት ፖሊሲ፣ “ለትውልድ የዘለቀ ጠበኛነትን አትርፏል፤” ሲሉ ከሠዋል፡፡ ዝርዝሩን ከዚህ ያገኙታል
https://minilik-salsawi.blogspot.com/2023/05/eritrea-president-accused-washington.html
በዐዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ፣ ለዓመታት ጎጆ ቀልሰው ከኖሩበት ቤታቸው፣ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳደር፣ “ሕገ ወጥ ናችኹ፤” በሚል እንደተፈናቀሉ፣ ቤታቸው ፈርሶ እና ንብረታቸው ተበትኖ ባዷቸውን መቅረታቸውን ነዋሪዎች አማረሩ።
በአካባቢው ይኖሩ ከነበሩ ሰዎች፣ በሕጋዊ ውል የገዟቸውን ቤቶች ጨምሮ፣ የአካባቢው አስተዳደር በሚያውቀው ኹኔታ የገነቧቸው ቤቶች፣ በግብረ ኃይል እንዲፈርሱ በመደረጋቸው ለችግር መጋለጣቸውንም፣ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። የማፍረሱ ሒደት፥ “አድልዎ የተሞላበትና ማንነትን የለየ ነው፤” በሚል የሚሟገቱም አሉ።
ስማቸው በምስጢር እንዲያዝ የጠየቁን ግለሰብ፣ በዐዲስ አበባ ዙሪያ ከሚገኙ ሥፍራዎች አንዱ በኾነው ለገዳዲ እና ለገጣፎ አካባቢ፣ ለ15 ዓመታት መኖራቸውን ይናገራሉ። ግለሰቡ ለዓመታት የኖሩበት ያ ቤት፣ ዛሬ፣ ለወትሮው ከቆመበት ሥፍራ እንደማይገኝ ገልጸዋል።
ሰሞነኛ አዳርና ውሎቸው፣ አንዴ በድንኳን፣ አልፎ አልፎ ደግሞ በኪራይ መጠለያ እንደኾነ አባወራው ያስረዳሉ። የዚኽ ምክንያቱ ደግሞ፣ የሠሩት ቤት፣ በአካባቢው አስተዳደር እንዲፈርስ መደረጉ ነው።
ሌላው አስተያየት ሰጪአችን ደግሞ፣ ከ13 ዓመታት በላይ የካ ጣፎ አካባቢ፣ “ከገበሬዎች ገዛኹት” ባሉት ይዞታ ላይ፣ ቤት ሠርተው ሲኖሩ እንደነበር ይናገራሉ። በመጋቢት ወር ግን ነገሮች መቀየራቸውን፣ ለአሜሪካ ድምፅ ያስረዳሉ።
በልዩ ልዩ አካባቢዎች ቤታቸው የፈረሰባቸውን ነዋሪዎች አነጋግረናል፤ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
ለአማራ ብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ከአማራ ሕዝባዊ ኮሚቴ የተሰጠ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ!

አማራ-ጠሉ ስርዓት ከተገነባበት 1983 ዓ/ም ጀምሮ የአማራ ሕዝብ እያለፈበት ያለው እጅግ አሰቃቂ መከራ ከማንም ፊት የተሰወረ አይደለም።
ይህ ውርደት እና አሰቃቂ መከራ የተፈጸመው የአማራ ክልልን ስሙን እየቀያየረ ሲመራ የኖረው፤ አሁን “የአማራ ብልጽግና” የሚል መጠሪያ ላይ የደረሰው የአማራ-ጠሉ ስርዓት
አማራዊ በሆነው ተወካይ ቡድን ቀዳሚ አጋፋሪነት ነው።
ይህ የገዛ ሕዝቡን አስሮ በማስገረፍ እና በመግረፍ የተሰማራ ቡድን አሁን ላይ ይህንን ስራውን በተለመደው መንገድ ማስኬድ ባለመቻሉ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ይገኛል።
በመሆኑም በየሳምንቱ ስብሰባ ላይ
ይቀመጣል። ከሕዝቡ ጋር ያጣላው የራሱ አሽከርነት አባዜ መሆኑን ረስቶ “ከሕዝቡ ጋር ያጣላኝ የጽንፈኞች ሴራ ነው” ሲል የራሱን ጭራ ወደ አማራ ሕዝብ እውነተኛ ልጆች እየወረወረ ይገኛል።
የአማራ ሕዝብ ትግል በአሁኑ ወቅት ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ ባህር ዳር መቀመጥ አስፈርቷችሁ አዲስ አበባ ላይ ለከረማችሁት ለእናንተ መዘርዘር አያስፈልገንም።
ስለሆነም ይህንን የሕዝብ ቁጣ ወደ መልካም ምዕራፍ መቀየር ከፈለጋችሁ፤ ስብሰባ ያስቀመጣችሁ መፍትሄ የማምጣት ፍላጎት አድሮባችሁ ከሆነ ልታጤኗቸው
የሚገቡ በርካታ ነጥቦች እንዳሉ ለማሳሰብ እንወዳለ።
ይህን ማስጠንቀቂያ ለመጻፍ የወደድነውም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ብልጽግና ፓርቲ ውስጥ የታችኛውና የመካከለኛው መዋቅሮች አማራ የአማራን ሕዝብ አሁን ያለበትን ከፍተኛ የውርደት ማጥ በመረዳት ለመፍትሄው በመስራት ላይ እንደሚገኙ መረጃዎች ስላሉን ነው።
የእኛም ፍላጎት የአማራ ሕዝብ ችግር ለሚገባው ሁሉ እገዛ አድርጎ የህዝባችንን መከራ ማስቆም በመሆኑ ይህንን ማሳሰቢያ ለመጻፍ ወሰንን።
የአማራ ብልጽግና አመራሮች አሁን የተቀመጣችሁት
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በተቀሰቀሰ ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸው ተነገረ
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ነዋሪዎች መካከል በተከሰተ ግጭት አምስት ሰዎች መገደላቸውን የልዩ ወረዳው አስተዳደር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታወቀ። በግጭቱ ጉዳት የደረሰባቸው ሰባት ሰዎች ደግሞ በህክምና ላይ መሆናቸውን አስተዳደሩ ገልጿል።
የኑዌር፣ አኝዋ እና ኮሞ ብሔረሰቦች መኖሪያ በሆነው ኢታንግ ልዩ ወረዳ ግጭት የተቀሰቀሰው፤ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እሁድ ግንቦት 13፤ 2015 መሆኑን የልዩ ወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኡቦንግ ጊሎ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በዚሁ ዕለት ጠዋት ጀልባ በመቅዘፍ ላይ የነበረ አንድ የሚሊሺያ አባል በጥይት ተመትቶ መገደሉ፤ በልዩ ወረዳው ለተነሳው ግጭት መነሻ ምክንያት መሆኑንም አስረድተዋል።
ጥቃት የተፈጸመበትን የሚሊሺያ አባል ሁኔታ ለመመልከት ወደ ስፍራው የሄዱ የአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ተኩስ ከተከፈተ በኋላ ሁኔታው ወደ ግጭት ማምራቱን አቶ ኡቦንግ ገልጸዋል። ተኩሱን የከፈቱት “ደፈጣ ላይ” የነበሩ ታጣቂዎች መሆናቸውን የጠቀሱት ዋና አስተዳዳሪው፤ ይህን ጥቃት ተከትሎ የአኝዋ እና ኑዌር ብሔረሰቦች መኖሪያ በሆኑ ቀበሌዎች መካከል “ውጊያ” መጀመሩን አብራርተዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11031/
ዶ/ር ይልቃል መልቀቂያ አስገቡ!! አመራሩ ጎራ ለይቷል| | የአማራ ድምጽ ዜና |
የትግራይ አባቶች ያስነሱት ሁለተኛው እሳት ፡ የአቶ ክርስቲያን ታደለ ቆንጆዎቹ
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 1 ቀን 2015ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ግንቦት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡ ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት እና መንፈሳዊ ዕድገት ትኩረት በመስጠት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
1. ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም ጉልላት እንደመሆኗ ሰላም መሠረታዊ ተልእኮዋ ነው፡፡ ስለዚህ ወቅታዊውን ችግር ታሳቢ በማድረግ በመላው አገራችን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ካሉ ተቋማት ጋራ የሚሠራ፣ በሀገሪቱ መንግሥትም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የሚኖረው የሰላም ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡
2. በትግራይ ክልል በሚገኙት አህጉረ ስብከት ተቋርጦ የነበረው መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ግንኙነትን በተመለከተ ቀደም ሲል በቅዱስ ሲኖዶስ ተሠይሞ በሥራ ላይ የሚገኘው ልዑክ የጀመረውን እንቅስቃሴ እንዲቀጥል የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትን በማነጋገር ተልዕኮውን እንዲፈጽም ምልዓተ ጉባኤው መመሪያ ሰጥቷል፡፡
3. በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት በትግራይ ክልል የሚገኙ ወገኖቻችን ያሉበትን ከፍተኛ ችግር ታሳቢ በማድረግ አስቸኳይ የሆነ ሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ሃያ ሚሊየን ብር ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
4. በወቅታዊ ችግር ምክንያት በመላው ሀገራችን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን

መጋቤ ብርሃናት ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ በጸጥታ አካላት ተይዘው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ውስጥ ይገኛሉ !
የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ም/ኃላፊ የሆኑት መጋቤ ብርሃናት ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2015 ዓ.ም ከቤታቸው ወደ ሥራ ብለው ከወጡ በኋላ ስልካቸው የተዘጋ እና መገኘት ያልቻሉ ሲሆን ከምሽቱ 12:00 ሰዓት በኋላ ግን በጸጥታ አካላት ተይዘው ወደ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን መወሰዳቸውን ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ችሏል።
በተመሳሳይ መ/ር ተሾመ በየነ ገላን አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል።
ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
በፀጥታ ኃይሎች የንግድ ቤታቸው የፈረሰባቸው በርካታ አካል ጉዳተኞች ለልመና ጎዳና ልንወጣ ነው አሉ

(አዲስ ማለዳ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ልዩ ሥሙ ከረሚላ ፋብሪካ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ከ2001 ጀምሮ ቋሚ ቦታ እስከሚሰጠን በጊዜያዊነት ሥንሰራ ነበር ያሉ በርካታ የአካል ጉዳተኞች፤ የሥራ ቦታችን በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በለሊት በመፍረሱ እና ዕቃችንም በመወሰዱ ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀናል ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ፡፡
ለዚህ ችግር የተጋለጡት የአካል ጉዳተኞች ቁጥራቸው ከ180 የማያንሱ መሆኑን ገልጸው፤ የሥራ ቦታቸው የፈረሰው እና ዕቃቸውም የተወሰደው ባሳለፍነው ሐሙስ ግንቦት 10/2015 ሌሊት ዘጠኝ ሰዓት መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የንግድ ቤቶቹን ያፈረሱት የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት እና የደንብ ሠራተኞ በጋራ መሆናቸውን የገለጹት አካል ጉዳተኞች፣ ሊያፈርሱብን እንደሆነ ቀድሞ መረጃ ደርሶን ለአስራ አምስት ቀን ስንጠብቅ ነበር፣ በኋላ ግን ትተውታል ብለን በተዘናጋንበት ነው ድንገት መጥተው ያፈረሱብንም ብለዋል፡፡
አካል ጉዳተኞቹ ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳድሩት በዚህ የንግድ ቦታ በሚያገኙት ገቢ እንደነበር ገልጸው፣ ‹‹አሁን ግን ወደ ለልመና ወደ ጎዳና ከመውጣት ውጭ ሌላ መፍትሄ የለም፡፡›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
መፍትሄ እንዲሰጣቸው ‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር ዓባይ ቢሯቸው ሄደን ብንጠይቃቸውም እኔ ሥራ እድል ፈጠራ እንጂ ስለእናንተ አይመለከተኝም ብለው ወደ ከንቲቫ ጽህፈት ቤት ላኩን›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡
‹‹ሆኖም ከንቲባ ጽህፈት ቤት ሄደን ስንጠይቅ ደግሞ ክፍለ ከተማ ሂዱ ተብለን ወደዚያው ሄደን ስንጠይቅ ደግሞ በአመጽ የሚፈታ ችግር የለም አርፋችሁ ተቀመጡ፡፡›› የሚል ምላሽ ነው
በባቱ (ዝዋይ) በመንግሥት እና በ‹‹ሸኔ›› ታጣቂዎች መካከል ግጭት መኖሩ ተገለጸ
(አዲስ ማለዳ)
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባቱ (ዝዋይ) ወረዳ እና አካባቢው በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራው ታጣቂ ኃይል መካከል ግጭቶች መኖራቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገለጹ፡፡
ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ግለሰብ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፤ በወረዳው በተለይም በገጠራማ ቀበሌዎች ሕዝቡ በከፍተኛ ሰቆቃ ውስጥ እንደሚገኝ ተናገረዋል፡፡
የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ‹‹ሸኔን ትደግፋላቸሁ›› ሲሉ፤ ራሱን የኦሮሚያ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን ደግሞ ‹‹የመንግሥት ኃይሎች ትደግፋላቸሁ›› በማለት የአካባቢው ነዋሪ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
ንጹኃንን በማገት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ መጠየቅ፣ የአርሶ አደሩን እንሰሳት አርደው መብላት፣ ዝርፊያ እና ማስፈራራት የኦነግ ሸኔ ታጣቂ ቡድን የዕለት ከዕለት ተግባር መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ሆኖም የአካባቢው ማኅበረሰብ ከፍተኛ ግፍና በደል እየተፈጸመበት ቢሆንም፤ በሥፍራው ያሉ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ነዋሪውን ሊታደጉ አልቻሉም ተብሏል፡፡
የታጣቂ ቡድኑ አባላት በአካባቢው መንቀሳቀስ ከጀመሩ ጊዜ አንስቶ፣ ለማህበረሰቡ ወጥቶ መግባት እና ሥራ መስራት ፈተና እንደሆነም ነው የተገለጸው፡፡
በዚህ ሳቢያ በወረዳው የሰዓት እላፊ ገደብ የተጣለ ሲሆን፣ ማንኛውም ተሽከርካሪ ከምሽቱ 12 ሰዓት በኋላ በከተማዋም ሆን በዙሪያዋ ባሉ አጎራባች አካባቢዎች መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ተጠቁሟል፡፡
‹‹በመንግሥት እና በታጣቂ ቡድኑ መካከል የሠላም ድርድር ከተደረገ በኋላ ነገሮች ይስተካከላሉ ብለን አስበን የነበረ ቢሆንም፣ ችግሮች እየባሱ እንጂ እየተስተካከሉ አልመጡም›› ሲሉ ነው ነዋሪዎቹ የተናገሩት፡፡
ስለሆነም መንግሥት አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ወስዶ የሕዝቡን ሠላም በዘላቂነት እንዲያስጠብቅ

በኢትዮጵያ ካሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ “ከፍተኛ” የሚባለውን ደረጃ ያሟሉ፤ አራት ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ካሉ 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተፈላጊውን “ከፍተኛ ደረጃ” የሚያሟሉት አራቱ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ወላጆች፣ የቀድሞ ተማሪዎች እና መምህራንን የሚያሳትፍ፤ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ያለመ ሀገር አቀፍ የትምህርት ዘመቻ በአንድ ወር ተኩል ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚያደርግም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 15፤ 2015 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው። ሪፖርቱን ለፓርላማ አባላት ያቀረቡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአጽንኦት ካነሷቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ፤ የትምህርት ቤቶችን ጥራት የሚመለከት ነው።
እርሳቸው የሚመሩት መስሪያ ቤት በሀገሪቱ አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ ባሉ 47 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ግምገማ ማድረጉን የተናገሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ በተገኘው ውጤት ላይ ተመስርቶ ትምህርት ቤቶቹ በአራት ደረጃዎች እንደተመደቡ ገልጸዋል። ግምገማው የተደረገው፤ ትምህርት ቤቶች በሚጠቀሟቸው ግብዓቶች፣ በመማር ማስተማር ሂደቶቻቸው እንዲሁም ተማሪዎቻቸው በሚያስመዘግቧቸው ውጤቶች ላይ እንደነበር አመልክተዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/11020/
የጴጥሮሳውያን ኅብረት ጸሐፊ የሆኑት መምህር ተሾመ በየነ በጸጥታ አካላት ተወሰዱ !
++++

በቋሚ ሲኖዶስ መልካም ፈቃድ ጥር 24 ቀን 2015 ዓ.ም የተቋቋመውን ሀገር አቀፍ የቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ጉዳይ አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ በጸሐፊነት እንዲያገለግሉ ተመድበው የነበሩት መምህር ተሾመ በየነ በዛሬው ዕለት በጸጥታ አካላት ተወስደዋል።
መምህር ተሾመ የጴጥሮሳውያን ኅብረት ጸሐፊ ሲሆኑ ኅብረቱን ወክለው በተቋቋመው ዐቢይ ኮሚቴ ውስጥ በከፍተኛ ኃላፊነት ቤተክርስቲያንን እያገለገሉ የነበሩ ወንድም ናቸው።
በዛሬው ዕለት ከቅዱስ ዑራኤል አካባቢ የጸጥታ አካላት ነን በሚሉ ግለሰቦች የተወሰዱት መምህር ተሾመ በአሁኑ ሰዓት የተወሰዱበት ቦታ እንደማይታወቅ ለዝግጅት ክፍላችን የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
መምህር ተሾመ ከዚህ በፊት ከዐቢይ ኮሚቴው አባላት ጋር በጋራ በመሆን በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን በኩል መግለጫ መስጠታቸው የሚታወስ ሲሆን ከዐቢይ ኮሚቴው በጸጥታ አካላት የተወሰዱ ሁለተኛው ሰው ሆነዋል ሲል ማኅበረ ቅዱሳን ዘግቧል። ምንጭ፦ ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
የዘጠኙ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት ሥርዓተ ሢመት ሐምሌ 9/2015 እንደሚከናወን ተገለጸ
👉የኤጲስ ቆጶሳቱን ምልመላና ምርጫ የሚያከናውን 7 ሊቃነ ጳጳሳት ያሉት አስመራጭ ኮሚቴ ተመርጧል
በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተመረጡ ዘጠኝ አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት ሥርዓተ ሢመት ሐምሌ 9/2015 እንደሚከናወን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ምልዓተ ጉባኤው የአዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት ምልመላና ምርጫ የሚያከናውን 7 ሊቃነ ጳጳሳት ያሉት አስመራጭ ኮሚቴ መምረጡን አስታውቋል።
የግንቦቱ ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተወያይቶ ውሳኔ ካሳለፈባቸው አጀንዳዎች መካከል የአዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫና ሢመት አንዱና ዋነኛው ነው።
በመሆኑም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጉዳዩ ዙሪያ ለሦስት ቀናት ከተወያየ በኋላ፤ ለአሁኑ ችግር ባላባቸውና አስፈላጊ በሆነባቸው ዘጠኝ አህጉረ ስብከት ላይ በዚህ ዓመት 2015 ዘጠኝ አዳዲስ ኤጲስ ቆጳሳት እንዲሾሙ ብሏል፡፡ እንዲሁም በጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የቤተ ክርስቲያን እውነትና ቀኖናን እንዲሁም መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ መሠረት ባደረገ መልኩ ብሎም አባቶች በሚያስፈልጉባቸው አህጉረ ስብከት የአዳዲስ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ጉዳይን እንደሚመለከተው ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚህም መሠረት በዚህ ዓመት በሚካሄደው ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት የሚሾሙ አባቶች የሚመደቡባቸው የ(9)ኙ አህጉረ ስብከት ሥም ዝርዝር
1. ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት
2. ምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት
3. ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ሀገረ ስብከት
4. የቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት
5. ምዕራብ አርሲ (ሻሸመኔ) ሀገረ ስብከት
6. ምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
7. ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት
8. ጌዴኦ ቡርጅና አማሮ ሀገረ ስብከት
9.

የሀገር አቀፍ የቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ጉዳይ አስተባባሪ ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ በእስር ላይ እንደሚገኙ ተረጋግጧል።
የነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር ሰብሳቢና የሀገር አቀፍ የቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ጉዳይ አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ የሆኑት ቀሲስ አክሊሉ ዳምጠው ትናንት ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም በጸጥታ አካላት የተወሰዱ ሲሆን በአኹኑ ሰዓት ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፓሊስ ኮሚሽን ውስጥ እንደሚገኙ እና አስፈላጊውን ሕጋዊ መፍትሔ እንዲያገኙ በጠበቆች በኩል ሙከራ እየተደረገ እንደሚገኝ ከቤተሰቦቻቸው ለማረጋገጥ ችለናል ሲል የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል ገልጿል።
ቀሲስ አክሊሉ አብረዋቸው በዐቢይ ኮሚቴው ላይ ከሚያገለግሉት አባላት ጋር በመሆን በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን በኩል ወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠታቸው ይታወሳል።
ግንቦት 15 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በኢትዮጵያ ከቀን ቀን እየተባባሰ የሄደው የኑሮ ውድነት የምግብ፣የፍጆታ፣የቁሳቁሶች፣የትራንስፖርትና የአገልግሎት ዋጋ ግሽበት አብዛኛውን ዜጋ አቅም አሳጥቷል።በተለይ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች የኑሮ ውድነትን መቋቋም የማይችሉበት ደረጃ ላይ ከደረሱ ሰንብቷል። የቤት ኪራይ ዋጋ እና የተለያዩ አገልግሎቶች ክፍያ በየጊዜው መናር ኑሮን እጅግ አክብዶታል። መንግሥት ለዓመታት የዘለቀውን የዋጋ ንረት ለማቃለል ይረዳሉ ያላቸውን የተለያዩ ዕርምጃዎችን መውሰዱን ቢያሳውቅም የኑሮ ውድነቱ እየባሰ እንጂ እየቀነሰ አልሄደም ።
ችግሩ የከፋ ደረጃ ላይ በደረሰበት በአሁኑ ወቅትም መንግሥት ለችግሩ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈለግ ጥያቄ እየቀረበለት ነው። የዋጋ ንረት በኢትዮጵያ ሠራተኞች ላይ ከፍተኛ የኑሮ ጫና ማድረጉን የሚገልጸው የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፈደሬሽን በምህጻሩ (ኢሰማኮ) በቅርቡ መንግስት ችግሩን መቀነስ የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስድ አሳስቧል። የሠራተኛው ደሞዝ የአሁኑን የገበያ ዋጋ ሊቋቋም በማይችልበት ደረጃ ላይ ነው የሚለው አንድ ሚሊዮን አባላት ያሉት ኢሰማኮ አስቸኳይ ያላቸውን የበኩሉን መፍትሄዎችም ከሦስት ሳምንት በፊት በተከበረው በዓለም የሠራተኞች ቀን

በአደባባይ ሰልፍ ለማቅረብ ቢያቅድም ሰልፉ ባለመፈቀዱ ሳይሳካላት ቀርቷል። ሆኖም ኮንፈደሬሽኑ ጥረቱን በመቀጠል ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የገንዘብ ሚኒስትርን ጨምሮ ለሌሎች ጉዳዩ በቀጥታ ይመለከታቸዋል ላላቸው ባለስልጣናት የችግሩን አሳሳቢነት በመግለጽ በአስቸኳይ ሊተገበሩ ይገባቸዋል ያላቸውን መፍትሄዎች ያካተተ ደብዳቤ መላኩን አስታውቋል።
ቀደም ሲል የምዕራብ ጎጃም ዞን በ14 የገጠር ወረዳዎችና በስምንት የከተማ አስተዳደሮች ተዋቅሮ ማዕከሉን ፍኖተ ሰላም አድርጎ ሲተዳደር ነበር። ሆኖም አንዳንድ ወረዳዎች ከማዕከሉ የራቁ በመሆናቸው አስተዳደራዊ ሥራዎችን ለማከናወን ነዋሪዎቹ ተቸግረው እንደቆዩና «ዞን ይከፈልልን» ጥያቄያቸውን በተደጋጋሚ ሲያቀርቡ እንደ ነበር ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል። ሆኖም ከብዙ ጊዜ በኋላ ጥያቄው ቢመለስም ማዕከሉ ባሕር ዳር መሆኑ ተገቢ እንዳልነበር ከምክንያታቸው ጋር የነገሩን የአዴት ከተማ አስተዳደር ነዋሪው አቶ ይሔነው ዐወቀ ናቸው።
«ዞኑ በጣም ሰፊና ለማስተዳደርም አስቸጋሪ ስለነበር ለሁለት መከፈሉ ትክክል ነው፣ ሆኖም ማዕከሉ በስሩ ካሉ ወረዳዎች በአንዱ መሆን ነበረበት ምክንቱም ያ ከተማ የማደግና ዘመናዊ የመሆን ዕድል ይኖረው ነበር፣ ባሕርዳር ከተማ መሆኑ ግን ለኃላፊዎች ምቾት ካልሆነ በስተቀር ሌላ ፋይዳ የለውም።» የብዙዎቹ ወረዳዎች ነዋሪዎች ጉዳይ ለማስፈፀም ወደ ፍኖተ ሰላም ሲጓዙ አዊ ብሔረሰብ አስተዳደርን ተሻግረው ይሄዱ እንደነበር የገለፁልን ደግሞ የዱር ቤቴ ከተማ ነዋሪውና የአስተባባሪ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ውበት ጥላሁን፤ ጥያቄው በመመለሱ ኅብረተሰቡ ደስተኛ እንደሆነ አስረድተዋል። የሰሜን ጎጃም ዞን ማዕከል ባሕር ዳር መሆኑንም ለሁሉም የአዲሱ ዞን ማዕከል በመሆኑ ተስማምተን ያደረግነው ነው ብለዋል።
ጉዳዩን ሲያስተባብሩ ከነበሩ የኮሚቴ አባላት መካከል አቶ አበረ ዓለሙ ኅብረተሰቡ ያመነባቸው አመራሮች ዞኑን እንዲመሩ መሾማቸውን ጠቅሰው በዚህም ኅብረተሰቡ ደስተኛ አንደሆነ ነው ያመለከቱት። የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ «አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት የዞንና የወረዳ ይከፈልልኝ ጥያቄዎች ተገቢ እንዳልሆኑ ጠቁመው የምዕራብ ጎጃም ዞን ለሁለት መከፈሉ ግን ትክክለኛና ተገቢ
የሱዳን ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች፣ ካለፈው ወር ሚያዝያ ሰባት ቀን ጀምሮ፣ በካርቱም እና በሌሎች አካባቢዎች በሚያካሒዱት ግጭት ምክንያት፣ 25ነጥብ7 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች፣ አስቸኳይ ሰብአዊ ርዳታ ፈላጊዎች ኾነዋል።
ዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(IOM)፣ ረቡዕ ዕለት ያወጣው መረጃ እንደሚያሳየው፣ በመላው ሱዳን ቢያንስ 843ሺሕ130 ሰዎች ሲፈናቀሉ፣ ወደ 259ሺሕ የሚደርሱ ሰዎች ደግሞ ወደ ጎረቤት ሀገራት ተሰደዋል።
ግጭቱ ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ፣ ኢትዮጵያንና ሱዳንን ወደምታገናኘው መተማ ከተማ፣ በቀን ከ700 እስከ 800 የሚደርሱ ሰዎች፣ የሱዳንን ድንበር ተሻግረው ይገባሉ። የቻይና ማዕከላዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ የኾነው ሲሲቲቪ ከአነጋገራቸው ስደተኞች መካከል አንዱ የኾነው እስማኤል ሁሴን፣ ግጭቱ ከመጀመሩ በፊት፣ እሱ እና ነፍሰ ጡር ሚስቱ፣ በካርቱም ይኖሩ እንደነበር ገልጾ፣ አለመረጋጋቱ መኖሪያ ቤታቸውን ጥለው እንዲሰደዱ እንዳስገደዳቸው ይናገራል።
“እዚኽ ለመድረስ በጣም ብዙ ቀናትን ወስዶብናል። በየመንገዱ የፍተሻ ጣቢያዎች አሉ። ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ከደረስን በኋላ፣ ለሌላ ዙር የደኅንነት ፍተሻ ወደ አልቃድሪፍ ተልከን ነበር፤” የሚለው እስማኤል፣ መተማ ለመድረስ፣ ለእርሱ እና ለነፍሰ ጡር ባለቤቱ በጣም ከባድ እንደነበርና በሱዳን የነበረውን ሁሉንም ነገር በማጣቱ ሕይወትን እንደገና ከምንም መጀመር እንዳለበት ገልጿል።
በሱዳን ይሠሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያንም፣ ደኅንነታቸውን ለማረጋገጥ ሌላ አማራጭ ስላልነበራቸው ወደ ትውልድ ሀገራቸው ተመልሰዋል። ከእነዚኽ አንዱ፣ በሱዳን ስደት ላይ ይኖር የነበረው ነብሱ መሐመድ ኑር አንዱ ነው።
በዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት(IOM) የኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቢባቱ ዌን-ፎል እንደሚያስረዱት፣ ከሱዳን እየሸሹ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞች፣ አስቸኳይ መሠረታዊ ርዳታ የሚያስፈልጋቸው ቢኾንም፣ በቂ ድጋፍ
በጋዜጠኛና የታሪክ ምሁሩ አቶ ታዲዎስ ታንቱ የክስ ሂደት ላይ ሲካሄድ የነበረው ምስክር የመስማት ሂደት ተቋረጠ!
👉ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ጀነራል አበባው ታደሰ ፍርድ ቤት አንቀርብሞ ብለዋል

በዛሬው ችሎት አቃቤ ህግ “የሰነድ ማስረጃዎች ከቀረበው ክስ ጋር ግንኙነት የላቸውም እንዲሁም እንዲመሰክሩ የተጠሩት ምስክሮች ተከላከሉ ከተባሉበት አግባብ አንፃር ትክክለኛና ቀጥተኛ የሆኑ ስላልሆኑ ሊሰሙ አይገባም” ሲል በፅሁፍ አቤቱታ ማስገባቱን ጠበቃ አዲሱ ጌታነህ ለሮሃ ቲቪ ተናግረዋል።
በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ሕገ መንግሥት እና ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮች ችሎት ጉዳያቸው እየታየ ያለው አቶ ታዲዮስ ታንቱ በአራት ክሶች መከሰሳቸውን ይታወቃል። ክሶቹም መከላከያ ሰራዊትን በተመለከተ፤ ከታሪክ አንጻር የተናገሯቸው ንግግሮች ፣ አንዱ ብሔር በሌላው ላይ እንዲነሳ አድርገዋል የሚልና የመንግሥት ባለሥልጣናትን ተሳድበዋል የሚሉት ናቸው።
በእነዚህ በቀረበቡባቸው ክሶች ዙሪያ እየተከራከሩ የሚገኙት አቶ ታዲዎስ ታንቱ የመከላከያ ምስክር ለማቅረብ በጠየቁት መሰረት በጠበቆቻቸው በኩል የመከላከያ ምስክሮቻቸውን እያሰሙ ይገኛሉ። በዚህም ጋዜጠኛ መስከረም አበራ ፣ የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳና የኢሰመኮ ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ምስክርነታቸውን ከሰጡ መካከል ናቸው። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ጀነራል አበባው ታደሰ ደግሞ ለመቅረብ ፍቃደኛ ያልሆኑ መሆናቸው ታውቋል።
በዚህም የሰነድ ማስረጃዎችና ቀሪ የመከላከያ ምስክሮች ከዛሬ ከግንቦት 14 እስከ 16 እንዲቀርቡ ትእዛዝ ተሰጥቶ ነበር። ነገር ግን ዛሬ ግንቦት 14/2015 በዋለው ችሎት አቶ ታዲዎስ ሲያሰሙት የነበረው መከላከያ ምስክር የማሰማት ሂደት ተቋርጧል። በዛሬው ችሎት አቃቤ ህግ “የሰነድ ማስረጃዎች ከቀረበው ክስ ጋር ግንኙነት የላቸውም

መንግሥት ገለልተኛ ተቋማትን በገዢው ፓርቲ አባሎች ጠፍሮ በመያዝ ሚናቸውን እንዳይወጡ እና በሕግ አግባብ እንዳይሠሩ ማድረጉን ቀጥሏል!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ከግጭት አዙሪት እንድንወጣ እና የሀሳብ የበላይነት አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ የመገናኛ ብዙኀን ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን በጽኑ ያምናል።
መገናኛ ብዙኀኑ ሙስናና ብልሹ አሰራርን በማጋለጥ፣ ዜጎች በመረጃ የበለፀጉ እንዲሆኑ በማድረግ በሥልጣን መባለግ እንዳይኖር እና መንግሥታዊ ተጠያቂነት እንዲሰፍን አይተኬ ሚና አላቸው።
መገናኛ ብዙኀን ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ፤ ነፃ ገለልተኛና የመረጃ ብዝኀነትን የሚያስተናግዱ ሊሆኑ ይገባል። ይህ በማይሆንበት ጊዜ አሰራራቸውን ሊቆጣጠር የሚገባው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 በተሠጠው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት የተለያዩ የእርምት እርምጃዎችን የመውሠድ ኃላፊነት እንዳለበት ይታወቃል።
ይሁን እንጂ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣኑም ሆነ የሕዝብ መገናኛ ብሮድካስቶች ሃቀኛ የህዝብ ድምጽ የመሆን ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዳይወጡ በገዢው ፓርቲ ካድሬዎች የተሞሉ በመሆናቸው ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት ባሻገር ሲያልሙ መመልከት አልተቻለም።
ኢዜማ እነዚህን በህዝብ መገናኛ ብዙኀን ስም በየዘመኑ ለሥልጣን የበቁ ገዢዎችን ፍላጎት ለማስፈፀም ከመሯሯጥ ውጪ የድሃን በደል እና የተዛነፈውን ፍርድ የማጋለጥ ስራ የዘነጉ መገናኛ ብዙኀኖች ከድርጊታቸውም እንዲታቀቡ በተደጋጋሚ ሲያሳስብ እንደከረመ የሚታወቅ ነው፡፡
ለዚህም ማሣያ ፓርቲያችን በተደጋጋሚ በጥቁር እና ነጭ የተፃፉ ሕጎች ተጥሰው ለመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣንም ሆነ ለሕዝብ መገናኛ ብሮድካስት የተሾሙ የገዢው ፓርቲ አባላት ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ፣ ባለቤትነታቸው ከዚህ ቀደም የኢህአዴግ የልማት ድርጅቶች የነበሩና ይህ ፓርቲ ሕጋዊ ማንነቱን ካጣ በኋላ በየትኛው አካል ባለቤትነትና አስተዳደር ሥር እንደሚገኙ በይፉ
ቢቢሲ ኒውስ – ባኪንግሃም ቤተ መንግሥት በዊንድሶር ካስል ውስጥ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የተቀበረውን የኢትዮጵያዊ ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስን አጽም እንዲመለስ የቀረበለትን ጥያቄ እንደማይቀበል ገለፀ።

ቤተሰብ፣ የልዑሉ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ እና መንግሥት የልዑሉ አጽም ወደ ትውልድ አገሩ እንዲመለስ ከየትኛውም ጊዜ በላይ አጥብቀው ቢጠይቁም፣ የእንግሊዝ ንጉሥውያን መልስ ግን “ለጥያቄው ምላሽ መስጠት አይቻለንም” የሚል ሆኗል።
የባኪንግሃም ቤተ መንግሥት ልዑል አለማየሁ ተቀብሮ ባለበት ስፍራ “አርፈው የሚገኙት ሳይረበሹ አጽሙን ማውጣት የሚቻል አይደለም፤ ስለዚህ ለጥያቄው ምላሽ መስጠት እንደማንችል እናሳውቃለን” ሲል ቢቢሲ ላቀረበው ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል።
ልዑል አለማየሁ እግሩ የእንግሊዝ ምድርን ሲረግጥ ገና የሰባት ዓመት ታዳጊ የነበረ ሲሆን፣ እናቱ በጉዞ ላይ መሞታቸውን ተከትሎ ወላጅ አልባ ሆኖ ነበር።
በጎንደር ያሉት የልዑሉ ቤተሰቦች ግን አጭር ዕድሜውን በሰው አገር በብቸኝነት አሳልፎ በሐዘን ሕይወቱ ያለፈው ልዑል፣ ከእንግሊዝ ነገሥታት ጎን መቀበሩ ብቻ “ለነፍሱ እረፍት አይሰጥም” ይላሉ።
በጎንደር የሚገኙ የአጼ ቴዎድሮስ ሦስተኛ እና አራተኛ ትውልድ ቤተሰብም ልዑሉ “የዘላለም እረፍት” ያገኝ ዘንድ አጽሙ ወደ ትውልድ አገሩ መመለስ አለበት ሲሉ ለባኪንግሃም ቤተ መንግሥት ይፋዊ ጥያቄ አቅርበው ነበር።
የአጼ ቴዎድሮስ አራተኛ ትውልድ ቤተሰብ የሆነው ፋሲል ሚናስ፣ ልዑሉ ማረፍ ያለበት በባዕድ አገር ሳይሆን በአባቱ አገር ጎንደር ነው ይላል።
“በዊንዘር መቀበሩ መልካም አስበው እንደሆነ እረዳለሁ፣ ከእንግሊዛውያን ነገሥታት ጎን መቀበሩም እኔን አይደንቀኝም። ምክንያቱም እርሱም ልዑል ነበር” ይላል።
ወደ ብሪታንያ ከተወሰደ በኋላ እኤአ በ1879 በ18 ዓመቱ በመተንፈሻ አካላት ሕመም የሞተው ልዑል
ዘጠኝ ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ ተወሰነ፤
* ዕጩዎች ለሰኔ 30 ቀርበው፣ ሐምሌ 9 ቀን ይሾማሉ፤
* ባለፈው ሹመታቸው አወዛጋቢ ከነበሩት መስፈርቱን የሚያሟሉት ሊካተቱ እንደሚችሉ ተመልክቷል።
+++++

(አደባባይ ሚዲያ):– የቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ አከራካሪውን የኤጲስ ቆጶሳት ሢመት በተመለከተ፣ ዛሬ ሰኞ፣ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም. በነበረው የቀትር በኋላ ውሎ ከስምምነት ላይ ደርሶ፣ ተከታዩን ውሳኔ አሳልፏል፤ ከዐማራ ክልል አህጉረ ስብከት በቀር፣ ለኦሮሚያ እና ለደቡብ፣ ሶማሌ፣ ድሬዳዋ እና አሶሳ አህጉረ ስብከት የሚሾሙ ዘጠኝ ዕጩዎች ተለይተው እንዲዘጋጁ ወስኗል፤
– አምስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በአባልነት የሚገኙበት የኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ ሠይሟል፤ እነርሱም፦ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ (ሰሜን ወሎ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ)፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ (የሐዲያ ከምባታ እና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ) እና ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ (የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና ምሥራቅ አፍሪቃ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ) ናቸው፤ – አስመራጭ ኮሚቴው እስከ መጪው ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ዕጩዎቹን ለይቶ ያቀርባል፤
– ዕጩዎቹ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተገምግመው እንዲሾሙ ከተወሰነ በኋላ በዓለ ሢመቱ ሐምሌ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በቅዱስ ፓትርያርኩ አንብሮተ እድ ኤጲስ ቆጶስነት ሢመቱ ይፈጸማል። – በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ምልዓተ ጉባኤ ደግሞ፣ ለዐማራ ክልል ብቻ ተጨማሪ የኤጲስ ቆጶሳት ሢመት እንደሚኖር ተመልክቷል።
– ከኦሮሚያ አህጉረ ስብከት በተጨማሪ ለደቡብ፣ ለሶማሌ፣ ለአሶሳ እና ለድሬዳዋ አህጉረ ስብከት ነው የአሁኑ ሹመት የሚካሔደው። የዐማራ ለቀጣይ ጥቅምት ምልዓተ ጉባኤ ተጠንቶ እንዲመጣ ነው
መንግሥት የሕግ የበላይነትን ያክብር! እናት ፓርቲ
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ!

የሕጎች ሁሉ የበላይ የሆነዉ ሕገ መንግሥት እጅግ ብዙ የማያስማሙ ጉዳዮች እንዳሉበት የምንሞግተውና ለመሻሻሉ ሌት ተቀን የምንተጋ ቢሆንም አግባብነት ባለው መንገድ ማሻሻያ/ለዉጥ እስኪደረግ ድረስ በግንባር ቀደምነት መንግሥት እንዲሁም ዜጎች ህገ መንግስቱን የማክበር ግዴታ አለባቸው። መንግሥትም ህገ መንግስቱን የማስከበር ኃላፊነት እንዳለበት በጽኑ እናምናለን፡፡ ይህ ሊሆን ካልቻለ ለግለሰባዊ፣ ቡድናዊና መንግሥታዊ ሥርዓት አልበኝነት ምቹ መደላድል ይፈጠራል፡፡
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፲፩ ንዑስ አንቀጽ ፫ በግልጽ እንደሚደነግገዉ “ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ሃይማኖትም በመንግሥት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም”፡፡ የሕገ መንግሥቱ ግልጽ ድንጋጌ በዚህ መልኩ ቢቀመጥም ሕገ መንግሥቱ ሥራ ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ ይህ አንቀጽ ሲተገበር አልታየም፡፡ መንግስት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ ሲገባ ኖሯል፤ እየገባም ይገኛል፡፡ የቅርብ ጊዜና ወቅታዊዉ የዚህ ሕገ መንግሥት አንቀጽ መጣስ ማሳያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዉስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት መንግሥት አገርን ባዋቀረበት የጎሳ መስመር ቤተክርስቲያንን ለመከፋፈል ከጥር ወር ፳፻፲፭ ዓ.ም ጀምሮ እየሠራ ያለዉ ግልጽ እና ስዉር (የዉስጥ ለዉስጥ አሠራር) እንቅስቃሴ ነዉ፡፡ ሁላችንም እንደምናስታውሰው ችግሩ በመንግሥት እንደተጠነሰሰና እንደተሠራ ሁሉ መፍትሄ የተበጀለትም በመንግሥት መመሪያ እና ትዕዛዝ እንደነበረ የአደባባይ ምስጢር ነዉ፡፡
መንግስት የቤተክርስቲያኒቷ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በተቀመጠበት በዚህ ወቅት ህገ መንግስቱን በመጣስ እና ረጅም እጁን በመስደድ የቤተክርስቲያኒቱን አንድነት በሚያናጋ ተግባር ላይ ተሰማርቷል፡፡ ይህ አካሄድ ደጋግመን እንደምንለዉ የአገሪቱን የሕጎች ሁሉ

” የሹመቱ ቀን ወደፊት ይገለፃል ” – ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን በተመለከተ አጭር መግለጫ ሰጥተዋል።
ምን አሉ ?
– የግንቦት 2015 ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በሰላም እና ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቋል።
– ዛሬ የመጨረሻው አጀንዳ ላይ ብዙ ውይይት ተካሂዷል።
– በመጨረሻ ሁሉም አባቶች ተወያይተው ቤተክርስቲያንን የሚጠቅመው ምንድነው ? የሚለው ላይ በመምከር ዛሬ ውሳኔ ተላልፏል።
– የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት እንዲካሄድ ተወስኗል። የመጀመሪያው ችግር ያለባቸው ሀገረ ስብከት የሚል ሲሆን አሁን 7 አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሟል እነሱ በሚያቀርቡት ጥናት ሹመት ይካሄዳል። የሹመቱ ቀን #ወደፊት ይገለፃል። ዋናው ነገር ለቤተክርስቲያን የሚጠቅመው የትኛው ነው ? የሚለውን የጉባኤው አባላት በሙሉ ተስማምቶ ፣ በአንድ ልብ፣ በአንድ ሃሳብ፣ በመነጋገር ውሳኔ ተላልፏል።
– ረቡዕ የማጠቃላይ መግለጫ በቅዱስ ፓትርያኩ ይሰጣል።
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ፦
” ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን፤ ምዕመናን በሙሉ ተጨንቃችኃል፤ አንዳንድ ጊዜ እውነት ነው ሌላ ጊዜ ወሬም ብዙ ይበዛል በዚህ ሚዲያ በበዛበት ዘመን በጣም ብዙ የተጨነቃችሁ ምዕመናን እንዳላችሁ እናውቃለን ፤ በእውነት እግዚአብሔርን እናመሰግናለን ግሩም የሆነ የትምህርት ጊዜ፣ ግሩም የሆነ የውይይት ጊዜ ፣ ቤተክርስቲያን ለይተን የምትፈልገው ምንድነው የሚለውን የተወያየንበት ጊዜ ነው እግዚአብሔርን እናመሰግናለን “
ህወሓት ከጊዜያዊ የትግራይ ክልል አስተዳደር ጋር ቅራኔ ውስጥ የገባ ምልክት የሚሰጥ መግለጫ አውጥቷል
የሚከተለው የመግለጫው ሙሉ ቃል ነው
የህወሓት ሊቀመንበር ለጋዜጠኞች የሰጡት መግለጫ
በዚህ ሳምንት በሁሉም ዞኖች የህወሓት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መድረኮች ተካሂደዋል ይህ መድረክ በዋናነት የፓርቲያችን ካድሬዎች መድረክ ነው።
የመድረኩ ቁጥር አንድ አላማ የፓርቲውን አቅም ከላይ እስከ ታች በማንቀሳቀስ ጊዜያዊ አስተዳደሩ የሚሰጣቸውን ተግባራት ከዳር ለማድረስ ነው። ይህ ለጊዜያዊ አስተዳደር የተተወ ሳይሆን የወያኔ ተግባር ነው። በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ተግባራዊ እየተደረገ በመሆኑ በትግራይ በኩል ህወሀት ፈራሚ ነው። ስለዚህ ኃላፊነት አለበት ማለት ነው። የትግራይ ህዝብ መብት፣ የህዝብ አገልግሎት መጀመርም በዚህ ስምምነት መረጋገጥ አለበት።
ሌላው ህወሓት ማድረግ ያለበት እና የፌደራሉ መንግስት በስምምነቱ መሰረት ማድረግ ያለበት ነው። ስለዚህ ተልእኳችንን መወጣት አለብን እና የግዚያዊ አስተዳደሩ ተግባራት እና ግቦች ስኬት ወይም ውድቀት ጉዳይ የራሱ ተልእኮ ቢኖረውም ብቻውን የሚተው አይደለም። የግዚያዊ አስተዳደር ተግባራትና ግቦች ስኬትም ሆነ ውድቀት የህወሓት ሃላፊነት ነው። ህዝቡም ሆነ ሌላ አካል የሚጠይቀው ወያኔን ነው። ይህ ስምምነት አለም አቀፍ ስምምነት ሲሆን አለም አቀፉ ማህበረሰብ እየተከተለው ነው እንጂ የሀገር ውስጥ እና የሀገር ውስጥ ጉዳይ አይደለም።
“ፕሬዚደንት ሙስጠፌ ሰው በደሙ ሳይሆን በሰውነቱ የሚታይበት ራዕይ ለኢትዮጵያ አምጥቷል፤ ወደፊት የኢትዮጵያ መሪ ይሆናል ብዬም አምናለሁ” – ዶ/ር ጎርሴ ኢስማኢል
ዶ/ር ጎርሴ ኢስማኢል – የኢትዮጵያ ሶማሌ ዲሞክራሲያዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም በሶማሌ ሪጂን የተካሄደው የሁለት ዓመታት የለውጥ ሂደት ስላስገኛቸው ስኬቶችና ገጥመውት ስላሉት ተግዳሮቶች ይናገራሉ።
https://www.sbs.com.au/language/amharic/am/podcast-episode/interview-with-dr-gorse-ismail-somali-regional-state/ga0v8nlt7
ቅ/ሲኖዶስ በወታደር ከበባ ውስጥ|| ጳጳሳትን ለማባበል እየተሞከረ ነው|| የጳጳሳት ምርጫ|| የማ/ቅዱሳን ሚዲያ መዘጋት ምሥጢር

ጋምቤላ 10 ሰዎች ሲገደሉ 12 ሰዎች ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ቅዳሜ ዕለት ከደቡብ ሱዳን በመነሳት የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው ወደ ጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን የገቡ የ ” ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ” 10 ሰዎችን ገድለው 12 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ማድረሳቸውን ከጋምቤላ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ታጣቂዎቹ ቅዳሜ ምሽት 3 ሰዓት ተኩል ገደማ ድንበር ጥሰው በመግባት በማኩዌይ ወረዳ ቢልኬች ቀበሌ እንዲሁም በዋንቱዋ ወረዳ መተሀር ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በፈፀሙት ጥቃት በአጠቃላይ 10 ሰዎችን ገድለው ፤ 12 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት አድርሰዋል።
በጥቃቱ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች ወደ ጋምቤላ ጠቅላላ ሆስፒታል ለህክምና የተላኩ ሲሆን ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች ደግሞ በኝንኛንግ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተነግሯል።
ከጥቃቱ በኃላ በጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ቴንኩዌይ ጆክ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በኑዌር ዞን በሙርሌ ጥቃት የደረሰባቸውን ዜጎች ምልከታ አድርጓል።
አቶ ቴንኩዌይ ጆክ ፤ በተደጋጋሚ ወቅትና ጊዜ እየጠበቁ ጥቃት የሚሰነዝሩት የደቡብ ሱዳን የሙርሌ ታጣቂዎች፣ ትቅዳሜ ምሽት ድንገተኛ ተኩስ በመክፈት ነው ጥቃቱን ያደረሱት ብለዋል።
የክልሉ መንግስት ጥቃት አድራሾችን ተከታትሎ ለማደን ጥረት እያደረገ ነው ያሉ ሲሆን ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይፈፀም የተጠናከረ ጥበቃ ይደረጋል ብለዋል።
የክልሉ መንግስት በጥቃቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስረድተዋል።
ከዚህ ቀደምም እነዚሁ ድንበር ጥሰው የሚገቡ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በኑዌር ዞንና አኙዋ ዞኖች ገብተው የተለያዩ ጥቃቶችን
++++++++++++++++++++++++++++++
“በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነው ዓለማዊ አጀንዳ ቢያራምዱም በከፍተኛ ትዕግስት ስናልፋቸው የነበሩ አባቶች ዛሬም ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ቤተክርስቲያንን ሲገፉ በዝምታ የምናይበት ሂደት አይኖርም፡፡”
++++++++++++++++++++++++++++++
ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግርን ለመቅረፍ በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው ዐብይ ኮሚቴ በኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደት ላይ መግለጫ አወጣ።
በአለፉት ሁለት ሦስት ቀናት በአባቶች ዘንድ ውይይት ተደርጎበት ስምምነት ላይ ሳይደረስበት የቀረው የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደትን አስመልክቶ በተደረገው ውይይት ላይ በአባቶች የተፈጠረው የሐሳብ መከፋፈልና አለመግባባት ሁኔታ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ለኮሚቴው በእጅጉ እያሳሰበው ይገኛል ሲል ከ10 በላይ ማኅበራትን የወከለው ኮሚቴው በመግለጫው ጠቅሷል።
በየጊዜው በሚነሱ ወሳኝ የቅድስት ቤተክርስቲያን አጀንዳዎች ውስጥ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ጀርባቸውን የሚሰጡ፣ በቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ዓለማዊ አጀንዳ የሚያራምዱና ከዛሬ ነገ የቤተክርስቲያንን ፍቅርና ምህረት ተረድተው ወደልባቸው ይመለሳሉ በማለት በከፍተኛ ትዕግስት ስናልፋቸው የነበሩ አባቶች ዛሬም ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ቤተክርስቲያንን ሲገፉ በዝምታ የምናይበት ሂደት አይኖርም ያለው ኮሚቴው
በዚህ ታሪካዊ ወቅት ለቅድስት ቤተክርስቲያን መቆም ሲገባችሁ እየሰማችሁ እንዳልሰማችሁ ሆናችሁ በዝምታ የምትመለከቱ አባቶችም ሆነ ዋነኛ የችግሩ አካላት የሆናችሁ አባቶች በእግዚአብሔርም በታሪክም በእኛም በልጆቻችሁ የሚያስጠይቃችሁ መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን ሲል አፅንዖት ሰጥቷል።
ቤተክርስቲያን ከማይጠፋ ዘር በክርስቶስ ደም የተመሠረተች እንጂ እንደ ፖለቲካ ምክር ቤት በዘር በጎሣ የተመሠረተች አይደለችም። ቤተክርስቲያን የሁሉም ለሁሉም ነች ያለው ዐብይ ኮሚቴው ዛሬ በወከባና በጫና ለተለየ ብሔርና ጎሣ ተለይቶ የኢጲስ ቆጶስ ሲመት ቢሰጥ ነገ በዚህ ሰበብ ቤተክርስቲያንን ለመከፋፈል ዘርና ቋንቋን መሠረት አድርጎ