Home › View all posts by EthiopianReporter.com
Blog Archives
በአማራ ክልል ዋግሕምራ ብሔረሰብ ዞን በተከሰተ ወረርሽኝ ሰዎች እየሞቱ መሆኑ ተነገረ
በአማራ ክልል በዋግሕምራ ብሔረሰብ ዞን በሁለት ወረዳዎች በተቀሰቀሰ ተቅማጥና ትውከት ወረርሽኝ (አተት) የአምስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ ከ300 መቶ በላይ የሚሆኑ ደግሞ መጠቃታቸውን የዞኑ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡ ወረርሽኙ የተቀሰቀሰባቸው ሰሐላ ሰየሞትና ዝቋላ የተባሉት የዞኑ ወረዳዎች ቀደም…
https://www.ethiopianreporter.com/131695/
በትግራይ ክልል በተጀመረ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ባለሥልጣናትን ጨምሮ በርካቶች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ
‹‹ኦፕሬሽኑ የወሰደውን ያህል ጊዜ ይውሰድ ተጠናክሮ ይቀጥላል›› አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት በፅዮን ታደሰ እና በልዋም አታክልቲ በትግራይ ክልል በተጀመረ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ባለሥልጣናትን ጨምሮ በርካቶችን በቁጥጥር ሥር ማዋል ተጠናክሮ መቀጠሉን፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የትግራይ…
https://www.ethiopianreporter.com/131697/
“ከሁለት ሳምንት በፊት ወደ ኤርትራ የማደርገውን በረራ እንዳሳድግ ተጠይቄ ነበር” የኢትዮጵያ አየር መንገድ
ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እንዲያሳድግ የሚጠይቅ ደብዳቤና ፈቃድ ከተሰጠው ከሁለት ሳምንት በኋላ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ሙሉ በሙሉ መታገዱን የሚያሳውቅ ደብዳቤ እንዲደረሰው መደረጉ እንዳስገረመው ገለፀ። የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሐና አጥናፉ…
https://www.ethiopianreporter.com/131778/
የኤርትራን እግድ ተከትሎ አየር መንገድ የሚከተለውን ብሏል።
ውድ መንገደኞቻችን … የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እ.ኤ.አ. 21 ጁላይ 2024 ለአየር መንገዳችን በላከው ደብዳቤ እ.ኤ.አ. ከሴፕቴምበር 30 ቀን 2024 ዓ.ም. ጀምሮ አየር መንገዳችን ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን ሁሉንም በረራ ማገዱን አሳውቆናል። ደብዳቤው ለክልከላ ውሳኔ ያደረሱ ምክንቶችን አልጠቀሰም። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጉዳዩን አስመልክቶ የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንን ለማግኘት ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኝና ጉዳዩም በበጎ መልኩ እልባት እንደሚያገኝ ያለውን ዕምነት ይገልጻል።በዚሁ አጋጣሚ አየር መንገዱ ተጨማሪ መረጃዎች እንደተገኙ ለውድ ደንበኞቹ እንደሚያሳውቅ ለመግለፅ ይወዳል። የኢትዮጵያ አየር መንገድየስታር አልያንስ አባል
‹‹በየቦታው ምርት እየገዙ የሚያከማቹ ከበርቴ ገበሬዎች ተፈጥረዋል››
አቶ ኡስማን ስሩር፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርናና የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ሻሸመኔ ከተማ ማደጋቸውንና መማራቸውን፣ በአግሮ ሜካኒክስ በዲፕሎማ…
https://www.ethiopianreporter.com/131671/
የአቪዬሽን ፈንድ ሊቋቋም መሆኑ ተገለጸ
የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ከሚሰጣቸው አገልግሎቶችና ከመንገደኞች የሚሰበሰብ የሲቪል አቪዬሽን ፈንድ ሊያቋቋም መሆኑ ተገለጸ። በአገሪቱ ያለው የአቪዬሽን ዘርፍ እንቅስቃሴ በየጊዜው እያደገ መምጣቱ ይገለጻል። በዚህም ዘርፉ የሚጠይቀውን መሠረተ ልማት በዕድገቱ እኩል ማሟላት እንዲቻል የአቪዬሽን ፈንድ ማቋቋም አስፈላጊ…
https://www.ethiopianreporter.com/131680/
ሲሞንፔትሮ ሳሊኒ
(እ.ኤ.አ. ከ1932 እስከ 2024) ከለገዳዲ እስከ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ሳሊኒ የሚለው ስም በኢትዮጵያ ግንባታና ገንቢ በተነሱ ቁጥር አብሮ ይነሳል፡፡ በኢትዮጵያ እጁን ካፍታታበት ውኃ ፕሮጀክት ከለገዳዲ እስከ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በብዙ የኮንስትራክሽን ሥራዎች ላይ አሻራውን ያኖረ…
https://www.ethiopianreporter.com/131677/
የአልኮልና ከአልኮል ነፃ መጠጥ አምራቾች በአዳዲስ ሕጎችና በውጭ ምንዛሪ እየተፈተንን ነው አሉ
የአልኮልና ከአልኮል ነፃ መጠጥ አምራቾች መንግሥት በየጊዜው በሚያወጣቸው አዳዲስ ሕጎችና በውጭ ምንዛሪ እጥረት መፈተናቸውንና ከገበያው ለመውጣት መገደዳቸውን ተናገሩ፡፡ አምራቾቹ ይህንን የተናገሩት ኮማሪ ቤቨሬጅ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ ሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም. በዘርፉ የተሰማሩ…
https://www.ethiopianreporter.com/131683/
ወ/ሮ ሜላት ካሳ ሦስተኛ ልጃቸውን ለመውለድ ከሁለት ወራት ያልበለጡ ጊዜያት ቀርቷቸዋል፡፡ በእርግዝና ወራት ለፅንሱና ለእናትየዋ ጤንነት ሲባል ከሕክምና ክትትል በተጨማሪ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ወይም የእግር ጉዞ ማድረግ በጤና ባለሙያዎች የሚሰጥ ምክር ነው፡፡
ወ/ሮ ሜላት ግን ይህንን ለማድረግ አልታደሉም፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ ከሚኖሩበት 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች 13ኛ ፎቅ ላይ ያለ አሳንሰር መውጣትና መውረድ ስለማይችሉ ነው፡፡
![Ethiopian Reporter | ሪፖርተር ሕይወት በአሳንሰር አልባዎቹ የጋራ መኖሪያ ቤቶች | Ethiopian Reporter | ሪፖርተር](http://www.ethiopianreporter.com/wp-content/uploads/2024/07/Cond-5-300x163.jpg)
ነፍሰ ጡሯ 13 ደረጃዎችን ወርደው መመለስ የሰማይ ያህል ይርቅባቸዋል፡፡ ‹‹ከዚህ ሁሉ ውጣ ውረድና ድካም አርፎ መቀመጥ በስንት ጣዕሙ፤›› የሚሉት ወ/ሮ ሜላት፣ የሕክምና ክትትላቸው ደርሶ አሊያም ሌላ ከበድ ያለ ጉዳይ ካልገጠማቸው ያን ሁሉ ደረጃ ወርደው መሬቱን ሳያዩ ፀሐይ ወጥታ ትገባለች፡፡
‹‹ወር ቆይቼ መሬቱን ረግጨ ስመለስ ለሳምንት መተንፈስ እስኪያቅተኝ ያመኛል›› የሚሉት ወ/ሮ ሜላት፣ በዚህ ወቅት ተከራይቶ ከመኖር ይሻላል በሚል እንጂ፣ ልጆችን ይዞ ያለ ምንም መውጫና መውረጃ አሳንሰር መኖር በጣም ከባድ ነው ሲሉ ያስረዳሉ፡፡
ልጆች መሬት ወርደው ተጫውተው ለመመለስ፣ ምድር ላይ ያለ ቤተሰብን ወይም ጎረቤትን ለመጠየቅ ቀላል አይደለም፡፡ ልጆች ሁሌ በወላጆች ጥበቃና ቁጥጥር ሥር ናቸው፡፡ ከቤት እንዳይወጡ ዘወትር ክትትል ማድረግ ግድ ነው፡፡ ከቤት ከወጡ ለአሳንሰር መግጠሚያ ተብሎ ክፍት በተተወው ቦታ ገብተው ይሞታሉ የሚለው የሕንፃው ነዋሪዎች ትልቅ ሥጋት ነው፡፡
ችግሩ የአብዛኞቹ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሲሆን፣ ብዙዎች ቤት ደረሰን ብለው ተደስተው ከገቡ በኋላ ጎዶሎው በዝቶ ሲያገኙት መልሰው ሲያማርሩ ይስተዋላሉ፡፡
የውኃ፣ የመብራት፣ የበርና የመስኮት እንዲሁም ሌሎች ጉድለቶች ይስተዋላሉ፡፡ ከተሟላ ቤት እንገባለን
የባንኮች ገደብ የለሽ የብድር ወለድ ምጣኔ ጤናማነትና አገራዊ ፋይዳና ይፈተሽ!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ዘርፉን ወደፊት ያራምዳል ያላቸውን የተለያዩ ዕርምጃዎች እየወሰደ ነው፡፡ በተለይ ባለፉት ሁለት ዓመታት እየተወሰዱ ያሉ ዕርምጃዎች ሥር ነቀል ሊባሉ የሚችሉም ናቸው፡፡…
https://www.ethiopianreporter.com/131599/
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ ትርፍ ቢያገኝም የውጭ ምንዛሪ ገቢው ቅናሽ ማሳየቱ ተጠቆመ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2016 የሒሳብ ዓመት ያሰባሰበው የውጭ ምንዛሪ ከቀዳሚው ዓመት በ300 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ያለ መሆኑ ተመላከተ፡፡ ባንኩ የ2016 የሒሳብ ዓመት የሥራ አፈጻጸሙን በተመለከተ…
https://www.ethiopianreporter.com/131604/
ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም በሌላት አገር ዘመናዊ ስታዲየም እየገነቡ ያሉ ክልሎች
አዲሱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዘመናዊ ስታዲየም ለማስገንባት ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን ይፋ አድርጓል፡፡ ክልሉ የሃላባ ዘመናዊ ስታዲየም ግንባታን ለማስጀመር የመሠረት ድንጋይ ጥሏል፡፡ በቀጣዮቹ…
https://www.ethiopianreporter.com/131578/
ዴሞክራሲ ጫካ ውስጥ አይደገስም
በገነት ዓለሙ
የዛሬ ሳምንት ባነሳሁት የኢሰመኮ ሪፖርት መነሻነትና በዚያም ምክንያት የዛሬውም ጉዳዬ የሰብዓዊ መብቶች ናቸው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችን ከመኖር፣ እነሱን መኗኗሪያ ከማድረግ፣ እነሱ ውስጥ ከመኖር፣ እነሱን…
https://www.ethiopianreporter.com/131597/
ኢትዮጵያዊ ማን ነው/ናት? ለምክክሩስ መግባባት አለን?
በደምስ ጫንያለው (ዶ/ር) የጽሑፉ መነሻ ዛሬ በአገራችን ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶችና የእርስ በርስ ጦርነቶች በርከትከት ብለዋል፡፡ መንስዔያቸው በአብዛኛው ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ቢመስልም በእኔ ዕውቀት፣ አረዳድና እምነት…
https://www.ethiopianreporter.com/131590/
ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን የምትችለው መቼ ነው?
መድረኩ ጠንከር ያሉ የፖሊሲ ጉዳዮች የተነሱበት ነበር፡፡ ስለረሃብ፣ ስለምግብ፣ ስለመሬትና በአጠቃላይ ስለግብርና ብዙ የተባለበት ነበር፡፡ ተከተል ዮሐንስ (ፕሮፌሰር) የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዴሚ ዋና ዳይሬክተር ተቋማቸው…
https://www.ethiopianreporter.com/131609/
በአንድ ዳኛ ለሦስት ዓመታት ሲታይ የከረመው የኮስሞ ትሬዲንግ ክስ በሦስት ዳኞች እንዲታይ ትዕዛዝ ተሰጠ
ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት የወንጀል ሕግም ተጠቅሶበታል
ከስምንት ዓመታት በፊት በ2008 ዓ.ም. በወቅቱ ግምቱ 250 ሚሊዮን ብር የነበረውንና በአሁኑ ወቅት ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት እየተሰጠው ያለው ኮሰሞ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ባለዘጠኝ ወለል ሕንፃን…
https://www.ethiopianreporter.com/131546/
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ ፀደቀ
የፀረ ሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎች በፖሊሲው ትኩረት ይሰጥባቸዋል ተብሏል የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የአገሪቱን የመከላከል አቅምን የሚያጠናክር የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ፖሊሲ በማዘጋጀት ማፅደቁ ተገለጸ። ፖሊሲው በሰው አልባ የአየር ላይ ክትትል፣ የፀረ ሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎች፣ ውስብስብ የበይነ መረብ መገናኛ ዘዴዎችና የሐሰተኛ መረጃ…
https://www.ethiopianreporter.com/131555/
በአበባና በፍራፍሬ ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች የፀጥታ ችግር ሊያሠራን አልቻለም አሉ
በአማራ፣ በደቡብና በኦሮሚያ ክልሎች በአበባና በፍራፍሬ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች፣ በየአካባቢው ያለው የፀጥታ ችግር የመሬት ይዞታ ባለቤትነታቸውን አደጋ ላይ ከመጣል ጀምሮ፣ በሥራዎቻቸው ላይ እንቅፋት እየፈጠረባቸው መሆኑን ተናገሩ፡፡ ባለሀብቶቹ ይህንን የተናገሩት ግብርና ሚኒስቴር የአበባና የፍራፍሬ (Horticulture)…
https://www.ethiopianreporter.com/131561/
ለሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ የሚቀርቡ አቤቱታዎች ቁጥራቸው እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ከሚቀርቡለት አቤቱታዎች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40 የተቀመጠው የንብረት መብት ጋር የተያያዙ ከመሆናቸውም በተጨማሪ አብዛኛዎቹ ውስብስብና ቁጥራቸው እየጨመረ መሆኑ ተነገረ። የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ በ2016 ዓ.ም. ያከናወናቸውን…
https://www.ethiopianreporter.com/131558/
ባንኮችና የኢንሹራንስ ኩባንያዎች የኢንቨስትመንት ባንክ እንዲያቋቁሙ የሚፈቅድ መመርያ ፀደቀ
ብሔራዊ ባንክ በአገሪቱ የሚገኙ 32 ባንኮችና 16 የኢንሹራንስ ኩባንያዎች የኢንቨስትመንት ባንክ ማቋቋም የሚያስችላቸውን መመርያ አፀደቀ። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማኅበር ዓርብ ሐምሌ 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ባዘጋጀው 21ኛው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ የተገኙት የካፒታል ገበያ…
https://www.ethiopianreporter.com/131566/
በህዳሴ ግድብ ላይ የግብፅን ፍላጎት ለማስከበር ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተከሰሱት አሜሪካዊው ሴናተር ጥፋተኛ ተባሉ
የዴሞክራት ፓርቲ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በህዳሴ ግድብ ላይ የግብፅን ፍላጎት ለማስከበር ጉቦ ተቀብለው በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የግብፅን አጀንዳ በማራመድና በሌሎች ክሶች ሐምሌ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ጥፋተኛ ተባሉ። በሴናተሩ ላይ የቀረቡትን ክሶች…
https://www.ethiopianreporter.com/131575/
የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተጠጋ መሆኑ ተገለጸ
‹‹መንግሥት በሱዳን ያሉ የኢትዮጵያ ስደተኞች እንዲመለሱ አይፈልግም የሚባለው አሉባልታ ነው›› የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሱዳን ከአንድ ዓመት በላይ እየተካሄደ ያለው የእርስ በርስ ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተጠጋ መሆኑን፣ ጉዳዩም በአገር አቀፍ ደረጃ በተቋቋመ ብሔራዊ ኮሚቴ የጋራ…
https://www.ethiopianreporter.com/131572/
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል በመቋረጡ ነዋሪዎች የከፋ ችግር ውስጥ ወድቀናል አሉ
የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ችግሩ ከቀጠለ አገልግሎት ያቆማል ተብሏል ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ አካባቢ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኃይል የሚያስተላልፈው የኤሌክትሪከ ተሸካሚ ምሰሶ ላይ ታጣቂዎች ጉዳት ካደረሱበት ጊዜ ጀምሮ፣ በክልሉ ሙሉ ለሙሉ ኤሌክትሪክ በመቋረጡ ነዋሪዎች የከፋ…
https://www.ethiopianreporter.com/131232/
የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶችና ተሟጋቾች ጥበቃና ከለላ የሚያደርግላቸው ሕግ እንዲወጣ ተጠየቀ
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ስምምነት ብትፈርምም ወደ ሕግ መቀየር አልቻለችም ተብሏል ኢትዮጵያ ውስጥ በሕግ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የሰብዓዊ መብቶች ተቆርቋሪ ድርጅቶችና ተሟጋቾች፣ ለሥራቸው ጥበቃና ከለላ የሚያገኙበት ሕግ እንዲወጣ ተጠየቀ፡፡ በርካታ አገሮች የፈረሙት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ለሰብዓዊ መብቶች…
https://www.ethiopianreporter.com/131235/
በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ መከልከሉ ሕግን መሠረት ያላደረገ ነው ሲል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ተቃወመ
ምንም ዓይነት የሕግ ድንጋጌ ሳይኖር ወይም ግልጽ የሆነ ሕግ ሳይወጣና ሕግን የተከተለ ክልከላ ሳይኖር፣ ከላይ በወረደ ወይም ተሰጠ በተባለ አቅጣጫ ላይ ብቻ በመመሥረት፣ በነዳጅ ኃይል የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከሉ፣ በተለያዩ የኢንቨስትመንት…
https://www.ethiopianreporter.com/131242/
በታጣቂዎች ከታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች 138ቱ ያህል መለቀቃቸው ተሰማ
ከአማራ ክልል ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም. የትምህርት ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ ላይ እያሉ፣ ከአዲስ አበባ በ155 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ገብረ ጉራቻ አካባቢ በታጣቂዎች ታፍነው ተወስደዋል ከተባሉት ተማሪዎች መካከል 138ቱ መለቀቃቸው ተሰማ፡፡ ከኢትዮጵያ…
https://www.ethiopianreporter.com/131245/
ብሔራዊ ባንክ በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይትን ለመቆጣጠር ፖሊሲ ነክ የወለድ ምጣኔ ጣለ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በወለድ ተመን ላይ ወደተመሠረተ የፖሊሲ ማዕቀፍ ያሸጋግረኛል ያለውን አዲስ የገንዘብ ፖሊሲ ይፋ አደረገ፡፡ የገንዘብ ፖሊሲው በዋናነት በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይትን በመቆጣጠር የዋጋ ንረትን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተመላክቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ…
https://www.ethiopianreporter.com/131248/
ከግጭት ጋር በተያያዘ በአገሪቱ ውስጥ የሚፈጸሙ ዓለማቀፍ ወንጀሎችን ለመዳኘት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ በኹለት ወራት ውስጥ ለሚንስትሮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ ይፋ ካልኾነ የፍትሕ ሚንስቴር ሰነድ መመልከቱን ጠቅሶ ሪፖርተር ዘግቧል።
ረቂቅ አዋጁ፣ የጦር ወንጀሎች፣ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች፣ በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች እንዲኹም አስገድዶ የመሠወር፣ የጾታዊ ጥቃትና የግርፋት ወንጀሎችን እንደሚሸፍንና ወደኋላ ተመልሶ እንደሚሠራ በሰነዱ ላይ እንደሠፈረ ዘገባው አመልክቷል።
ፍትሕ ሚንስቴር፣ ለሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው ማስፈጸሚያ የልዩ ፍርድ ቤት ማቋቋሚያ፣ የልዩ ፍርድ ቤት ዳኞች አመራረጥ እንዲኹም የልዩ ዓቃቤ ሕግ ማቋቋሚያ አዋጆችን እያዘጋጀ እንደኾነም ዘገባው ጠቅሷል።
በሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው ማዕቀፍ ሥር የእውነት አፈላላጊ ኮሚሽን ለማቋቋም፣ የዳኞች፣ የወንጀል መርማሪዎችና ባለሙያዎች ቡድን ልምድ ለመቅሰም ወደ ሩዋንዳና ሔግ ወደሚገኘው ዓለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት እንዲሄድም ታስቧል ተብሏል።
‹‹የአጎራባች ክልሎች የሰላም ዕጦት በእኛ ላይ ሸክምና ጫና ፈጥሮብናል›› ከአቶ ባበከር ሀሊፋ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ…
አቶ ባበከር ሀሊፋ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ወንዶ ገነት ኮሌጅ በፎረስትሪ ሠርተዋል። ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተምረው አጠናቀዋል። ከ2002 ዓ.ም. እስከ 2003 ዓ.ም….
https://www.ethiopianreporter.com/131167/
መኩሪያና መታፈሪያ ምሽጋችን የሕግ የበላይነት ይሁን ስንል…
በገነት ዓለሙ
የሕግ የበላይነት ማለት ዛሬ ጭምር አልገባን እያለ የሚያስጨንቀንን ያህል አዲስና እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ዲስኩር ውስጥ ለረዥም ጊዜ ለይስሙላም ይሁን ለስም ጌጥ…
https://www.ethiopianreporter.com/131160/
የአብዮቱ ስንክሳሮች ከኮሎኔሉ ማኅደር
በአብርሃም ገብሬ ደቢ
ዕውቁ የአፍሪካ ቀንድ አገሮች የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ክርስቶፈር ክላፋም፣ የ1966 ዓ.ም. የኢትዮጵያ አብዮትና አብዮቱ ያስከተላቸው ውጤቶችን የሚያትት “Transformation and Continuity in Revolutionary…
https://www.ethiopianreporter.com/131163/
‹‹ሁሉንም ሰው በአንዴ ለማስደሰት ከፈለግህ አይስክሬም ነጋዴ ሁን›› የሚል የተለምዶ አባባል ይታወቃል፡፡ በፖለቲካው መስክ በተለይ ሥልጣነ መንበሩን የጨበጠ ኃይል ለሚያስተዳድረው ሕዝብ ባለበት ኃላፊነት፣ በተቻለ መጠን ሁሉንም ማስደሰት ባይችልም ሁሉንም ማስከፋት ግን አይኖርበትም፡፡ በመንግሥት ውሳኔና ዕርምጃ የሚደሰቱ ያሉትን ያህል የሚከፉ መኖራቸው የሚጠበቅ ቢሆንም፣ ሁሉንም ወገኖች ያማከለ አስተዳደር እንዲኖር ግን የገባውን ቃል ጠብቆ መሥራት ይጠበቅበታል፡፡ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታም መንግሥት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ ጉዳዮችና በዲፕሎማሲው ጭምር በሚያከናውናቸው ተግባራት መንግሥት የሚወደስባቸውም ሆነ የሚነቀፍባቸው ምክንያቶች መኖራቸው ተጠባቂ ነው፡፡ የተለያዩ ፍላጎቶች፣ ዓላማዎችና ስሜቶች ከግራ ወደ ቀኝ በሚያላጓት የአሁኗ ኢትዮጵያ ደስታና መከፋት የሚፈጥሩ በርካታ ጉዳዮች አሉ፡፡ እነዚህን ሁለት ጉዳዮች ከአገርና ከሕዝብ ዘለቄታዊ ሰላምና ደኅንነት አኳያ በቅን መንፈስ የሚያስተናግድ ዓውድ መፍጠር አስፈላጊ ነው፡፡
አዲስ አበባ ከተማን በኮሪደር ልማቱ አማካይነት ወደ ‹‹ስማርት ሲቲ›› ለመለወጥ በሚደረገው ጥረት፣ የልማቱ መነሻና መድረሻ ሰው መሆን አለበት፡፡ ልማቱ በደፈናው ‹‹ሰው ተኮር ነው›› ከመባል አልፎ ለበርካታ ዓመታት ከኖሩበት ቀዬ የሚነሱ ነዋሪዎችን መብት፣ ጥቅምና ክብር በተግባር ማሳየት ይኖርበታል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደ የተባበሩት መንግሥታት ደርጅት ሃቢታት (UN-Habitat) ዓላማ፣ ማኅበራዊና አካባቢያዊ ጥበቃን መሠረት ያደረጉ ሥራዎች በማከናወን ዜጎች በቂ መጠለያና የሥራ ዋስትና ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡ በኮሪደር ልማቱ አማካይነት ለኑሮ ከማይመቹ ያረጁና የተፋፈጉ መንደሮች ወደ ተሻሉ መኖሪያ ሥፍራዎች እንደተዘዋወሩ ወገኖች ሁሉ፣ ቅሬታና ስሞታ እያቀረቡ ያሉ የልማት ተነሺዎችም ልዩ ትኩረት ተሰጥቷቸው መንግሥት ቃሉን ጠብቆ ማስተናገድ ይኖርበታል፡፡ የተለያዩ ሰበቦች እየተደረደሩ ጎዳና ላይ
ንግድ ምክር ቤቱ ጠቅላላ ጉባዔውን በወቅቱ ማካሄድ ያልቻልኩት በንግድ ሚኒስቴር ጫና ነው አለ
የአገሪቱ የንግድ ኅብረተሰብ በቀዳሚነት ይወክላል የተባለው የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የተለያዩ ምክንያቶችን በማቅረብ ለዓመታት ያዘገየውን ጠቅላላ ጉባዔና ምርጫ፣ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም. የሚካሄድ ለመሆኑ ማረጋገጫ ሰጥቷል፡፡ የንግድ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት መላኩ ዕዘዘው…
https://www.ethiopianreporter.com/131179/
ቴሌ ቲቪ የተሰኘ የኦላይን ሲኒማ መተግበሪያ ይፋ ተደረገ
የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማበልፀግ የሚታወቀው ኤግላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ፣ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ቴሌ ቲቪ የተሰኘ የኦላይን ሲኒማ መተግበሪያ ይፋ አደረገ፡፡ ኩባንያዎቹ በጋራ ያበለፀጉትን መተግበሪያ ሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ ባደረጉበት ወቅት፣ የተለያዩ ፊልሞችን ለተወሰኑ ቀናት…
https://www.ethiopianreporter.com/131123/
ለ22 ዓመታት ሳይካሄድ የቆየው የግብርና ናሙና ቆጠራ በመስከረም ወር እንደሚጀመር ተገለጸ
62 ሺሕ ሠራተኞች በቆጠራው ይሳተፋሉ ተብሏል የግብርናው ዘርፍ በአገር አቀፍ ደረጃ በኢኮኖሚው ላይ ያለውን አስተዋጽኦ በትክክል ለመለየት ያስችላል የተባለለት የግብርና ናሙና ቆጠራ፣ ከ22 ዓመታት በኋላ በ2017 በጀት ዓመት ከመስከረም ወር ጀምሮ ለአንድ ዓመት እንዲከናወን…
https://www.ethiopianreporter.com/131125/
የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ለስድስት ባለኮኮብ ሆቴሎች ዕውቅና ሰጠ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የአየር ብክለትን በመቀነስና በኃይል ቁጠባ አጠቃቀም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ስድስት ባለአራትና ባለአምስት ኮከብ ሆቴሎች የአረንጓዴ ካርድ ዕውቅና መስጠቱን አስታወቀ፡፡ በመሀል ከተማ በሚገኙ አሥር ባለኮከብ ሆቴሎች የአካባቢ ብክለትን ከመቀነስ…
https://www.ethiopianreporter.com/131132/
በመስኖ ይለማል ከተባለው አሥር ሚሊዮን ሔክታር መሬት ውስጥ እየለማ ያለው 13 በመቶው ብቻ መሆኑ ተነገረ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሦስት ሚሊዮን ሔክታር የሚጠጋ መሬት መልማቱን ተናግረዋል በኢትዮጵያ በመስኖ የሚለማ አሥር ሚሊዮን ሔክታር መሬት ቢኖርም፣ እየለማ ያለው 13 በመቶ ወይም 1.2 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ብቻ መሆኑን፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጸው…
https://www.ethiopianreporter.com/131129/
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መብላትና መልበስን ጨምሮ ለዜጎች መድኃኒት ማቅረብ ከተቻለ ሌላው ትርፍ ነው አሉ
መንግሥት ከዓለም ባንክና ከአይኤምኤፍ 10.5 ቢሊዮን ዶላር ካገኘ የበጀት ማስተካከያ አደርጋለሁ ብሏል ኢትዮጵያ ውስጥ የሚበላ፣ የሚለበስና ታክሞ መድኃኒት የሚያገኝ ዜጋ ካለ ሌላው ጉዳይ ትርፍ ሊባል እንደሚችል፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን…
https://www.ethiopianreporter.com/131142/
ኢትዮጵያ ለዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የጀመረችው ድርድር በመጪው መስከረም ሊካሄድ ነው
መንግሥት የንግድና የፋይናንስ ዘርፎችን ለመክፈት መወሰኑ ድርድሩን ያከብደዋል ተባለ በግንቦት ወር ይካሄዳል ተብሎ የነበረው የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት አምስተኛ ዙር ድርድር፣ በመጪው መስከረም ወር 2017 ዓ.ም. እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡ ድርድሩን በበላይነት የሚመራው የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሲሆን፣…
https://www.ethiopianreporter.com/131138/
በኢትዮጵያ በሕይወት የመኖር መብት አሳሳቢ መሆኑን ኢሰመኮ አስታወቀ
በኢትዮጵያ በሚከናወኑ የትጥቅ ግጭቶች፣ ጥቃቶች ወይም የፀጥታ መደፍረሶች ምክንያት፣ በታጣቂ ኃይሎችና በመንግሥት የፀጥታ አካት በተወሰዱ ዕርምጃዎች፣ በሲቪል ሰዎች ላይ የሚደርስ የሞትና የአካል ጉዳት አሳሳቢነት ቀጥሏል ሲል፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ፡፡ በሕይወት የመኖር…
https://www.ethiopianreporter.com/131143/
ሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ዘርፉን በማያውቁ አካላት ክሶች እየቀረቡበት መሆኑን ተናገረ
ሚድሮክ ወርቅ ማዕድን እስከ ምክር ቤት ድረስ ባሉና የወርቅ ማዕድን ዘርፉን በማያውቁ አካላት ክሶች እየደረሱበት መሆኑን ገለጸ፡፡ ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ሚድሮክ ወርቅ ማዕድን በአካባቢ ጥበቃ የ‹‹ISO 14001:2015 Environmental Management System›› መሥፈርቶችን ማሟላቱን…
https://www.ethiopianreporter.com/131022/
የግል ሚዲያዎች በፌዴሬሽን ምክር ቤት ዓመታዊ ጉባዔና በፓርላማው የበጀት ውይይት ላይ እንዳይገቡ ተከለከሉ
የአገሪቱ ከፍተኛ የሥልጣን አካል የሆኑት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት በየራሳቸው የስብሰባ አዳራሾች በሚያካሂዷቸው ስብሳባዎች፣ የግል መገናኛ ብዙኃን ገብተው እንዳይዘግቡ ተከለከሉ፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ከሰኔ 24 ቀን ጀምሮ ለሁለት…
https://www.ethiopianreporter.com/131019/
የፀረ ሙስና ሥራዎች አፈጻጸም በዕቅድም ሆነ በውጤት ወጥነት የጎደላቸው ናቸው ተባለ
ከ857 ሺሕ በላይ ሠራተኞችና አመራሮች ውስጥ ሀብት ያስመዘገቡ ከ21 በመቶ በታች ናቸው ተብሏል በፌዴራል፣ በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽኖች በአራት የተለያዩ ዘርፎች በ2016 ዓ.ም. የተያዙ ዕቅዶችም ሆነ የተመዘገቡ ውጤቶች ወጥነት የጎደላቸው መሆናቸው…
https://www.ethiopianreporter.com/131028/
በአዲስ አበባ ምትክ ቦታ ያልተሰጣቸው የልማት ተነሺዎች መንግሥት መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠየቁ
‹‹አንድም ሰው ምትክ ቦታ ወይም ካሳ ሳያገኝ ከቦታው አልተነሳም›› የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በየካ ክፍለ ከተማ ከመለስ ፋውንዴሽን ወደ አዋሬ (አቧሬ) የሚወስድ መንገድ ለመገንባት በቀድሞዎቹ ቀበሌ 23፣ 18 እና ቀበሌ 19…
https://www.ethiopianreporter.com/131025/
ከአፍሪካ አገሮች ጋር የንግድ ልውውጥ ለማካሄድ የታሪፍ ማሻሻያ እየተዘጋጀ መሆኑ ተነገረ
ስምምነቱ ተግባራዊ ሲደረግ ኢትዮጵያ ልታጣ የምትችለው ገቢ እየተጠና ነው ተብሏል ኢትዮጵያ በፈረመችው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት መሠረት፣ ምርቶች ወደ አገር ውስጥ ሲገቡ፣ ከታሪፍ ነፃ የሚደረጉበት የሕግ ማዕቀፍ ማሻሻያ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ለማፀደቅ እየተሠራ መሆኑ…
https://www.ethiopianreporter.com/131031/
ነዳጅ አከፋፋዮች አምስት መቶ ሺሕ ሊትር የሚይዝ ዴፖ የመገንባት ግዴታ ሊጣልባቸው ነው
ባለቤቱ እያወቀ የጫነውን ነዳጅ ባልተፈቀደ ቦታ ያራገፈ ተሽከርካሪ ይወረሳል ነዳጅ አከፋፋዮች በሁለት ዓመት ውስጥ 500‚000 ሊትር የሚይዝ ዴፖ፣ አራት ማደያዎች፣ እንዲሁም በሦስት ዓመታት ውስጥ ተጨማሪ ስድስት ማደያዎችን የመገንባት ግዴታ ሊጣልባቸው ነው፡፡ የነዳጅ ውጤቶችን የግብይት ሥርዓት ለመደንገግ…
https://www.ethiopianreporter.com/131041/
በከፍተኛ ሙስና ሲጠረጠር የተሰወረው ግለሰብ ቦሌ ሥጋ ቤት ከፍቶ ማስታወቂያ ሲያስነግር ተያዘ
በከፍተኛ የሀብት ምዝበራ (ሙስና) ጋር በተያያዘ ከተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ውስጥ 14ቱ ክልሉን ለቀው መሰወራቸውን፣ ስድስቱ በቁጥጥር ሥር ሲውሉ አንደኛው ተጠርጣሪ ግን በአዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ ውስጥ ሥጋ ቤት ከፍቶ ማስታወቂያ ሲያስነግር መያዙ ተገለጸ፡፡ …
https://www.ethiopianreporter.com/131044/
ወልቃይት ለአራት ዓመታት ከፌዴራል መንግሥት የበጀት ድጎማ ባለማግኘቱ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ቅሬታ ቀረበ
የአማራ ክልል ምክር ቤት ጥያቄው የፍትሐዊነት ጉዳይ በመሆኑ መልስ እንዲሰጠው ጠይቋል በአማራና በትግራይ ክልሎች የወሰን ይገባኛል ጥያቄ የሚነሳበት ወልቃይት፣ ከፌዴራል መንግሥት ባለፉት አራት ዓመታት ምንም ዓይነት የበጀት ድጋፍ አለማግኘቱ ተጠቅሶ፣ መፍትሔ እንዲሰጥበት ለፌዴሬሽን ምክር ቤት…
https://www.ethiopianreporter.com/131047/
ምርጫ ቦርድ የተሰረዘው ሕወሓት እንዲመዘገብ ሚኒስቴሩ ያቀረበውን የትብብር ጥያቄ ውሳኔ እንደሚሰጥበት አስታወቀ
ሕወሓት በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መስማማቱን በመጥቀስ፣ በቅርቡ በፀደቀው ማሻሻያ አዋጅ መሠረት እንደገና እንዲመዘገብ የፍትሕ ሚኒስቴር ትብብር እንዲደረግለት ደብዳቤ የተጻፈለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ በጉዳዩ ላይ በቅርቡ ውሳኔውን እንደሚያስታውቅ ገለጸ፡፡ የፍትሕ ሚኒስቴር ሰሞኑን ለምርጫ ቦርድ በላከው…
https://www.ethiopianreporter.com/130901/
በአየር ንብረት ለውጥ ዋናው ችግር በዙሪያው የሚወጡ ፖሊሲዎች በየጊዜው መለዋወጥና ተግባራዊ አለመሆን እንደሆነ ተነገረ
በተለያዩ ወቅቶች በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የሚወጡ ፖሊሲዎችና መመርያዎች ወደ መሬት ወርደው ተግባር ላይ አለመዋላቸው፣ በዘርፉ መሻሻል እንዳይኖር መሠረታዊ ችግር መሆኑ ተነገረ፡፡ ዳን ቸርች ኤድ (Dan Church Aid) የተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት፣ በሦስት የአፍሪካ አገሮችና…
https://www.ethiopianreporter.com/130905/
የሕዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ገለልተኛና በመሪዎች መቀያየር የማይዛነፉ ሆነው እንዲገነቡ ተጠየቀ
ከአገሪቱ የፖለቲካ ሥርዓትና ከተቋማት መሪዎች መቀያየር ጋር አብረው የማይቀያየሩና የማይፈርሱ ነፃ፣ ገለልተኛና ጠንካራ ተቋማት እንዲገነቡ ምሁራን ጠየቁ፡፡ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የቢሮክራሲ መዋቅርና የመንግሥት አስተዳደር ከተጀመረ አንድ ክፍለ ዘመን የተሻገረ ቢሆንም፣ እስካሁን ድረስ ራሳቸውን ችለው መንቀሳቀስ የሚችሉ…
https://www.ethiopianreporter.com/130908/
የቤት ሠራተኞች ሕጋዊ የሰነድ ውል እንዲኖራቸው የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ሊዘጋጅ ነው
የአገር ውስጥ የቤት ሠራተኞች ከአሠሪዎቻቸው ጋር ሕጋዊ የሰነድ ውል እንዲኖራቸው ጥናት በማድረግ፣ የሕግ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ ይህንን ያስታወቀው ለዓለም አቀፍ በጎ አገልግሎት የቆመ ክርስቲያናዊ ድርጅት የቤት ሠራተኞች የሥራ…
https://www.ethiopianreporter.com/130911/
በትግራይ ክልል አገራዊ የምክክር ሒደት እንዲጀመር ጥያቄ ቀረበ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የአገራዊ ምክክር ሒደቱ በትግራይ ክልል እንዲጀመር ጥያቄ አቀረቡ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያቀረበውን የሥራ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫ አስመልክቶ ከትናንት በስቲያ ዓርብ ሰኔ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ውይይት…
https://www.ethiopianreporter.com/130917/
ዩኒቨርሲቲዎች የቀጣይ ዓመት የምግብ በጀት ካልተስተካከለላቸው ተማሪዎችን መቀበል እንደማይችሉ አስታወቁ
ማረሚያ ቤቶችም ታራሚዎችን መመገብ እንደከበዳቸው ተነግሯል በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች በመንግሥት ተገንብተው ተማሪዎችን በራሳቸው ወጪ እያስተናገዱ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች፣ እንዲሁም የፌደራል ማረሚያ ቤቶች በቀጣይ ዓመት የሚመደበው የምግብ በጀት ካልተስተካከለ ምግብ ማቅረብ አዳጋች እንደሚሆንባቸው አስታወቁ፡፡ ዩኒቨርሰቲዎች ተማሪ ለመቀበል…
https://www.ethiopianreporter.com/130923/
አዲስ አበባን የፈተናት ያልተናበበ አካባቢ ጥበቃ
በቀንም ሆነ በማታ የሚሠሩ ወንጀሎች፣ ለአካባቢ ብክለት መንስዔ የሚሆን ቆሻሻ በዘፈቀደ ሲወገድና ሌሎችም ተመሳሳይ ችግሮች ሲፈጸሙ ከማኅበረሰቡ ዓይን የተሰወሩ አይደሉም፡፡ ሆኖም የአካባቢ ብክለትን የሚያባብሱ ሕገወጥ…
https://www.ethiopianreporter.com/130849/
የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና ምክትላቸው የሥራ መልቀቂያ አስገቡ
የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት ለክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት የሥራ መልቀቂያ አስገቡ። ሪፖርተር ያገኘው የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ እንደሚያሳየው፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ፀጋይ ብርሃነ ገብረተኸለ (ዶ/ር)፣ እንዲሁም ምክትል ፕሬዚዳንቱ አቶ ገብረ…
https://www.ethiopianreporter.com/130788/
ሰሞኑን በአዲስ አበባ ያጋጠመው የነዳጅ እጥረት በበዓል ምክንያት ከጂቡቲ ባለመጫኑ እንደሆነ ተገለጸ
በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ሰሞኑን የሚታየው የነዳጅ እጥረት፣ በበዓል ምክንያት ለሁለት ቀናት ከጂቡቲ ነዳጅ ባለመጫኑ እንደሆነ ተነገረ፡፡ የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢዎች ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ እስመለዓለም ምሕረቱ የነዳጅ እጥረቱ በከተማዋ መከሰቱን ለሪፖርተር አረጋግጠው፣ እጥረቱ ያጋጠመው…
https://www.ethiopianreporter.com/130800/
ለመጪው በጀት ዓመት ከፍተኛ መጠባበቂያ በጀት መቅረቡ በፓርላማ ጥያቄ አስነሳ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከሁለት ሳምንታት በኋላ ለሚጀመረው የ2017 በጀት ዓመት ያቀረበው የመጠባበቂያ በጀት፣ ካለፈው ዓመት ከእጥፍ በላይ ያደረገው ምን የተለየ ሥጋት ስላለ ነው በማለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ አስነሳ፡፡ ለ2017 በጀት ዓመት ከተረቀቀው 971.2…
https://www.ethiopianreporter.com/130803/
የገንዘብ ሚኒስቴር የደመወዝ ገቢ ግብር ለማሻሻል ጥናት መጀመሩ ታወቀ
ዝቅተኛ ገቢ ያለውን የኅብረተሰብ ክፍል ለመደገፍ በደመወዝ ገቢ ላይ የሚጣለውን የግብር ምጣኔ ለማሻሻል የገንዘብ ሚኒስቴር ጥናት መጀመሩ ታወቀ፡፡ ማንኛውም ተቀጣሪ የሚያገኘው ጠቅላላ ገቢ ከ600 ብር በላይ ከሆነ አሥር በመቶ የደመወዝ ገቢ ግብር የሚከፍል ሲሆን፣ ከአሥር…
https://www.ethiopianreporter.com/130806/
ተመድ ኢትዮጵያና ሶማሊያ የሶማሌላንድ ወደብ ስምምነት ጉዳይን በሰላም እንዲፈቱ አሳሰበ
ሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮች ድንበሬን ጥሰው ገብተዋል ስትል ከሳለች የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት፣ ሞቃድሾና አዲስ አበባ በሶማሌላንዱ ጉዳይ የተፈጠረውን ችግር በሰላም እንዲፈቱ አሳሰበ፡፡ ምክር ቤቱ በኢትዮጰያና ሶማሌላንድ መካከል የተፈረመው ስምምነት፣ በአፍሪካ ቀንድ የፀጥታ ሥጋቶች ላይ…
https://www.ethiopianreporter.com/130797/
በአማራ ክልል ከተፈጠረው ቀውስ ጋር በተያያዘ የታሰሩ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞችን ጨምሮ ሁሉም እስረኞች እንዲለቀቁ ተጠየቀ
በባህር ዳር ከተማ ላለፉት ሁለት ቀናት የተካሄደው የሰላም ጉባዔ ባለአሥር ነጥቦች የአቋም መግለጫ በማውጣት ትናንት ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. ሲጠናቀቅ፡፡ በክልሉ ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘ የታሰሩ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ ምሁራንና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እንዲፈቱ…
https://www.ethiopianreporter.com/130812/
ክልሎች ለፌዴራል ፕሮጀክቶች ካሳ እንዲከፍሉ የሚያስገድድ አዋጅ አፀደቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል መንግሥት ለሚያከናውናቸው መሠረተ ልማቶችና ማኅበራዊ አገልግሎት ማስፈጸሚያ ሥራዎች፣ ንብረት መገመትና ካሳ መክፈል ክልሎች እንዲያስፈጽሙ የሚያስገድድ አዋጅ አፀደቀ፡፡ ምክር ቤቱ ትናንት ማክሰኞ ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ ለሕዝብ…
https://www.ethiopianreporter.com/130815/
ሕግ የማጥቂያ መሣሪያ እንዳይሆን ጥንቃቄ ይደረግ!
የሕግ መሠረታዊ ዓላማ ዜጎችን ከማናቸውም ዓይነት ጥቃቶች መጠበቅ፣ ለሕይወታቸውና ለንብረታቸው ከለላ መስጠትና በሥርዓት እንዲኖሩ ማድረግ ማስቻል ነው፡፡ በዚህ መሠረት ሁሉም ዜጎች በሕግ ፊት እኩል…
https://www.ethiopianreporter.com/130702/
ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ሥርዓት ሳይዘረጉ አገልግሎት ለመስጠት መነሳት ስህተት ነው!
በተለያዩ የመንግሥትና የግል ተቋማት ውስጥ ተገልጋዮች በከፈሉት ልክ የሚፈልጉትን አገልግሎት ለማግኘት ይቸገራሉ፡፡ የሚከፍሉትን የገንዘብ የሚመጥን አገልግሎት ያለማግኘት ብቻ ሳይሆን እንደ አንድ ተገልጋይ መብታቸው የሆነን…
https://www.ethiopianreporter.com/130739/
የመጋቢቱ ለውጥና ፈተናዎቹ
በታደሰ ሻንቆ
ሀ) ችኩሎችና ገታሮች፣ መፈናቀልና ሞትን ያነገሡበት ጊዜ እላይ የተጠቀሱት ዓለማዊና አካባቢያዊ የተሞክሮ ትምህርቶች፣ የለውጥ አካሄድንና የሕዝብ ግንዛቤን እንዳገዙ ሁሉ፣ ከልምድ ተምሮ የድሮ አቋማቸውን…
https://www.ethiopianreporter.com/130734/
‹‹ወላድ ላማቸውን አርደው ከደኸዩት ወንድማማቾች›› ሁሉም ይማር
በንጉሥ ወዳጅነው የዕለቱን ጽሑፍ በአንድ አንጋፋ አባት ወግ ልጀምር፡፡ ‹‹የአንድ ባለፀጋ ልጆች የሆኑ ሁለት ሰዎች ነበሩ፡፡ እነኚህ ልጆች አባታቸው በድንገተኛ ሞት ያልፍና ንብረት ክፍፍል ውስጥ…
https://www.ethiopianreporter.com/130730/
አስጨናቂው የኑሮ ውድነት ወዴት እያመራ ነው?
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የኑሮ ውድነት እንደ አገር ከባድ ፈተና ሆኗል፡፡ ሰዎች የተለያዩ ወጪዎቻቸውን ሸፍነው ለመኖር ፈጽሞ አልቻሉም፡፡ መሠረታዊ የሚባሉ ነገሮችን አሟልቶ ለመኖር ቅንጦት እስከመሆን…
https://www.ethiopianreporter.com/130768/
በአዋጁ በተጀመረው የቤት ኪራይ ውል አከራዮች ከፍተኛ ጭማሪ እያደረጉ መሆኑ ተከራዮችን አስጨንቋል
‹‹በተከራይና አከራይ መካከል ስምምነት ከሌለ አንመዘግብም›› የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ውል ምዝገባ በሁሉም ወረዳዎች ማካሄድ ከጀመረ በኋላ፣ አከራዮች ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ እያደደረጉ በመሆናቸው ተከራዮች ከአቅማቸው በላይ መሆኑንና መጨነቃቸውን እየገለጹ…
https://www.ethiopianreporter.com/130588/
ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ብዛት ያላቸው የኦዲት ክፍተት ግኝቶችን ለፓርላማ አቀረበ
ሪፖርቱ ሲቀርብ የመንግሥት ባለሥልጣናት አለመገኘታቸው ጥያቄ አስነስቷል ለኦዲተሮች የሚመደብላቸው 300 ብር የቀን አበል እንዲሻሻል ተጠይቋል የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በባለበጀት የመንግሥት ተቋማት ላይ ባካሄደው የ2015 በጀት ዓመት የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲትና የክዋኔ ኦዲት፣ ብዛት ያላቸው…
https://www.ethiopianreporter.com/130607/
በአየር ንብረት ለውጥ የሚከሰቱ ተባዮች በሆርቲካልቸር ምርቶች ላይ ችግር እየተፈጠሩ መሆኑ ተገለጸ
በዓለም አቀፍ ደረጃ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ዕፅዋትን የሚያጠቁ ተባዮች በሆርቲካልቸር ምርቶች ገበያ ላይ ጫና መፍጠራቸው ተገለጸ፡፡ የሆርቲካልቸር ምርቶችን የሚገዙ የአውሮፓ ኅብረት አገሮች የቁጥጥር ሥርዓታቸውን በማጠናከራቸው በላኪዎች ላይ ችግር እየተፈጠረ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ በሆርቲካልቸር ምርት ጥራትና…
https://www.ethiopianreporter.com/130694/
የመብት ተሟጋቾች በመንግሥት ጫና ምክንያት የሲቪል ምኅዳሩ እየጠበበ ነው ሲሉ ወቀሳ አቀረቡ
በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ 12 የሲቪክ ማኅብረሰብ ድርጅቶች የበረታ የመንግሥት ጫና የሰቪክ ምኅዳሩን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያጠበበው ነው ሲሉ ወቀሳ አቀረቡ፡፡ በሰብዓዊ መብቶች ላይ አተኩረው የሚሠሩና አገር በቀል የሰብዓዊ መብቶች በአገሪቱ ያለው የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ እንዲሻሻል የበኩላቸውን…
https://www.ethiopianreporter.com/130697/
ኢሠማኮ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የደመወዝ ቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ ያቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ተቃወመ
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) በፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች ረቂቅ አዋጅ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሜሪትና የደመወዝ ቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ ማቅረብ ተገቢ አለመሆኑን ተናገረ፡፡ ኢሠማኮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቦርድ ሰብሳቢ መሆን የለባቸውም የሚል ሐሳብ ያቀረበበት ምክንያት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቦርዱን…
https://www.ethiopianreporter.com/130705/
የኤሌክትሪክ አገልግሎትና የቴሌኮም ኩባንያዎች ቫት እንዳይጣልባቸው ጠየቁ
የእምነት ተቋማት ቫት እንዲከፍሉ ይደረጋል ተብሏል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የቴሌኮም ኩባንያዎች የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) እንዳይጣልባቸው ጥያቄ አቀረቡ፡፡ ጥያቄው የቀረበው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ባካሄደው…
https://www.ethiopianreporter.com/130700/
አረንጓዴ አሻራ ከአገሪቱ ዓመታዊ በጀት እስከ አንድ በመቶ ድርሻ እንዲኖረው የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ
በ2017 ዓ.ም. ከ8 ቢሊዮን እስከ 5.6 ቢሊዮን ብር በጀት ሊመደብለት ይችላል የፌዴራል መንግሥት በየዓመቱ ከአገር ውስጥ ገቢ ምንጭ ከሚመድበው ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ0.5 በመቶ እስከ አንድ በመቶ ያህል፣ ለአረንጓዴ አሻራና ለተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ እንዲሰጥ…
https://www.ethiopianreporter.com/130711/
ለወሎ ተርሸሪ ኬርና ማስተማሪያ ሆስፒታል ማስገንቢያ ከተዘጋጀው ኩፖን ከዘጠኝ ሚሊዮን ብር በላይ መጥፋቱ ተገለጸ
ለወሎ ተርሸሪ ኬር የሕክምናና የማስተማሪያ ሆስፒታል ፕሮጀክት ግንባታ ለማዋል ወደ ተለያዩ ክልሎችና በውጭ አገሮች በሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምሲዎችና ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች በኩል ይሸጣል ተብሎ ተሠራጭቶ…
https://www.ethiopianreporter.com/130635/
የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅና የሚስተጋቡ ሥጋቶች
ከሰሞኑ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ ከአገር ውስጥ እስከ ውጭ አገሮች በሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጭምር መነጋገሪያ…
https://www.ethiopianreporter.com/130661/
ለግል ባለሀብቶች ከተሰጠው 2.2 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ውስጥ እየለማ ያለው 41 በመቶ ብቻ መሆኑ ተነገረ
ለግል ባለሀብቶች ከተላለፈው 2.2 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ውስጥ እስካሁን ድረስ እየለማ ያለው 41 በመቶ ብቻ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ግብርና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በመሆን በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ላይ ያሉትን ተግዳሮቶችና የቀጣይ አቅጣጫዎችን በተመለከተ…
https://www.ethiopianreporter.com/130604/
በአዋጁ በተጀመረው የቤት ኪራይ ውል አከራዮች ከፍተኛ ጭማሪ እያደረጉ መሆኑ ተከራዮችን አስጨንቋል
‹‹በተከራይና አከራይ መካከል ስምምነት ከሌለ አንመዘግብም›› የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ውል ምዝገባ በሁሉም ወረዳዎች ማካሄድ ከጀመረ በኋላ፣ አከራዮች ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ እያደደረጉ በመሆናቸው ተከራዮች ከአቅማቸው በላይ መሆኑንና መጨነቃቸውን እየገለጹ…
https://www.ethiopianreporter.com/130588/
ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ብዛት ያላቸው የኦዲት ክፍተት ግኝቶችን ለፓርላማ አቀረበ
ሪፖርቱ ሲቀርብ የመንግሥት ባለሥልጣናት አለመገኘታቸው ጥያቄ አስነስቷል ለኦዲተሮች የሚመደብላቸው 300 ብር የቀን አበል እንዲሻሻል ተጠይቋል የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በባለበጀት የመንግሥት ተቋማት ላይ ባካሄደው የ2015 በጀት ዓመት የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲትና የክዋኔ ኦዲት፣ ብዛት ያላቸው…
https://www.ethiopianreporter.com/130607/
የፐርፐዝ ብላክ የባንክ ሒሳቦች የታገዱት በሕግ መሠረት መሆኑ ተጠቆመ
በግብርና፣ በሪል እስቴትና በሌሎችም የተለያዩ የንግድ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የሚገኘው የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ኩባንያ የባንክ ሒሳቦች የታገዱበት፣ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የሚለውን የሕግ ደንጋጌ መሠረት አድርጎ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጠቆመ፡፡ ዋና ሥራ…
https://www.ethiopianreporter.com/130586/
አስተዳደሩ ኦዲት ለማድረግ ዕግድ በጣለበት የማኅበር ቤቶች መሬት ላይ አስቸኳይ ውሳኔ እንዲሰጥ ጥያቄ ቀረበ
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በቱሉ ዲምቱና በዓለም ባንክ አካባቢዎች በ1996 ዓ.ም. በሕጋዊ መንገድ ተደራጅተው የመኖሪያ ቤት መሥሪያ መሬት የተሰጣቸው የማኅበር ቤቶች፣ እስካሁን ኦዲት ተደርጎ ግኝት ባለመቅረቡና ውሳኔ ባለመሰጠቱ፣ ንብረታቸውን እንዳያንቀሳቅሱ የተደረገበት ምክንያት በአስቸኳይ ውሳኔ…
https://www.ethiopianreporter.com/130592/
በትግራይ ክልል ለ13 ወረዳዎች የተበላሸ የምግብ እህል መሠራጨቱ ተረጋገጠ
የዕርዳታ እህሉን ያቀረበው ድርጅት በሕግ ይጠየቃል ተብሏል በትግራይ ክልል ያጋጠመውን የረሃብ አደጋ ለመከላከል የተቋቋመው የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሰጪ ግብረ ኃይል፣ ለ13 ወረዳዎች የላከው የምግብ ዕርዳታ የተበላሸ በመሆኑ እንዳይሠራጭ መታገዱ ገተለጸ፡፡ ግብረ ኃይሉ ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሚያቀርበው…
https://www.ethiopianreporter.com/130595/
‹‹በመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ውስጥ የብሔር ተዋፅኦ መካተቱ በአተገባብሩ ላይ ፖለቲካዊ ጫና ያመጣል›› የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕንባ ጠባቂ
በሥራ ላይ ያለውን የመንግሥት ሠራኞች ረቂቅ አዋጅ በማሻሻል እንደ አዲስ ተዘጋጅቶ በቀረበውና ውይይት እየተደረገበት በሚገኘው ረቂቅ አዋጅ ውስጥ፣ የብሔር ተዋፅኦ የሚል ድንጋጌ ማካተት፣ በአተገባብሩ ላይ ፖለቲካዊ ጫና ያመጣል ሲሉ የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና…
https://www.ethiopianreporter.com/130598/
በራያና በወልቃይት እንደገና ወደ ኃይል ፍልሚያ?
የወልቃይት ፖለቲካዊ ውዝግብ በሰላማዊ አማራጭ እንደሚፈታ ከፕሪቶሪያ ስምምነት ጀምሮ በሰፊው ሲነገር ቆይቷል፡፡ ወልቃይት በጥይት እልባት እንደማያገኝም ብዙ ሲባልበት ቆይቷል፡፡ በስምምነቱ ሰነድ ላይ አጨቃጫቂ የሆኑ…
https://www.ethiopianreporter.com/130539/
ከአገር ግንባታ ጋር የተያያዙ ወሳኝ የቅርብ ታሪካችን አንጓዎች
በታደሰ ሻንቆ
በአያሌው የተመረጡና ልጥ የሌላቸው ነጥቦች የተደራጁበት ይህ ታሪክ ነክ ቢጋር፣ ዓላማው የኢትዮጵያ ታሪክ ተብሎ ሲጻፍ በኖረው ላይ ፍርድ መስጠት ወይም ወቀሳ መደርደር አይደለም፡፡…
https://www.ethiopianreporter.com/130527/
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የውጭ ግንኙነት የሺሕ ዘመናት ታሪኳና እሴቶቿን የሚመጥን መሆን ይኖርበታል
(ክፍል አንድ)
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)
እንደ መንደርደሪያ ለዛሬው የግል ትዝብቴንና ታሪክን ላዛነቀው ጽሑፌ መነሻ የሆነኝ በቅርቡ በአፍሪካ ኅብረት ኔልሰን ማንዴላ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለአንድ ቀን የተካሄደው፣ ‹‹የአፍሪካ መንፈሳዊ…
https://www.ethiopianreporter.com/130521/
ከባለአንድ ዋልታ ወደ ባለብዙ ዋልታ የዓለም ሥርዓት የመሸጋገራችን እውነታ
በአብዱ ሻሎ
አንገት ማስገቢያ እ.ኤ.አ. በፌብሩዋሪ 2022 የሩሲያ መንግሥት በዩክሬን ‹‹ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን›› በሚል ጦሩን ወደ ዩክሬን ካዘመተ ከቀናት በኋላ በዓለም አቀፍ የጂኦ ፖለቲካ አረዳዱ በጣም…
https://www.ethiopianreporter.com/130525/
የምግብ ዋጋ ንረት አጣዳፊ ዕርምጃ ያስፈልገዋል!
መንግሥት የሚቀጥለውን ዓመት በጀት ይዞ ሲቀርብ በአንገብጋቢነት ከሚነሱ ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ የዋጋ ንረትን ለመቀነስ ምን ታስቧል የሚለው ጥያቄ ነው፡፡ በጀት ለተለያዩ መንግሥታዊ ወጪዎች ሲደለደል…
https://www.ethiopianreporter.com/130489/
አገራዊ ምክክሩ ከመንግሥትና ከፖለቲካ ተፅዕኖ እንዲላቀቅ ተጠየቀ
በአገራዊ የምክክር ኮሚሽን የሚከናወነው ምክክር፣ ከመንግሥት አስተሳሰብና ከፖለቲካ ተፅዕኖ ገለልተኛ እንዲሆን ጥያቄ ቀረበ፡፡ ይህ የተባለው ስለፅናት ለኢትዮጵያ የአገር ወዳዶች ማኅበር (ፅናት ለኢትዮጵያ) እና ሰላምና አንድነት ለኢትዮጵያ ማኅበር ‹‹በምክክር አገር ትዳን›› በሚል መሪ ቃል ሰኔ 6…
https://www.ethiopianreporter.com/130468/
ምርጫ ቦርድ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሕግ ማሻሻያዎችን ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቀ
በምርጫ በሚያዙ ወንበሮች ፍትሐዊ ውክልና ለማረጋገጥ የምርጫ ክልል ወሰኖች ይሻሻላሉ ተብሏል የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት ምርጫዎችንና ሕዝበ ውሳኔዎችን ለማከናወን የሚያስችሉና የቦርዱን አቅም የሚያጠናክሩ የሕግ ማሻሻያዎችን እንደሚያደርግ ገለጸ፡፡ በሕግ ማዕቀፎች ላይ ያሉትን ክፍተቶች ለማየት ጥናቶች…
https://www.ethiopianreporter.com/130470/
ኢሰመኮ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች ያገረሸው ግጭት አፋጣኝ መፍትሔ ያስፈልገዋል አለ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአፋርና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ በድጋሚ ያገረሸው ጦርነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዳሳሰበው ገልጾ አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጥ ጠይቋል፡፡ ኮሚሽኑ ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ እንደ አዲስ ባገረሸው ግጭት ንፁኃን እየሞቱ…
https://www.ethiopianreporter.com/130476/
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ ታሪፍ ሊያሻሽል መሆኑን አስታወቀ
ከ367 ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ እንዳለበት ተገልጿል በየዓመቱ በአማካይ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ እያገኘ ቢሆንም 26 ቢሊዮን ብር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑ ተጠቁሟል በሚያመነጨው ኃይል መጠንና በማመንጫዎቹ ከአፍሪካ የኤሌክትሪክ ኃይል አስተዳዳሪ ተቋማት ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው የኢትዩጵያ…
https://www.ethiopianreporter.com/130479/
የጠፋ አውሮፕላን ፈልጎ የማዳን ቴክኖሎጂ በልፅጎ ለሥራ ዝግጁ መሆኑ ተነገረ
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የጠፋ አውሮፕላን ፈልጎ የማዳን ቴክኖሎጂ አበልፅጎ ለሥራ ዝግጁ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ አሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ አገልግሎት ከሚሰጡ ሁለት ቴክኖሎጂዎች አንደኛው የሆነው ‹‹ኢንሲደንት ኮማንደር ፕሮ ኤይት›› የተሰኘ ቴክኖሎጂ በመግዛት፣ አገር ውስጥ ማስገባቱን የሲቪል…
https://www.ethiopianreporter.com/130482/
በኢትዮጵያ ሁለት ክልሎች የሚካሄዱ ግጭቶች ለሰብዓዊ መብቶች መጣስ ምክንያት መሆናቸውን ተመድ ገለጸ
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (UNOHCHR)፣ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ በተመለከተ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች የሚካሄዱ ውጊያዎች ዋነኞቹ ለሰብዓዊ መብት መጣስ ምክንያት መሆናቸውን ገለጸ፡፡ ኮሚሽኑ የአውሮፓዊያኑ የ2023 የኢትዮጵያን…
https://www.ethiopianreporter.com/130485/
የትግራይና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቃዮች ጊዜው ያለፈበት እህል እየተሰጣቸው ስለመሆኑ ለፓርላማው ተናገሩ
‹‹ጊዜው ያለፈበት የዕርዳታ እህል ያሰራጨ አካል ወይም ተቋም ተጠያቂ ይደረጋል›› የአደጋ ሥጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን የትግራይና የቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተፈናቃዮች ጊዜው ያለፈበት የዕርዳታ እህል እየተሰጣቸው መሆኑን፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ…
https://www.ethiopianreporter.com/130487/
ከፓርቲ ፖለቲካ የፀዳ ሲቪል ሰርቪስ የመገንባት ጉዳይ በአገራዊ ምክክሩ እንዲታይ ተጠየቀ
የዩኒቨርሲቲ መምህራን በዶላር ይከፈለን እያሉ ነው ተብሏል ከፓርቲ የፖለቲካ ዕሳቤ የፀዳና ነፃና ገለልተኛ የሲቪል ሰርቪስ አደረጃጀት የመገንባት ሥራ አገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በጀመረው ሒደት እንዲታይ፣ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ጠየቁ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመንግሥት…
https://www.ethiopianreporter.com/130492/
ኑሮ የከበዳቸው የመንግሥት ሠራተኞች የምሳ ሰዓትን በቤተ እምነቶች እያሳለፉ መሆኑ ተነገረ
የቤት ኪራይ መክፈል ያልቻሉ ተደብቀው ቢሮ ውስጥ ያድራሉ ተብሏል መንግሥት የሚከፍላቸው ወርኃዊ ደመወዝ አልበቃ ያላቸው የመንግሥት ሠራተኞች የምሳ ሰዓታቸውን ወደ ቤት እምነቶች በመሄድ፣ እንዲሁም ቤት ተከራይተው መኖር የማይችሉት ደግሞ ቢሮ ውስጥ ተደብቀው እንደሚያድሩ ተገለጸ፡፡ በ2010 ዓም…
https://www.ethiopianreporter.com/130495/
የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡና የአገር ውስጥ ባንኮች እንዲዋሃዱ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ቀረበ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የአገር ውስጥ ባንኮችን ውህደትና የውጭ ባንኮች በተገደበ ሁኔታ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ እንዲገቡ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ባለፈው ዓርብ ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ አፀደቀ። በረቂቅ አዋጁ የተካተቱ በርካታ ድንጋጌዎች…
https://www.ethiopianreporter.com/130502/
ከውጭ በተላከ ገንዘብ ሀብት አፍርቶ የተላከበትን ደረሰኝ ያላቀረበ ንብረቱ እንዲወረስ የሚደነግግ አዋጅ ቀረበ
በጥፋተኝነት ላይ ያልተመሠረተ ንብረት የመውረስ ድንጋጌም በአዋጁ ተካቷል አዋጁ የሚፀድቅ ከሆነ 10 ዓመት ወደኃላ ተመልሶ ተፈጻሚ ይሆናል ከውጭ በተላከ ገንዘብ ሀብት አፍርቶ የተላከበትን ደረሰኝ ያላቀረበ ሰው ወይም ሊታወቅ ከሚችል ገቢው በላይ ሀብት አፍርቶ ምንጩ ሕጋዊ መሆኑን…
https://www.ethiopianreporter.com/130508/
የአየር ብክለት በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ ያደረሰው የጤና ጫና
ተፈጥሮ በበርካታ ውስብስብ ፈተናዎች ውስጥ እያለፈች ትገኛለች፡፡ ከእነዚህ ፈተናዎች መካከል የአየር ብክለት በቀዳሚነት ከሚጠቀሱት የሚመደብ ነው፡፡ ለከባቢ አየር ብክለት በዋናነት ምንጩ የሰው ልጅ ሲሆን፣…
የ‹‹ክብር ዶክትሬት›› ዲግሪ ጉዳይ
በንጉሥ ወዳጅነው ‹‹የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ግልጽ የሆነ መመርያ እስኪወጣ ድረስ እንዳይሰጥ በጊዜያዊነት ታገደ›› የሚል መረጃ ከትምህርት ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ከተነገረ አንድ ወር አልፎታል፡፡ እንደ መግለጫው…
https://www.ethiopianreporter.com/130436/