Home › View all posts by Konjit Sitotaw
Blog Archives
ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ ዛሬ ጠዋት ከቤተሰብ እና ጠበቃው ጋር መገናኘቱ ተገለጸ
ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ “እብደት በሕብረት” የተሰኘ የአንድ ሰው ቴአትሩን ለማሳየት ወደ እስራኤል አገር ሊጓዝ ሲል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት በፖሊሶች መያዙ ይታወሳል።
በአዲስ አበባ ፖሊስ መምሪያ ውስጥ ታስሮ የሚገኘው ተዋናዩ የቅርብ ወዳጅ የሆነው ያሬድ ሹመቴ እንደገለጸው አማኑኤል ሃብታሙ “እጁ ከተያዘበት ሰዓት አንስቶ የተከሳሽነት ቃል ሳይሰጥ እንዲሁ በእስር ላይ” እንደሚገኝ ቤተሰቦቹን ዋቢ አድርጎ ጽፏል።
ይኹን እንጂ የቤተሰብ ጠበቃ የማግኘት መብቱ ተጠብቆለት ከቤተሰብ እና ከጠበቃ ጋር ዛሬ ጠዋት ሊገናኝ መቻሉን እና “በመልካም” ሁኔታ ላይ መኾኑ ተመልካቷል።
በሕጉ መሰረት ወደ ቀጣይ ሕጋዊ ሂደቶች ለማምራት እስከ ነገ የሚሆነውን ለማየትም ቤተሰቦቹ እየተጠባበቁ ነው ተብሏል።
እያዩ ፈንገስ የአንድ ሰው ቴያትር ‘ቧለቲካ’ የተሰኘው ምዕራፉ ለዕይታ ከቀረበ ከእጭር ጊዜ በኋላ ማለትም ከጥር 2 ቀን 2016 ጀምሮ የመንግስት የፀጥታ አካላት ለዓለም ሲኒማ የስራ ሀላፊዎች ባስተላለፉት ትእዛዝ ለህዝብ እንዳይታይ መከልከሉ አይዘነጋም።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከ ‘ ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ‘ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።
በቃለምልልሱ ፥ ባለፉት ሳምንታት በአማራ እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች የነበረው ግጭት በ ” የሚሊሻ አባላት ” መካከል እንጂ መደበኛ ኃይሎች የተሳተፉበት አልነበረም ብለዋል።
” አማራ ክልል በኩል የነበሩ ሚሊሻዎች የተለያዩ አስጊ እንቅስቃሴያዎችን ሲያደርጉ ነበር። በእኛ በኩል ያሉ የሚሊሻ አባላት ምላሽ ሰጥተዋል ” ሲሉ ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ያወጣውን መግለጫም ” መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያላገናዘበ ” ብለዋል።
የሰላም ስምምነቱ ተፈጻሚ እንዳይሆን እያደረገ ያለው ” ሕጋዊ የልሆነ የአማራ አስተዳደር ነው ” ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ጌታቸው በዚሁ ቃለ ምልልስ ፥ በሰላም ስምምነቱ መሰረት በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉትን ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ከስምምነት መደረሱን አስታውሰዋል።
” ሕጋዊ ያልሆኑ አስተዳደሮችን ለማፍረስ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር አብረን እየሠራን ነው። ከአማራ ክልል ጋርም ቢሆን በተወሰነ ደረጃ አብረን እየሠራን ነው ” ብለዋል።
” የፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚሹ አካላት እንዳሉ ግን በጣም እርግጠኞች ነን ” ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ጌታቸው እነዚህ አካላት እነማን እነደሆኑ በግልጽ በስም ጠርተው አልጠቀሱም።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ የኾኑትን ቀሲስ በላይ መኮንንን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ 8 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን የአገር ውስጥ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
የቀሲስ በላይ መኮንን እና ተጠርጣሪ ግብረ አበሮቻቸው ጠበቆች፣ ፖሊስ ዋስትና ለማስከልከል ያቀረባቸው ምክንያቶች አሳማኝ አይደሉም በማለት ተከራክረው እንደነበር ዘገባዎቹ አመልክተዋል።
ፖሊስ ካኹን ቀደም በተሰጠው የ7 ቀን የምርመራ ጊዜ፣ በወቅቱ የነበረ የካሜራ ቅጂ ከአፍሪካ ኅብረት መጠየቁን፣ ለወንጀል ተግባር የዋለ ተሽከርካሪ ማረጋገጫ ለማግኘት ለሚመለከተው አካል ጥያቄ ማቅረቡን፣ በተጠርጣሪው ኹለት መኖሪያ ቤቶች ላይ ብርበራ ማድረጉንና በብርበራ የተገኘ አንድ የጦር መሳሪያ ሕጋዊነቱን የማረጋገጥ ሥራ እየሰራ መኾኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል ተብሏል።
ቀሲስ በላይ ከሳምንት በፊት በቁጥጥር ስር የዋሉት፣ ከአፍሪካ ኅብረት የባንክ አካውንት በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በሐሰተኛ ሰነዶች ለማውጣት ሞክረዋል ተብለው ተጠርጥረው እንደኾነ አይዘነጋም።
ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራዊ ምክክር ላይ በአጀንዳነት የሚቀርቡ ጉዳዮችን እንዲያዘጋጁ ተጠየቁ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ በሀገራዊ ምክክር ላይ “አጀንዳ ሊሆኑ ይገባሉ” የሚሏቸውን ጉዳዮች እንዲያዘጋጁ ለተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በደብዳቤ ጥሪ አቀረበ። የፖለቲካ ፓርቲዎቹ በሚያቀርቧቸው አጀንዳዎች ላይ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት እና የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት የሚያካሄዱበትን ሁኔታ እንደሚመቻች ኮሚሽኑ አስታውቋል።
“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው እና ባለፈው ሳምንት ለተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተላከው ደብዳቤ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከባለድርሻ አካላት “አጀንዳዎችን የመሰብሰብ ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ” ጠቅሷል። በዚህም መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎቹ “ለሀገራዊ ምክክር ሊቀርብ ይገባል” የሚሏቸውን “የአጀንዳ ነጥቦች” የማዘጋጀት ስራ እንዲያከናውኑ ኮሚሽኑ በደብዳቤው ጠይቋል።
በታህሳስ 2014 ዓ.ም. በጸደቀው የኮሚሽኑ የማቋቋሚያ አዋጅ፤ የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ “በተለያዩ የፖለቲካ እና የሃሳብ መሪዎች፣ በመንግስት እንዲሁም በህብረተሰብ ክፍሎች መካከል፤ ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ያሉ ልዩነቶችን ወይም የአለመግባባት መንስኤዎችን በትክክል የሚዳስሱ ጉዳዮች” መሆናቸውን አስቀምጧል። ኮሚሽኑ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የሚቀርቡለትን እነዚህን አጀንዳዎች ካደራጀ በኋላ ውይይቶች የሚካሄዱባቸውን ርዕሰ ጉዳዮች የመለየት ሚናም በአዋጁ ተሰጥቶታል።
* ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13001/
የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤቱ ያስቀመጣቸው መፍትሔዎች “በሙሉ” በገዢው ፓርቲ የተያዙ ናቸው አለ
በኢትዮጵያ ውስጥ የትጥቅ ትግል እያደረገ የሚገኘው እና በአገሪቱ ፓርላማ “አሸባሪ” ተብሎ የተፈረጀው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነሠ) ዛሬ ረፋድ የብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት ለአገሪቱ ስብራት ያስቀመጣቸው መፍትሔዎች በሙሉ በገዢው ፓርቲ አለ።
አዲስ ማለዳ ከድርጅቱ ይፋዊ የኤክስ ገጽ እንደተመለከተችው “የብልጽግና ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት” የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ እና ለትውልድ የተሸጋገሩ ቀውሶች ለመፍታት ፍኖተ ካርታውን “አሳትሟል” በማለት ገልጿል።
የብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤቱ በመግለጫው “የታሪክ ስብራቶቹን” ለመጠገን ፖለቲካዊ ችግሮችን በአገራዊ ምክክር፤ እንዲሁም በሽግግር ፍትሕ እና በተሐድሶ ለመጠገን መስራት እንደሚገባ መግለጹን አዲስ ማለዳ ዘግባ ነበር።
ታጣቂ ቡድኑ “ሦስቱም ሂደቶች ሙሉ በሙሉ በገዢው አካል ባለቤትነት የተያዙ እና በጥቃቅን የሚተዳደሩ ናቸው” ማለቱን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልታለች። “እንደ የሽግግር ፍትህ እና ብሔራዊ ውይይት ያሉ የቃላት ቃላቶችም ሕዝቡን ለማደናገር እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እጅ መንሻ ነው” ሲል የኦርሞ ነጻነት ግንባር አስታውቋል።
ተጨማሪ ያንብቡ https://addismaleda.com/archives/36504
ከትዕግሥት በኋላ የሚከሠት “ሕግ የማስከበር ሥራ” ያለውን አስከፊ ውጤት “ከቅርቡ ታሪካችን ልንማር ይገባል”- ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት
👉🏿 በትግራይ ክልል ያለው የልማት ስራ “መንግሥታዊ ኃላፊነት እንጂ ፍርሃት” አይደለም ተብሏል
ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ከተመካከረ በኋላ ባወጣው መግለጫ “በስምምነቱ መሠረት የህሐት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው” ብሎ “የማንነት እና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄ ያለባቸውን አካባቢዎች ጉዳይ እልባት ለመስጠት እንዲቻል የተቀመጠው አቅጣጫ ተግባራዊ መደረግ አለበት” ሲል አስታውቋል።
መንግስት “እንቅስቃሴያቸው ሕገ ወጥ ስለሆነ ብቻ ጉዳዩን በጉልበት ብቻ ይፈታ ማለት እንደሌለበት ይገነዘባል”… https://addismaleda.com/archives/36504
ህ.ወ.ሓ.ት ከብልጽግና ፓርቲ ጋር ለመቀላቀል ውይይት አላደረግኩም፤ መሰረታዊ ልዩነቶችም አሉን ሲል ገለጸ
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከብልጽግና ፓርቲ ጋር “ለመቀላልቀል” ውይይት አላደረግኩም ሲል አስታወቀ።
የህወሓት እና የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች እያደረጉ የሚገኙት ውይይት “ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ የተፈጠረውን አንፃራዊ ሰላም ለማስፋት እና ለማጠናከር ያለመ ነው” ሲል ድርጅቱ ትላንት እና ዛሬ እየወጡ የሚገኙ ዘገባዎችን ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ ማስተባበሉን ተመልክተናል።
ህወሓት እና ብልጽግና ፓርቲ ለመዋሀድ ተከታታይ ውይይትና ድርድር እያደረጉ ይገኛሉ የሚሉ ዘገባዎች መውጣታቸው ይታወሳል።
አዲስ ማለዳ ከህወሓት አጭር መረጃ እንደተመለከተችው “ህወሓት እና ብልጽግና መሰረታዊ የዓላማ እና የአስተሳሰብ ልዩነት ያላቸው ፓርቲዎች ናቸው” በማለት በይፋዊ ገጹ ሰፍሯል።
ይኹን እንጁ ልዩነቶቹ እንዳሉ ሆኖ ሁለቱ ፓርቲዎች ሊወያዩባቸው የሚገቡ ብዙ አጀንዳዎች በመኖራቸው ተከታታይ ውይይት ተጀምሯል ተብሏል።
“ከዚህ ባለፈ ግን ህወሓት ከብልጽግና ጋር ለመቀላቀል ንግግሮች ተጀምረዋል የሚለው መረጃ ሙሉ በሙሉ ከእውነት የራቀ ነው” ሲል ድርጅቱ ማስታወቁን አይተናል
ሕወሓት ገዥውን ፓርቲ ብልፅግና ለመቀላቀል ተከታታይ ድርድሮች እያደረገ ነው በሚሉት ዘገባዎች የሕወሓት ሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል በአዲስ አበባ ተገኝተው ይህን ድርድር መጀመራቸው እና ከሁለት ሳምንታት በኋላ የብልፅግና ምክትል ሊቀ መንበር አደም ፋራህ ወደ መቀሌ ተጉዘው ድርድሩን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
እነዚሁ ዘገባዎች በህወሓት ውስጥ ብልፅግናን መቀላቀል “ስህተት ነው” በሚሉ እና “ውህደቱ ለትግራይ ችግሮች መፍትሄ ለማምጣት ጠቀሜታ አለው” በሚሉት ሃሳቦች መከፋፈል መኖሩን የጠቆሙ ቢሆንም ህወሓት ጉዳዩን ሙሉ በሙሉ አስተባብሏል።
16 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በጀልባ መገልበጥ ሲሞቱ 28ቱ የደረሱበት አልታወቀም- በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
👉🏿 ከ2 ሳምንታት በፊት 38 ኢትዮጵያውያን መሞታቸው ይታወሳል
ትላንት ምሽቱን ከየመን የባህር ዳርቻ ልዩ ስሙ ‘አራ’ የተባለ ስፍራ 77 ኢትዮጵያውያን ሕገ ወጥ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ ጅቡቲ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ በመገለብጧ 16 ኢትዮጵያዉያን መሞታቸው ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ኤምባሲ በጅቡቲ እንዳስታወቀው ጀልባዋ ‘ጎዶሪያ’ በሚባል አካባቢ በደረሰባት የመገልበጥ አደጋ የ5 ሕፃናት እና ሴቶችን ጨምሮ 16 ዜጎች ሕይወታቸው አልፏል። ይህ መረጃ እስወጣበት ጊዜ ድረስ አብረው ተሳፍረው የነበሩ 28 ፍልሰተኞችን ማግኘት አልተቻለም።
33 ፍልሰተኞች ደግሞ በሕይወት ተርፈው ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደሆነ አዲስ ማለዳ ከኤምባሲው ያገኘችው መረጃ ያመለክታል።
ኤምባሲው ከጅቡቲ ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት የሚደረገው ህገ ወጥ ጉዞ እጅግ አደገኛ ከመሆኑም በላይ በየጊዜው የዜጎቻችንን ሕይወት እያሳጣ እንደሚገኝና አሳስቧል።
የፍትህ አካላት “ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ” ሲል ጥሪውን አስተላልፏል።
ከ2 ሳምንታት በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ ከጅቡቲ የባህር ዳርቻ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ የመን በመጓዝ ላይ የነበረች ጀልባ በመስጠሟ የ38 ፍልሰተኛ ኢትዮጵያውያን ሕይወት ማለፉ አይዘነጋም።
ኢሠማኮ፣ ዘንድሮ ሚያዝያ 23 ቀን በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ሠራተኞች ቀን በአዳራሽ ውስጥ ብቻ እንዲከበር መወሰኑን አስታውቋል።
ኢሠማኮ፣ በበዓሉ የአከባበር ሁኔታ ላይ እዚህ ውሳኔ ላይ የትደረሰው፣ “የአገሪቱን አጠቃላይ ኹኔታ” እና “በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ” ሥር የሚገኙ አከባቢዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደኾነ ገልጧል።
ኾኖም ይህ የበዓሉ አከባበር፣ ባሕርዳር፣ ኮምቦልቻና በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚገኙ ከተሞችን እንደማይጨምር ኢሠመኮ አመልክቷል።
የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት፣ እስከ በዓሉ ድረስ ጠቅላይ ሚንስትሩ የሠራተኞችን ተወካዮች በሠራተኛው ጥያቄዎች ዙሪያ እንዲያነጋግሩ መወሰኑንና ጥያቄው ለጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት መቅረቡን ኢሠማኮ ጨምሮ ገልጧል።
አማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረ ጃርሶ ወረዳ ከአማራ ክልል በተነሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ባለፈው ሳምንት ዓርብ በርካታ ሰዎችን አፍኖ መውሰዱን ዋዜማ በስፍራው ካሉ ምንጮቿ ሰምታለች።
አማጺው ቡድን እገታውን የፈጸመው፣ በጎሃጽዮን እና ቱሉ ሚልኪ ከተሞች መሃል ባለች ቢቱ ወንዝ ተብላ በምትጠራ ሥፍራ እንደሆነ ምንጮች ተናግረዋል።
እገታው የተፈጸመው፣ መነሻውን ከምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ ባደረገው በተልምዶ “ታታ” ተብሎ በሚጠራ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ እና በሦስት ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ሲጓዙ በነበሩ መንገደኞች ላይ እንደኾነ ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ፣ ታፍነው የተወሰዱት ሰዎች በታጣቂ ቡድኑ ቁጥጥር ስር መኾናቸውንም ዋዜማ ባደረገችው ማጣራት መረዳት ችላለች።
ህወሓት ብልጽግናን ለመቀላቀል እየተደራደረ መሆኑ ተሰማ
ህወሓት ከአራት ዓመት በፊት “ሕገወጥ ነው” ያለውን ገዥውን ፓርቲ ብልጽግና ለመቀላቀል ተከታታይ ድርድሮች እያደረገ መሆኑ ተሰምቷል።
ከኹለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የተፈረሙት ህወሓት እና ገዥው ፓርቲ ብልጽግና ውህደት ለመፍጠር ድርድር እያደጉ መሆኑን ዋዜማ ራዲዮ ዘግባለች።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በሊቀመንበርነት የሚመሩትን ብልጽግናን በመቀላቀል ህወሓት ለመቀላቀል ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡን ዘገባው አመለክቷል፡፡
ከብልጽግና በፊት የነበረው ኢሕአዴግ እኩል የሥራ አስፈፃሚና ማዕከላዊ ኮሚቴ ውክልና ያላቸው አራት ንዑስ ፓርቲዎች ጥምረት ሲሆን፣ ብልጽግና ግን አንድ ወጥ ፓርቲ ነው። የብልጽግና የፓርቲ ውክልና በህዝብ ብዛት የሚወሰን እንጂ እንደ ኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች እኩል ውክልና አይኖራቸውም።
አሁን እየተደረገ ባለው ድርድር ህወሓት እና የብልጽግና ፓርቲ ሕገ-ደንብ ተሻሽሎ በፓርቲ ውስጥ አባል ድርጅቶች እኩል የማዕከላዊ ኮሚቴና የሥራ አስፈፃሚ ውክልና እንዲኖራቸው ይፈልጋል ተብሏል። ብልጽግና ግን ህወሓት የተናጠል ህልውናውን አክስሞ ብልፅግናን እንዲቀላቀልና ውክልናውም በትግራይ ህዝብ ቁጥር ልክ የሚወሰን መሆኑን ይገልጻል።
የህወሓት ሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል በአዲስ አበባ ተገኝተው ይህን ድርድር የጀመሩት ሲሆን፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ የብልጽግና ምክትል ሊቀመንበር አደም ፋራህ ወደ መቀሌ ተጉዘው በጉዳዩ ላይ በስፋት መነጋገራቸው ተገልጿል።
በህወሓት በኩል ብልጽግናን መቀላቀል “ስህተት ነው፣ አስፈላጊም አይደለም” ብለው የሚያምኑ አመራሮች መኖራቸው ተመላክቷል፡፡ አበንጻሩ “ውህደቱ ለትግራይ ችግሮች መፍትሄ ለማምጣት ጠቀሜታ አለው፣ በተለይም የትግራይን ጸጥታና ደህንነት ለመስጠበቅ ከብልጽግና ጋር አብሮ መቆም አስፈላጊ ነው” ብለው የሚያምኑ መኖራቸውንም ዘገባው አመላክቷል።
ዋዜማ– የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ ከአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም ፊት ለፊት ለኮሪደር ልማት በሚል የፈረሱ ሰፈሮችን ጨምሮ ከ250 በላይ በሚሆኑ ቦታዎች ላይ የሊዝ ጨረታ ማውጣቱን ዋዜማ ከተመለከተችው የጨረታው ሰነድ ተረድታለች።
የሊዝ ጨረታው ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ውጭ በተቀሩት የከተማው አስር ክፍለ ከተሞች ባሉ ቦታዎች ላይ ወጥቷል። የሊዝ ጨረታው ለአመታት ከተቋረጠ በኋላ ሲወጣ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
የጨረታው ሰነድም ከረቡዕ ሚያዝያ 9 2016 አ.ም ጀምሮ መሸጥ የተጀመረ ሲሆን ፣ የሰነድ ሽያጩ እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2016 አ.ም ድረስ እንደሚቀጥል ተነግሯል።
ለሊዝ የቀረበ ከፍተኛ ቦታ ያቀረበው ክፍለ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ሲሆን ቦሌ እና ቂርቆስ ክፍለ ከተሞች አንድ አንድ ቦታ ለሊዝ ጨረታ ቀርቦባቸዋል።
በኮሪደር ልማት በፈረሰው የአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም አካባቢ 22 ቦታዎች ለሊዝ ጨረታ ቀርበዋል። በዚህ አካባቢ ትልቁ ለሊዝ የቀረበው ቦታ 2,179 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን ፣ ዝቅተኛ ስፋት ያለው መሬት ደግሞ 650 ካሬ ሜትር ነው።
በደረጃ አንድ ለተመደቡት ለ22ቱም ቦታዎች የሊዝ መነሻ ዋጋ በካሬ 2,213.25 ብር ተቆርጦላቸዋል። ለአንድ ካሬ ከፍተኛ መነሻ ዋጋ የተቆረጠላቸውም እነዚሁ በአራዳ ክፍለ ከተማ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም አቅራቢያ ላሉት ቦታዎች ነው።ንፋስ ስልክ ላፍቶ ከፍለ ከተማ በመጠን ብዙ (ከ150 በላይ ቦታዎችን) በማቅረብ ቀዳሚው ነው።
የጨረታ ሰነዱ 2,300 ብር እየተሸጠ ሲሆን ፣ ጨረታው
” የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል ”
ሰሞኑን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪ የምግብ አገልግሎት ጋር ተያይዞ ፤ ” የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል ያለውን ብሉ ” አይነት ማስታዎቂያዎች መለጠፋቸውን ተከትሎ በበርካቶችን አነጋግሯል።
ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የተለጠፉ ማስታወቂያዎች ምንድነው የሚሉት ?
– ” እንደ ሀገር የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል። የምግብ ጥሬ ዕቃ ዋጋም በየቀኑ ከመጨመሩ ጋር በተያያዘ የተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት ተቆጥሯል። ”
– ” ተቋማችን የሚያደርገው ድጎማ ተማሪዎቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ ባሉን የምግብ ጥሬ እቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ቢሆንም በአሁን ሰዓት እጅግ በጣም እየከበደ ስለሆነ የሜኑ ማሻሻያ ለማድረግ ተገደናል። ”
– ” ከአሁን በኃላ የተሻሻለው ሜኑ ተግባራዊ ይሆናል። ”
– ” በተወሰኑ በስቶራችን ውስጥ ባሉ የምግብ ጥሬ ዕቃዎች እና በአትክልት የምግብ አገልግሎት እየሰጠን ነው። በአስቸኳይ የምግብ ጥሬ ዕቃ ግዥ አቅርቦት እንዲሟላ ጠይቀናል እስከዛ ታገሱ። ”
… ይላሉ ማስታወቂያዎቹ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ በዲላ እንዲሁም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ካሉ የቤተሰቡ አባላት ማህተም ያረፈባቸውን ማስታወቂያዎች ተልኮለት ተመልክቷል።
ይህ ነገር የቤተሰብ የጭንቀት ምንጭ ከመሆኑ በላይ ፦
° ዩኒቨርሲቲን የሚያክል እጅግ ትልቅ ተቋም እንዴት መጭውን የዋጋ ንረት እንዲሁም የዓመቱ የምግብ ወጪ ያላገናዘበ በጀት ይይዛል ?
° ለረጅም ዓመታት ለተማሪ በቀን የሚመደበው ገንዘብ አነስተኛ ሆኖ ሳለ እንዴት ይህ ሊፈጠር ቻለ ? የሚሉና ሌሎች ነቀፌታዎች ተሰምተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ” የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል ” የሚል ማስታወቂያ ከተለጠፈባቸው ተቋማት
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ዛሬ ባወጣው ሪፖርት 29,000 ሰዎች ከአላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች ከቤታቸው ተፈናቅለው ፦
° በቆቦ / በሰሜን ወሎ
° ሰቆጣ / በዋግኽምራ በሚገኙ መጠለያዎች መጠለላቸውን ገልጿል።
23,000 ሰዎች ወደ ቆቦ ሰሜን ወሎ እንዲሁም 5,980 ሰዎች ወደ ሰቆጣ ዋግኽምራ ዞን ነው የተፈናቀሉት።
በአካባቢው ያለው ሁኔታ ሲታይ የተፈናቃዮች ቁጥር ከዚህ ሊጨምር እንደሚችል አመልክቷል።
ከተፈናቀሉት ዜጎች በዋነኝነት 70 በመቶዎቹ ህጻናትና ሴቶች ሲሆኑ ቀሩት ደግሞ አዛውንቶችና ታዳጊዎች ናቸው።
እንደ UN OCHA ሪፖርት ፦
🔘 ተፈናቃዮች ባሉበት ከበድ ያለ #የምግብ እና የውሃ እጥረት በመኖሩ አስቸኳይ የሆነ የህይወት አድን እርዳታ ያስፈልጋል።
🔘 ክፍት በሆኑ ቦታዎች ላይ የተጠለሉ ቤተሰቦች አስቸኳይ መጠለያ ያስፈልጋቸዋል።
ኦቻ ድጋፍ በሚያደርጉ አጋር_አካላት የግብዓት እጥረት ምክንያት በጣም ተጋላጭ ለሆኑት የምግብ እና ውሃ ድጋፍ እየተደረገ ያለው መደበኛ ባልሆነ መንገድ በህብረተሰቡ ነው ብሏል።
ተጨማሪ ፦
🛑 እስከ ትላንት ድረስ በራያ አላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች ላይ አንዳንድ መጠነኛ ግጭቶች መከሰታቸውን ቢቀጥልም በአላማጣ ፣ ቆቦ ፣ ወልዲያ ከተሞች የጸጥታ ሁኔታው የተረጋጋ ነው።
⭕️ በአላማጣ እና በቆቦ መካከል ያለው መንገድ ተከፍቶ የንግድ ትራንስፖርት የቀጠለ ሲሆን እንደ ባንኮች ያሉ የህዝብ አገልግሎቶች ቀስ በቀስ ቀጥለዋል።
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ብድር ለማግኘት ድርድር ላይ ናት።
እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከ2020 ጀምሮ ምንም ፈንድ ያላገኘችው ኢትዮጵያ ብድር እንዲለቀቅላት ከIMF ተከታታይ ድርድሮች እያካሄደች ነው።
ከIMF 3.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንደጠየቀች ተነግሯል።
ድርጅቱ ብደሩን ለመስጠት ኢትዮጵያ ብር ከዶላር አንጻር ያለው የመግዛት አቅም እንዲዳከም ማድረግ እንዳለባት እንደጠየቀ ተጠቁሟል።
ግን ይህ እንደቅድመ ሁኔታ ይቀመጥ አይቀመጥ ድርጅቱ ማረጋገጫ አልሰጠም። ነገር ግን ተለዋዋጭ የሆነ የገበያ ሁኔታ የሚወስን የውጭ ምንዛሬ ተመን መኖር እንዳለበት እንደሚያምን ሮይተርስ አስነብቧል።
ምንም እንኳን እየተካሄዱ ባሉ ተከታታይ ድርድሮች በኢትዮጵያ እና IMF መካከል ልዩነቶች ቢኖሩም ስምምነት ላይ የመድረስ ተስፋ እንዳለ የIMF የኢትዮጵያ ልዑክ አልቫሮ ፒርስ ተናግረዋል።
ፒስርስ ፥ ” አሁንም ልዩነቶች ቢኖሩም ድርድር ግን ቀጥሏል። አስቸጋሪ ነግሮች ቢኖሩም ስምምነት ላይ የመድረሱ ተስፋ አለ ” ብለዋል።
የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሪፎርም መደገፍ ላይ በአብዛኛው ስምምነት እንዳለ ነው የተሰማው።
ከዶላር አንጻር የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም ከፍተኛ በሆነ የዋጋ ንረት እየተፈተነች ላለችው ኢትዮጵያ ይበልጥ ፈተና ሊሆንባት ይችላል።
ግን ደግሞ IMF የግዴታ ያ ካልተደረገ ብድር አለቀም ካለ ኢትዮጵያ በከፍተኛ ውጭ ምንዛሬ እጥረት ውስጥ የምትገኝ በመሆኑ ሌላ አማራጭ ላይኖራት ይችላል የሚሉ አሉ።
ከቀናት በፊት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ እና የብሄራዊ ባንክ ገዢው ማሞ ምህረቱ በተገኙበት ከIMF ኃላፊ ክሪስታሊያ ጆርጂያ ጋር ተገናኝተው መክረው ነበር።
ምክክሩ IMF በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሪፎርም በሚደግፍበት መንገድ ላይ ያተኮረ እንደሆነ
የዓለም ጤና ድርጅት “ጆንሰን ኤንድ ጄንሰን” በተባለው የሕጻናት ሲረፕ መድኃኒት ላይ የጤና ማስጠንቀቂያ ሊያወጣ እንደሚችል መናገሩን ሮይተርስ ዘግቧል።
ድርጅቱ ይህን የገለጠው፣ ናይጀሪያ “ቤኒሊን” በተሰኘው የ”ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን” የሲረፕ ዓይነት ላይ መርዛማ ንጥረ ነገሮችን አግኝቼበታለኹ በማለት ባለፈው ሳምንት ክትባቱን ማገዷን ተከትሎ ነው።
መርዛማው ንጥረ ነገር፣ በጋምቢያ፣ ካሚሮን፣ ኢንዶኔዥያና ኡዝቤኪስታን ከዓመት በፊት ለ300 ሕጻናት ሞት ምክንያት እንደኾነ ዘገባው አስታውሷል።
መርዛማ ንጥረ ነገር የተገኘበት ሲረፕ፣ “ጆንሰን ኤንድ ጆንሰን” ኩባንያ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ያመረተው ነው።
የቡድን ሰባት ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፤ በኢትዮጵያ ያሉ “ውጥረቶች” እንደሚያሳስቧቸው ገለጹ
የቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ይታያሉ ያሏቸው፤ “የማያቋርጡ እና ኃይለኛ ውጥረቶች” እንደሚያሳስቧቸው ገለጹ። በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ይፈጸማሉ የሚባሉ “የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እና በደሎች ሪፖርቶች”፣ “ብርቱ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ” እና “የምግብ ዋስትና እጦት መስፋፋት” እንዳሰጋቸውም አስታውቀዋል።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በኢትዮጵያ ጉዳይ ስጋታቸውን ያንጸባረቁት፤ በጣልያኗ ካፕሪ ደሴት ያካሄዱትን ስብሰባ ሲያጠናቅቁ ዛሬ አርብ ምሽት ባወጡት መግለጫ ነው። ሚኒስትሮቹ በዚሁ መግለጫቸው፤ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና በህወሓት መካከል በተፈረመው ግጭት የማቆም ስምምነት አተገባበር ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎችን በበጎ እንደሚቀበሉ ገልጸዋል።
በሰብዓዊ መብቶች እና በሲቪል ሰዎች ጥበቃ፣ ውጥረቶችን ለመፍታት በሚደረግ ፖለቲካዊ ውይይት፣ በዕርቅ፣ በብሔራዊ ውይይት፣ የሽግግር ፍትህ እና በግጭት ወቅት ወንጀል የፈጸሙ ተጠያቂ ለማድረግ፤ ተጨማሪ እና ዘላቂ እርምጃዎች ተግባራዊ እንዲደረጉ አበረታተዋል። በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመካሄድ ላይ በሚገኙ ግጭቶች የሚሳተፉ ወገኖች፤ በንግግር ሰላም ለማውረድ ተመሳሳይ ቁርጠኝነት እንዲኖራቸውም ጥሪ አቅርበዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር )
* ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/12978/
የአብይ አህመድ የመጨረሻ ካርድ
አማራ ክልልን ከወረረ ዘጠኝ ወር አስቆጥሯል ( ዶክተር መንግስቱ ሙሴ)
=================
አላማጣን ህወሓት ወረረ በሚል አዲስ ስልት ይዞ ብቅ አለ። ለመሆኑ ታደሰ ወረደ የአብይ አህመድ ሹመኛ አይደለም? ጌታቸው እረዳን ማን ሾመው? ነው ጻድቃን ሁሉም አብይ አህመድ የሾማቸው የብልጽግና ሹመኞች ናቸው። አዛዥ ናዛዣቸውም አብይ አህመድ ነው። ጎበዝ መላ የአማራ ሕዝብ በአብይ (ኦሮሙማ) ይፋዊ ወረራ ከተደረገበት እና የአብይ አህመድ ጦር ካወጀበት 9 ወር አስቆጥሯል። ይህን ወረራ የአማራ ሕዝብ በድል ሲወጣ ወልቃይትም እራያም ሰላም ይሆናል።
ይህ የእራያ እና የወልቃይት የጠለምት ጉዳይ የአብይ አህመድ የመጨረሻ ካርዱ እንጅ ጅማሮው አይደለም። ምንም መታለልም ሆነ መወናበድ ሊኖር አይገባም። አረመኔው አብይ አህመድ ይህን ካርድ የሳበው በአማራ ክልል ያስገባው ሰራዊት አቅሙ ማነሱ እና በመቸነፉ ነው። እንደ አለመታደል ሆኖ የትግራይ ልሂቃን በተለይ የተማረው እና ፊደል የቆጠረው አሁንም ለትግራይ ሕዝብ የክፉም የደግም ዘመናት ወንድም የሆነውን የአማራን ሕዝብ ህወሓት በ 1967 ተወልዳ በጠላትነት በመፈረጀችለት ቦይ እየፈሰሰ ለአብይ አህመድ የቁማር ካርድ ምቹ ሆኖለታል።
የትግራይ ልሂቃን አብሮ ኖሮ ሐገር አስከብሮ የኖረን ወንድማማች እህታማች ሕዝብን የለያየውን ከሞሶሎኒ፤ ከቱርክ ፓሻ እና ከግብጽ የተቀዳውን ህወሓታዊ እና ሰይጣናዊ የፖለቲካ አስተሳሰብ ተረድተው መለወጥ ባለመቻላቸው የጭንጋፉ እና የአረመኔው የአብይ አህመድ የመጫወቻ ካርድ መሆናቸው ዛሬም ከረፈደ አለመንቃት እና በትቂት ባንዶች የጥላቻ ሰንሰለት መያዝ አሁንም እስከወዲያኛውም የትግራይን ህዝብ ይጎዳል እንጅ አይጠቅምም።
ለማሳረጊያ ይህ በሰሜን የተቀሰቀሰው አራተኛው ዙር ጦርነት
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ የዶላር ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ፡፡
የፌደራል ፖሊስ መርማሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ከትናንት በስቲያ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ በአካል ቀርበው ሀሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመያዝ ለ3 ግለሰቦች እና ለአንድ የግል ድርጅት ሒሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሊያዘዋውሩ ሲሉ በአፍሪካ ህብረት ሴኪዩሪቲዎች ተይዘው ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ተላልፈው መሰጠታቸውን ጠቅሶ የጥርጣሬ መነሻውን ለችሎቱ አቅርቧል።
በዚህ መነሻ መሰረትም መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ሥራ ለማከናወን የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል። ተጠርጣሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ድርጊቱ መፈጸሙን አምነው፤ ይሁን እንጂ ወንጀል አለመፈጸማቸውን አስረድተዋል፡፡ ስለሆነም የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።
የግራ ቀኝ ክርክሩን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
በሌሎች ክልሎች ልዩ ኃይልና ታጣቂዎች ሲበተኑ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰጠው መብት ለአሁኑ ቀውስ መነሻ ነው- ኢዜማ
ባለፉት ጥቂት ቀናት በአላማጣ እና አከባቢው የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ታጣቂዎች “የኃይል እርምጃ እየወሰዱ” መሆኑን ተከትሎ መንግሥት “ጦርነት የሚጎስመውን የሕወሓት ስብስብ በፕሪቶሪያው ሥምምነት መሠረት ትጥቅ እንዲፈታ” በማድረግ ሕግ እና ሥርዓት እንዲያስከብር ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ አሳሰበ።
መግለጫው ቡድኑን [ህወሓት] ትጥቅ የማስፈታት ጉዳይ ዛሬም ቢሆን ከአጎራባች ክልሎች አልፎ ለአገር ሉዓላዊነት ጠንቅ ሊሆን እንደሚችል መታሰብ ይኖርበታል ብሏል።
መንግስት ቡድኑ በፈረመው ሥምምነት መሠረት በሰላሳ ቀናት ውስጥ መሣሪያ አስረክቦ ወደ ሰላም አስተሳሰብ እንዲመጣ ሊደረግ ሲገባ ይበልጥ እራሱን አደራጅቶ ዛሬም ንፁሀን ዜጎችን ለመከራ ለእንግልት እና ከቀያቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ እንዲወድቁ እያደረገ ይገኛል ሲል ኢዜማ ህወሓትን ተችቷል።
ኢ-ሕገ መንግስታዊ አደረጃጀት የነበረው የክልል ልዩ ኃየል ትጥቅ በማስፈታት መዋቅሩ እንዲፈርስ ሲደረግ፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅና የሌለው “ፓርቲ” ከመሆኑ ባሻገር “መሣሪያ የታጠቁ የራሱ ኃይሎች ያሉት ብቸኛ ስብስብ” ነው ሲል ኢዜማ መግለጹን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልክታለች።
በተለይ በሌሎች ክልሎች ያሉ ልዩ ኃይሎች እና ታጣቂዎች ሁሉ ፈርሰው ወጥ በሆነ የጸጥታ አመራር ሥር ሆነው እንዲንቀሳቀሱ ቢደረግም “ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ልዩ መብት በማጎናፀፍ በሌሎች ክልሎች በሌለ እና ፈጽሞ በማይታሰብ መልኩ ታጣቂ ኃይል የማሠማራት መብት በመሰጠቱ” አሁን በአማራ ክልል ያለው ቀውስ እንዲቀጣጠል መነሻ መሆኑን ጠቁሟል።
ሕወሓት አንዴ “ትጥቅ ፈትተናል” ሌላ ጊዜ ደግሞ “የምንፈልገውን
አማራ ክልል የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ለመለዮ ለባሾች በሙሉ በማለት በለጠፈው ማስታወቂያ መሰረት የታጠቁት መሳሪያ ስለሚፈለግ እንዲያስረክቡ መመሪያ አስተላልፎላቸዋል። አማሮች መሳሪያውን ይዘው ፋኖን ይቀላቀላሉ በሚል ፍራቻ ከበላይ በመጣ ትዕዛዝ የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ የመሳሪያ ፈታችሁ አስረክቡ ማስታወቂያ ለጥፏል።
መኢአድ፤ ኢሕአፓ፤ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ እናት ፓርቲ በጋራ ባወጡት መግለጫ ፥ በሰላማዊ የፖለቲካ አመራሮችና አባላት ላይ እስራትና ወከባ እየደረሰ እንደሆነ ገልጿል።
ፓርቲዎች ይህ እስራትና ወከባ ” ለፖለቲካ ትግሉም ሆነ ለአገር በአጠቃላይ በቀደሙ ጊዜያትም ያመጣው በጎ ነገር የለም ” ሲሉ አስገንዘበዋል።” ዛሬም ቢሆን ከዚህ የተለየ ውጤት የማያመጣም ” ሲሉ አክለዋል።
ፓርቲዎቹ በመግለጫቸው እየተወሰደ ነው ያሉት እርምጃ በአስቸኳይ እንዲቆም የጠየቁ ሲሆን ” የታሰሩ አመራሮችም የሃሰት ማስረጃ ማቀነባበር ሳያስፈልግ በአስቸኳይ እንዲፈቱ አጥብቀን እንጠይቃለን ” ብለዋል።
” የስምምነት ሃሳቡ ተቀባይነት ካገኘ ኢትዮጵያ የተረጋጋ እና ተገማች የባህር ሀብት ተደራሽነት ይሰጣታል ” – ኮሪር ሲንግኦኢ
ኬንያ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ ቀጠናዊ የባህር ላይ ስምምነት ሃሳብ ማቅረቧን ሮይተርስ ዘግቧል።
ኬንያ የስምምነት ሃሳቡን ያቀረበችው ፤ ከጅቡቲ እና ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅት ኢጋድ ጋር በመመካከር ነው።
ይህ ስምምነት ወደብ የሌላቸው ሀገራት በንግድ እንዴት ወደብ መጠቀም እንደሚችሉ የሚገዛ መሆኑን የኬንያ የውጭ ጉዳይ ዋና ጸሃፊ ኮሪር ሲንግኦኢ ተናግረዋል።
ኢጋድ የባህር ሃብትን ለመጋራት የሚያስችል ስምምነት መፍጠር እንደሚችልም ገልጸዋል።
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ትላንት ከኬንያ አቻቸው ዊሊያም ሩቶ ጋር በኬንያ ዋና ከተማ ለውዝግቡ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ላይ መወያየታቸው ተሰምቷል።
በውይይቱ መጨረሻም ” ቀጠናው የተረጋጋ እንዲሆን ለማድረግ ከሁሉም አካላት ጋር መገናኘታችንን እንቀጥላለን ” ሲሉ ሲንግኦይ ተናግረዋል።
የናይሮቢ መፍትሄ ተቀባይነት ካገኘ ኢትዮጵያ የተረጋጋ እና ተገማች የባህር ሀብት ተደራሽነን ስለሚሰጥ የንግድ ስራዋን ያለምንም እንቅፋት እንድትፈጽም እንደሚያደርግ እና የሶማሊያን የግዛት አንድነት እንደሚያከብርም አክለዋል።
ኮሪር ሲንግኦኢ ፥ ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ ሃሳቡን እያጤኑበት ነው ያሉ ሲሆን ” መሪዎቻቸው ሂደቱን ወደፊት ለማራመድ ተገናኝተው እንዲመክሩበት ተጠይቀዋል ” ብለዋል።
መረጃው የሮይተርስ / ዶቼ ቨለ ነው።
በኢትዮጵያ የጅምላ ግድያ በአስደንጋጭ ሁኔታ እየተለመደ ነው- አምነስቲ ኢንተርናሽናል
ዓለም አቀፉ የመብቶች ተሟጋች ተቋም አምነስቲ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ የጅምላ ግድያ መበራከት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል አለ።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል በጥር ወር በአማራ ክልል መራዊ ከተማ የተፈጸመ “የጅምላ ግድያን” አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ የመንግስት ቸልተኛነት ለከፋ ጉዳት አጋላጭ ሆኗል በማለት ወቅሷል።
በአማራ ክልል ጥር 21 ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል በነበረበት ዕለት ከ50 የሚበልጡ ሰዎች መገደላቸውን መረጃ አግኝቻለሁ ያለው የመብት ድርጅቱ፤ ከ20 የሚበልጡ አስክሬኖች በመንገድ ላይ ተጥለው የሚያሳይ የሳተላይት ምስል ዛሬ አጋርቷል።
“የኢትዮጵያ መንግስት ተአማኒነት ያለው ጥረት አለማድረጉ የተገደሉት ቤተሰቦች ፍትህ እንዳያገኙ፣ መሰል ወንጀሎች ለመከላከል እንዳይቻልና ለከፋ ጉዳት የሚያጋልጥ ሆኗል” ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል መንግስትን ወቅሷል።
ከሦስት ሳምንታት በፊት የመራዊ ጥቃትን በተመለከተ የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶችን ለኢትዮጵያ መንግስት መላኩን ያስታወቀው ድርጅቱ፤ እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘ እና እየተጠባበቀ መሆኑን ገልጿል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል በግድያው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ለፋኖ የሚዋጉ ሰዎችን ቤት ለቤት በመፈለግ እንደወሰዱ እና አንዳንዶችን ደግሞ ያሉበትን እንዲጠቁሙ በማስገደድ ከቤት እየወሰዱ እንደገደሉ አመልክቷል።
ከአንድ ዓመት በፊት የመንግስታቱ ድርጅት መርማሪዎች ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ ለሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ በቆየው ትግራይ ክልል ብቻ ከፈረንጆቹ 2020 ጀምሮ ከ48 በላይ “ትላልቅ” ግድያዎች ተፈጽመዋል።
ይኹን እንጂ ጥር 24 ቀን 2016 ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዙ ወንጀሎች በተመለከተ የፌደራል መንስግቱ “ተገቢውን እርምጃ በእርሱ በኩል” መውሰዱን እንዳስታወቀ ሰምተን ነበር።
ብሪታንያ፣ በኦነግ አመራር አባል በቴ ኡርጌሳ ግድያ ዙሪያ “አስቸኳይ”፣ “ገለልተኛ” እና “ሙሉ” ምርመራ እንዲደረግና የድርጊቱ ፈጻሚዎች ተጠያቂ እንዲኾኑ ጠይቃለች።
በኢትዮጵያ የአገሪቱ አምባሳደር ዳረን ዌልች፣ በግድያው ዙሪያ “ፍትህ እና ተጠያቂነት” እንዲሰፍን አሳስበዋል።
በኦሮሚያ ክልል በሲቪሎች ላይ የሚፈጸመው ግድያ እንዲያበቃ፣ ፖለቲካዊ ንግግር ማድረግ ቁልፉ ርምጃ እንደኾነም አምባሳደር ዌልች በ”ኤክስ” (ትዊተር) ገጻቸው ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የአሜሪካ የላይኛው ሕግ አውጭ ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀመንበር ሴናተር ቤን ካርዲን፣ በኦነግ አመራር በቴ ኡርጌሳ ግድያ ዙሪያ ዓለማቀፍ መርማሪ አካል “ተዓማኒ”፣ “ገለልተኛ” እና “ጥልቅ” ምርመራ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት እንዲፈቅዱ ጠይቀዋል። ሴናተር ካርዲን፣ የበቴ ኡርጌሳ ግድያ “አስደንጋጭ” እና “የሚረብሽ” እንደኾነ ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል ከሕግ ውጭ የኾኑ ግድያዎች፣ ማንገላታት እና ፖለቲካዊ አፈና ተንሠራፍቷል ያሉት ሴናተር ካርዲን፣ የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ መንግሥት በፖለቲካ ተቃዋሚዎችና መገናኛ ብዙኀን ላይ በኦሮሚያ ክልል ብቻ ሳይኾን በመላው ኢትዮጵያ ይፈጽመዋል ያሉት “የማሳደድ” እና “የአፈና” ድርጊት በአገሪቱ አለመረጋጋት እንዲሰፍን እያደረገ ይገኛል በማለት ወቅሰዋል። ሴናተር ካርዲን፣ በአገሪቲ የጭቆናና አፈና ፖሊሲ አራማጆችና የመብት ጥሰት ፈጻሚዎች መጋለጥና ተጠያቂ መኾን አለባቸው በማለትም አሳስበዋል።
መንግስት ለበርካታ አመታት የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ብቻ እንዲሳተፉበት ተከልሎ የቆየው ቡናን ፣ ጫትን ፣ የቁም እንስሳትን እና ቆዳና ሌጦን ለውጭ ገበያ የመላክ ስራ ለውጭ ባለሀብቶች የሚፈቅድ መመሪያ ማዘጋጀቱን ዋዜማ ተረድታች።
ከማዳበሪያ እና ነዳጅ ውጪ ሌሎች ምርቶችን ማስገባትንም መመሪያው ለውጭ ባለሀብቶች ይፈቅዳል
በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ በሚመራው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ የተዘጋጀው እና ዋዜማ የተመለከተችው ሰነድ (መመሪያ) መንግስት በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ውሳኔን ለመወሰን ያበቃውን ምክንያት ያትታል።
ዝርዝሩን ያንብቡት- https://tinyurl.com/cw57akyj
➡️ ” እስሮች እንዳሉ መረጃዎች እየደረሱን ነው ” – ኢሰመኮ
➡️ ” ምናልባት ወንጀል ፈጽመው ሊሆን ይችላል ” – የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ምክንያቱ በትክክል ባልታወቀ ጉዳይ ሲቪል በለበሱ የፀጥታ አካላት አማካኝነት አፈሳና እስር እየተከናወነ መሆኑ እየተነገረ ነው።
ከተለያዩ ቦታዎች ላይ ሰዎች እየታፈሱ ወደ ፖሊስ ጣቢዎች እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን እንዲሁም የታሰሩትን ለመልቀቀ የገንዘብ ድርድር የሚያደርጉ የፀጥታ አካላት እንዳሉ እና በገንዘብ ተደራድረው የተፈቱ ስለመኖራቸው በማህበራዊ ሚዲያዎች ተነግሯል።
ስልክ አስከፍተው የሚበረብሩ እና ውስጡ ባሉት የተለያዩ ይዘቶች ” እናተ ተልዕኮ አላችሁ ” በሚል የሚታሰሩ እንዳሉም ተገልጿል።
የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትም ለእስር እየተዳረጉ ነው ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም እየተፈጸመነ ነው የተባለውን የአፈሳና እስር ጉዳይ ሰምቶ እንደሆን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)ን የጠየቀ ሲሆን ፣ አንድ የኮሚሽኑ አካል በሰጡት ቃል ፤ ” በከተማው እስሮች እንዳሉ መረጃዎች እየደረሱን ነው ” ብለዋል።
አክለውም ” ሰዎቹ የታሰሩበትን ጉዳይ ለማጣራት አዲስ አበባ ላይ ከሚሰራው የእኛ ቲም ጋር እየተነጋገርን ነው። አሁን ላይ የተረጋገጠ መረጃ የለም። በተለመደው ሁኔታ የታሰሩ ሰዎች ሲኖሩ ክትትል ነው የምናደርገው ፣ አሁንም እሱን ነው የምናደርገው ” የሚል ቃል ሰጥተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንንም ጠይቋል።
የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ” ምናልባት ወንጀል ሰርተው ሊሆን ይችላል ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
” የታሳሪ ቤተሰቦች በርካቶች ሰዎች ታሰሩባቸው
ፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ “በጸጥታ አካላት” ከተያዘ በኋላ ነው የተገደለው- የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት
ግድያው “ባልታወቁ ሰዎች” የተፈጸመ ነው- የኦሮሚያ ክልል መንግስት
ሚያዝያ 03 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) ብሎ የሚጠራው ቡድን ቃል አቀባይ ኦዳ ተርቢ በኩል ባወጣው መግለጫ በቴ ኡርጌሳ በመቂ ከተማ ካረፉበት ሆቴል እኩለ ሌሊት ላይ “በጸጥታ አካላት” ከተወሰዱ በኋላ ተገድለዋል ሲል ገልጿል።
ኢሰመኮን ጨምሮ ሌሎችም የኦነግ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ግድያ ነጻ ምርመራ እንዲድረግበት እየጠየቁ ሲሆን… ዝርዝሩን https://addismaleda.com/archives/36451 ይመልከቱ
መንግስታዊው የፖሊሲ ባንክ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጊዜያዊት ብድር መልቀቅ ማቆሙን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች ። ንግድ ባንኩ ብድር ለማግኘት የተለያዩ ሂደቶችን አልፈው ፤ ብድሩ ተፈቅዶላቸው የመልቀቅ ሂደት ላይ ያሉትም እንዲቆም ነው ያዘዘው ። ባንኩ ይህን ትእዛዝ ያስተላለፈው ረቡዕ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ/ም መሆኑንም ሰምተናል ። ዝርዝሩ እነሆ- https://tinyurl.com/39dw5j8k
ነአመን ዘለቀ ፡ እንደዛሬው በትብኢት ፣ እብሪትና በህዝብ ንቀት ሳይወጠር፣ የፍትህ፣ የዴሞክራሲ፣ የህግ የበላይነትና ፣ ጭንብሎቹ ሳይወልቁ፣ የበሻሻው ደላላ ፋሽስቱ እለቃችሁ አብይ አሕመድ አሊ ወደ ስልጣን እንደመጣና በቀጠሉት አመታት፣ በማር በተጠቀለሉ ቃላት ለፍትህ፣ ለህግ የበላይነት ፣ ለዴሞክራሲ ያለውን ቀናኢነት በገለጸበት የተስፋ ቃላቶቹ በእርግጥም ህዝብ “በነቂስ” ወጥቶ ደግፎት ነበር።
ሆኖም ከቅርብ አመታት ወዲህ በእናንተ፣ በብልጽግና በተለይም በኦሮሚያ ብልጽግና ሁሉንም የህዝብ ጥያቄ ረግጣችሁ፣ ማስመስል፣ ማጭበርበር፣ “የከተማውን ህዝብ” ቤቱን በላዪ ላይ ማፍረስ፣ ከማህበራዊ ትስስሩ መናድ፣ ቅርሱን ማፍረስ (አዲስ አበባ ላይ በየቦታው ፣ ሰሞንኑን በፒያሳና “ዶሮ በምትታነቅበትን” ዶሮ ማነቂያን የተፈጸመውን ኢፍትሃዊ፣ ጋጠ ወጥ እርምሃዎች ይጨምራል) ማፈናቀል፣ ዘረፋና ሙስና፣ የግፍና የበደል ስርአት እስፍናችሁ የከተማው ህዝብ “በነቂስ” ወጥቶ ለበሻሻው ደላላ ፋሽስቱ አብይ አህመድን ድጋፍ ሰጠ ማለት ጸሃይ የሞቀውን ሃቅ መካድ ይሆናል፣ ለቀባሪው አረዱት እንዲሉ። ህዝቡን በግድ አሰገድዳችሁ ነው ያስወጣችሁት። ይህ ሊካድ የማይችል ሀቅ ነው።
የብልጽግና ካድሬዎቻችሁ ሲቀነሱ ማለት ነው። በፌደራል እስከ ወረዳ መስሪያ ቤቶች በየቀበሌው፣ ወረዳዎች ማስፈራሪያ ደብዳቤዎች ለሰራተኛው ፣ ለህዝቡ እንዲደርስ እድርጋችሁ ነው “የነቂስ” ሰልፍ የተወጣው። የማስገደዱ እርምጃዎች የሚያሳዩ በርካታ መረጃዎች በወጡበት ሁኔታ “ከተማችን ነዋሪዎች በነቂስ ወጥተው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የተመራው ለውጥ 6ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ድጋፋቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ገልጸዋል።” የሚል ቅጥፈትና ሸፍጥ እየተናገራችሁና እያስነገራችሁ አይናችሁን ጨፍኑና እናሞኛችሁ ትጫወታላችሁ። ከቀድሞ አለቆቻችሁ ከህወሃቶች ምንም የማትማሩ ፣ በቀን ቅዠት ውስጥ የምትዋኙ ጉዶች ናችሁ። ሃፍረትም፣ይሉኝታም፣
አንድ የታሪክ ተመራማሪ በመቅደላ ጦርነት የተሰረቁት የአፄ ቴዎድሮስ አልባሳት የት እንዳሉ ለማወቅ እየጣሩ ነው ተባለ
በእንግሊዝ አንድ የታሪክ ተመራማሪ ከ156 ዓመታት በፊት የተሰረቁት የዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ አልባሳት የት እንዳሉ ለማወቅ እየጣሩ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።
ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ በእንግሊዝ ወረራ ወቅት እጅ አልሰጥም ብለው መቅደላ ላይ የራሳቸውን ሽጉጥ ጠጥተው ከሞቱ በኋላ ለብሰውት የነበረው የክብር ካባ እና የአንገት ልብስ ከአስክሬናቸው ላይ ተገፍፎ ተወስዷል።
አልባሳቱ ወደ እንግሊዝ ከተወሰዱ በኋላም በስታሊይብሪጅ፣ ስታምፎርድ ፓርክ ሙዚየም ውስጥ ተቀምጠው እንደነበር ሲገለፅ ሙዚየሙ በ1950ዎቹ ከፈረሰ በኋላ ግን እነዚህ ጥንታዊ ቅርሶች የት እንዳሉ አይታወቅም ተብሏል።
በጉዳዩ ላይ መጽሐፍ የጻፉት ሔቨንስ የተባሉት የታሪክ ተመራማሪ እንደሚሉት በመቅደላ ጦርነት ወቅት የተወሰዱ ቅርሶች ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በአገሪቷ ውስጥ ይገኛሉ። ከሐር የተሠራው የንጉሡ ትንሽ የአንገት ልብስም ስታሊይብሪጅ ውስጥ በሚገኘው ሰታምፎርድ ፓርክ ሙዚየም ውስጥ ተቀምጦ ነበር።
ሙዚየሙ በ1950ዎቹ ከፈረሰ በኋላ የንጉሡ የአንገት ልብስ ወይም የካባው ክፍል በሆነ ሰው ቤት ውስጥ እንደሚገኝ ሔቨንስ እምነት እንዳላቸው እና የተረፉት ሌሎች ቅርሶችም ወደ ሌሎች የአካባቢው ሙዚየሞች መሰራጨታቸውን ገልፀዋል።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የታሪክ ምሁሩ ለታሜሳይድ የአካባቢ ጥናት ተቋም፣ ለመዘክሮች እና ለማንቸስተር ሙዚየም ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። የከተማዋ ነዋሪዎች የጥንታዊ ዕቃዎች ማስቀመጫዎቻቸውን እንዲፈትሹ እያሳሰቡም ነው ተብሏል።
ኦነግ፣ በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቶሌ ወረዳ የመንግሥት ወታደሮች ሰሞኑን በፈጸሙት ጥቃት 20 ንጹሃን የጅምላ ግድያ እንደተፈጸመባቸው አረጋግጫለሁ በማለት ትናንት ባወጣው መግለጫ ከሷል።
ግንባሩ፣ የሟቾችን ስም ጭምር ዘርዝሯል። መንግሥት በክልሉ የንጹሃን ዜጎችን ደም ማፍሰስን የዕለት’ተለት ሥራው አድርጎታል ያለው ኦነግ፣ የጅምላ ግድያው እንዲቆምና የዜጎች ደኅንነት እንዲጠበቅ ተደጋጋሚ መግለጫ ባወጣም ችግሩ እየባሰ ሄዷል ብሏል።
ኦነግ፣ ግድያዎች እንዲቆሙ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና ሲቪል ማኅበራት ጫና እንዲያደርጉ ጠይቋል።
ብልጽግና ፓርቲ “ፍሬያማ” ያላቸው 6 ዓመታት ለአገሪቱ አደጋ ናቸው ተባለ
ያለፉት ስድስት ዓመታት መንግስት ቅድሚያ መስጠት ላለበት ጉዳይ ትኩረት ሳይሰጥ እና አገሪቱን የመበተን አደጋ ላይ የሚጥሉ ተግባራት ተስፋፍተው ያሉበት እንደሆነ ከአዲስ ማለዳ ጋር ቆይታ ያደረጉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅቶች ገለጹ።
የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደ ስልጣን የመጡበት ስድስተኛ ዓመት መጋቢት 24 ቀን 2016 ነበር። በተለያዩ አካባቢዎች የድጋፍ ሰልፎች ከመደረጋቸው ጎን ለጎን የፓርቲው አባላት “ፍሬያማ” ስድስት ዓመታት እንዳለፉ እየገለጹ ነው።
ብልጽግና ፓርቲ የትኛውም ምድራዊ ኃይል የማያደናቅፈው የለውጥ ጉዞ ላይ ነን ቢልም ተፎካካሪዎቹ አገሪቱን የሚበትን አደጋ መንሰራፋት፣ ለዜጎች ሰላም ቅድሚያ አለመስጠት፣ ከጎረቤት አገራት ጋር መቃቃር እና… https://addismaleda.com/archives/36407
በአዲስ አበባ ‘የከተማዋ ነፍስ’ በድንጋጤ እየሞተች ነው።
አዲስ አበባ በመዲናዋ የሚገኝ ታሪካዊ ወረዳ ፈርሶ የሰዎች መኖሪያ እና ኑሮ ወድሟል። ( ዘጋርዲያን )
ኢትዮጵያ ቱሪዝምን እና ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ በሚል ሰበብ በልማት ስም በመዲናዋ የሚገኝ ታሪካዊ ወረዳ ፈርሶ የሰዎች መኖሪያ እና መተዳደሪያ ወድሟል።
In the heart of Addis Ababa, the historic, ramshackle neighbourhood of Piassa once teemed with shops and cafes. People would come from across Ethiopia’s capital city to buy anything from jeans to jewellery. Today it lies in ruins. Its distinctive stone houses, with their wooden balconies and slanting metal roofs, are almost all gone. In their place are jagged fields of rubble, picked over by workers with sledgehammers.
በአዲስ አበባ መሀል ላይ፣ የፒያሳ ታሪካዊ ሰፈር በአንድ ወቅት በሱቆችና በካፌዎች የተሞላ የነበረው ሰዎች ከጂንስ እስከ ጌጣጌጥ ለመግዛት ከመላው የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ይመጡ ነበር ። ዛሬ ፍርስራሹ ላይ ወድቋል። ለየት ያሉ የድንጋይ ቤቶች፣ ከእንጨት የተሠሩ በረንዳዎች እና የተንቆጠቆጡ የብረት ጣራዎቻቸው ከሞላ ጎደል ጠፍተዋል። አከባቢው ትልልቅ መዶሻዎች በያዙ አፍራሾች ተሞልቷል። ሰዎች ፍርስራሹን ለማየት ይቆማሉ። አንዳንዶች ፎቶ ያነሳሉ። ነገር ግን ብዙም አይቆዩም፡ ፍርስራሾቹ በፖሊሶች ይጠበቃሉ። አንድ የቀድሞ ነዋሪ “ተናድጃለሁ” ብሏል። “ምንም ምክክር ሳይደረግ በዓይኔ ፊት የፈረሰው የእኔ ቅርስ ነው። እቅዱ አልተነገረንም።” ሲልም ተናግሯል።
https://amp.theguardian.com/global-development/2024/apr/04/dismay-in-addis-ababa-as-the-soul-of-the-city-is-razed-for-development-ethiopia
ሂውማን ራይርስ ዎች፣ ተመድ እና አፍሪካ ኅብረት በኢትዮጵያ በአማራ ክልል ከሚፈጸሙ ጥሰቶች ጋር በተያያዘ የአገሪቱን ወታደሮች ፌደራል ፖሊሶች ከዓለማቀፍ የሰላም ማስከበር ሥምሪቶች እንዲያግዱ ጠይቋል።
ሂውማን ራይትስ ዎች፣ ጉዳዩ የሚያሳስባቸው መንግሥታት በኢትዮጵያ የመብት ጥሰት ላይ ክትትል እንዲጀመር በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በኩል ጥረት እንዲያደርጉና የድርጅቱ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር በአማራ ክልል የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችንና በጥር ወር በመራዊ ከተማ በበርካታ ንጹሃን ላይ የተፈጸሙትን ግድያዎች ባስቸኳይ እንዲመረምሩ እንዲጠይቁም አሳስቧል።
አውሮፓ ኅብረትም በመራዊ የተፈጸመው ግድያ በገለልተኛ አካል እንዲጣራና ወንጀል ፈጻሚዎች ተጠያቂ እንዲኾኑ እንዲሠራ ሂውማን ራይትስ ዎች ጠይቋል።
የፓሪስ ክለብ አበዳሪ እገራት ኢትዮጵያ ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ጋር የብድር ስምምነት ላይ እንድትደርስ የሦስት ወራት ተጨማሪ ጊዜ መስጠታቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
አበዳሪ እገራት ኢትዮጵያ ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት ጋር እስከ መጋቢት 23 ገደማ አዲስ የብድር ስምምነት ላይ ካልደረሰች፣ እስከ ቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት ያራዘሙላትን የብድር መክፈያ የእፎይታ ጊዜ ሊያጥፉት እንደሚችሉ አስጠንቅቀው ነበር።
ኾኖም ኢትዮጵያ እና ድርጅቱ በቀነ ገደቡ የብድር ስምምነት ላይ ሳይደርሱ መቅረታቸውን ተከትሎ፣ አበዳሪ እገራቱ ቀነ ገደባቸውን እስከ ሰኔ መጨረሻ ማራዘማቸውን ከምንጮች መስማቱን ዘገባው አመልክቷል።
የብሄራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምኅረቱ፣ የአበዳሪዎች ኮሚቴ ጊዜውን ማራዘሙን ኢትዮጵያ በደስታ እንደተቀበለችው መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት በብድሩ ዙሪያ ከመንግሥት ጋር የሚደረገው ንግግር በተያዘው ወር መጨረሻ ዋሽንግተን ላይ እንደሚቀጥል ከትናንት ወዲያ መግለጡ ይታወሳል።
43 አገራት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የቀጠሉ ግጭቶችና የመብት ጥሰቶች በጣም እንዳሳሰቧቸው ትናንት ለተካሄደው 55ኛው የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ስብሰባ ባስገቡት መግለጫ ላይ ገልጸዋል።
አገራቱ፣ ኹሉም የግጭቶች ተሳታፊ ወገኖች በንግግር ሰላምን እንዲሽቱና በአገራዊ የውይይት ሂደቱ እንዲሳተፉ ጠይቀዋል።
አገራቱ፣ በኢትዮጵያ ሰላምና እርቅ ለማስፈን ተዓማኒነት ያለው የሽግግር ፍትህ ፖሊሲና ተጠያቂነት አስፈላጊ መኾኑንም አውስተዋል።
የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማዕቀፉ፣ እውነተኛ ተጠያቂነትን፣ እውነት አፈላላጊነትን፣ ካሳ እና ጥሰቶች ድጋሚ ላለመፈጸማቸው ማረጋገጫ መስጠትን ማካተት እንዳለበትም አገራቱ አሳስበዋል።
በትግራይ፣ አማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ በጦርነትና ድርቅ ሳቢያ ባኹኑ ወቅት ከ4 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ኾነው እንደሚገኙ ዋዜማ ካሰባሰበችው መረጃ ተረድታለች።
የትግራይ ትምህርት ቢሮ፣ ከጦርነቱ በኋላ ከ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዳልተመለሱ ለዋዜማ ተናግሯል።
105 ትምህርት ቤቶች አኹንም የተፈናቃዮች መጠለያ እንደኾኑንና የክልሉ 88 በመቶ ትምህርት ቤቶች በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ በጦርነቱ እንደወደሙ ቢሮው ተናግሯል።
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮም፣ በግጭቱ ሳቢያ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ገደማ ተማሪዎች ዘንድሮ ወደ ትምህርት ቤት እንዳልተመለሱ ገልጧል።
3 ሺሕ 500 የአንደኛና 225 የኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ ዓመቱ አጋማሽ ዝግ ኾነው እንደቆዩና 300 ትምህርት ቤቶች በግጭቱ እንደወደሙም ቢሮው ጨምሮ ገልጧል።
የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ በበኩሉ፣ ዘንድሮው 131 ሺሕ 338 ተማሪዎች ከአንድ ሳምንት እስከ ወር የዘለቀ የትምህርት መቆራረጥ አጋጥሟቸዋል ብሏል። ዋዜማ
የብልጽግና ፓርቲ 14 ሚልየን አባላት በሥራ ወይስ በአበል?
(አዲስ ማለዳ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባቀረቡት የሦስት ቀናት የፕሮጀቶች ጉብኝት፣ የውይይት እና የስልጠና መርሃ ግብር መሰረት ለውይይት ተቀምጠው ነበር።
በውይይቱ የተነሱ ሃሳቦችን የተተቸው እና የተሞገሰው ውይይቱ፣ የፖለቲካ ምህዳር ስለመጥበቡ፣ የብልጽግና ፓርቲ የመንግስት ሃብትን አጠቃቀም እና ሠላም በሚሉ ጉዳዮች ተመልክታዋለች።
የፖለቲከኞች እስር፣ የብልጽግና የህዝብ ሀብት መጠቀምና የሌሎች ፓርቲዎች መቀጨጭ፣ የፓርቲዎች ብዛት ከ5 ባይበልጥ መባሉ https://addismaleda.com/archives/36399
የዓለማቀፉ ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ልዑካን ቡድን ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ባደረገው ውይይት የመንግሥትን አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብር መደገፍ በሚቻልበት ኹኔታ ዙሪያ ብዙ እድገት መታየቱን ገልጧል። ድርጅቱ የአብይ አስተዳደር አዲስ የፋይናንስ ሕግ እንዲያወታ እና ግልጽነት ያለው የፋይናንስ ሲስተም እንዲኖር መመሪያ የሰጠ ሲሆን የብር ተመን እና ሌሎች የፋይናንስ ተመኖችን ድርጅቱ ባቀረበው ሰነድ መሰረት እንዲያሻሽል እና ብድርም እንደሚፈቀድለት ለአብይና ለባለስልጣናቱ ተነግሯቸዋል።
ውይይቱ፣ ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና ዓለም ባንክ በቀጣዩ ወር መጨረሻ ገደማ በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ እንደሚቀጥል ቡድኑ ትናንት ሌሊት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።የልዑካኖችን ተደራድረው መመለስ ተከትለው “በቅርቡ አዲስ ወጥ የሆነ የፋይናንስ ህግ እናወጣለን” ሲሉ አቶ ማሞ ምህረቱ መግለጫ ሰተዋል።
በሚቀጥሉት ዓመታት በኢትዮጵያ የፋይናንስ ሥርዓት መሰረታዊ ለውጥ ይመጣል ሲሉ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ተናግረዋል።
ይህም የሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት በቅርጽ፤ በሚያቀርበው አገልግሎት እና በሚሳተፉት ተዋናዮች መሰረታዊ የሆነ ለውጥ እንደሚኖር ነው የጠቆሙት።
“በቅርቡ አዲስ ወጥ የሆነ የፋይናንስ ህግ እናወጣለን” ያሉት ገዢው በዘርፉ አዳዲስ ተዋናዮች እንደሚኖሩም አንስተዋል።
አክለውም አሁን ላይ ቴሌብርን ጨምሮ 11 የፊንቴክ ካንፓኒዎቾ ሥራ እየሰሩ ሲሆን ፈቃድ በማውጣት ላይ ያሉ 14 የፊንቴክ ካንፖኒዎች እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
“እነሱን ጨምረን የባንኩን ዘርፍ ክፍት በምናደርግበት ጊዜ የኢትዮጵያ የፋይናንስ ሥርዓት መሰረታዊ በሆነ መልኩ ላንድ ስኬፕ ይቀየራል።” ነው ያሉት።
የድርጅቱ ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ ከመጋቢት 10 እስከ መጋቢት 24 /2016 ቆይታ ማድረጉን ገልጧል።
አበዳሪ አገራት የኢትዮጵያ መንግሥት እስካለፈው የፈረንጆች
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እና ብልፅግና ፓርቲ በፕሪቶሪያ ውል መሰረት ፓለቲካዊ ውይይት ለመጀመር መስማማታቸው ተገለጸ።
ህወሓት በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገፁ ባሰራጨው መረጃ ፥ በብልፅግና ምክትል ፕረዚደንት አቶ አደም ፋራህ የሚመራ ቡድን ዛሬ መጋቢት 24/2017 ዓ.ም በመቐለ ከህወሓት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጋር ተወያይቷል።
የሁለቱም ፓለቲካዊ ፓርቲዎች የፓለቲካ ውይይት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ቀደም ብሎ መጀመር እንደነበረበት በመተማመን በአጭር ጊዜ ውስጥ ውይይት እንዲጀምሩ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ህወሓት ገልጿል።
ሳውዲ አረቢያ በአንድ ሳምንት ውስጥ ህግ ተላልፈዋል ያለቻቸውን ከ500 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን አሰረች
ሳውዲ አረቢያ በአንድ ሳምንት ውስጥ በተደረገ ኦፕሬሽን በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገሪቱ ለመግባት ሞክረው ህግ ተላልፈዋል ያላቻቸውን 966 ሰዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሏን ባለስልጣናቱ አስታወቁ።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት ውስጥ 59 በመቶ ወይም 569 ገደማ የሚሆኑት ዜጎች ኢትዮጵያዊውያን ናቸው ተብሏል። ሀገሪቱ በአጠቃላይ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ባደረገችው የተቀናጀ ኦፕሬሽን 21,537 ሰዎችን ማሰሯ ተነግሯል።
በሀገሪቱ የድንበር ህግን የጣሱ፣ የሌላ ሀገር ዜጎችን በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገሪቱ እንዲገቡ የረዱ እና ህጋዊ የመኖሪያ ሰነድ የሌላቸው የሌላ ሀገር ዜጎች እስከ 15 አመት የሚደርስ ቅጣት ይጠብቃቸዋል መባሉን አረብ ኒውስ ዘግቧል።
አዲሱ አዋጅ “ስለ መኖሪያ ቤት ኪራይ ውል” ዘመን ምን ዝርዝር ይዟል?
ዛሬ በፓርላማ በጸደቀው “የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ” ከተዘረዘሩ ድንጋጌዎች ውስጥ፤ “የመኖሪያ ቤት የኪራይ ውል ዘመንን” የሚመለከቱት የሚጠቀሱ ናቸው። “የመኖሪያ ቤት ኪራይ የውል ዘመን ከሁለት ዓመት ሊያንስ አይችልም” ሲል የደነገገው አዋጁ፤ ይህ የተደረገበትን ዋነኛ ምክንያት በማብራሪያው ላይ አስፍሯል።
“የአዋጁ ዓላማ የመኖሪያ ቤት ኪራይ የተረጋጋ እንዲሆን ለማድረግ በመሆኑ፤ [ውሉ] ከሁለት ዓመት ያነሰ ቢሆን አከራዩ ውሉን ለማደስ ፍቃደኛ ላይሆን ስለሚችል፤ ተከራይ በየጊዜው በቀጣይ ስለሚከራየው ቤት በመጨነቅ የተረጋጋ ህይወት እንዳይመራ ያደርገዋል” ሲል የአዋጁ ማብራሪያ አትቷል። “ከሁለት ዓመት ያለፈ ዘመን ይኑረው ቢባል ደግሞ የአከራይን መብት እንዳይጫን፤ ሚዛናዊ በሆነ መልኩ የውል ዘመኑ ከሁለት ዓመት ያላነሰ ጊዜ እንዲሆን” መደረጉን የአዋጁ ማብራሪያ አስገንዝቧል።
“አዋጁ ከመውጣቱ በፊት ከሁለት ዓመት በታች የተደረጉ የቤት ኪራይ ውሎች ላይ ይህንን አዋጅ ተግባራዊ ማድረግ ፍትሐዊ ስለማይሆን፤ በውላቸው ላይ ያጸደቁት ቤት ኪራይ የውል ዘመን ተቀባይነት እንዲያገኝ ተደርጓል” ሲል ማብራሪያው አክሏል። ዝርዝሩን ከላይ ከተያያዘው ምስላዊ መረጃ ይመልከቱ።
በመኖሪያ ቤቶች ኪራይ ላይ የሚደረገው የዋጋ ጭማሪ፤ በተቆጣጣሪ አካል እንዲወሰን የሚያደርግ አዋጅ በፓርላማ ጸደቀ
በመኖሪያ ቤቶች የሚደረገው የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ላይ፤ በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እንዲሁም በክልሎች በሚቋቋም ተቆጣጣሪ አካል በሚወስነው መሰረት እንዲከናወን የሚያደርግ አዋጅ ዛሬ በፓርላማ ጸደቀ። የተቆጣጣሪ አካሉ “የሀገሪቱን ነባራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች” ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ በየዓመቱ ከሰኔ 30 ጀምሮ ለአንድ
የዐማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ድንቅ ኦፕሬሽን!
ከአዲስ አበባ በ130 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ሸዋ ደብረ ብርሃን ከተማ ላይ ትላንት ማለትም መጋቢት 19/2016 ዓ.ም ሌሊት በሸዋ ፋኖ ዕዝ በተሰራ ድንቅ ኦፕሬሽን አንድ የስርዓቱ አገልጋይ ባንዳ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ይህ ባንዳ የደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘደንት ሲሆን ዶ/ር የሚባል የግዢ ዱክትርና ይዞ ለስርዓቱ አሽከር በመሆን ስልጣኑን ተጠቅሞ በዩኒቨርሲቲው የአማርኛ ትምህርት እንዳይሰጥ ያገደ፣ የታሪክ ዲፓርትመንትን ያገደ፣ የተቋሙን በጀት ለ”መከላከያ” ያዋለ፣ ተቋሙ እንደ ማሰልጠኛ እና ካምፕ እንዲያገለግል የፈቀደ፣ የግቢውን ታሪካዊ ነገሮች በሙሉ ያፈረሰና እያፈረሰ ያለ ከየትኛውም የብልፅግና ከፍተኛ የፖለቲካ እና የወታደራዊ አመራሮች ያልተናነሰ ነውረኛ ተግባር በአማራውያን ላይ የፈፀመ ባንዳ ነው።
ይህን ነውረኛ በትላንትናው ዕለት በደብረ ብርሃን ከተማ ሌሊት ላይ የዐማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በቁጥጥር ስር አውሎታል።
የግብጽ የመስኖ ሚንስትር ሃኒ ስዊላም፣ የሕዳሴ ግድብ በግብጽ ላይ ለሚያደርሰው ጉዳት ኢትዮጵያ ዋጋ ትከፍልበታለች በማለት ማስጠንቀቃቸውን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ሚንስትሩ፣ ግብጽ በናይል ወንዝ ላይ ያላት ጥቅም ከተነካባት፣ አስፈላጊ የኾኑ ርምጃዎችን ትወስዳለች በማለት እንደዛቱ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።
ሚንስትሩ፣ በድርቅ ጊዜ ምን መደረግ እንዳለበት እንዲኹም በግድቡ ውሃ አሞላል ሂደት እና በውሃ ሃብት አጠቃቀም ዙሪያ አስገዳጅ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል ተብሏል።
የሦስቱ አገራት የመርኾዎች ስምምነት፣ በታችኞቹ ተፋሰስ አገሮች ላይ ጉዳት ያደረሰ አገር የጉዳት ማካካሻ እንዲከፍል ያስገድዳል ማለታቸውን የጠቀሱት ዘገባዎቹ፣ እስካኹን ባለው የድርድሩ ቅርጽ ሌላ ዙር ድርድር ማድረግ ጊዜ ማባከን እንደኾነም መናገራቸውን አመልክተዋል።
” ወንድም እና እህቱን በቁጥጥር ስር አድርገን ምርመራ እያካሄድን ነው ” – የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንና የባህር ዳር ከተማ የመሀል ሜዳው ተጫዋች አለልኝ አዘነ ለህልፈት መዳረጉን ተከትሎ ቤተሰቦቹ በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፥ ” አሟሟቱ ድንገተኛና አሰቃቂ መሆኑን ተከትሎ የቅርብ ግንኙነት ያላቸዉን አካላት ይዤ ምርመራ ጀምሪያለሁ ” ብሏል።
የወጣቱ ህይዎት ይቀጠፍ ዘንድ ምክኒያት የሆኑ ጉዳዮችን ለማወቅ የስልክ ልውውጦችን ከመመርመር በተጨማሪ በዙሪያው የነበሩ አካላትንም በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ገልጿል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ እነማን ተያዙ ? የምርመራዉ አካሄድስ ምን ይመስላል ? ሲል ለአርባምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የለሆኑት ኢንስፔክተር አብርሀም ሙሄ ጥያቄ አቅርቧል።
” የተጫዋቹ መሞት በተሰማበት ወቅት አጠራጣሪ ጉዳዮች ስለነበሩ ፖሊስ የምርመራ እንቅስቃሴ ጀምሯል ” ያሉት ኢንስፔክተር አብርሀም ” በዚህ ወቅት ወንድም እና እህቱን በቁጥጥር ስር አድርገን ምርመራ እያካሄድን ነው ” ብለዋል።
በሶሻል ሚዲያ እየተዘዋወረ ያለዉን የእናቱ እና ባለቤቱ መያዝ በተመለከተ ላነሳንላቸዉ ጥያቄ ” አሁን ላይ ከእህት እና ወንድሙ ዉጭ የተያዘ አካል የለም በማለት ወደፊት ግን ከተያዙት የሚለቀቅ ካልተያዙት ደግሞ የሚያዝ ሊኖር ይችላል ” ብለዋል።
” አሁን ላይ ምርመራዉን በፍጥነትና በጥንቃቄ እያካሄድን ነው ” ያሉት ኢንስፔክተር አብርሀም ሙሄ ውጤቱን ለመላ የኢትዮጵያን ህዝብ ለማድረስ ማሰባቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ እየተስፋፋ የመጣው የእገታ ወንጀል ( ኤሊያስ መሰረት )
ከሰሞኑ በስፋት እየደረሱኝ ያሉ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በፊት በፊት በክፍለ ሀገራት፣ ከዛም በአንዳንድ የአዲስ አበባ አቅራቢያ ስፍራዎች ሲከናወኑ የነበሩ የእገታ ወንጀሎች አሁን ላይ በአዲስ አበባ ከተማ መታየት ጀምረዋል።
ከ10,000 ብር ጀምሮ እስከ 1 ሚልዮን ዶላር የተጠየቀባቸው ሰዎች እንዳሉ፣ እገታዎቹ በቀንም ይሁን በጭለማ እንደሚከናወኑ፣ አብዛኞቹ የፀጥታ አካላትን በመምሰል (ወይም ሆነው… ይህ ሲጣራ ይታወቃል) ድርጊቱን እንደሚፈፅሙ እና ከመኖርያ ቤታቸው ጭምር የተወሰዱ ሰዎች እንዳሉ አረጋግጫለሁ።
እንደ ነጋዴዎች፣ ዲያስፖራዎች እና የውጭ ዜግነት ያላቸው ሰዎች እና ብር አላቸው ተብለው የሚገመቱ ማንኛውም ሰዎች በተለይ ኢላማ እንደሆኑ ታውቋል።
አጋቾቹ ድርጊቶቹን ከፈፀሙ በኋላ ታጋቾች ድርጊቱን ለፖሊስ እንዳያሳውቁ ስለሚያስፈራሩ ትክክለኛ የድርጊቱን መጠን ለማወቅ አስቸጋሪ ነው።
ማስተባበል መቼም መፍትሄ ስለማይሆን አሁንም ሳይረፍድ የሚመለከተው አካል በይፋ ወደፊት በመምጣት ድርጊቱን ቢያንስ በይፋ ለህዝብ ማሳወቅ አለበት።
ከእንዲህ አይነት እገታ ‘ተጠንቀቁ’ ቢባል እን
የተጀመረው የኮሪደር ልማት በርካታ ጥንታዊና ታሪካዊ ህንጻዎች እንዲፈርሱ ምክንያት ሆኗል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የምጣኔ ሀብት ባለሞያ ለአዲስ ማለዳ እንደገለጹት “በኮሪደር ልማቱ” 200 ሺህ ይሚሆኑ ነባር ይዞታዎችና ሱቆች እንደሚፈርሱ ግምታቸውን አስቀምጠው ከ1.5 ሚልየን በላይ ሰዎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ይጎዳሉ ብለዋል።
አዲስ ማለዳ ያነጋገረቻቸው ፖለቲከኛዎች ደግሞ ብልጽግና ፓርቲ ምርጫ ለማሸነፍ የሚያስችለውን ሕዝብ ለማስፈርና “አደረግኩላችሁ” ለማለት… https://addismaleda.com/archives/36369 ዝርዝሩን አንብቡ።
በአፋር ክልል፣ በአፋር እና ኢሳ ሱማሌ ጎሳዎች መካከል በድጋሚ በተያዘው ሳምንት ግጭት ማገርሸቱን ዋዜማ ሰምታለች።
ግጭቱ የተከሰተው፣ በገቢ ረሱ ዞን (ዞን ሦስት) አሚባራ ወረዳ ውስጥ አፋርና ሱማሌ ክልሎች በሚወዛገቡበት ገዳማይቱ ቀበሌ እንደኾነ ታውቋል።
በግጭቱ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች ሳይገደሉና ሳይቆሰሉ እንዳልቀሩ ተነግሯል።
በሕገ ወጥ መንገድ ዜጎችን ማሰር እና ማንገላታት የገዢውን ፓርቲ እንባገነናዊ ፈላጭቆራጭነት ያመለክታል- ኢሕአፓ
(አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ”በሕገወጥ መንገድ ዜጎችን ማሰር እና ማንገላታት የሚያመለክተው የገዢውን ፓርቲ እየሄደበት ያለውን አንባገነናዊ ፈላጭ ቆራጭነት ባህሪ ነው ሲል አወገዘ።
የኢሕአፓ ሊቀ መንበር ረዳት ፕሮፌሰር ዝናቡ አበራ ከትላንት ወዲያ በፓርቲው ጽህፈት ቤት በስራ ላይ እንዳሉ “በህገ ወጥ” መንገድ በጸጥታ ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጿል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ትላንት መጋቢት 19 ቀን 2016 ካወጣው መግለጫ አዲስ ማለዳ እንደተመለከተችው በተመሳሳይ ቀደም ሲል የድርጅቱ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ መንበር “ጦርነት ይቁም ሰላም ይስፈን” የሚል ሰላማዊ ሰልፍ ለማዘጋጀት በመሞከራቸው ለወራት እስር ተዳርገው በቅርቡ መለቀቃቸውን አስታውሷል።
ፓርቲው የኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግሮች እንዲፈቱ የሚደረገውን ትግል ለማሰናከል እና “መሪዎቻችን ይፈቱ” በሚል ጥያቄ ዙሪያ እንድንጠመድ አንደኛው አመራር በተፈቱ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሊቀ መንበሩ መታሰራቸውን ገልጿል።
በመሆኑም በስልጣን ላይ ያለው የብልጽግና ፓርቲ በምክክር እና በውይይት ከአቻ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር የሚሰራ ሳይሆን ከፓርላማ አባላት እስከ ፖለቲካ ድርጅት መሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍል አባላትን ማፈንና ማሰር ኢ-ፍትሀዊ በመሆኑ ድርጅቱን እንደሚኮንን ኢሕአፓ አስታዉቋል።
“መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት አባቶችንና ምእመናንን አሰቃቂ ግድያ በማስቆም ከደሙ ነጻ መሆኑን በአስቸኳይ ሊያረጋግጥ ይገባል።”
እናት ፓርቲ
ዩንቨርሲቲው በትምህርት ላይ ለነበሩ መምህራን ያላግባብ ከ7 ሚሊዮን በላይ ብር እንደከፈለ እና ተመላሽ እንዳላደረገ ተገልጿል
አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ 18 መምህራኑ ደብዛቸው እንደጠፉበት አስታወቀ፡፡
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የኦዲት ግኝት ሪፖርት ላይ መክሯል፡፡
የቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር እና የዩንቨርሲቲው አመራር አባላት በጋራ ባደረጉት ውይይት ላይ እንደተገለጸው ለሶስተኛ ድግሪ በሚል ለትምህርት የተላኩ እና የጠፉ የዩንቨርሲቲው መምህራን ጉዳይ ዋነኛው ነው፡፡
የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ እና የፌደራል ዋና ኦዲተር አመራሮች ዩንቨርሲቲው ለሶስተኛ ድግሪ ትምህርት ብሎ ስፖንሰር ሆኖ የላካቸው መምህራን በወቅቱ ትምህርታቸውን አጠናቀው እንዳልተመለሱ፣ ዩንቨርሲቲውም ለነዚህ መምህራን የከፈለውን ከ7 ሚሊዮን በላይ ብር ገንዘብ ለምን ተመላሽ አላደረክም? በሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር) ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስተኛ ድግሪ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ 18 መምህራን ትምህርታቸውን በተቀመጠላቸው ጊዜ አጠናቀው እንዳልተመለሱ፣ የመመለሻ ጊዜያቸውም እንዳለፈ መናገራቸውን በምክር ቤቱ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ በተላለፈው ላይ የቀጥታ ስርጭት ላይ ሲናገሩ ተደምጧል፡፡
በዩንቨርሲቲው ህግ መሰረት አንድ የዶክትሬት ወይም የሶስተኛ ድግሪ ትምህርትን ለማጠናቀቅ አራት ዓመት በቂ ሲሆን በተለያዩ አስቸጋሪ ምክንያቶች ትምህርቱን ማጠናቀቅ ላልቻሉ ደግሞ ሁለት ዓመት እንዲጨመርላቸው ይፈቅዳል ሲሉም ፕሬዝዳንቱ አክለዋል፡፡
ይሁንና እነዚህ የዶክትሬት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በተለያዩ ዩንቨርሲቲዎች ከተላኩ መምህራን መካከል ትምህርታቸውን በስድስት ዓመታት ውስጥ አጠናቀው ባለመምጣታቸው ከስራ
ነአመን ዘለቀ ፡ የፕያሳን ነዋሪ አዲስ አበቤ ለንቅለ ተከላ ግባቸው አፈናቀሉት፣ ማህበራዊ ትስስሩን ናዱት። ቅርሶችን አፈረሱ። በዛሬው ዜጎችን ማፈናቀል፣ ታሪክና ቅርስ ማውደም፣ በፒያሳ እንደማያቆሙ ባለፉት ጥቂት አመታት የአብይ አህመድና የኦሮሚያ ብልጽግና በአዲስ አበባ ህዝብ ላይ የፈጸሟቸው የክፋት፣ የመሰሪነት፣ የዘረኝነትና፣ የአግላይነት፣ ጸረ ደሃም ተግባራት ያረጋግጣሉ። ያለምንም ይሉኝታና ሀፍረት፣ ለዜጎች ርህራሄ አልባ ግፍ እንዲፈናቀሉ የተደረጉ መቶ ሺዎች፣”ህጋዊ ድሃ” የተድረጉ፣ ሰው መሳይ አውሬው የሸገር ከተማ ከንቲባ እንደነገረን በአዲስ አበባ ልዩ ልዩ አካባቢዎች ነዋሪዎችን በግፍ በማፈናቀል የፈጸሙት ይህ ነው የማይባል ግፍና ሰቆቃ በርክታ ማረጋገጫዎች ልባችን እየደማ እይተናል። በየአካባቢው ነባር ሰፈሮችን ማፈስ፣ ማህበራዊ ትስስሮችን መበጣጠስ፣ የአዲስ አበባ አዲስ አበባ ያደረጉ ቅርሶች ማውደምና መሰረዝ፣ ማንነትን መጨፍለቅ ይቀጥላል። አላማው ልማት አይደለም፣ ፓለቲካ ነው’’
በአለማችን የከተማ ልማት አስተሳሰብና ማእቀፍ/ፓራዳም/ፍሬምወርክ ፣ ዘላቂነት፣ ጽኑነት ፣ አካታችት ፣ ፍታዊነት/Environmental sustainability/Climate Resilience/Socially inclusive and just በሚሉ ዋና ዋና ማገሮች የሚመራ እየሆነ ነው፣ ይህም በበርካታ ሀገሮች ገዢ አስተሳሰብና አሰራር እየሆነ ይገኛል ። በ 2050 የአለማችን ህዝብ 70% የከተማ ነዎሪዎች እንደሚሆኑ የበርካታ ጥናቶች ትንበያ ያሳያል። ስለሆነውም ልማት የከተማውን ኢንፍራስታክቸሮች ማስፋፋት ብቻ ሳይሆን ጽኑ፣ ዘላቂ/እንዲሆኑ ፣ ዜጎች ፣ የከተማ ነዋሪዎች ማህበራዊና አካታችነት፣ ፍትሃዊነት፣ ኢኮኖሚ ጽናትና ዘላቂነት/ሶሻል ኢኮኖሚክ ስስተኔብሊቲ/ሬሲሊያንስ እንዲኖራቸው ማድረግን ታሳቢ ያደረገ የልማት አስተሳሰብ ማእቀፍ/ፍሬምወርክ ነው። በመሰረቱ ልማት መዳረሻውም ፣ መነሻውም ሰው ነው። የልማት ግብ የሰዎች፣ የማህበረቦች፣ የዚጎች ልማት ነው፣ የኮንክሪት ጫካ ወይንም ኮንክሪት ጃንግል
በምዕራብ አርሲ ዶዶላ ከተማ ላይ ትላንት ማታ 3:00 አከባቢ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ናቸው የተባሉ አንድ ካህንን ከእነቤተሰቡ እንዲሁም ካገባ ገና ሶስት ወር እንኳ ያልሞላውን ዲያቆን እና አብራው ስትኖር የነበራቸውን እህቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለዋቸው ሄደዋል ተብሏል።
ከሁለቱ ቤተሰቦች አጠቃላይ ሰባት ሰዎችን ገድለዋቸው ሄደዋል ብለዋል።
አንድ ህፃን እንደ አጋጣሚ ያለቤተሰብ ቀርታ ተርፋለች ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ ለስራ ከሲዳማ ክልል የመጡ አራት ወጣቶችም ተገድለዋል ብለዋል።
አጠቃላይ 11 ሰው ሞቷል ብለዋል።
ጥቃቱ የተፈፀመው ከገብረክርስቶስ ቤተክርስቲያን 50ሜርቀት ላይ ነው ብለዋል። ግድያውን የፈፀሙት በቢለዋና በጥይት ነው
“አሁን ቀብር ተፈፅሟል፣ የጭካኔ ግድያ የተፈፀመባቸው ለዘመናት በአካባቢው ያገለገሉ ሰዎች ጭምር ናቸው”
ሁለት የዶዶላ ደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች ከነቤተሰቦቻቸው በትናንትናው እለት መገደላቸውን በስፍራው ካሉ ሰዎች እና በደብሩ ቀደም ብለው ካገለገሉ አንድ አባት መረጃ ይጠቁማል።
በዚህ በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ያገለግሉ የነበሩ መሪጌታ ስምረት የተባሉ አባት ባለቤታቸውን እና ሁለት ልጆቻቸውን፣ እንዲሁም ዲያቆን ዳንኤል የተባለ አገልጋይ ከነባለቤቱ እና ሌላ አንድ ሰው ጋር በድምሩ ሰባት ሰው እንደተገደለ እነዚህ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
“አሁን ቀብር ተፈፅሟል፣ የጭካኔ ግድያ የተፈፀመባቸው ለዘመናት በአካባቢው ያገለገሉ ናቸው። ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ምሽት ሶስት ሰአት ገደማ ነው” ያሉኝ ምንጮች ከዚህ በፊትም በጥቅምት 2012 ዓ.ም ብዙ ሰዎች ተግድለው እንደነበር አስታውሰዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምን አለ ?
” … አንድ ሰው ያወጣው ትልቁ ገንዘብ 324 ሺህ ብር ነው ፤ 567 ደንበኞች ጠፍተዋል፤ የጠፉት ደንበኞች 9.8 ሚሊዮን ብር ነው ያወጡት ” – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህም መግለጫቸው ባንኩ አጋጥሞት ከነበረው ችግር ጋር በተያያዘ እስካሁን ስለደረሰበት ደረጃ አብራርተዋል።
ምን አሉ ?
– ችግሩ የት ጋር ነው ያጋጠመው ? የሚለው ላይ በባለሙያ ጥናት እየተደረገ ነው ገና አላለቀም።
– አርብ መጋቢት 6 በተፈጠረው የሲስተም ችግር ከ801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ተወስዶበት እንደነበርና 622 ሚሊዮን ያህሉን ወደ ባንኩ ተመላሽ ተደርጓል።
– ቀሪ 567 ግለሰቦች የወሰዱትን 9.8 ሚሊዮን ብር ማግኘት አልተቻለም።
– መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ምሽት ላይ ከ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ 8: 45 ድረስ ባለዉ ጊዜ ነው 25 ሺህ 761 ደንበኞች ብር 801.4 ሚሊዮን ነው የወሰዱት።
– ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በሂደቱ ዉስጥ የተሳተፉ 15 ሺህ ያህል የሂሳብ ቁጥሮች ተገኝተዋል።
– የሲስተም ችግር በነበረበት በወቅት 25 ሺህ 761 ደንበኞች ግብይት ፈጽመዋል። በዚሁ ሰዓት ችግር ያለበት 238 ሺ 293 ጊዜ ግብይት ተፈጽሟል። አንድ ደንበኛ በአማካይ ከ9 ጊዜ በላይ ግብይት ፈፅሟል።
– በእለቱ አንድ ወይም ሁለት ግብይት የፈጸሙ ደንበኞች ጥርጣሬ ውስጥ አልገቡም። ያለ አግባብ የተወሰደ ገንዘብ ከሂሳባቸው ተቀናሽ ተደርጎ እንደሚመለስ ተደርጓል። በአካውንታቸው ላይ በቂ
” ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚከተለው ነገር ሁሉ የአማራ ክልል ሙሉውን ኃላፊነት ይወስዳል ” – የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ ምን አለ
?
” የአማራ ክልል የትግራይ መሬት በካርታው በማስፈር የትምህርቱ ሰርዓቱ አካል በማድረግ እያስተማረበት ይገኛል ” ሲል የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ ከሰሰ።
” ክልሉ የትግራይ መሬት በሚመለከት በስርዓተ ትምህርቱ ያሰፈረው ካርታ ኃላፍነት የጎደለው ብቻ ሳይሆን የትግራይ ህዝብ ከፋፍሎ ለማጥፋት ያወጀው ዘመቻ በማስቀጠል በከፋ መልኩ እየሰራበት እንደሚገኝ ማረጋገጫ መሆኑ ተገንዝበናል ” ብሏል።
” የአማራ ክልል መንግስት በህዝባችን ላይ አየፈፀመው የቆየውና አሁንም በሃይል በያዛቸው የትግራይ አከባቢዎች እየፈፀመ የሚገኘው ግፍና መከራ ተሰሞቶት በመፀፀት ፈንታ ወደ ባሰ ታሪካዊ ስህተት መግባቱ በቀጣይነት ዋጋ እንደሚያስከፍለው በማወቅ በአስቸኳይ እርምት ማድረግ አለበት ” ሲል አስስቧል።
ካቢኔው ፤ ” የፌደራል መንግስት ከአሁን በፊት የፌደራል ተቋማት ዛሬ ደግሞ በአማራ ክልል እየተዘጋጁ ያሉ ኃላፊነት የጎደላቸው ካርታዎች እንዲያርማቸውና በጥፋት ፈፃሚዎች ላይ ተገቢ እርምጃ መውሰድ እየተገባው በዝምታ ማለፉ የጥፋቱ አካል መሆኑ የሚያመላክት ነው ” ብሏል።
” የትግራይ ህዝብና ጊዚያዊ አስተዳደሩ የፕሪቶሪያ ውል በተሟላ መልኩ በመፈፀም ሰላም እና መረጋጋት እንዲመጣ በከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ በሚሰሩበት ወቅት ፤ የአማራ ክልል የሰላም ሂደቱ ለማወክ ይህ መሰል ነገር ጫሪ ጥፋት ሆን ብሎ መፈፀሙ ሊሰመርበት ይገባል ” ሲልም ገልጿል።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ ፥ ” የአማራ ህዝብም ሆነ ሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች በአማራ ክልል መንግስት በትግራይ ህዝብ
ክፉ ቀን ሲዘከር
የዶ/ር ተስፋየ ደበሳይ የመጨረሻ ጽዋ ( ዶክተር መንግስቱ ሙሴ )
========================
መጋቢት 15 1969 ዓም ከእንጨት አልጋየ እንደተጋደምሁ ያንዘመን የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ዜና ስርጭትን ማዳመጥ የኢንፎርሜሽን ዋና መንገድ ነበር። ድፍን 1969 ዓም መልካም ዜና የሚሰማበት ዘመን አልነበረም ቀደም ብሎ በጥር 29 1969 የሆነው የድፍን ኢትዮጵያን ሕዝብ አፍ ያስጨበጠ የርእሰብሔሩን ጄ ተፈሪ በንቲ እና ሌሎች ባለስልጣናት መርዶን ሰምተን ነበር። ጄኔራሉ ያን ቀን ስለእርቅ መውረድ እና ሰላም ነበር ለሕዝብ ያቀረቡት የገጠማቸው ግን ሌላ ነበር።
በሁለተኛው ወር አጋማሽ መጋቢት 15 ቀን ግን የብዙ ዜጎች የሐገር ተስፋ የነበረው ምሁር እና የኢሕአፓው መሪ ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ማለፉን የምታውጀዋ ዜና በብዙ ወታደራዊ ማርሽ ታጅባ በተለመደው መርዶኛ ተነበበች።
እኔም ከተጋደምሁበት እንኳን ንቅንቅ ሳልል የዜናው ክፋት እና ምንነት አደመጥሁ በእጅጉም አስደነገጠኝ። ወቅቱ የትግል በመሆኑ ቀደም በነበሩ ቁልፍ እና አሳቢ የሐገር ልጆችን ገድሎ ያነን ለሕዝብ ለማርዳት የሚከተለው የዜና የፉከራ የፍየል ወጠጤ እና መሰል ዜናወች ልቤን ያነዱት ያበሳጩት እንጅ እንደዚህ ቀን ድንጋጤ ምርር ያለ ሐዘን አስከትለውብኝ አያውቁም ነበር።
“ተስፋየ ደበሳይ” ማን መሆኑን ያወቅሁም በዚህ ዜና ነው። ከወራት በፊት የእነ ብርሐነ መስቀል ረዳ፤ ጌታቸው ማሩ (ሀ እና ለ) አንጃ ፈጥሮ በመሰረቱት ድርጅት ላይ ተቃራኒ መሆናቸውን በድርጅት አስራር አውቄ ነበር። በተለየ የብርሐነ መስቀል ረዳ ጉዳይ በዚያ ዘመን የኢትዮጵያ አብዮታውያን ሁሉ የአፍ መፍቻ የነበር ግዙፉ ሰው በልዩነት መለየት በድርጅቱ እንቅስቃሴ
የፍትሕ ተቋማት በመንግስት አስፈጻሚ አካላት ላይ ክስ እንዲመሰረት አያደርጉም- የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም
የፍትሕ አካላት ለሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ስራዎች የማይተባበሩ የመንግስት አሰፈጻሚ አካላት ላይ ክስ እንዲመሰርት አይተባበሩም ሲል ተቋሙ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በአቤቱታ ቅበላ፣ ምርመራና የመፍትሄ ሀሳብ አፈጻጸምን በተመለከተ ባደረገው ውይይት እንደተገለጸው ከተቋሙ ክስ እንዲመሰረት ጥያቄ ቢቀርብም ተባባሪ ያለመሆን ችግሮች አሉ።
ዋና እንባ ጠባቂ እንዳለ ኃይሌ በኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገመንገስት አንቀጽ 37/1 ማንኛውም ሰው በፍርድ ቤት ወይም በሌላ በህግ የዳኝነት ስልጣን ለተሰጠው አካል ጉዳዩን የማቅረብና ውሳኔ ወይም ፍርድ የማግኘት መብት እንዳለው ይደነግጋል ብለው የመንግስት አስፈጻሚ አካላት ላይ ግን እየተፈጸመ እንዳልሆነ አመላክተዋል።
ዋና ዕንባ ጠባቂው የዜጎች ፍትሕ የማግኘት መብት ሲጓደል ሕዝብ በመንግስት ላይ ያለው አመኔታ እንደሚሸረሸር ገልጸዋል።
በመንግስት አስፈጻሚ አካላት ላይ የሚደርሰውን የአስተዳደራዊ በደል ችግሮች በዋነኛነት ለመቅረፍ ተጠያቂነት መረጋገጥ እንደሚያስፈልግ አጽንዖት ተሰጥቷል።
ዝቋላ ድጋሚ ሥጋት ገጥሞታል
በቅርቡ መነኮሳቱ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉበት የደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም መጠነኛ ጥበቃ ሲሰጠው የነበረው መከላከያ ትናንት እሑድ ገዳሙን ለቅቆ በመውጣቱ ድጋሚ ሥጋት ላይ መውደቁን የተላከልን መረጃ ያመለክታል።
ከዚህ በፊት ከመንግሥት ጋር በነበሩት ውይይቶች ገዳሙ ከሥጋት ነጻ የሚሆንበት ሥራ እንደሚሠራ ስምምነት ላይ መደረሱ የሚታወስ ሲሆን ምክንያቱ ለጊዜው ግልጽ ባልሆነበት ሁኔታ የመከላከያ ሠራዊቱ በምሽት ገዳሙን ለቅቆ መውጣቱ ማኅበረ መነኮሳቱ ላይ ከፍተኛ ሥጋት ፈጥሯል።
“የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡ እናሳስባለን” ብሏል ገዳሙ። (አደባባይ ሚዲያ)
ዋዜማ- የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በግፍና በኢ-ፍትሀዊነት ከቀየው ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) እንዲሰደድ የተደረገውን የኦሮሞ ሕዝብ ወደ ቀደመ ስፍራው እንዲመለስ እያደረግን ነው ሲሉ በይፋዊ ማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ተናግረዋል።
የኦሮሞ ሕዝብ ለዘመናት ሲደርስበት በነበረው መገፋት የተነሳ ከተማዋን ለሌሎች ለቆ እስከመውጣት ደርሷል ያሉት ሽመልስ፣ይህም መገፋት ሄዶ ሄዶ እትብቱ በተቀበረባት ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) የባዕድነት ስሜት እንዲሰማውና በራሱ ቀየ ላይ ባይተዋር እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል።
ከተማዋ በሌሎች የበላይነት ስር ሆና በተለይም የኦሮሞን ሕዝብ ለዘመናት እንደ ባዕድ የመመልከት አካሄድን ስትከተል ቆይታለች ያሉት ርዕሰ መሥተዳድሩ፣ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በከተማዋ አንዳችም የኦሮሞን ህዝብ ማንነት የሚገልጽ ምልክት (symbolic represention) አለመኖሩ ነበር በማለት ጠቁመዋል።
“ከዚህ በኋላ ግን መንግሥታችን፣ያለፈውን የውድቀት ታሪክ፣ጉዳትና መፈናቀል ማውራት፣ እንዲህ ተደረግን ብሎ ስሞታ ማቅረብ አይሻም” ሲሉ ገልጸዋል።
ይልቁንም የተገኘውን ዕድል በመጠቀም፣ትላንት በሕዝባችን ላይ ሲደርስ የነበረውን ግፍና በደል ለመካስ ብሎም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም አዲስ ምዕራፍ ከፍተን ወደ ሥራ ገብተናል ብለዋል።
በዚህም መሠረት፣መንግሥት በግፍ ከቀየው የተፈናቀለውን ሕዝብ በመመለስ በከተማዋ በሁሉም ዘርፍ ካሉ ዕድሎች ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ ይገኛልም ሲሉ ጠቁመዋል።
አዲስ አበባን በዚህ ወቅት ስንመለከት፣ በፖለቲካው፣በኢኮኖሚ፣በማኅበራዊ እንዲሁም በባሕል የሕዝባችንን ሰፊ ተሳትፎ የሚሹ እጅግ ግዙፍ የሆኑ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ይገኛሉ ያሉት ሽመልስ፣ይህም ሀሳባችንን ከግብ ለማድረስ ትልቅ መሳሪያ ይሆነናል ብለዋል።
እየተሠሩ ካሉት ከነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል፣የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣የኦቢኤን ሚዲያ
‹‹ምከረው ምከረው እንቢ ካለ መከራ ይምከረው›› የሚለው አገራዊው ዕድሜ ጠገብ ምሳሌያዊ አባባል፣ በግለሰብም ሆነ በአገር ደረጃ በሚፈጸም ስህተት ወይም ደንታ ቢስነት ሊከሰት የሚችለውን ጣጣ ቀድሞ ማመላከቻ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ከሚታወቁበት ምሳሌያዊ አነጋገር አንዱ፣ ‹‹የውድቀት ጥሪ የቀረበው የአዋቂ ምክር አይሰማም›› የሚለው ይጠቀሳል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ባህሉና የአኗኗር ዘይቤው ይለያይ ይሆን እንጂ፣ ምክር ለማይሰሙ ሰዎች የሚነገሩ በርካታ ምሳሌያዊ አነጋገሮች አሉ፡፡ አገር በቀል የሆኑት ምሳሌያዊ አነጋገሮች የሕዝቡን ዘመን ተሻጋሪ የጋራ ማኅበራዊ እሴቶችና መስተጋብሮች ከማንፀባረቃቸው ባሻገር፣ ለአገር ሰላምና ደኅንነት የሚጠቅሙ ህልቆ መሳፍርት የሌላቸው ምክሮችና ማሳሰቢያዎች በውስጣቸው ያጨቁ ናቸው፡፡ እነዚህ ምክሮችና ማሳሰቢያዎች ችግር አጋጥሞ በአገርና በሕዝብ ላይ መከራ ከመድረሱ በፊት፣ እንደ ቅድመ ማስጠንቀቂያ የሚያገለግሉ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገሩ እዚህ ዘመን የደረሱ ናቸው፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ካለፉት ስህተቶች ለመማር ፈቃደኝነት በመጥፋቱ በርካታ ወርቃማ ዕድሎች ማምለጣቸው ብዙ ጊዜ ተወስቷል፡፡ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት በየካቲት 1966 ዓ.ም. አብዮት ከመገርሰሱ ዓመታት በፊት፣ የአገር ጉዳይ ያሳሰባቸው ወገኖች ሥርዓቱ ማሻሻያ እንዲያደርግ በተደጋጋሚ ማሳሰባቸው ይነገራል፡፡ ፍፁም ፈላጭ ቆራጭ የሆነው ዘውዳዊ ሥርዓት ወደ ሕገ መንግሥታዊ ዘውድ ተለውጦ፣ የአገሪቱ መንግሥት ለፓርላማ ተጠሪ በሆነ ጠቅላይ ሚኒስትርና ካቢኔ እንዲመራ ልመና ቀርቦ እንደነበር በቁጭት ሲነገር ይደመጣል፡፡ በአገሪቱ የተንሰራፋው የፊውዳል ሥርዓት የመሬት ሥሪቱ ተስተካክሎ ዜጎች ከገባርነት እንዲወጡ የቀረበው ተደጋጋሚ የመሬት ለአራሹ ጥያቄ ምላሽ በማጣቱ፣ ለአብዮቱ መፈንዳትና ለሥርዓቱ መንኮታኮት ምክንያት እንደነበር አይዘነጋም፡፡ አብዮቱ ሥር ነቀል የለውጥ ጉዞ ውስጥ ገብቶ ለአገር የሚበጁ
መብታቸውን የሚጠይቁ ግለሰቦች ለተደጋጋሚና ረጅም እስር ተዳርገዋል- የኢሰመኮ ብሔራዊ ምርመራ
👉🏿 ማሰቃየትና ኢ ሰብዓዊ አያያዝ እንዲሁም የዘፈቀደ እስር ከፍተኛ ነበር
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለአምስት ዓመታት በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ እና የቀድሞ ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች ያካሄደውን የዜጎች ነጻነት የተመለከተ ብሔራዊ ምርመራ ይፋ አደረገ።
ኮሚሽኑ በሪፖርቱ ማሠቃየት እና ኢ-ሰበአዊ አያያዝ ሲል የጠቀሳቸው ደብዛን አጥፍቶ ማሰርን፣ በግዳጅ መሰወር፣ በእስር ቤቶች ውስጥ ክብርን ያልጠበቁ አካላዊ ፍተሻዎች፣ በቂ ምግብና ውሃ በሌላቸው፣ በተጨናነቁ፣ የንፅሕና እና የሕክምና አገልግሎት በሌላቸው እስር ቤቶች ማሰር አንዱ ግኝት ነው።
መብታቸውን የሚጠይቁ ግለሰቦችን ከድርጊቶቻቸው ለማስቆም በተደጋጋሚ እና ለረጅም ጊዜ አስሮ ማቆየት፣ መደበኛ ባልሆኑ ቦታዎች ማሰር፣ የተጠርጣሪ ቤተሰብ አባላትን በምትክ ማሰር፣ በአደራ እስረኛነት ሰበብ ፍርድ ቤት ሳያቀርቡ ለረዥም ጊዜ ማረሚያ ቤት ማቆየት፣ ፍርድ ቤት የሰጠውን የዋስትና መብት በመጣስ ማሰርን እንዲሁም መንግሥትን በፍትሐብሔር ጉዳዮች የከሰሱ ግለሰቦችን ማሰርን የመሰሉ የዘፈቀደ እስርም በክልሎቹ ተፈጽመዋል።
ከኮሚሽኑ ሪፖርት እንዳመለከተው የሕግ አማካሪ ጋር መገናኘትን መከለከል፣ የቤተሰብ ጉብኝት መከልከል፣ ወሲባዊ ትንኮሳና ጥቃት፣ የመተዳደሪያ ገቢ ማጣት፣ ስለ ሰብዓዊ መብቶች በቂ ግንዛቤ አለመኖር እና ለጥሰቶቹ መፍትሔ እንዲሁም ማካካሻ ስርዓት አለመኖሩ ዋነኛ ችግሮች መሆናቸው በብሄራዊ ምርመራው ታውቋል።
በምርመራ ሪፖርቱ መሰረት “የሰብአዊ መብቶች ጥሰቱ የተፈጸመው በሚሊሻ አባሎች፣ የቀበሌ አስተዳዳሪዎች፣ የመደበኛ ፖሊስ አባላት፣ በቀድሞው የልዩ ኃይል ፖሊስ አባላት፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት እና የመንግሥት ኃላፊዎች ነው”።
ኢሰመኮ ከሚያዝያ
የሕዝብ ተመራጮች የኾኑት ክርስትያን ታደለ፣ ዮሃንስ ቧያለው፣ ካሳ ተሻገርና ሌሎች እስር ቤት የሚገኙ 11 ተጠርጣሪዎች “አካላዊ፣ ሞራላዊና ሥነ ልቦናዊ ጥቃት” እየተፈጸመባቸው እንደኾነ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለጠቅላይ ፍርድ ቤትና ለፍትህ ሚንስቴር በደብዳቤ አቤቱታ ማቅረባቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል።
ተጠርጣሪዎቹ በደብዳቤያቸው፣ ለከፍተኛ የምግብ እጥረትና ለጊዜያዊና ቋሚ በሽታዎች ተጋላጭ እንድንኾንና ከቤተሰብ፣ ከጠበቃ፣ ከኃይማኖት አባቶች፣ ከመብት ድርጅቶችና ከሌሎች ጠያቂዎች ጋር እንዳንገናኝ ተደርገናል ማለታቸውን ዘገባው አመልክቷል።
ዘገባው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነትን መሠረት ያደረጉ ስድቦች፣ ዘለፋዎች፣ ዛቻዎችና ድብደባዎች እንደተፈጸሙባቸው ጠቅሰዋል ብሏል።
ፌዴራል ፖሊስ ጉዳዩ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መርማሪ ቦርድን እንደሚመለከት በመግለጽ፣ በአቤቱታው ዙሪያ ምላሽ እንዳልሰጠ ዜና ምንጩ ጠቅሷል።
ኢሰመኮ፣ ነጻነታቸውን በተነፈጉ ሰዎች ላይ “ተደጋጋሚ” እና “ስልታዊ” የመብት ጥሰቶች እንደሚፈጸሙባቸው ማረጋገጡን አዲስ ባወጣው የምርመራ ሪፖርት አስታውቋል።
ኢሰመኮ ይህን ያለው፣ ከ2010 እስከ 2015 ዓ፣ም በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌና የቀድሞው ደቡብ ክልሎች ያደረገውን ምርመራ አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት ነው።
ኮሚሽኑ በሪፖርቱ፣ መደበኛ ባልኾኑ ቦታዎች ማሰር፣ የፍርድ ቤት ዋስትናን አለማክበር፣ የዘፈቀደ እስር፣ ወሲባዊ ጥቃት፣ ደብዛን ማጥፋት፣ በቂ ምግብና ውሃ በሌላቸው ቦታዎች ማሰር፣ ማሠቃየትና በቤተሰብ እና በሃይማኖት አባትና በሕግ አማካሪ አለመጎብኘት ተጠቃሽ የመብት ጥሰቶች እንደኾኑ ገልጧል።
ኢሰመኮ፣ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት የመብት ጥሰቶቹን በማስቆም ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈልጉና ጥሰት ፈጻሚዎችን ተጠያቂ ለማድረግ ቁርጠኛ እንዲኾኑ ጠይቋል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በትግራዩ ጦርነት ወቅት የተማረኩ 112 የመከላከያ ሠራዊት አባላትን ትናንት “በምኅረት” ከእስር እንደፈታ አስታውቋል።
ከእስር የተፈቱት የሠራዊቱ አባላት “በከባድ ወንጀል” ተጠርጥረው በእስር ላይ የቆዩ እንደኾኑ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጧል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ ምርኮኛ የሠራዊቱን አባላት የፈታው፣ በቅርቡ በአፍሪካ ኅብረት አስተባባሪነት ፌደራል መንግሥቱና ሕወሃት ባደረጉት የግጭት ማቆም ስምምነት ግምገማ ላይ በተደረሰ መግባባት መሠረት እንደኾነ ጠቅሷል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ፌደራል መንግሥቱ የትግራይ ተወላጅ የኾኑ የሠራዊቱን አባላት በተመሳሳይ ይለቃል ብሎ እንደሚጠብቅ ገልጧል።
የአቶ ታዬ ደንደአ ምርመራ ተጠናቅቆ ለጠቅላይ ዐቃቤ ህግ መላኩን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስታወቀ
ከሶስት ወራት በፊት ከሰላም ሚኒስትር ዴኤታነታቸው ከተነሱ በኋላ በቁጥጥር ስር በዋሉት አቶ ታዬ ደንደአ ላይ የጀመረውን ምርመራ አጠናቅቆ ለፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ መላኩን የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ፖሊስ ይህን ያስታወቀው፤ የአቶ ታዬን “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ እየተመለከተ ለሚገኘው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በሰጠው ምላሽ ነው።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጉዳዩን መመልከት የጀመረው፤ በአቶ ታዬ ጠበቃ በኩል የቀረበውን አቤቱታ ባለፈው ሰኞ መጋቢት 9፤ 2016 ከተቀበለ በኋላ ነው። “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው በሶስት ገጾች የተዘጋጀው አቤቱታ፤ የፌደራል ፖሊስ የአቶ ታዬን “በነጻነት የመዘዋወር ሕገ መንግስታዊ መብት በመጣስ”፣ “ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ”፣ “ህገወጥ በሆነ መንገድ” ያሰራቸው መሆኑን የሚያትት ነው።
አቶ ታዬ በጠበቃቸው በኩል ባቀረቡት በዚህ አቤቱታ ማገባደጃ ላይ፤ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ ልደታ ምድብ፤ ስምንተኛ የፍትሐብሔር ችሎት ጉዳያቸውን ተመልክቶ ዳኝነት እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። በዚህም መሰረት የፌደራል ፖሊስ “ወደ ፍርድ ቤት እንዲያቀርባቸው” እንዲደረግ እና ፍርድ ቤቱም አቶ ታዬ “የታሰሩበትን ምክንያት በማጣራት የአመልካችን አካል ነጻ እንዲያወጣቸው” በአቤቱታው ጥያቄ ቀርቧል። አመልካች በ“አፋጣኝ ከህገ ወጡ እስራት እንዲለቀቁ”፤ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለፌደራል ፖሊስ “ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸውም” በአቤቱታቸው አመልክተዋል።
* ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/12819/
30 ሺህ ሰው ያሳተፈው ‘ብኩን’ ፊልም! ኤሊያስ መሰረት
ከትግራይ እስከ አማራ እና አፋር ክልሎችን አዳርሶ ቢያንስ 600,000 ሺህ ህዝብ እንዳለቀበት የሚገመተው የሰሜኑ ጦርነት ዳፋ ገና ተነግሮ እንኳን አላለቀም።
በውጊያ ወቅት ሞተው አስከሬናቸው ገና ያልተቀበሩ በርካቶች አሉ፣ የአካል ጉዳተኞች ዊልቼር ሳያገኙ መሬት ለመሬት እየዳሁ እያየን ነው፣ የተደፈሩ ሴቶች ስነ ልቦና ገና አልተጠገነም፣ የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሚደረገው እንቅስቃሴ ገና ከመሬት አልተነሳም፣ የሰላም ስምምነቱን ማፅናት ላይ እንኳን ከሰሞኑ እንደሰማነው ውይይት ገና እየተደረገ ነው።
በዚህ ሁሉ መሀል በታንክ፣ ጀት፣ መድፍ፣ ክላሽ እና RPG የታገዘ በጭካኔ የተገዳደልንበትን ፊልም በ30 ሺህ ህዝብ አጅቦ የሚተርክ ፊልም በተለይ አሁን ባለንበት ወቅት ምን ሊጠቅመን ነው?
ዳግም ግጭት የመቀስቀስ ሙከራ ወይስ ሌላ? በዚህ ፊልም እናት፣ አባት፣ እህት፣ ወንድም… ወዘተ ለዘላለም ያጡ ወገኖች አሟሟታቸውን በፊልሙን ቢመለከቱ ምን ይሰማቸዋል?
ከማውቃቸው ሰዎች ተደጋግሞ እንደሰማሁት የፊልሙ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ ፊልሙ በብዙ መቶ ሚልዮን ብሮች እንደወጣበት፣ በመንግስት በኩል የቁሳቁስ እና የሰው ሀይል ድጋፍ ተደርጎለት እንጂ ተጨማሪ ብዙ መቶ ሚልዮን ብሮች ሊያስወጣ የሚችል ፊልም እንደሆነ ተናግሯል።
ሌላው ቀርቶ በቅርቡ ወደ አሜሪካ ፊልሙን ለትርዒት ይዞ በሄደበት ወቅት “ፊልሙን እዚህ አሜሪካ ተቃውመው የሚንከባለሉ ሰዎች ይኖራሉ” ሲል እንደነበር በስፍራው የነበሩ ሰዎች አጫውተውኛል።
ጊዜውን ያልጠበቀ ‘ብኩን’ የሆነ የ image ግንባታ ፊልም ብዬዋለሁ። Timing የሚባል ነገር ወሳኝ ነው። ኤሊያስ መሰረት
የዓለማቀፉ ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ልዑካን ቡድን ማክሰኞ’ለት አዲስ አበባ መግባቱን ብሉምበርግ ዘግቧል።
ልዑካን ቡድኑ ላንድ ሳምንት ቆይታ አዲስ አበባ የገባው፣ መንግሥት ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብሩ ማስፈጸሚያ በጠየቀው ብድር ዙሪያ ከፋይናንስ ሚንስቴርና ከብሄራዊ ባንክ ባለሥልጣናት ጋር ለመወያየት ነው። w
ኢትዮጵያ ከድርጅቱ ጋር በጠየቀችው ብድር ዙሪያ እስከ ጥር 23 ገደማ ከስምምነት ላይ ካልደረሰች፣ አበዳሪ አገራት እስከ ቀጣዩ የአውሮፓዊያን ዓመት የሰጧትን የብድር መክፈያ እፎይታ እንደሚሰርዙ ቀደም ሲል አስጠንቅቀዋል።
መንግሥት ከድርጅቱ የጠየቀው ብድር 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ነው። የድርጅቱ ልዑካን ቡድን ካኹን ቀደም ወደ ኢትዮጵያ ተጉዞ በብድር ጥያቄው ዙሪያ የተወያየው ባለፈው ጥቅምት ወር ነበር።
እያሳሰበ የመጣዉ የአዲስ አበባ ከተማ የደህንነት ጉዳይ
መዲና አዲስ አበባ ውስጥ አንድ ታዋቂ የቀዶ ህክምና ባለሙያ መገደል እየተዘገበ ነዉ። ታዋቂው የቀዶ ህክምና ባለሙያ ዶክተር በሃይሉ ሃይሉ ባለፈው እሁድ የጠዋት ወትሮ እንደሚያደርጉት ለስፖርት ሩጫ ለማድረግ ከቤት ወጥተዉ አልተመለሱም።
ቤተ ዘመዶቻቸዉ ከሩጫ ባለመመለሳቸዉ ሲጠብቁ እንደነበር እና በመጨረሻ አስከሬናቸዉ መንገድ ላይ መገኘቱ ተዘግቧል።
ፖሊስ እስካሁን ስለ ዶ/ሩ ግድያ በይፋ የሰጠዉ ዝርዝር መረጃ የለም።
ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ መዲና አዲስ አበባ ዉስጥ እየጨመረ የመጣዉ የግድያ እና የዘረፋ ወንጀል የከተማዉን ነዋሪ አሳስቧል።
አምባ ዲጂታል፤
ከስድስት ዓመት የእስር ቤት ቆይታ በኋላ ባለፈው ሳምንት መጋቢት 5፣ 2016 የተለቀቁት የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) ከእስር ቤት መልስ የፌዴራል መንግሥት አዲስ ሹመት ሊሰጣቸው እንደሚችል የዘገበው አፍሪካ ኢንተሊጀንስ ነው።
የአሁኑ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው ከዓመታት በፊት ጀምሮ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው የሠሩት አብዲ፣ በክልሉ ውስጥ ከተፈጸሙ በርካታ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ግድያዎች እና የመንግሥት ሐብት ብክነት ጋር በተያያዘ ነበር የታሠሩት።
በቀድሞው ርዕሰ መስተዳደር ላይ ከቀረቡባቸው ክሶች መካከል በ2010 የክረምት ወራት ውስጥ በሶማሌ ክልል የእርስ በርስ ግጭት እንዲፈጠር ለማድረግ በማሰብ ‘ሄጎ’ በሚል ሥያሜ የሚታወቅ ወጣቶች ቡድን አደራጅተዋል የሚል ይገኝበታል።
በወቅቱ በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጂግጂጋ በተፈጸመ ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸው፣ ንብረት እና አብያተ ክርስቲያናት ላይ ጉዳት መድረሱ ይታወቃል።
ነሐሴ 2010 አዲስ አበባ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውለው በእስር ላይ የቆዩት አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር ባለፈው ሳምንት ከእስር የተለቀቁት ዐቃቤ ሕግ ክሱን በማንሳቱ መሆኑ ተነግሯል።
አፍሪካ ኢንተሊጀንስ አብዲ ኢሌ በፌዴራል መንግሥቱ ውስጥ ሹመት ያገኛሉ ከማለቱ ውጭ በየትኛው ቦታ ላይ እንደሚሆን አልጠቀሰም። የዜና ድረ ገጹ አብዲ የፌዴራል መንግስቱን ሹመት ባያገኙ እንኳን ቱርክን መሳይ አገራት ሊላኩ እንደሚችሉ ጠቁሟል።
ከእስር ቤት መልስ ለሹመት ታጭተዋል የተባሉት የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳደር፣ ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ ከባህር በር ጋር በተገናኘ ባኮረፈቻት ጎረቤት ሱማሊያ በርካታ ወዳጆች እንዳሏቸው
አምነስቲ ኢንተርናሽናል የአሜሪካው የጆ ባይደን አስተዳደር በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ለተፈጸሙ ወንጀሎች “ፍትህና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ምንም ዓይነት አዲስ የፖሊሲ ለውጥ አላደረገም” በማለት ተችቷል።
አምነስቲ፣ አሜሪካ ተጎጂዎች ፍትህ እንዲያገኙና ተጠያቂነት እንዲሰፍን እንድትደግፍ ጠይቋል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከንም፣ ፍትህ እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን በጦርነቱ የጦር ወንጀልና በሰብዓዊነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች ተፈጽመዋል በማለት ቀደም ሲል ያሳለፉትን ብያኔ እንዲያድሱ አምነስቲ ጠይቋል።
ብሊንከን ከአፍሪካ ኅብረትና ከዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ጋር በመተባበር ሠራዊቱ በአማራ ክልል ሲቪሎችን ዒላማ ማድረጉን መንግሥት እንዲያስቆም እንዲጠይቁም ጥሪ አድርጓል።
አምነስቲ፣ ብሊንከን በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች በሚካሄዱ የትጥቅ ግጭቶች በሚፈጸሙ ጥሰቶች ላይ የዓለማቀፍ ወንጀል ብያኔ እንዲሰጡም ጠይቋል።
በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በትጥቅ የታገዘ የጎሳ ግጭት በድጋሚ ማገርሸቱን ዋዜማ ከምንጮች ሰምታለች።
ግጭቱ ያገረሸው፣ በልዩ ወረዳዋ አራት ቀበሌዎች እንደኾነ ምንጮች ተናግረዋል።
የክልሉ መንግሥት በልዩ ወረዳዋ የተወሰኑ ቀበሌዎች በዋናነት በአኝዋክ እና ኑዌር ጎሳዎች መካከል ለሚቀሰቀሰው የጎሳ ግጭት ዘላቂ መፍትሄ ለማስገኘት በርካታ ሕዝባዊ ውይይቶችን ቢያደርግም፣ እስካኹን ግጭቱን በዘላቂነት ማስቆም አልተቻለም።
በተደጋጋሚ በተከሰቱትና ወደ ጋምቤላ ከተማ ጭምር በተዛመቱት ግጭቶች የበርካቶች ሕይወት መጥፋቱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከጥቂት ሳምንታት በፊት መግለጡ ይታወሳል።
ከአማራ ፋኖ በጎንደር የተላለፈ የጀግና መሪያችን ሽኝት እና የ‹‹ዘመቻ ውባንተ›› ጥሪ!
አገር ሰሪው ታላቁና ጀግናው የአማራ ሕዝብ ባለንበት በ21ኛው ክ/ዘመን እንደ ሕዝብ ለከፋ የሰብዓዊ ቀውስና ምስቅልቅል ተዳርጎ፣ በሀገሩ ላይ የዘር ማፅዳትና ማጥፋት ዓለማቀፍ ወንጀል እየተፈፀመበት፣ በአገዛዙ የጀምላ ፍጅትና ጦርነት ታውጆበት፣ ህልውናው ከምን ግዜውም በላይ የከፋ አደጋ ላይ ወድቆ ይገኛል።
ይሁንና በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የአምደ ፅዮንን ጦር የመዘዙ እልፍ የአማራ ሙሴዎች ጠላቶቹን አምበርክከው የቀደመ ልዕልናውን ለማስመለስ በአንድነት በመነሳት አማራነትን በሞታቸው እያፀኑት ይገኛል። ከእነዚህ ቁጥር ስፍር ከሌላቸው ጀግኖች መካከል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ172 በላይ አውደ ውጊያዎችን በታላቅ ጀብዱ የመራው አርበኛ ሻለቃ ውባንተ አባተ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
ከእነዚህ አውደ ውጊያዎች ውስጥ 128ቱን በቀጥታ ግንባር ሆኖ በከፍተኛ ጀብዱ ያዋጋ ሲሆን፤ ቀሪውን 44 አውደ ውጊያዎች ከዋና ማዘዣ ኮማንድ ቦታ በመሆን በጀግንነት፣ በጦር ጥበብና ስትራቴጂዊ በሆነ ወታደራዊ ስምሪት በመስጠት የጠላትን አከርካሪ እንደሰበረ የሻለቃ ውባንተ አባተ የጦር ሜዳ ውሎ ሪከርድ ያስረግጣል፡፡ በዚህም በማይገመት ሁኔታ እጅግ አደገኛ ጸረ-አማራ የአገዛዝ መዋቅር ተተክሎበት የነበረውን ደቡባዊ የጎንደር ቀጠናን ከጠላት በማጽዳት የቴዎድሮስን መንፈስ በክብር ወደቦታው የመለሰ፣ ወትሮም ቀጠናው ይታወቅበት የነበረውን የጀግንነት ካባ በዚህ በኛ ዘመን መልሶ አጎናጽፎታል፡፡ ይህ የማይሞት ታሪክ ሲከወን ሕዝባዊ መሠረቱ እንደተጠበቀ ሆኖ የጦሩ ገበሬ ሻለቃ ውባንተ አባተ የአዲሱ ታሪክ ምዕራፍ መሐንዲስ ሆኖ ለዘላለም ሲዘከር ይኖራል፡፡
በዚህ የአማራን ሕዝብ ህልውና ለማስቀጠልና የህይወትን መስዋዕትነት ጭምር በሚጠይቅ
የአብይ አህመድ አገዛዝ ለአዲስ አበባና ለከተማዋ ነዋሪዎች ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻ ላለፉት ስድስት ዓመታት ስናየው የከረምነው እውነታ ነው ። ለዚህ ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልግ ዓለም ያወቀው ተግባሩ ምስክር ነው ። ይህ ጥላቻው ከእለት ወደ እለት እየባሰበት መጥቶ ዛሬ ላይ መላ አዲስ አበባን ወደማፈራረሱ አድርሶታል ።
ዛሬ አዲስ አበባና ታሪኳ በአዳነች አቤቤ አጥፊ ሀይሎች እየተናዱ ፣ እየጠፉና እንዳልነበሩ እየሆኑ ነው ። አዲስአበባ ትላንቷን እያጣች ማንነቷን እየተነጠቀች ትገኛለች ። አዲስ አበባን ዘረኞች እያረሷት ፣ ተረኞች እያወደሟት ይገኛሉ ። ትዝታዋ እየተፋቀ በታሪክ አልባና እሷን በማይመስል ማንነት እየተዋጠች እንደሆነ እዚህም አዚያም በልማት ስም የሚደረጉ ተግባሮች ማሳያ ናቸው ።
ነዋሪዋ እየተፈናቀለ በነዋሪው ህይወት ፈንታ ችግኝ ተከብሮ እየተተከለባትም ትገኛለች።በከተማችን ሠውነት ረክሶ ዛፍ ከብሯል ። ዜግነት ተጥሎ የሚያብለጨልጭ መብራት ነግሷል ። አዲስ አበባን የማያውቋት አዲስ አበባን እያጠፏት ነው ስንልም በምክንያት ነው ። ፍቅር ላበደረ በቀል፣ይቅርታን ለለገሰ ቂም ፣ ሠላምን ለናፈቀ ቁርሾ መስጠት የአዲስ አበባና የብልጽግና ህይወት ከሆነ ሰነባብቷል ።
ግብግቡ እናጠፋችኃለን አንጠፋም ቢሆንም እውነቱን ለመናገር ለብልጽግና የጥፋት እጆች መዘርጋት የእኛ የአዲስ አበባ ልጆች ዝምታ የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው መካድ አይቻልም ። ይህ ዝምታችን በበዛ መጠን የመጥፋት መጠናችንም አብሮ ይጨምራል ። የአዲስ አበባ ህዝብ የብልጽግና ልክ ያለፈ የጥፋት እጆችን ለመቁረጥ ትግል እየጀመረ መምጣቱን የተረዳው አገዛዙ ሰሞኑን ደግሞ ሳይቀድሙኝ ልቅደማቸው በሚል እሳቤ ይመስላል ጥፋቱን በእጥፍ አጠናክሮ ቀጥሏል ። የአማን እንቅስቃሴ ፣
ርዕሷ ፈርሷል!
(አሌክስ አብርሃም)
አዲስ አበባ የብሎኬትና የእንጨትና የጭቃና ስሚንቶ ውጤት አይደለችም ፤ የታሪክ የስልጣኔና የማንነት ክታብ ናት! ፒያሳ ደግሞ የዚህ ክታብ ርዕስ ነበረች! አሁን አዲስ በልጆቿ ልቦና ርዕሷ የፈረሰ ፅሁፍ ናት!
ከገጠር መጥተው ከተማ የሚያስተዳድሩ ፣ ከከተማም ሄደው ገጠር የሚያስተዳድሩ ሰዎች መሠረታዊ ከተማንና ከተሜነትን ፣ ገጠርና ገጠሬነትን የመረዳት ችግር እንዳለባቸው በብዙ ማስረጃ መተንተን ይቻላል! የቱንም ያህል ከተማ ቢኖሩ፣ የፈለገ ስልጣን እውቀትና ገንዘብ ቢኖራቸው ከተሜውም ገጠሩን ገጠሬውም ከተሜውን የመሆን ሙሉ እድል አይኖራቸውም! ለምን? ማንም ሰው ያደገበትን ስነልቦና በአንድ ጀምበር ነቅሎ መጣል አይችልም ! በብዙ ጀምበርም መንቀል አይችልም! የራሱን የተዛባ አመለካከት ነቅሎ ከሚጥል ይልቅ የሌሎችን መገለጫ ቢነቃቅል ይቀለዋል!
ለውጥን አሮጌ እና አዲስ በሚል መንገድ ብቻ ነው የሚረዱት! አሮጌ ማለት ከጭቃና እንጨት፣ ከስሚንቶና ብረት የተገነባ ብዙ ዘመን ያስቆጠረ ቤት ማለት አይደለም ፣ማንነት ነው፣ ሰዎች ዕድሜ ከፍለው የገዙት የጊዜ አሻራ ነው፤ አሻራው ነፍስ ላይ ስለሚታተም ላልኖረበት ላላደገበት ላልተሳተፈበት አይታይም! የሚታየው አሮጌ ጣራና ግድግዳ ነው። እንከን ቢኖር እንኳን እንደቀዶ ጥገና በጥንቃቄ ሊታረሙ የሚገቡ የከተማ ላይ አይነኬ ቅርሶች በግሬደር ሲፈራርሱ ማየት የአፍራሹንም ስብዕና ከህዝቡ አዕምሮ የሚያፈራርስ አጥፊ ድርጊት ነው!
ይሄ የማንነት ቀውስ እንዳለ ሆኖ በዛ ላይ አስተዳደሩ ላይ ሙስና ፣የተጣመመ የፖለቲካና መሀበራዊ አመለካከት ፣ የቅጥፈት ትርክት ፣ጥላቻ የመሳሰሉት ጉዳዮች ሲጨመሩ አውዳሚ ማንነት ይፈጠራል! ያኔ የሌሎች አሻራ አያሳየኝ የራሴን ላስቀምጥ ወደሚል እብሪት ይቀየራል። የሆነ ሁኖ በሰሞኑ
የሳሞአው ስምምነት ከምን ደረሰ ?
ኢትዮጵያ ከ79 ሀገራት ጋር የፈረመችው የሳሞዓ ስምምነት እስካሁን ለፓርላማ አለመቅረቡን “ ስለ ኢትዮጵያ ዝም አንልም ትውልዱን ከግብረሰዶም እንታደግ ” ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
ኢትዮጵያን ጨምሮ አጠቃላይ 79 የአፍሪካ እና የካረቢያንና ፓስፊክ ሀገራት (48 ከአፍሪካ፣ 16 ከካረቢያን፣ 15 ከፓስፊክ) ሳሞአ ላይ አንድ ስምምነት መፈራረማቸው ከወራት በፊት ተዘግቦ ነበር።
የተፈረመው ስምምነት ” የአፍሪካ፣ የካረቢያን እና የፓስፊክ ሀገራት ከአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ጋር የሚያደርጉት የንግድ እና ኢኮኖሚ ትብብር ” መሆኑ፣ ምስምነቱ 22 ዓመታትን የዘለቀ ” የኮቶኑ ስምምነት ” ቀጣይ እንደሆነ በወቅቱ መብራራቱ አይዘነጋም።
ይህንኑ ስምምነት በበርካታ ሀገራት ጥያቄ አስነስቶ ነቀፌታ ሲያስተናግድ የተስተዋለ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ የዘርፉ ተቋማት በበኩሉቸው ስምምነቱን ” ትውልድ ገዳይ ” ሲሉ አውግዘውታል።
“ ስለ ኢትዮጵያ ዝም አንልም ትውልዱን ከግብረሰዶም እንታደግ ” የተሰኘው ማኀበር፣ ኢትዮጵያ ከ79 አገራት መካከል አንዷ ሆና የሳሞዓ ስምምነትን እንደፈረመች፣ ስምምነቱ ግብረሰዶማዊነትን ማስፋፊያ ሃሳብ መያዙን በአንክሮ በማስረዳት፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ውድቅ እንዲደረግ (እንዳይጸድቅ) ጠይቆ ነበር።
ይህን ተከትሎም ጉዳዩ ከምን ደረሰ ? ፓርላማ ላይ ቀርቦ እንዳይጸድቅ ተደረገ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማኀበሩ ፕሬዚዳንት ሊቀ ትጉሃን መምህር ደረጀ ነጋሽ (ዘወይንዬ) ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ “ አላቀረቡትም እነርሱም ቁጭ ብለዋል። ግን ብዙዎቹን አናግረናቸዋል፣ ብዙዎቹ አልወደዱትም። እነርሱም ፈርተው ነው እስካሁን ያላቀረቡት ” ብለዋል።
ያለውን ሂደት በተመለከተ ባስረዱበት አውድ ፥ “ በዚሁ ዙሪያ እኛም የግንዛቤ ማስጨበጫ እየሰጠን
” ስለ ትውልዱ ግድ ይለናል የምትሉ ኃላፊዎች መፍትሄ ስጡን ” – ተማሪዎቹ
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፤ ” መፍትሄ የሚሰጠን አጥተን ያለ ትምህርት ቤታችን ቁጭ ብለናል ፤ ጊዜያችንም እየተቃጠለ ነው ” ሲሉ አማረዋል።
የባህር ዳር ዩንቨርሲቲ የ2016 ዓ/ም የ1ኛ ዓመት እና የሬሚድያል ተማሪዎች ወደ ግቢ እንዲገቡ ጥሪ ተደርጎላቸው በኃላም መራዘሙ ይታወሳል። ነገር ግን እስካሁን ምንም አይነት ጥሪ አልተደረገላቸውም ፤ ተማሪዎቹም የትምህርት ገበታቸው ላይ መገኘት አልቻሉም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዚህን ተማሪዎች ጉዳይ እየተከታተለ ተደጋጋጋሚ የመረጃ ልውውጥ ማድረጉ ይታወሳል።
አሁንም ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል ፤ ሌላ ቦታ ያሉ እኩዮቻቸው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ፣ እነሱ ያለ ትምህርት እድሜያቸው እየሄደ ፣ የራሳቸው መፍትሄ እንዳይወስዱም ጊዜው እየገፋ መሄዱን በመግለፅ ቁርጥ ያለ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በድጋሚ ጠይቀዋል።
” የሚጠሩን ከሆነ ይጥሩን ፤ የማይጠሩን ከሆነም ይንገሩን ፤ አልያም ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ሌሎች ተቋማት ይመድበን እየደረሰብን ያለው የስነልቦና ጫና ከባድ ነው ” ብለዋል።
ስለ ትውልዱ ግድ ይለናል የሚሉ ኃላፊዎች መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ያነጋገራቸው አንድ የዩኒቨርሲቲው አካል ተቋሙ ተማሪዎችን ያልጠራበት ምክንያት በአካባቢው ካለው ደህንነት ጋር በተያያዘ መሆኑን መግለፃቸው ይታወቃል።
ተቋሙ ተማሪ አልጠራም ማለት እንደማይችል ፤ ከዛ ይልቅ አንፃራዊ ሰላም ሲኖር አስገብቶ በ45 ቀን 1 ሴሚስተር አስተምሮ ሊያካክሰው እንደሚችል (ልክ ከአሁን በፊት በኮሮናና ጦርነት እንደተደረገው) ተናግረው ነበር።
ከዚህ ቀደም ” በአካባቢው ተማሪዎችን ለመጥራት አስቻይ ሁኔታ ከሌለ ለምን የልጆቹ ጊዜ ይቃጠላል
የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ በተያዘው ዓመት ምንም ስኳር አለማምረቱን የመንግሥት ዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ፋብሪካው ስኳር ያላመረተው፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ምንጩ የኾነው የቁንዝላ ኃይል ማመንጫ ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ብልሽት ስለገጠመውና በፋብሪካው ላይ የማሽን አቅርቦት እጥረት በመፈጠሩ እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል።
ፋብሪካው ዘንድሮ 183 ሺህ ኩንታል ስኳር እንዲያመርት ታቅዶ የነበረ ሲኾን፣ ከጅምሩ ሲገነባ ግን በቀን 12 ሺህ ቶን ስኳር የማምረት አቅም እንዳለው ተገልጦ ነበር።
በጋምቤላ ከተማ ሰሞኑን በጸጥታ ስጋት ሳቢያ የነዋሪዎች የዕለት’ተለት እንቅስቃሴ መገደቡንና ውጥረት መስፈኑን ዋዜማ ከምንጮች ሰምታለች።
በከተማዋ ውጥረት የተፈጠረው፣ አንድ የከተማዋ ትራፊክ ፖሊስ አባል ባልታወቁ ታጣቂዎች መገደላቸውን ተከትሎ እንደኾነ ምንጮች ተናግረዋል።
በከተማዋ ትናንት አንዳንድ የንግድ ተቋማት ተዘግተው እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል።
በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች የውሃ አቅርቦት ችግር እንዳለ የከተማዋ ነዋሪች ለአዲስ ማለዳ ቅሬታቸውን ተናግረዋል።
“መንግስት መጀመሪያ የሕዝቡን የውሃ አቅርቦት ችግር ሳይፈታ የመንገድ ላይ እና የፓርኮችን አትክልቶች በቀን ሶስት ጊዜ ሲያጠጡ መዋል አግባብነት የሌለው ነው” ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች ተመሳሳይ የሆነ የውሃ አቅርቦት ችግር እንዳለ እና ችግሩን ለማስተካከል እየተሰራ ያለ የሚታይ ጥረት አለመኖሩን አዲስ ማለዳ ካነጋገረቻቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ተረድታለች።
በጉለሌ ክፍለ ከተማ በወረዳ 4፣5 እና 7 አካባቢዎች ከፍተኛ የውሃ ችግር እንዳለ እና በሳምንት አንድ ጊዜ የሚመጣው ውሃ በበቂ ሁኔታ ሳይዳረስ እና የሚመጣበትም ሰአት ለሊት በመሆኑ ለመቅዳት አስቸጋሪ በመሆኑ ከፍተኛ ችግር ላይ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
የነዋሪዎቹን ቅሬታ በመያዝ አዲስ ማለዳ የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣንን ለማነጋገር ባደረገችው ጥረት ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል። ነገር ግን በተለያዩ አካባቢዎች ውሃ በሳምንት አንድ ቀን እንደሚመጣና ኃይል የሌለው በመሆኑ አንድ ጀሪካን ለመሙላት ከ30 እስከ 40 ደቂቃ ይፈጃል ሲሉ ነዋሪዎች በምሬት ይናገራሉ።
“እሱን ሌሊት ስንቀዳ አድረን ጠዋት ተነስተን ስራ መግባት አልቻልንም። ከሳምንት ሳምንት መድረስም ከብዶናል” ሲሉም ጠቁመዋል።
በተወሰኑ አካባቢዎች ደግሞ የአካባቢው ሰው ገንዘብ በማዋጣት የታንከር ውሃ በመኪና እያስመጡ እየተጠቀሙ እንደሆነ እና ለተጨማሪ ወጪ መዳረጋቸውን እንዲሁም በመኪናው ለሚመጣው ውሃ የመክፈል አቅም የሌላቸው ሰዎች በእጅጉ እየተጎዱ መሆኑን ቅሬታቸውን አመላክተዋል።
እንዲሁም በልደታ ክፍለ ከተማ ልደታ መናፈሻ አካባቢ “ውሃ ከጠፋ አንድ ወር ሆኖታል”
በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የስነ ሕዝብ፣ ስደትና ፍልሰት ረዳት ሚንስትር ጁሌይታ ኖይስ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ኖይስ፣ ትናንት ከተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ሃላፊ ራሚዝ አላክባሮቭ እና ከሌሎች የተመድ ሃላፊዎች ጋር ተመድ ለተረጂዎች በሚያቀርባቸው ሰብዓዊ ድጋፎች ዙሪያ መወያየታቸውን በ”ኤክስ” ገጻቸው ገልጸዋል።
ረዳት ሚንስትሯ ዛሬና ነገ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትና ዓለማቀፍ አጋሮች ጋር ስደተኖችን በሦስተኛ አገራት በማስፈር፣ በሰብዓዊ ዕርዳታ፣ ረድዔት ሠራተኞችን ከጥቃት በመጠበቅና ኢትዮጵያ ባለፈው ታኅሳስ ጀኔቫ ላይ በገባቻቸው የስደተኞች ቃል ኪዳኖች ዙሪያ ይወያያሉ።
መንግስት ወደ ኦሮሚያ ክልል የመለሳቸው ተፈናቃዮች “የከፋ በመሆኑ” ወደ ደብረብርሃን እየተመለሱ ነው
ወደ ኦሮሚያ ክልል የተመለሱ ተፈናቃዮች ወደመጡበት ደብረ ብርሃን መልሱን የሚል ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑን አዲስ ማለዳ ሰምታለች።
ተመላሾቹ በኦሮሚያ ክልል ዞኖች የሚገኙበትን ሁኔታ ሲገልጹ “እንጨት እንኳን መስበር አንችልም። ለህይወታችን አስጊ ነው፤ ከመጠለያችን መውጣት አንችልም።
በዛ ላይ ከመንግስት ምንም አይነት ድጋፍ እየተደረገልን አይደለም” ብለዋል።
ደብረ ብርሃን የሚገኙትም የከፋ ችግር ውስጥ ሲሆኑ ተፈናቃዮቹ ወደ ኦሮሚያ ክልል እንዲመለሱ ሆን ተብሎ እንዲቸገሩ እየተደረገ ስለመሆኑና… https://addismaleda.com/archives/36342 የአዲስ ማለዳን ልዩ ዘገባ ሙሉ ያንብቡ
ዋዜማ- ቅዳሜ ዕለት በየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል መዋቅር ላይ የተከሰተውን ግድፈት ተጠቅመው ገንዘብ የወስዱ አካላትን ለማደን ግብረ ኀይል መቋቋሙን ዋዜማ ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች ሰምታለች።
ከብሔራዊ ባንክና ንግድ ባንክ ባለሙያዎች እንዲሁም የፀጥታ አካላት የተካተቱበት ይህ ግብረ ኀይል በስድስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ከባንኩ ያለ አግባብ ተወስዷል ያለውን ገንዘብ ለማመለስ ያለመ ነው። ባንኩ የተወሰደበትን የገንዘብ መጠን አላሳወቀም። ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ግን ከ66 ሺህ በላይ ደንበኞች አካውንት በችግሩ መታወኩን፣ ቅዳሜ ለስድስት ሰዓታት በቆየው መታወክ 25 ሺ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር መደረጉን እንዲሁም ሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊየን ብር ተንቀሳቅሷል። ባንኩ መረጃውን ማረጋገጥ አልፈለገም።
አንዳንድ የትምህርት ተቋማት ከወዲሁ ገንዘብ ከክፍያ ማሽኖች የወሰዱና በህገወጥ ዝውውሩ የተሳተፉ ተማሪዎች ገንዘቡን ለባንኩ እንዲመልሱና ራሳቸውን ከህግ ተጠየቂነት እንዲያተርፉ የሚያሳስብ ጥሪ አድርገዋል።
በባንኩ ላይ የደረሰው ችግር የሳይበር ጥቃት አለመሆኑንና ውስጣዊ ግድፈት መሆኑን ባንኩ አበክሮ ገልጿል።
የባንኩ የውስጥ ምንጮች ለዋዜማ እንደተናገሩት ግን ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የተከናወነ አንድ መንግስታዊ የባንክ ክፍያ (ከአንድ መቶ ሚሊየን ብር ያላነሰ) ከአንድ በላይ የከፋይ ወገን በዲጂታል ፊርማ ሊያፀድቀው ሲገባ በአንድ ሰው ፈራሚነት ወደ ተከፋይ መተላለፉ የባንኩን ሀላፊዎች አስደንግጦ ነበር። አርብ ዕለት ችግሩን ለማወቅና ለመፍታት ሙከራ ሲደረግ መዋሉንና የቅዳሜ ሌሊቱ ቀውስ መከተሉን ሰምተናል።
ባንኩ የሳይበር ጥቃት አለመፈፀሙን ይናገር እንጂ ክስተቱ በባንኩ ዲጂታል መዋቅር ላይ በውስጥ አዋቂ የተፈፀመ ጥቃት ሊሆን እንደሚችል የሳይበር ደህንነት ባለሙያዎች ይናገራሉ። ባንኩ ከተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ ጋር በተያያዘ
ዋዜማ- በአዲስ አበባ በተለያየ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች በማያውቁት ስልክ እየተደወለላቸው ገንዘብ እየተጠየቁ ፤ ገንዘቡን የማይሰጡ ከሆነም ለደህንነታቸው የሚያሰጋ ማስፈራርያ እየደረሰባቸው እንደሆነ ዋዜማ ካሰባሰበችው መረጃ ተረድታለች ።
አዳማና ባህርዳር ያሉ ባለሀብቶችም በታጣቂዎች ከአንድ ጊዜ በላይ ገንዘብ መጠየቃቸውን ነግረውናል።
እየደወሉ በማስፈራርያ ገንዘብ የሚጠይቁ ግለሰቦች ፤ ባለሀብት ነው ብለው ያሰቡትን ሰው ሙሉ አድራሻ ብቻ ሳይሆን ፤ በባንክ ውስጥ የሚያንቀሳቅሱትን ገንዘብ እና የባንክ መረጃቸውን የሚያውቁ መሆኑ ደግሞ በግለሰቦች ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ተረድተናል ።
ለዚህ ዘገባ ሲባል ጉዳያቸውን የተከታተልነው እና ለደህንነታቸው ስማቸው እና የኩባንያቸው ስም እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ ግለሰብ ፤ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ማምረቻ ፋብሪካ አሏቸው ሌሎች የንግድ ስራዎች ላይም ተሰማርተዋል ።
ሆኖም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በስልካቸው እየተደወለ መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ እየተጠየቁ ፤ ይህን ማድረግ የማይችሉ ከሆነ ዛቻ እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል።የሚደውሉላቸው ሰዎች ግለሰባዊ ጉዳዮቻቸውን ሳይቀር የሚያውቁበት ደረጃ ስላሰጋቸውም መጀመርያ ይኖሩበት ከነበረበት ቦታ ሁለት ግዜ የመኖርያ ሰፈር እንደቀየሩም መረዳት ችለናል።ሁኔታውን በስራ እና ኑሯቸው ላይ ስጋት እንደፈጠረባቸውም ገልጸዋል ።
ሌላው ባለሀብት እንዲሁ በአዲስ አበባ በንግድ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ፤ በተመሳሳይ በስልክ እየተደወላላቸው መጠኑ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብን እየተጠየቁ እንደሆነ ያስረዳሉ። በዚሁ ሳቢያ የእጅ ስልካቸውን ለቤተሰብ አባላቸው ሰጥተው በሌላ ስልክ እንደሚጠቀሙ ይገልጻሉ ።ሆኖም ለቤተሰብም እንፈልጋቸዋለን እየተባለ እንደሚደወል ይናገራሉ ።
ለዚህ ዘገባ ጉዳያቸውን የተመለከትናችው ግለሰቦች ከሚደውሉላቸው ሰዎች ንግግር በመነሳት ገንዘብ ካላመጣችሁ ብለው
የኤርትራ መንግሥት፣ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ዋና ጸሃፊ ኤሊዜ ኪሪስ “ኤርትራ ሕግ የሌለባት አገር ናት” በማለት በተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በቅርቡ መናገራቸውን አጣጥሎታል።
የኤርትራ መንግሥት፣ ረዳት ዋና ጸሃፊዋ የኤርትራ ወታደሮች ትግራይ ውስጥ እንደሚገኙ መግለጣቸው፣ አውቀውም ኾነ ሳያውቁ የዓለማቀፉን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ አለመቀበላቸውን ያሳያል በማለት ተችቷል።
ሃላፊዋ ያወጡት መግለጫ፣ ያልተረጋገጡና ሐሰተኛ መረጃዎችን ያካተቱ እንደኾነም ኤርትራ ጠቅሳለች።
የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ዓለማቀፍ ወንጀል ፈጽማ የማታውቀውን ኤርትራ ለቀቅ አድርጎ፣ በሌሎች የዓለም ክፍሎች ለሚፈጸሙ ዓለማቀፍ የመብት ጥሰቶች ቅድሚያ ቢሰጥ ይሻላል በማለትም ኤርትራ መክራለች።
የአሜሪካ ዓለማቀፍ ተረድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ አይ ዲ) ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ትናንት በድጋሚ በመቀሌ ጉብኝት አድርጓል።
በሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ የዋና ዳይሬክተሯ ረዳት ሶናሊ ኮርዴ የመሩት ልዑካን ቡድን፣ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ሃላፊዎች ጋር በክልሉ በተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስና በወቅታዊ ኹኔታዎች ዙሪያ መክሯል።
ልዑካን ቡድኑ ወደ አፋር ክልልም አቅንቶ፣ የዕርዳታ ሥርጭት ሂደቱን ተመልክቷል።
ከጥር ወር ወዲህ፣ ድርጅቱ በትግራይ፣ አፋር፣ አማራ፣ ኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች ለ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ተረጂዎች አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ማቅረቡን ገልጧል።
የከተመን ማክተም፤ ድሃ ጠል የከተማ ዝመና ፖሊሲ ውጤት ነው ፟ ( ያሬድ ሃይለማርያም ፡ የሰብዐዊ መብት ተሟጋች )
+++++
“Eviction is a cause, not just a condition, of poverty.”
Matthew Desmond
የዛሬው የመልዕክተ ቅዳሜ ትኩረት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እና በዙሪያዋ እየታየ ያለው የጅምላ ቤት ፈረሳ እና የዜጎች ስቃይና እንግልት ላይ ነው። ለአብዛኛው የአገራችን ሕዝብ ትንሽ የምትባለውም ደሳሳ ጎጆ ሁሉ ነገሩን ያሳረፈባት ደሴቱ ነች። ያችን ደሴቱን ስታፈርስበት ልክ አውላላ ውቂያኖስ መሃል አንድ መዋኘት የማይችልን ሰው ከነቤተሰቡ ዋኝተህ ውጣ ብለህ ከጀልባ ላይ እንደወረወርከው ያህል ነው የሚቆጠረው። በዛሬዋ ኢትዮጵያ ሚሊዮን ዜጎች ይህ እጣ ፈንታ ገጥሟቸዋል። ልጆቻቸውን ይዘው፣ እቃቸውን በየሜዳው ላይ በትነው፣ ገሚሱም ተዘርፎባቸው በተንጣለለ ውቃኖስ መሃል የመጣል ያህል አደጋ ተጋርጦባቸዋል። በላዩ ላይ መቆሚያ ያጣው የኑሮና የገበያ ግሽፈት በውቂያኖሱ ላይ የሚጋልብ ማዕበል ነው። ሌሎች ሚሊዮኖች ደግሞ ይሄው እጣ ፈንታ ዛሬ ወይ ነገ ይገጥመናል በሚል አንድ አይናቸውን ጨፍነው ተኝተው እንድ አይናቸውን ገልጠው በሌሊት በተኙበት መጥተው በላያቸው ላይ ቤት የሚንዱና የሚያፈርሱ ሕገ ወጥ ግብረሃይሎችን ኮቴ ሲጠባበቁ ያድራሉ። ያገዛዝ ሥርዓቶቹ አንድ ያልተረዱት ነገር ቢኖር ከመሬቱና ከቤቱ በከተማ ዝመና ወይም በልማት ስም ያፈናቀልከው ሕዝብ ከልቡ ፈንቅሎ ይጥልሃል። ሕዝብ ከልቡ ያወጣው ሥርዓት ደግሞ አክራሞቱ በግጭት የተሞላ ብቻ ሳይሆን አወዳደቁ እጅግ የከፋና ዘግናኝ መሆኑን ነው።
የከተማ ዝመና እና ሰፋፊ የልማት ሥራዎች ሁሌም የሚነሳባቸው ጥያቄ ምን ያህል ሰዋዊ ገጽታ አላቸው
የአብይ ቀይ መስመር ለአባቶች – የእስክንድር ነጋ የቪዲዮ መልዕክት
!function(r,u,m,b,l,e){r._Rumble=b,r[b]||(r[b]=function(){(r[b]._=r[b]._||[]).push(arguments);if(r[b]._.length==1){l=u.createElement(m),e=u.getElementsByTagName(m)[0],l.async=1,l.src="https://rumble.com/embedJS/u4"+(arguments[1].video?'.'+arguments[1].video:'')+"/?url="+encodeURIComponent(location.href)+"&args="+encodeURIComponent(JSON.stringify([].slice.apply(arguments))),e.parentNode.insertBefore(l,e)}})}(window, document, "script", "Rumble");
Rumble("play", {"video":"v4gw84h","div":"rumble_v4gw84h"});
በአፋር ክልል በኢሳ እና አፋር ጎሳዎች መካከል ግጭት መቀጠሉ ተሰምቷል ።
ትናንት በአፋር ክልል ዞን 6 ወይም ማሂ ረሱ ዞን ውስጥ በሚገኘውና አፋር እና ሶማሌ ክልሎች በሚወዛገቡበት አዳዶ ወረዳ በኹለቱ ጎሳዎች መካከል ግጭት ማገርሸቱን ምንጮች ተናግረዋል።
በኹለቱ ጎሳዎች መካከል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተደጋጋሚ ግጭቶች የተከሰቱ ቢኾንም፣ ኹለቱ ክልሎች ግን ስለ ጎሳ ግጭቶች መግለጫ ሲያወጡ አይሰሙም።
የጎሳ ግጭቱ ትናንት በድጋሚ ያገረሸው፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስተባባሪነት የኸለቱ ክልሎች የጎሳ እና የአገር ሽማግሌዎች ተገናኝተው ከመከሩና ለግጭቶችና አለመግባባቶች ዘላቂ መፍትሄ ለመፍታት ጠቅላይ ምክር ቤቱ የሚመራው መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ካቋቋሙ ከጥቂት ቀናት በኋላ ነው።
ዋዜማ ራዲዮ
18 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በኬንያ ዋጅር ተያዙ
በኬንያ ዋጅር ካውንቲ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገሪቱ ገብተዋል የተባሉ 18 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የዋጅር ፖሊስ ገልጿል።
18ቱ ፍልስተኞች የተያዙት በዛሬው እለት ኮሮንዲሌ በሚባል የከተማይቱ አውራጃ በተደረገ ኦፕሬሽን መሆኑ ተነግሯል።
ፍልሰተኞቹ በኮሮንዲሌ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ ሲሆን በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኬንያ በመግባት ክስ እንዲመሰረትባቸው የሚያስችለውን ሂደት በመጠባበቅ ላይ እንዳሉ ተጠቁሟል።
በኬንያ በህገ-ወጥ መንገድ ገብተው የተገኙ የሌላ ሀገር ዜጎች የመባረር ወይም እስራት ሊገጥማቸው እንደሚችል ሲገለፅ በተጨማሪም፣ በኬንያ የኢሚግሬሽን ህጎች በተገለፀው መሰረት ቅጣት ሊጣልባቸው እንደሚችልም ነው የተገለፀው።
አሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የግጭትና መረጋጋት ረዳት ሚንስትር የኾኑት አን ዊትኮውስኪ ከመጋቢት 8 እስከ 17 በኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሞዛምቢክ ይፋዊ ጉብኝት ያደርጋሉ።
ረዳት ሚንስትሯ በኢትዮጵያ እና ኬንያ በሚኖራቸው ቆይታ፣ አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን ለቀጠናዊ ጥረቶች የምታደርጋቸውን ጥረቶች ለማጠናከር ያለመ ውይይት እንደሚያደርጉ መስሪያ ቤታቸው ዛሬ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።
ረዳት ሚንስትሯ፣ በሦስቱ አገራት ከመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከሲቪል ማኅበረሰብና ከዓለማቀፍ አጋሮች ተወካዮች ጋር የግጭት ተጎጂ ማኅበረሰቦችን መልሶ ለማቋቋም በማደረጉ ጥረቶች ዙሪያ ጭምር እንደሚወያዩና አሜሪካ በዚኹ መስክ ለሦስቱ አገራት እያደረገች ያለችውን ድጋፍ እንደሚገመግሙ ተገልጧል።
የአሜሪካ የላይኛው ምክር ቤት አባላት የባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ እንዲሰጥ ጠየቁ
የአሜሪካ የላይኛው ምክር ቤት አባላት ሴናተር ቲና ስሚዝ፣ ጄፍ ሜርክሌይ፣ ኤሚ ክሎቡቻር፣ ጆን ሂክንሎፐር፣ ክሪስ ቫን ሆለን፣ እና ቲም ኬይን፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ እንዲሱጡ ጠይቀዋል።
ሴናተሮቹ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አንቶኒ ብሊንከን እና የአሜሪካ አለማቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) ዋና ዳይሬክተር ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ በጦርነት እና ግጭት ምክንያት ለተከሰተው ሰብዓዊ ቀውስ ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ ድጋፍ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጡ በፃፉት ደብዳቤ ጥሪ አቅርበዋል።
በኢትዮጵያ ያለው የእርስ በርስ ግጭትና የአየር ንብረት መዛባት በሀገሪቱ ያለውን አስከፊ ሰብዓዊ ቀውስ አባብሶታል ያሉት የምክር ቤት አባላቱ 4.4 ሚሊዮን ሰዎች በአገር ውስጥ እንደተፈናቀሉና ኢትዮጵያ ወደ 942,ሺ የሚጠጉ የጎረቤት ሀገራት ስደተኞችን አስጠልላ እንደምትገኝ ገልፀዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ 20.1 ሚሊዮን የሚገመቱ ሰዎች አፋጣኝ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ሴናተሮቹ የጠቆሙ ሲሆን በኢትዮጵያ በ2024 የሰብዓዊ እርዳታ እቅድ መሰረት ለዜጎች ድጋፍ ለማድረግ 3.24 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገውና ለ6.6 ሚሊዮን ሰዎች የምግብ እርዳታ ለማድረግ 500 ሚሊዮን ዶላር በአስቸኳይ የሚያስፈልግ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ሴናተሮቹ የባይደን አስተዳደር በሀገሪቱ የሚደረገውን ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማሳደግ ከሌሎች ለጋሽ አገራትና የተራድኦ ድርጅቶች ጋር እንዲተባበር የጠየቁ ሲሆን በተጨማሪም በሀገሪቱ ሰብአዊ ፍጡራን ላይ ተፅዕኖ የሚያደርጉ ግጭቶችን ለማስወገድ ግፊት እንዲደረግም ጠይቀዋል።
በአብይ አህመድ አገዛዝ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በር ላይ ታፍነው ከተወሰዱ ተማሪዎች መካከል፦
1 ,ጆን ተሻገር
2, ቃልኪዳን እያሱ
3, ቴዎድሮስ ይበልጣል እና
4, አራጋው ሞሳው ይገኙበታል።( ምስላቸው ከታች ይገኛል
ከተማሪዎቹ መካከል ሦስቱ የ4ኛ አመት እና አንደኛው ደግሞ የ3ኛ አመት የህግ ተማሪዎች መሆናቸውን ለማወቅ ችለናል። ተማሪዎቹም እስካሁኗ ሰዓት የት እንዳሉ እንደማይታወቅ ከቅርብ ጓደኞቻቸው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በአብይ አህመድ አረመኔአዊ አገዛዝ አማራ ከሆንክ የትም እና በምንም አይነት ሁኔታ ትታገታለህ፣ ትታፈናለህ፣ ትገደላለህ፣ ትፈናቀላለህ።
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ከእስር ተፈቱ
ላለፈው አንድ ወር ከ12 ቀን በእስር ላይ የቆዩት፤ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ዛሬ ከሰዓት መለቀቃቸውን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ)፣ የቀድሞው የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘውም “በምህረት” ከእስር እንደሚፈቱ ታማኝ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
ዶ/ር ደሳለኝ “በዋስትና እንደሚለቀቁ” የተነገራቸው፤ ዛሬ ምሳ ሰዓት ገደማ መሆኑን በስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ገልጸዋል። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ፤ ጥር 22፤ 2016 ምሽት በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ታስረው የቆዩት በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው የፌደራል የወንጀል ምርመራ የእስረኞች ማቆያ ስፍራ ነው።
ዶ/ር ደሳለኝ ከእስር ከመለቀቃቸው ከሰዓታት በፊት በተካሄደ የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ፤ ከፓርላማው “የምክር ቤት ጉዳዮች አማካሪ ኮሚቴ” አባልነታቸው ተነስተዋል። ይህ ኮሚቴ “የተወካዮች ምክር ቤት የሚወያይበትን ማንኛውም አጀንዳ የመቅረጽ” ኃላፊነት ያለበት ሲሆን የሚመራው በፓርላማው አፈ ጉባኤ ነው። በዛሬው ስብሰባ፤ ላለፉት ሰባት ወራት በእስር ላይ ያሉት ሌላኛው የአብን የፓርላማ ተወካይ አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት መነሳቱ ይታወሳል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አዲስ አበባን ጨምሮ ከተለያዩ ክልሎች ተወካዮች ጋር ተከታታይ ውይይቶች ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ወክለው በውይይቶቹ የተገኙ ግለሰቦች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በርካታ ጥያቄዎች አቅርበዋል፡፡ ከጥያቄዎቹ መካከል የልማትና የፀጥታ ጉዳዮች ሰፊ ትኩረት ያገኙ ነበሩ፡፡ የመንገድ፣ የኤሌክትሪክ፣ የውኃ፣ የጤና፣ የትምህርትና መሰል መሠረተ ልማቶች ከኑሮ ውድነትና ተዛማጅ ጉዳዮች ጋር ተነስተው ነበር፡፡ በፀጥታ ጉዳይም በየአካባቢው በሚካሄዱ ግጭቶች ምክንያት እየደረሱ ያሉ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳቶች በስፋት ተዳሰዋል፡፡ ብዙዎቹ የተነሱት ጥያቄዎች በጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ በገዥው ፓርቲና በሚመሩት መንግሥት የሚታወቁ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ምላሽ ሲሰጡ ጥያቄዎቹን ተራ በተራ በማንሳት በማነፃፀሪያዎች እያስደገፉ ነበር፡፡ ሕዝብና መንግሥት በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ሊያግባባቸው የሚችል አማካይ እንዲኖር አንዳንድ መሠረታዊ ጉዳዮች መነሳት አለባቸው፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ ‹‹በወንዝ ዳር ፕሮጀክት›› እና ‹‹በመንገድ ኮሪደር ልማት›› መርሐ ግብሮች፣ ይዞታዎችን የማፍረስና አጥሮችን ወደ ውስጥ የማስገባት ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ ነው፡፡ ‹‹ስማርት ሲቲ›› በተሰኘው ከተማን የመለወጥ ግዙፍ እንቅስቃሴ፣ የከተማዋን ገጽታ የሚለውጡ ተግባራት ሲከናወኑ በከተማ አስተዳደሩና በነዋሪዎች መካከል መግባባት መኖር አለበት፡፡ አገሩ ወይም ከተማው በልማትና በዕድገት ስትለወጥለት የሚጠላ ዜጋ ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ልማቱም ሆነ ዕድገቱ የጋራ ሲሆን፣ ከአንድ አካባቢ ተነስተው ወደ ሌላ የሚሠፍሩ ዜጎች፣ በተቻለ መጠን ከነበሩበት ያላነሰ ተስማሚ የመኖሪያና የመሥሪያ ቦታ ማግኘታቸው መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ በከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ እንደተነገረው ነዋሪዎች የተሻለ መኖሪያና መሥሪያ አግኝተው ከሆነ መልካም ነው፡፡ ነገር ግን የተባለውና እየተደረገ ያለው የማይመጣጠን ከሆነ ማስተካከያ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ ሐሙስ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም. በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካይ የሆኑትን የአቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት ሊያነሳ ነው።
አቶ ክርስቲያን ታደለ ፓርላማ የገቡት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ቋሪት ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)ን ወክለው ተወዳድረው ነው።
አቶ ክርስቲያን ፓርላማ ከገቡ በኋላ በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነዋል።
ሆኖም በአማራ ክልል የተፈጠረውን የፀጥታ መደፍረስ ተከትሎ ባለፈው ሐምሌ ወር በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት ላላፉት ሰባት ወራት በእስር ላይ ይገኛሉ።
አቶ ክርስቲያን በቁጥጥር ስር ከዋሉ ከሰባት ወራት በኋላ ነው ምክር ቤቱ ያለመከሰስ መብታቸውን ነገ የሚያነሳው።
ቢቢሲ የተመለከተው እና ለፓርላማ አባላት የተላከው አጀንዳ የአንድ የምክር ቤት ያለመከሰስ መብት እንደሚነሳ ያትታል።
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የቢቢሲ ምንጮች ያለመከሰስ መብታቸው የሚነሳው የምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከአቶ ክርስቲያን በተጨማሪ ሌላኛው የአብን ተወካይ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔም ባለፈው ጥር መጨረሻ ላይ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወሳል።
ሆኖም ግን ምክር ቤቱ በአሁኑ ወቅት ያለመከሰስ መብት የሚያነሳው የአንድ የምክር ቤት አባልን ብቻ ነው።
የአገሪቱ ሕገ መንግሥት፤ “ማንኛውም የምክር ቤት አባል ከባድ ወንጀል ሲፈጽም እጅ ከፍንጅ ካልተያዘ በስተቀር ያለ ምክር ቤቱ ፈቃድ አይያዝም፤ በወንጀልም አይከሰስም” ሲል ይደነግጋል።
ነገ የአቶ ክርስቲያን ያለመከሰስ መብት የአባላትን አብላጫ ድምጽ አግኝቶ የሚነሳ ከሆነ በሥራ ላይ ባለው ምክር ቤት ያለመከሰስ
ዋዜማ- መንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅጥር ሲፈጽሙ ሀሰተኛ የትምህርት ሰነድን ያቀረቡ 220 ሰራተኞቹን ማበረሩን ዋዜማ ከባንኩ ምንጮች ሰምታለች።
ባንኩ ከሰሞኑ ሀሰተኛ የትምህርት ሰነድ አቅርበዋል በሚል ከስራ ያባረራቸው ሰራተኞቹ ባለፈው አመት ንግድ ባንኩ ባወጣው የስራ ማስታወቂያ ተወዳድረው በማለፍ በስራ ላይ የነበሩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፈው አመት በአንድ ቅጥር ክብረ ወሰን በተባለ ሁኔታ ወደ 12 ሺህ ሰራተኞችን መቅጠሩ ይታወሳል።ሆኖም ባንኩ እነዚህ ተቀጣሪዎች ፈተና አልፈው የስራ ቅጥር ውል ፈጽመው ወደ ስራ ከገቡ በሁዋላ ተመርቀንበታል በሚል ያስገቡትን የከፍተኛ ትምህርት ሰነድ ፣ በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በመላክ በጀመረው የማጣራት ስራ ከ200 ዋዜማ በላይ ሰራተኞች ያቀረቡት የትምህርት ሰነድ ሀሰተኛ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብሏል።
ተቀጣሪዎች የፈጸሙት የሰነድ ማጭበርበር ሁለት አይነት መልክ እንዳለው የተገለጸ ሲሆን ፣ የተወሰኑት ተቀጣሪዎቹ እንዳስገቡት ሰነድ የመጀመርያ ዲግሪ ያላቸው ቢሆንም ፣ ተወዳዳሪነታቸውን ከፍ ለማድረግ በማሰብ በትክክል ካመጡት የመመረቂያ ውጤት ላይ ከፍተኛ የሆነ የነጥብ ጭማሬ እንዳላቸው በማስመሰል ሀሰተኛ የትምህርት ሰነድ ማሰራታቸው ተረጋግጦባቸዋል።
ሌሎቹ ደግሞ ለባንኩ ለቅጥር ያስገቡት የከፍተኛ ትምህርት ሰነድ ፍጹም ሀሰተኛ መሆኑ በመረጋገጡ ከስራ እንዲሰናበቱ ተደርገዋል።ንግድ ባንኩ ጉዳዩን ወደ ህግ ይውሰደው አይውሰደው ለማወቅ ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።
ሆኖም ባለፈው አመት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀጠራቸው ሰራተኞች ላይ የጀመረው የትምህርት ሰነድ ማጣራት እስካሁን አለመጠናቀቁን ፤ ይህ የትምህርት ሰነድ ከአምና ተቀጣሪዎች ባለፈ ቀድሞ ተቋሙን በተቀላቀሉ ባልደረቦችም ላይ የትምህርት ሰነዶች ትክክለኝነትን በስፋት ወደ ማጣራት እንደሚገባም ሰምተናል።
በኢትዮጵያ የተለያዩ የመንግስት
” ፍርዱ ለሚዲያ 16 ዓመት ከተባለ በኃላ ወደ 10 ዓመት ዝቅ እንዳለ ሰምቻለሁ ” – ጸጋ በላቸው
” ጉዳዩ ለቢሮዉም ሆነ ለኔ አዲስ ነው ” – ወ/ሮ ወይንሸት ብርሀኑ
በሀዋሳ ከተማ የዳሽን ባንክ ሰራተኛ ከሆነችዉ ጸጋ በላቸዉ ጋር በተያያዘ በጠለፋና አስገድዶ መድፈር ወንጀል ተከሶ የነበረው ኮንስታብል የኃላመብራት ወ/ማርያም ” ለብዙዎች አስተማሪ ይሆናል ” በተባለ መልኩ የ16 አመት ጽኑ እስራት እንደተፈረደበት ይታወሳል።
ይሁንና ይህ ለሚዲያ የተገለጸው ፍትህ ከተበዳዩዋ እውቅና ውጭ በሆነ መልኩ የእስራት ፍርዱ ከ16 አመት ወደ 10 መቀነሱን እንደሰማች በሶሻል ሚዲያ ባስተላለፈችዉ በዕንባ የታጀበ ቅሬታ ገልጻለች።
ወይዘሪት ጸጋ ፤ ጉዳዩን ለማወቅ ብዙ ድካም እንደነበረዉና በመጨረሻ የሰማችዉ ጉዳይ እጅግ እንዳሳዘናት በመግለጽ አቤቱታዋን አሰምታለች።
ጸጋ ፤ ” የፍርድ ሂደቱ በጥሩ ሂደት ሄዶ ፍርድ ቤት 16 ዓመት ተፈርዶበታል በሚል ለኔ ውሳኔ ሰጥቶኝ ነበር ፤ አሁን ግን እኔ በማላውቅበት ሁኔታ የፍርዱ ውሳኔ ይግባኝ ብሎ #እንደተስተካከለ ሰምቻለሁ፤ ይህ ውሳኔ መቼ እንደተላለፈ አልተነገረኝም ለግል ጉዳዬ የውሳኔ ወረቀት እንዲሰጠኝ በተደጋጋሚ ወደ ፍርድ ቤት በምደውልበት ጊዜ ምላሽ እየተሰጠኝ አልነበረም ጉዳዩን አጥብቄ በተደጋጋሚ ስጠይቅ ውሳኔው በይግባኝ እንደተስተካከለ ተነገረኝ ” ስትል አስረድታለች።
ውሳኔው አሁን ላይ ወደ 10 ዓመት ዝቅ እንዳለ የገለፀችው ጸጋ ፤ በድርጊቱ እጅግ እንዳዘነችና ካሳለፈችው የስቃይ ሁኔታ ጋር በፍፁም እየሚገባ እንዳልሆነ በእምባ ታጅባ ገልጻለች።
ከዚህ ባለፈ ህዝብ የማያውቀው ብዙ ነገር እንደተፈፀመ ፤ ከጠለፋው እገታ ከተለቀቀች በኃላ በማታውቀው ምክንያት
ደቡብ አፍሪቃ ለመግባት በሚሞክሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የሞት አደጋ ተባብሷል
ወደ ደቡብ አፍሪቃ ለመግባት በሚሞክሩ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች ላይ የሚደርሰው የሞት አደጋ እየተባባሰ መምጣቱን ከኬኒያ እና ታንዛኒያ እሥር ቤቶች ተለቀው ዛሬ በኢትዮጵያ ሞያሌ በኩል ወደ አገራቸው የገቡ ተመላሽ የአይን እማኝ ፍልሰተኞች መመልከታቸውን ዶይቼ ቬለ ዘግቧል።
በስደት ጉዞና በእሥር ቆይታቸው አስቸጋሪ ፈተናዎችን ማለፋቸውን የተናጉሩት ከፍልሰት ተመላሾቹ ” ዜጎች በጉዞ ላይና በበረሃና በእሥር ቤቶች ለሞት ሲዳረጉ በርካቶች ሕይወታቸው ሲያጡ ተመልክተናል። አብዛኞቹ የሞት አደጋ የሚጋጥማቸው በጉዞ ላይ ሲሆን በበረሃ፣ እስር ቤቶች ውስጥ በረሃብና በበሽታ የሞቱ ሰዎችንም አይተናል” ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃድያ ዞን ነዋሪ የሆኑት ወጣት ታደሰ ተመስገን እና ብሩክ ግርማ በሞያሌ በኩል ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ከዓመት በፊት ጉዞ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ እነ ታደሰ የተስፋይቱ ምድር ብለው ጉዞ የጀመሩባት ደቡብ አፍሪካ እንዳሰቡት መድረስ አልቻሉም። ይልቁንም በተሽከርካሪ ኮንቴይነር ውስጥ ተደብቀው ከኬኒያ ሞምባሳ ወደ ታንዛኒያ በበረሃ በመጓዝ ላይ ሳሉ አየር ለመውሰድ በወጡበት በአገሬው ፖሊሶች ተይዘው ለእሥር መዳረጋቸውን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ ሞያሌ በኩል ዛሬ ወደ አገራቸው የተመለሱት ከሦስት መቶ በላይ ፍልሰተኞች ከስድስት ወራት እስከ አንድ ዓመት በእሥር መቆየታቸው ሲገለፅ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙት የሃድያና የከምባታ ዞኖች ወደ ደቡብ አፍሪካ ለሚደረገው ፍልሰት በመነሻነት የሚጠቀሱ መሆኑም ነው የተገለፀው።
ኦነግ፣ መንግሥት ያቋቋመው ሚስጢራዊ የጸጥታ ኮሚቴ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚፈጽማቸው ግድያዎች እንዲቆሙ ሕዝቡ፣ ዓለማቀፉ ኅብረተሰብና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል።
የጸጥታ ኮሚቴው አባላት ለፈጸሟቸው ተግባራት ተጠያቂ እንዲኾኑ እነዚኹ አካላት ጥረታቸውን እንዲቀጥሉም ኦነግ ጥሪ አድርጓል። ኦነግ ጨምሮም፣ በአብዛኞቹ የክልሉ ዞኖች ከፍርድ ውጭ የኾኑ ግድያዎች፣ የዘፈቀደ እስሮች፣ ስቃይ እና ምዝበራ እንደቀጠለ ነው ብሏል።
የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተካተቱበት ሚስጢራዊ የጸጥታ ኮሚቴ የሚያስፈጽማቸውን ከሕግ ውጭ የኾኑ ግድያዎች ሮይተርስ በጥልቅ ምርመራ በቅርቡ አጋልጧል ያለው ኦነግ፣ የሚስጢራዊው ኮሚቴ መዋቅር እስከ ዞን፣ ወረዳ፣ ከተማ እና ቀበሌ አስተዳደሮች ድረስ የተዘረጋ መኾኑን ጠቅሷል።