Home › View all posts by EthiopianReporter.com
Blog Archives
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ትግል በሕግ አምላክ ይላል
በገነት ዓለሙ
የአገራችንን ሰላም፣ የመላውን ዓለም ሰላም ጭምር የሚፈታተነውና አደጋ ላይ የጣለው ልዩ ልዩነታችን በጭራሽ አይደለም፡፡ ሕመማችን፣ ጠንቀኛው በሽታችን ራሱ ልዩ ልዩነታችን ቢሆን ኖሮማ የዓለም…
https://www.ethiopianreporter.com/128814/
ኢኮኖሚው ኢትዮጵያን እንዳያፈርሳት ያሠጋል
በጌታቸው አስፋው ኢትዮጵያን እንዳያፈርሱ የሚያሠጉኝ አንድ ሁለት ብዬ ልቆጥራቸው የምችላቸው ከሃያ በላይ የሚሆኑ ዋና ዋና የኢኮኖሚ አደጋዎች አሉ፡፡ ለጊዜው የግራ ቀኙን ጥቅምና ጉዳት ተመልክቼና መርምሬ…
https://www.ethiopianreporter.com/128817/
ሰው መሆን ምንድን ነው? ቅርስና ማኅበራዊ ፍትሕ
በሱራፌል ወንድሙ (ዶ/ር)
ዳራ ከጎራዎች፣ ከመፈራረጅ፣ ነገሮችን ከማቅለልና ከጊዜያዊ ማለባበስ ወጥተን ስለሕዝቦቻችን የተሻሉና ዘለቄታዊ ሕይወቶች ስንል በወግና በሀቅ ለመመካከር ነው ሐሳቤን የምሰነዝረው። “ለልማት” የተባለውም ለጥፋት እንዳይሆን።…
https://www.ethiopianreporter.com/128815/
ሰሞኑን በራያና አካባቢው እንደገና ያገረሸው ግጭት አስቸኳይ መፍትሔ ካልተሰጠው፣ አድማሱ ሰፍቶ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚደርስ አያጠራጥርም፡፡ በራያ በኩል የተጀመረው ትንኮሳ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ተዛምቶ ተጨማሪ ጥፋት ከመድረሱ በፊት መፍትሔ ይፈለግ፡፡ የአማራና የትግራይ ክልሎች የሚወዛገቡባቸው የወልቃይትና የራያ አካባቢዎች፣ ከዚህ በፊት ለሁለት ዓመታት የተካሄደውን አውዳሚ ጦርነት የሚያስንቅ ጥፋት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ሕጋዊ፣ ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ መፍትሔዎች በአማራጭነት ቀርበው ንግግርና ድርድር ማድረግ ካልተቻለ ደም መፋሰሱ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ከሰሞኑ በራያ በኩል በተከሰተ ግጭት ምክንያት በአላማጣ ከተማና በአካባቢው ሰዎች መገደላቸው፣ ነዋሪዎችም ሕይወታቸውን ለማትረፍ በብዛት መሸሻቸው ተሰምቷል፡፡ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ከተካሄደው ጦርነት ያላገገመው ይህ አካባቢ፣ እንደገና ሌላ ዙር ግጭት አገርሽቶ ዜጎች ሲገደሉና ከመኖሪያቸው በገፍ ሲፈናቀሉ ያስደነግጣል፡፡
በተደጋጋሚ ለመግለጽ እንደተሞከረው በአራቱም ማዕዘናት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጦርነት አንገፍግፏቸዋል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች በሚዘጋጁ የውይይት መድረኮችም ሆነ የመገናኛ ዘዴዎች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሰላም ያለህ እያለ እየጮኸ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ በተደጋጋሚ ግጭቶች በሚካሄዱባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ወገኖች ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እየተማፀኑ ነው፡፡ በአማራ፣ በትግራይና በአፋር ክልሎች የተካሄደው አውዳሚው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን ሕይወት መቅጠፉ በተደጋጋሚ ሲነገር ተሰምቷል፡፡ ሕይወታቸው ከዚያ መአት ውስጥ የተረፈ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ለአካላዊና ለሥነ ልቦናዊ ጉዳት ከመዳረጋቸው በተጨማሪ፣ የሚቀምሱት አጥተው የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ እየተለመነላቸው ነው፡፡ ዕርዳታው በበቂ መጠን ባለመገኘቱም ብዙዎቹ በከፍተኛ ችግር ውስጥ ነው ያሉት፡፡ ከመኖሪያ ቀዬአቸው ተፈናቅለው በየመጠለያው የወደቁ ቁጥራቸው በርካታ ነው፡፡ እነዚህ ወገኖች እንደገና አዲስ ጦርነት ሲጀመርባቸው ያሳቅቃል፡፡
‹‹ሐሳብ ማቅረብ ባልተገባ መንገድ የሚያስበይን ከሆነ እንደ አገር በአጠቃላይ የሳትነው ነገር አለ ብዬ እገምታለሁ›› ደስታ ጥላሁን፣ የኢሕአፓና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ
ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ‹‹እርስዎ ንጉሥ ነዎት ወይስ ጠቅላይ ሚኒስትር?›› የሚል ጥያቄ እንዳቀረበች በሰፊው ሲወራ ሰንብቷል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ያደረጉት የቅርቡ የግማሽ ቀን ውይይት በአንድ ሰዓት ከ40 ደቂቃ ተመጥኖ በመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ብቻ በመተላለፉ፣ እሷን ጨምሮ ጠያቂ ፖለቲከኞች ለዓብይ (ዶ/ር) ያነሱትን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ለማወቅ ከባድ ነበር፡፡ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃንና ማኅበራዊ ዓምዶች ወጣቷ ፖለቲከኛ ደስታ ጥላሁን ጠቅላይ ሚኒስትሩን አፋጠጠች እየተባለ ስለሚነገረውም ሆነ፣ በውይይቱ ወቅት ስለገጠማት ነገር በተመለከተ ሰፊ ቆይታ ከሪፖርተር ጋር አድርጋለች፡፡ ከዚህ ቀደም የሪፖርተር ቆይታ ዓምድ እንግዳ የነበረችው የኢሕአፓና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ የሆነቸው ደስታ፣ ከዚህ በተጨማሪም ወቅታዊ አገራዊ የፖለቲካ ጉዳዮችን በተመለከተ ለተነሱላት ጥያቄዎችም ምላሾችን ሰጥታለች፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የውይይት መድረክ ላይ የነበረውን ሁኔታ፣ እንዲሁም ስለሰላማዊ ፖለቲካ ሰፊ ገለጻ ያደረገችበት ከዮናስ አማረ ጋር ያደረገችው ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ ለማንበብ ይህን ይጫኑ
‹‹ሐሳብ ማቅረብ ባልተገባ መንገድ የሚያስበይን ከሆነ እንደ አገር በአጠቃላይ የሳትነው ነገር አለ ብዬ እገምታለሁ›› ደስታ ጥላሁን፣ የኢሕአፓና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ
የጨርቃ ጨርቅ አምራቾች ከመንግሥት ድጋፍ ባለማግኘታችን ከገበያ እየወጣን ነው አሉ
በተመስገን ተጋፋው መንግሥት ለአገር ውስጥ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት አምራች ኢዱስትሪዎች በቂ ድጋፍ ባለማድረጉና ጥሬ ዕቃዎች ዋጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ በመወደዱ፣ የአገር ውስጥ አምራቾች ከገበያ ለመውጣት መገደዳቸውን ተናገሩ፡፡ የኢትዮጵያ የጨርቃ ጨርቅ አልባሳት አምራቾች ይህንን የተናገሩት፣ የአምራች ኢንዱስትሪ…
https://www.ethiopianreporter.com/128821/
የውጭ ባለሀብቶች ለኢትዮጵያውያን ብቻ በተፈቀዱ የንግድ ዘርፎች እንዲገቡ የመወሰኑ ፋይዳና ሥጋቶች
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አዓመድ (ዶ/ር) የውጭ ኩባንያዎች በጅምላና ችርቻሮ ንግድ እንዲሁም በገቢና ወጪ ንግድ ላይ ተሳታፊ እንደሆኑ የሚያስችል የሕግ ማሻሻያ እንደሚደረግ በገለጹ በሁለት ሳምንት ልዩነት ውስጥ ይህንኑ የሚፈቅድ መመርያ ወጥቷል፡፡ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ይፈቀዱ የነበሩ የንግድ…
https://www.ethiopianreporter.com/128720/
በጋምቤላ ክልል በእርሻ ልማት የተሰማሩ የአሥር ኢንቨስተሮች ንብረት በሐራጅ ሊሸጥ መሆኑ ተሰማ
ከ2007 ዓ.ም. ጀምሮ በጋምቤላ ክልል በእርሻ ልማት የተሰማሩ ከአሥር በላይ የሆኑ ኢንቨስተሮች ከልማት ባንክ የተበደሩትን ብድር መመለስ ባለመቻላቸው ባንኩ ንብረታቸውን በሐራጅ ሊሸጥባቸው መሆኑ ተሰማ፡፡ የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሎው አቡፕ (ዶ/ር) ለሪፖርተር እንደገለጹት…
https://www.ethiopianreporter.com/128829/
በአማራና በትግራይ ክልሎች ያገረሸው የሰላም ዕጦት
ያለፈው ሳምንት የተጀመረው በአወዛጋቢዎቹ የወልቃይትና የራያ አካባቢዎች ግጭት ስለመጀመሩ በሚጠቁሙ ወሬዎች ነበር፡፡ ሰኞ ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. አማራና ትግራይ ክልሎች እንደገና ግጭት ውስጥ…
https://www.ethiopianreporter.com/128835/
‹‹ራሱን መመገብ ያልቻለ ሕዝብና አገር የሌሎች ተላላኪ ይሆናል›› የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
በጀኔቫ በተካሄደ የዕርዳታ ማሰባሰቢያ መድረክ 21 አገሮች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል ‹‹ራሱን መመገብ ያልቻለ ሕዝብና አገር፣ የሌሎች ተላላኪ እንጂ፣ የውጭ ግንኙነት ቀርፆ ሊንቀሳቀሰ የሚችልበት ዕድል ጠባብ ነው፤›› ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ፡፡ …
https://www.ethiopianreporter.com/128766/
የሞጆ ደረቅ ወደብ ጥበቃ ሠራተኞች የጦር መሣሪያዎቻቸው ተወስደውባቸው በዱላ እየጠበቁ ነው ተባለ
የአገሪቱን 90 በመቶ ደረቅ ጭነት የሚያስተናግደው የሞጆ ደረቅ ወደብ የጥበቃ ሠራተኞች፣ በእጃቸው የነበሩ የጦር መሣሪያዎች በመወሰዳቸው በዱላ ጥበቃ እያደረጉ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ ይህ የተገለጸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ ሚያዝያ…
https://www.ethiopianreporter.com/128770/
የፓዌ ወረዳ ነዋሪዎች ከአማራ ክልል ተሻግረው በሚመጡ ታጣቂዎች ጥቃት እየደረሰብን ነው አሉ
ከአማራ ክልል አዋሳኝ ድንበር አካባቢ በምትገኘው ፓዌ ወረዳ ውስጥ የሚኖሩ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ነዋሪዎች፣ ከአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ተሻግረው በሚመጡ ታጣቂዎች ጥቃት እየተፈጸመባቸው እንደሆነ አስታወቁ፡፡ በፓዌ ወረዳ ሥር የሚገኙ አራት ቀበሌዎች ማለትም ቀበሌ 14፣…
https://www.ethiopianreporter.com/128773/
የገቢና የወጪ ንግድን ጨምሮ በጅምላና በችርቻሮ የሚሳተፉ የውጭ ባለሀብቶች የሚያሟሉት የካፒታል መጠን ይፋ ተደረገ
ሰባት ተቋማት የተካተቱበት ተቆጣጣሪ ኮሚቴ ይደራጃል ተብሏል ከዚህ ቀደም ለውጭ ባለሀብቶች ዝግ በነበሩ በገቢ፣ በወጪ፣ በጅምላና በችርቻሮ ንግድ እንዲሳተፉ የሚያደርግ መመርያ ከፀደቀ በኋላ ሊያሟሉት የሚገባ የካፒታል መጠን ይፋ ተደረገ፡፡ ባለሀብቶቹ እንደሚሰማሩበት ዘርፍ ከ500 ሺሕ ዶላር…
የባህርና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ክፍያ አንፈጽምም ያሉ የመንግሥት ተቋማትን እንዲያግባባለት ለፓርላማው ጥያቄ አቀረበ
ዋና ኦዲተር ከ2.5 ቢሊዮን ብር በላይ አለመሰብሰቡን አስታውቋል የቀድሞው ሜቴክ የአሁኑ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ያለበትን ዕዳ መክፈል አይችልም ተብሏል የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርትና የየብስ ወደቦች አገልግሎት የሰጣቸው የመንግሥት ተቋማት ያለባቸውን ክፍያ ባለመፈጸማቸው፣…
https://www.ethiopianreporter.com/128782/
የመንግሥትና የሃይማኖት ተቋማትን ግንኙነት በግልጽ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ
ረቂቅ አዋጁ ክልከላዎች የተካተቱባቸው ድንጋጌዎች ይኖሩታል ተብሏል መንግሥትና ሃይማኖት አንዱ በአንዳቸው ተግባርና እንቅስቃሴ ውስጥ ጣልቃ አይገቡም የሚለውን ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ መሠረት በማድረግ፣ መንግሥት ከሃይማኖት ተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት በግልጽ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱ ተገለጸ፡፡ በሰላም ሚኒስቴር…
https://www.ethiopianreporter.com/128778/
በራያ አካባቢ አስተዳደራዊ መዋቅሮች ሙሉ በሙሉ መፍረሳቸው ተነገረ
ከሰሞኑ በአማራና በትግራይ አዋሳኝ የራያ አካባቢዎች እንደገና በተቀሰቀሰው ግጭት፣ የወረዳና የቀበሌ አስተዳደራዊ መዋቅሮች ሙሉ በሙሉ መፍረሳቸው ተገለጸ፡፡ ኮረም፣ ዛታ፣ ኦፍላ የተባሉ ወረዳዎች ሙሉ በሙሉ በትግራይ ታጣቂዎች በመያዛቸው አስተዳዳሪዎችን ጨምሮ በርካታ ነዋሪዎች ወደ ቆቦ፣ ሰቆጣና ወልዲያ…
https://www.ethiopianreporter.com/128785/
የአገሪቱ ባንኮች የመጭበርበር ተጋላጭነት እየጨመረ መሆኑን ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ
በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ2 ቢሊዮን ብር መጭበርበሩን ገልጿል ቀሲስ በላይ መኮንን በማጭበርበር ድርጊት ፍርድ ቤት ቀርበዋል በዮሐንስ አንበርብር የአገሪቱ ባንኮች ከአሠራር ጋር በተያያዙ ክፍተቶች በተለያዩ ሥልቶች ለሚፈጸሙ የማጭበርበር ድርጊቶች በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ እየሆኑ መምጣታቸውን፣ ይህ ሁኔታም በቀጣይ…
https://www.ethiopianreporter.com/128791/
በሽግግር ፍትሕ እንዲታዩ የታሰቡ የወንጀል ጉዳዮች በልዩ ፍርድ ቤት ሳይሆን በልዩ ችሎት እንዲታዩ ተወሰነ
የኤርትራ ወታደሮች በሌሉበትም ቢሆን ይዳኛሉ ተብሏል ; የሽግግር ፍትሕ የባለሙያዎች ቡድን በቅርቡ ባቀረበው ረቂቅ ፖሊሲ የፍርድ ቤቶችን ሒደት በሚመለከት ልዩ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም የሚለው ምክረ ሐሳብ ውድቅ ተደርጎ፣ በመደበኛ ፍርድ ቤቶች ልዩ ችሎት በማቋቋም እንዲታይ…
https://www.ethiopianreporter.com/128793/
አስማማው ቀለሙ (ዶ/ር) ሲታወሱ (ከ1932 እስከ 2016 ዓ.ም.)
በፋና ገብረሰንበትና ዮናስ ታሪኩ ቅዳሜ ሚያዝያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ሌሊት ኢትዮጵያ ከታላላቅ ጀግናዎቿ መካከል አንዱ የነበሩትን አስማማው ቀለሙን (ዶ/ር) አጥታለች፡፡ አስማማው የአገርን ቋሚ ጥቅምና…
https://www.ethiopianreporter.com/128850/
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምኅዳር አሁንም ጤና አልባ ሆኖ የተለመደው ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡ ካለፉት ሃምሳ ዓመታት ወዲህ ሊሻሻል ያልቻለው የፖለቲካ ምኅዳር ሰሞኑን አዲስ ክስተት ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ባለፈው ሰሞን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ስብሰባ ከተቀመጡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የተወሰኑት፣ ለአደባባይ ያበቁት ቅሬታና ስሞታ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ በስብሰባው ወቅት ያነሷቸው ጥያቄዎችና የተሰጧቸው ምላሾች ከመቆራረጣቸው ባሻገር፣ ለሰላማዊ ትግል የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ የሚያውኩ ድርጊቶች መብዛታቸውን ድምፃቸውን ካሰሙ ፓርቲዎች ተወካዮች መረዳት ተችሏል፡፡ የፖለቲካ ምኅዳሩ ውስጥ የማይመቹና የሚጎረብጡ ችግሮች መኖራቸው የሚጠበቅ ቢሆንም፣ ገዥው ፓርቲም ሆነ የሚመራው መንግሥት ሰላማዊ የፖለቲካ ፉክክሩ ጨርሶ እንዳይዳፈን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው፡፡ የመድበለ ፓርቲ ፖለቲካ ሥርዓት ዕውን የሚሆነው ሰላማዊ ፉክክር ሲኖር ብቻ ነው፡፡
ገዥው ብልፅግና ፓርቲ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር የሚኖረው ግንኙነት ጤናማ መሆን ይጠበቅበታል፡፡ በጋራ ፖለቲካ ምክር ቤት አማካይነትም ሆነ በተጠናል የሚደረጉ ግንኙነቶች ጤነኝነት ሲጎድላቸው፣ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ወደ ጎን እየተገፋ የትጥቅ ትግል አማራጭ ይሆናል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያዋጣናል እስካሉ ድረስ ቢፈልጉ በነጠላ ካልሆነም በጥምረት ወይም በግንባር የመሰባሰብ ኃላፊነት የራሳቸው ሲሆን፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ ከመስጠት ይልቅ የፖለቲካ ምኅዳሩ ወለል ብሎ እንዲከፈት ትኩረት መስጠት ነው የሚገባው፡፡ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ዋና ሥራ ገዥውን ፓርቲ በማሳጣት የሕዝብ ድጋፍ ማግኘት ስለሆነ፣ ከገዥው ፓርቲ በኩል የሚፈለገው ሕዝብን የሚያሳምን ሥራ ማከናውን ነው፡፡ ሕዝብ የሥልጣን ሉዓላዊ ባለቤትነቱ የሚረጋገጠው ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በእኩል ምኅዳር ውስጥ በነፃነት ሲንቀሳቀሱ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ግብይት የሚፈጸምበት የቡና ምርት በከፍተኛ ደረጃ እያሽቆለቆለ ነው
በኢትዮጵያ ዘመናዊ የግብይት ሥርዓትን በመዘርጋት ረገድ በፈር ቀዳጅነት የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በዋናነት ሲያገበያይ የቆየው የቡና ምርት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰ መምጣቱና የቡና ምርት ግብይትም ከምርት ገበያው እጅ እየወጣ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ ላለፉት 16 ዓመታት የቡና ምርትን…
https://www.ethiopianreporter.com/128409/
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከተለያዩ የማኅበረሰብረ ተወካዮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ቀጥለዋል፡፡ ከሰሞኑ ከአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ ወዘተ እያለ ከሴቶች ተወካዮች ጋር አሥር ተከታታይ የውይይት መድረክ ቪዲዮዎችን የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን አከታትለው ሲያሠራጩ መመልከት ተችሏል፡፡ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም. ምሽት ደግሞ 11ኛው የውይይት መድረክ ሥርጭት በመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ተላልፏል፡፡
ይህ መድረክ ደግሞ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር የተካሄደ እንደመሆኑ መጠን፣ በመድረኩ ምን ሊነሳ ይችላል የሚለው ጉዳይ ብዙዎች በጉጉት የጠበቁት ነበር፡፡ ከተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮቹ መንግሥትን አይዞህ በርታ ብለው የሚደግፉ፣ ስለሠራቸው የፓርክ፣ መናፈሻና ሪዞርት ፕሮጀክቶች ሙገሳ የሚያቀርቡ ብዙ እንደሚሆኑ የገመቱ ነበሩ፡፡ ይህን አንድ ሰዓት ከ44 ደቂቃ የረዘመ የስብሰባው ቪዲዮ በተደጋጋሚ መመልከት የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህ በተቃራኒው አገሪቱ የምትገኝበትን ቀውስና አደጋ እንዲሁም ኅብረተሰቡ የሚያነሳቸውን አሳሳቢ ችግሮች ያማከሉ ጥያቄዎችም መቅረባቸውን ከውይይቱ ሥርጭት መታዘብ ተችሏል፡፡
ያም ቢሆን ግን ወደ 19 የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጥያቄ ያነሱበት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ለግማሽ ቀን የተካሄደው ሰፊ ውይይት፣ በመንግሥት ሚዲያዎች ተመጥኖ ከተለቀቀው ምጥን ሥርጭት በላይ ድባብ ሊኖረው እንደሚችል ይገመታል፡፡ በዚህ የተነሳም በውውይቱ አዳራሽ በአካል ተገኝተው ውይይቱን ከተካፈሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ሪፖርተር በውይይቱ ድባብ ዙሪያ ምጥን ቆይታዎችን በማድረግ የነበረውን ሁኔታ ለማስቃኘት ይሞክራል፡፡
የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር በየነ ጴጥሮስ (ፕሮፌሰር)
በሰላማዊ ትግል ለረጅም ዓመታት ያሳለፉት አንጋፋው ፖለቲከኛ አጋጣሚው ለጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ ለፓርቲዎቹ አገሪቱን በተመለከተ ያላቸውን አረዳድ በቀጥታ ለመነጋገር ዕድል የፈጠረ
በአሶሳ ከተማ በተፈጠረ የውኃ እጥረት ነዋሪዎች ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ተናገሩ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ በተፈጠረ የውኃ እጥረት ነዋሪዎች ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ተናገሩ፡፡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ በአሶሳ ከተማ በተፈጠረ ከፍተኛ የውኃ ችግር፣ አንድ ጄሪካን ውኃ እስከ ሃያ ብር ለመግዛት ተገደዋል፡፡ የከተማዋ የውኃ ችግር…
https://www.ethiopianreporter.com/128354/
ቡናን ከምርት ገበያው ውጭ መገበያየት መጀመሩ አሳሳቢ መሆኑ ተነገረ
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለፉት 16 ዓመታት 386 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው የግብርና ምርቶችን ቢያገበያይም፣ በዋናነት ሲያገበያያው የነበረው የቡና ምርት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱ አሳሳቢ ሆኗል፡፡ በአምስት ዓመት የግብይት መጠኑ ከ24 ቢሊዮን ብር ወደ…
https://www.ethiopianreporter.com/128355/
በስምንት ወራት የተገኘው የወጪ ንግድ ገቢ ከዓምናው በ164 ሚሊዮን ዶላር ማሽቆልቆሉ ተገለጸ
አፈጻጸሙ ዝቅ ያለበት ምክንያት የጫትና የቡና ኤክስፖርት በመቀነሱ ነው ተብሏል በስምንት ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ የተገኘው 2.16 ቢሊዮን ዶላር ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ164.18 ሚሊዮን ዶላር ማሽቆልቆሉ ተገለጸ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች…
https://www.ethiopianreporter.com/128358/
በመተከል ዞን በተፈጸመ ጥቃት ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የጉሙዝና የሸኔ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት የንፁኃን ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አስታወቀ፡፡ የቦሮ ዴሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበርና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገጠር መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አመንቴ ገሺ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ…
https://www.ethiopianreporter.com/128364/
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ ስላለው የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ክትትል ባለማድረጉ ተወቀሰ
በፅዮን ታደሰ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት፣ የሰብዓዊ መብቶች ባለሙያዎች ኮሚቴ በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜው ካበቃ በኋላ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝን አስመልክቶ የሚያደርገው ክትትል ቀንሷል ሲል ሂዩማን ራይትስዎች ወቀሳ አቀረበ፡፡ ዓለም አቀፉ…
https://www.ethiopianreporter.com/128367/
በታዳጊዎች ዕድሜ ገደብ ላይ ጥያቄ ያስነሳው የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ ፀደቀ
‹‹የግል ዳታ›› እና ‹‹ጥንቃቄ የሚፈልግ የግል ዳታ›› ተብሎ በሁሉም ሴክተሮች የግለሰቦችን ዳታ ማቀናበር የሚያስችል የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ የፀደቀ ቢሆንም፣ በታዳጊዎች የዕድሜ ገደብ ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ጥያቄ አስነስቷል፡፡ በግል ዳታ ጥበቃ ረቂቅ አዋጅ ‹‹በዳታ…
https://www.ethiopianreporter.com/128370/
ግልጽ የሆነ መመርያ እስኪወጣ ድረስ የክብር ዶክትሬት እንዳይሰጥ መከልከሉን ትምህርት ሚኒስትሩ አስታወቁ
በኢትዮጵያ የሚሰጠው የክብር ዶክትሬት በዘፈቀደና መሥፈርቱን ያላሟላ መሆኑም ተነግሯል ‹‹የተበታተነ አሠራርን ለመቅረፍ ግልጽ የሆነ መመርያ እስኪወጣ ድረስ ዩኒቨርሲቲዎች የክብር ዶክትሬት የሚባል ነገር መስጠት እንዲያቆሙ እንደተነገራቸው›› የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) አስታወቁ፡፡ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት ‹‹የኢትዮጵያ ሳይንስ…
https://www.ethiopianreporter.com/128373/
የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ከተቆጣጠሩት የኢትዮጵያ ይዞታ ቢለቁም የሚሰነዝሩት ጥቃት አለመቆሙ ተነገረ
ግጭቶችን ለመፍታት የጋራ ኮሚቴ መቋቋሙን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል በ2014 ዓ.ም. በይፋ የተመሠረተው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልልን በሚያዋስነው ድንበር በኩል የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች የተቆጣጠሩትን ይዞታ ቢለቁም፣ ለነዋሪዎች ሥጋት የሆነውን ጥቃት አለማቆማቸውን ክልሉ አስታወቀ፡፡ ለረዥም ጊዜ መፍትሔ ሳይሰጠው…
https://www.ethiopianreporter.com/128376/
‹‹በሌሎች ክልሎች ያለው የሰብዓዊ ዕርዳታ ፍላጎት ከትግራይ አንፃር አነስተኛ ነው ብዬ ለመግለጽ አልችልም›› ራሚዝ አላክባሮቭ (ዶ/ር)፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት…
…በኢትዮጵያ የተመድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የሰብዓዊ ዕርዳታ አስተባባሪ እንደ መሆኔ ሁሉንም ክልሎች ጎብኝቻለሁ። በእርግጥ ትግራይ የጦርነቱ ማዕከል ነበረች። ነገር ግን በሌሎች ክልሎች ያለው የሰብዓዊ ዕርዳታ ፍላጎት ከትግራይ አንፃር አነስተኛ ነው ብዬ መግለጽ አልችልም። እንዲያውም…
https://www.ethiopianreporter.com/128382/
የፌዴራል ተቋማት ለክልል የልማት ተነሺዎች ካሳ የመክፈል ግዴታ ሊነሳላቸው ነው
ካሳ የመክፈል ኃላፊነት ልማቱ የሚከናወንበት ክልል ይሆናል የፌዴራል ተቋማት ለክልል የልማት ተነሺዎች እስካሁን ሲፈጽሙ የቆዩት ካሳ የመክፈል ግዴታ እንዲነሳላቸው የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ፡፡ በፌዴራል መንግሥት ለሚከናወኑ መሠረተ ልማቶችና ለማኅበራዊ አገልግሎት ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ግንባታ የልማት ተነሺ ዜጎች…
https://www.ethiopianreporter.com/128387/
እ.ኤ.አ. መስከረም 2020 በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ንግግር ያደረጉት ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አንድ ቃል ገቡ፡፡ የዚያን ጊዜ ገና ወደ ሥልጣን ከመጡ ሁለተኛ ዓመታቸው ነበር፡፡ ‹‹ባለፉት ሁለት ዓመታት የፖለቲካ ምኅዳሩን ለማስፋት የምንችለውን ያህል ጥረት አድርገናል፡፡ የዴሞክራሲ መብቶችና የሰብዓዊ መብቶችን አከባበር ለማሻሻል እየሠራን እንገኛለን፡፡ ይህ ሥራ ቀላልና አልጋ በአልጋ እንደማይሆን እንገነዘባለን፡፡ ይልቁንም ከባድ ፈተና እንደሚገጥመን እናውቃለን፡፡ ይሁን እንጂ የፈለገ ፈተናው ቢበዛ ጥረታችንን ለመቀጠልና በአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ለማምጣት ከፍተኛ ቁርጠኝነቱ አለን፡፡ ሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ ለማድረግም ቁርጠኛ ነን፤›› በማለት ነበር የተናገሩት፡፡
ይህ የዓብይ (ዶ/ር) ንግግር በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ፊት ኢትዮጵያን ለማሸጋገር የተገባ ቃል ነበር፡፡ ከዚያ አንድ ዓመት ቀደም ብሎ በአሜሪካ በተለይ በዋሽንግተንና በዙሪያዋ ካሉ የዳያስፖራ አባላት ጋር ሲነጋገሩም ስለዴሞክራሲያዊ ሽግግር ቃል ገብተው ነበር፡፡ ‹‹የሽግግር ሒደት፣ ሽግግር፣ ሽግግር፣ የሚባለው አንዴ ከተቀመጡ መነሳት የማይፈልጉ ሰዎች ስላስቸገሯችሁ የምታነሱት ጥያቄ እንደሆነ ይገባኛል፡፡ ሽግግርን በሚመለከት ችግር የለም እኔ አሻግርላችኋለሁ፤›› በማለት ነበር ለዳያስፖራው ቃል የገቡት፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ የሽግግር ሒደቶች ለኢትዮጵያውያንም ሆነ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ቃል ከገቡ እነሆ ስድስት ዓመታት ተቆጠሩ፡፡ ቃል በገቡት መሠረት ዴሞክራሲያዊ ሽግግሩ መከናወኑን የሚጠራጠሩ ዛሬም በርካታ ናቸው፡፡
ከአንድ ዓመት በፊት በአንድ የፓርላማ ቆይታቸው ወቅት ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካዩ ከደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) የሽግግር ጉዳይ ጥያቄ ተነስቶላቸው ነበር፡፡ ‹‹አሁንም ኢትዮጵያን አሻግራለሁ ይላሉ? ወይስ ሁሉን አቀፍ የሽግግር ሒደት ለመፍጠር ያስባሉ?›› የሚል ይዘት ያለው ጥያቄ ነበር
መንግሥት የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ማዳመጥ አለበት!
በአገር ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ ሁሌም መስማማት ሁሌም መጣላት አይቻልም፡፡ በሚያስማሙ ጉዳዮች ላይ የጋራ ግንዛቤ እንደሚኖረው ሁሉ፣ በማያስማሙት ላይም ልዩነትን በማክበር በጨዋነት መነጋገር ተገቢ ነው፡፡ ሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት በሚወስዳቸው የተለያዩ ዕርምጃዎች ምክንያት ደጋፊዎች ሲኖሩት፣ የዚያኑ ያህል ተቃውሞ የሚያሰሙበት መኖራቸው የሚጠበቅ ነው፡፡ የአገር ጉዳይ ሲነሳ ከብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅም ቀጥሎ ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች የጋራ ስምምነት ይጠይቃሉ፡፡ በዕቅድና በአፈጻጸም ላይ ግን የተለዩ ምልከታዎች መኖራቸውም አይቀሬ ነው፡፡ ሥልጣን የያዘው ገዥው ብልፅግና ፓርቲ በሕዝብ ድምፅ ለአምስት ዓመታት በተሰጠው ኮንትራት መሠረት አገር ሲያስተዳድር፣ በሚወስዳቸው የተለያዩ ዕርምጃዎች ምክንያት የተለያዩ ጥያቄዎች ከመራጩ ሕዝብ ሲነሱለት ምላሽ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡ አሠራሩም በሕጉ መሠረት የግልጽነት፣ የተጠያቂነትና የኃላፊነት መርህ መከተል ይኖርበታል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመረው ‹‹የኮሪደር ልማት›› ከተለያዩ አቅጣጫዎች ጥያቄዎች እያስነሳ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) እና የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ለሚነሱት ጥያቄዎች በአለፍ ገደም ምላሽ እየሰጡ ነው፡፡ ይህ መጠነ ሰፊ ፕሮጀክት በርካታ የከተማዋን ነዋሪዎች ሕይወት የሚነካ በመሆኑ፣ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ጥያቄዎች መነሳታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡ በልማት ስም ከመኖሪያቸውና ከመሥሪያ ቦታቸው የሚነሱ ዜጎች ጉዳይ አንደኛው ሲሆን፣ ከከተማዋ ነባር ቅርሶችና ትውስታዎች መጥፋት ጋር የተያያዘው ሌላው ጉዳይ ነው፡፡ መንግሥት ነዋሪዎችን ከአካባቢያቸው ሲያስነሳቸው የማኅበራዊ ትስስር ድራቸው መበጣጠሱም ሌላው ጥያቄ ነው፡፡ አዲስ አበባ ከተማ ተለውጣ እንደ ስሟ ውብ ትሆናለች እየተባለ ሲነገር፣ ለልማቱ አካባቢዎቻቸውን ለቀው ወደ ሌላ
የንግድ ማዕከላት ባለቤት የሆኑ አክሲዮን ማኅበራት ላይ የተለያዩ የግብር ግዴታዎች ተጣሉ
የገቢዎች ሚኒስቴር በንግድ ማዕከልነት የሚያገለግሉ ሕንፃዎችን በጋራ ገንብተው በባለቤትነት የሚያስተዳድሩ አክሲዮን ማኅበራት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስና የዲቪደንድ (የትርፍ ድርሻ) ታክስን ጨምሮ የተለያዩ የግብር ዓይነቶችን እንዲከፍሉ ወሰነ። በንግድ ማዕከልነት የሚያገለግሉ ሕንፃዎችን ገንብተው በባለቤትነት የሚያስተዳድሩ አክሲዮን ማኅበራት የሕንፃውን…
https://www.ethiopianreporter.com/128069/
ቡና ላኪዎች የስም ማጥፋት ዘመቻ እንደተከፈተባቸውና ከውጭ ገዥዎች ክፍያ መሰብሰብ እንዳቃታቸው ተናገሩ
በሁለት ስያሜ ላኪዎችን ሲያጭበረብር የነበረ የቻይና ድርጅት መያዙ ተጠቁሟል የተለያዩ የቡና ዓይነቶችን የሚልኩ ድርጅቶች በውጭ ገበያ ከሚገኙ ገዥዎች የስም ማጥፋት ዘመቻ እንደተከፈተባቸው፣ እንዲሁም ሚሊዮን ዶላሮች የሚያወጣ በዱቤ የተላከ ቡና ክፍያ መሰብሰብ እንዳቃታቸው ተናገሩ፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ ሪፖርተር…
https://www.ethiopianreporter.com/128163/
ሕወሓት ዕውቅናው እንዲመለስለት ያቀረበውን ጥያቄ ቦርዱና ፍትሕ ሚኒስቴር የሕግ መሠረት የለውም አሉ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን ዕውቅናውና ፈቃዱ እንደሚመለስ ተናግረዋል በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ የዕውቅና ፈቃዱን የተነጠቀው ሕወሓት፣ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንደተገለጸው በሕገ መንግሥቱ መሠረት እንዲመለስለት ያቀረበው ጥያቄ የሕግ መሠረት የለውም ሲሉ…
https://www.ethiopianreporter.com/128166/
አገራዊ የምክክር ውይይቶች በብልፅግና ካድሬዎች የተሞሉ ሆነዋል ሲል ኢዜማ ከሰሰ
በጉዳዩ ዙሪያ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ ማቅረቡን አስታውቋል ‹‹የአገር አቀፍ የምክክር ውይይቱ ላይ እየተሳተፉ ያሉት የገዥው ፓርቲ አባላት ብቻ ናቸው የሚለው ክስ አልገባኝም›› ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ፓርቲ፣ የኢትዮጵያን ውስብስብና ሥር የሰደዱ ችግሮች ይፈታል ተብሎ…
https://www.ethiopianreporter.com/128157/
ብልፅግና ፓርቲና ሕወሓት በመቀሌ ተገናኝተው መከሩ
በብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ የፓርቲው ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ትናንት መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ.ም. ወደ መቀሌ በመጓዝ ከሕወሓት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ጋር መወያየቱ ታወቀ። ሕወሓት ባወጣው አጭር መግለጫ እንዳስታወቀው፣ የብልፅግና አመራሮች…
https://www.ethiopianreporter.com/128171/
ጁምዓና ከተራን ጨምሮ አራት ቀናት ሥራ ዝግ ሆኖ እንዲከበሩ ጥያቄ ቀረበ
ጁምዓ፣ ከተራና ቃና ዘገሊላ የአደባባይ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች፣ እንዲሁም የካቲት 12 የሰማዕታት መታሰቢያ በዓላት ሥራ ዝግ ሆነው እንዲከበሩ በፓርላማ ጥያቄ ቀረበ፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለጤና፣ ማኅበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴና በተባባሪነት ለሕግና ፍትሕ…
https://www.ethiopianreporter.com/128177/
የመንግሥት ተቋማትና አመራሮች ሳይናበቡ ሲቀሩ በአገልግሎት ፈላጊዎችም ሆነ በአጠቃላይ ሕዝቡ ኑሮ ላይ ችግሮች መፈጠራቸው አይቀሬ ነው፡፡ ሁሉም የመንግሥት ተቋማት ስለተግባራቸው፣ ኃላፊነታቸውና ተጠያቂነታቸው በተቋቋሙበት ሕግ ተደንግጓል፡፡ አመራሮቻቸውም እንዴት ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡና ስለሚኖርባቸው ተጠያቂነትም በሕጎች ውስጥ በሚገባ ሠፍሯል፡፡ በሕግ በተወሰነላቸው ጊዜ መሠረትም ዕቅዳቸውና አፈጻጸማቸው በሕግ አውጭ ምክር ቤቶች ይገመገማል፡፡ በሕግ ከተሰጣቸው ሥልጣን ውጪ አላግባብ ከተሰማሩም በሕግ ተጠያቂነት አለባቸው፡፡ በሥራ ላይ ባለው ሕገ መንግሥትም ሥራቸውን በግልጽነት፣ በተጠያቂነትና በኃላፊነት መርህ እንዲወጡ ድንጋጌ አለ፡፡ በዚህ መሠረት ተቋማትም ሆኑ አመራሮች እየተናበቡ ሥራቸውን ማከናወን አለባቸው፡፡ በሕግ ከተሰጣቸው ኃላፊነት ውጪ ‹‹በተሰጠ አቅጣጫ መሠረት›› በማለት ሥራን መምራት ፈፅሞ አይቻልም፡፡ እንዲህ ዓይነት ጉዳይ ሲያጋጥም ሕግ አውጭው፣ ሕግ አስፈጻሚውና ሕግ ተርጓሚው በቅንጅት ማስቆም አለባቸው፡፡
የአስፈጻሚው አካል የሆነው ካቢኔም ቢሆን በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችና በተጠሪ ተቋማት በዘፈቀደ የሚከናወኑ ሥራዎችን መመርመር አለበት፡፡ ሁሉም የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችና ተጠሪ ተቋማት በማንኛውም አሠራር መናበብ እንዳለባቸው ቁጥጥር ማድረግ አለበት፡፡ በየጊዜው ሲሰበሰብም ይህ ጉዳይ አፅንኦት ሊሰጠው ይገባል፡፡ ለምሳሌ አገሪቱ ከውጭ ስለምታስገባቸው የተለያዩ ምርቶች በሕግ ከተወሰነው ውጪ፣ ማንም እየተነሳ ፈቃጅና ከልካይ መሆን እንደሌለበት በግልጽ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ የአገሪቱን በጀት የሚያዘጋጀው አካል እያለ ሌላው በማይመለከተው ጣልቃ እንዳይገባ መደረግ አለበት፡፡ በሌተር ኦፍ ክሬዲትም ሆነ በፍራንኮ ቫሉታ ስለሚገቡ ምርቶችም ሆነ ማሽነሪዎች በሕግ ከተደነገገ ውጪ ‹‹በልዩ ሁኔታ›› የሚባል አሠራር መቅረት አለበት፡፡ በሕግ የተፈቀደ መግባት ሲኖርበት፣ ያልተፈቀደ ደግሞ መቅረት ይኖርበታል፡፡ ለዚህ ደግሞ በአግባቡ መናበብ ያስፈልጋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከአዲስ አበባ ከተውጣጡ ነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ስብሰባ የ1997 ዓ.ም. ምርጫ ወቅት አጋጣሚ ያሉትን በምሳሌነት አንስተው ነበር፡፡ በ1997 ዓ.ም. ምርጫ ሰሞን ተቃዋሚዎች ኢሕአዴግን የማጥላላት ዘመቻ በሰፊው መክፈታቸውን በማስታወስ በየቤተ ክርስቲያኑ፣ በየዕድሩ፣ በየትራንስፖርቱ፣ በየቦታው ኢሕአዴግ ዘረኛ ነው፣ ኢሕአዴግ እንዲህ ነው፣ እንዲያ ነው… ወዘተ እያሉ፣ በወሬ ስሙን ማስጠፋት እንደ ምርጫ መፎካከሪያ ስትራቴጂ መጠቀማቸውን ገልጸው ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከከፍተኛ ግብር ከፋዮች ጋር ባደረጉት የውይይት መድረክ የተካፈሉ ተወያዮች
ያኔ እንደ አሁኑ የመገናኛ ብዙኃን ባለመስፋፋታቸው ተቃዋሚዎቹ የከፈቱት በወሬ የኢሕአዴግን ስም የማጠልሸት ዘመቻ በመላ አገሪቱ ተዳርሶ የሚፈልጉትን ውጤት ማምጣት ባያስችልም፣ በአዲስ አበባ ከተማ ግን እንደተሳካላቸው ተናግረዋል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ ልክ እንደ 1997 ዓ.ም. ብልፅግናን በወሬ ማሸነፍ አይቻልም ሲሉ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹እከሌ ይህን አልሠራህም ቢለኝ እኔ አለኝ ብዬ የማሳየው የሠራሁት ብዙ ሥራ አለና በወሬ ማጠልሸት አይቻልም፤›› ነበር ያሉት፡፡
በዚሁ የውይይት መድረክ ስለፖለቲካ ፓርቲዎች ተፎካካሪነትና ስለፓርቲያቸው ብልፅግና ትኩረት የሚስቡ ነጥቦችን ሲያሰሙ ተደምጠዋል፡፡ ‹‹የብልፅግና ፈተና የቀነጨሩ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ኦነግ፣ ኢሕአፓ፣ መኢሶን ምናምን 50 ዓመት አስቆጥረዋል፡፡ ነገር ግን ከሞቱ ቆይተዋል፣ እነሱ አሁንም አለን ይላሉ፡፡ ብልፅግና 14.5 ሚሊዮን አባል ይዞ በአፍሪካ ትልቁ ፓርቲ ቢሆንም በውስጡ ገና ብዙ አሰስ ገሰስ አለ፡፡ ብዙ ሌባ፣ ቀጣፊ፣ አጭበርባሪና የማይሠራ አለ፤›› በማለት እሱን የማጥራት ሥራ እንደሚከናወን ተናግረዋል፡፡
ዓብይ (ዶ/ር) በዚህ የውይይት መድረክ ያነሷቸው እነዚህ ነጥቦች ግን ጥያቄ የሚያስነሱ
የኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃላፊነታቸው ታገዱ
የአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ጥላሁን ታደሰ ከኃላፊነታቸው ታገዱ፡፡ አቶ ጥላሁን ከኃላፊነታቸው እንደታገዱ የሚገልጸው ደብዳቤ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለሥልጣን ዋና ሥራ…
https://www.ethiopianreporter.com/127952/
ከወሊድ ጋር በተያያዘ የሕክምና ስህተት 66 እናቶች ሕይወታቸውን ማጣታቸው ተገለጸ
የአዲስ አበባ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከመጋቢት 2007 እስከ መጋቢት 2016 ዓ.ም. በግልና በመንግሥት ጤና ተቋማት በተፈጠረ የሕክምና ስህተት 66 እናቶች ሕይወታቸው ማለፉን አስታወቀ፡፡ ባለሥልጣኑ ማክሰኞ መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ፣ የስምና የመለያ (ብራንዲንግ)…
https://www.ethiopianreporter.com/127954/
ኮሌራና ኩፍኝን ጨምሮ በወባ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር መጨመሩ አስጊ ሆኗል ተባለ
በወባ፣ በኮሌራና ኩፍኝ ወረርሽኞች የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከፍ ማለቱና የወረርሽኞቹ መስፋፋት አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ፡፡ በየካቲት ወር ብቻ 705 ሺሕ ሰዎች በወባ ተይዘው 764 ሰዎች መሞታቸውን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽሕፈት…
https://www.ethiopianreporter.com/127965/
ከአምስት ዓመታት በላይ የተከማቸ የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዝቃጭ ቆሻሻ ወደ ሐይቅ እየገባ ነው ተባለ
በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከአምስት ዓመት በላይ የተከማቸ ዝቃጭ ቆሻሻ ወደ ሐዋሳ ሐይቅ እየገባ መሆኑ በዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ተረጋገጠ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ፣ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ..
https://www.ethiopianreporter.com/127970/
የፍትሕ ሥርዓቱ ክፍተት ሴቶች ሕፃናት ተገቢውን ፍትሕ እንዳያገኙ ማድረጉን ኢሰመኮ አስታወቀ
በፅዮን ታደሰ በወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ውስጥ በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች፣ በወንጀል ሥነ ሥርዓትና በማስረጃ ደንቦች ባለመካተታቸው፣ የጥቃት ተጎጂ ሴቶችና ሕፃናት ፍትሕ እንዳያገኙ ማድረጉን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (አሰመኮ) አስታወቀ፡፡ ኮሚሽኑ በወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ውስጥ የጥቃት…
https://www.ethiopianreporter.com/127978/
አዲስ የኤሌክትሪክ ኃይል ታሪፍ በተያዘው ዓመት ተግባራዊ ሊደረግ ነው
በ2014 ዓ.ም. ተጀምሮ የነበረው አዲስ ኤሌክትሪክ ኃይል የታሪፍ ማሻሻያ ጥናት ተጠናቆ፣ በተያዘው ዓመት ተግባራዊ እንደሚደረግ ታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና አገልግሎት በጋራ በዓለም ባንክ ድጋፍ በውጭ አማካሪ ድርጅት ያስጀመሩት ጥናትና የተዘጋጀው አዲሱ የታሪፍ ፖሊሲ የሚመለከታቸው የመንግሥት…
https://www.ethiopianreporter.com/127983/
በእስረኞች ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ይፍጸማል ተብሏል
የ‹‹ምትክ እስራት›› ከጥሰቶቹ አንዱ መሆኑም ተጠቁሟል
በኦሮሚያ ክልል በባሌ ዞን የአልሸባብ ክንፍ በመሆን የሚጠረጠር የታጠቀ ቡድን መደራጀቱንና እንቅስቃሴ መጀመሩን በፀጥታ ሥጋትነት የክልሉ ባለሥልጣናት ማስቀመጣቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰማኮ) ዓርብ መጋቢት 13 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ሪፖርት አስታወቀ፡፡
በኬንያ፣ በኡጋንዳና በሶማሊያ ኃይሎች ጭምር ይደገፋል የሚባለው ይህ ሸማቂ ኃይል፣ በፖሊሶችና በመንግሥት ባለሥልጣናት ላይ ጥቃት መክፈቱ ችግሩን እንዳወሳሰበ ባለሥልጣናቱ ስለመናገራቸው ኢሰመኮ በሪፖርቱ አብራርቷል፡፡
የሶማሌ ክልልን ጨምሮ በአራቱ ሰፋፊ ክልሎች በማሰርና በእስር አያያዝ ሒደት ባለፉት አምስት ዓመታት የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን በሰፊው የሚዘረዝረው የኢሰማኮ ሪፖርት፣ ከባድ የመብት አያያዝ ጉድለቶችን ማግኘቱን አብራርቷል፡፡ ኢሰብዓዊ አያያዝን ጨምሮ ጭካኔ የተሞላበት ማሰቃየት፣ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጥቃት መብታቸው በተገደበ ሰዎች ላይ ስለመፈጸሙ የኢሰመኮ ሪፖርት አሳሳቢ ጉዳይ ነው ሲል አስታውቋል፡፡
ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ነፃነታቸውን በተነፈጉ (በታሰሩ) ሰዎች ላይ የመብት ጥሰቶች እንደሚፈጸና ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም. ባሉት አምስት ዓመታት በአራት ክልሎች የታሰሩ ሰዎችን የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ በገመገመበት ሪፖርት ላይ አብራርቷል፡፡
ኢሰመኮ ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ ሥልታዊና የዘፈቀደ እስራት እንደሚፈጸም አስታውቆ፣ በእስር አያያዝ ሒደትም የመብት ጥሰቶች ይፈጸማሉ ብሏል፡፡
በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በሶማሌና በቀድሞው አጠራሩ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በታሰሩ ሰዎች ላይ ስለሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶች የሚዘረዝረው ሪፖርቱ፣ 86 ተጎጂዎችንና ምስክሮቻቸውን ማነጋገሩን ያስረዳል፡፡ በአራቱም ክልሎች አቤቱታ መቀበያ መድረኮችን በማዘጋጀትም የሕግ አካላትንና የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 365
‹‹የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ወደ ቀዬአቸው የመመለስ ሥራ ፖለቲካዊ መፍትሔ ይሻል›› ወ/ሮ ራኬብ መለሰ፣ የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር
በፅዮን ታደሰ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች አሁንም ድረስ የቀጠሉ ግጭቶች በመኖራቸው፣ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ወደ ቀዬአቸው የመመለሱ ሥራ ፖለቲካዊ መፍትሔ እንደሚያስፈልገው፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ምክትል ዋና ኮሚሽነር ወ/ሮ ራኬብ መለሰ አስታወቁ፡፡ ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ይህንን…
https://www.ethiopianreporter.com/127865/
ኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች በበርካታ ውስብስብ ችግሮች ውስጥ እያለፈች ነው፡፡ ሰላም የራቃት ኢትዮጵያ በተለያዩ ሥፍራዎች በሚካሄዱ ግጭቶች መታመስ ከጀመረች ዓመታት እየተቆጠሩ ነው፡፡ ግጭቶቹ የበርካታ ንፁኃን ወገኖችን ሕይወት ከመቅጠፋቸው ባሻገር፣ በአገርና በሕዝብ ንብረት ላይ ከባድ ጉዳት እያደረሱ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የፓርኮች፣ የሪዞርቶችና ከቱሪዝም ጋር የተገናኙ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ የአገሪቱ የፋይናንስ ተቋማትና ሌሎች ድርጅቶች ራሳቸውን በዲጂታል ቴክኖሎጂዎች እያስታጠቁ ነው፡፡ ከባንኮችና ከቴሌኮም ኩባንያዎች በተጨማሪ ከዘመኑ ዕድገት ጋር እኩል ለመራመድ የሚተጉ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ ፈጣኑን የዲጂታል ቴክኖሎጂ በመጠቀም እየዘመኑ ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ አዲስ አበባ ከተማ ግዙፍ አፍርሶ የመገንባት ሥራ ውስጥ ገብታለች፡፡ እነዚህ ከብዙ በጥቂቱ የቀረቡ ማሳያዎች ላይ መነጋገር ያስፈልጋል፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን መጠነኛ ማሳያዎች መነሻ በማድረግ ስንነጋገር የሰላምና የፀጥታ ጉዳይ ትልቅ ትኩረት እንደሚሻ ነጋሪ አያስፈልገውም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተከታታይ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር እያደረጓቸው ባሉ ውይይቶች በስፋት እየተነሳ ነው፡፡ ብዙዎች እንደ መጡበት የኅብረተሰብ ክፍል ባህሪ የሚነሱ የተለያዩ ጉዳዮች ቢኖሩም፣ በብዙዎች ግን የሰላምና የፀጥታ ጉዳይ ሳይነሱ አላለፉም፡፡ አሁንም ከእነዚህ ውይይቶችና ወደፊት ይደረጋል ተብሎ ከሚጠበቀው የአገራዊ የምክክር መድረክ ባሻገር፣ የሰላምና የፀጥታ ጉዳይ ከምንም ነገር በላይ ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ ኢትዮጵያን በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስሟን ከግጭትና ከውድመት ጋር የሚያስነሳው የጥፋት ምዕራፍ መዘጋት አለበት፡፡ ለዚህ ደግሞ ከሕጋዊና ከፖለቲካዊ የሰላም ጥረቶች በተጨማሪ፣ ለአገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴዎች ዕድል መስጠት
በደብረ ብርሃን በካምፕ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ዕርዳታ በመቋረጡ ወደ ቀን ሥራ እየተሰማሩ ነው ተባለ
ከተለያ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተፈናቅለው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በደብረ ብርሃን ከተማ መጠለያ ካምፕ የሚገኙ ተፈናዮች ከመንግሥትና ከተለያዩ በጎ አድራጎት ማኅበራት ይደረግ የነበረው ድጋፍ በመቋረጡ ወደ ቀን ሥራ መግባታቸው ተገለጸ፡፡ ከአራት ዓመታት በላይ በመጠለያ ካምፕ…
https://www.ethiopianreporter.com/127748/
በኢትዮጵያ 52 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች ሕይወት የሚያልፈው ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች መሆኑ ተገለጸ
በየማነ ብርሃኑ በኢትዮጵያ ከ52 በመቶ በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ሕይወታቸውን በማጣት ላይ እንደሚገኙ የቅርብ ጥናቶች ማረጋገጣቸው ተነገረ፡፡ የኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማኅበር ከመጋቢት 8 እስከ 10 ቀን 2016 ዓ.ም. ‹‹ሁሉን አቀፍ የጤና ተደራሽነት›› በሚል መሪ…
https://www.ethiopianreporter.com/127751/
የተጎጋ የሲሚንቶ ፋብሪካን 49 በመቶ ድርሻ ለውጭ አገር ኩባንያዎች ለመሸጥ ዕቅድ መያዙ ተሰማ
በትግራይ ክልል ከመቀሌ ከተማ ምዕራብ አቅጣጫ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘውን የተጎጋ ሲሚንቶ ፋብሪካን በ17.2 ቢሊዮን ብር ለመገንባት ከባንኮች ብድር ማግኘት ካልተቻለ፣ 49 በመቶ አክሲዮኑን ለውጭ ኩባንያዎች ለመሸጥ ዕቅድ መያዙን የፋብሪካው የቦርድ ሰብሳቢ…
https://www.ethiopianreporter.com/127754/
አስጎብኚ ድርጅቶች ለጥያቄያቸው ምላሽ ሳያገኙ እንደገና ተመዝገቡ መባላቸውን ተቃወሙ
ሲያቀርቧቸው የነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ ሳያገኙ እንደገና ‹‹ተመዝገቡ›› መባሉ፣ ተገቢ እንዳልሆነ አስጎብኚ ድርጅቶች አስታወቁ፡፡ ቀደም ሲል አስጎብኚ ድርጅቶች ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሳይሰጥባቸው የቱሪዝም ሚኒስቴር ዳግም ምዝገባ እንዲካሄድ መጠየቁ አግባብ አለመሆኑን፣ የታላቁ የኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅቶች ማኅበር…
https://www.ethiopianreporter.com/127757/
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ተተኪ ቦታ ሳይሰጠው 980 ቤቶች እንደፈረሱበት ተገለጸ
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተተኪ መሬት ሳይሰጠው 980 የሚጠጉ ቤቶች እንዳፈረሱበት ተገለጸ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 18ኛ መደበኛ ስብሰባውን ማክሰኞ መጋቢት 9 ቀን 2016 ሲያደርግ አቶ ፈይድ ሸራብ የተባሉ የምክር ቤት አባል…
https://www.ethiopianreporter.com/127760/
የመንግሥት ፕሮጀክቶች ማኅበረሰቡን ታሳቢ እንዲያደርጉ ተጠየቀ
በፅዮን ታደሰ የመንግሥት ፕሮጀክቶች ማኅበረሰቡን ታሳቢ ሊያደርጉ እንደሚገባ ለመልሶ ማልማት የተነሱ የአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ነዋሪዎች አሳሰቡ፡፡ መንግሥት የሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች የማኅበረሰቡን አቅምና ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉ ሊሆን ይገባል ሲሉ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አራዳ ክፍለ…
https://www.ethiopianreporter.com/127772/
የዓድዋ ድል በዓል ባለቤትነት ለመከላከያ ሚኒስቴር መሰጠቱ በፓርላማ ጥያቄ አስነሳ
የዓድዋ ድል በዓል አከባበር ኃላፊነትና ባለቤትነት የተሰጠው የመከላከያ ሚኒስቴር በፓርላማ ጥያቄ ተነሳበት፡፡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ የማኅበራዊ ልማት፣ የባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የሕዝብ በዓላትንና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ን በሚመለከት ከአስረጂዎች ጋር…
https://www.ethiopianreporter.com/127766/
የኢትዮጵያ አየር መንገድን አክሲዮን ድርሻ ለሶማሌላንድ ለማቅረብ የወጣ መመርያም ሆነ አቅጣጫ እንደሌለ ተገለጸ
ከሶማሌላንድ የባህር በር ለማግኘት እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ መጠኑ ያልተገለጸ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የአክሲዮን ድርሻ ሊሰጥ ይችላል በሚለው ጉዳይ ላይ፣ የተላለፈ መመርያም ሆነ መንግሥታዊ አቅጣጫ እንደሌለና በሐሳብ ደረጃ ብቻ የተያዘ መሆኑ ታወቀ። መንግሥት የአገሪቱን ጥቅሞች…
https://www.ethiopianreporter.com/127775/
ሰሞኑን አምስት መንግሥታዊ ተቋማት ማለትም የግብርና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ኢትዮጵያ ፖስታና ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የስኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በሥራቸው የተመሰከረላቸው ተቋማት ሲሸለሙ መልካም የሆነውን ያህል፣ ሽልማቱም የበለጠ ለመሥራት የሚያነሳሳ መሆን ይገባዋል፡፡ የግብርና ሚኒስቴር በስንዴ ልማት ፕሮግራም ከተሸላሚዎች ተርታ የተገኘ ብቸኛ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ሲሆን፣ ሌሎቹ ግን ተጠሪ ተቋማት ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ አንቱታን ያተረፈና የበርካታ ሽልማቶች ባለቤት በመሆኑ፣ በኢትዮጵያ ብቸኛው ታላቅ ደረጃ ላይ የደረሰ ተቋም ነው ቢባል የተጋነነ አይደለም፡፡ ሥራው በከፍተኛ ፉክክር የተፈተነ የላቀ ውጤት አስመዝጋቢ ነው፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም በከፍተኛ ዕድገት ላይ ሲገኝ፣ ኢትዮጵያ ፖስታ እመርታዊ ለውጥ እያሳየ ነው፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ለአገር ዕድገት ትልቅ ምሳሌ ነው፡፡
ከላይ የተጠቀሱት መንግሥታዊ ተቋማት በጣም ብዙ ከሚባሉት ውስጥ ተመርጠው በአርዓያነት የስኬት ተሸላሚ ሲሆኑ፣ ሌሎችም የሚጨበጥ ሥራ አከናውነው ለስኬት ይበቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ነገር ግን አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ብዙዎቹ መንግሥታዊ ተቋማት በመዳህ ላይ ናቸው ቢባል ይቀላል፡፡ እርግጥ ነው ከተወሰኑ ጊዜያት ወዲህ ምሥጉን ሥራዎችን የሚያከናውኑ ተቋማት እየታዩ ነው፡፡ እነሱ አሳማኝ የሆነ ተግባር አከናውነው ተመራጭ የሚሆኑበት ዕድል አለ፡፡ ይሁንና የብዙዎቹ ተቋማት ጉዳይ ግን ሰፊና ጥልቅ ምርመራ ያስፈልገዋል፡፡ ተቋማቱ መሠረታዊ ለውጥ አድርገው ተመራጭ ሊሆኑ የሚችሉት ግን አሁን ባሉበት ሁኔታ አይደለም፡፡ ተቋማዊ የአደረጃጀት ሪፎርም ተደርጎባቸው ብቁ አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ ሠራተኞች፣ ዘመኑ ያፈራቸው ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችና የመሳሰሉት ድጋፎች
የፕሪቶሪያ ስምምነት ትግበራ ሊፈጥረው የሚችለው የፖለቲካ ኃይል አሠላለፍ ልዩነት
የሰላም ጥረት ገና ሲጀመር ጀምሮና ወደ ፕሪቶሪያ ስምምነትም ሲገባ አርቆ አሳቢ ወገኖች ሒደቶቹ ሁሉንም ወገን አቃፊ እንዲሆኑ ሲወተውቱ ነበር፡፡ በጦርነቱ ተሳታፊ የነበሩ ሁሉም ኃይሎች…
https://www.ethiopianreporter.com/127688/
የኢትዮጵያ አርታኢያን ማኅበር በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን መከታተል የሚያስችለውን ድረ ገጽ ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ አርታኢያን ማኅበር (ኢአማ) በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከታተልና ለመመዝገብ የሚያስችል ድረ ገጽ ወይም ‹‹ፖርታል›› አዘጋጅቶ በሥራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ፡፡ ማኅበሩ በአገር አቀፍ ደረጃ በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን በመከታተልና በመመዝገብ በየሦስት…
https://www.ethiopianreporter.com/127631/
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ሐኪሞች በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ ማከም መቸገራቸውን ተናገሩ
‹‹ሆስፒታሉ ማስተማሪያ እንጂ ሙሉ በሙሉ ሕክምና የመስጠት ግዴታ የለበትም›› ጅማ ዩኒቨርሲቲ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሕክምና መስጫ ዕቃዎችና መድኃኒቶች እጥረት በመፈጠሩ፣ ታካሚዎችን ማስተናገድ የማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል ሲሉ የሕክምና ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የሚሠሩ ስማቸው…
https://www.ethiopianreporter.com/127634/
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሕጎችን እንድታፀድቅና የሠራተኞች መብት እንዲከበር ተጠየቀ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) መንግሥት ሠራተኞችን የተመለከቱ ዓለም አቀፍ ሕጎች እንዲያፀድቅና የሠራተኞችን መብት እንዲያከብር ጥያቄ አቀረበ፡፡ ኢሰመጉ ሐሙስ መጋቢት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ መንግሥት የሠራተኞች ሰብዓዊ መብቶችን አስመልክቶ ልዩ ልዩ የሕግና የተቋማት…
https://www.ethiopianreporter.com/127641/
በትግራይ ክልል በጦርነት ንብረታቸው የወደመባቸው ባለሀብቶች ብድር የሚከፍሉበት ጊዜ እንዲራዘምላቸው ጠየቁ
በትግራይ ክልል በጦርነቱ ንብረታቸው የወደመባቸው ባለሀብቶች ከጦርነቱ በኋላ ምንም ዓይነት የሥራ እንቅስቃሴ ማድረግ ስላልቻሉ፣ ከተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ሌላ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጣቸው ጥያቄ አቀረቡ፡፡ የትግራይ ክልል ባለሀብቶች ጥያቄውን ያቀረቡት ዓርብ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. በጠቅላይ…
https://www.ethiopianreporter.com/127653/
‹‹እንኳን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት የአገሪቱ ህልውናም እንዴት ነው ተጠብቆ የሚቀጥለው የሚለው ጉዳይ ጥያቄ እየሆነ መጥቷል›› መላኩ ተገኝ (ዶ/ር)፣ አንጋፋ ፖለቲከኛና ጸሐፊ
‹‹እንኳን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት የአገሪቱ ህልውናም እንዴት ነው ተጠብቆ የሚቀጥለው የሚለው ጉዳይ ጥያቄ እየሆነ መጥቷል›› መላኩ ተገኝ (ዶ/ር)፣ አንጋፋ ፖለቲከኛና ጸሐፊ – ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best And Reliable News Source In Ethiopia
የሕግ የበላይነት አለመከበርና ሌሎች ምክንያቶች ለሰላምና ለደኅንነት ፈተና መሆናቸውን የፍትሕ ሚኒስትሩ አስታወቁ
በፅዮን ታደሰ የፍትሕ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የሕግ የበላይነት አለመከበር፣ ሙስና፣ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሠራጩ ሐሰተኛ መረጃዎች፣ እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በሚከሰት የድርቅና የጎርፍ አደጋ፣ ለሰላምና ለደኅንነት ፈተና መሆናቸውን አስታውቁ፡፡ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ዓለም አቀፍ የልማት…
https://www.ethiopianreporter.com/127637/
በፓርላማ በተፎካካሪ ፓርቲ ተይዞ የነበረው የመንግሥት ወጪ ቁጥጥር ሰብሳቢነት ለብልፅግና ተሰጠ
የአቶ ክርስቲያን ታደለ ያለ መከሰስ መብት ሲነሳ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በዋስ ከእስር ተለቀዋል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለረዥም ዓመታት በምርጫ አሸንፈው ፓርላማውን ለተቀላቀሉ ተፎካካሪና አጋር የፖለቲካ ፓርቲ አባላት በመስጠት ሲሠራበት የነበረውን፣ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና…
https://www.ethiopianreporter.com/127655/
በዮናስ አማረ
ኒቫዳ ግዛት በአሜሪካ ለመናፈሻ እየተባለ የሚተከል የሳር መስክን በመከልከል የመጀመሪያዋ ግዛት መባሏን፣ ቢዝነስ ኢንሳይደር ከዘጠኝ ወራት በፊት በለቀቀው አጭር ዶክመንተሪ መግለጹ ይታወሳል፡፡ ናሽናል ጂኦግራፊ ከስምንት ዓመታት በፊት በሠራው ዘጋቢ ፊልም፣ በካሊፎርኒያም ቢሆን ለምለም የሳር መስክ መናፈሻ መሥራት እየቀረ የመጣ ፋሽን ስለመሆኑ ይተርካል፡፡ በአሜሪካ በተለይ ሞቃታማ በሚባሉ ምዕራባዊ የአገሪቱ ክፍሎች የሳር መናፈሻ መሥራት እየተተወ የመጣ መሆኑ ይነገራል፡፡ ይህ የሆነው ደግሞ በእነዚህ የአገሪቱ ክፍሎች የሕዝብ ቁጥር መጨመርና የከተሜነት መስፋፋት ብቻ ሳይሆን፣ ከአሥር ዓመታት በላይ በአካባቢው በተከሰተው ድርቅ አስገዳጅነትና በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ጭምር መሆኑን የተለያዩ ዘገባዎች ይጠቁማሉ፡፡
የአሜሪካ ቱጃሮች የግል ጎልፍ ሜዳ በመገንባት ሰፊ ሔክታር መሬት ሳር ያለብሳሉ፡፡ የሌላቸው ደግሞ በቅጥር ግቢያቸው ወይም በደጃቸው ያለ መሬትን ሳር ማልበሳቸው የተለመደ ነው፡፡ የከተማ ማዘጋጃ ቤቶች፣ የመንገድና የመናፈሻዎች ልማት የሚመለከታቸው ሁሉ ብዙ ቦታዎችን በሳር መሸፈን ልማዳቸው ሆኖ መቆየቱ ይነገራል፡፡ ይህ ሁሉ በየቦታው መሬቱን የሳር መስክ ለማልበስ የሚደረግ ጥረት ደግሞ፣ በየቀኑ 34 ቢሊዮን ሊትር ውኃ የሚፈልግ ሥራ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ በአሜሪካ በአየር ንብረት ለውጥና በድርቅ ተፅዕኖ የተነሳ ይህን እያደረጉ መቀጠል አገሪቱን ለኪሳራ እንደዳረገ ይነገራል፡፡ ሳር ማብቀል ከፍተኛ የመስኖ ውኃ የሚጠይቅ በመሆኑ፣ ዜጎች ድርቅ የሚቋቋሙ ተክሎችን በምትኩ ለመናፈሻና ለውበት እንዲጠቀሙ ግፊትና ግዴታ መደረግ ስለመጀመሩ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ሲዘገብ ቆይቷል፡፡
በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየቦታው በለመለመ ሳር እንዲሸፈኑ የሚደረጉ መናፈሻዎችና የመንገድ ዳር ልማቶች ይታያሉ፡፡ ኢትዮጵያ ድርቅ ደጋግሞ
አሜሪካ አልሸባብን በመደገፍ በተጠረጠሩ በተባበሩት ኤምሬትስና በሌሎች አገሮች ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጣለች
የአሜሪካ ግምጃ ቤት የውጭ ሀብት ቁጥጥር ቢሮ (OFAC) ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ላለውና በሶማሊያ ለሚንቀሳቀሰው አልሸባብ የሽብር ቡድን ገንዘብ በሚያሰባስቡና በሚያንቀሳቅሱ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ፣ ኬንያና ኡጋንዳ 16 ኩባንያዎችና ግለሰቦች ላይ፣ ሰኞ መጋቢት 2 ቀን 2016…
https://www.ethiopianreporter.com/127543/
በሕዝብ በዓላት አከባባር ወቅት በሕግ የተደነገገ ሰንደቅ ዓላማ እንዲውለበለብ ጥያቄ ቀረበ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝብ በዓላትንና የበዓላት አከባባርን ለመወሰን በወጣው ረቂቅ አዋጅ ላይ ባደረገው ውይይት፣ በሕዝብ በዓላት ወቅት በሕግ የተደነገገ ባንዲራ እንዲውለበለብ ጥያቄ ቀረበ፡፡ ለዓመቱ አጋማሽ ዕረፍት ወጥቶ የተመለሰው ምክር ቤቱ በ16ኛ መደበኛ ስብሰባው በረቂቁ…
https://www.ethiopianreporter.com/127547/
የአደገኛ ቦዘኔ መቆጣጠሪያ አዋጅ የሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ ቀረበበት
መንግሥት አደገኛ ቦዘኔነት ‹‹እየጨመረና እየተስፋፋ›› በመሄድ ላይ ነው በማለት ከ20 ዓመታት በፊት ባወጣው የአደገኛ ቦዘኔ መቆጣጠሪያ አዋጅ ውስጥ፣ የዋስትና መብትን የሚነፍገው ድንጋጌ ሕገ መንግሥቱን የሚሰጥ ነው ተብሎ የሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ ቀረበበት፡፡ አደገኛ ቦዘኔነትን ለመቆጣጠር…
https://www.ethiopianreporter.com/127557/
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሠሩ የአውሮፓ ኢንቨስተሮች የመሬትና የቢሮክራሲ ማነቆዎች እንዳስቸገራቸው ገለጹ
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሠሩ የአውሮፓ ኢንቨስተሮች ከመሬትና ከቢሮክራሲ ጋር የተያያዙ ማነቆዎች ሊያሠሯቸው እንዳልቻሉ አስታወቁ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙና ወደፊት መጥተው መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ ዕቅድ ያላቸው አውሮፓውያን ባለሀብቶች መሬት ለማግኘት ከፍተኛ ቢሮክራሲ እንደሚገጥማቸው፣ ውሳኔ ለማግኘት ረዥም ጊዜ…
https://www.ethiopianreporter.com/127565/
ኢሠማኮ ለመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ወለል ማስተካከያና የግብር ቅነሳ ጥያቄ እንደገና እንደሚያቀርብ አስታወቀ
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) የመንግሥት ሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ማስተካከልና የግብር ቅነሳን በተመለከተ ያቀረበው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ ካላገኘ፣ እንደገና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ እንደሚያስገባ አስታወቀ፡፡ ኢሠማኮ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል መጠን እንዲወሰንና በሠራተኞች ላይ የተጫነው ግብር…
https://www.ethiopianreporter.com/127562/
በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶች አገራዊ የምክክር መድረክ ማስጀመር አለማስቻላቸው ተነገረ
በፅዮን ታደሰ የአገራዊ የምክክር ኮሚሽን የውይይት መድረኩን በ2016 ዓ.ም. አጋማሽ ለማካሄድ ዕቅድ ይዞ የነበረ ቢሆንም፣ በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ማስጀመር አለመቻሉ ተገለጸ። በአማራ ክልልና በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ ግጭትና በትግራይ ክልል ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት፣…
https://www.ethiopianreporter.com/127568/
ኢትዮጵያ ውስጥ አንዱ ሌላውን ጠልፎ ለመጣል የተደረጉ የሴራ ፖለቲካ ልፊያዎች ጦሳቸው ዛሬም አገርን እየለበለበ ነው፡፡ የሴራ ፖለቲካ ማዕከላዊ ማንጠንጠኛው ሥልጣን ሲሆን፣ የሥልጣን ሉዓላዊ ባለቤት መሆን የሚገባው ሕዝብ ደግሞ የሴረኞች መቀለጃ ነው፡፡ ለዚህ ማስረጃ የሚሆነው ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ዴሞክራሲ የሚባለው ጽንሰ ሐሳብ በሕዝብ ላይ ለመቀለድ ማገልገሉ ነው፡፡ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሥርዓት ይቃወሙ የነበሩ የዘመኑ ወጣቶች ከመሬት ለአራሹ እኩል ሲያቀነቅኑ የነበሩት፣ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የማነፅን አስፈላጊነት ነበር፡፡ የንጉሠ ነገሥቱ ሥርዓት በየካቲት 1966 ዓ.ም. ግብታዊ አብዮት ከተወገደ በኋላ የተፈለፈሉት የፖለቲካ ኃይሎችም ሆኑ ነፃ አውጭዎች፣ ከመጠሪያቸው ጋር ተቆራኝቶ የዘለቀው ዴሞክራሲ ከግብራቸው ጋር ሲመሳሰል አልታየም፡፡ ብዙዎቹ ሕዝባዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊ፣ ሪፐብሊካዊና የመሳሰሉ ተራማጅ መለያዎች ቢያነግቡም ከመጠሪያቸው ጋር የሚያመሳስላቸው አንዳችም ነገር አልነበረም፣ ዛሬም የለም፡፡ የሁሉም መነሻና መድረሻ እስኪመስል ድረስ ሴረኝነት ነበር የሚገልጻቸው፡፡
አሁንም ሆነ በፊት በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ንድፈ ሐሳባዊ መሠረቶች ላይ ንባቡም ሆነ ትርጓሜው አንድ ነው፡፡ ተግባር ላይ ሲገባ ግን ‹‹ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ›› እንደሚባለው፣ ከውስጣዊ አደረጃጀት እስከ ውጫዊ መስተጋብር ድረስ የብዙዎቹ ባህሪ አንድ ዓይነት ነው፡፡ በሐሳብ መለያየት ሞት አይደለም በሚባልበት ዓለም ውስጥ፣ አንዱ የሌላውን ሐሳብ በጨዋነትና በስክነት ለማስተናገድ ይተናነቀዋል፡፡ ሥልጣን ላይ ያለው መንበሩ እንዳይነቀነቅበት አንዳችም ዓይነት ተቃውሞ መስማት አይፈልግም፡፡ ለሥልጣን የሚታገለውም እንቅስቃሴውን ሲያካሂድ ተቃውሞ እንዲቀርብበት አይሻም፡፡ ሥልጣኑን የሚዘውረው ተቃውሞን አዳፍኖ የሚፈልገውን ዓላማ ለማሳካት እንዳሻው መሆን ስለሚፈልግ አምባገነን ይሆናል፡፡ ሥልጣን ፈላጊው የውጭውን ቀርቶ በውስጥ የሚነሱ ጥያቄዎችን
አሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋ ማይክ ሐመርን ወደ አዲስ አበባ ልካለች፡፡ ከሐሙስ የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ መጪው ረቡዕ መጋቢት 4 ቀን 2016 ዓ.ም. በሚካሄደው የፕሪቶሪያ ስምምነት አተገባበር መገምገሚያ ስብሰባ ላይ፣ ስምምነቱን ፈራሚዎች ብቻ ሳይሆኑ አደራዳሪዎቹም ይታደሙበታል፡፡ በዚህ ስብሰባ በሕወሓትና በፌዴራል መንግሥት መካከል የተፈረመው የፕራቶሪያ ስምምነት የትግበራ ሒደት ምን እንደሚመስል አንድ በአንድ እንደሚገመገም ተነግሯል፡፡
በዚህ ግምገማ ደግሞ የስምምነቱ አንድ አንቀጽ የያዘው የታጠቁ ኃይሎችን ትጥቅ የማስፈታትና መልሶ የማቋቋም ጉዳይ ይገመገማል ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡፡ የታጠቁ ኃይሎችን ትጥቅ የማስፈታትና መልሶ የማቋቋም ሥራ ለረጅም ጊዜ መንግሥትና ሕወሓትን ሲያወዛግብ የቆየና ብዙ መጓተት የገጠመው መሆኑ ተደጋግሞ ይወሳል፡፡ መንግሥት የሕወሓት ኃይሎችን ሆን ብሎ ትጥቅ ሳያስፈታ እንደቆየ ሲወቀስ ቆይቷል፡፡ በተቃራኒው ብዙ ሰበቦችን እየደረደረ ጦሩን ትጥቅ ሳያስፈታ ደብቆ ያቆየው ሕወሓት ነው በሚል ወቀሳ ይቀርባል፡፡ ሁለቱ ወገኖች ከሚሰጧቸውና እርስ በርስ የመወቃቀስ ይዘት ካላቸው አመክንዮዎች በዘለለ ደግሞ፣ ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሥራ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ በመሆኑ ተፈጻሚ እንዳልሆነ በርካቶች ይናገራሉ፡፡
ይህን ምክንያት የሚያቀርቡ ወገኖች ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታት ሥራው በትግራይ ሸማቂዎች ብቻ የተገደበ ሳይሆን በጋምቤላም፣ በቤኒሻንጉልም፣ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎችም የሚሠራ ሰፊ አገር አቀፍ ዕቅድ መሆኑን ያነሳሉ፡፡ ይህን ዜጎችን ከመሣሪያ በመነጠል ሥልጠና ሰጥቶ ወደ መደበኛ ሕይወት እንዲገቡ የማድረግ ጥረት የሚጠይቅ ሥራን ደግሞ፣ መንግሥት ብቻውን መወጣት እንደማይችል ብዙዎች ይናገራሉ፡፡ ለዚህ የፕሪቶሪያ ስምምነት አካል ለሆነ ጉዳይ የውጭ የልማት አጋሮች፣ በተለይም ድርድሩ ላይ የነበሩ አደራዳሪዎች እንደሚደግፉት
የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ መመርያ ፀድቆ ሥራ ላይ ዋለ
የትምህርት ሚኒስቴር ‹‹ለትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥና ለአቻ ግመታ›› የወጣ መመርያ ፀድቆ ሥራ ላይ መዋሉን አስታወቀ፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ.ም. በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ፊርማ ለትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በላከው የመሸኛ ደብዳቤ እንዳስታወቀው፣ መመርያው…
https://www.ethiopianreporter.com/127448/
ሰንሻይንና የቻይናው ሲሲሲሲ የአየር መንገድ ሠራተኞች ቤቶችን በ460 ሚሊዮን ዶላር ሊገነቡ ነው
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ ከ35 ዓመታት በላይ የዘለቀው ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኩባንያ፣ ከቻይናው ሲሲሲሲ ኩባንያ ጋር በመሆን ከ460 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ይጠይቃል የተባለውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ቅዳሜ የካቲት 30 ቀን…
https://www.ethiopianreporter.com/127456/
ቡና አቅራቢዎች ክፍያ እየተፈጸመላቸው ባለመሆኑ ከገበያ ለመውጣት መገደዳቸውን አስታወቁ
ቡናና ሻይ ባለሥልጣን በአምስት ኤክስፖርተሮች ላይ ዕርምጃ ወስጃለሁ አለ ቡና አቅራቢዎች ቡናቸውን ለኤክስፖርተሮች ሲያቀርቡ ክፍያ በትክክለኛው መንገድ ስለማይፈጸምላቸውና ከባንኮች ብድር በአግባቡ ስለማያገኙ፣ ከገበያ ለመውጣት መገደዳቸውን ተናገሩ፡፡ ቡና አቅራቢዎቹ ይህንን የተናገሩት ዓርብ የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም….
https://www.ethiopianreporter.com/127460/
ዕንባ ጠባቂ ተቋም ቤቶች ኮርፖሬሽን ባወጣው የመኖሪያ ቤቶች ጨረታ ላይ የሕጋዊነት ጥያቄ አነሳ
የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የ1997 ዓ.ም. የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ዕጣ ያልወጣላቸው ቆጣቢዎች ያቀረቡለትን አቤቱታ መሠረት በማድረግ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከሦስት ሺሕ ቤቶች በላይ በሽያጭ ለማስተላለፍ ያወጣው ጨረታ ላይ…
https://www.ethiopianreporter.com/127463/
የኤርትራ ወታደሮች በሽግግር ፍትሕ በሚቋቋመው ልዩ ፍርድ ቤት ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥያቄ ቀረበ
በሚቋቋመው ልዩ ፍርድ ቤት የውጭ አገር ባለሙያዎች እንዲካተቱ ተጠይቋል በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ‹‹በጦር ወንጀልና ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት የተሳተፉ›› የኤርትራ ወታደሮች ጉዳይ በሌሉበትም ቢሆን፣ በሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ በሚቋቋመው ልዩ ፍርድ ቤት ሊታይና ተጠያቂነታቸውም ሊረጋገጥ…
https://www.ethiopianreporter.com/127466/
“መሬታችን በመንግስት እየተወሰደብን ነው” የምዕራብ ሸዋ ዞን ናኑ ወረዳ ነዋሪዎች
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ናኑ ወረዳ ልዩ ስሙ ናኑ ጉዲና ቀበሌ 01 ‘መዳሎ’ አካባቢ “ግብር የምንከፍልበት እና ሕጋዊ ካርታ ያለውን ንብረታችንን ከ2 ሄክታር መሬት በላይ መያዝ አትችሉም በማለት የተቀረውን ሰብስበው ላመጧቸው ወጣቶች እየሰጡ መሆኑን” ጠቁመዋል።
እንደ ነዋሪዎቹ ገለጻ፤ የአካባቢው ሚሊሻዎች ከባድ መሳሪያ በመታጠቅ አጅበው ያመጧቸው ወጣቶች ደግሞ “ስለት እና መሰል መሳሪያዎችን በማስያዝ ማህበረሰቡን እያስፈራሩና ባስ ሲል… https://addismaleda.com/archives/36275
ታላቁ የዓድዋ ድል 128ኛ ዓመት ክብረ በዓልን አስመልክቶ በዕለቱም ሆነ በዋዜማው በነበሩ ቀናት ጎልተው ከተሰሙ ጉዳዮች መካከል፣ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ህልውና የመጣባቸውን ጠላት ለመመከት ሲሉ ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን ማድረግ የተካኑበት እሴታቸው መሆኑ ተጠቃሽ ነበር፡፡ የአገር መሪም ሆነ በየቦታው ያለ አስተዳዳሪ፣ እንዲሁም መላው ሕዝብ በሰላሙ ጊዜ ስምምነት ባይኖራቸውም በአገር ጉዳይ ግን አንድ መሆን ያለና የነበረ ባህል እንደሆነ ተደጋግሞ ተጠቅሷል፡፡ በእርግጥም በአገር ጉዳይ አንድ መሆን አለመቻል ይዞት ሊመጣ የሚችለው መዘዝ እንደ ቀልድ የሚታይ አይደለም፡፡ በመደበኛው ሕይወት ሊስማሙ ያልቻሉ የውጭ ጠላት ሲመጣ አንድ ላይ መቆማቸው ለአገር ህልውና ዋልታና ማገር መሆኑ በስፋት ይነገራል፡፡ ጀምስ ብሩስ የተባለ አገር አሳሽም ይህንን ሀቅ በጉዞ ማስታወሻው ከትቦታል፡፡ ‹‹…በሰላም ጊዜ በአጥንት እንደሚጣሉ ውሾች እርስ በርሳቸው የሚናከሱት ኢትዮጵያውያን፣ የውጭ ጠላት ሲመጣ ግን በአንድነት ተሠልፈው ይደቁሱታል…›› ማለቱ በተደጋጋሚ የተነገረ ታሪክ ነው፡፡
በዚህ ዘመን ትውልድም በተደጋጋሚ የሚስተዋለው ልዩነት ግን ከጥንቱ ጋር ይመሳሰላል ለማለት እያዳገተ ነው፡፡ ቀደም ሲል በነገሥታቱ፣ በመሣፍንቱና በሰፊው ሕዝብ መካከል የሚኖረው ልዩነት አገርን በጋራ ከመጠበቅ አግዶ አያውቅም፡፡ ምናልባት አንዳንድ ግለሰቦች ለጥቅማቸው ሲሉ በባንዳነት ለጠላት ማደራቸው ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በመንግሥት ላይ ያኮረፈ በሙሉ ለጠላት ሲወግን በየትኛውም የታሪክ ምዕራፍ ውስጥ አልተሰማም፡፡ ቅሬታ ወይም ተቃውሞ ያላቸው ግለሰቦች ሸሽተው ጎረቤት ወይም ራቅ ያለ አገር ቢሄዱ እንኳን፣ ብሔራዊ ደኅንነትንና ጥቅምን አሳልፎ የሚያሰጥ ድርጊት ውስጥ ሲሳተፉ አይታወቅም፡፡ በጣም ጥቂት ግለሰቦች በአዋራጅ ድርጊት ውስጥ በመሳተፋቸው ዘር ማን ዘራቸው
የዲጂታል ዕውቅና ያለው የመጀመሪያ ዲግሪ ወይም የድኅረ ምረቃ የሚሰጥ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ የለም ተባለ
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአይሲቲ መሠረተ ልማትን በማሳደግ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ቢያደርጉም፣ በአሁኑ ጊዜ በዲጂታል መርሐ ግብር ዕውቅና ያለው የመጀመሪያ ዲግሪ ወይም የድኅረ ምረቃ ትምህርት የሚሰጥ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ እንደሌለ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው…
https://www.ethiopianreporter.com/127356/
ፐርፐዝ ብላክ ቢጂአይ ኢትዮጵያ የሽያጭ ውሉን ካልፈረመ ክስ ሊመሠርት እንደሚችል ገለጸ
ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማኅበር ከቢጂአይ ኢትዮጵያ ጋር ያደረገው የዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ ሽያጭ ውል በድንገት በመቋረጡ፣ ክስ እንደሚመሠርት አስታወቀ፡፡ ፐርፐዝ ብላክ ሜክሲኮ ከተግባረዕድ ኮሌጅ አጠገብ የሚገኘውና ከቢጂአይ ኢትዮጵያ ለመግዛት የተስማማውን የዋና መሥሪያ ቤት…
https://www.ethiopianreporter.com/127365/
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ‹‹በታሪኩ›› ለመጀመሪያ ጊዜ ግዙፍ 20 አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከቦይንግ ጋር ተፈራረመ
የአውሮፕላኖቹ ዋጋ እስከ 11 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት ተገልጿል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ‹በታሪኩ› ካሉት አውሮፕላኖች ግዙፍ ናቸው ያላቸውን እስከ 20 የሚደርሱ የቦይንግ 777-9 አውሮፕላኖች ለመግዛት ከቦይንግ ኩባንያ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡ በትናንትናው ዕለት የካቲት 26 ቀን 2016…
https://www.ethiopianreporter.com/127368/
የከተማ አስተዳደሩን የብቃት መለኪያ ፈተና የወደቁ ሠራተኞች ከደረጃቸው ዝቅ ያሉበት ድልድል ይፋ ሊደረግ ነው
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ሠራተኞችና አመራሮች የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ወስደው የወደቁ ከ7,500 በላይ ሠራተኞች፣ ከደረጃ ዝቅ ተደርገው የተመደቡበት የሥራ ዕርከን ድልድል መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ እንደሚደረግ፣ የከተማው የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት…
https://www.ethiopianreporter.com/127371/
በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ተጀምሮ አማራና አፋር ክልሎችን ያዳረሰው የሁለት ዓመቱ አውዳሚ ጦርነት በፕሪቶሪያ ስምምነት ቢገታም፣ ከነሐሴ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል የተጀመረው ጦርነት ግን እንደ ቀጠለ ነው፡፡ ከአማራ ክልል በተጨማሪ ኦሮሚያ ውስጥም በተለያዩ አካባቢዎች ውጊያ እየተካሄደ ነው፡፡ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በመቶ ሺዎች አልቀው፣ ሚሊዮኖች ተፈናቅለው፣ ቁጥራቸው የበዛ ዜጎች የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጽሞባቸው፣ ሕፃናት፣ ሴቶች፣ አረጋውያንና አቅመ ደካሞች አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳቶች ደርሰውባቸውና በአገር ኢኮኖሚ ላይ መጠነ ሰፊ ውድመት ደርሶ በፕሪቶሪያ ስምምነት መገታቱ ትልቅ ዕፎይታ ፈጥሮ ነበር፡፡ ከአንዴም ሁለቴ በፌዴራል መንግሥትና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት (ኦነግ ሸኔ) መካከል የሰላም ንግግር ቢጀመርም፣ በበርካቶች ዘንድ ተፈጥሮ የነበረው ተስፋ ንግግሩ በመቋረጡ እንደ ጉም ነበር የበነነው፡፡ በአማራ ክልል ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መልስ የክልሉን ልዩ ኃይልና ኢመደበኛ አደረጃጀት ትጥቅ ለማስፈታት የተደረገው ጥረት ተቃውሞ በመቀስቀሱ፣ የለየለት ጦርነት ውስጥ ከተገባ ሰባት ወራት ተቆጥረዋል፡፡
በቅርቡ አዲስ አበባን ጨምሮ በአማራና በኦሮሚያ ክልል ተካሂደው በነበሩ ሕዝባዊ ውይይቶች ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል፣ የአገር ሰላምና ፀጥታ ጉዳይ ብዙዎችን ያሳሳበ ዋነኛ ጉዳይ ነበር፡፡ የአገር ሰላም ዕጦትን አስመልክቶ ጥያቄ ካቀረቡ የስብሰባዎቹ ተሳታፊዎች መገንዘብ እንደተቻለው፣ በየቦታው የሚካሄዱ ጦርነቶችንም ሆነ ግጭቶችን ማስቆም ለምን አቃተ የሚለው እንቆቅልሽ ለምን እንደማይፈታ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በሁሉም አካባቢዎች በማኅበረሰቦችም ሆነ በግለሰቦች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት፣ እንደ ባህሉና እምነቱ መሠረት የሚከናወኑ የግጭት ማስወገድና የዕርቅ ዘዴዎች ከበቂ በላይ ይታወቃሉ፡፡ እንዲህ ዓይነት ነባር አገር በቀል
ዮናስ አማረ
የኢትዮጵያ ሕዝቦች የዴሞክራሲ ለውጥ ጥያቄ የሚነሳው ከፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ማግሥት ጀምሮ እንደሆነ በርካታ የታሪክ መዛግብት አስፍረዋል፡፡ ለሺሕ ዓመታት የቆየውን ዘውዳዊ መንግሥት መነቅነቅ የጀመሩ የፖለቲካ ቡድኖች የተነሱት በፋሺስት ወረራ ማግሥት ነው ይባላል፡፡ በግለሰብ ደረጃ ዜጎች የፖለቲካ ለውጥ ሲጠይቁ መታየት የጀመሩት በዚሁ ወቅት መሆኑን ብዙዎች ይገልጻሉ፡፡ በተናጠል ከሚነሱ ጥያቄዎች እስከ ሥር ነቀል የፖለቲካ ለውጥ ጥያቄ በብዙ መንገዶች የሕዝብ ብሶቶች መስተጋባት የጀመሩት ከፋሺስት ወረራ በኋላ መሆኑ በስፋት ይወሳል፡፡
ይህ ዑደት ደግሞ ወደ ተማሪዎች እንቅስቃሴ እስኪሸጋገር ድረስ በነበሩት ዓመታት፣ በግልም በቡድንም ሆነው ነፃነትን የጠየቁና መስዋዕትነት የከፈሉ የታዩበት እንደሆነ በብዙ ጸሐፍት ተከትቧል፡፡
ባህሩ ዘውዴ (ፕሮፌሰር)፣ ‹‹የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847-1983›› በሚለው መጽሐፋቸው በኢትዮጵያ ታሪክ በአፄ ኃይለ ሥላሴ ላይ ተቃውሞ በማንሳት እንደ ብላታ ታከለ ወልደ ሐዋሪያት ዓይነት ሰዎች ቀዳሚ እንደሆኑ ያወሳሉ፡፡ ከአልጋ ወራሽነታቸው ጀምሮ የንጉሡ አገልጋይ የነበሩት ብላታ ታከለ በጣሊያን ወረራ ወቅት ንጉሡ ከአገር መሸሻቸው እንዳስከፋቸው ታሪክ ጸሐፊው ይጠቅሳሉ፡፡ በዚህ ያቄሙት ብላታ ታከለ ከድል በኋላ የንጉሡን መመለስም ተቃውመዋል፡፡ በተለይ ሀቀኛ አርበኞች ወደ ጎን ተብለው ባንዳ የነበሩትን ንጉሡ መሰብሰባቸው እንዳስቆጣቸው ይነገራል፡፡ በህቡህ ተቃውሞ ሲያደራጁ እየተያዙ በተደጋጋሚ ታሰሩ፡፡ ከእስር ባለፈ መንግሥት ተቃውሞ እንዲተው በሹመትና በጥቅም ሊደልላቸው ሞከረ፡፡ ሆኖም ንጉሡን አምርረው የጠሉት ብላታ ታከለ በ1962 በንጉሡ ላይ ቦምብ በመወርወር የግድያ ሙከራ አደረጉ በማለት መጽሐፉ ይተርካል፡፡ በዚሁ ንጉሡን የማስወገድ ጥረታቸው በፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን የሚገልጸው መጽሐፉ፣ ብላታ ታከለ ለ30 ዓመታት ንጉሡን
ፕላስቲክን መልሶ መጠቀም እንዲያስችል የተረቀቀ ሕግ በፍጥነት ፀድቆ ሥራ ላይ እንዲውል ተጠየቀ
ከፕላስቲክ መልሶ መጠቀም ሊገኙ የሚችሉ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጥቅሞችን ለማሳደግ የሚያስችሉ ረቂቅ ሕጎች፣ በፍጥነት ፀድቀው ወደ ሥራ እንዲገቡ ተጠየቀ፡፡ በየዓመቱ እስከ 380 ሺሕ ቶን የፕላስቲክ ቆሻሻ በምታመነጨው ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ቆሻሻን በሁሉም ደረጃ መልሶ ለማስጠቀም የሚያስችሉ…
https://www.ethiopianreporter.com/127238/
ከአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ ፍጥነት ጋር ሊራመድ የሚችል የሕግ ሥርዓት እንደሚያስፈልግ ተነገረ
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ የመጣውን አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ (ሰው ሠራሽ አስተውሎት) ሊገዛ የሚችል የሕግ ሥርዓት እንደሚያስፈልጋት ተገለጸ፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአውሮፓ ኅብረት ጋር በጋራ የተሰናዳ የቢዝነስ ከባቢና ዲጂታል ኢትዮጵያ ኮንፈረንስ የካቲት 21 ቀን 2016…
https://www.ethiopianreporter.com/127242/
የአበባ ምርት 60 በመቶ ለውጭ ገበያ የሚያቀርቡ የሰባት ኩባንያዎች እርሻዎች በተባይ መጠቃታቸው ተነገረ
የአበባ እርሻዎችን ሙሉ በሙሉ ከተባይ ማፅዳት አይቻልም ተብሏል ለውጭ ገበያ 60 በመቶ የአበባ ምርት የሚልኩ የሰባት ኩባንያዎች የአበባ እርሻ በከፍተኛ የ‹‹እሳት እራት›› በተሰኘ ተባይ መጠቃቱን፣ የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡ ባለሥልጣኑ ይህንን ያስታወቀው ከኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር አምራችና ላኪዎች…
https://www.ethiopianreporter.com/127232/
የኤርትራ መንግሥት ‹‹ወታደሮቼ በኢትዮጵያ ምድር የሉም›› አለ
ሕወሓት 270 ሺሕ የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ አላስፈታም ሲልም ከሷል በለንደን የሚገኘው የኤርትራ፣ የእንግሊዝና የአየርላንድ ኤምባሲ የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ የኤርትራ ወታደሮች በሉዓላዊ የኤርትራ ግዛቶች ውስጥ መሆናቸውንና በኢትዮጵያ ምድር አይገኙም በማለት አስታወቀ፡፡ ለመግለጽ አስቸጋሪ…
https://www.ethiopianreporter.com/127244/
በአክሲዮን አሻሻጥ ላይ የተሠሩ ወንጀሎችን ወደኋላ በመመለስ ምርምራ ይደረጋል ተባለ
በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን አነሳሽነት የተዋቀረው በርካታ የመንግሥት ተቋማት ያሉበት የካፒታል ገበያ ተዓማኒነት ግብረ ኃይል፣ በአክሲዮን መሸጥና መግዛት ላይ የተሠሩ ወንጀሎችን ወደኋላ በመመለስ እንደሚመረምር ተገለጸ፡፡ ባለሥልጣኑ፣ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ እንዲሁም…
https://www.ethiopianreporter.com/127249/
ምርጫ ቦርድ ፓርላማው ያፀደቀለትን 304 ሚሊዮን ብር አለማግኘቱን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ሰኔ 2016 ዓ.ም. በአራት ክልሎች ሊያካሂደው ላቀደው ምርጫ የሚያስፈልገውን 304 ሚሊዮን ብር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያፀደቀለት ቢሆንም እስካሁን እንዳላገኘ አስታወቀ፡፡ በ2013 ዓ.ም. በተካሄደው አገራዊ ምርጫ በቦርዱ ውሳኔ ምርጫ ባልተካሄደባቸውና…
https://www.ethiopianreporter.com/127255/
በአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ላይ ምርመራ እንዲደረግ ውሳኔ ተላለፈ
ፕሬዚዳንቷና ዋና ጸሐፊው ተጠያቂ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሏል ከአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የዳይሬክተሮች ቦርድ ዕውቅናና ውሳኔ ውጪ፣ በምክር ቤቱ ላይ የተለያዩ ሕገወጥ ተግባራት ተፈጽመዋል በማለት፣ የኦዲት ምርመራ እንዲደረግ የምክር ቤቱ ዳሬክተሮች ቦርድ ውሳኔ…
https://www.ethiopianreporter.com/127259/
የታላቁ ዓድዋ ድል 128ኛ ዓመት ክብረ በዓል ሲዘከር፣ ለአገርና ለሕዝብ ክብር የሚመጥኑ ተግባራት ላይ ማተኮር ይገባል፡፡ በዓድዋ ከወራሪው ኮሎኒያሊስት ኃይል ጋር ተፋልመው ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ አይረሴ አሻራ ያሳረፉ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን በዚህ ዘመን ሲታወሱ፣ የእነሱን የአገር ፍቅር ስሜትና የሞራል ልዕልና የሚመጥን ካልሆነ የዘመኑ ትውልድ የታሪክ ተጠያቂ ይሆናል፡፡ ጀግኖቹ የታላቁ የዓድዋ ድል ባለቤቶች በዳግማዊ ምኒልክና በእቴጌ ጣይቱ መሪነት ዓለምን ያስደነቀ ተጋድሎ ያደረጉት፣ በዘመኑ የነበሩ ውስጣዊ ሽኩቻዎችንና አለመግባባቶችን ከአገር ፍቅር ስሜት በታች በማድረግ በአንድነት ለመቆም በመቻላቸው ነው፡፡ ይህንን የመሰለ አርቆ አሳቢነትና አስተዋይነት የነበራቸው ጀግኖቹ የዓድዋ ድል ባለታሪኮች፣ ማንኛውም ዓይነት ልዩነት ከእናት አገራቸው በታች መሆኑን ለመገንዘብ የሚያስችል ከፍተኛ ሞራላዊ ልዕልና ስለነበራቸው ነው፡፡ የዚህ ዘመን ትውልድ አባላት አገር ከሚመሩ ግለሰቦች ጀምሮ እስከ ተርታው ዜጋ ድረስ፣ የዓድዋ ጀግኖችን የሞራል ከፍታ ለመጎናፀፍ የሚያስችል የአገር ፍቅር ስሜት ሊኖራቸው ይገባል፡፡
ታላቁ የዓድዋ ድል ዘወትር እንደሚባለው የኢትዮጵያውያን ወይም የአፍሪካውያን ብቻ ሳይሆን፣ የመላው ዓለም ጥቁር ሕዝቦችና በቅኝ ገዥዎች ሲረገጡ ይኖሩ የነበሩ ሕዝቦች ጭምር የሚጋሩት ነው፡፡ ይህንን የመሰለ አንፀባራቂና ተምሳሌታዊ ፀረ ኮሎኒያሊስት ድል ባለቤት የሆነች አገር ፖለቲከኞች፣ ምሁራን፣ ልሂቃን፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና የተለያዩ ማኅበረሰቦች አባላት ራሳቸውን በቅጡ መመርመር ይኖርባቸዋል፡፡ ታላቁ የዓድዋ ድል ከአራቱም ማዕዘናት የተሰባሰቡ ጀግኖች ኢትዮጵያውያን በጋራ ያስገኙት ድል ነው፡፡ እነዚያ አርቆ አሳቢ ጀግኖች እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎችን ከታጠቀ፣ በቂ የሎጂስቲክስ አቅርቦት ከነበረው፣ ዘመናዊ የትራንስፖርትና የግንኙነት አውታር ከዘረጋ፣ በጦር ሥልቶች
በዮናስ አማረ
የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም. ቢሾፍቱ አቅራቢያ በሚገኘው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አራት ካህናት በግፍ መገደላቸው ተሰማ፡፡ የገዳሙ መጋቢ አባ ተክለ ማርያም አሥራት፣ የገዳሙ ጸሐፊ አባ ኪዳነ ማርያም ጥላሁን፣ የገዳሙ የመጽሐፍ መምህርና ቀዳሽ አባ ገብረ ማርያም አበበ፣ እንዲሁም በአመክሮ የሚኖሩ ኃይለ ማርያም የተባሉ መናኝ በታጠቁ ኃይሎች በግፍ መገደላቸውን ያረጋገጠ ዜና ይፋ ተደረገ፡፡
ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ሌሊት ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ መገደሉ ከተሰማ በኋላ በሻሸመኔ ከተማ በደረሰ ሁከት ከተከሰቱ ቁሳዊ ውድመቶች በጥቂቱ ፎቶ፡- ታምራት ጌታቸው
ዘገባውን በወቅቱ ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቴሌቪዥን፣ ግድያው ኦነግ ሸኔ ተብሎ በሚጠራው የታጠቀ ቡድን መፈጸሙን በወቅቱ ገልጾ ነበር፡፡ ለዚህ ውንጀላ የካቲት 17 ቀን 2016 ዓ.ም. የማስተባበያ መግለጫ ያወጣው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) በግድያው እጁ እንደሌለበት አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቴሌቪዥን ጥቃቱን ኦነግ ሸኔ በሚባለው ቡድን እንደተፈጸመ መዘገቡን የተቃወመው የኦነግ መግለጫ፣ የኦሮሚያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጥቃቱ በኦነግ ሸኔ የተፈጸመ ነው ማለቱንም አጥብቆ ተቃውሞታል፡፡
‹‹ኦነግ በንፁኃንና ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚፈጸም ግድያንና የሰብዓዊ መብት ረገጣን በሁሉም መልኩ መወገዝ እንዳለበት ያምናል፤›› ሲል የኦነግ መግለጫ ይገልጻል፡፡ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የመንግሥት መዋቅሮች የሁሉንም ዜጎች ሕይወትና ደኅንነት የመጠበቅ ግዴታ አለባቸው ሲል የሚጠቁመው መግለጫው፣ በኢትዮጵያ ግን ይህ እንደሌለ አስታውቋል፡፡
ከዚህ ይልቅ ባለፉት አምስት ዓመታት ጥፋትን በሌላ አካል ማላከክና ማጭበርበር በመንግሥት እንደተለመደ
በአፍሪካ ተመሳሳይ የፍልሰት ሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ በአሠራር ላይ ክፍተት መፍጠሩ ተነገረ
የአፍሪካ አገሮች አንድ ዓይነት የፍልሰት አስተደደር ቅኝት ውስጥ ባለመሆናቸውና ተመሳሳይ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ ስለሌላቸው፣ በአሠራር ላይ ክፍተት መፈጠሩን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ ይህንን ያስታወቀው ሰኞ የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም. ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት…
https://www.ethiopianreporter.com/127153/