Blog Archives

ፋኖ አሰግድ መኮንን እጅ ሰጠ እየተባለ የሚነገረው ተራ ቅጥፈት ነው፤ በመንግስት ኃይሎች ተይዞ ነው ( ጀኔራል ተፈራ ማሞ)

በፋኖ ውስጥ የተፈጠረው ክፍፍል በፖለቲካ ኃይሉ እንጂ በወታደራዊ ኃይሉ ዘንድ ባለመሆኑ በትግሉ ላይ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ጀኔራል ተፈራ ማሞ ገለጹ። ፋኖ አሰግድ መኮንንም በተመለከተ እጅ ሰጠ እየተባለ የሚነገረውም ተራ ቅጥፈት እንጂ በመንግስት ኃይሎች ተይዞ ነው ብለዋል። በፋኖ ውስጥ የተፈጠረው ክፍፍል በፖለቲካ ኃይሉ እንጂ በወታደራዊ ኃይሉ ዘንድ ባለመሆኑ በትግሉ ላይ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ጀኔራል ተፈራ ማሞ ገለጹ። ፋኖ አሰግድ መኮንንም በተመለከተ እጅ ሰጠ እየተባለ የሚነገረውም ተራ ቅጥፈት እንጂ በመንግስት ኃይሎች ተይዞ ነው ብለዋል። ጄኔራል ተፈራ ማሞ ይህን የገለጹት ኤቢሲ ቴሌቪዥን ከተሰኘ የማህበራዊ ሚድያ ጋር ባደረጉት ቆይታ ነው። ከሚዲያ ተቋሙ በቅርብ ጊዜ ስለ ፋኖ አመራሮች ይፋ ስለወጣው ክፍፍል የተጠየቁት ጄነራሉ በምላሻቸው የፖለቲካ ኃይሉ በጋራ ተግባብቶ እና ፖለቲካዊ የአመራርነቱን ሚና እንዲጫወት ከነበረው ሰፊ ፍላጎት የተነሳ ቢደረግም አመራሮቹ ሲታዩ ግን ጉዳዩን በደንብ ትኩረት እና ጊዜ ሰጥተው ማየት አልቻሉም በማለት ወቅሰዋል። አመራሮቹ እየተከፈለ ያለውን የህይወት መስዋእትነት ከግምት ከተው በቅንነት እና ሰፋ ባለ አመራር ኃይል በሚያሳትፍ መልኩ ማድረግ እንደተሳናቸውም አክለው ገልጸዋል። ይህም ሆኖ በፖለቲካ አመራሩ ዘንድ የታየው መከፋፈል በተዋጊ ሰራዊቱ ላይ ምንም አይነት ተጽእኖ እንዳይፈጥር በማድረጋችን በትግሉ ላይ የሚፈጥረው ነገር የለም ብለዋል። ቃለመጠይቁን ሙሉውን እዞህ ያገኙታል። ፋኖ አሰግድን በተመለከተ ለመንግስት እጅ መስጠት ነው ወይንስ ሌላ መሆኑን የተጠየቁት ጀኔራል ተፈራ ማሞ “ሸዋ ላይ ያሉት አመራሮች ጥሩ እየሰሩ ባሉበት ሰዓት በመሃላቸው የተፈጠረውን መለስተኛ ቅራኔ ማስተናገድ እና መፍታት አለመቻላቸው
Posted in Amharic News, Ethiopian News, Video

አብይ አሕመድ በየመንገዱ የተከለውን ብልጭልጭ መብራት እና ዘንባባ እንዲጠብቁ ስድስት ሺህ ደንብ አስከባሪዎች አሰማራ

ዘንባባ ዛፍ መግጨት እስከ 300ሺ ብር ያስቀጣል፣ የከረሜላ ሽፋን መጣልስ? የከተማ ማስዋብና የኮሪደር ልማት ግንባታን ተከትሎ የአዲስ አበባ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ቅጣቶችን አሻሽሎ ማውጣቱንና ይህን የሚያስፈፅሙ ስድስት ሺህ ደንብ አስከባሪዎችን ማሰማራቱን ዋዜማ ተረድታለች። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለዋዜማ እንደተናገሩት በጽዳትና ተያያዥ ህገ-ወጥ ተግባራት ዙሪያ ቀድሞ ሲጠቀምበት የነበረው ደንብ ቁጥር 150/2015 ተሻሽሎ ጠንከር ያለ ቅጣት የሚጥለው አዲሱ ደንብ ከሰኔ ወር ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል። ዝርዝሩን ያንብቡት- https://tinyurl.com/mr24ru27
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአብይ አገዛዝ የሀምሌ 25 ልዩ ዘመቻ ቀጠሮ = የአብይ አሕመድ ኃይል በጣም አደገኛ ጦርነት ለማድርግ አቅዶ ወደልዩ ዘመቻ ዝግጅት ተልዕኮ ገብቷል።

የአገዛዙ የሀምሌ 25 ልዩ ዘመቻ ቀጠሮ! የጠላት ኃይል በጣም አደገኛ ጦርነት ለማድርግ አቅዶ ወደልዩ ዘመቻ ዝግጅት ተልዕኮ ገብቷል። ይህ ኦፕሬሽን በዋነኝነት በአብይ አህመድ እንደተወሰነ ለ ኢትዮ 251 ሚዲያ መረጃው ደርሷል (ዝርዝር ከታች አለው)። የፋኖ ኃይል ከመደበኛ ውጊያ ይልቅ የሽምቅ ውጊያ ስልቱ ላይ ያተኩር። በምንም መልኩ ቢሆን የውጊያ ዓላማዎችን ከመግለፅ ይቆጠብ። የውጊያ ታክቲኮች መክበብ፣ መቆራርጥ፣ እረፍትና ፋታ መንሳት፣ እየቆራረጡ በማሳሳት ደፈጣ መጣል…ወዘተ ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል። በጠላት በኩል ያሉ የውስጥ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከወትሮው የተለየ የውጊያ እቅድና እንቅስቃሴ አለ። ከሰኔ ጀምሮ ታቅዶ የነበረው የክልሉ የ100 ቀናት የፀጥታ እቅድ ተከልሷል። በብልጽግና ሰራዊት በኩል አዲስ የውጊያ አቅዶ ወደልዩ ዘመቻ ለመግባት የዝግጅት ተልዕኮ ውስጥ ገብቷል። ከሐምሌ 25 ቀን 2016 ጀምሮ በፋኖ ካምፖች ላይ ጥቃት የመክፈት ዝግጅቶች አሉ። የዚህ ዕቅድ ፓይለት ወርክ ጎጃም ላይ ቀደም ብሎ ተጀምሯል። ቀጣዩ ተረኛ ጎንደር ቢሆንም ተመሳሳይ የውጊያ ዕቅዶች ለአራቱም ግዛቶች ታቅዶ ዝግጅት ላይ ይገኛል የጠላት ኃይል! በሌላ መረጃ በምስራቅ ጎጃም ቀጠና በፋኖ ላይ የተደረገው ወታደራዊ ግምገማ ሊከለስ ይገባል ሲል የአብይ አህምድ የግል ጀነራሎች ወስነዋል። በአገዛዙ በኩል መጠነ ሰፊ ለማጥቃት እንዲረዳ ከደቡብ ጎንደር አንዳንድ ቀጠናዎች የሰራዊት እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ የውስጥ አርበኞች ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋል። ስለሆነም የጎንደርና የጎጃም ፋኖ በመረጃ ልውውጦችና በጋራ ኦፕሬሽኖች ዙሪያ ጥንቃቄ የታከለበት ግንኙነት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ሲሉ የወስጥ ምንጮች ጨምረው ገልፀዋል። በተለይም በሞጣ መስመር ባለው ቀጠና የእንቅስቃሴ መገደቢያ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሜታ ኩባንያ የእርቃን ምስሎችን በማስላክ ሲያጭበረብሩ የነበሩ 63 ሺ አካውንቶችን አስወገደ።

ሜታ ኩባንያ የእርቃን ምስሎችን በማስላክ ሲያጭበረብሩ የነበሩ 63 ሺ አካውንቶችን አስወገደ። የሜታ ኩባንያ መቀመጫቸውን በናይጄርያ ያደረጉና በማጭበርበር የተቀበሉትን የግለሰቦችን የእርቃን ፎቶ በመጠቀም ለማጥቃት ሲሞክሩ የነበሩ 63,000 የኢንስታግራም አካውንቶችን አስወግጃለው ብሏል። እነዚህን አካውንቶች በመጠቀም ጥቃት የሚፈፅሙት ግለሰቦች የማህበራዊ ሚድያው ተጠቃሚ የሆኑ ወጣቶችን ግልፅ የሆኑ ምስሎች በተለያየ መንገድ እንዲልኩ በማታለል እና በማሳመን ይቀርባሉ። ከዚህም በኋላ ይህን ተጠቅመው ገንዘብ ካልከፈሉ ወይም ፆታዊ ግንኙነት ካልፈፀሙ ምስሎቹን ይፋ እንደሚያደርጉ በማስፈራራት ሲፈጽሙ ነበር ብሏል። ከቅርብ አመታት ወዲህ በናይጀሪያም ሆነ በተለያዩ ሀገራት ይህን መሠል ድርጊቶች መበራከታቸውን ሜታ ተናግሯል። በተለይም ተጎጂዎቹ ከ14-17 አመት የሚሆኑ ታዳጊዎች ሲሆኑ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች የዚህ ማህበራዊ ሚድያ ጥቃት ሰለባዎች ናቸው። ኢንስታግራም በባለፈው ሚያዚያ ወር ወጣቶችን ከተለያዩ ፆታዊ ምዝበራዎች ለመጠበቅ አዳዲስ ስርዓቶችን እንደሚዘረጋ ገልፆ የነበረ ሲሆን በሙከራ ላይ ይገኛሉም ብሏል። አክሎም ተጠቃሚዎቹ  ከእነዚህ አይነት መጭበርበሮች እራሳቸውን እንዲጠብቁ አሳውቋል።
Posted in Ethiopian News

ፕሬዚዳንት ፑቲን እና አንቶኒዮ ጉተሬዝ በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

ፕሬዚዳንት ፑቲን እና አንቶኒዮ ጉተሬዝ በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ ፕሬዝዳንት ፑቲን እና አንቶኒዮ ጉተሬዝ በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለኢትዮጵያ መንግስት ባስተላለፉት የሀዘን መልዕክት በአደጋው ቤተሰቦቻቸውን ላጡ ዜጎች መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ፑቲን በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በፍጥነት እንዲያገግሙ መልካም ምኞታቸውን መግለጻቸውንም በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡ በሌላ በኩል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልጸዋል፡፡ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች ጥልቅ ሃዘን አንደተሰማቸው ገልጸዋል፡፡ በጎፋ ዞን በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሟቾች ቁጥር እስከ 500 ሊደስር እንደሚችል ኦቻ መግለጹ ይታወሳል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር በልማት ሰበብ እየፈጸመ ያለውን ኢ- ህገመንግስታዊ ድርጊት ሊያቆም አልቻለም ሲል ካውንስሉ ከሰሰ

የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር በልማት ሰበብ እየፈጸመ ያለውን ኢ- ህገመንግስታዊ ድርጊት ሊያቆም አልቻለም ሲል ካውንስሉ ከሰሰ የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር በልማት ሰበብ እየፈጸመ ያለውን ኢ- ህገመንግስታዊ ድርጊት ሊያቆም አልቻለም ሲል የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ካውንስል ከሷል፡፡ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኘው የኩሪፍቱ ማዕከል ከህግ ውጪ በሀይል በተወሰደ እርምጃ መነጠቁን አስመልክቶ የፍትህ ጥያቄ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አቅርቦ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ካውንስሉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በደብዳቤ እና በአካል ሲወያይ ቆይቶ ይዞታውን ማልማት አልቻሉም በሚል ቦታው እንደተወሰደበት ነው ባወጣው መግለጫ ያስታወቀው፡፡ አክሎም ቤተ ክርስቲያኒቱ የፍትህ ጥያቄ ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ያቀረበች ቢሆንም ምንም አይነት ምላሽ እንዳልተሰጣት ነው ካውንስሉ የጠቆመው፡፡ ካውንስሉ አክሎም በሀይል የተወረረው መሬት እና የታጠረው አጥር እስኪፈርስ ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንታገላለን ብሏል፡፡ ጉዳዩ የእምነት ብዝሃነት ባለበት አገር የሃይማኖት ነጻነትን የሚገፍ ተራ እርምጃ መሆኑን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ተረድቶ ከቤተክርሰቲያኗ ጎን ሊቆም ይገባል ሲል በመግለጫው ጥሪ አቅርቧል፡፡ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ በሕጋዊ መንገድ ለቤተ ክርስቲያኗ ከተላለፈ የመሬት ይዞታ ላይ 40 ሺህ ካሬ ሜትር የሚሆነውን በግድ ተነጥቀናል፤ ይዞታውን በሀይል በመቀማት ለሁለት ግለሰቦች እንደተሰጠ እና ጉዳዩን አስመልክቶ ወደ ፍርድ ቤት በመውሰድ ይዞታው የቤተ ክርስቲያኗ እንደሆነ ተወስኖ ነበር ማለቱን አዲስ ማላዳ መዘገቧ አይዘነጋም፡፡
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ ለደረሰው አደጋ እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ እንዳልሆነ ታወቀ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ ለደረሰው አደጋ እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ እንዳልሆነ ኢሰመኮ አስታወቀ አደጋውን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጠው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በዞኑ የደረሰው አደጋ በዜጎች ሕይወት ፣ በመኖሪያ ቤቶችና እና በስራ ቦታዎች ላይ ከፍተና ጉዳት ማድረሱን ገልቷል፡፡ የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ የሚደርሱት ጥቆማዎች እና ሪፖርቶች በእጅጉ አሳሳቢ ናቸው ያለው ኮሚሽኑ በአፋጣኝ ለተጎጂዎች ድጋፍ እንዲደረገም አሳስቧል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሠለ ለተጎጂዎች የሚደረገው ድጋፍ በተፈጥሮ አደጋ ወቅት በተለይ በሴቶች፣ በህጻናት፣ በአረጋዊያን እና በአካል ጉዳተኞች ላይ የሚደርሰው ጉዳት የበለጠ ሊሆን እንደሚችል ከግንዛቤ ያስገባ ሊሆን እንደሚገባም ጠቁመዋል። ሀምሌ 14 ቀን በጎፋ ዞን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሟቶች ቁጥር 260 በላይ መድረሱን እና ፍለጋው መቀጠሉን እንዲሁም የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አዲስ ማለዳ መዘገቧ ይታወሳል፡፡ የፌደራል የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በአደጋው 400 ያህል ነዋሪዎች እንደተፈናቀሉና እርዳታ እየቀረበላቸው እንደሆነ አስታውቋል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

IMF የዳይሬክተሮች ቦርድ ኢትዮጵያ በጠየቀችው አዲስ ብድር ዙሪያ ለመምከር ስብሰባ ሊቀመጥ ነው

ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) የዳይሬክተሮች ቦርድ ኢትዮጵያ ለኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብሯ በጠየቀችው አዲስ ብድር ዙሪያ ለመምከር በቀጣዩ ሳምንት ስብሰባ ሊቀመጥ እንደኾነ ከድርጅቱ ምንጮች መስማቱን ጠቅሶ ብሉምበርግ ዘግቧል። ኾኖም ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር አዲስ የብድር ስምምነት ላይ ስለመድረሱ እስካኹን ይፋ አላደረገም። በደንቡ መሠረት የድርጅቱ የዳይሬክተሮች ቦርድ የአገራትን የብድር ጥያቄ ለማጽደቅ ወይም ማሻሻያዎችን ለማድረግ ስብሰባ የሚቀመጠው፣ የድርጅቱ መካከለኛ ሃላፊዎች በብድር ዙሪያ ከብድር ጠያቂ አገራት ጋር የመጀመሪያ ደረጄ ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ነው። የኢትዮጵያ አበዳሪ አገራት እስከ ቀጣዩ ዓመት ታኅሳስ ድረስ ያራዘሙት የብድር መክፈያ እፎይታ ዕጣ ፋንታ የተንጠለጠለው፣ በዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት የብድር ውሳኔ ላይ ነው። ዋና ዋና አበዳሪ አገራት፣ ኢትዮጵያ ከዓለማቀፍ ድርጅቶች አዲስ ብድር እንድታገኝ ፍቃዳቸውን እንደገለጡ ከቀናት በፊት ተዘግቦ ነበር። ኢትዮጵያ ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት የጠየቀችው አዲስ ብድር 3 ቢሊዮን ዶላር ነው።
Posted in Ethiopian News

ህወሓት ለማዘጋጀት ያቀደው ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ራሳቸው ከሃላፊነታቸው አገለሉ።

ህወሓት ለማዘጋጀት ያቀደው ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ራሳቸው ከሃላፊነታቸው አገለሉ። የኮሚቴው ም/ሰብሳቢ ተስፋይ ገ/እግዚአብሔር ለህወሓት ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ በጻፉት ደብዳቤ ከሃላፊነት ራሳቸው ስለማግለላቸው አሳውቀዋል። ” በኮሚቴው ስራ ውስጥ የሚታዩ ጣልቃ የመግባት ፣ ከፕሮግራም ውጪ ስብሰባ መጥራት፣ ውሳኔዎችን መጠምዘዝ የመሳሳሉ ተግባራት እንዲታረሙ ለመስራት ብሞክርም  አልተሳካም ” ብለዋል። ” የምታገልበት ድርጅት ዴሞክራሲያዊ ፣ ግልፅና አሳታፊ መሆኑ አምናለሁ ” ያሉት ምክትል ሰብሳቢው ” ሆኖም በኮሚቴው ስራ ውስጥ ልቋቋማቸው የማልችላቸው አካሄዶች እየታዘብኩ ነው ” ሲሉ አብራርተዋል። ” ይህንን ስርዓት የለሽ አካሄድ ከእምነቴ ፣ ከትግል አቋሜና ከሞራሌ የማይሄድ በመሆኑ ከሀምሌ 13/2016 ዓ.ም ጀምሮ ከሃላፊነቴና ከኮሚቴ አባልነቴ አግልያሎህ ” ብለዋል። ” የድርጅቱ አባልና አመራር ግልፅ እንዲሆንለት እስካሁን የገጠሙኝ እንቅፋቶችና ንቀት በመደበኛ ሚድያ ይፋ አደርጋለሁ ” ብለዋል። አቶ ተስፋይ የትግራይ ልማት ማህበር ስራ አስፈፃሚም ናቸው።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የብዙ ወገኖች ሕይወታቸው በማለፉ ጥልቅ ኀዘናቸውን ገለጹ።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የብዙ ወገኖች ሕይወታቸው በማለፉ ጥልቅ ኀዘናቸውን ገለጹ።“ትግሁ እንከ እስመ ኢተአምሩ በዓይ ሰዓት ይመጽእ እግዚእክሙ ፤ጌታችሁ በማናቸውም ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና ተግታችሁ ኑሩ።ማቴ ፳፬፥፵፪”በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ ድንገት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ላይ በደረሰው አሰቃቂና አሳዛኝ አደጋ ታላቅ ሀዘን ተሰምቶናል።በመሆኑም የድንገተኛ አደጋው ተጎጂ ለሆኑ ወገኖቻችን እግዚአብሔር አምላክ በወዲያኛው ዓለም ዕረፍተ ነፍስን፣ለተጎጂ ቤተሰቦች፣ ለአካባቢው ነዋሪዎችና ለመላው ኢትዮጵያውያንም መጽናናትን እንዲሰጥልን በመለመን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልጻለን።“አምላካችን እግዚአብሔር ለአገራችንና ለዓለሙ ሁሉ ሰላምን ይስጥልን!”አባ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዋናሥራ አስኪያጅ፣የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃምአህጉረስብከት ሊቀ ጳጳስ©የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ስለአርበኛ አሰግድ መኮነን አንዳንድ ነገሮች .. !?

ስለአርበኛ አሰግድ መኮነን አንዳንድ ነገሮች .. !? አርበኛ አሰግድ መኮነን በጠላት እጅ ወድቋል። በጠላት እጅ ከወደክ በኋላ ደግሞ አንተ የምትናገረውን መርጠህ ሳይሆን እነሱ ተናገር ያሉህን ነው። አርበኛ አሰግድ መኮነን በሸዋ ቀጠና በጂፔስ ትራክ እንደተያዘ ነው መረጃዎች እየወጡ ያሉት፣ ትናንት ምሽት ከክፍለጦር አመራሮች ጋር የስራ ስምሪት መስጠቱን ከሕዝብ ግንኙነቶች መረጃ ማግኘት ችያለሁ። ትናንት ምሽት ለክፍለጦር አመራሮች ትዕዛዝ የሰጠ አርበኛ ዛሬ በጧት 12 ሰዓት ላይ እጄ ሰጠ የሚለውን ዜና አምነን እንቀበል የምትለኝ ከሆነ እየታግልሁት ነው የምትለውን አገዛዝ አላወቀውምና እንደ አዲስ አጥናው እልሃለሁ። አገዛዙ በዛሬው ዜና ላይ ሁለት ነገሮችን ለማሳካት አስቦ እየሰራ እንደሆነ ለማወቅ ችያለሁ። እነሱም:- አንደኛ- ዋና የፋኖ መሪ እጁን ሰጥቷል፣ ቀሪዎቹ ተከታዮች እጃችሁን ስጡኝ ለማለት አስቧል፣ በቀጣይ ቀናትም በብልፅግና ሚዲያዎች “የፋኖ ኃይሎች ኮ/ል አሰግድ መኮንን ተከትለው ለመንግስት እጃቸውን ሰጡ” የሚል ዜና Lead አስበዋል። ግን አይሆንም፣ አይሳካምም። ሁለተኛ- የፋኖ ዋና መሪውንና አዛዡን ይዤዋለሁ፣ ፋኖን አጥፍቼዋለሁ ስለዚህ ተስፋ የምታደረጉ አዲስ አበቤ፣ ብሔር ብሔረሰቦች፣ ባለሀብቶች እና ወዘተ አርፋችሁ ተቀመጡ ለእኔም ገብሩ የሚል መልዕክት ማስተላለፍ ፈልገዋል። የአርበኛ አሰግድ መኮነን ማዕረግ “ኮለኔል” አይደለም፣ ኮለኔል የሚል ማዕረግና “የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮለኔል አሰግድ መኮነን” ብለው የሰጡት ለፕሮፓጋንዳ ጠቀሜታቸው ነው። ስለዚህ የአገዛዙ የሴራ መንገድ አስፈጻሚዎች አትሁኑ! የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ አራቱም ክፍለ ጦሮች በዛሬው ዕለትም ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ የብልጽግና ወታደርን እየገረፉት ይገኛል። #ማስታወሻ:- የስልክ ታወራሮች የአገዛዙ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

° ” የተቆራረጠ ደሞዝ አንወስድም ምክኒያቱም ካሁን በፊትም እንዲሁ ተደርገናል ” – የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች

° ” የተቆራረጠ ደሞዝ አንወስድም ምክኒያቱም ካሁን በፊትም እንዲሁ ተደርገናል ” – የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች ° ” የተፈጠረው የካሽ እጥረት በመሆኑ ወደስራ ተመለሱ ” – የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች ” ከግንቦት ወር ጀምሮ ደሞዝ አልተከፈለንም ” በሚል ስራ አቁመው ወደ ዞኑ ጤና መምሪያ ጥያቄ ለማቅረብ ለመሄድ ሲሞክሩ በሀድያ ዞን ፖሊስ ተደብድበው ወደ ሆሳዕና ከተማ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል። ጉዳዩን ከምን ደረሰ ? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላችሁ ሰራተኞቹ አሁንም ስራ እንዳቆሙ መሆኑን በመግለጽ የተፈቀደውን የአንድ ወር ደሞዝ እንዳይወስዱ በ2015 ዓ/ም በዚህ መልኩ እንደተቃጠለው ገንዘባቸው እንዳይሆን ስጋት እንደገባቸው ገልጸዋል። ሰራተኞቹ አሁን ላይ ውይይት አድርገዉ አንዳች ውሳኔ ላይ ለመድረስ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን በመግለጽ በቅርቡ አቋማቸውን እንደሚገልጹ ነግረዉናል። የሰራተኞቹን ስራ ማቆም ተከትሎ በስራ ላይ  ችግር አልተፈጠረም ወይ ? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላቸው የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ  አብርሀም ሎምቤ ፥ ” ስራ ያላቆሙ ሰራተኞች በጫና ውስጥ ሆነው እየሰሩ ቢሆንም ስራ ያቆሙ ሰራተኞች ወደስራ ገበታቸው ተመልሰው ብንነጋገር የተሻለ ነው ” ብለዋል። ለምን የሰሩበትን ክፍያ አትሰጧቸውም ? በሚል ላነሳነው ጥያቄ ” የካሽ እጥረት ነው የተፈጠረው ፤ የካሽ እጥረት እንደሀገር የሚገጥም በመሆኑ ክፍያቸው አይቀርባቸውም ” ሲሉ መልሰዋል። በሌላ በኩል ስራቸውን ያቆሙ ሰራተኞች ወደስራ መመለሳቸውን በደብዳቤ እየገለጹ የአንድ ወር ደሞዝ ይውሰዱ ስለተባለው ጉዳይ የጠየቅናቸው አቶ አብርሀም ” ዋናው ወደስራ መመለሳቸው በመሆኑ በቃልም
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት ናዳ ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች የነፍስ አድን ስራ ከክልሉ አቅም በላይ ሆኗል ተባለ

በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት ናዳ ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች የነፍስ አድን ስራ ከክልሉ አቅም በላይ ሆኗል ተባለ 👉 የሟቾች ቀጥር ከ157 በላይ መድረሱ ተገለፀ ከቀናት በፊት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰ ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ የበርካታ ሰዎች ሕይወት ማለፉ የሚታወስ ነው። ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ሰአት ድረስ የሟቾች ቁጥር 157 መድረሱ የተገለፀ ሲሆን ይህ ቁጥር ግን በየሰአቱ እያሻቀበ መሆኑን የሚገልጹት የአካባቢው ነዋሪዎችም የነብስ አድን ስራው ከዞኑ አልፎም ከክልሉ አቅም በላይ ሆኗል ሲሉ ጠቁመዋል፡፡ ከአንድ ቤተሰብ 8 ሰዎች የሞቱበት መራር አደጋ መድረሱን የገለጹት አንድ ነዋሪ በነብስ አድን ስራ ላይ የተሰማሩ የአካባቢው ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ጭምር ህይወት ማለፉን አንስተዋል፡፡ አሁን ላይ ተጨማሪ የቁፋሮና መሰል ማሽኖችን ወደ አካባቢው ማሰማራት ያስፈልጋል ይህ ደግሞ ከዞኑና ከክልሉ አቅም በላይ ሆኗል በማለት የአደጋውን አሳሳቢነትም ገልጸዋል፡፡ በትናንትናው እለት የዞኑ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ማርቆስ መለሰ በበኩላቸው በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በመለየት የነፍስ አድን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው እንደነበር አይዘነጋም፡፡ የአካባቢው መልካምድራዊ አቀማመጥና በእለቱ በአካባቢው የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎም ጉዳቱን ከፍተኛ እንዳደረገው መረጃ ያመላክታል፡፡
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በጎፋ ዞን የሟቾች ቀጥር ከ146 በላይ መድረሱ ተገለፀ

በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰ ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ እስካሁን የሟቾች ቀጥር ከ146 በላይ መድረሱ ተገለፀ። የዞኑ የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካና ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ እና አስቸኳይ የአደጋ ጊዜ መልሶ ማቋቋሚያ ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሀብታሙ ፌተና አደጋውን አስመልክተው የሰጡት መግለጫ ያሳያል። በመግለጫቸውም እስካሁን በተደረገው ፍለጋ ሴቶችና ሕፃናትን ጨምሮ ወንድ 96 እና ሴት 50 በድምሩ የ146 ሰዎች አስክሬን የተገኘ ሲሆን፣ የአስክሬን ፍለጋ አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችልና የነፍስ አድን ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል።
Posted in Ethiopian News

አዳነች አቤቤ ተጫራች ስላጣሁ የሊዝ ጨረታውን ቀን አራዝሜያለሁ አለች

የአዲስ አበባ የመሬት ሊዝ ጨረታ ለተጨማሪ 10 ቀናት ተራዘመ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በፒያሳ በኮሪደር ልማት ያጸዳቸውን አካባቢዎች ጨምሮ በስምንት ክፍለ ከተሞች ለሚገኙ መሬቶች ያወጣው ሶስተኛ ዙር የሊዝ ጨረታ፤ ለተጨማሪ 10 ቀናት ተራዘመ። ➡️ ከዛሬ ሰኞ ሐምሌ 15፤  2016 ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ሊካሄድ የነበረው ጨረታ የተራዘመው፤ “በቂ ተጫራቾች ባለመገኘታቸው ነው” ተብሏል። ➡️ የከተማይቱ አስተዳደር የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ለሶስተኛው ዙር ጨረታ ያቀረባቸው መሬቶች ብዛት 228 ነው። ➡️ ከእነዚህ መሬቶች ውስጥ የተወሰኑት ከዚህ ቀደም የነበራቸው የሊዝ ውላቸው ተቋርጦ ወደ መሬት ባንክ የገቡ መሆናቸው ከከተማ አስተዳደሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ➡️ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካለፈው የካቲት ወር መጨረሻ ጀምሮ ተግባራዊ በማድረግ ላይ በሚገኘው “የመንገድ ኮሪደር ልማት” ሳቢያ እንዲጸዱ በተደረጉ አካባቢዎች የሚገኙ መሬቶችም እንዲሁ በሶስተኛው ዙር ጨረታ እንዲካተቱ ተደርገዋል። ➡️ እነዚህ መሬቶች በአብዛኛው የሚገኙት በአራዳ ክፍለ ከተማ የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም አቅራቢያ ባሉ የፒያሳ አካባቢዎች ነው። 🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13618/
Posted in Ethiopian News

ገብረ ጉራቻ ላይ ታግተው በነበሩት ተማሪዎች ዙርያ ምን አዲስ ነገር አለ?

ገብረ ጉራቻ ላይ ታግተው በነበሩት ተማሪዎች ዙርያ ምን አዲስ ነገር አለ? ማሰባሰብ የቻልኳቸውን መረጃዎች ላካፍላችሁ:  ኤሊያስ መሰረት ከቁጥር ጋር የተያያዘ መረጃ •አጠቃላይ ተያዙ የተባሉ ተማሪዎች ብዛት 106 (ይህ ግን ጥቂት ተማሪ ያልሆኑ ተጓዦችን ሊያካትት ይችላል) •በነጻ የተለቀቁ ተማሪዎች ብዛት 29 ወይም 30 •እስካሁን ገንዘብ ከፍለው እንደተለቀቁ የተሰማ ተማሪዎች ቁጥር 8 •አመለጡ የተባሉ ተማሪዎች ቁጥር 1 ከተለቀቁ ተማሪዎች የተሰበሰበ መረጃ •ከአንድ ተማሪ በተገኘው መረጃ 106 የሚሆኑ ተማሪዎችን ከመኪና አውርደው በመሳሪያ እና በዱላ እያስፈራሩ ጫካ ውስጥ እየመሩ ወሰዷቸው። ከዚህ ውስጥ እስከ 30 የሚሆኑትን ባንክ አካውንታቸው ውስጥ ያለውን ገንዘብ ከወሰዱ በኋላ ለቀቁ (በብሄር እየለዩ)፣ ሌሎቻቸውን ይዘው ሄዱ። አግተው ሶስት ቀን ያክል ካቆዩአቸው በኋላ ገንዘብ ከፍለው ተለቀዋል። •ሌላ ተማሪ ደግሞ ተማሪ ካልሆኑ ከአጋቾቹ ጋር ከነበሩ ወጣቶች ጋር ወደ ከተማ በሌሊት እንደላኳቸውና ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ሲሆን መንገድ ላይ ወደ አንድ ቤት ገብተው እንዳደሩ፣ ከዚያም ጉዟቸውን ቀጥለው ሲነጋጋ ቱሉ ሚልኪ ወደምትባል ከተማ እንደደረሱ ተናግረዋል። •ሌላ ተማሪ ደግሞ ስለአጋቾቻቸውና ስለቆይታቸውም መረጃ ሰጥተዋል። ተማሪዎቹን መንደር ውስጥ ያሉ ጎጆ ቤቶች እንዳቆዪአቸውና ምግብም ከመንደር አምጥተው እንደሚያበሏቸው ጠቅሰዋል። በነበራቸው ቆይታ ምንም ዓይነት የጾታ ጥቃት አላየሁም ብላዋል። ተጨማሪ መረጃ •አንድ የተማሪ አባት “እኔ እዚህ ግባ የሚባል ገንዘብ የለኝም። አንድ ሚሊዮን ተጠይቄያለሁ፣ እኔ ግን መቶ ሺህ እንኳ የለኝም። አሁን ዘመዶቼን፣ ጓደኞቼንና ቤተክርስቲያኔን ጠይቄ ያገኘሁት ብር በቂ ስላልሆነ ገበያ መሃል አንጥፌ መለመን ጀምሬያለሁ። በአካባቢዬ
Posted in Ethiopian News

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንዲት ተሳፋሪውን አባሮ ለሚኒስትሩ ቦታዋን መስጠቱ እያነጋገረ ነው።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንዲት ተሳፋሪ ከተቀመጠችበት አስነስቶ ለሚኒስትሩ ቦታዋን መስጠቱ ተቃውሞ አስነስቷል። በአይሮፕላን ውስጥ በነበሩ ተሳፋሪዎች የተለቀቀው ቪዲዮ እንደሚያሳየው ተሳፋሪዋ ከአየር መንገዱ ሰራተኞች ጋር በጥልቀት ተጨቃጭቃለች፤  አየር መንገዱ ተሳፋሪዋን ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል ሲሉ የማሕበራዊ ድረ ገፅ ተተቃሚዎች እየተናገሩ ይገኛል። በጩኸትና በጭቅጭቅ የታጀበው የበረራ መጀመሪያ ሚኒስትሩ ቦታውን ላለመቀበል ትብብር ባለመደረጋቸው የተወቀሱ ሲሆን አሳፋሪ ተብለዋል በተሳፋሪዎቹ ። Ethiopian Airlines kicked out a passenger on my flight because a minister took her seat. They didn’t apologize and they eventually forcefully offloaded her screaming. The minister did nothing. Disgraceful pic.twitter.com/RSgDUbbDez — Larry Madowo (@LarryMadowo) July 20, 2024
Posted in Amharic News, Ethiopian News, Video

ለአጋቾቹ የምንከፍለው ገንዘብ ስለሌለን በየገበያው እና በየመንደሩ እየለመንን ነው የምንገኘው_ የታጋቾች ቤተሰቦች

ከሁለት ሳምንት በፊት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በገርበ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ በታጣቂዎች ታግተው የሚገኙ ተማሪዎችን ለማስለቀቅ፤ አጋቾቹ የጠየቁትን ገንዘብ ለመክፍል የድጋፍ ደብዳቤ በማጻፍ በልመና ላይ እንደሚገኙ የታጋቾች ቤተሰቦች ገለጹ። ባለፈው ሰኔ ረቡዕ ሰኔ 25 ቀን 2016ዓ.ም በአማራ ክልል ከሚገኘው የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተነስተው ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያሉ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገርበ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ በታጣቂዎች ከታገቱ ከ150 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች መካከል እስከአሁን ያልተለቀቁ መኖራቸውንና በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ የታጋች ቤተሰቦች ለአዲስ ስታንዳርድ ገልፀዋል:: አዲስ ስታንዳርድ ያነጋገራቸው የታጋቾች ቤተሰቦች እንደገለፁት ከሆነ የተጠየቁትን ክፍያ ከፍለው የተለቀቁ ተማሪዎች ቢኖሩም ገንዘቡን መክፈል ያልቻሉ ግን እስከአሁን ድረስ በታጣቂዎች ተይዘው እንደሚገኙ አስታውቀዋል:: ለደህንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የታጋች እህት ረቡዕ ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ.ም የታገተች እህታቸው እስከአሁን እንዳልተለቀች ተናግረዋል:: “ያለብር የሚያስለቅቅ ምንም አካል የለም:: እኛ ብር እያሰባሰብን ነው ያለነው:: እህቴን ትላንትም ዛሬ ጠዋትም አውርቻታለሁ:: ታስራ ነው ያለችው:: ከእሷ ጋራ የነበሩ 4የሚሆኑ ሰዎች የተጠየቁትን እስከ አንድ ሚሊየን የሚደርስ ገንዘብ ከፍለው ወጥተዋል:: እኛ የምንከፍለው ስለሌለን ከወረዳው የድጋፍ ደብዳቤ አጽፈን በየገበያው እና በየመንደሩ እየለመንን ነው የምንገኘው” ሲሉ ገልጸዋል። “ገንዘቡ የሚሞላልን ከሆነ አጋቾቹ የሚያዘጋጁት ሰው አለ:: ለሱ ሄደን እናስረክባለን:: ከዛ ልጅቷን ወደ እኛ ያመጣሉ:: ይህን እንድናደርግ ነው አጋቾቹ መመሪያ የሰጡን::” ሲሉ አክለው ገልፀዋል:: ሌላኛው ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የታጋች ወንድም ለአዲስ ስታንዳርድ እንደገለፁት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ንግድ ባንኮች በተለያዩ ዘርፎች ላይ በተገደበ ሁኔታ እንዲሰማሩ ተፈቀደ ።

ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ንግድ ባንኮች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ እንዳይሰማሩ ያደረገው በ2009 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወጥቶ የነበረው መመሪያ በአዲስ መመሪያ ተተክቶ ንግድ ባንኮች በተለያዩ ዘርፎች ላይ በተገደበ ሁኔታ እንዲሰማሩ ተፈቀደ ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሀምሌ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ባወጣው መመሪያ ንግድ ባንኮች ሊሰማሩባቸው የሚችሏቸውን ዘርፎች ዘርዝሯል። ያንብቡት-https://tinyurl.com/yf6bpkfd
Posted in Amharic News, Ethiopian News

” ሰበብ እየተፈለገ ከስራ እየተባረርን ነው ” – የደቡብ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ሰራተኞች

° ” ሰበብ እየተፈለገ ከስራ እየተባረርን ነው ” – የደቡብ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ሰራተኞች ° ” ከህግና ስርአት ውጭ የተሰናበተ አንድም ሰራተኛ የለም ” – የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ ” የደቡብ ክልል መንግሥት ፈርሶ ሰራተኛዉ ሲበተን ደቡብ ኢትዮጵያ ቢደርሰንም እንደ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኛ መብታችን ተከብሮ መስራት አልቻልንም ” ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። ” ቢሮው መቀመጫውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ  ካደረገና ስራ ከጀመርን ጀምሮ በርካታ ግፍ እየተፈጸመብን ነው ”  የሚሉት ከቢሮው የተባረሩ እና ያለጥፋታችን በከባድ ማስጠንቀቂያ ውስጥ ነን ያሉ  ሰራተኞች ” ቅጣቶች እና ክሶች ያለህግና ስርአት የቢሮው ዲስፕሊን ኮሚቴ እንኳን በማያዉቀዉ መልኩ እየተተገበሩ ናቸው ” ሲሉ ከሰዋል። ” በዚህ አመት ብቻ ስራ ከጀመርነዉ ዉስጥ ወደ 5 ሰራተኞች ያለማስጠንቀቂያ እና ህጋዊ ስርአት ከቢሮዉ ተገፍትረን ተባረናል ” በማለት ገልጸዋል። ” ከቢሮ ተገፍትረን ከተባርንና ደሞዝ ከተቋረጠብን በኋላ ከስራ ገበታ መቅረታችን የሚገልጽ ደብዳቤ ይለጠፍብናል ” የሚሉት ሰራተኞቹ  ጉዳዩን ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ  ብናሳውቁም መፍትሄ አላገኘነም ብለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰራተኞችን ቅሬት ይዞን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊን ዶክተር ኦንጋዮ ኦዳን አነጋግሯል። እሳቸው ፥ ” ከህግ እና ስርአት ውጭ አንድም ሰራተኛ አልተሰናበተም ” ብለዋል። ” በደል ደርሶብኛል የሚል ካለም ለመነጋገርና ስህተት ተሰርቶ ከሆነ ለመጠየቅ ዝግጁ ነን ” ሲሉ ቃል ገብተዋል። ” በብዛት ከቢሮዉ የለቀቁ ሰራተኞች ፦ – ከስራ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአዳነች አቤቤ አስተዳደር የተበደረውን 29.8 ቢሊዮን ብር እንዲከፍል ቀነ ገደብ ተሰጠው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኮንዶሚኒየም ግንባታ የወሰደውን ብድር “በአስቸኳይ” እንዲከፍል ቀነ ገደብ ተሰጠው  የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) ቤቶች ግንባታ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወሰደውን 29.8 ቢሊዮን ብር ብድር “በአስቸኳይ” እንዲከፍል ቀነ ገደብ ተሰጠው። አስተዳደሩ ብድሩን በአንድ ወር ከአስራ አምስት ቀን ጊዜ ውስጥ እንዲከፍል ቀነ ገደብ የሰጠው የገንዘብ ሚኒስቴር ነው። የገንዘብ ሚኒስቴር ለከተማ አስተዳደሩ ፋይናንስ ቢሮ ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 8፤ 2016 በጻፈው ደብዳቤ፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለ40/60 እና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ የሚውል ብድር በተለያየ ጊዜ መስጠቱን ጠቅሷል። ባንኩ ለከተማ አስተዳደሩ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ብድሩን የሰጠው፤ የቦንድ ግዢ ዋስትና በመያዝ እንደሆነም “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” በተመለከተችው ደብዳቤ ላይ ሰፍሯል። ሆኖም ኮርፖሬሽኑ የወሰደውን ብድር በተዋዋለበት ጊዜ ባለመመለሱ እና ውዝፍ ዕዳ በመጠራቀሙ፤ ወደ ባንኩ የተበላሸ ብድር መደብ ውስጥ እንዲገባ መደረጉን ያትታል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ክትትል ክፍል ይህንንኑ በመጠቀስ፤ ገንዘብ ሚኒስቴር በሰጠው ዋስትና መሰረት ቀሪው ብድር እንዲከፈለው ጥያቄ ማቅረቡም በደብዳቤው ተመላክቷል። 🔴 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13615/
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከ”ዐማራ ፋኖ በጎንደር” የተሰጠ መግለጫ

ከ”ዐማራ ፋኖ በጎንደር” የተሰጠ መግለጫ የዐማራ ሕዝብ የገጠመውን መንግሥት መር የኅልውና አደጋ ለመቀልበስ ዱር ቤቴ፣ አራዊት ዘመዴ ካለ ዓመታት ተቆጥረዋል። በየቀጠናው ነጻነትን ሽቶ፣ ግፍን ተጸይፎ፣ ኅልውናውን አስቦ በሐቅ ላይ መሠረቱን አድርጎ የፈነነው አርበኛ ተቋማትን እያሳደገ ወደ አንድ ማዕከላዊ ተቋም ማምጣት አስፈላጊነቱ ውሎ ያደረ ሐቅ ነው። ይህንን ጉዳይ በወጉ የተረዱ የዐማራ ሕዝብ የኅልውና ታጋዮች አንድ ድርጅታዊ አታጋይ ተቋም ለማቆም በብርቱ ከሚደክሙ ቀጠናዊ ተቋማት መካከል “የአማራ ፋኖ በጎንደር” አንዱ ነው። እንደ ተቋም አንድ ዐማራዊ ድርጅት እንዲፈጠር ያለን ጽኑ ፍላጎት ከንግግር ባለፈ በተግባርም ጭምር ዋጋ የከፈልንለተና የምንከፍልለት መሠረታዊ ጉዳይ ነው። ዳሩ ግን ተቋምን የምናዋልደው ለሕዝባችን ዘለቄታዊ ኅልውናን በማረጋገጥ ሂደት የጀመርነውን ትግል አንድ እርምጃ ወደፊት እንዲያስፈነጥር እንጅ ግለሰባዊ ክብርና ዝናን እንዲሁም መርኅ አልባ የሥልጣን ፍትወትን ለማስተናገድ እንዳልሆነ መላው ሕዝባችንና አርበኛው የሚገነዘበው ሐቅ ነው። መሠረታዊ ጉዳዩ ይህ ሆኖ እያለ “የዐማራ ፋኖ በጎንደር” አንድ ማዕከላዊ ድርጅት አዋልደናል በሚለው ውሳኔ ላይ እንደ ተቋም እንደሌለንበት ለሕዝባችንና ለመላው የትግል ጓዳችን ማስገንዘብ እንወዳለን። ይሁን እንጅ ተቋማችን አንድ ዐማራዊ አታጋይ ድርጅት እንዲፈጠር ከሌሎች ጠቅላይ ግዛቶች ጋር የሚሠራ አመቻች ኮሚቴ መርጦ በመላክ በመርኅና በአሠራር የሚወለድ ተቋም እንዲፈጠር ብንሰይምም ከጅምሩ የአካሄድና የመርኅ ጥሰቶች ጭምር እንደነበሩበት በመሪያችን በኩል የይስተካከል አቋማችንን ብናሳይም ጉዳዩ ትኩረት ሳይሰጠው አድሮ እዚህ ደረጀ ደርሷል። ከዚህ ጉዳይ ጋር ተያይዞ በተለያዩ ግለሰቦች ጭምር በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚቀርቡ ጉዳዮች ተቋማዊ አሠራርንና መርኅን ከመጣሳቸው
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

የ3 ወር ውዝፍ ደሞዝ አልተከፈለንም ያሉ የወላይታ ዞን የመንግስት ሰራተኞች ቁጣቸውን አሰሙ፡፡

የ3 ወር ውዝፍ ደሞዝ አልተከፈለንም ያሉ የወላይታ ዞን የመንግስት ሰራተኞች ቁጣቸውን አሰሙ፡፡ 👉የአካባቢው ባለስልጣናት በበኩላቸው ለደሞዝ የተያዘው በጀት ለአፈር ማዳበሪያ ግዢ ውሏል የሚል መልስ ሰጥተዋል፡፡ ሐምሌ 12 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የ 3 ወር ደሞዝ ስላልተከፈለን ቤተሰባችን አደጋ ላይ ወድቋል ሲሉ በወላይታ ዞን ሆቢቾ ወረዳ የሚያገለግሉ የመንግስት ሰራተኞች ናቸው ቁጣቸውን ያሰሙት፡፡ መሰረታዊ የሚባለውን መብታችንን ተነጥቀናል የሚሉት ሰራተኞቹ ከወርሃ ግንቦት አንስቶ ወርሃዊ ደሞዛችንን እያገኘን አይደለም፤ ይህም ኑሮን ከባድ አድርጎብናል በዚህ ዘመን እንኳን ያለደሞዝ በደሞዝም ህይወትን መምራት ከባድ ነው ሲሉ ያሉበትን አስቸጋሪ ሁኔታ ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡ ለሙሉ ዘገባ፡ https://addismaleda.com/archives/38336
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ለአርበኞች መታሰቢያ በአጼ ኃይለ ስላሴ የተገነባ ህንጻ ፈረሰ

ለአርበኞች መታሰቢያ በአጼ ኃይለ ስላሴ የተገነባ ህንጻ፤ ቦታው “ለኮሪደር ልማት” በመፈለጉ ፈረሰ ከጣሊያን ወራሪ ሰራዊት ጋር ለተፋለሙ አርበኞች መታሰቢያ እንዲሆን በአጼ ኃይለ ስላሴ ዘመነ መንግስት የተገነባው የአርበኞች ህንጻ፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትዕዛዝ እንዲፈርስ ተደረገ። ዘንድሮ 60 ዓመቱን የደፈነው ህንጻ እንዲፈርስ የተደረገው፤ ቦታው ለመንገድ ኮሪደር ልማት በመፈለጉ ምክንያት እንደሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል። በአዲስ አበባ አራት ኪሎ ከሚገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፊት ለፊት የሚገኘው ይህ ህንጻ ንብረትነቱ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ነው። ማህበሩ “የዐርበኞች ግንብ” በሚል ስያሜ በ1956 ዓ.ም ከተገነባለት ከዚህ ህንጻ ጎን፤ ሌላ ባለ አራት ወለል ህንጻ ከ13 ዓመት በፊት አሰርቶ ለአገልግሎት አብቅቷል። ማህበሩ በባለቤትነት ሲያስተዳድራቸው የቆያቸውን ሁለት ህንጻዎች ለቅቆ የወጣው ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ሐምሌ 3፤ 2016 እንደሆነ የማህበሩ ፕሬዝዳንት የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እዝራ ንጋቱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የማህበሩን አንድ ህንጻ ተከራየቶ የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መናገሻ ምድብ ችሎት፤ ከዚህ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ አገልግሎት ማቋረጡን ባወጣው ማስታወቂያ ይፋ አድርጓል። ምድብ ችሎቱ በዚሁ ማስታወቂያው፤ የአድራሻ ለውጥ ለማድረግ የተገደደው “ቦታው ለኮሪደር ልማት የሚውል” በመሆኑ ምክንያት እንደሆነ ገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ለማህበሩ በጻፈው ደብዳቤም፤ ህንጻዎቹ የሚፈርሱት “ቦታው ለልማት በመፈለጉ” እንደሆነ መጥቀሱን አቶ እዝራ አስታውቀዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13608/
Posted in Ethiopian News

ኢትዮጵያ ቤንዚን ጨመረ

ቤንዚን ጨመረ ከዛሬ ከሀምሌ 3 ቀን 2016 ዓም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ከአውሮፕላን ነዳጅ በስተቀር በቤንዚን፣ በኬሮሲን፣ በነጭ ናፍጣ፣ በቀላል ጥቁር ናፍጣና በከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደርጎል። 👉 ቤንዚን …………………………… ብር 82.60 በሊትር 👉 ነጭ ናፍጣ……………………… ብር 83.74 በሊትር 👉 ኬሮሲን ……………………………ብር 83.74 በሊትር 👉 የአውሮፕላን ነዳጅ …………….ብር 70.83 በሊትር 👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ…………….ብር 65.48 በሊትር 👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ…………….ብር 64.22 በሊትር የአለም ገበያ ላይ እየታየ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መሠረት በማድረግ ከዛሬ ሀምሌ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ሥራ ላይ የሚውለው የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማሰተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ልጆቻችን በእገታ ስር ናቸው፤ ….. ተማሪዎቹን ወደ ወለጋ እንደወሰዷቸው እየሰማን ነው !

“በተደረገ ጥብቅ ኦፕሬሽን ከ167 ታጋች ተማሪዎች መካከል 160ዎቹ ተለቀዋል”— የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ “እውነት ይሆን?” ብዬ የታጋቾች ቤተሰቦችን፣ የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ወንጌላዊያን ህብረትን እና የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንትን ማምሻውን ጠየቅኩ። ምላሹ ይህን ይመስላል: “አሁንም ልጆቻችን በእገታ ስር ናቸው፣ የማስለቀቂያ ገንዘብ ከህዝብ እየለመንን ነው። በዚህ ግዜ እንዲህ አይነት መረጃ ማውጣት የጭካኔ ስራ ነው”— የታጋቾች ቤተሰቦች “ታግተው ያሉ በርካታ ተማሪ አልተለቀቁም፣ ተለቀቁ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ከየት እንደመጣ አናውቅም። እንደውም አሁን ተማሪዎቹን ወደ ወለጋ እንደወሰዷቸው እየሰማን ነው”— የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ወንጌላዊያን ህብረት “አንዴ መረጃ ሰጥቻለሁ፣ እኔ ጋር ለምን ትደውላላችሁ?”— የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር አስማማው ዘገዬ ( ጋዜጠኛ ኤሊያስ መሰረት)
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሰበር ዜና! ~ ጄነራል ተፈራ ማሞ ከግንባር ጥሪ አቀረቡ

ሰበር ዜና! ~ ጄነራል ተፈራ ማሞ ከግንባር ጥሪ አቀረቡ ይህን ተጭነው መልዕክቱን ያዳምጡ  =   https://t.me/merejamedia/6302
Posted in Ethiopian News

ንጹሀንን ለገንዘብ ማገት በአስቸኳይ ይቁም- በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር

ንጹሀንን ለገንዘብ ማገት በአስቸኳይ ይቁም- በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር እየተደጋጋመ የመጣው ንጹሀን ዜጎችን እና ተማሪዎችን ለገንዘብ ጥቅም ብሎ ማገት እንዲቆም በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ገለጹ። በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ መረጃን አዲስ ማለዳ እንደተመለከተችው፤ “በኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች አሁንም የቀጠለው የንጹሀን እገታ፤ የተራዘመ ጦርነት የወንጀል መስፋፋት እና የሕግ የበላይነት መዳከም እንደሚያመጣ ያሳያል” ተብሏል። ባለፈው አንድ ሳምንት ብቻ ከአንድ መቶ በላይ ተማሪዎች እና ተጓዦች በመንገድ ላይ ታግተው የማስለቀቂያ ገንዘብ እየተጠየቀባቸው ይገኛል ሲሉ አምባሳደሩ መግለጻቸውን ኤምባሲው አስታውቋል። #Ethiopia #StopViolence pic.twitter.com/Cqh3J0lfBT — U.S. Embassy Addis (@USEmbassyAddis) July 8, 2024
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ፣ የግቢው የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት እና የታጋች ቤተሰብን ምን አዲስ አለ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬም ጥያቄ አቅርቧል። የታጋች ቤተሰቦች አጋቾቹ ወደ 20 የሚሆኑ ታጋቾችን ከትላንት ጀምሮ ወደ ማያውቁትና ጫካ በበዛበት ቦታ በቡድን ከፋፍለው በእግር እያጓጓዟቸው እንደሆነ ተናግረዋል። ይህንን ነገር የሰሙት አጋቾቹ ደውለው ” ልጆቻችሁ እንዲለቀቁ ገንዘብ አምጡ ” ብለው በዛቱበት እና ከልጆቻቸው ጋር በስልክ በተገናኙበት ወቅት ነው። አጋቾቹ ገንዘብ እንዲላክላቸው ፤ ለዚህም ትንሽ ጊዜ እንዲሰጡ ቢጠየቁም ለመስማት ፈቃደኞች እንዳልሆኑ የታጋች ቤተሰቦች ገልጸዋል። የልጆቻቸው ደህንነት እጅግ በጣም በከፋ ጭንቀት ላይ እንደጣላቸው ገልጸው ልጆቻቸውን ወደ ሌላ አገር እንዳያስወጧቸው መከላከያ እና ፌደራል ፓሊስ ክትትል አድርገው እንዲታደጉላቸው ተማጽነዋል። ቲክቫህ ያነጋገረው የወጌላዊያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረትን በበኩሉ፣ ትላንት መኪና እየጠበቁ የነበሩት መኪና አግኝተው ወደ ቤተሰብ ጉዞ ማድረጋቸውን ገልጿል። ቀሪዎቹ ግን አሁንም ገንዘብ በታጋቾቹ እየተጠየቁ ነው ብሏል። በታጋች ተማሪዎቹ ጉዳይ አዲስ ነገር አለ ? ሲል ቲክቫህ የጠየቃቸው የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አንድ አካል ፥ ለበላይ ሪፓርት ከማድረግ ውጪ ምንም ማድረግ እንዳልተቻለ ገልጸዋል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአብይ አሕመድ አስቀያሚ ንግግሮች በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ዘንድ ቅሬታን አስነስቷል

ተሰናባቹ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር የጠቅላይ ሚኒስትሩን የፖለቲካ ምክንያት ውንጀላ ውድቅ አደረጉ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰብአዊ መብት አካላት ላይ ያነጣጠረ ከባድ ትችት ቅሬታ አስነስቷል። Outgoing Human Rights Commissioner rejects PM’s political motive allegations , Harsh criticism from the Prime Minister aimed at human rights bodies has raised eyebrows at civil society organizations. https://www.thereporterethiopia.com/40953/
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

” የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲፈርደኝ እፈልጋለሁ ” ፍሬወይኒ ሀይሉ

” የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲፈርደኝ እፈልጋለሁ ” ፍሬወይኒ ሀይሉ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ያለአግባብ በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር ተሳታፊ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ሳልካተት ቀርቻለሁ ስትል ቅሬታዋን ህዝብ ይወቅልኝ በማለት ገልፃለች። በ1500 እና 5000 ሜትር ተወዳዳሪ መሆኗን ያስታወሰችው አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ በአመቱ ውስጥ በሁለቱም ርቀቶች ከሌሎች አትሌቶች የተሻለ ውጤት አስመዝግቤ ነበር ትላለች። አትሌቷ በ2024 የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በ1500ሜ ወርቅ እና የተሻለ ሰዓት እንዲሁም በ5000ሜ የ2024 የአለም ምርጥ 3ኛ ሰዓት ባስመዘግብም ከሁለቱም ርቀቶች ከኦሎምፒክ ውጪ ሆኛለሁ ብላለች። አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ቀጥላም ” እኔ በዚህ አመት የተሻለ ሰዓት ባስመዘግብም ከአመት በፊት ጥሩ ውጤት ያላቸው አትሌቶች ተመርጠው እኔ ቀርቻለሁ የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልኝ። በ2024 ምንም ውድድር ሳይወዳደሩ የ2023 አላቸው ተብሎ መምረጥ አግባብ አይደለም ለምን በሀቀኝነት አይመረጥም ምንም ሳይሮጡ እየተመረጡ ነው እኛ ግን ደክመንም እየቀረን ነው። የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ እና አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለምንድን ነው የእኛን ማየት የማይችለው በዚህ ላይ ማብራሪያም እፈልጋለሁ።”ስትል ተናግራለች። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በትላንትናው ዕለት ኢትዮጵያን በኦሎምፒክ የሚወክሉ አትሌቶችን ይፋ ሲያደርግ አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ የ5000ሜ ተጠባባቂ ሆና ተመርጣለች። ምንጭ – ሀገሬ ቴሌቪዥን
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሁለተኛው ጀኔራል ፋኖን ተቀላቀለ!

ሁለተኛው ብርጋዲየር ጀኔራል ፋኖን ተቀላቀለ! ብርጋዲየር ጀኔራል ተዘራ ንጉሴ ፋኖን መቀላቀሉ ተሰምቷል! የቀድሞው የአማራ ልዩ ኃይል ከፍተኛ አመራር የነበረው ብርጋዲየር ጀኔራል ተዘራ ንጉሴ የሕልውና ትግሉን በይፋ መቀላቀሉን የአማራ ድምፅ የጎንደር ዘጋቢዎች ለማረጋገጥ ችለዋል። የቀድሞው የአማራ ልዩ ኃይል ዋና አዛዥ የነበሩት ብርጋዲየር ጀኔራል ተፈራ ማሞ ከሳምንት በፊት ወደ ፋኖ መቀላቀላቸውን ተከትሎ በርካታ የክልሉ ፅጥታ አባላት እና አመራሮች የሕልውና ትግሉን እየተቀላቀሉ መሆኑን የአማራ ድምፅ ሚድያ ካሰባሰበው መረጃ ለማረጋገጥ ችሏል። የብርጋዲየር ጀኔራል ተፈራ ማሞ ወደ ፋኖ መቀላቀልን ተከትሎ ነው ሌላኛው የብርጋዲየር ጀኔራልነት ማዕረግ ያለው ተዘራ ንጉሴ ፋኖን የተቀላቀለው ተብሏል። ### የአማራ ድምፅ ሚዲያ!
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በአማራ ክልላዊ መንግሥት ፣ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዛሬ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተሰማ።

አቶ አህመድ አሊ ዛሬ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተሰማ። በአማራ ክልላዊ መንግሥት ፣ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ ዛሬ በከሚሴ ከተማ ከሚገኝ መስጅድ ጁምአ ሶላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተነግሯል። የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ባወጣው የሀዘን መግለጫ ” ግድያው የተፈጸመው በጽንፈኛው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ነው ” ብሏል። አቶ አህመድ ከዋና አስተዳዳሪነታቸው በተጨማሪ የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በመሆን ማገልገላቸው ተገልጿል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሙሉ በሙሉ በፍላጎቴ ነው ላለመቀጠል የወሰንኩት ” – ዶክተር ዳንኤል በቀለ

ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ተጨማሪ የሥራ ዘመን መቀጠል የሚችሉበት እድል ነበር ? ” ቴክኒካሊ ይቻላል ማድረግ (በኃላፊነት ቦታው ላይ መቀጠል)  ፤ … ሙሉ በሙሉ በፍላጎቴ ነው ላለመቀጠል የወሰንኩት ” – ዶክተር ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የ5 ዓመት የሥራ ዘመን አብቅቷል። ምንም እንኳን ዶክተር ዳንኤል ለተጨማሪ የኃላፊነት ዘመን በቦታው ላይ ለመቆየት እድል ቢኖራቸውም ለ2ኛ ዙር የኃላፊነት ዘመን መቀጠል እንደማይፈልጉ ወስነዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ም/ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለን የዋና ኮሚሽነሩ ስልጣናቸው ሊራዘም ይችል ነበር ወይ ? ሲል ጠይቋል። እሳቸውም ፦ ” አንዱ የሪፎርሙ ሀሳብ የኃላፊነት ጊዜው ሲያልቅ ሊለቅ ይችላል የሚል ነው። ሌላ የሚከተለውን ሰው እንዲያመጣ። ሁል ጊዜ ቢሆን እስከመጨረሻ ድረስ በአዋጁ ላይ የተቀመጠውን ለጥጦ መጠቀም ሳይሆን አንዳንድ ጊዜ አንድ የኃላፊነት ዘመን / ዙር ጨርሶ ሌላ ሰው ይምጣ ፤ በተለይም ውስጥ ያለ ሰው መተካት ይቻላል ነው። ዋና ኮሚሽነሩ እራሳቸው ናቸው ከዚህ በኃላ ለሁለተኛ የኃላፊነት ዘመን አልሄድም ብለው የወሰኑት ” ሲሉ መልሰዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚሁ ጉዳይ ላይ ዶክተር ዳንኤል በቀለንም አነጋግሯቸዋል። ሁለተኛ ዙር ላለመቀጠል በራስዎት ፍላጎት ወስነው ነው ? ቢፈልጉ ሕጉ ይፈቅድሎታል ? ሲል ጠይቋል። ዶክተር ዳንኤል ፥ ” አዎን !!! በራሴ በፍላጎቴ ነው። ቴክኒካሊ ይቻላል ማድረግ (በኃላፊነት መቀጠል) ከተቋም ግንባታ አንጻር እኔ እንደዛ አልመክርም ምክንያቱም ተቋም መገንባት ማለት አንድ ሰው ዝም ብሎ መቀጠል ሳይሆን (renewal ስለሚፈቅድ) ተቋም ፈጥረህ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የዘፈቀደ እስር፣ የጅምላ እስር ወይም የፍርድ ቤት ውሳኔ አለማክበር ተፈጽሟል- የኢሰመኮ ዓመታዊ ሪፖርት 

በሁሉም ክልሎች ለማለት በሚያስችል ሁኔታ የዘፈቀደ እስር፣ የጅምላ እስር ወይም የፍርድ ቤት ውሳኔ አለማክበር ተፈጽሟል- የኢሰመኮ ዓመታዊ ሪፖርት  ዓርብ ሰኔ 28 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰኔ 2015 እስከ ሰኔ 2016 ድረስ ያለውን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አድርጓል። 132 ገጾችን የያዘው ዓመታዊ ሪፖርት በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክልሎች የትጥቅ ግጭቶች፣ ጥቃቶች ወይም የጸጥታ መደፍረሶች ከሐምሌ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. እስከ ግንቦት ወር 2016 ዓ.ም. የተመዘገቡ ሲሆን፣ በዚህ ሳቢያ በታጣቂ ኃይሎች እና በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች በሲቪል ሰዎች ላይ የሚደርስ የሞት እና የአካል ጉዳት አሳሳቢነት እንደቀጠለ ተመላክቷል። ለተጨማሪ ንባብ፡ https://addismaleda.com/archives/38260
Posted in Amharic News, Ethiopian News

“ማናቸውም አይነት ተጽእኖ ደርሶብን አያውቅም፤ ቢደርስብንም አንቀበልም” – ዶ/ር ዳንኤል በቀለ

“ማናቸውም አይነት ተጽእኖ ደርሶብን አያውቅም፤ ቢደርስብንም አንቀበልም” – ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የሰብአዊ መብት ተቋማት ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ወይም አጋር ሀገራት ገንዘብ ማሰባሰባቸው፤ “ነጻነታቸውን የሚቃረን” ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ተናገሩ። እርሳቸው የሚመሩት ተቋም ከአለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ገንዘብ ቢያሰባስብም፤ “ማናቸውም አይነት ተጽእኖ” ደርሶበት እንደማያውቅም ገልጸዋል። ➡️የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ይህን ያሉት፤ የሰብአዊ መብት ተቋማትን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በትላንትናው ዕለት ለሰነዘሩት ትችት በሰጡት ምላሽ ነው። ➡️ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ትላንት ሐሙስ ሰኔ 27 በተካሄደ የፓርላማ ስብሰባ ላይ የሰብአዊ መብት ተቋማትን እና አሰራራቸውን “መፈተሽ” እንደሚያስፈልግ ተናግረው ነበር። ➡️ ይህን መሰሉ ትችት “በመንግስት በጀት የማይተዳደሩ” የሰብአዊ መብት ተቋማት ላይ “ብዙ ጊዜ ይቀርባል” ያሉት ዶ/ር ዳንኤል፤ ጉዳዩ በሌሎች ሀገራትምም “የተለመደ እና በተደጋጋሚ የሚሰማ” እንደሆነ አመልክተዋል። ➡️ እንደ ኢሰመኮ ሁሉ ሌሎችም የሰብአዊ መብት ተቋማት “ሃብት ማሰባሰባቸው በራሱ ስህተት አይደለም” ሲሉም ዶ/ር ዳንኤል ዛሬ አርብ በመስሪያ ቤታቸው በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ➡️ “የተወሰኑ መንግስታዊ ድርጅቶች ብቻ ሳይሆኑ መንግስትም፣ ከአለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ሀብት ያሰባስባል። ስለዚህ ከአለም አቀፍ ድርጅቶች ወይም አጋር ሀገራት፤ ሀብት እና ገንዘብ ማሰባሰብ በራሱ የተቋምን ነጻነት የሚቃረን ነገር አይደለም” ሲሉ ዋና ኮሚሽነሩ አክለዋል። 🔴ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13517/
Posted in Amharic News, Ethiopian News

‘የጎንደር ዩንቨርስቲ’ን የማፍረስ እና ልምድ ያላቸውን መምህራንን እና ዶክተሮች ወደ ጅማ የማዘዋወር የነ ዐቢይ አሕመድ ድብቅ ፕሮጀክት

አማራን ተቋም አልባ የማስቀረት ግዙፍ ሴሪዎች በነ ዐቢይ አሕመድ… በሕክምና ትምህርት ዘርፍ ከ65 ዓመት በላይ ልምድ ያለው ‘የጎንደር ዩንቨርስቲ’ን የማፍረስ እና ልምድ ያላቸውን መምህራንን እና ዶክተሮች ወደ ጅማ የማዘዋወር የነ ዐቢይ አሕመድ ድብቅ ፕሮጀክት በሰፊው እየተሰራበት ነው። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የተመሰረተና በህክምናው ዘርፍ ከአዲስ አበባው (ጥቁር አንበሳ) ዩኒቨርሲቲ በመቀጠል በምስራቅ አፍሪካ ደረጃ አንጋፋው የህክምና ተቋም ነው። በህክምናው ዘርፍ ብቻ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ባለሙያዎችንም አፍርቷል። ይህን አንጋፋ የአፍሪካ ሀብት የሆነ ተቋም በግብዓትና በሰው ኃይል ለማፍረስ ጅማ ዩኒቨርሲቲን ለማንገሥ በጥናት ላይ የተመሠረተ ሴራ እየተሰራበት ነው። (መረጃው ከጎንደር ዩንቨርስቲ ሰዎች የተላከልን ነው) በኦሕዴድ በኩል፦ “ጅማን የ ሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል እናደርጋለን” በሚል የጎንደር ዩንቨርስቲን ማፍረስ እንደ ግብ ማስፈፀሚያ መሳሪያ ሆኗል። ይህ አማራን የተቋማት መዃን የማድረግ የኦህዴድ ፕሮጀክት፣ ከጥልቅ ጥላቻ እና አማራ ጠልነት የሚመነጭ ነው። የጎንደር ዩንቨርስቲ በወልቃይት ጉዳይ በሰራቸው ወገን ተኮር (አማራዊ) ተግባራት በሁለቱም ኃይሎች ማለትም በወያኔም፣ በኦሕዴድም ጥርስ ውስጥ የገባ ተቋም ነው። ለዚህ አንጋፋ የትምህርት ተቋም ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ምንም ዓይነት አዳዲስ የሕክምና ግብዓት አልተሰጠውም፤ ተቋሙም በበጀት እየታሸ ይገኛል። በአንፃሩ ጅማ ዩንቨርስቲ ራሱን እንዲያደራጅ የማድረግ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ኢንቨስት እየተደረገበት ነው። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሚሰሩ ከፍተኛ ልምድና ዕውቀት ያላቸው የሕክምና ሳይንስ መምህራንና ተመራማሪዎችን በከፍተኛ ጥቅማ ጥቅም በማማለል እንዲፈልሱ የማድረግ ሥራው በትልቅ በጀት እየተሰራበት ነው። በአንፃሩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በግብዓትና
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አማራ ክልል በሰላም ወተው ኦሮሚያ ክልል ገብረጉራቻ ላይ የታገቱት 2 አውቶብስ ሙሉ የደባርቅ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች 400 ሺ ብር በአንድ ታጋች ተጠየቀባቸው።

“ የ2 አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል ” – ከእገታ ያመለጠ ተማሪ “ ‘ ከአሁን ወዲህ ስልኬ አይሰራም ፤ ታግተናል ’ አለችኝና ከዛ ስልኳ አይሰራም ” – የአንዷ ታጋች ተማሪ እህት “ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እየጠየቁ ነው ” – የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት ሰኞ እለት ተሳፍረው ወደ ቤተሰብ እየተጓዙ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዓመት ያሉ ተማሪዎች በታጣቂዎች መታገታቸውን የዓይን እማኝ፣ የታጋች ቤተሰብና ዩኒቨርሲቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ። አንድ ከእገታው አመለጥኩ ያለ ተማሪ ፥ ሶስት (3) አውቶብሶች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እየተጓዙባቸው የነበሩ ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ የሚባል ቦታ ሲደርሱ መታገታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል። ከ3 አውቶብሶች 2ቱን ታጣቂዎች እንዳስቆሟቸው፣ ተሳፋሪዎቹን ካስወረዷቸው በኋላ አግተው ወደ ጫካ እንዳስገቧቸው፣ እርሱ ገለባ ውስጥ ተደብቆ እንዳመለጠ ገልጾ፣ “ የሁለቱ አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል ” ብሏል። ከታጋቾቹ መካከል የሚያውቃቸው የIT ፣ የአኒሚል ሳይንስ ዲፓርትመንት ተማሪዎች እንዳሉ ገልጾ፣ ያገቷቸው “የሸኔ ታጣቂዎች” መሆናቸውን አስረድቷል። አንዷ የታጋች እህት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል፣ “ ረቡዕ 3 ሰዓት ከ28 ደቂቃ ደወለችልኝ (እየሮጡ ነበር፣ የተኩስ ድምጽም ነበር) ‘በቃ ከአሁን ወዲህ ስልኬ አይሰራም። ላታገኝኝ ትችያለሽ በታጣቂዎች ታግተናል’ አለችኝ። መለሽ ስደውል ስልኳ አይሰራም ” ብላለች። ቤተሰቡ ሁሉ በጣም ከፍተኛ ጭንቀት ላይ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ታጋቾቹን በህይወት እንዲያተርፏቸው ተማጽናለች። በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ፤ የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የዐቢይ አሕመድ የፓርላማ ቅጥፈቶች…

የዐቢይ አሕመድ የፓርላማ ቅጥፈቶች… (ከኢትዮ 251 ሚዲያ ዝግጅት ክፍል) *** የዐቢይ አሕመድ የዛሬ የፓርላማ ቅጥፈቶችን በአራት ጉዳዮች ማለትም በፖለቲካ፣ በፀጥታ/በጦርነት፣ በኢኮኖሚና በዲፕሎማሲ ጉዳዮች ከፋፍለን እንመለከተዋለን፡፡ በዚህኛው ጥፍል ፖለቲካውንና ጦርነቱን እንመለከተዋለን። አብራችሁን ቆዩ🙏 ⏺ፖለቲካ ፡- በኢትዮጵያ አሁናዊ ሁኔታ ፖለቲካና በአማራ ላይ የተከፈተውን የዘር ማጥፋት ዓላማ ያለውን ጦርነት ለያይተን ማየት አንችልም፡፡ አሁን በተጨባጭ ያለው የፖለቲካ አየር የኦሮሙማ ማኒፌስቶ የሚተገበርበት በመሆኑ ስለፖለቲካ ስናወራ አሁን በአማራ ላይ ስለተከፈተው የዘር ማጥፋት ጦርነት እያወራን ነው፤ ስለጦርነት ስናወራም ስለፖለቲካ እያወራን ነው፡፡ ምክንያቱም፦ የዘመናዊው ስትራቴጂ ጥናት ምሁራን እንደሚያስረዱት፦ ‹ጦርነት ለየት ባለመልክ የሚካሄድ የፖለቲካ ዓላማ ወይም የፖለቲካ ፖሊሲ ተቀጥላ ነው› ነው፡፡ በዚህ ብያኔ መሰረት ዐቢይ አሕመድ የኦሮሙማ ፖለቲካ ዓላማውን ለማሳካት በአማራ ሕዝብ ላይ የከፈተው የዘር ማጥፋት ዓላማ ያለው ጦርነትን ነው፡፡ እናም ዐቢይ አሕመድ በዛሬው የፓርላማ ውሎ የአያቶቻችን ጦርነት፤ አባቶቻችን ተዋጉት፤ የአባቶቻችንን ጦርነት ደግሞ እኛ እየተዋጋን ነው በማለት፤ አሁን ያለውን ጦርነት ሕዝባዊ መሰረት ያለው እሱም ከአያት ቅድመ አያቶቹ የወረሰው እንደሆነ በግልጥ ተናግሯል፡፡ ይህ ብዙ የሚያስብል ጉዳይ ነው፡፡ በአንድ በኩል የሰራዊት ቋቱ ስላለቀ ጦርነቱን የአሮሞ ሕዝብ ደግፎት እንዲቆም ለማድረግ ሆነ ብሎ ያመጣው ሀሳብ ነው፤ በሌላ በኩል የታሪክ ቁርሾ አለብን እና እሱን እናወራርድ የሚል አንድምታ ያለው መልዕክት ለማስተላፍ ሲጋጋጥ ውሏል፡፡ (“የምክክር ኮሚሽን” ካልተቀበላችሁ ከአያቶቻችን የወረስነውን ጦርነት እንደአባቶቻችን እናስቀጥለዋለን ነው የፋሽስቱ አባባል) እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ነገር፦ ጦርነት ተራ የፖለቲካ ተግባራዊ እንቅስቃሴ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አደገኛ ኑሮ ውድነት የሚያስከትለውን፤ አብይ አሕመድ በዚህ አመት መጨረሻ ብርን ለማዳከም ለአይ ኤም ኤፍ ቃል መግባቱ ተሰምቷል።

አደገኛ ኑሮ ውድነት የሚያስከትለውን፤ አብይ አሕመድ በዚህ አመት መጨረሻ ብርን ለማዳከም ለአይ ኤም ኤፍ ቃል መግባቱ ተሰምቷል።  በዓመቱ 2024 መጨረሻ ብር እንዲዳከም ኢትዮጵያ ልትፈቅድ ትችላለች የሚል ዘገባ ይፋ ተደርጓል። የዴቪድ ዋይትሃውስ የአፍሪካ ሪፖርት ዘገባ እንገለጸው የተዳከመ ብርን የአብይ አስተዳደር እንደሚቀበል ከ IMF ጋር በዓመቱ መጨረሻ ላይ ስምምነት ላይ ለመድረስ መዘጋጀቱ ታውቋል። Ethiopia may allow birr to weaken to secure IMF board agreement by year end . The government’s acceptance of a weakening birr could lead to an agreement with the IMF by the end of the year. Report by David Whitehouse ባለሥልጣናቱ የአጭር ጊዜ የዋጋ ግሽበትን ከደካማ ምንዛሪ መውጣት እንደሚችሉ እርግጠኞች ናቸው ሲሉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይናገራሉ። የኢትዮጵያ ፖሊሲ አውጪዎች የብርን ቀስ በቀስ የመዳከም አስፈላጊነትን መቀበል በዚህ ዓመት መጨረሻ ወደ አይኤምኤፍ ሰራተኞች እና የቦርድ ደረጃ ስምምነቶችን ሊያመጣ ይችላል ፣ ኬኛን እና ኢትዮጵያን የጎበኙት በጄ.ኤስ. ዋና አማካሪ ኮኖር ቫሴ እንደገለፁት  ……..  https://www.theafricareport.com/353810/ethiopia-may-allow-birr-to-weaken-to-secure-imf-board-agreement-by-year-end/
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

አጭር የፅሁፍ መልእክት = “አርፈህ ብትቀመጥ ይሻላል! ምንም አታመጣም!” = ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ ለአትሌት ሀይሌ ገ/ስላሴ

ጀግናው አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገ/ስላሴ የዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስን ህገወጥ አካሄድ በማጋለጥ ላይ ይገኛል። ባለፈው ቅዳሜ በሀትሪክ ጋዜጣ ጠንካራ ሃሳብ ለሰነዘረው ሀይሌ በስልኩ የደረሰው አጭር የፅሁፍ መልእክት “አርፈህ ብትቀመጥ ይሻላል! ምንም አታመጣም!” የሚል ሲሆን ቴክስት የላኩት ደግሞ አሸብር ናቸው። ሀይሌ መልስ እንዳልሰጠ ታውቋል። አሸብር ግን ህግ የሚገዛው መቼ ነው!? በስፖርቱ የሰላም አየር የሚተነፍሰውና አሸብር ከቦታው ገለል የሚለው መቼ ይሆን!? የሌሎቹ ታዋቂ አትሌቶች ማድፈጥና ዝምታን መምረጥ ሚስጥሩ ምንድነው!? – የኢቲቪ ስራ አስኪያጅ በኤዲቶሪያል ስብሰባ ላይ “ስለአሸብር ምንም ነገር ማውራት አይቻልም” ሲሉ ለጋዜጠኞች ቀጭን የማስጠንቀቂያ ትእዛዝ ሰጥተዋል። ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ እና የማንሸራሸር ህገመንግስታዊ ድንጋጌና መብት ላይ የግላቸውን ሚስማር ቸክለዋል! ለምንና እንዴት ስለአሸብር ጥብቅና ቆሙ!? የሚለውን ሃላፊው ብቻ ናቸው የሚያውቁት! እጀ ረጅሙ ሽብሩ በመኪናው፣ በስልኩና በፅፈት ቤቱ፣ በመኖሪያ ቤቱ ስውር ካሜራ እንደሚጠቀም ስንቶች ታውቁ ይሆን!? ጉቦ ሲሸጉጥ የሚሸጎጥላቸውን ግለሰቦች ሳያውቁ ይቀርፃቸዋል። ባለስልጣን ዘንድ ለልጅ ልደት ጎራ ሲል ስጦታ ይዞ ሄዶ ተመሳሳይ ቀረፃ ይጠቀማል። አንድ ቀን ውልፍት ካሉ የያዘውን ይመዝባቸዋል! ( ጋዜጠኛ አርአያ ተስፋማርያም )  
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በአዳማ/ናዝሬት ተቃውሞ የወጡ ሰልፈኞች ውስጥ 7 ሰወች በአብይ ኃይሎች ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ከተማ ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 26/2016 ዓ.ም አሮሬቲ እና ቶርበን ኦቦ ቀበሌዎች በነዋሪዎች ከተቀሰቀሰ ተቃውሞ ጋር ተያይዞ ከመንግሥት ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት፣ የ 7 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ዋዜማ ሰምታለች። ተቃውሞው በነዋሪዎቹ የተቀሰቀሰው የከተማ አሥተዳደሩ በቀበሌዎቹ የሚገኙ 1 ሺህ 500 ደገማ ቤቶችን ሕገ ወጥ ብሎ የማፍረስ ሥራ ሲጀምር መሆኑን ዋዜማ ከአካባቢው ነዋሪዎች አረጋግጣለች። ነዋሪዎቹ መሬቱን በአካባቢው ካሉ አርሶ አደሮች የገዙ መሆናቸውና ከ 2005 ዓ.ም አንስቶ እስከ አሁን ድረስ ላለፉት 11 ዓመታት በሕጋዊ መንገድ ለአዳማ ከተማ መሥተዳድር ግብር ሲገብሩበት መቆየታቸውን ለዋዜማ ተናግረዋል። ሆኖም ቀደም ብሎ ይፈርሳሉ የተባሉትን ቤቶች እየዞሩ ቀለም ሲቀቡ መቆየታቸውንና ዛሬ ጠዋት ላይ ዶዘርና ሌሎች ማፍረሻ ማሽኖችን ይዘው ወደ ስፍራው መምጣታቸውን ተከትሎ አመጹ መቀስቀሱን አናግረዋል። በዚህም ሳቢያ የሰባት ሰዎች ሕይወት ወዲያው ማለፉን፣ ቀጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸውንና ከሟቾች መካከልም አንዲት ነፍሰጡር ሴት እንደምትገኝበት ገልጸዋል። ነዋሪዎቹ ባለፉት ጊዜያት ለጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት ጭምር ቤቶቹ እንዳይፈርሱባቸው ግብር የከፈሉበትን ሕጋዊ ደረሰኝ በማቅረብ መጠየቃቸውንና ጽ/ቤቱም ቤቱ እንዳይፈርስና ጉዳያቸው በይደር እንዲታይ ወስኖ እንደነበር ዋዜማ ተረድታለች። ይህ ዘገባ እየተጠናቀረ እስካለበት ሰዓት ድረስ ተቃውሞው መቀጠሉንና ድባቡም አስፈሪ መሆኑን ዋዜማ የሰማች ሲሆን፣ በጉዳዩ ላይ የፌዴራል ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ እና የኦሮሚያ ሚሊሻ ተሳታፊዎች መሆናቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ዋዜማ በጉዳዩ ላይ የከተማ አሥተዳደሩን ለማነጋገር በተደጋጋሚ ያደረገችው ጥረት ባለመሳካቱ ህሳባቸውን ማካተት አልተቻለም። [ዋዜማ]
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በሲጋራ ወረቀት ላይ መፅሐፍ የተረጎመው ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ከዚህ አለም በሞት ተለየ

ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ከዚህ አለም በሞት ተለየ የአዲስ አድማስ ዝግጅት ክፍል፣ የጋዜጣው መሥራችና ዋና አዘጋጅ የነበረው ገጣሚና ደራሲ  ነቢይ መኮንን ህይወቱ ማለፉን ሸገር ሬዲዮ ከልጁ ራዕይ ነብይ አረጋግጧል። ነቢይ ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ፤ ድንገት ያረፈው ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ረፋዱ ላይ ነው። ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ የሆነውና በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት የሚጠቀሰው ነቢይ ብርቱ ተርጓሚ፣ ገጣሚ ወግ አዋቂ የጥበብ ሰው እንደሆነ ይነገራል። ነቢይ በደርግ ዘመን በእስር ላይ እያለ Gone with the wind የተሰኘውን የማርጋሬት ሚቼል መፅሀፍ  በሲጋራ ወረቀት ላይ ወደ አማርኛ በመተርጎም ይታወቃል። ነቢይ የፃፋቸው ግጥሞች ወደ እንግሊዝኛ እና ፈረንሳይኛ የተተረጎሙ ሲሆን በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በተከታታይ ይፅፋቸው በነበሩ የኛ ሰው በአሜሪካ የተሰኘው የጉዞ ማስታወሻ ተወዳጅነትን አትርፏል። ነብይ ህይወቱ ያለፈው በተወለደ በ68 ዓመቱ ሲሆን የሶስት ሴት ልጆች አባት ነበር። የቀብር ስርዓት ባለቤቱ እና ልጁ ከውጭ ሀገር ከመጡ ብኋላ እንደሚፈፀምም ነው የተገለፀው። መረጃ ሚዲያ በገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ህልፈት የተሰማውን ሀዘን ይገልጻል።
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News, Poem, Sem ena Worq

በጀኔራል ተፈራ ጉዳይ “የፀጥታና ደህንነት ግብረኃይሉ” ግምገማ ምን ይላል? (ጥብቅ ሚስጢር)

በጀኔራል ተፈራ ጉዳይ “የፀጥታና ደህንነት ግብረኃይሉ” ግምገማ ምን ይላል? (ጥብቅ ሚስጢር) ጀኔራል ተፈራ ማሞ ይፋዊ በሆነ መልኩ የአማራ ፋኖን ትግል መቀላቀሉ በብልጽግና አገዛዝ ዘንድ ከፍተኛ መረበሽ ፈጥሯል። በተለይም “የፖለቲካ እንጂ የወታደር ታማኝ የለውም” የሚባለው ብአዴን በስሩ ያለው ቅልብ ሰራዊቱ ተበትኖ እንዳያልቅ በነ ዐቢይ አሕመድ ዘንድ ስጋት ፈጥሯል። የጨረቃ ካቢኔ ስብስቧን ብአዴንም በጀኔራሉ ውሳኔ ጨንቋታል። በአገዛዙ ዘንድ “የሥርዓቱ አደጋ” ሊሆኑ የሚችሉ ክስተቶች ሲያጋጥሙ ከመደበኛ ስብሰባዎች ውጭ በአስቸኳይ ጉዳዮን ላይ “የፀጥታና ደህንነት ግብረ-ኃይል” የሚባለው የዐቢይ አሕመድ የግል ኮሚቴ፣ የመሰብሰብ ልምድ አለው። ስብሰባውን የሚጠራው ዐቢይ አሕመድ ሲሆን፤ የፀጥታና ደህንነት ግብረ ኃይሉ ከመከላከያ፣ ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከብሔራዊ ደህንነት፣ ከኢንሳ፣ ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ከውጭ ጉዳይና ከፋይናንስ ሚኒስትር በመሪ ደረጃ የኮሚቴው አባል ናቸው። ነገር ግን ዛሬ ረፋድ ላይ የነበረው የፀጥታና ደህንነት ግብረኃይሉ አስቸኳይ ስብሰባ ከመከላከያ፣ ፌዴራል ፖሊስ፣ ብሔራዊ ደህንነትና ከኢንሳ የተውጣጡ አካላት የተገኙበት እንደነበር፣ ከነዚህ ተቋማት ለኦፕሬሽናልና ክትትል ቡድን መሪዎችም እንዲገኙበት የተደረገ አስቸኳይ ስብሰባ መሆኑን ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰው የውስጥ መረጃ ያመለክታል። ዐቢይ አሕመድ በከፍተኛ ጭንቀትና ብስጭት በባለሙያዎች ፊት ሬድዋን ሁሴንንና ጌታቸው ጉዲና የሚመራውን የመከላከያ መረጃ መምሪያ ወቅሷል፤ በሰዎች ፊት አዋርዷቸዋል። “ከእጃችሁ እንዳይወጣ ደጋግሜ ተናግሬ ነበር” በሚል ብስጭት ለአክቲቭ ሰርቬላንስ (በሰው ኃይል የሚደረግ አካላዊ ክትትል) ቡድን መሪዎች ሳይቀር በሥም እየጠራ ዘልፏል። “ሰብሳቢ አጥቶ ተበትኖ የነበረውን ፅንፈኛ በናንተ ድክመት አባት አቀበላችሁት። ተፈራ ቀጣይ ምን እንደሚሰራ ታውቃላችሁ…? ሊወጋን ብቻ አይደለም
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአብይ አሕመድ የጸጥታ ሃይሎች በአማራ ክልል በህክምና ባለሙያዎች፣ ህሙማን እና የጤና ተቋማት ላይ የጦር ወንጀሎችን ፈፅመዋል

Abiy Ahmed security forces have committed widespread attacks amounting to war crimes against medical professionals, patients, and health facilities in the Amhara region. Human Rights Watch …………… የአብይ አሕመድ የጸጥታ ሃይሎች በሀገሪቱ ሰሜናዊ ምዕራብ የአማራ ክልል በህክምና ባለሙያዎች፣ ህሙማን እና የጤና ተቋማት ላይ የጦር ወንጀሎችን ያደረሱ ጥቃቶች መፈጸማቸውን ሂውማን ራይትስ ዎች ዛሬ ባወጣው ዘገባ አመልክቷል። “ወታደሩ ከሞተ በአንተ ላይ ነው” የሚለው ባለ 66 ገጽ ዘገባ በኢትዮጵያ የአማራ ግጭት በሕክምና ላይ የተፈፀመው ጥቃት የኢትዮጵያ ፌዴራል ኃይሎችና ከመንግሥት ጋር የተገናኘ ሚሊሻ በሕክምና ባለሙያዎች፣በጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማትና በማጓጓዣዎች ላይ ጥቃት እንደፈጸሙ ያሳያል። https://minilik-salsawi.blogspot.com/2024/07/ethiopia-army-attacks-health-care-in.html .
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአብይ አሕመድ እና አዳነች አቤቤ የተጀመረው የኮሪደር ልማት 33 ቢሊዮን ብር ሪፖርት ሲጋለጥ

33 ቢሊየን ብር ➖➖➖➖➖ አዎ 33 ቢሊየን ብር ምን ላይ እንደዋለ ታውቃለህ..? ለሰሞኑ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት! 33 ቢሊየን ብዙ ነገር ነው። ብዙ ሃብት ነው። ለአንዲት መናጢ ድሃ ሀገር ደግሞ እጅግ በ ጣ ም….ብዙ ነው። እስኪ ግዝፈቱን በሌላ መልኩ ላስረዳህ… ◾️የንግድ ባንክ አዲሱ ሰማይ ጠቀስ ህንፃ በስንት እንደተሰራ ታውቃለህ…? 8 ቢሊየን ብር ◾️ሰሞኑን የተመረቀው ግዙፉ የዓባይ ድልድይ በጀት 4.1 ቢሊየን ብር ነው ◾️የሞጆ ሀዋሳ 92 ኪሜ ፈጣን መንገድ በጀቱ 6.3 ቢሊየን ብር ነው ◾️ለሸገር ቀለበት መንገድ የመጀመሪያ ምዕራፍ የተያዘው በጀት 4.5 ቢሊየን ብር ነው ➖በክልል በጀት ደግሞ እንይ: 33 ቢሊየን ብር ማለት ለ 2016 የትግራይ ክልል ም/ቤት ካፀደቀው በጀት በሁለት እጥፍ ይበልጣል። ከ2016 የአፋር ክልል በጀት ደግሞ በሶስት እጥፍ ይበልጣል። ◾️ለ2017 ዓ.ም የፌዴራል መንግስት ለክልሎች ከያዘው የድጋፍ በጀት ውስጥ ከ33 ቢሊየን ብር በላይ የተመደበላቸው ለኦሮሚያ እና ለአማራ ክልል ብቻ ነው ◾️ለሌሎች የሚሰጠው ከ33 ቢሊየን በታች ነው ◾️ በሌላ መልኩ 33 ቢሊየን ብር ማለት 1870 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የሚችለው ግልገል ጊቤ ሦስት ግድብ ማለት ነው። ➖➖ እናም 33 ቢሊየን ብር ማለት ብዙ ፋብሪካ፣ የአዳማ-አአ አይነት ፈጣን መንገድ፣ የግልገል ጊቤ 3 አይነት የኃይል ማመንጫ ግድብ፣ ብዙ ሺህ ኮንዶሚኒየም፣ 4 የንግድ ባንክ ትልቁ ህንፃ፣ ብዙ ሺህ የስራ ዕድል… ነበር ባይሰበር – ኮሪደሩ ባይደረደር
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር ተፈቱ።

መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር ተፈቱ። የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ  መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር መለቀቃቸውን የማሕበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል። ዋና ሥራ አስኪያጁ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ለእስር የተዳረጉት። ከሁለት ወራት በኋላ ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016  ዓ.ም  ከእስር  መለቀቃቸውን  ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ተችሏል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ውይይት ያለ ውጤት ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ውይይት ያለ ውጤት ተጠናቀቀ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታዬ አጽቀስላሴ እና የሶማሊያ አቻቸው አህመድ ሙዓሊም ፊቂ በቱርክ አንካራ ያደረጉት ውይይት ያለ ውጤት ተጠናቀቀ። ሁለቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በመጪው ነሐሴ መጨረሻ ዳግም ለመገናኘት መስማማታቸውን አስታውቀዋል።ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር በተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት ምክንያት ከሀገሪቱ ጋር ውዝግብ ውስጥ የገባችው ሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯን ወደ አንካራ የላከችው፤ በቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሐካን ፊዳን ግብዣ ነበር። የውይይት ግብዣውን የተቀበሉት ሁለቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፤ በአንካራው ውይይት ፊት ለፊት ተገናኝተው እንዳልተነጋገሩ በቱርክ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኩል የወጣው መግለጫ ይጠቁማል።ሚኒስትሮቹ ትላንት ሰኞ ሰኔ 24 ቀን 2016 በቱርክ አመቻቺነት ባደረጉት ውይይት፤ ልዩነቶቻቸውን በሁለቱም ተቀባይነት ባለው ማዕቀፍ ለመፍታት “ቅን፣ ልባዊ እና ወደፊት የሚመለከት” የሃሳብ ልውውጥ ማድረጋቸውን መግለጫው አመልክቷል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 25፤ 2016 ባወጣው አጭር መግለጫ፤ በውይይቱ “ግልጽ እና ወዳጅነት የተሞላበት የሃሳብ ልውውጥ” እንደተደረገ አረጋግጧል። የአንካራው ውይይት “በሁለቱ አገራት መካከል ላሉ አለመግባባቶች መፍትሔ በሚያመጡ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ” እንደነበርም ሚኒስቴሩ በመግለጫው ጠቅሷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጀነራል ተፈራ ማሞ በይፋ የህልውና ትግሉን ተቀላቀሉ !

ጀነራል ተፈራ ማሞ በይፋ የህልውና ትግሉን ተቀላቀሉ ! ጄኔራል ተፈራ ማሞ የአማራ ፋኖ እያደረገ ያለውን የህልውና ትግል በይፋ ተቀላቀሉ። ጄኔራሉ ከሰው በላው አፈና ለጥቂት ማምለጣቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ዛሬም ጄኔራል ተፈራ ማሞ የአማራ ህዝብ የህልውና ትግልን በይፋ መቀላቀላቸውን ከፋኖ አመራሮች አረጋግጠናል።በአዲስ አበባ ከተማ ከቤተክርስቲያን መልስ በእግር ጉዞ ላይ እንዳሉ በ”ኮሬ ነጌኛ” ገዳይ ቡድን የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው የነበረው ጀኔራል ተፈራ ማሞ፣ ከግድያ ሙከራው ወታደራዊ ጥበባቸውን ተጠቅመው በማምለጥ አሁን ላይ በይፋ የአማራ ፋኖን ትግል መቀላቀላቸውን ኢትዮ 251 ሚዲያ ከፋኖ አመራሮች አረጋግጣለች፡፡ የጄኔራል ተፈራ ማሞ ይፋዊ በሆነ መንገድ የአማራ ፋኖን ትግል መቀላቀል የሕልውና ትግሉን በሞራል፣ በወታደራዊ አመራርና በሕዝባዊነቱ ላይ ከፍ ያለ መነቃቃት እንደፈሚፈጥር ይጠበቃል፡፡ ጀኔራል ተፈራ ማሞ ገና ከአፍላ ዕድሜቸው ጀምሮ፣ ከ40 ዓመት በላይ የወታራዊ አመራር ልምድ ባለቤትና የሸማቂ ኮማንዶ መሪ በመሆን ወርቃማ የትግል ሕይወት ያሳለፉ ግንባር ቀደሙ ከፍተኛ መኮንን ናቸው፡፡ ከጀኔራል አሳምነው ጽጌና ሌሎች የትግል ጓዶቻቸው ጋር በመሆን የአማራ ልዩ ኃይልን በማደራጀትና የተዋጊነት አቅሙን በማሳደግ በአማራ ሕዝብ ትግል ውስጥ ልዩ ታሪክ መስራታቸው ይታወቃል፡፡ ጀኔራሉ፦ በኮማንዶ ሥልጠና፣ ኢንዶክትሪኔሽን፣ የአደረጃጀት፣ ወታደራዊ ስምሪት፣ ሎጀስቲክስ፣… ቅኝት፣ ተልዕኮ፣ ግዳጅ አፈጻጸም፣ ወታደራዊ ግምገማ፣ መልሶ ማደራጀት፣ የሽምቅ ውጊያ፣ የግንባር ፍልሚያ፣ የአንገት ቦታ ቁጥጥር፣ ገዥ መሬትን ቀድሞ መያዝ፣ ምሽግ ሰበራ፣ … የተካኑቸው ወታደራዊ ጥበባቸው እንደሆኑ በቅርብ ጓዶቻቸው የተመሰከረላቸው ናቸው።ጀኔራል ተፈራ ማሞ በይፋ የአማራ ፋኖን ትግል መቀላቀል ተከትሎ የመጀመሪያው ጀኔራል ያደርጋቸዋል፡፡  
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ቱርክ፣ ኢትዮጵያንና ሱማሊያን ማደራደር ጀመረች

ቱርክ፣ ኢትዮጵያንና ሱማሊያን በባሕር በር ውዝግባቸው ዙሪያ ዛሬ አንካራ ውስጥ እንዳደራደረች ከባለሥልጣናት ምንጮች መስማቱን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል። ኾኖም ኹለት ለድርድሩ ቅርብ የኾኑ ምንጮች የድርድሩ ግብ ምን እንደኾነ ግልጽ እንዳልኾነና ከድርድሩ ኹነኛ ውጤት የመገኘቱ እድሉ ዝቅተኛ መኾኑን መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። የኢትዮጵያ፣ ሱማሊያና ቱርክ ባለሥልጣናት በቱርክ-መራሹ ድርድር ዙሪያ አስተያየት ከመስጠት እንደተቆጠቡ ዜና ምንጩ ገልጧል። የሶማሊላንድ ራስ ገዝ መንግሥት ቃል አቀባይ ግን፣ ሶማሊላንድ በቱርክ አደራዳሪነት በሚካሄደው ድርድር ውስጥ ተሳታፊ እንዳልኾነች ተናግረዋል ተብሏል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ከሱማሊያ ጋር በቱርክ አመቻቺነት ዛሬ ይደረጋል ስለተባለው ንግግር ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ያለው ነገር የለም።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአማራ ታሪካዊ ርስቶችን አሳልፈው የሰጡ ዋና ባንዳዎች እና የጠለምት አሁናዊ ሁኔታዎች…

የአማራ ታሪካዊ ርስቶችን አሳልፈው የሰጡ ዋና ባንዳዎች እና የጠለምት አሁናዊ ሁኔታዎች… *** የአማራ ሕዝብ የምንግዜም የጥቃት ምንጭ የሆነው ብአዴን የአማራ ሕዝብ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለባቸውን፣ በደምና በአጥንቱ ነጻ ያወጣቸውን ታሪካዊ ርስቶቹን ዳግም አሳልፎ ለጠላት ወያኔ ማስረከቡን ቀጥሏል። የዐቢይ አሕመድ የትሮይ ፈረስ የሆነው ተመስገን ጥሩነህ፤ ምስለኔው አረጋ ከበደ፤ አድርባዩ አብዱ ሁሴን፤ ካድሪው ይርጋ ሲሳይ የአማራ ታሪካዊ ርስቶችን ዳግም በመሸጥ ዋናዎቹ ባንዳዎች ናቸው። አብዱ ሁሴን የተባለው ሰው የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሆኖ፣ ዋና ስራው የአማራ ሕዝብ ማንነትና ወሰን ጥያቄ ይዞ ታግሎ ነፃ ያወጣቸውን ራያ፣ ኮረም፣ አበርገሌ፣ ጠለምት፣ ወልቃይት ጠገዴን ለጠላት አንድ በአንድ አሳልፎ የሚሰጠውን ዐቢይ ኮሚቴ መምራት ነው፤ ሪፖርት የሚያቀርበውም ለተመስገን ጥሩነህ ነው። ተመስገን ለዐቢይ እንዲህ ባለ የባንዳነት ቅብብል የአማራ ታሪካዊ ርስቶች አንድ ባንድ ለጠላት ተላልፈው እየተሰጡ ነው። የዐማራ ሕዝብ ታሪካዊ ርስቶችን በድጋሚ ከሸጡት ዋናዎቹ ባንዳዎች እነዚህ ሰዎች ከፊት መስመር ይጠቀሳሉ። ሚያዚያ 5/2016 ራያ እና ኮረምን ሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጠለምትን ዳግም ለጠላት አሳልፈው ሰጥተዋል። ከትላንት ምሽት ጀምሮ ከሦስቱ የጠለምት ከተሞች በአስር ሺዎች የሚቆጠር ሕዝብ ተፈናቅሎ አዳርቃይ ከተማ ገብቷል። ዛሬም በርካታ ተፈናቃይ እየገባ ነው። ምክንያቱም ሜካናይዝድ የሆነው አርሚ 42 እና አርሚ 11 በርካታ ኃይላቸውን ይዘው ወደአማራ ታሪካዊ ግዛት ጠለምት እንዲገቡ በአረጋ ከበደ የልዑካን ቡድን መሪነት፤ በብልጽግና ሰራዊት አጃቢነት ወደ ጠለምት ገብተው ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ እንዲያቋቁሙ ስለተስማሙ በዚህ ስጋት የገባው ሕዝብ ከሦስቱም የጠለምት ወረዳዎች ተፈናቅሎ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

“ዶክተር አሸብር ሙያን ለሙያተኛ ትተው ከስፖርቱ ዞር ይበሉ! ” ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ

“ዶክተር አሸብር ሙያን ለሙያተኛ ትተው ከስፖርቱ ዞር ይበሉ! ” ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ጀግናው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ከሃትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ለኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ከስፖርቱ ገለል እንዲሉ መክሯል ። ኃይሌ ፣ “እኔ ዶክተር ልሁን ብል ሠው ይስቅብኛል፤ የተከበሩ ዶክተር አሸብር ስፖርቱንና የኢትዮጵያን ህዝብ የሚወዱ ከሆነ ሙያን ለሙያተኛ ትተው ከስፖርቱ ዞር እንዲሉ እመክራለሁ” ሲል ምክር አዘል መልእክት አስተላልፏል ።
Posted in Ethiopian News

ከህግ አግባብ ውጪ የመምህራን ደመወዝ እየተቆረጠ ነው !

” ለልማት በሚል ከደመወዛችን እየተቆረጠብን ነው ” – መምህራን ” እውነት ነው። ከህግ አግባብ ውጪ የመምህራን ደመወዝ እየተቆረጠ ነው ” – የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር የደመወዝ በወቅቱ አመከፈል፣ የጥቅማጥቅም ክፍያ አለማግኘት ችግር ባልተቀረፈበት ሁኔታ፣ ያለፈቃዳቸው ከደመወዝ ለልማት በሚል እየተቆረጠባቸው መሆኑን መምህራን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረሩ። መምህራኑ በሰጡት ቃል፣ ” ለልማት በሚል እስከ 50 በመቶ ከደመወዛችን እየተቆረጠብን ነው። የወር አስቤዛን በቅጡ ከማይሸፍን ደመወዝ ላይ እየተቆረጠ እንዴት ቤተሰብ እናስተዳድር ? ” ሲሉ ጠይቀዋል። ይህ የመንግስት ድርጊት ሰንበትበት እንዳለ ገልጸው፣ ጭራሽ ቤተሰብ ማስተዳደር አቅቷቸው በብድር እየማቀቁ በመሆኑ ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል። መምህራኑ ያቀረቡት ቅሬታ እውነት ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበለት የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር፣ ” እውነት ነው ችንሩን በደንብ ነው የምናውቀው ”  ብሏል። የማኀበሩ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ሽመልስ አበበ በሰጡት ቃል፣ ” በየክልሉ የተለያየ የመልካም አስተዳደር ችግር አለ። ያለመምህራን ፈቃድ የደመወዝ  ቆረጣም በጣም ትክክል ያልሆነ፣ ጉልበተኝነት የበዛበት፣ ሰሚ ያጣ ነው ” ብለዋል። ታዲያ ለቅሬታው ማኀበሩ ምን እየሰራ ነው ? ለሚለው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ” ትክክል አይደለም ብለን እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አድርሰናል። ባለፈው ነሐሴ ወር በነበረን ውይይት ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። አሁንም በተለይ ዳውሮ ዞን የሚገኙ መምህራን እንደሚያለቅሱ፣ ማኀበሩም ለትምህርት ሚኒስቴር እንዳሳወቀ፣ ትምህርት ሚኒስቴርም ያለፈቃዳቸው ደመወዝ እንዳይቆረጥ ለክልሉ ትምህርት ቢሮ ደብዳቤ እንደጻፈ፣ ክልሉም ደመወዛቸው እንዳይቆረጥ ለሚመለከተው አካል እንዳሳወቀ አስረድተዋል። ” ዞኑ ላይ ‘ለማዕከል ግንባታ’
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አማራ ክልል የአብይ አሕመድ ወታደሮች ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ንፁሃንን ገለዋል

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች በቀናት ልዩነት “የአብይ አሕመድ ወታደሮች ቤት ለቤትና መንገድ ላይ ‘ሰላማዊ ሰዎችን’ መግደላቸውን የዐይን እማኞችና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል ጥቃቶቹ ሰኞ ሰኔ 17 እና ረቡዕ ሰኔ 19፤ 2016 ዓ/ም መፈጸማቸው የተነገረ ሲሆን በጥቃቶቹም ከ27 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል። በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ ሾላ ሜዳ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሰኔ 19 በመንግሥት ኃይሎች ደርሷል በተባለ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን እና አራት የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በከተማዋ ‘አጋም በር መገንጠያ’ በተባለ ሰፈር ጥቃቱ 11፡30 አካባቢ እንደተፈጸመ ለቢቢሲ የተናገሩ አንድ ከጥቃቱ የተረፉ እማኝ፤ በጥቃቱ በአብዛኛው ማዳበሪያ ለመውሰድ ከተለያዩ ቀበሌዎች የመጡ አርሶ አደሮች እንደተገደሉ ገልጸዋል። ከዘጠኝ እስከ 12 የሚሆኑ ወታደሮች “ቀጥታ መጥተው ሱቅ ላይ የተኩስ እሩምታ ጀመሩ” ያሉት የዐይን እማኙ፤ እሳቸውን ጨምሮ ማዳበሪያ ለመጫን በመጠባበቅ ላይ የነበሩ አርሶ አደሮች የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን ተናግረዋል። “የመንግሥት ኃይሎች” ማሙሽ በተባለ ሻይ ቤት ‘ሻይ ቡና’ እያሉ ነበር የተባሉ ስምንት የሚሆኑ ሰዎችን ቤቱ ውስጥ ገብተው እንደገደሏቸው ተናግረዋል። “ማዳበሪያ ለመጫን እዛው አካባቢ ላይ ነበርን። ስምንት ሰዎች የወደቁት እዛው ሻይ ቤት ነው” ያሉት እማኙ፤ እሳቸውና ጥቂት ሰዎች በጓዳ ዘለው ማምለጣቸውን ገልጸዋል። “እኔ ምን እንዳዩ እንጃ። ማታ ነው፤ ሰዓት እላፊ እንኳ መጥተው አያውቁም ነበር። 12፡00 ላይ መጥተው አጋም በር መገንጠያ የምትባል መስመር አለች፤ እዛ ላይ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መቀሌ 12 ሴቶች ሲገደሉ 178 የግድያ ሙከራዎች መፈጸማቸውን ፖሊስ አስታወቀ

የመቀሌ ከተማ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ባለፉት 11 ወራት ውስጥ በከተማው 12 ሴቶች ተገድለው በድምሩ ከ4 ሺህ በላይ ወንጀሎች ተፈጽመዋል አለ። አዲስ ማለዳ ከክልሉ መገናኛ ብዙኀን እንደተመለከተችው ከሰሞኑን የዘጠኝ ወር ሪፖርት ተብሎ በተለያዩ ሚዲያዎች ሲሰራጭ የነበረው መረጃ የ11 ወራት ሪፖርት መሆኑን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በ2016 ባለፉት 11 ወራት 4 ሺህ 340 ወንጀሎች የተመዘገቡ ሲሆን ወንጀሎቹ 7 ዓይነት ናቸው። 12 ሴቶች ሲገደሉ፣ 80 የአስገድዶ መደፈር፣ 1 ሺህ 953 የስርቆት፣ 583 የድብደባ፣ 178 የግድያ ሙከራ እንዲሁም 10 የጠለፋ ወንጀሎች መሆናቸውን የመቀሌ ከተማ ፖሊስ ገልጿል። ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከ170 በላይ የማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ ሃይሎችን የማጠናከር ስራ እየተሰራ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን የህብረተሰቡ ተሳትፎ በእጅጉ ያስፈልጋል ተብሏል። በቅርቡ በክልሉ ዋና ከተማ እና ሌሎችም አካባቢዎች በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ግድያ እና አፈና ለማውገዝ ሰላማዊ ሰልፎች እንደተካሄዱ መዘገባችን አይዘነጋም።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የጃር መሮ ወታደሮች ከአማራ ክልል ተነስቶ አዲስ አበባ የሚሄደውን የሕዝብ ማመላለሻ ተሳፋሪዎች አግተው ሶስቱን ገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ዋጫሌ ወረዳ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች መነሻውን ከአማራ ክልል አድርጎ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ በተለምዶ “ታታ” ተብሎ በሚጠራ የሕዝብ ማመላሻ አውቶቡስ ላይ ልዩ ስሙ ጃቴ በተባለ ቦታ ሐሙስ’ለት በፈጸሙት ጥቃት ሦስት ሰዎች እንደተገደሉ ባካባቢው የነበሩ የዐይን እማኞች ለዋዜማ ተናግረዋል። ሰዎቹ የተገደሉት፣ ታጣቂዎቹ አውቶብሱን በኃይል ለማስቆም ሲሞክሩና ሹፌሩ ለማምለጥ ጥረት ሲያደርግ በከፈቱት ተኩስ መኾኑን እማኞቹ ገልጸዋል። ሾፌሩ ቆስሎ ማምለጡንና የአውቶቡሱ ተሳፋሪዎችና ሌላ “ዶልፊን” ተብሎ በሚጠራ መለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በሙሉ በታጣቂዎቹ ታፍነው መወሰዳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። [ዋዜማ]
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የእናት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር በአዲስ አበባ ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊስ ተወስደው ታሠሩ

እናት ፓርቲ፣ የሕግና ሥነ ሥርዓት ኃላፊው ዋለልኝ አስፋው ባለፈው ማክሰኞ በአዲስ አበባ ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊስ ተወስደው እንደታሠሩ አስታውቋል። የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ረቡዕ’ለት ታሳሪውን ፍርድ ቤት እንዳቀረባቸው የገለጠው ፓርቲው፣ ፖሊስ ወጣቶችን በመሰብሰብ ኹከት አነሳስተዋል በማለት እንደጠረጠራቸውና ፍርድ ቤቱም ሰኔ 23 ጉዳዩን ለማየት ቀጠሮ መስጠቱን ገልጧል። ፓርቲው፣ መንግሥት አባሎቹን ማሳደድና ማሰር እንዲያቆምና የታሠሩትን አመራሩንም እንዲፈታ ጠይቋል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የተጋነነው የሴት እና የአካል ጉዳተኞች የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት ቁጥር

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት ማምሻውን ባወጠው መግለጫ 21 የፖለቲካ ፓርቲዎች በ2016 ዓ.ም ለቦርዱ ያሳወቁት የሴት እና የአካል ጉዳተኞች አባላት ካለፉት ሁለት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር የተጋጋነነ ነው ሲል አስታወቀ። ፓርቲዎቹ በ2014 እና በ2015 ዓ.ም ካቀረቧቸው ቁጥሮች አንፃር የሴት እና አካል ጉዳተኛ አባላት ቁጥር የተጋነነ በመሆኑ ማብራሪያ ተጠይቀዋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጋቢት ወር ላይ ላቀረበላቸው የማብራሪያ ጥያቄ 10 ፓርቲዎች የተለያዩ ምላሾችን እንደሰጡ አስታውቆ ገዢው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ጨምሮ 11 ፓርቲዎች ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል። ቦርዱ መግለጫውን ካወጣበት ሰኔ 20 ጀምሮ ባሉት ሰባት ቀናት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጡ የጠየቀ ሲሆን ከጊዜ ገደቡ በኋላ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አሳስቧል። ምላሽ ያልሰጡት 11 ፓርቲዎች በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከ10 ሺህ እስከ 900 ሺህ የሚደርሱ ሴት እና አካል ጉዳተኛ አባላትን እንዳቀረቡ ተሰምቷል። ብልጽግና ፓርቲ፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)፣ የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ህብረት፣ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ፣ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር፣ ራያ ራዩማ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ የጋምቤላ ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉዓላዊነት፣ ሞቻ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ የተጋነነ ቁጥር አቅርበዋል የተባሉ ፓርቲዎች ናቸው። የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዐብይ አህመድን ጨምሮ ምክትላቸው አደም ፋራህ በተለያየ ጊዜያት እንደተናገሩት የአባላቱ ቁጥር 14 ሚሊዮን ደርሷል ያሉ ቢሆንም ምርጫ ቦርድ ግን በተለይ የሴቶችና አካል ጉዳተኞቹ መረጃዎች አላሳመኑኝም ሲል ውድቅ አድርጓል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

° “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም ” – የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች

° “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም ” – የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ° “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል ” – የከተማው ውሃና ፍሳሽ  በአማራ ክልል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ኢንተርን ሀኪሞች፣ የውሃ ችግር እንደፈተናቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። የከተማው ነዋሪዎች በሰጡት ቃል፣ “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም። በአፋጣኝ መፍትሄ እንሻለን ” ብለዋል። በከተማው የውሃ አቅርቦት እንደሌለ፣ በተለይ ህፃናት የውሃ ጥሙን መቋቋም እንዳልቻሉ፣ ሰው የክረምት ውሃ ለመጠጣት መገደዱን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል። ከዚህ ባለፈ ነዋሪዎች የጉርጓድ ውሃ በሰልፍ የመጠቀም ደረጃ እንደደረሱ አመልክተዋል። ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው የጎንደር ከተማ ውሃና ፍሳስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ አያል ፤ “ እውነት ነው። እንዲያውም ማህበረሰቡ ታጋሽ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። “ አሁን ዝናብ ስለዘነበ ትንሽ ይቀንሳል እንጂ በአንድ ወር ነው ሰው ውሃ ሲያገኝ የነበረው። ግድቡ ሙሉ ለሙሉ ቆሞ ነበር። አሁን ትንሽ ውሃ ስለያዘ ምርት ስለጀመርን አሁን ወደ 25 ቀን እየወረደ ነው ” ብለዋል። የኢንተርን ሀኪሞቹን ቅሬታ በተመለከተ፣ “ ሆስፒታል ላይ ግን 24 ሰዓት ነው የምንሰጠው። መብራትና አጠቃላይ ምርት ቆሞ ካልሆነ አይቋረጥም ” ነው ያሉት። “ የማህበረቡ ቅሬታ ግን እውነቱን ለመናገር ከቅሬታ ባለፈ ሌላ ነገር ቢሉም አይፈረድባቸውም ትክክል ናቸው ” ያሉት አቶ ወርቅነህ፣ “ እንደዚህ ትዕግስተኛ የሆነ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ህወሓት “በልዩ ሁኔታ” እንዲመዘገብ፤ የፍትሕ ሚኒስቴር ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቀረበ

ህወሓት “በልዩ ሁኔታ” እንዲመዘገብ፤ የፍትሕ ሚኒስቴር ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቀረበ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በፓለቲካ ፓርቲነት “በልዩ ሁኔታ” መመዝገብ እንዲችል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ ቀረበ። ምርጫ ቦርድ ጥያቄው ከፍትሕ ሚኒስቴር እንደቀረበለት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጧል። ◼️ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ፤ ህወሓት “ኃይልን መሠረት ያደረገ የአመጻ ተግባር ላይ መሳተፉን” እንዳረጋገጠ በመጥቀስ የፖለቲካ ፓርቲውን “ህጋዊ ሰውነት” የሰረዘው በጥር 2013 ዓ.ም ነበር። ◼️ቦርዱ በወቅቱ ባስተላለፈው ውሳኔ፤ የህወሓት ኃላፊዎች “በፓርቲው ስም መንቀሳቀስ እንደማይችሉ” እገዳ መጣሉም ይታወሳል። ◼️የፍትሕ ሚኒስቴር ከሶስት ሳምንት በፊት በፓርላማ የጸደቀን አዋጅ መሰረት በማድረግ፤ ህወሓት “በልዩ ሁኔታ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ለመመዝገብ እንዲችል” ምርጫ ቦርድ “አስፈላጊውን ትብብር” እንዲያደርግ በደብዳቤ ጥያቄ አቅርቧል። ◼️ ከሁለት ቀን በፊት ሰኞ ሰኔ 17፤ 2016 ለምርጫ ቦርድ የተላከው ይህ ደብዳቤ፤ በግልባጭ ለሰላም ሚኒስቴር፣ ለብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት እንዲሁም ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መላኩ ተገልጿል። ◼️ የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞትዮስ ፊርማ ያረፈበት ይህ ደብዳቤ ለምርጫ ቦርድ መድረሱን የቦርዱ የኮሚዩኒኬሽን ክፍል ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጧል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀረበለትን ጥያቄ “በስራ ላይ ካሉ ህጎች አንጻር በመመርመር ውሳኔውን እንደሚያሳውቅ” የኮሚዩኒኬሽን ክፍሉ ገልጿል። 🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2024/13414/
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሀይ ባይ ያጡት የኢትዮጵያ ባንክ ሹመኞች እና የምዝበራ ስራዎቻቸው

(በግል ከደረሰኝ ጥቆማ የተወሰደ ነው) – ጋዜጠኛ ኤሊያስ መሰረት ዱሮ ዱሮ አይደለም የባንክ ባለስልጣን መሆን ተራ የባንክ ሰራተኛ መሆን እንደ ትልቅ ማዕረግ ይቆጠር ነበር። ለዛም ነበር ባንከሮች “Trust me, I am a banker” የሚሉት። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ከወትሮ በተለየ አብዛኛው በተለይ የኢትዮጵያ የግል ባንኮች መደበኛ የባንክ ስራ መስራትን ወደ ጎን ትተው የወንበዴዎች እና ወንጀለኞች መፈንጫ ከመሆንም አልፎ በህዝብ ገንዘብ የተመሰረቱት እና ከድሃ ማህበረሰብ በተሰበሰበው ተቀማጭ ገንዘብ የሚንቀሳቀሱት እነዚህ ባንኮች ምዝበራዎቻቸው ልክ ከማጣቱ የተነሳ ህልዉናቸውን አደጋ ላይ እስከመጣል ደረጃ ላይ ደርሰዋል። ይሄ ብቻ ሳይሆን በነዚህ ባንኮች ዉስጥ በሚደረገው ምዝበራ እና ጤናማ የንግድ ሂደትን ባልተከተለው የንግድ ሰንሰለት የተነሳ የኢትዮጵያ ህዝብን እያማረረ ከሚገኘው የዋጋ ግሽበት እና የኑሮ ዉደነት አስተዋፅኦአቸው ይህ ነው የማይባል ከፍ ያለ ነው። ለዚህ ህገወጥ እና ልክ ያጣ ድርጊታቸው ምክንያት የሆናቸው ደግሞ እጅግ ክፍት የሆነ የህግ ማዕቀፍ መኖሩ እና ባለፉት አመታት ከተቆጣጣሪ አካል (ብሔራዊ ባንክ, Finacial intelligence እና ሌሎች የመንግስት አካላት) ተገቢ ትኩረት ባለማግኘቱ ነው። ሰሞኑን የበዛው የብሔራዊ ባንክ የመመሪያ ጋጋታም ይሄንኑ ክፍተት የተገነዘበ ይመስላል፣ ብቻ ያለፈው አልፎ የሚመጣውን ችግር ቢያስቀርልን የሚናቅ አይደለም። ለማንኛዉም በነዚህ የግል ባንኮች ከፍተኛ ኃላፊዎች ከሚሰሩት ምዝበራዎች ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል: 1. ለብዙ ሰው ለማመን በሚከብድ ደረጃ በዋናነት የ black ማርኬት ዋነኛ አዋዋዮች ወይም አገናኞች ሆነው የሚሰሩት እነዚህ ሹመኞች ተብለው የተሰየሙት የባንክ ባለስልጣናት ናቸው። ይሄም አሰራሩ እንዲህ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በቦሊቪያ የተሞከረው መፈንቅለ መንግሥት ከሸፈ።

ሙከራው ሰዓታትን እንኳን አልቆየም። የፕሬዜዳንቱን ቤተመንግሥት በኃይል ሰብረው ገብተው የወረሩት ወታደሮች ከቤተመንግሥቱ አካባቢ መሄዳቸው ተሰምቷል። ፕሬዜዳንት ሉዊስ አርሴ ፤ ወታደሮችን እየመሩ ቤተመንግሥት የገቡትን የሠራዊቱን አዛዥ ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋን ከስልጣን አውርደው በሌላ ተክተዋል። አዲሱ የሠራዊት አዛዥ ጆሴ ዊልሶን ሳንቼዝ ሁሉም ቤተመንግሥት የመጡ ወታደሮች ወደ የመጡበት ወታደራዊ ሰፈር /ክፍል እንዲመለሱ አዘዋል። ይህን ተከትሎም ወታደሮቹ ከስፋራው ለቀው ሄደዋል። ፕሬዝዳንት አርሴ አዲስ የአየር ኃይል አዛዥ እና የባህር ኃይል አዛዥም ሾመዋል። ፕሬዝዳንቱ ወታደሮች ቤተመንግሥቱን ሰብረው መግባታቸውን እና መውረራቸውን ተከትሎ ህዝቡ በነቂስ ተደራጅቶ ወደ ጎዳና እንዲወጣና የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እንቅስቃሴውን እንዲያከሽፍ እና ዴሞክራሲውን እንዲያስጠብቅ ጥሪ አቅርበው ነበር። በዚህም በርካቶች የሀገሪቱን ባንዲራ ይዘው በቤተመንግሥቱ አካባቢ ተሰብሰበው ነበር። ፕሬዝዳንቱ ሙከራው መክሸፉን ተከትሎ ህዝቡን  በእጅጉ አመስግነዋል። ወታደሮችን እየመሩ ቤተመንግሥት የገቡት ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋን ምንም እንኳን የመፈንቅለ መንግሥቱ መሪ ነኝ ብለው በግልጽ ባይናገሩም ፥ ” ጥፋት ይቁም ፤ ሀገራችንን ወደ ድህነት መምራት ይቁም፣ ሠራዊታችንን ማዋረድ ይቁም ” ሲሉ ተደምጠው ነበር። ጦሩ ዴሞክራሲን ወደነበረበት ለመመለስ እና የፖለቲካ እስረኞችን ነጻ ለማድረግ እንደሚጥርም ሲናገሩ ተደምጠዋል። ዙኒጋን አዲስ የሚኒስትሮች ካቢኔ እንደሚቋቋም ከአሁን በኃላ ሀገሪቱ አሁን ባለው መንገድ እንደማትቀጥልም ገልጻው ነበር። ጄነራል ዙኒጋን ከሽፏል ከተባለው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኃላ ቀጣይ ዕጣፋንታቸውን እና በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለጊዜው አልታወቀም። ቦሊቪያ 🇧🇴 ፦ በደቡብ አሜሪካ የምትገኝ ከ12 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖሩባት ሀገር ናት።
Posted in Ethiopian News

የአብይ አሕመድ የድርድር ጥሪ ለፖለቲካ ገፅታ ግንባታ እንጂ ሰላም ለማምጣት ምንም ፋይዳ የለውም።

እውነተኛ የሰላም ድርድር እንዴት ? እንዲህ አይነት አካሄድ የፖለቲካ ገጽታ ግንባታ ላይ ሚና ይኖረው እንደሆን እንጂ ሰላም በማምጣት ረገድ ግን ፋይዳው እምብዛም ነው  በአማራ ክልል የተፈጠረውን የሰላም እጦት “በሰላማዊ መንገድ መፍታት ያስችላል” የተባለለት የሰላም ኮንፈረንስ በባህር ዳር ከተማ ትናንት እና ዛሬ ተካሂዷል። ትናት በተካሄደው የመክፈቻ ሥነስርዓት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ፤ “ሁሉም ነገሮች ከብረት (ከጠብመንጃ) በመለስ በውይይት፣ በድርድር፣ በሰጥቶ መቀበል መርህ ህዝብና አገርን በሚያሳድግ አቅጣጫ መነጋገር አለብን፣ መወያየት አለብን የሚል አቋም መያዝ አለበት፤ መንግስት ጭምር ይህን አቅጣጫ እንዲከተል፣ በተጨባጭ ውጊያ እያደረገ ያለውም ኃይል ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ በማድረግ ወደ ሰላም አማራጭ እንዲመጣ የሚያደርግ አካሄድ ውይይት ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡ ” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ እንዲህ ዓይነት የሰላም የምክክር መድረኮች ሰላማዊ መፍትሄን ለማፈላለግ ጠቀሜታቸው የጎላ እንደሆነ የሚናገሩ አሉ። በአንጻሩ ደግሞ ከዚህ ቀደም ከተካሄዱ ተመሳሳይ መድረኮችና የሰላም ጥሪዎችን በመነሳት እውነተኛ የሰላም ንግግር በቀጥታ የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተው ነፍጥ ካነገቡ ሃይላት እንጂ የሃገር ሽማግሌዎችን በማናገር አይመጣም በማለት የሚከራከሩም አሉ። እንዲያም ሲል እንዲህ አይነት አካሄድ የፖለቲካ ገጽታ ግንባታ ላይ ሚና ይኖረው እንደሆን እንጂ ሰላም በማምጣት ረገድ ግን ፋይዳው እምብዛም ነው በማለት የሚሞጉቱ አሉ።  
Posted in Ethiopian News

2.8 ሚሊዮን ብር የተከፈለባቸው 3 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ደብዛቸው ጠፋ

“ በታጣቂዎች ከታገቱ 9 ወራት አለፉ፤ ያሉበትን እንኳ አናውቅም። ወደ ማን እንጩህ ? ”- የታጋች ባለቤት መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም በታጣቂዎች ታግተው የተወሰዱ 3 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ደብዛቸው እንደጠፋ መሆኑን የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ። ወደባቱ ለስራ እየተጓዙ በነበረበት ወቅት በታጣቂዎቸ ታገቱ የተባሉት ሠራተኞቹ ያልተለቀቁት አጋቾቹ ገንዘብ ጠይቀው ከ2.8 ሚሊዮን ብር ከተላከ በኋላ እንደሆነ የታጋች ቤተሰቦች ከዚህ ቀደምም ገልጸው ነበር። አሁንስ ምን አዲስ ነገር አለ ? – አቶ ልዑል አስፋወሰን – አቶ ሰይፉ እንዳለ – አቶ አብዩ ደገፋው የተባሉ ሠራተኞች በህይወት ይኑሩ አይኑሩ አይታወቅም። ትላንት ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ 2 የታጋች ቤተሰቦች ስለ 3ቱም ታጋቾች ምንም የሰሙት ፍንጭ እንኳ እንደሌለ ገልጸዋል። አንዷ የታጋች ባለቤት “ በታጣቂዎች ከታገቱ 9 ወራት አለፉ ፤ ያሉበትን እንኳ አናውቅም። ወደ ማን እንጩህ ? ” ሲሉ ሀዘን ያጀበው ጥያቄ አንስተዋል። የሰው ልጅ ለ9 ወራት ያህል ያለበት እንኳን አለማወቅ ከባድ ሀዘን መሆኑን ፤ ኤሌክትሪክ ኃይልን በቅርቡ ቢጠይቁም ካቅሙ በላይ እንደሆነበት መግለጹን ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረበለት የኤሌክትሪክ ኃይል ጉዳዩ ከአቅሙ በላይ እንደሆነበት መግለጹ ይታወቃል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በሚገኙ እስረኞች መካከል ተነሳ በተባለ ግጭት ታራሚዎች መጎዳታቸው ተነገረ

በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በሚገኙ እስረኞች መካከል ተነሳ በተባለ ግጭት ታራሚዎች መጎዳታቸው ተነገረ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ባለፈው ቅዳሜ በእስረኞች መካከል ተነሳ በተባለ ግጭት ሳቢያ፤ ቢያንስ አምስት ታራሚዎች መጎዳታቸውን የእስረኛ ቤተሰቦች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በዕለቱ ግጭት እንደነበር ቢያረጋግጥም፤ በክስተቱ “ቀላል ጉዳት የደረሰበት አንድ ታራሚ ብቻ ነው” ሲል አስተባብሏል። ➡️ ግጭቱን ተከትሎ በማረሚያ ቤቱ ሆነው የፍርድ ቤት ጉዳያቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ጋዜጠኞች እና ሌሎች  እስረኞች ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ መደረጉን የእስረኞቹ ቤተሰቦች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስረድተዋል። ➡️ በቃሊቲ ማረሚያ ቤቱ ግጭት ተቅስቅሶ የነበረው፤ ከሁለት ቀን በፊት ጠዋት ሶስት ሰዓት ገደማ እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። ➡️ ልጃቸው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደታሰረ የጠቀሱ አንድ የአካባቢው ነዋሪ፤ ቅዳሜ ጠዋት በቤት ውስጥ እንዳሉ “የመሳሪያ ተኩስ ድምጽ” መስማታቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ➡️ በድንጋጤ ውስጥ ሆነው ሁኔታውን ለማጣራት ወደ ማረሚያ ቤት አቅጣጫ ሲሄዱ፤ በአቅራቢያው ባሉ መንገዶች “በፓትሮል የመጡ” በርካታ የፌደራል ፖሊሶች መመልከታቸውን አስረድተዋል። ➡️ በማረሚያ ቤት የታሰረ የቤተሰብ አባላቸውን ለመጠየቅ በዕለቱ በስፍራው ተገኝተው የነበሩ የዓይን እማኝም ይህንኑ አረጋግጠዋል። “የታጠቁ የፌደራል ፖሊስ አባላት  ማረሚያ ቤቱን ዙሪያውን ከበውት ነበር” ብለዋል እኚሁ የዓይን እማኝ። ⚫️ ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13410/ 
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግሥት ያረቀቀውን አዲስ የታክስ ሕግ የተቃወሙ ኬንያውያን የአገሪቱን ፓርላማ ቅጥር ጊቢ ጥሰው ገብተዋል።

በኬንያ ተቃውሞ ሰዎች ተገደሉ። የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግሥት ያረቀቀውን አዲስ የታክስ ሕግ የተቃወሙ ኬንያውያን የአገሪቱን ፓርላማ ቅጥር ጊቢ ጥሰው ገብተዋል። ፖሊስ በከፍተኛ ቁጥር የወጡ ተቃዋሚ ወጣቶችን ለመበተን ጥይት እና አስቀሽ ጭስ ተኩሷል። እስካሁን ድረስ ቢያንስ 5 ሰዎች በጥይት የተመቱ ሲሆን ሁለቱ ሕይወታቸው አልፏል። ከጥቂት ሰዓታት በፊት የአገሪቱ ም/ ቤት አባላት ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ገጥሞት የነበረውንና በተለያዩ ምርት እና አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ ታክስ የሚጥለውን ረቂቅ ሕግ አጽደቀዋል። ” አዲሱ የቀረጥ ሕግ ኑሯችንን ያስወድድብናል ” ሲሉ የቆዩት ኬንያውያን ወጣቶች ከአገሪቱ ፓርላማ ፊት ለፊት የተቃውሞ ድምጻቸውን ለማሰማት በከፍተኛ ቁጥር ወጥተዋል። ከፖሊስ ቁጥጥር አቅም በላይ የሆኑ አብዛኛዎቹ ወጣቶች የሆኑ ተቃዋሚዎች የፓርላማውን በር ጥሰው ገብተዋል። በመቶዎች የሚቆጠሩ የፓርላማ አባላት ከምክር ቤቱ ምድር ቤት ለመደበቅ ሲሯሯጡም ተይተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ፥ ተቃዋሚዎች አንደኛውን የፓርላማውን ክፍል በእሳት ማያያዛቸውን ቢቢሲ እና የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አቶ ታዬ ደንደኣ ከመንግስት በሚደርስ ጫና ምክኒያት ከጠበቆቻቸው ጋር መገናኘት አለመቻላቸውን ገለጹ

አቶ ታዬ ደንደኣ ከመንግስት በሚደርስ ጫና ምክኒያት ከጠበቆቻቸው ጋር መገናኘት አለመቻላቸውን ገለጹ በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደኣ ጠበቆቻቸው ላይ ከመንግስት የሰላ ማስፈራሪያ በመድረሱ ከጠበቆቻቸው ጋር መገናኘት አዳጋች እንደሆነባቸው ገለጹ፡፡ አቶ ታዬ ዛሬ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ-መንግስትና ሕገ-መንግስት ስርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮች ችሎት ላይ ቀርበው እንዳስረዱት “አቃቤ ህግ እና ሰዎቻቸው” ባሏቸው አንድም ጠበቃ እንዳይቆምላቸው በጠበቆቻቸው ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ ደርሷል፡፡ የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም የሰጠው የንብረት ማስመለስ ትዕዛዝም አለመከበሩን አንስተው ቅሬታቸውን እንዳሰሙ አዲስ ማለዳ ሰምታለች፡፡
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ፋሽስቱ ዐቢይ አሕመድ፤ በፀረ-ሽብር ዘመቻ ሥም ጦርነትን ኤክስፖርት የማድረግ ስትራቴጂው ሲጋለጥ…

ጥብቅ መረጃ! ፋሽስቱ ዐቢይ አሕመድ፤ በፀረ-ሽብር ዘመቻ ሥም ጦርነትን ኤክስፖርት የማድረግ ስትራቴጂው ሲጋለጥ… ዐቢይ አሕመድ በምዕራባውያን ያጣውን ድጋፍ ለማግኘት በፀረ-ሽብር ዘመቻ ሥም ጦርነትን ኤክስፖርት የማድረግ ስትራቴጂ ይዞ እየሰራ ነው። ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሱት መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሰላም አስከባሪ በሚል በሶሚሊያ የዘመተው የኢትዮጵያ ጦር እንዲወጣ በሞቃዲሾው መንግሥት ከተጠየቀ ወራት ተቆጥረዋል። ለዚህም በሞቃዲሾው መንግሥትና በአፍሪካ ሕብረት ጦር (አሜሶን) በኩል የቴክኒክ ዝግጅቶች በመደረግ ላይ ናቸው። ዐቢይ አሕመድ በአገር ቤት በገጠመው ከፍተኛ የቅቡልነት ቀውስ በተለይም ከአማራ ሕዝብ ጋር በገባበት ጦርነት ዓለማቀፍ ጫናዎች በርትተውበታል። ብድር አቅራቢ፣ እርዳታ ለጋሽ ምዕራባዊያን ፊታቸውን ካዞሩበት ከራርሟል። የኢትዮጵያን ካዝና ለጦር መሳሪያ ግዥ ያራገፈውና በዶላር ረሃብ ጠኔ የመታው በፋሽስቱ አገዛዝ በምዕራባዊያን ዘንድ ያጣውን ድጋፍ መልሶ ለማግኘት የፀረ-ሽብር ዘመቻ የምትለውን የተለመደች ካርድ መዝዟል። ለዚህ ይረዳው ዘንድ ቀደም ሲሉ በነበሩ ወራት በእጅ አዙር አልሸባብን በጦር መሳሪያ በማገዝ በቅርቡ ራሱን መልሶ ያጠናከረውን አልሸባብ ለመደምሰስ ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ እንደከፈተ ለማሳየት ጥረት ላይ ነው። አልሸባብ በዚህ ሳምንት መጠናከሩን ሚያሳይ የ 1 ሰዓት ተኩል ቪዲዮ የለቀቀው በዐቢይ አሕመድ የደህንነት ሰዎች ምክረ-ሀሳብ እንደሆነ ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሳት መረጃ ያሳያል። ይህን ጉዳይ የአሜሪካ፣ እንግሊዝና የአውሮፓ ሕብረት የቀጠናው ዲፕሎማቶች ጭምር የሚያውቁት ሰሞነኛ መረጃ ነው። በሌላ በኩል ቢቢሲ በዛሬ ዘገባው ላይ፦ የኢትዮጵያ ሰራዊት በቅርቡ ራሱን ባጠናከረው የአልሸባብ ሃይል ላይ ሶማሊያ ውስጥ በርካታ ኪሎ ሜትር ዘልቆ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል የሚል ዜና ማስወራት ጀምሯል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሰባት የዐቢይ አሕመድ የግል ጀኔራሎች ተደራጅተው ሃገር እየዘረፉ ነው ( ዝርዝር መረጃዎችን ይዘናል)

‹‹የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት›› ይባል የነበረውን ተቋም ወደ ዐቢይ አሕመድ ግል ጉዳዩ አስፈጻሚነት በዐቢይ ይሁንታ ልቅ የሆነ የዘረፋ መብት ያገኙት የብልጽግና መለዩ ለባሽ ጀኔራሎች የጠረፍ ኮንትሮባንዲስት፤ የመሀል አገር ደላላ ሆነዋል፡፡ የዐቢይ አሕመድ ጀኔራሎች በግላቸውና በቡድን በኢትዮጵያ ምድር የሚያካሂዱት ዘረፋ፣ እንደተጋነነው ማዕረጋቸው ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ምድር ተሰምቶና ታይቶ የማይትወቅ ደረጃ ላይ ደርሷል። የኢትዮ 251 የጥናትና ምርምር ቡድን፣ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰራውን ምርመራ፦ ‹በደላላ ጀኔራሎች የምትዘረፍ ሀገር፤ ኢትዮጵያ› በሚል ርዕስ ትክሻቸው ላይ ያለው ወታደራዊ ማዕረግ የከበዳቸው የዐቢይ አሕመድ ጀኔራሎች ኢትዮጵያን እንዴት ተደራጅተው እየዘረፏት እንዳለ ከብዙ ገመናዎቻቸው እጅግ በጥቂቱ ጨልፈን እንመለከታለን፡፡ የኢትዮ 251 ሚዲያ ጥናትና ምርምር ቡድን በሚከተሉት ሰባት የዐቢይ አሕመድ የግል ጀኔራሎች፦ 1) ብርሃኑ ጁላ ገለልቻ 2) አለምሸት ደግፌ ባልቻ 3) ይልማ መርዳሳ ኛጷ 4) አበባው ታደሰ አስረስ 5) ጌታቸው ጉዲና ሰልባና 6) መሀመድ ተሰማ ገረመው 7) ብርሃኑ በቀለ በዳዳ የዘረፋ ኔትወርክ ዙሪያ የሰራነውን የምርመራ ሪፖርት እንድታነቡና በተገኘው የሚዲያ አማራጭ ሁሉ ታሰራጩት ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን። ማሳሰቢያ፦ ኢትዮ 251 ሚዲያ ይህን የምርመራ ሪፖርት ለሕዝብ ይፋ ሲያደርግ፤ የሥርዓቱን ገመና በማጋለጥ ትግሉን ማቀጣጠል ቀዳሚ ዓላማው በመሆኑ ነው። ማንኛውም የትግል ሚዲያ ይህን የምርመራ ሪፖርት በራሱ ሚዲያ ማቅረብ ይችላል። ምንጭ መጥቀስ ሙያዊ ግዴታ መሆኑን ማስታወስ እንወዳለን። መሉዉን ያንብቡ፥ https://drive.google.com/file/d/1MoPoBQ4k8EdBvVvJD8ksuouuKTxnruBT/view
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ከእግር ኳሱ ቢባረሩም ኦሎምፒክ ኮሚቴን እየበጠበጡት ነው፤ 156 ሚሊዮን ብር ኦዲት አላስደርግም ብለዋል።

በሕግ አምላክ‼️ ህገወጡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምርጫ ከተካሄደ ሁለት ሳምንት ሆኖታል፤ ይህንን ድብቅ ጉባኤ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ገፅ ይፋ ካደረኩት በኋላ በብዙዎች መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል፤ አብዛኞቹ የሚመለከታቸው አካላት ግን ምርጫው የጨረባ መሆኑን እያወቁ ዝምታን መርጠዋል፤ ጥቂቶች ብቻ አደባባይ ወጥተዋል፤ እነማን ምን አሉ? ዝምታን የመረጡትስ ለምን? ቀጣይስ ምን ታስቧል? በጥቂቱ እንቃኘው፦ 🔷 ማን ምን አለ? ምክትል ፕሬዝዳንት ተብሎ የተመረጠው የአትሌቲክሳችን ምልክት ሻለቃ ሀይሌ ገ/ስላሴ ስለ ምርጫው ምንም እንደማያውቅ በወቅቱም ሀገር ቤት እንዳልነበረ፣ ሹመቱን ከሰው መስማቱን ተናግሯል፤ ከሶስት አመት በፊት በሙያህ አገልግል ተብዬ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውስጥ ገብቼ ነበር የሚለው ሀይሌ ሆኖም የማየው ሁሉ ደስ ስላላኝ ውሳኔዎች በጋራ ሳይሆን በግል ሲወሰኑ ስመለከት ለመራቅ ተገደድኩ፥ ከሶስት ስብሰባ በላይ አልተሳተፍኩም ብሏል፤ ጉባኤም ሆነ ምርጫ ከኦሊምፒክ በኋላ መደረግ እንዳለበት የሚናገረው ሀይሌ የአሁኑ ምርጫም ህጋዊ አይደለም ይላል፤ የፓሪስ ውጤት ሳይታይ የኦሊምፒክ ኮሚቴው ስራ ሳይገመገም ተቻኩሎ ምርጫ መደረጉ እንዳስገረመውና ምናልባትም የፓሪስ ውጤታችን ጥሩ ካልሆነ ስለማንመረጥ ሳይቀድሙን እንቅደማቸው ብለው ሊሆን እንደሚችል ግምቱን አስቀምጧል፤ ይህ ምርጫ ተሽሮ በቀጣይ በህጋዊ መንገድ ከተካሄደ ለመወዳደር ማሰቡን ጠቁሟል፤ የእሱን ሹመት በተመለከተ ለኦሊምፒክ ኮሚቴውና ለባህልና ስፖርት ሚንስቴር ማሳወቁን ገልፆ ኸረ በህግ ብሎ መፍትሄ ጠይቋል፤ ሀይሌ ተቃውሞውን ካሰማ በኋላ ኦሊምፒክ ኮሚቴው ሀይሌን እንዳልመረጠው ቢገልፅም በዕለቱ የተመረጡት የቦርድ አባላት ለተሳታፊዎቹ ይፋ ሲሆኑ ግን የሀይሌ ስም መኖሩን በግል አረጋግጫለሁ በሌላ በኩል የባህልና ስፖርት ሚንስቴር በማህበራት ጉባኤና ምርጫ ወቅት በታዛቢነት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ብአዴን ለወያኔ “የአድኑኝ” ጥሪ አቀረበ!

ብአዴን ለወያኔ “የአድኑኝ” ጥሪ አቀረበ! ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰው ጥብቅ መረጃ! “ዛሬ የተሰበሰብነው የፋኖ ኃይል ስለጠነከረ የሕወሓት ኃይል ወደጎንደር ይግባ ያግዘናል የሚለውን የድርጅታችንን የፖለቲካ ውሳኔ ለማስፈፀም ነው” የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪው ዲያቆን ሸጋው ውቤ የጠለምት አማራን ለዳግም ባርነት አሳልፎ በመስጠት የትግል አቅጣጫውን ለማሳት ብአዴን የወያኔ ታጣቂ ከነትጥቁ ወደጠለምት ገብቶ እንዲወር ከፌዴራል የተሰጠውን ውሳኔ ለማስፈፀም ለዞን አመራሮች መመሪያ አውርዷል። ይህን የሚያስፈጽሙት የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳዳሪው ዲያቆን ሸጋው ውቤ እና የዞኑ የብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊ ይመር ሥዩም ናቸው። የምዕራብ ጠለምት፣ የማይጠምሪ ከተማ እና የምስራቅ ጠለምት የዲማ አስተዳዳሪዎችን ፣ የፀጥታ ሀላፊዎችንና የማንነት አስመላሽ ኮሚቴዎችን በመሰብሰብ ፋኖ አያድናችሁም በሰላም መኖር ከፈለጋችሁ ብልጽግና ያወረደውን ትዕዛዝ ተቀብሉ በማለት ለማስፈራራት የሞከረ ቢሆንም የማንነት ኮሚቴው ወደባርነት ሕይወት አንመለስም በማለት አቋማቸውን ማሳወቃቸውን ኢትዮ 251 ሚዲያ አረጋግጣለች። እነ ዲያቆን ሸጋው ወደባህርዳር ተጠርተው ነው ይህ ትዕዛዝ የተሰጣቸው። ትዕዛዙን መሰረት በማድረግ ነው፦ “ዛሬ የተሰበሰብነው የፋኖ ኃይል ስለጠነከረ የሕወሓት ኃይል ወደጎንደር ይግባ፣ ያግዙናል የሚለውን የድርጅታችንን የፖለቲካ ውሳኔ ለማስፈፀም ነው” በሚል በስብሰባው ላይ የተናገው። የወያኔ ኃይል ከእነ ትጥቁ የሚገባው ሕዝቡን ለመጠበቅ ነው፤ በአካባቢው ሰርጎ የሚገባ የፋኖ ኃይል ይከላከላል፤ ለኛም እፎይታ ነው ሲል የተናገረው ደግሞ የዞኑ የብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊ ይመር ሥዩም ሲሆን በተጨማሪም “ይህ ቀጭን ትዕዛዝ የመጣው ከዐቢይ አሕመድ እና ከተመስገን ጥሩነህ ነው። አረጋ ከበደ ትኩስ ድንች ውሳኔውን ወደታች ከማቀበል በዘለለ ምንም ሚና የለውም።” ሲል
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በርካታ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ሱማሊያ ግዛት ዘልቀው ገቡ

በርካታ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከባድ የጦር መሳሪያዎችንና ታንኮችን በመያዝ ትናንት ወደ ሱማሊያ ግዛት ዘልቀው እንደገቡ የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከኢትዮጵያ የተነሱት ወታደሮች ያቀኑት፣ ሒራን ወደሚባለው የሱማሊያ ግዛት እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የኢትዮጵያዊያኑ ወታደሮች ተልዕኮ ምን እንደኾነ ለጊዜው ግልጽ እንዳልኾነም የዜና ምንጮቹ ጠቅሰዋል። የሱማሊያ ጦር ሠራዊት ባለፉት ኹለት ዓመታት ያገኛቸውን ወታደራዊ ድሎች፣ አልሸባብ ባለፉት ጥቂት ወራት ሙሉ በሙሉ እንደቀለበሳቸው የአሜሪካ ባለሥልጣናት መናገራቸውን የአሜሪካ ዜና ምንጮች ሰሞኑን ዘግበው ነበር። የሱማሊያ ባለሥልጣናት ግን፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ግምገማ የተሳሳተ በማለት እያጣጣሉት ይገኛሉ።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከ4 በላይ ወረርሽኞች ተከስተዋል። ከ2,400 በላይ ሰዎች በወረርሽኙ ተጠቅተዋል። ከፍተኛ ሞት አለ

” ከ4 በላይ ወረርሽኞች ተከስተዋል። ከ2,400 በላይ ሰዎች በወረርሽኙ ተጠቅተዋል። ከፍተኛ ሞት አለ ” – የዋግኸምራ ብሔረሰብ ጤና መምሪያ በአማራ ክልል ፤ በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ከተከሰተ በሰነበተው ድርቅ ሳቢያ ከአራት በላይ ወረርሽኞች መከሰታቸውን ተከትሎ ሰዎችና እንስሳት እየሞቱ መሆኑን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ። የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊው አቶ አሰፋ ነጋሽ በሰጡት ቃል፣ ” ከ4 በላይ ወረርሽኞች ተከስተዋል። ከ2,400 በላይ ሰዎች በወረርሽኙ ተጠቅተዋል። ከፍተኛ ሞት አለ ” ብለዋል። በወረርሽኙ ምን ያህል ሰዎች ሞተዋል ? ለሚለው ጥያቄ፣ ” ሞቱ ከፍተኛ ነው። ቁጥሩን Specifically ለመናገር እርግጠኛ አይደለሁም ” ነው ያሉት። ቢያንስ ከ5,000 በላይ እንስሳት እንደሞቱ፣ ለመከተብ አቅም እንዳልተገኘ፣ በሽታው (አባሰንጋ) ከእንስሳት ወደ ሰው እየተላለፈ መሆኑን ገልጸው፣ ከአንድ ወረዳ ብቻም ወደ  140 ሰዎች አባሰንጋ እንደተላለፈባቸው አስረድተዋል። – ኮሌራ – ኩፍኝ – እከክና – አባሰንጋ (የከብት በሽታ) እና ሌሎች ወረርሽኞች በሁሉም በሚባል ደረጃ በብሔረሰብ አስተዳደሩ ላይ ተከስተዋል ሲሉ ተናግረዋል። ” ኩፍኝ በሁሉም ወረዳዎች ተከስቷል። በጣም ብዙ ቁጥር ያላቸው ህፃናት ታመውብናል ” ያሉት አቶ አሰፋ፣ ” ለወረርሽኙ ምላሽ ክትባት እየሰራን ነው ” ብለዋል። ” እከክ በተለይ ድርቁ በስፋት ባጠቃቸው ወረዳዎች ተከስቶ ነበር ለመቆጣጠር እየተሞከረ ነው። የውሃ አቅርቦት፣ የንጽህ እና መጠበቂያ ግብዓት ካልቀረበ እሱንም መቅጣጠር እጅግ አስቸጋሪ ነው ” ነው ያሉት። ድርቅ ከመከሰቱ በፊትም አካባቢው ትርፍ አምራች ስላልነበር የምግብ እጥረት እንደነበር አሁን የድርቁ መከሰት የምግብ እጥረቱን እጅጉን
Posted in Ethiopian News

ኢንቨስተር ሆነው ኢትዮጵያ የገቡት ዶ/ር ፍሰሐ እሸቱ ደረሰብኝ ባሉት ማስፈራሪያ ከአገር መውጣታቸውን ገለፁ

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሐ እሸቱ (ዶ/ር) ደረሰብኝ ባሉት ጫና እና ማስፈራሪያ ከአገር መውጣታቸውን አስታወቁ። ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ኩባንያ በህገ ወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ የራስ አስመስሎ በማቅረብ፣ በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ፣ ፋኖን በመደገፍ ፣ በህገወጥ መሳሪያ ዝውውር እንድሁም በሽብርና በሌሎች ተደራራቢ ውንጀላዎች የኩባንያውና የዋና ሥራ አስፈፃሚው የግል የባንክ ሒሳቦች ከሦስት ሳምንት በፊት መታገዳቸውን ዋና ሥራ አሰፈፃሚው ገልፀዋል። የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሐ እሸቱ ዶ/ር ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በበይነ መረብ ቀርበው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ቀደም ሲል ከፍትህ ሚኒስቴር ለባንኮች በተፃፈ ደብዳቤ እግድ የተጣለበት የኩባንያው የባንክ ሒሳብና የግል የባንክ ሒሳባቸውን ለማስለቀቅ 250 ሚሊዮን ብር እንደተጠየቁ ተናግረዋል። የተጠየቁትን ገንዘብ ለመክፈል ድርድር ጀምረው እንደነበር የጠቀሱት ፍሰሐ ዶ/ር በመጨረሻም 200 ሚሊዮን ብር እንድከፍሉ ተጠይቀው ” አልከፍልም” በማለታቸው ከአገር መውጣታቸውን አስታውቀዋል። የትኛው አካል ገንዘቡን ክፈሉ እንዳላቸውና ከማን ጋር እንደተነጋገሩ ያልገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው ነገር ግን ድርድሩን ያደረጉት ሁኔታዎች እስከሚመቻቹ ድረስ እንደነበር ተናግረው በወቅቱ ከተዳራዳሪዎች ያደረጉትን የስልክ ልውውጥና ሌሎች ዶክሜንቶን በማስረጃነት ማቅረብ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። “የተጠየከውን ገንዘብ በአፋጣኝ ካልከፈልክ እናስርሃለን እንገልሀለን” የሚሉ ዛቻና ማስፈራሪያዎች ሲደርስባቸው እንደነበር ተናግረዋል። ነገር ግን የተጠየቁትን ገንዘብ ለመክፈል ከተስማሙ የታገደባቸውን የባንክ ሒሳብ ከማስከፈት ባሻገር ከመንግስት ጋር አብረው እንድሰሩ ሁኔታዎችን እንደሚያመቻቹና ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንደሚያገናኟቸው ሲያግባቡአቸው እንደነበር ዶ/ ር ፍሰሐ ተናግረዋል። የተጠየቁትን ጉቦ ባለመክፈላቸው በደረሰባቸው ጫናና ማስፈራሪያ ተገደው
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በጎጃም ጅጋ የተፈጸመው መንግስታዊ ግድያ እንዲጣራ አራት ፓርቲዎች ጠየቁ

እናት ፓርቲ፣ መኢአድ፣ ኢሕአፓ እና የዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ የመንግሥት ኃይሎች ምዕራብ ጎጃም ጅጋ ከተማ ውስጥ ባለፈው ሰኔ 9 ቀን በንጹሃን ላይ የፈጸሙት ግድያ ባስቸኳይ በገለልተኛ አካል እንዲጣራና አጥፊዎች ለሕግ እንዲቀርቡ ዛሬ በጋራ ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል። ፓርቲዎቹ፣ ወታደሮች ጎህ በተባለ ሆቴል በመመገብ ላይ የነበሩ 12 ሰላማዊ ሰዎችን አሰልፈው ረሽነዋል በማለት ከሰዋል። የመንግሥት ወታደሮች በሰላማዊ ሰዎች ላይ “የበቀል ርምጃ” የወሰዱት፣ ከጅጋ ከተማ ወጣ ብሎ ከፋኖ ታጣቂዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ካደረጉ በኋላ እንደኾነ ፓርቲዎቹ ገልጸዋል። ከተገደሉት መካከል፣ የባንክ ሠራተኞች፣ መምህራንና የጉልበት ሠራተኞች እንደሚገኙበት የገለጡት ፓርቲዎቹ፣ የመንግሥት ኃይሎች ስድስት ሰዎችን ከንግድና መኖሪያ ቤቶች ጭምር እያስወጡ ረሽነዋል ብለዋል። ኹለት በጥይት ተመተው የቆሰሉ ሰዎች በባሕርዳር ፈለገ ሕይወት ሆስፒታል ሕክምና እየተከታተሉ ናቸው ተብሏል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ከሰኔ 15 ጀምሮ በሁሉም ቀጠና የሚያካልል ውጊያ እንደታቀደ የብልፅግና ሰነድ ያሳያል።

የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ክረምቱ ከመግባቱ በፊት የመጨረሻ መጨረሻ ያለውን ወታደራዊ ኦፕሬሽን ለማድረግ እስከ ሰኔ 30 አዲስ ዕቅድ ይዟል። ለዚህም ከ ሰኔ 15 ጀምሮ በሁሉም ቀጠና የሚያካልል ውጊያ አለ። ሸዋ ግንባር፦ ይፋት ቀጠና፣ ምንጃር በረኸት እና ሰላ ድንጋይ፣ ጎጃም ግንባር፦ ከሰከላ ውጪ ባሉ ቀጠናዎች እስከአባይ ሸለቆ ድረስ የሚያካልል ውጊያ ታስቧል፣ የሰከላን ውጊያ ቀጥታ ከፍኖተሰላም ለመምራት የ ኮሚኒኬሽን ስራ እየሰሩ ነው። ከ መቶ አዛዥ ጀምሮ ቀጥታ ከ ፍኖተሰላም እና ደብረማርቆስ ለማዘዝ አቅደዋል። ነገር ግን የሚሆነውን እናያለን። በወሎ ግንባር፦ በአንበሳ መጋጫ አስፍቶ መሄድ እና ወገል ጤና ነጻ ከተማ የማድረግ አምባሰልን ማርዬን መቆጣጠር ፣ሳይንት ቀጠና ወታደራዊ ዘመቻዎች ይኖራሉ፣ ጎንደር ግንባር፦ ደቡባዊውን ቀጠና በአምስት ግንባር በማስፋት ወደመሀል አስገብቶ ፋኖን ነጻ መሬት የማሳጣት ዕቅድ አለ። ማዕከላዊና ሰሜናዊው የጎንደር ቀጠና በወገራ ጃኖራ ቆላማው ስፍራ፣ መሀል አርማጭሆ ምዕራባዊው የጎንደር ቀጠና ቋራን ጨምሮ መተማና ሽንፋ ገዥ እና አንገት የሆኑ ወታደራዊ ገዥ መሬቶችን መልሶ ለመቆጣጠር ወታደራዊ ዕቅድ አለ። በተመሳሳይ ሁኔታ ደቡባዊ ጎንደር ጫፍ ላይ ከጋይንት እስከ መቄት የቆረጣ ውጊያ የማድረግ እቅድ ተይዟል። እንደመረጃ ምንጮቻችን፦ ይሄ ዕቅድ በአመዛኙ ከመደበኛ ውጊያ ይልቅ ጸረ-ሽምቅ ባህሪ አለው። በሌላ በኩል ፋኖን ወደ ከተማ በመሳብ መምታት የታሰበባቸው ግንባሮች እንዳሉ ከውስጥ ምንጮቻችን የደረሰን መረጃ ያሳያል። ላስታን ጨምሮ ሰሜናዊውን የወሎ ቀጠና በተመለከተ ያለው ግምገማ፦ ያልተነካ ትልቅ ኃይል አለ በሚል በነ ሌተናል ጀኔራል አሰፋ ቸኮል ተገምግሟል። ሰራዊቱ ላይ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኦሕዴድ ብልጽግና ኃይል በአማራ ሕዝብ ላይ የመጨረሻ ያለውን ዘመቻ ቅድመ-ክረምት ዕቅድ በሚል ዝግጅት ላይ ነው።

‘የኦሮሙማ ማሸነፍ በአማራ ሕዝብ ታሪክ ሽንፈት ላይ የተመሰረተ ነው’ ብሎ የሚያምነው የኦሕዴድ ብልጽግና ኃይል የመጨረሻ ያለውን ዘመቻ ቅድመ-ክረምት ዕቅድ በሚል ዝግጅት ላይ ነው። ጠላት ከዚህ ቀደም ወደአማራ ጠቅላይ ግዛቶች ያስገባው ኃይል በከፍተኛ ሁኔታ ተመትቶበታል፡፡ መንገድ መሪና ጥይት ማብረጃ ይሆነኛል ያለው የብአዴን አድማ ብተና፣ ሚሊሻ፣ ፖሊስ፣… እየተናደ የሰው ኃይል ቋቱ ተዳክሟል፡፡ በዚህ በኩል የአማራ ፋኖ የሚያደርስበት ከባድ ምት፤ በዚያ በኩል ደግሞ ከዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ የሚደርስበት ጫና አገዛዙን ረፍት ነስቶታል፡፡ ለስንተኛ ጊዜ እንደሆነ እርግጡን መናገር ባይቻልም አሁንም ‹‹የመጨረሻ ዘመቻ›› ያለውን ክረምቱ ጨርሶ ከመግባቱ በፊት ለዘመቻ ተዘጋጅቷል፡፡ ለዚህ ዘመቻ ከሰኔ 15 እስከ ሰኔ 30 የሚል የአስራ አምስት ቀናት ገደብ አስቅምጧል፡፡ ኦሕዴድ ብልጽግና ‹አለኝ› የሚለውን ኃይሉን እና ትጥቁን ይዞ “የመጨረሻ” የሚለውን ዘመቻ ሲጀምር ከመደበኛ ውጊያ በተጨማሪ የጸረ-ሽምቅ ታክቲኮችን ለመጠቀም እንደተዘጋጀ ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሳት መረጃ ያመለክታል፡፡
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ የተንሰራፋው ሌብነት ልዩ ትኩረት ይሻል!

በየዓመቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከበጀት ረቂቅ በፊት መቅረብ የነበረበት የፌዴራል ዋና ኦዲተር ግኝት ሪፖርት ማክሰኞ ሰኔ 11 ቀን 2016 ዓ.ም. ዘግይቶ ሲቀርብ፣ እንደተለመደው የባለበጀት መንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ የሚስተዋሉ ችግሮች ተዘርዝረዋል፡፡ ከችግሮቹ መካከል ውዝፍ ተሰብሳቢ ገንዘብ መበራከት፣ በመረጃ ዕጦት ትክክለኛነታቸውን ማረጋገጥ ያልተቻለና ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገቡ ሒሳቦች ማጋጠም፣ ከደንብና ከመመርያ ውጪ ያላግባብ ክፍያዎች መፈጸም፣ የግዥ አዋጅና ደንብ ያልተከተሉ ግዥዎች መፈጸማቸው፣ ከሥራ ለተሰናበቱ ሠራተኞች ደመወዝ መክፈል፣ በአማካሪ መሐንዲሶች ሳይረጋገጥ ለግንባታዎች ክፍያ መፈጸምና ሌሎችም በኦዲት ግኝቱ ተካተዋል፡፡ ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎች በርካታ ቢሊዮን ብሮች የባከኑባቸውና የተዝረከረኩባቸው መንግሥታዊ ተቋማት፣ በአገር ላይ ምን ያህል ከባድ ኪሳራ እያስከተሉ እንደሆነ በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡ ምንም እንኳ መሻሻል ያሳዩ ተቋማት ቢኖሩም የብዙዎቹ ችግር ግን አገር እየጎዳ መቀጠሉ እስከ መቼ ያስብላል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በሁሉም የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዘርፎች ውስጥ የተሰገሰገው ሌብነት አደብ እንዲገዛ መደረግ አለበት፡፡ በየዓመቱ በፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የኦዲት ግኝት ሪፖርት ከሚቀርብባቸው ባለበጀት መንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶች ብዙዎቹ፣ ጤነኛ ያልሆነ የፋይናንስና የክዋኔ አፈጻጸም እንዳለባቸው በተደጋጋሚ ስማቸው ይነሳል፡፡ በጣም በተሻለ ደረጃ ላይ መገኘት የሚገባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳይ ደግሞ በእጅጉ አነጋጋሪ ነው፡፡ ይህ ችግር ከፌዴራል አልፎ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የሚንፀባረቅ ሲሆን፣ ጠንከር ያለ ዕርምጃ መወሰድ ቢጀመር ብዙዎቹ የተቋማት ኃላፊዎች ለእስር ይዳረጉ ነበር፡፡ ከሆስፒታሎችና ከክሊኒኮች ግንባታ፣ ከትምህርት ተቋማት ግንባታና ማስፋፊያ፣ ከመንገድና ከሌሎች መሠረተ ልማቶች ግንባታና ዝርጋታ፣ ከሕዝብ አገልግሎት መስጫዎችና ከተለያዩ
Posted in Amharic News, Articles, Ethiopian News

በኢትዮጵያ 17 ሚሊዮን የሚጠጉ ሕፃናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸውን ዩኒሴፍ አስታወቀ

በኢትዮጵያ 17 ሚሊዮን የሚጠጉ ሕፃናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸውን ዩኒሴፍ አስታወቀ ኢትዮጵያ ውስጥ በቅድመ መደበኛ፣ በመጀመሪያ እና 2ኛ ደረጃ ላይ ያሉ17 ሚሊዮን የሚጠጉ ሕፃናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸውን የተመድ የህፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) አስታወቀ። ዩኒሴፍ 3.5 ሚሊዮን የሚገመቱ በአንደኛ ደረጃና በሁለተኛ ደረጃ የሚገኙ ሕፃናት ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ሥጋት መጋለጣቸውንና ይህም ትምህርት ላይ የተጋረጠውን ቀውስ የበለጠ ማባባሱን ገልጿል። በኢትዮጵያ የሚገኘው የዩኒሴፍ ጽ/ቤት፤ መንግሥታት የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ቅድሚያ እንዲሰጥ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ወጪ ቆጣቢ የትምህርት ዝግጅቶችን እንዲያሰናዱ ጥሪ ማድረጉን ዶይቼ ቬለ በዘገባው አመልክቷል።
Posted in Ethiopian News

በአማራ ክልል ጅጋ ከተማ ቢያንስ 18 ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

በአማራ ክልል ጅጋ ከተማ ቢያንስ 18 ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ጅጋ ከተማ፤ ቢያንስ 18 ሰዎች “በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን” አራት የከተማው ነዋሪዎች “ለኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ብሔራዊው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ “በአካባቢው ጥቃት ተፈጽሟል” የሚል መረጃ እንደደረሰው ገልጾ፤ ክስተቱን እያጣራ መሆኑን አስታውቋል። 🔴 የዓይን እማኞቹ፤ የጅጋ ከተማ ነዋሪዎች የተገደሉበት ክስተት የተፈጸመው ከትላንት በስቲያ እሁድ ሰኔ 9፤ 2016 አመሻሽ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። 🔴 በዚሁ ዕለት 11 ሰዓት ተኩል ገደማ፤ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የጫኑ “ሶስት ፓትሮል” ተሽከርካሪዎች ከደንበጫ ወደ ጅጋ ከተማ እየገቡ በነበረበት ወቅት፤ “በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት” ከፊት በነበረው መኪና ላይ ጥቃት ካደረሱ በኋላ መሸሻቸውን የዓይን እማኞቹ አብራርተዋል። 🔴 ጥቃት ከደረሰበት መኪና ኋላ የነበሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፤ በጥቃቱ “የወደቁትን አባሎቻቸውን” እነርሱ በነበሩባቸው ተሽከርካሪዎች ላይ ጭነው መሄዳቸውንም የከተማይቱ ነዋሪዎች ገልጸዋል። ከደቂቃዎች በኋላ “የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች” ወደ መሃል ከተማ በመምጣት፤ በዚያ የነበሩ ሰዎችን ጥይት በመተኮስ መግደላቸውን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” በስልክ ያነጋገረቻቸው የከተማይቱ ነዋሪዎች አስረድተዋል። * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13361/
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በዋግ ኽምራ ዞን በተባባሰው ረኀብ በቢላዛ ቀበሌ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተነገረ

በዋግ ኽምራ ዞን በተባባሰው ረኀብ በቢላዛ ቀበሌ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተነገረ በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን በሰሀላ ሰየምት ወረዳ፣ በ2015/16 የምርት ዘመን የተከሠተው ድርቅ ያስከተለው ረኀብ ጉዳቱ በመባባሱ፣ ባለፈው ሳምንት በቢላዛ ቀበሌ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ቪኦኤ ዘግቧል። የድርቁ ኹኔታም እየከፋ መኾኑን እና ተጨማሪ አምስት ሺሕ እንስሳት መሞታቸውን ሲገለፅ ከ46ሺሕ በላይ ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የቀበሌው አስተዳደር መግለፁን ዘገባው ጠቅሷል። ለተጎጂዎች የርዳታ እህል የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች በጸጥታው ችግር ምክንያት ወደ አካባቢው ለመምጣት ፈቃደኛ አለመሆናቸው፣ እንዲሁም የተሰበረው የተከዜ ድልድይ አለመጠገኑ፣ ችግሩን እንዳባባሰውም ነው የተገለፀው።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ባለፉት 5 ወራት በኢትዮጵያ 50 የሰብዓዊ እርዳታ ሰራተኞች ህይወታቸውን አጥተዋል

” ባለፉት 5 ወራት በኢትዮጵያ 50 የሰብዓዊ እርዳታ ሰራተኞች ህይወታቸውን አጥተዋል ” – የዓለም የምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ባለፉት 5 ወራት 50 የሚሆኑ የሰብዓዊ እርዳታ ሰራተኞች በሰብአዊ አገልግሎት ላይ እያሉ ህይወታቸውን ማጣታቸውን(WFP) ባወጣው ሪፖርት አስታወቀ። ተቋሙ ባወጣው ሪፖርት በሀገሪቱ ያለው የጸጥታ ችግር በተለያዩ አካባቢዎች ለሚያደርገው የሰብአዊ እርዳታ አገልግሎት እንቅስቃሴ ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑን ገልጿል። በቅርቡ የዓለም የምግብ ፕሮግራም አጋር ድርጅት ሹፌር በአማራ ክልል እንደተገደለ ያስታወሰው ተቋሙ ህወታቸውን ያጡ የሰብዓዊ እርዳታ አገልግሎት ሰጪ ሠራተኞች ቁጥር ሃምሳ መድረሱንም ነው የገለፀው።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በ14 መ/ቤቶች 1.7 ቢሊዮን ብር በተከፋይ ሂሳብ ተይዞ ተገኝቷል፤ ለማን እንደሚከፈል እንኳን ተለይቶ አይታወቅም፤ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል።

(ከ2015 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት) ➡️ የበጀት አጠቃቀም ፦ ኦዲት በተደረጉ መስሪያ ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በስራ ላይ ያዋሉት ሂሳብ ሲነጻጸር ከበጀት በላይ ወጪ የተደረገበት ፣ በርካታ ያልተሰራበት በጀት ተገኝቷል። በ20 መ/ቤቶች በልዩ ልዩ የሂሳብ መደቦች በደንቡ መሰረት #ሳያስፈቅዱ ለእያንዳንዱ የበጀት ኮድ ከተደለደለው በላይ ወጪ የሆነ ሂሳብ ከመደበኛው በጀት ብር 524. 7 ሚሊዮን ፣ ከውስጥ ገቢ 288.9 ሚሊዮን ፣ ከካፒታል በጀት 489.4 ሚሊዮን በድምሩ 1.3 ቢሊዮን ብር ተገኝቷል። በኮድ ከተደለደለው በጀት በላይ ውጭ ያደረጉ ዋና ዋና መ/ቤቶች ፦ 🟠 ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 322.5 ሚሊዮን 🟠 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ተጠሪ ተቋማቱ 267.9 ሚሊዮን 🟠 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 173.2 ሚሊዮን 🟠 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ 125.1 ሚሊዮን 🟠 የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት 109.5 ሚሊዮን 🟠 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ 91.3 ሚሊዮን 🟠 አምቦ ዩኒቨርሲቲ 83.3 ሚሊዮን 🟠 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 75.1 ሚሊዮን ሁለት መስሪያ ቤቶች ደግሞ 9.7 ሚሊዮን ብር በጀት ስለመኖሩ ሳይረጋገጥ / ሳይፈቀድ ክፍያ ተፈጽሞ ተገኘቷል። ➡️ ከደንብ እና መመሪያ ውጭ የተከፈለ ፦ በ30 መ/ቤቶች ብር 16 ሚሊዮን 470 ሺህ ከደንብና መመሪያ ውጭ አላግባብ ተከፍሏል። ዋና ዋናዎቹ መ/ቤቶች ፦ 🔴 ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን 🔴 የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት 2 ሚሊዮን 889 ሺህ 🔴 ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2 ሚሊዮን 42 ሺህ 🔴 መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ 1 ሚሊዮን 156 ሺህ ➡️ በመስሪያ ቤት
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በ11 መስሪያ ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ብር ምንም ማስረጃ ሳይኖር ወጪ ተደርጓል።

በ2015 የበጀት ዓመት መ/ቤቶች የተፈቀደላቸውን በጀት በአግባቡ ወጪ ማድረጋቸውን / በአግባቡ መጠቀማቸውን ፣ ተገቢ ማስረጃ መቅረቡንና ሂሳቡ በትክክል መመዝገቡን ለማጣራት ኦዲት ተደርጓል። በዚህም ፥ ምንም አይነት ማስረጃ ሳይቀርብ በወጪ የተመዘገበ ክፍያ / ሂሳብ ተገኝቷል። በ11 መ/ቤቶች 43.5 ሚሊዮን ማስረጃ ሳይኖረው በወጪ ሂሳብ የተመዘገበ ሲሆን ማስረጃም ባለመቅረቡ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ አልተቻለም። ➡️ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 17.4 ሚሊዮን ➡️ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ባለስልጣን 8.7 ሚሊዮን ➡️ የመንገድ ደህንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት 8.7 ሚሊዮን ➡️ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 4.4 ሚሊዮን ➡️ የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት 3.3 ሚሊዮን ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ከዚህ ባለፈ ፤ በወጪ ለተመዘገቡ ክፍያዎች የተሟላ ማስረጃ መቅረቡን ለማረጋገጥ በተደረገው ኦዲት በ 48 መ/ቤቶች የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 44 ሚሊዮን 440 ሺህ በወጪ ተመዝግቦ ተገኝቷል። የተሟላ ማስረጃ ሳይዙ ወጪ ከመዘገቡት መካከል ፦ 🔴 ማዕድን ሚኒስቴር 5 ሚሊዮን 719 ሺህ 🔴 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ 5 ሚሊዮን 716 ሺህ 🔴 የጤና ሚኒስቴር 4 ሚሊዮን 677 ሺህ 🔴 ገንዘብ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን 34 ሺህ 🔴 በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ገዋኔ የግብርና የቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ 2 ሚሊዮን 450 ሺህ 🔴 የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት 2 ሚሊዮን 185 ሺህ ዋና ዋናዎቹ ናቸው። የፌዴራል ኦዲተር መስሪያ ቤት ፤ ማስረጃ ካልቀረበ የሂሳቡን ትክክለኝነት ማረጋገጥ እንደማይቻል ፤ የወጪ ማስረጃ ላልቀረበላቸው ክፍያዎች የወጪ ማስረጃ እንዲቀርብላቸው የማይቀርብላቸው ከሆነ ገንዘቡ ተመላሽ እንዲደረግ አሳስቧል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በኢትዮጵያ 15.8 ሚልየን የምግብ እርዳታ የሚያስፈጋቸው እና 1 ሚልየን የውጭ ስደተኞች ይገኛሉ ተባለ

የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) በኢትዮጵያ እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ለመደገፍ ለሚቀጥሉ ስድስት ወራት 374 ሚልየን ዶላር እንደሚያስፈልገው አስታወቀ። የዓለም የምግብ ፕሮግራም እንደገለጸው ከአጋር ድርጅቶቹ የአንዱ ሾፌር በአማራ ክልል ውስጥ የተገደለ ሲሆን በአጠቃላይ በአገሪቱ እየተካሄዱ የሚገኙ ግጭቶች እና የገንዘብ እጥረት የበርካታ ሰዎችን ስቃይ እያራዘመ ይገኛል። በኢትዮጵያ 15.8 ሚልየን የምግብ እርዳታ የሚያስፈጋቸው ሰዎች መኖራቸውን ያስታወቀው ድርጅቱ፤ በጦርነት፣ በድርቅ እና የጎርፍ አደጋ ሳቢያ የተፈጠረው ቀውስ በአብዛኛው በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ክልሎች ውስጥ እንደሆነ ገልጿል። በተጨማሪም አገሪቱ ከደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ኤርትራ እና ሱዳን የተፈናቀሉ 1 ሚልየን ስድተኞችን እያስተናገደች የሚገኝ ሲሆን ከሱዳን አሁንም ስደት የቀጠለ መሆኑ ተመላክቷል። የዓለም የምግብ ፕሮግራም ባለፉት ስድስት ወራት 2.7 ሚልየን ዜጎችን በእርዳታ ተደራሽ ያደረገ ሲሆን ጦርነት፣ ድርቅ፣ ጎርፍ እና የኑሮ ውድነት በኢትዮጵያ ላለው የምግብ ዋስትና ፈተና ምክንያቶች እንደሆኑ አስታውቋል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ስራቸውን መስራት አልቻሉም

የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ተባብሶ የቀጠለውን በሲቪክ ተቋማት እና ገለልተኛ የአገር ውስጥ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ላይ የሚደርስ ጫና እንዲያቆሙ ዓለም አቀፍ ጥምረት ጠይቋል። አምስት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እንዳሳሰቡት በአካላዊ እና ዲጂታል ክትትል፣ የቃል ትንኮሳ፣ ማስፈራራት እና አስደንጋጭ ምልክት መላክ እንዲሁም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ስራቸውን እንዳይሰሩ መከላከል በአገሪቱ ተፍስፍቷል። “ከቅርብ ወራት ወዲህ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ)ን ጨምሮ በአገሪቱ ውስጥ ባሉ ታዋቂ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ላይ የኢትዮጵያ የደህንነት እና የስለላ ኃይሎች ወከባ እና ማስፈራሪያ ጨምረዋል” ሲሉም ድርጅቶቹ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሚዲያ ባለሙያዎች ስብስብ የሆነው የኢትዮጵያ ፕሬስ ነፃነት ተሟጋቾች ጥምረት በቅርቡ እንዳስታወቀው ከፈረንጆች 2019 ጀምሮ ብቻ 200 የሚደርሱ ጋዜጠኞች የታሰሩ ሲሆን  የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ገለልተኛ ምርመራን እና ትችትን ለማፈን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መሰረታዊ መብቶችን በግልፅ በመጣስ ከፍተኛ እርምጃ ሄደዋል ሲሉ ድርጅቶቹ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በቀልን ሳይፈሩ ሥራቸውን ማከናወን እንዲችሉ መደረግ አለበት ሲሉም አሳስበዋል። የዓለም ጸረ ሰብዓዊ ስቃይ ድርጅት፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ፌዴሬሽን፣ ሂዩማን ራይትስ ዋች፣ ፍሮንት ላይን ዲፌንደርስ እና አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባሉት ድርጅቶች በጋራ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት የተጣለባቸውን የሰብዓዊ መብት ግዴታዎች፣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትን፣ የአፍሪካ የሰብዓዊና ሕዝቦች መብቶች ቻርተርን፣ የስቃይ እና ሌሎች የጭካኔ፣ ኢሰብዓዊ ወይም አዋራጅ ኮንቬንሽንን፣ የሲቪል እና የፖለቲካ ዓለም አቀፍ የመብት ቃል ኪዳንን እና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን የማክበር፣ የመጠበቅ እና የማስከበር
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱ

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱ ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ያቀረቡት ሶስት ጋዜጠኞች ከእስር ተፈቱ። ዛሬ እና ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከእስር የተለቀቁት ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ፣ ቴዎድሮስ ዘርፉ ናቸው። ➡️ ሶስቱ ጋዜጠኞች የፌደራል ፖሊስ “ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ በእስር እንዲቆዩ” ማድረጉን በመጥቀስ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡት ባለፈው ሳምንት ነበር። ➡️ ከአቤቱታ አቅራቢዎች አንዱ የሆነው ጋዜጠኛ በላይ ከእስር የተፈታው፤ ዛሬ ሰኞ ሰኔ 10፤ 2016 ከሰዓት መሆኑን ባለቤቱ በላይነሽ ንጋቱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ➡️ “ኢትዮ ኒውስ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በላይ፤ በህዳር 2016 በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ለሰባት ወራት በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በእስር ላይ ቆይቷል። ጋዜጠኛው ባለፈው ግንቦት ወር አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ መዘዋወሩ ይታወሳል። ➡️ አስር ወራትን በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በእስር ያሳለፈው ሌላኛው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ፤ ባለፈው አርብ ሰኔ 7፤ 2016 ወደ አዲስ አበባ እንዲመጣ ከተደረገ በኋላ በማግስቱ ከእስር መለቀቁን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጿል። ➡️ “ምኒልክ” እና “ዓባይ”በተሰኙ የበይነ መረብ እና የሳተላይት ቴሌቪዥን ቻናሎች ላይ በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ፕሮግራም ያዘጋጅ የነበረው ቴዎድሮስ፤ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፓርላማ ከጸደቀ ከአንድ ሳምንት በኋላ ነበር። 🔴  ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13348/
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አስር አመት ወደኃላ ተመልሶ የሚሰራ ከሕግ ውጪ የሚያስፈፅም ፤ ብልፅግና በግልፅ የሰው ሀብት የሚዘርፍበት አዋጅ

በጥፋተኝነት ላይ ያልተመሠረተ ንብረት የመውረስ ድንጋጌም በአዋጁ ተካቷል አዋጁ የሚፀድቅ ከሆነ 10 ዓመት ወደኃላ ተመልሶ ተፈጻሚ ይሆናል ከውጭ በተላከ ገንዘብ ሀብት አፍርቶ የተላከበትን ደረሰኝ ያላቀረበ ሰው ወይም ሊታወቅ ከሚችል ገቢው በላይ ሀብት አፍርቶ ምንጩ ሕጋዊ መሆኑን ማረጋገጥ ያልቻለ ሰው፣ ንብረት በመንግሥት እንዲወረስ የሚፈቅድ ድንጋጌ የያዘ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ። ረቂቅ አዋጁ ‹‹የንብረት ማስመለስ አዋጅ›› የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፣ ባለፈው ማክሰኞ ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የመጀመሪያ ንባብ ተካሂዶበታል። የረቂቁ ስያሜ ‹‹የንብረት ማስመለስ አዋጅ›› እንዲሆን የተመረጠበት ምክንያት ወንጀል የሚለው ቃል ከገባ ምንጩ ያልታወቀ ሀብትን፣ እንዲሁም ወንጀልን ማቋቋም አስፈላጊ ሳይሆን ሲቀርና በወንጀል ኃላፊነት የማይረጋገጡ ንብረቶች በሚኖሩበት ወቅት ንብረቶችን ለማስመለስ አያስችልም ተብሎ በመታመኑ እንደሆነ ረቂቅ አዋጁን ለማብራራት የቀረበው አባሪ ሰነድ ያስረዳል። የረቂቅ አዋጁ ድንጋጌዎችና አባሪ የተደረገው ማብራሪያ ሰነድ እንደሚያስረዱትም፣ መንግሥት ንብረትን ለማስመለስ ሲል በሦስት ዋና ዋና መንገዶች ንብረቶችን ሊወርስ ይችላል። እነዚህም መንገዶች፣ ‹‹ምንጩ ያልታወቀ ንብረት መውረስ››፣ ‹‹በጥፋተኝነት ላይ ያልተመሠረተ መውረስ›› እና ‹‹በጥፋተኝነት ላይ የተመሠረተ›› መውረስ ናቸው። በረቂቅ አዋጁ ድንጋጌ መሠረት፣ ማንኛውም ሰው ምንጩ ያልታወቀ ንብረት አፍርቷል ተብሎ ንብረቱ ሊወረስ የሚችለው፣ ግለሰቡ ያለው ንብረት ወይም የኑሮ ደረጃው አሁን ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት ሥራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ሕጋዊ ገቢ ጋር የማይመጣጠን ሲሆንና የንብረቱን ወይም የኑሮ ደረጃውን ምንጭ በተመለከተ ምክንያታዊ የሆነ የወንጀል ጥርጣሬ ሲኖር
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አንዳንዴ ሠራተኞች ቢሮ መጥተው ያለቅሱብናል ፤ ምሳ የምንበላበት የለም በማለት በግልጽ ይናገራሉ !!

” አንዳንዴ ሠራተኞች ቢሮ መጥተው ያለቅሱብናል ፤ ‘ ምሳ የምንበላበት የለም ‘ በማለት በግልጽ ይናገራሉ !! ” በ2010 ዓ/ም ተሻሽሎ ወደ ሥራ ገበቶ የነበረው ባለ 106 አንቀጽ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ፣ ከ6 ዓመታት አገልግሎት በኋላ፣ በ160 አንቀጾች ተዋቅሮ በረቂቅ አዋጁ ላይ ውይይት እየተደረገበት ነው። ምን አስተያየት ተሰጠ ? በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ የሰው ሀብት ሥራ አመራር ድጋፍና ክትትል ቡድን መሪ አቶ አብርሃም ደግፌ ፦ ” በከተማ አስተዳደሩ 70 ያህል የመንግሥት ተቋማት ላይ ክትትል እናገደርጋለን ፤ የሠራተኛው ሕይወት እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ላይ ይገኛል። በከተማ አስተዳድሩ አንድ ከፍተኛ የሚባል ባለሙያ ያልተጣራ ደመወዙ 9,056 ብር ነው። ከዚህ ግብር ተከፍሎበት በእጁ የሚደርሰውን ገንዘብ አስልታችሁ ድረሱበት። በዚህ ደመወዝ የቤት ኪራይ የከተማዋ ጫፍ እንኳ ቢኬድ 10,000 ብር ደርሷል።ነገር ግን ይህ ከፍተኛ ባለሙያ ሙሉ ደመወዙን ለቤት ኪራይ ላድርግ ቢል ገንዘቡ አይበቃውም። በዚህ ሁኔታ ላይ ያለ አንድ ሠራተኛ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ይቻላል ወይ?  ተፈጥሯዊ ሁኔታውስ በራሱ ይፈቅድለታል ወይ ? ይህ ችግር ደመወዝ በመጨመርም ይፈታል ብዬ አላስብም። በሌሎች አማራጮች ሰራተኛ እንዲጠቀም ቢደረግ ችግሩ ሊቀል ይችላል እንጂ 2,000 ብር ቢጨመር እንኳን ሕይወቱ ላይ ለውጥ አያመጣም። በዚህም የተነሳ ሠራተኞች አንዳንዴ ቢሮ መጥተው ያለቅሱብናል፣ ምሳ  የምንበላበት የለም በማለት በግልጽ ይናገራሉ። ገንዘብ አልበቃቸው ያሉ የመንግሥት ሠራተኞች ደግሞ በምሳ ሰዓት ወደ ቤተ እምነቶች ሄደው ያሳልፋሉ። የመንግሥት ሠራተኛው ታማኝ
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የውጭ አገር ዜጎች በሕገ ወጥ መንገድ ቢሮ ከፍተው እየሰሩ መሆኑ አደጋ ፈጥሮብኛል ሲል አባይ የጥበቃ አሰሪዎች ማህበር ገለጸ

የውጭ አገር ዜጎች በሕገ ወጥ መንገድ ቢሮ ከፍተው እየሰሩ መሆኑ አደጋ ፈጥሮብኛል ሲል አባይ የጥበቃ አሰሪዎች ማህበር ገለጸ በጥበቃ ስራ ላይ የውጭ አገር ዜጎች መሰማራታቸው በስራችን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እና አደጋ እየፈጠረ ነው ሲል አባይ የጥበቃ አሰሪዎች ማህበር ቅሬታውን ገለጸ። ከ31 በላይ አባላት ያሉት አባይ የጥበቃ አሰሪዎች ማህበር ከ21 ሺ በላይ ሰራኞችን ደግሞ በጥበቃ፣በጽዳት እና በቢሮ አስተዳደር ስራዎች ላይ አሰማርቶ የሚገኝ ሲሆን ላለፉት ስድስት ወራት ክትትል ያደረገበትን የዘርፉ ሕገ ወጥ ድርጊት በመግለጫ አስታውቋል። ለተጨማሪ ንባብ፡ https://addismaleda.com/archives/38167
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢሚግሬሽን አዋጅ ማሻሻያ፤ “የፍርድ ቤትን መሰረታዊ ስልጣን የሚወስድ ነው” በሚል ተተቸ

የኢሚግሬሽን አዋጅ ማሻሻያ፤ “የፍርድ ቤትን መሰረታዊ ስልጣን የሚወስድ ነው” በሚል ተተቸ ዜጎች ከሀገር እንዳይወጡ የማገድ ስልጣንን ለኢሚግሬሽን መስሪያ ቤት ኃላፊ የሚሰጠው የአዋጅ ማሻሻያ፤ “የፍርድ ቤትን መሰረታዊ ስልጣን የሚወስድ ነው” በሚል ተተቸ። ማሻሻያው “ከኢሚግሬሽን ተልዕኮ እና ባህሪ የሚመነጩ ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ እንጂ”፤ ፍርድ ቤት የሚያከውናቸውን ስራዎች “ደርቦ ለመስራት በማሰብ” የቀረበ እንዳልሆነ የመስሪያ ቤቱ አመራሮች ገልጸዋል። ▶️ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤት አመራሮች ይህን የገለጹት፤ ትላንት አርብ ሰኔ 7፤ 2016 በተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደ ይፋዊ የህዝብ ውይይት ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ነው። ▶️ የምክር ቤቱ የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በጠራው በዚህ  ውይይት፤ ከሁለት ሳምንት በፊት ለፓርላማ በቀረቡ ሶስት የአዋጅ ረቂቆች ላይ የህዝብ ጥያቄ እና አስተያየቶች ተስተናግደዋል። ▶️ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህግ ጥናትና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አሮን ደጎል፤ “ከዚህ በፊት የነበረው ድንጋጌ፤ ማንኛውም ሰው ከኢትዮጵያ እንዳይወጣ ሊታገድ የሚችለው ወይ የመዘዋወር መብቱ ሊገደብ የሚችለው በፍርድ ቤት እና በፍርድ ቤት ውሳኔ ብቻ [ነበር] የሚለው” ሲሉ አስታውሰዋል። ለፓርላማ በቀረበው የአዋጅ ማሻሻያ ላይ ግን “የፍርድ ቤትን መሠረታዊ ስልጣን የመውሰድ አካሄድ ነው የሚታየው” ሲሉ ተችተዋል። ▶️ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከልን የወከሉት አቶ ኖህ የሱፍ የተባሉ ተሳታፊ፤ “አዋጁ የህግ የበላይነትን በህግ የመገደብ አካሄድ ያለው ይመስላል” ሲሉ ተደምጠዋል። 🔴 ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13339/
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በጉራጌ ዞን የአማራ ገበሬዎችን ትጥቅ በማስፈታት በሸኔ ታጣቂዎች የማስጠቃት ዕቅድ አለ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ የአማራ ገበሬዎችን ትጥቅ በማስፈታት በሸኔ ታጣቂዎች የማስጠቃት ዕቅድ አለ ተባለ። እስከ ሰኔ 13 ቀን በፍቃደኝነት አሰረክቡ ካላሰረከባቹህ እየረሸንን እንወሰዳለን ያሉት ባለስልጣናት የሚከተሉት ናቸው ተብሏል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ተመስገን ካሳ የክልሉ ፐሊስ ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ የዞኑ ሰላምና ፀጥታ የህያ ሱልጣን የወረዳው አሰተዳዳሪ ካሱ ጁሃር የወረዳው ፀጥታ ኃላፊ ፀጋዬ አምድሳ የዳርጌ ቀበሌ ሊ/ር ከበደ ገብሬ ከንቲባው አለምዬ ኪታባ ድርጊቱ በዐማራው ላይ የሚፈፀመውን የዘር ማጥፋት በመንግሥት መዋቅር ለመተግበሩ ማሣያ ነው። ለጉዳዩ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትኩረት እንዲሰጠው የአካባቢው ነዋሪዎች ጠይቀዋል። መረጃው የ በለጠ ካሳ ነው።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

” በምዕራብ ወለጋ ዞን የወባ በሽታ ተባብሷል ” – ነዋሪዎች

” በምዕራብ ወለጋ ዞን የወባ በሽታ ተባብሷል ” – ነዋሪዎች ” ባለፉት 10 ወራት በዞኑ ደረጃ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወባ ተይዘዋል ” – የምዕራብ ወለጋ ዞን ጤና መምሪያ በምዕራብ ወለጋ የወባ በሽታ ስርጭት መጨመሩን እና ባለፈው ሳምንት ብቻ በዞኑ 19ሺ ሰዎች በበሽታው ተይዘው 11 ሰዎች መሞታቸው ተገለፀ። በዞኑ ቆንዳላ እና ጌንጂ አካባቢዎች የወባ በሽታ ስርጭት መጨመሩን በበሽታው ቤተሰቦቻቸውን የተነጠቁ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በዞኑ የወባ በሽታ ዝናብ በመጣሉ ስርጭቱ በጣም እየጨመረ ነው ተብሏል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ባለሙያ ባለፈው ሳምንት ገንጂ ወረዳ ውስጥ በምትገኘው ላሊሳ ዲቤ መንደር ሰባት ሰዎች በወባ በሽታ መሞታቸውን ገልጸዋል። በዞኑ ገንጂ፣ ቢቂልቱ ኡምባኦ እና ላሊሳ ዲቤ የተባሉ አካባቢዎች በብዛት የተጠቁ መሆናቸውንም አስረድተዋል። የምዕራብ ወለጋ ዞኑ ጤና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው ሆስፒታሎች በአሁኑ ጊዜ በቀን ብዙ ሰዎችን እያስተናገዱ እንደሆነ ጠቁመዋል በዞኑ በሳምንት ከ10ሺ እስከ 20ሺ ሰው በበሽታው እየተያዘ መሆኑንም የገለፁት ኃላፊው ባለፉት 10 ወራት በዞን ደረጃ 5 መቶ 19ሺ የሚደርሱ ሰዎች በወባ በሽታ መያዛቸውንም ጨምረው ገልፀዋል። በእነዚህ አካባቢዎች ለወባ በሽታ ተጋላጭ የሆኑ ነዋሪዎች በበሽታው ምክንያት ስጋት እንዳደረባቸው በመግለፅ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገቢው እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቀዋል።  መረጃው ከአዲስ ስታንዳርድ እና ዶይቼ ቬለ ነው።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ምዕራብ ሸዋ ዞን የዐማራ መሬት እየተነጠቀ ነው።

ምዕራብ ሸዋ ዞን ናኖ ወረዳ መዳሎና ኖኖ ጉድና(ሀዳድ8) ቀበሌዎች የዐማራ መሬት እየተነጠቀ ነው። የወረዳው አመራሮች መሬሬት መንጠቃቸውን ተከትሎ በተነሳ ግጭት በሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል። ሰኔ 8/2016 ዓ.ም የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ከቄሮዎች ጋር በመሆን የዐማራውን መኖሪያ መንደሮች በእሳት እያቃጠሉ ነው። ዐማሬው አርሶ አደር አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ በሚል አሰቃቂ ግዲያ እየተፈጸመ ነው። በመኖሪያ ቤቶች ውስጥ ሕፃናት እንዳይወጡ ተደርገው እየተቃጠሉ ነው። ወደ እሳት የተወረወሩ ሕፃናትም አሉ ተብሏል። መረጃው የ በለጠ ካሳ ነው።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአብይ አገዛዝ በአንድ ዓመት ዉስጥ ለ 3ኛ ጊዜ የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ እና የዶ/ር ፍሰሃ እሸቱ የባንክ አካዉንቶች እንዲታገድ አደረገ

የአብይ መንግስት የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ የባንክ አካዉንት እንዲታገድ አደረገ የዚህ ድርጅት ሁኔታ እና አሰራር እስከሚታወቅ መንግስት የወሰደው እርምጃ ትክክለኛ ይመስለኛል። ፟  ጋዜጠኛ ኤሊያስ መሰረት ተቋሙ በምን ምንክንያት እንደሆነ በማናዉቅበት ምክንያት በአንድ ዓመት ዉስጥ ለ 3ኛ ጊዜ የባንክ አካዉንቱ ሙሉ በሙሉ እንዲታገድ መደረጉን አስታዉቋል ። ፐርፐዝ ብላክ ባለፉት ሳምንታት ተቋሙን ህልዉና ዉስጥ የሚከተዉ ችግሮች እንደገጠመው አስታዉቋል። ላለፉት ሶስት ሳምንታት የተቋሙ አካዉንት ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ ከመደረጉ በተጨማሪ የዋና ስራ አስፈጻሚዉ ፍስሃ እሸቱ ( ዶ/ር) አካዉንት ጨምር ተመሳሳይ እጣ ፈንታ መድረሱ ተገልጿል። ደመወዝ መክፈል የማንችልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው የቢሮ ኪራይን ጨምሮ የፕሮጀክቶች ስራዎች እንዲቆሙ መደረጉ ስራ አስፈፃሚው በሰጠዉ መግለጫ ገልጿል ። ከ20 ሺህ በላይ ባለአክሲዮኖች እንዳሉት እና ከ 1 ሺህ በላይ ቋሚ ሰራተኞች ያሉት ተቋሙ አሁን ላይ ካፒታሉ 2.4 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታዉቋል ። ጋዜጠኛ ኤሊያስ መሰረት በዚህ ጉዳይ ላይ በሰጠው አስተያየት ድርጅቱ አንድ ግዜ ሜክሲኮ ላይ በ1.5 ሚልዮን ብር አፓርትመንት ልንሸጥ ነው፣ ሌላ ግዜ ደግሞ የአክሲዮን ሽያጭ ውል እንጂ የአፓርትመንት ሽያጭ አይደለም ሲል ገዢዎችን “ይሄን ነገር ቆም ብላችሁ አስቡበት” ብለን ነበር የዚህ ድርጅት ሁኔታ እና አሰራር እስከሚታወቅ መንግስት የወሰደው እርምጃ ትክክለኛ ይመስለኛል። አሁን ትኩረት ሊሆን የሚገባው ከ20 ሺህ በላይ ባለአክሲዮኖች ገንዘባቸው አስፈላጊ በሆነው ሁኔታ ሊያገኙ ወይም ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን ሁኔታ ማመቻቸት ነው።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የመንግስት የልማት ድርጅቶች ከንግድ ባንክ ተበድረው ያልከፈሉት 900 ቢሊየን ብር ገንዘብ ሚኒስቴር እንዲወርስ ታዘዘ

ላለፉት በርካታ አመታት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ከመንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተበድረው ያልከፈሉት 900 ቢሊየን የሚሆን ብርን የገንዘብ ሚኒስቴር እንዲወርስ መወሰኑን ዋዜማ ከሁነኛ ምንጮቿ ሰምታለች። ዝርዝሩን ያንብቡት- https://tinyurl.com/zb3wr5p6
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያ መንግስት በፈጸማቸው የድሮን ጥቃቶች 248 ንጹሃን ተገድለዋል – ተመድ

በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ከተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች 70 በመቶዎቹ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች መፈጸማቸውንም ድርጅቱ ገልጿል ተመድ መንግስት በአማራ ክልል የጣለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አለማራዘሙን እደግፋሁ ብሏል በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ከተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች 70 በመቶዎቹ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች መፈጸማቸው ተገለጸ፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በኢትዮጵያ ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የተመድ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ቮልከር ቱርክ በኢትዮጵያ እየተፈጸመ ያሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የሀገሪቱን ሰላም እና አንድነት እያናጉ ነው ብለዋል፡፡ “ሁሉም ተፋላሚዎች ውጊያ እንዲያቆሙ እጠይቃለሁ” ያሉት ኮሚሽነሩ ልዩነቶቻቸውን በውይይት እንዲፈቱም አሳስበዋል፡፡ ተፋላሚ ወገኖች ንጹሃንን ከማንኛውም ጥቃት የመጠበቅ ሀላፊነት እንዳለባቸው፣ ይህን የተላለፉት ወደ ህግ ቀርበው ተገቢውን ቅጣት ማግኘት እንዳለባቸውም አክለዋል፡፡ አሁን እየተፈጸሙ ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ባሳለፍነው ዓመት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር ከግማሽ በላይ እንደጨመረም በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡ መንግስት ካሳለፍነው ነሀሴ እስከ ታህሳስ ባሉት አምስት ወራት ውስጥ በፈጸማቸው የድሮን ጥቃቶች ምክንያት 248 ንጹሃን ሰዎች ተገድለዋል ያለው የተመድ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ሪፖርት እንደ ትምህርት ቤቶች እና ሆስፒታሎች አይነት የህዝብ መገልገያ ተቋማት ወድመዋልም ብሏል፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ 594 የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደተፈጸሙ የተገለጸ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 70 በመቶ ያህሉ በመንግስት 22 ከመቶ አካባቢ ደግሞ በግጭቱ ተሳታፊዎች እንደተፈጸሙ ተገልጿል፡፡ ኮሚሽኑ በሪፖርቱ ላይ አክሎም የፋኖ ታጣቂዎች 52 ንጹሃንን እንደገደሉ የገለጸ ሲሆን የግለሰቦችን ንብረት ጨምሮ የህክምና ባለሙያዎችን፣ ተቋማትን እና የመንግስት ተቋማት ሃላፊዎችን
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኢሰመኮ በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶች ያሳስቡኛል አለ

ኢሰመኮ እንደገለጸው ይህ ግጭት የተከሰተው ሁለቱ ክልሎች ባለፈው ሚያዝያ ወር የተኩስ አቁም ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ነው ኢሰመኮ የፌዴራል ባለስጣናት ጥረት አድርገው ግጭት እንዲያስቆሙ ጥሪ አድርጓል ኢሰመኮ በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶች ያሳስቡኛል አለ። በአፋር እና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ ቦታዎች ላይ የትጥቅ ግጭቶች፣ የንጹሃን ሞት እና መፈናቀል መኖሩን የሚያሳዩ ሪፖርቶች እንደሚያሳስቡት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጿል። ኢሰመኮ እንደገለጸው ይህ ግጭት የተከሰተው ሁለቱ ክልሎች ባለፈው ሚያዝያ ወር የተኩስ አቁም ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ነው። የንጹሃን ሞትን እና በግል እና በህዝብ ንብረት ላይ የደረሱ ውድመቶችን የተመለከቱ ቅሬታዎች እና ሪፖርቶች እየደረሱት መሆኑን የገለጸው ኢሰመኮ ከሳምንት በፊት ወደ ትጥቅ ግጭት ያመራው ውጥረት እየተባባሰ ነው ብሏል። ኢሰመኮ በሁለቱ ክልሎች የጸጥታ ኃይሎች መካከል ግጭት መፈጠሩን እና በንጹሃን ላይ ጉዳት መድረሱን የክልሎቹ የጸጥታ እና የአስተዳደር ባለስልጣናት እንዳረጋገጡለት ገልጿል። ከዚህ በፊት በሁለቱ ክለሎች አዋሳኝ ቦታዎች በተቀሰቀሱ ግጭት በሁለቱም በኩል የሰው ህይወት ጠፍቷል፤ ንብረት ወድሟል። ኢሰመኮ በመግለጫው በፌደራል የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት አማካኝነት ባለፈው ሚያዝያ ወር የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ ክልሎቹ የቆዩ ችግሮችን ለለፍታት ላደረጉት ጥረት እውቅና እንደሚሰጥም ገልጿል። የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መለሰ የፌዴራል ባለስጣናት ጥረት አድርገው ግጭት እንዲያስቆሙ ጥሪ አድርገዋል። የፌደራል መንግስት በሁለቱ ክልሎች መካከል ተፈጥሯል ስለተባለው ግጭት እስካሁን በይፋ ያለው የለም። በኢትዮጵያ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉት ግጭቶችም እንደቀጠሉ ናቸው።
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በራያ አለማጣ ወረዳ የዋጃ እና ጥሙጋ አካባቢዎች ነዋሪዎች የሕወሐት ኃይሎች ጥቃት እያደረሱብን ነው አሉ

አማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በራያ አለማጣ ወረዳ የዋጃ እና ጥሙጋ አካባቢዎች ነዋሪዎች የሕወሐት ኃይሎች እያደረሱብን ነው ያሉትን ጥቃት በመቃወም ትናንት የአደባባይ ሰልፍ ማድረጋቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል። ሰልፈኞቹ የሕወሃት ታጣቂ ኃይሎች ከራያ ወረዳዎች ባስቸኳይ ለቀው እንዲወጡና ፌደራል መንግሥቱም ሕግ እንዲያስከብር መጠየቃቸውን አስተዳደር ባሠራጨው መረጃ ገልጧል። የዞኑ አስተዳደር፣ ሰልፈኞቹ ሕወሃት በድጋሚ ሕጋዊ ፓርቲ ኾኖ እንዳይመዘገብ፣ ፌደራል መንግሥቱ የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት እንዲያከበር የሚጠይቁና የራያ ሕዝብ በማንነቱ አማራ መኾኑን የሚገልጹ መፈክሮችን አሰምተዋል ብሏል።
Posted in Ethiopian News

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በ”ማንነት ተኮር” ጥቃት ከ20 በላይ ንጹሃን ተገደሉ

ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው አማጺ ቡድን በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ግራር ጃርሶ ወረዳ ግንቦት 25 ፈጸመው በተባለ “ማንነት ተኮር” ጥቃት ከ20 በላይ ንጹሃን እንደተገደሉ ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። በክልሉ የተለያዩ ዞኖች ሰሞኑን በመንግሥት ወታደሮችና አማጺው ቡድን መካከል ተከታታይ ውጊያዎች እየተካሄዱ ስለመኾኑ ዋዜማ ከምንጮቿ ተረድታለች። በቄለም ወለጋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከፍተኛ ውጊያ እየተካሄደ መኾኑን፣ ነዋሪዎችም ከቤት ለመውጣት እንደተቸገሩና ውጊያው በተለይ የመከላከያ ሠራዊት ካምፕ በሚገኝበት ሰዮ ወረዳ እየተካሄደ እንደኾነ ተናግረዋል። በምስራቅ ወለጋ ዞን ቢሎ ቦሼ፣ ሌቃ ዱለቻ እና ኑኑ ቁምባስን ወረዳዎችም በተለይ የመከላከያ ሠራዊት ካምፖች በሚገኙባቸው ጅማቴ እና አዳሚን በተባሉ አካባቢዎች ከባድ ውጊያዎች እየተካሄዱ እንደኾነ ተሰምቷል። በምዕራብ ሸዋ ዞን ግንደበረትና ጀልዱ ወረዳዎች እንዲኹም በሰሜን ሸዋ፣ በጉጂ፣ በምሥራቅ ሸዋና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞኖች የተለያዩ ወረዳዎች ግጭት ሲካሄድ መሰንበቱ ታውቋል።
Posted in Amharic News, Ethiopian News