” ለምሳሌ የካ ክፍለ ከተማ ወደ 100 የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን በማስረጃዎች አረጋግጠናል፤ ወደ ቦሌ ወደ 200 የሚሆኑ አሉ ” – ድርጅቱ
” ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ ” የመብት ተሟጋች የተሰኘው ድርጅት፣ ” የትግራይ ተወላጆች በአዲስ አበባ በዘፈቀደ እየታሰሩ ነው ” ሲል ለቲካቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ስለእስሩ በተጨባጭ ያላችሁ መረጃ ምንድን ነው ? ብለን የጠየቅናቸው የድርጅቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ መብሪሂ ብርሃነ፣ ” በባለፉት ሁለት፣ ሦስት ሳምንታት ያለየፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ ያለበቂ ጥርጣሬ ሰዎች በማንነታቸው ብቻ እየታሰሩ ስለሆነ ይህን መሠረት አድረገን ክትትል ስናደርግ ቆይተናል ” ብለዋል።
” ከክትትል ባለፈ ደግሞ ተጨባጭ ማስረጃ ካገኘን በኋላ እና ታስረው የወጡት፣ የታሳሪ ቤተሰቦችና ጓደኞችን ከጠየቅን በኋላ ሪፖርት አውጥተናል ” ብለው፣ ” ሰዎች ከሕግ ውጪ ሲታሰሩ ብቻ ሳይሆን ያለበቂ ጥርጣሬ ታስረው ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ሲቀር ይሄ የዘፈቀደ እስር ነው ” ሲሉ ወንጅለዋል።
” ሰዎች ሊታሰሩ ይችላሉ። ግን ሕግ ቢተላለፉ እንኳ ወደ ፍርድ ቤት ነው እንጂ የሚቀርቡት ከ48 ሰዓታት በላይ ፓሊስ አስሮ ማቆየት አይችልም በወንጀል እንኳ የተጠረጠረውን። እነዚህ ግን የወንጀል ጥርጣሬም የላቸውም፣ ለምን እንደታሰሩም አይነገራቸውም ” ነው ያሉት።
እስራቱ ከምን ጋር የተያያዘ እንደሆነ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ” እስሮች በየጊዜው ይፈጸማሉ አሁን በትግራይ ተወላጆች ትኩረቱን አደረገ እንጂ፤ ከዚህ በፊትም ማንነት ተኮር እስሮች አሉ። ምክንያቱን አሳሪዎቹ ናቸው የሚያውቁት ” ብለዋል።
” አንድ ሰው ከታሰረ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት እንጂ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የኒው ዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቅርቡ በካሕናት አባቶች ላይ የደረሰውን ግድያ አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት …. አብይ አሕመድን አውግዘው ለሕዝቡ አስቸኳይ ጥሪ አስተላልፈዋል ። ….. #MerejaTv ….@mohammed_meaza… pic.twitter.com/CqoXi1PHL5
— Mereja TV (@merejatv) June 30, 2025
በአማራ ክልል ከጎንደር መተማ መንገድ ላይ “መቃ” በተባለች ሥፍራ የቅማንት ታጣቂዎች ሰኞ’ለት በፈጸሙት ጥቃት 16 አሽከርካሪዎች ተገድለው በርካቶች መቁሰላቸውን ታውቋል። በቅማንት ታጣቂዎች ከተገደሉት ሾፌሮች በተጨማሪ ተሳፋሪዎችና በርካታ አሽከርካሪዎች ታፍነው መወሰዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል። አብዛኞቹ አሽከርካሪዎች የተገደሉት፣ ከጥቃቱ ለማምለጥ ጥረት በማድረግ ላይ ሳሉ በእሩምታ ተኩስ እንደኾነ ተነግሯል። የፋኖ ታጣቂዎች በመተማ ወረዳ ከቅማንት ብሄረሰብ ታጣቂዎች ዘረፋ ለማስቆም የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ምንጮች ተናግረዋል። የቅማንት ታጣቂዎች በአብይ አሕመድ ድጋፍ እየተደረገላቸው በዘረፋ እና እገታ ላይ መሰማራታቸው የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
የኢትዮጵያ የባንክ አገልግሎት ለውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች በይፋ መከፈቱን ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ
ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያውያን ባለሃብቶች ብቻ ሲካሄድ የቆየው የባንክ ስራ አገልግሎት፤ ከዛሬ ጀምሮ ለውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች በይፋ መከፈቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። በዘርፉ መሰማራት የሚፈልጉ የውጪ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች ከዛሬ ጀምሮ ማመልከቻዎቻቸውን ለብሔራዊ ባንክ ማስገባት እንደሚችሉም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
አቶ ማሞ ምህረቱ በገዢነት የሚመሩት ብሔራዊ ባንክ ይህን ያስታወቀው፤ የውጭ ባለሃብቶች የባንክ ስራ ፈቃድ ለማግኘት እና ለማሳደስ የሚያስችላቸውን መመሪያ ይፋ ባደረገበት መግለጫ ነው። አዲሱ መመሪያ የውጭ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የውክልና ጽህፈት ቤት ለመክፈት ማሟላት የሚያስፈልጋቸውን ቅድመ-ሁኔታዎችም ይዘረዝራል።
መመሪያው ብሔራዊ ባንክ ባለፈው ዓመት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ያደረገው “ሰፊ ምክክር” ውጤት እንደሆነ የመስሪያ ቤቱ መግለጫ አመልክቷል። የኢትዮጵያ መንግስት ለውጪ ባንኮች እና ለኢንቨስተሮች ተዘግቶ የቆየውን የባንክ ስራ ዘርፍ ለመክፈት ዝግጅት ሲያደርግ ከቆየ በኋላ ወደ ተግባር የገባው ከሶስት ዓመት በፊት ነበር።
🔴ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16188/