Blog Archives

አክሳሪ የቁጠባ መጣኝ (ጌታቸው አስፋው)

አክሳሪ የቁጠባ መጣኝ *** ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) *** የገጠሬው ቁጠባ ያልደረሳቸው አንዳንድ የከተማ ነጋዴዎች በብድር ጥሬ ገንዘብ እጦት ሥራ ሊቆም ነው ይላሉ፤ ንግድ ባንኮች መንግሥት በምናበድረው ጥሬ ገንዘብ ሃያ ሰባት በመቶ ቦንድ እንድንገዛ ስለሚያስገድደን ለደንበኞቻችን የምናበድረው ጥሬ ገንዘብ አንሶናል ይላሉ፡፡ ብሔራዊ ባንክ በሚያዘጋጀው ዓመታዊ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ሪፖርት ንግድ ባንኮች በሕግ ተደንግጎ በብሔራዊ ባንክ ማስቀመጥ ከሚገባቸው መጠባበቂያ ተቀማጭ በላይ እስከ ዐሥር ቢልዮን ትርፍ ምንዛሪ ጥሬ ገንዘብ ወይም ብር በያመቱ እንደሚያስቀምጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ የግልና የመንግሥት ንግድ ባንኮች የጥሬ ገንዘብ ችግር እንደሌለባቸው የባንክ ለባንክ መበዳደር እጅግ በጣም ዝቅተኛ መሆንም ማስረጃ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ውዥንብር ምንጩ ምንድነው? ሪፖርተር ጋዜጣ፣ እሑድ ታኅሣሥ 19 ቀን 2007 ዓ.ም. “የፋይናንስ አቅርቦት አሁንም እያከራከረ ነው፤” በሚል ርዕስ ለንግዱ ማኅበረሰብ አንድ የብሔራዊ ባንክ ባለሥልጣን የአክስዮን ንግድ ሳይስፋፋ የመዋዕለንዋይ ባንክ ማቋቋም ዋጋ የለውም በማለት የሰጡትን መልስና የልማት ባንክ ባለሥልጣንም ልማት ባንክ ብሔራዊ ባንክ የፈቀደለትን ገንዘብ እንኳ አበድሮ አልጨረሰም በማለት የሰጡትን መከራከሪያ መልስ አውጥቶ ነበር፡፡ ስብሰባውን ያልተካፈለው የገንዘቡ ምንጭ የሆነው ቆጣቢው ድምጹን የማሰማት ዕድል አጥቶ እንጂ የርሱን ያህል የተጎዳ የለም፡፡ ከ2003 እስከ 2007 የነበሩት የዋጋ ንረት መረጃዎች አማካይ 16.3 ነው፡፡ በዚህ የዋጋ ንረት የገንዘብ ሸቀጦችን የመግዛት አቅም በዐሥራ ስድስት ነጥብ ሶስት በመቶ ስለሚወድቅ አምስት በመቶ የቁጠባ ወለድ እያገኘ ገንዘቡን ባንክ የሚያስቀምጥ ሰው ለተበዳሪው ዐሥራ አንድ ነጥብ ሦስት በመቶ ከፍሎ
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በሊብራል ገበያ የንግድ ሥነ-ምግባር ( ጌታቸው አስፋው )

በሊብራል ገበያ የንግድ ሥነ-ምግባር *** ጌታቸው አስፋው *** በዓለም ዐቀፍ ኢኮኖሚ ጥናት ከምርትም በላይ ትኩረት ስቦ ብዙ የተባለለት ንግድ ነው፡፡ በተግባር ቅደም ተከተል ማምረት ከመነገድ ይቀድማል፡፡ ሆኖም ግን ሰዎች ከራሳቸው የግል ፍጆታ አልፈው በግብይይት መልክ ያመረቱትን ሽጠው ከገበያ የሚፈልጉትን ለመግዛት ያደረጉት እንቅስቃሴ በኢኮኖሚ ጥናት ውስጥ ትልቅ ቦታ አለው፡፡ የዚህ ምክንያቱም ማምረት ግላዊ ብቻ ሊሆንም ሲችል፣ ንግድ ግን ማኅበራዊ ስለሆነ ነው፣ የሰፊ ሕዝብ እንቅስቃሴ ስለሆነ ነው፡፡ ተጨማሪ እሴት የሚፈጠረው በምርት ሂደት ቢሆንም ዋጋ ግን የሚወሰነው በንግድ ሂደት ውስጥ ስለሆነ ነው፡፡ ኢኮኖሚክስ እንደ የማኅበራዊ ኑሮ ዘዴ የጥናት መስክ ሆኖ ሲጀምር የሞራልና የሥነ-ምግባር ጥበብ ነበር፡፡ ጥንት ከከፕሌቶና አሪስቶትል ጀምሮ ስለ ሀብት ይዞታና አጠቃቀም በሥነ-ምግባር ደንብ ተጠንቷል፡፡ ከኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ውስጥ በተለይ ንግድ ለብዙ ዘመናት ማጭበርበርና ማታለል ያለበት የማኅበረሰብ ጠንቅና የተወገዘ ነገር ተደርጎ ይቆጠር ነበር፡፡ ሮማውያንም የግሪኮችን ወርሰው ለንግድ በጎ አመለካከት አልነበራቸውም፡፡ በመካከለኛው ክፍለ ዘመን የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ከጥሬ ገንዘብ ንግድ (ብድር) ወለድ መውሰድን እንደነውር ቆጥራ አውግዛለች፡፡ ዛሬም በእስልምና ሃይማኖት ባንክ ከሚቀመጥ ጥሬ ገንዘብ ወለድ መቀበል ሀጢዓት ተደርጎ ወለድ አይቀበሉበትም፡፡ አቅመቢሱን በንግድ ግንኙነት በዝብዞ፣ ሌላውን አደህይቶ ራስ መክበር ዛሬም ቢሆን የግለሰቦችና የአገራት የብልጽግና መንገድ ነው፡፡ ሆኖም ንግድ በሁለት ሕጋዊ ሰውነት ባላቸው አካላት ስምምነት የሚፈጸም ስለሆነ ሕጋዊ ነው፡፡ በሕግ ከተደነገጉት የሰው አካልን ወይም እጾችን ከመነገድ ሸቀጦችን ደብቆ አላግባብ እጥረት ፈጥሮ ከማትረፍ በቀር በስምምነት መነገድ ማትረፍ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ግራ አጋቢ ምክር በውጭ ጣልቃ ገቦች ( ጌታቸው አስፋው)

ግራ አጋቢ ምክር በውጭ ጣልቃ ገቦች ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) *** ታዳጊ አገራት በቀጥታ ወደ ገበያ ኢኮኖሚ ሊገቡ ስለማይችሉ በቅድሚያ በኢኮኖሚ ልማት ራሳቸውን ማሳደግ አለባቸው ብለው ያማከሩት በገበያ ኢኮኖሚ ፍልስፍና ያደጉ ምዕራባውያን ናቸው፣ ከጊዜ በኋላ ሐሳባቸውን ቀይረው የመዋቅር ማሻሻያ ፕሮግራም ነድፈው ወደ ገበያ ኢኮኖሚ ግቡ ያሉትም እነሱው ናቸው፡፡ ከቅኝ ግዛት ማብቃት ጀምሮ እስከ ግሎባላይዜሽን በነበረው ጊዜ የእያንዳንዱ አገር ኢኮኖሚ ግንኙነት የተመሠረተው በኹለትዮሽ የአገራት ንግድ ስምምነት ላይ ስለነበረ፣ ታዳጊ አገራት ራሳቸውን ችለው በኢኮኖሚ ልማት ፍልስፍና ለአገራቸው የሚበጅ የውስጥና የውጭ ኢኮኖሚ ግንኙነት ቢያድጉ ምዕራባውያንን የሚጎዳቸው ነገር ስለሌለ አልተቃወሟቸውም፡፡ በግሎባላይዜሽን ዘመን ግን በሌላ አገር ጥሬ የተፈጥሮ ሀብት ለማደግ የንግድ ትስስር መፍጠርና በሌላ አገር ርካሽ ጉልበት ለመጠቀም በውጭ አገር መዋዕለንዋይ ማፍሰስ ተፈልጎ ምዕራባውያን መንግሥታት በዓለም ዐቀፍ ድርጅቶች ተጽዕኖ ታዳጊ አገራት የገበያ ኢኮኖሚን እንዲከተሉ ግፊት አደረጉ፡፡ የውስጥና የውጭ ኢኮኖሚ ግንኙነት ፖሊሲያቸው የዓለም ዐቀፍ ንግድን እንዳያደናቅፍ ብለው ከለከሏቸው፡፡ ለአገራቸው ከማሰብ ይልቅ ለዓለም እንዲያስቡ መከሯቸው፡፡ የመዋቅር ማሻሻያ ፕሮግራም ወይም አንዳንዴ እንደሚጠራው የዋሽንግተን መግባቢያ ስምምነት ዓለም ዐቀፍ ድርጅቶች ለታዳጊ አገራት በሚሰጡት ብድርና እርዳታ ወደ ገበያ ኢኮኖሚ ለማስገባት በቅድመ ሁኔታነት እንዲያሟሉ የነደፉት ፕሮግራም ነው፡፡ ይህን ፕሮግራም ብዙ ታዳጊ አገራት አልጠቀመንም ብለው ሲተውት፣ ዓለም ዐቀፍ ተቋማቱ ያልጠቀማቸው ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ስላላደረጉት ነው ይላሉ፡፡ የፕሮግራሙ ዋና ዓላማ ብሔራዊ ኢኮኖሚውን ማረጋጋት እና ከግሎባላይዜሽን ጋር አብሮ ለመራመድ ለንግድና ለውጭ ኢንቨስትመንት በርን
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የወዳጅ ከበርቴ ቡድን መንግሥት ( ጌታቸው አስፋው)

የወዳጅ ከበርቴ ቡድን መንግሥት *** ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) *** ኢትዮጵያ ሶሻሊዝምን አስወገድሁ ካለች በኋላ ገነባሁት የምትለው የነጻ ገበያ ካፒታሊዝም ሥርዓት፣ እስካሁን በብዙ የአገር ውስጥ ባለሙያዎች ተቀባይነትን አላገኘም፡፡ በተቃራኒዎች አብሮ የመኖር ሕግ መሠረት ካፒታሊስት ካለ ወዛደርም መኖር ስላለበት፣ ከመቶ ሚልዮን ሕዝብ ውስጥ ግማሽ ሚልዮን ያልሞላ ወዛደር ያለባት ኢትዮጵያ፣ በዚያው ልክ ቁጥር ውስጥ የሚገባ ካፒታሊስትም የላትም፤ ኢትዮጵያ ያላት ካፒታሊስት ያልሆነ የከበርቴ ቡድን ነው በማለት የሚሞግቱ አሉ፡፡ ካፒታሊስት ሀብቱን በመዋዕለንዋይ መልክ አውጥቶ ሠርቶ የሚያሠራ ሲሆን፣ ከበርቴ ግን ሀብቱ ከየት እንደመጣ እንኳ የማያውቅ ኅብረተሰብን ቦርቡሮ የሚከብር ነቀዝ ነው፡፡ የኖቤል ተሸላሚው ጆሴፍ ስቲግሊዝ በ2011 ‹ቫኒቲ ፌር› ለተባለ መጽሔት “የአንድ በመቶው፣ በአንድ በመቶው፣ ለአንድ በመቶው” በሚል ርዕስ በጻፉት መጣጥፍ አሜሪካ ለአንድ በመቶዎቹ (the 1%) ባለፀጎች ጥቅም በቆመ የባለፀጎች አስተዳደር (ፕሉቶክራሲያዊ) መንግሥት እየተዳደረች ነው አሉ፡፡ አሜሪካውያን ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጡ፣ የሚይዙት መፈክርም “እኛ ዘጠና ዘጠኝ በመቶዎቹ” በማለት አንድ በመቶዎቹ በዝባዦች፣ ዘጠና ዘጠኝ በመቶዎቹ ተበዝባዦች ብለው ራሳቸውን በመከፋፈል ሆኗል፡፡ የገበያውን ማድላት ተጠቅመው የከበሩ የአሜሪካ ቢልየነሮች ካርል ማርክስ ካፒታሊዝም ብዝበዛውን አስፋፍቶ የራሱን መቃብር ራሱ ይቆፍራል ትንበያን ስለሚያውቁ፣ ስጋትም መልካም አጋጣሚ ውስጥም እንዳሉ ይገምታሉ፡፡ ስጋቱ፣ “የሀብት ሥርጭት ክፍተቱ ካርል ማርክስ የተነበየውን ካፒታሊዝም የራሱን ጉድጓድ ራሱ ይቆፍራል ሊሆን ነው እንዴ?” የሚለው ነው፡፡ መልካም አጋጣሚውም ለሀብታሙ ከዘነበ ለድሃውም ያካፋል በሚል መርህ፣ የድሆቹን ገቢና የፍጆታ አቅም በማሳደግ ቢልየነር ካፒታሊስት ትሪልየነር ካፒታሊስት
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በባንኮች የዶላር ምንዛሬ ከዚህ በፊት ከነበረው ምንዛሬ ጋር ሲነጻጸር በከፍተኛ ሁኔታ ጨመረ።

የዶላር ምንዛሬ ከዚህ በፊት ከነበረው ምንዛሬ ጋር ሲነጻጸር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገለጸ።ባንኩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ ግለሰቦች የያዙትን የውጭ ሀገር ገንዘብ በባንክ እንዲመነዝሩ መልእክት ማስተላለፋቸውን ተከትሎ የመጣ ከፍተኛ የምንዛሬ ለውጥ መሆኑን ተናግሯል። በአሁኑ ወቅትም ሰዎች በተለያዩ የባንኩ ቅርንጫፎች በመገኘት የሚመነዝሩት እለታዊ የውጭ ምንዛሬ መጠን ከ4 ሚሊየን እስከ 6 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደሆነ ነው ያስታወቀው።ባሉት ሁሉም ቅርንጫፎች የውጭ ሀገር የገንዘብ ምንዛሬ መጨመሩ የተላለፈው መልእክት ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን ያመለክታል ብሏል ባንኩ። ይህ ከፍተኛ የሆነ የዶላር ምንዛሬ መጠን መጨመሩም አስደሳች እንደሆነ እና ሊበረታታ እንደሚገባም ተገልጿል።ከዚህ ባለፈም ባንኩ ይህንን ጥሩ ተሞክሮ ለማስቀጠል ህብረተሰቡ በእጁ የያዘውን ዶላር በባንኩ በመመንዘር ሀገራዊ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ነው ጥሪ ያስተላለፈው።
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ገና ምንም ያልተነካው የኢኮኖሚ ጉዳይ (ጌታቸው አስፋው)

ገና ምንም ያልተነካው የኢኮኖሚ ጉዳይ (ጌታቸው አስፋው) (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሥልጣን ከተረከቡበት ጊዜ አንስቶ በአገር ውስጥና በውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውን ከፍተኛ ድጋፍ እንደተቸራቸው ለማንም ግልጽ ነው፡፡ ዐፄ ቴዎድሮስ በዐሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን በመሳፍንት የተበታተነችውን ኢትዮጵያ አንድ አድርገው፣ እስከዛሬ ድረስ በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ያልተዳፈነ ፍቅር ተጎናጽፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም ኹለት መቶ ዓመታት የማይዳፈን ፍቅር ከኢትዮጵያውን ሊያገኙ እንደሚችሉ፣ በአዲስ አበባ በተደረገላቸው የድጋፍ ሰልፍ ላይ አንዲት አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊት ይዛ የወጣችውን መፈክር ብቻ አይቶ ማወቅ ይቻላል፡፡ የያዘችው መፈክር “አገሬን ስላከበርክ አከበርኩህ፤” የሚል ነበር፡፡ በየትኛውም ዘመን የነበሩ ያሉና የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለአገራቸው እንደዚህ ናቸው፡፡ በዚህ ዘመን የሕዝብን ሙሉ ፍቅርና ክብር ለማግኘት ፍቅሩም ዘመን ተሸጋሪ እንዲሆን አንድነትን ከመፍጠሩ ባሻገር የሚቀረው ነገር አለው፡፡ ለዚህ ዘመን ከፖለቲካዊ አንድነት ባሻገር የሰዎች ኢኮኖሚያዊ ሕይወትም በመንግሥት ፖሊሲ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ዶ/ር ዐቢይ በዓይን ስለሚታዩት የከተማ ፎቆች ብቻ ሳይሆን በዓይን ስለማይታዩት፣ ስለሚራቡ፣ ስለሚጠሙ፣ ስለሚታረዙና መጠለያ ስላጡ ብዙ ሚልዮን ዜጎች ሕይወትም ግድ እንደሚላቸው አልጠራጠርም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝባዊ አንድነት ፖለቲካው የሰጡትን ትኩረት ያህል ለኑሮ ደረጃ መሻሻል እንዲሰጡ በፖለቲካው እንደተሳካላቸው በኢኮኖሚውም እንዲሳካላቸው ሁላችንም በሙያችን ልናግዛቸው ይገባል፡፡ ስለሚታየው ብቻ ሳይሆን ስለማይታየውም እንንገራቸው፡፡ እርሳቸው ከመጡ በኋላ የውጭ ምንዛሪ ግኝትን የሚያሳድጉ የመንግሥት ተቋማትን በግልና በመንግሥት ሽርክና እስከ መስራት የደረሱ አንዳንድ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎችን ስለወሰዱ የውጭ ምንዛሪ መጣኝ ኦፊሴላዊ ዋጋ እና የጥቁር ገበያ ዋጋ እየተቀራረቡ መጥተዋል፣
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

አንደኛ ደረጃና ኹለተኛ ደረጃ ዜጋ (በጌታቸው አስፋው)

አንደኛ ደረጃና ኹለተኛ ደረጃ ዜጋ ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) የፊተኞች የኋለኞች የኋለኞች የፊተኞች ሆኑና በደርግ ጊዜ እያንዳንዱ በአገር ውስጥ የኖረ ሰው ላቡን አፍስሶ ያፈራውና የሕዝብና የመንግሥት የነበረውን የአገር የጋራ ሀብት ከበረሃና ከወጭ አገር ተለቃቅመው የመጡት በወራት ውስጥ በእጃቸው አስገቡት፡፡ አንጡራ የጋራ ንብረታቸውን እነርሱ እያላበቸው ሲያመርቱ በቦታው ያልነበሩ አዲሶች የኢንዱስትሪ ባለቤት፣ የአገልግሎት መስጫ ድርጅት ባለቤት ሆነው፣ የትላልቅ ኩባንያዎች ባለቤት ሆነው፣ በኢንዶውመንት ለታጋዮች ለተሰጡት ድርጅቶች ሥራ አስኪያጅ ሆነው በመንግሥት እጅ ለቀጠሉት ድርጅቶችም ሥራ አስኪያጅ ሆነው በአገሪቱ አንደኛ ደረጃ ዜጋ ሆነዋል፡፡ ነባሮቹ የላባቸውን ፍሬ ተቀምተው በድጋፍ ሰጪ አነስተኛ አገልግሎቶች ተሰማርተው አዲስ መጪዎቹን በወሬ በሙዚቃ በቲያትር ለማዝናናት፣ ሆቴል ከፍቶ ምግብ አብስሎ በመቀለብ፣ ታክሲ ነድቶ በማመላለስ፣ ልጆች በማስተማር፣ ንግድ ነግዶ ሸቀጥ በማቅረብ፣ የሰርግ የልደት የቀብር ማስፈጸሚያ አገልግሎት በመስጠት ለዋና አምራቾቹ ኹለተኛ ደረጃ ሥራዎችን ሠርቶ ለማገልገል የተፈጠሩ ኹለተኛ ደረጃ ዜጎች መስለዋል፡፡ ከዚህም በላይ በፖለቲካ ሥልጣንና በሀብት ይዞታ የነበራቸውን አደህይቶና ያልነበራቸውን አክብሮ ሌላ ዓይነት የኅብረተሰብ አደረጃጀት ለመፍጠር ግብ ይዞ ተግቶ የሠራው የኢሕአዴግ ፖለቲካል ኢኮኖሚ ሦስት መንገዶችን ተጠቅሞ አንደኛና ኹለተኛ ደረጃ ዜጎችን ለመፍጠር የያዘውን ዓላማ አሳክቷል፡፡ በአንደኛውና በመጀመሪያው መንገድ ደርግ ወርሶ የሕዝብ ያደረገውን የአገር ሀብት አንድ ጠብታ ላብ እንኳን ያላፈሰሱ ሰዎች በብሔራዊ ባንክ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቤቶችና ኮንስትራክሽን ባንክ በልማት ባንክ ተቀምጦ በነበረ የሕዝቡ ገንዘብ ራሳቸው ሻጭ ራሳቸው ገዢ በመሆን ተከፋፈሉት፡፡ በሁለተኛውና በሦስተኛው መንገዶች ከሀብት ክፍፍሉም
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዋጋዎችን ትክክለኛ ማድረግ (በጌታቸው አስፋው)

ዋጋዎችን ትክክለኛ ማድረግ *** በጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) *** ባለፈው ጽሑፌ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት በግማሽ መቀነስ እንዳለበት ለኢኮኖሚ ባለሙያዎችና ለመንግሥት አስተያየት አቅርቤ ነበር፡፡ ዛሬም ይህንኑ አስተያየቴን የሚያበለጽግ ጽሑፍ ይዤ ቀርቤአለሁ፡፡ ግብዓተ ምርቶችና ምርቶች ትክክለኛ ዋጋቸውን ሳያገኙ በፊት ለማደግ የሚደረግ ሩጫ መጨረሻው ግብ ላይ ሳይደርሱ ተደነቃቅፎ መውደቅ ነው፡፡ ኢኮኖሚስቶች ይህንን እውነታ getting the prices right በማለት ይገልጹታል፡፡ የሠራተኛው የሥራ ዋጋ ደሞዝ፣ የካፒታል ዋጋ ወለድ፣ የመሬት ዋጋ ኪራይ፣ የድርጅት ዋጋ ትርፍ፣ የቁሳዊ ምርትና የአገልግሎት ምርት ዋጋዎች ሁሉም በተወዛገበ የዋጋ አወሳሰን ሥርዓት ውስጥ ሆነው የተረጋጋ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ሰማይን ለመቧጠጥ እንደመሞከር ነው፡፡ ሁላችንም ኢኮኖሚያችን እንዲያድግ እንፈልጋለን፡፡ ኢኮኖሚው በጤናማ ሁኔታ እንዲያድግ ግን በቅድሚያ የዋጋ አወሳሰን ሥርዓቱ መስተካከል አለበት፡፡ በገበያው ውስጥ ግብዓተምርቶችና ምርቶች ትክክለኛውን ዋጋቸውን እንዲያገኙ ማድረግ ከቻልን ስለዕድገቱ ገበያው ራሱ ያስብበት ነበር፡፡ ዐይናችንን ጨፍነን ወደ የማናውቀው ግብ ከመሮጥ ዕድገትን በዋጋ መረጋጋት ሥርዓት ውስጥ ለማምጣት ግብዓተ ምርቶችም ሆኑ ምርቶች ትክክለኛ ዋጋቸውን ማግኘት አለባቸው፡፡ ሠራተኛውም ካፒታሉም መሬቱም ድርጅቱም በምርታማነታቸው ልክ የሚገባቸውን ካላገኙ ግን የሚገኘው ተጨማሪ ገቢ ከዕድገት የመጣ ሳይሆን አንዱ ሌላውን እየበዘበዘው ነው፡፡ በአንድ ነጥብ ሁለት ሚልዮን ካሬ ኪሎ ሜትር የቆዳ ስፋት ላይ ያለን፣ ከመቶ ሚልዮን በላይ የሆነ ሕዝብ በዝብዛ በፍጥነት ባደገች የአምስት መቶ ካሬ ኪሎ ሜትር የአዲስ አበባ ምድር ላይ የምንገኝ ጥቂት ሰዎች የራሳችንን ማደግ የአገሪቱ ዕድገት አድርገን እንቆጥራለን፡፡ በአዲስ አበባዋም ቢሆን ከጥቂት
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት በግማሽ መቀነስ አለበት – ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ)

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት ለቀጣይነቱ፣ ለሰላምና ለማኅበራዊ መረጋጋት እንዲሁም ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል ሲባል፣ እስካሁን ከሚያስመዘግባቸው የዐሥርና ዐሥራ አንድ በመቶ ዕድገት መጣኞች በግማሽ ቀንሶ ለተወሰኑ ዓመታት ወደ አምስትና ስድስት በመቶ የዕድገት መጣኞች ዝቅ ማለት አለበት፡፡ የአገር ኢኮኖሚ ዕድገት ይቀንስ ሲባል ያማል ነገር ግን ታሞ ከስቃይ መዳን የሚቻል ከሆነ፣ እየተሰቃዩ ለረጅም ጊዜ ከመኖር ለጥቂት ጊዜ ታሞ መዳን ይሻላል፡፡ እየተራብን እየታረዝን መጠለያ አጥተን የፍጆታችን መጠን ከዓለም የመጨረሻውን ደረጃ ይዞ በዕድገት ከዓለም አንደኛ ነን ብለን መፎከር፣ ሥቃያችንን አምቀን ይዘን በዕድገታችን ከእኛ የሚስተካከል አገር የለም ማለት አላዋጣንም፡፡ በሁለት አሃዝ ማደጋችንን ለዓለም ሕዝብ ለማውራት ፈልገን በዓለም ዐቀፍ ድርጅቶችና ለአንድ ቀን በጎበኘን ፈረንጅ የምናስመሰክረው የጉራ ወሬ ማኅበራዊ መሠረታችንን አናጋው ሰላማችንን አደፈረሰው፡፡ ማንኛውም ነገር የዕጦት ወጪ (Opportunity Cost) አለው፤ ለመዋዕለንዋይ በወጣ ወጪ ብዙዎች ፍጆታ ቀርቶብናል፡፡ በተሠሩት ሕንጻዎች ልክ በተዘረጉት መንገዶች ልክ በተከፈቱት ዩኒቨርሲቲዎች ልክ ዜጎቻችን ተርበዋል፣ ታርዘዋል፣ መጠለያ አልባ ሆነዋል፤ ተሰደዋል፤ በበረሃ በባሕርና በወንበዴዎች እጅ ሞተዋልም፡፡ የሚታዩትን ሕንጻዎች፣ መንገዶች፣ ዩኒቨርሲቲዎች፣ እየቆጠርን የማይታዩትን የተራቡ አንጀቶች፣ የታረዙ ገላዎች፣ መጠለያ ያጡ ነፍሶች፣ በኑሮ ሁኔታ የተሰደዱና እስከዘላለሙ ያሸለቡ ወጣቶቻች ሕይወት ሳንቆጥር በዕድገታችን እንኩራራለን፡፡ የብራችን ሸቀጥን የመግዛት አቅሙ እና ከውጭ አገሮች ምንዛሪዎች ጋር የመመነዛዘሪያ አቅሙ ቁልቁል ወርዶ ወጣቶች በአገር ውስጥ ሠርቶ ከመኖር በውጭ አገር ሰርቶ መኖር በብር ተመንዝሮ የሚገኘው ገቢ ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው አስልተው በበረሃና በባህር እየሞቱም ወደ ውጭ ለመኮብለል ልባቸው እስከሚሸፍት ድረስ የአገር
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የ“አድገናል አላደግንም፤ ለምተናል አለማን፤” ስሜታዊ ትርጉም (ጌታቸው አስፋው)

የ“አድገናል አላደግንም፤ ለምተናል አለማን፤” ስሜታዊ ትርጉም ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) ስለ አብዛኛው ሰው የኑሮ ዓይነትና ደረጃ አንዳንድ ሰዎች ሲገልጹ ኑሮ ተሻሽሏል ብለው ይናገራሉ፤ ይጽፋሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎችም ይሰማሉ፤ አይናገሩም፡፡ ያነባሉ፤ አይጽፉም፡፡ የማይናገሩ የማይሰሙ፤ የማይጽፉና የማያነቡም ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ቁጥራቸውም ቀላል አይደለም፡፡ ከሚናገሩት ከሚሰሙት፤ ከሚጽፉትና ከሚያነቡትም በእጅጉ ይበልጣል፡፡ ሐሳብ ለሐሳብ ከሚለዋወጡት ውስጥ የተማሩት ከልተማሩት፤ ያልተማሩት ካልተማሩት፤ የተማሩት ከተማሩት ይጨቃጨቃሉ፡፡ ኢኮኖሚው አድጓል አላደገም፤ ለምቷል አለማም፤ አድጓል ግን አለማም፤ ለምቷል ግን አላደገም፤ የንትርኩ ጭብጦች ሆነዋል፡፡ ሁሉም የራሱን ሐሳብ እንጂ የሌላውን ሊቀበል አይፈልግም፡፡ የማንኛቸውም ማስረጃ ውኃ አይቋጥርም፤ ለሌላውም አይዋጥም፡፡ ውይይቱና ክርክሩ በእውነት ስለ እውነት ሳይሆን ኢሕአዴግንና ኢሕአዴግ መራሹን መንግሥት ከመውደድና ከመጥላት የተነሳ ነው፡፡ በጽንሰ-ሐሳብ ላይ ያልተመሠረተ አመለካከት የግል ወይም የቡድን ብቻ ነው፡፡ ሙግቱም በተጨባጭ ሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ ፍሬ ከርሲኪ ሊሆን ስለሚችል፣ ስህተትን ለማስረዳት የሚችል ብቃት አይኖረውም፡፡ ለዚህም ነው፣ ኢኮኖሚው አድጓል የሚሉም፣ አላደገም የሚሉም፣ ለማደጉም ላለማደጉም፣ ለመልማቱም፣ ላለመልማቱም፣ ለመሻሉም፣ ላለመሻሉም ማረጋገጫ የሌላቸው፡፡ ሙግታቸውም ከመውደድና ከጥላቻ፣ ከማመንና ከመጠራጠር የመነጨ ብቻ የሚመስለው፡፡ ለማደጉም ላለማደጉም፣ ለመልማቱም ላለመልማቱም፣ አድጎ ላለመልማቱም፣ ለምቶ ላለማደጉም የሚቀርቡት ማስረጃዎች ምንጫቸው ሁለት ነው፡፡ አንዱ ለመንግሥት የኢኮኖሚ ባለሟሎች በቀር ለሌሎች ሰዎች የማይታይ ቢታይም የማይቀበሉት በባለሟሎቹ የሚዘጋጅ ስታቲስቲካዊ መረጃ ሲሆን፣ ሌላው ለመንግሥት ባለሟሎችና ባለሥልጣናት የማይታይ ቢታይም የማይቀበሉት ለአብዛኛው ሕዝብ በገበያ ውስጥ የሚታይ የኑሮ ሁኔታ ነው፡፡ በፖለቲካ እምነት ልዩነት ላይ ጥራዝ ነጠቅ ዕውቀት ተደርቦ መጠላላቱና መናናቁ ስለ
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የዶላር መንገድ – የሚያዛልቀንና ውጤት የሚያስገኝልን ሁነኛው መንገድ የትኛው ነው? ( ዮሃንስ ሰ)

• የግል ኢንቨስትመንት የሚስፋፋበትና ኤክስፖርት የሚያድግበት መንገድ! ይሄ ነው የሚያዋጣን! • የዳያስፖራ ዶላርስ? መልካም ነው። ግን፣ በእቅድ በዘመቻ ማሳደግና ማቋረጥ አይቻልም። • ወደ ውጭ የሸሸ ዶላር መመለስስ? ጥሩ። ግን፣ ተቀጥላ ችግር እንጂ ዋና ችግር አይደለም። • የነዳጅ ወጪን መቆጠብስ? ይሁን። ግን፣ ኢትዮጵያ በነዳጅ ፍጆታ የዓለም “ውራ” ናት። • ዶላር መበደርስ? በተቃራኒው፣ የዶላር እጥረት የሚያባባብስ ሆኗል – የብድር እዳና ወለድ! • እርዳታስ? ከኢኮኖሚ እድገት ጋር የተራራቁ የአውሮፓ አገራት፣ እርዳታ ሊጨምሩ? አይሆንም። በአጭሩ፣ ሌላው ሌላው ሁሉ፣ ተቀጥላና ቅርንጫፍ ነው። ዋና ችግሮችና መፍትሄዎች፤ ሁነኛውና ዘላቂው መንገድ፣ የግል ኢንቨስትመንትንና ኤክስፖርትን አለማደናቀፍ! መንግስት፣ ከውጭ በገፍ እንዳይበደርና በከንቱ ሃብት እንዳያባክን፣ ልጓም ማጥበቅ! ለተቋም መሪ፣ በተለይ ደግሞ መንግስትን የመሰለ ግዙፍ ተቋምን ለሚመራ ሰው፣… ከሁሉም በላይ፣ ቀዳሚና ትልቁ ስራው፣… ዋና ዋና መርሆችንና አላማዎችን… አንጥሮና አጥርቶ፣… 1፣ 2፣ 3… እያለ በግልፅ ማሳየት፣… ዋና ዋና የተግባር ዘዴዎችንና መሰረታዊ ትኩረቶችንም፣… በጥንቃቄ ለይቶ፣… 1፣ 2፣ 3 ብሎ ማስረዳት ነው። ይሄ ነው ከባዱና ዋናው የመሪ ስራ! አለበለዚያ፣ መያዣ መጨበጫ የሌለው ውጥንቅጥ ውስጥ፣ ጭራና ቀንዱ የተደበላለቀበ፣ የእልፍ አእላፍ ጉዳዮች ግርግር ውስጥ ተተብትቦ መቅረት ይሆናል መጨረሻው። ይህንን በሚገባ በመገንዘብም ይመስለኛል፣ ጠ/ሚ አብይ አህመድ፣ በየአካባቢው በርካታ ንግግሮችን በጥንቃቄ ለማቅረብ የመረጡት – ከሌሎች ስራዎች ሁሉ ቅድሚያ በመስጠት። (በዚያውም፣… በሦስት ዓመታት ቀውስ ጋር የተናጋውን አገር ለማረጋጋት፣ ክፉኛ እየተሸረሸሩ የመጡ የአገር ስረመሰረቶችንም ለመደገፍ፣ እንዲሁም ከየአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በሚደረጉ ውይይቶች፣
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ግንዛቤ እርከኖች (ጌታቸው አስፋው)

የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ግንዛቤ እርከኖች (ጌታቸው አስፋው) (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) የሥልጣን ዘመናቸውን ለማራዘም ያልተሠራውን ተሠርቷል ብለው፣ ሌላው የሠራውንም እኛ የሠራነው ነው ብለው በሚያቀርቡ መንግሥታትና ባለሟሎቻቸው ላለመታለልና የራሳቸው ተልዕኮ ያላቸውን የዓለም ዐቀፍ ድርጅቶች ምስክርነት ላለመቀበል፣ ስለራስ ጥንቅቆ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ምስክር ሳንፈልግ ሰው ሳይነግረን እኛው ራሳችን የኢኮኖሚያችንን ዕድገት ደረጃና ያለንበትን ተጨባጭ ሁኔታ ለክተን በልማት ኢኮኖሚውም ሆነ በገበያ ኢኮኖሚው ወይም ሁለቱን በማጣመር የዕድገት ጎዳና ምን ያህል እንደተጠቀምንና ምን ያህል እንደተጎዳን እነማን ተጠቅመው እነማን እንደ ተጎዱ ለወደፊት ምን ተስፋ እንዳለን ለመረዳት በፖለቲካ ጥላቻና ፍቅር እምነት ሳንወሰድ በሙያ ጥበብ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን በአረዳድ ቅርጽና መልክ ከፍለን ማየትና ማወቅ እንችላለን፡፡ የማያስፈልገውን ግሳንግስ ሁሉ ለማወቅ መሞከር ጊዜ ማጥፋትና ከንቱ ልፋት ነው፤ ማወቅ የሚገባን ብቻ ለይቶ ለማወቅም እንዴት መለየት እንደሚቻል ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ አዋቂዎች መረጃና ዕውቀትን ይመርጣሉ የመጣውን ሁሉ አያግበሰብሱም፡፡ ስለ ኢኮኖሚ የሚጠቅመውን እና የማይጠቅመውን ለመለየት ከዚህ በሚከተሉት በእርከን የተሳሰሩ የመረጃና የዕውቀት ቅደም ተከተሎች ተመርቶ ጠቃሚውን ከማይጠቅመው መለየት ይገባል፡፡ የሐሳቦችን እርስ በርስ ዝምድናና ግንኙነት አውቆ በግንዛቤ ማዕቀፍ ሳይንሳዊ ጥናት ለማድረግ ሐሳቦች እንዴት እንደሚፈጠሩና እንዴት እንደሚዳብሩ በእርከን በእርከን ማየት ይቻላል፡፡ ግንዛቤ ማለት ተጨባጭ ሁኔታን ሙሉ በሙሉ በአእምሮ ለማየት ማብሰልሰልና መረዳት ማለት ነው፡፡ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ሂደት ውስጥ የሚከሰቱ አንኳር ጉዳዮችን በኢኮኖሚ ጥበብ ወይም ኢኮኖሚክስ ለመረዳት በልዩ ልዩ እርከኖች ከፍሎ በየአንዳንዱ እርከን የሆነውን መመርመርና መገንዘብ ይቻላል፡፡ የሚከተሉት ስድስት እርከኖች ይህን ጽሑፍ በቅደም ተከተል
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ሦስት እጥፍ ያደገ ኢኮኖሚ — ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ)

በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ሦስት እጥፍ ያደገ ኢኮኖሚ — ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) *** ከላይ በእንቆቅልሽ መልክ በተመለከተው የአገር ውስጥ ጥቅል ምርት ዕድገት የሕዝቡን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ረገድ ፋይዳ ቢስ መሆኑን በገበያ መገለጫ ያረጋገጥን ቢሆንም፣ በስታቲስቲካዊ መረጃውም የተሳሳተ እንደሆነ ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ብዙ ኢትዮጵያውን ስለኢኮኖሚው የመንግሥትን መረጃ ፈጽሞ እንዳያምኑ ካደረጋቸው ምክንያቶች አንዱና ዋናው፣ የጥቅል የአገር ውስጥ ምርት ዕድገት ተብሎ የሚጠራው ነው፡፡ ገበያ ውስጥ ምርት ጠፍቶ ዋጋው በየጊዜው ከሚገባው በላይ ወደላይ እየተሰቀለ ምርቱና አቅርቦቱ በየዓመቱ በዐሥራ አንድ በመቶ አደገ ሲሉ ሕዝቡ ታዲያ እንዴት ይመናቸው? ይህ በፍጥነት አደገ የሚባል ጥቅል የአገር ውስጥ ምርት መጠን የሕዝቡን ዓመታዊ ነፍስ ወከፍ ገቢን ከልክ በላይ አሳድጎ በድህነት ቅነሳ መለኪያ አመልካች የሕዝቡ ኑሮ ደረጃ የተለወጠ በማስመሰል ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ሆኖበታል፡፡ ጥቅል የአገር ውስጥ ምርት በዓመት በአገር ውስጥ በሚኖሩ ሰዎች በገበሬው፣ በወዛደሩ፣ በፀጥታ አስከባሪው፣ በመከላከያ ሠራዊት አባሉ፣ በዳኛው፣ በጋዜጠኛው፣ በመምህሩ፣ በሀኪሙ፣ በቢሮ ሠራተኞች፣ በነጋዴው፣ በሙዚቀኛው፣ በፀጉር አስተካካዩ፣ በቤት ሠራተኛው፣ በሾፌሩ፣ በዘበኛው በጫማ አሳማሪው በዳንስ አስተማሪው በጭፈራ ቤት ሥርዓት አስከባሪው ወዘተ ተመርቶ በሸቀጥ መልክ ለገበያ የቀረበ ወይም ለገበያ እንደቀረበ ተቆጥሮ ዋጋው የተተመነ ቁሳዊ ዕቃና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ነው፡፡ ጥቅል የአገር ውስጥ ምርት በገንዘብ ዋጋ በሁለት መልክ ይለካል፡፡ አንዱ ምርቱ በተመረተበት ዓመት የገበያ ዋጋ መለካት ሲሆን ሁለተኛው የዋጋ ንረትን በምርቱ ልኬት ውስጥ ላለማስገባት በአንድ በተመረጠ ዓመት ቋሚ ዋጋ አማካኝነት የተከታታይ
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኮከቡ ያልሰመረው ‹ትሪልዮን› አገራዊ ምርት

ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) ብዙ ሰው መንግሥት ስለ ኢኮኖሚው ዕድገት የሚያቀርበው መረጃ እውነት ነውን? ለምንስ ሁልጊዜ በዐሥራ አንድ በመቶ ያድጋል? የሚል ጥያቄ በጭንቅላቱ ውስጥ ይመላለሳል፡፡ ዐሥራ ሦስት ዓመታት ድርቅ ሲኖርም ሳይኖርም፣ የውጭ ምንዛሪ እየተሟጠጠም፣ ሥራ አጥነት እየበረከተም፣ ኢኮኖሚው በዐሥራ አንድ በመቶ አደገ ይባላል፡፡ ይኽ የሕዝብ እንቆቅልሽ መፈታት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ ራስ ለራስ ምስክር መሆን አይከብድም፡፡ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ የዓለምን አምስት እጥፍ የአፍሪካን ሁለት እጥፍ በሆነ የዕድገት መጣኝ በየዓመቱ እያሳደግን ለዐሥራ ሦስት ዓመታት ያህል ዘልቀናል፤ ከሚሉት የራስ ለራስ ምስክርነት የኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ መረጃዎች ተነስተን፣ ከገበያው ሁኔታ ጋር አነጻጽረን የተደበቀውን እውነት ከተሸፈነበት መጠቅለያ በመግፈፍ እርቃኑን እናያለን፡፡ ዓይን ራሱ በቀጥታ አይቶ ስለሚለካና ስለሚገምት እንደ ጆሮ ከሌላ ሰው በሰማው አይታለልም፡፡ ራሱ ባዘጋጀው ስታቲስቲክስ ከራሱ ከመንግሥት ባለሟል አፍና በሁለት ቀን ቆይታው የተነገረውን መልሶ ከሚነግር የውጭ እንግዳ የኢትዮጵያ ሕዝብ አልታለልም ካለ ቆይቷል፡፡ ቀባጣሪዎች ብዙ ቀባጥረው ስለ ኢኮኖሚው የተባለው ሁሉ ውሸት ሆኖ ራሳቸውን ሊቆጫቸውም አየጀመረ ነው፡፡ የመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ኢኮኖሚው ከ2003 እስከ 2007 ለአምስት ዓመታት በየዓመቱ በአማካይ በ10.1 በመቶ አድጓል ተባለ፡፡ ዓመታዊ አማካይ የነፍስ-ወከፍ ገቢ በ2002 ከነበረበት 377 የአሜሪካን ዶላር በ2007 መጨረሻ ወደ 691 የአሜሪካን ዶላር አድጓል፤ በ2017 ዓ.ም. መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ የማሰለፍ አገራዊ ራዕይ ተይዟል ተባለ፡፡ እነ ጂቡቲ፣ እነ የመንና እነ አፍጋኒስታን ኢትዮጵያን ቀድመው መካከለኛ ገቢ ውስጥ ይገባሉ ስለተባለ መካከለኛ የከፍተኛና የዝቅተኛ መሃል
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

እንደኛ የሚቆጥብ ማን አለ? (ጌታቸው አስፋው)

ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) ቁጠባ የዕድገት መሠረት ነው፡፡ ለነገው ሳይቆጥብ ዛሬ ያመረተውን ዛሬ ተጠቅሞ የሚጨርስ ሰው አያድግም፡፡ ቁጠባ ወደ መዋዕለንዋይነት ሲቀየርና የማምረቻ መሣሪያ ሲሆን የኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት ይሆናል፡፡ የመዋዕለንዋይ የጀርባ አጥንት ቁጠባ ነው፡፡ በብሔራዊ ኢኮኖሚ ትርጉም፣ ቁጠባ ማለት በዚህ ዓመት ከተመረተው ውስጥ ለዚህ ዓመት ፍጆታ ወጥቶ የተረፈውና ወደሚቀጥለው ዓመት የተሸጋገረው ማለት ነው፡፡ በዚህ የብሔራዊ ኢኮኖሚ ትርጉሙ ኢትዮጵያውያን እንደ ማንኛውም ታዳጊ አገር ራሳችን ከምናመርተው ውስጥ ለቁጠባና መዋዕለንዋይ የሚተርፈው በጣም ጥቂቱ ብቻ ነው፡፡ በግለሰብና በቤተሰብ ደረጃ ግን ብዙሀኑ ሕዝብ በመቆጠብ የሚያህለንም የለም ልንል አንችላለን፡፡ ምንም እንኳ ኑሯችን ከእጅ ወደ አፍ ቢሆንም ነገ ስለሚያስፈራን እንደ እኛ የሚቆጥብ የለም፡፡ ግማሹ በጥሬ ገንዘብ መልክ ይቆጥባል፤ ግማሹ በዕቃ መልክ ይቆጥባል፤ ግማሹ በቤት እንስሳት መልክ ይቆጥባል፡፡ ገበሬው ጎተራው ለከርሞ እንዳጎድልበት አንጀቱን አስሮ ይራባል፤ ያለመጫሚያ ይሄዳል፤ የተቀደደ ይለብሳል፤ ይህ ሁሉ ለቁጠባ ሲል የሚያደርገው ነው፡፡ ሁሌም ስለማትገኝ ዓመት በዓል በመጣ ቁጥር አምረን ለመታየት ቆጥበን ሳጥን ውስጥ ለብዙ ዓመታት የምናስቀምጣትን እጀ ጠባብ ሱሪና ኮት ወይም ባለ ጥበብ ቀሚስ የክት ልብስ እንላታለን፤ ስሟን አሳምረን፡፡ እሷም ቁጠባ ነች፡፡ እንደኛ ለዓመት በዓል ብሎ ከዓመት ዓመት ልብስ በሳጥን ውስጥ ቆጥቦ የሚያስቀምጥ ይኖር ይሆን? ጌጣ ጌጥም እንደ ቁጠባ አድርገን እንይዛለን፤ ለክፉ ቀን ሽጠን ለመጠቀም፡፡ ዶሮ ወይም በግ ወይም ወይፈን ወይም ጊደርም ስጋ እያማረንም ቢሆን ለዓመት በዓል ብለን ቆጥበን እናስቀምጣለን፡፡ እንደኛ ለሆዱ የዓመት ቀጠሮ
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የሊብራል ገበያ ኢኮኖሚ ጽንሰ ሐሳብ ( ጌታቸው አስፋው )

የሊብራል ገበያ ኢኮኖሚ ጽንሰ ሐሳብ ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) ዴዶ (ሼኪ) ከጂማ ከተማ ሃያ ኪሎ ሜትር የምትርቅ ከተማ ናት፡፡ የዴዶ ከተማና የአካባቢዋ ቀበሌዎች ኗሪዎች የሚገበያዩት በሳምንት አንድ ቀን ቅዳሜ በሚውል ገበያ ነው፡፡ ቅዳሜ ገበያተኛው ከጧት ጀምሮ ወደ ገበያው ቦታ የተማል፡፡ ሦስት አራትና አምስት ሰዓት ላይ ገበያ ለመሄድ የቸኮሉ ወላጆችና ጎረቤቶች የመንደሩን ልጆች የገበያውን መሞቅ አለመሞቅ አማትራችሁ አይታችሁ ንገሩን ይላሉ፡፡ ስድስት ሰባት ስምንትና ዘጠኝ ሰዓት ደርሶ ገበያው ሳይሞቅ፤ ሳይደራ ወይም ፈረንጆቹ እንደሚሉት ገበያው ሳይጠራ በፊት የገበያው መረጃ አነስተኛ ስለሚሆን ወይ ሻጩ ከገበያ በላይ በሆነ ዋጋ ሽጦ ሸማቹን ያሞኘዋል ወይ ሸማቹ ከገበያ በታች በሆነ ዋጋ ገዝቶ ሻጩን ያሞኘዋል፡፡ ከስድስት እስከ ዘጠኝ ባሉት ሰዓታት ግን ገበያው ይሞቃል ወይም ይደራል ወይም እንደፈረንጆቹ አጠራር ይጠራል፡፡ አቅርቦትና ፍላጎትን እኩል የሚያደርጋቸው የገበያ ማጣሪያ ወይም የተመረተውን ለገበያ የቀረበው የሚሸጥበት የገበያ ዋጋ ይፈጠራል፡፡ ሊመሽ ተቀርቦ ገበያው መነሳት ከጀመረበት ከዘጠኝ ሰዓት ጀምሮም የጠዋቱ የገበያ አለመጥራት ሁኔታ ይደገማል፡፡ አብዛኛው ሸማችም ሻጭም ወደ ቤቱ በመሄድ ላይ ስለሚሆን ገበያው እንደገና ይቀዘቅዛል፡፡ ይህን የገበያ ባሕርይ አጥንቶና አቃላይ መርህ አድርጎ ነው፣ አዳም ስሚዝ የነጻ ገበያ ኢኮኖሚን ወይም የሊብራል ገበያ ኢኮኖሚን የተነተነው፡፡ አዳም ስሚዝ ከኹለት መቶ ሐምሳ ዓመት በፊት ተመራምሮ የጻፈውን ነው እኛ ዛሬ አንብበን መረዳት ያቃተን፡፡ ልብ-ወለድ ታሪክ ከአንበብን የሚበቃን፣ ሁሉን የምናውቅ ይመስለናል፡፡ መሬት ሽጠንም ቢሆን ቢራ መጠጫና ቪትዝ መኪና መግዣ ካገኘን ሌላ
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የገበያ ኢኮኖሚ ዓይነት ጽንሰ ሐሳቦችን ማምታታት (ጌታቸው አስፋው)

ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) ለመሆኑ የገበያ ኢኮኖሚ ምንድን ነው ስንት ዓይነት የገበያ ኢኮኖሚዎችስ አሉ፡፡ መንግሥት ጧት ማታ ኒዮ-ሊብራሊዝም እያለ የገበያ ኢኮኖሚን እያጥላላ መግለጫ ስለሚሰጥ ብዙ ሰው አንድ ዓይነት ብቻ የገበያ ኢኮኖሚ እንዳለና እርሱም ኒዮ-ሊብራሊዝም እንደሆነ ነው የሚገምተው፡፡ የልማት ኢኮኖሚ ነው ከሚለው ራሱ ከሚተዳደርበት የኢኮኖሚ መርህ ጋር የሚያነጻጽረውም የጭራቅ ያህል ስም የሰጠውን የኒዮ-ሊብራሊዝም የገበያ ኢኮኖሚን ነው፡፡ ኢኮኖሚስቶች የሚያውቁት ግን ኹለት ዓይነት የገበያ ኢኮኖሚዎች እንዳሉና ከእነዚህ የገበያ ኢኮኖሚ ዓይነቶች አንዱ በአዳም ስሚዝ የተተነተነው የገበያ ኢኮኖሚ ጽንሰ ሐሳብ፣ ከዐሥራ ስምንተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ ኹለተኛው የዓለም ጦርነት በምዕራብ አውሮፓና በአሜሪካ ይተገበር የነበረ፣ የሊብራል ነጻ ገበያ ኢኮኖሚ የገበያ ኢኮኖሚ የመጀመሪያ ምዕራፍ ነው፡፡ ኹለተኛው በኢኮኖሚስት ጆን ሜናርድ ኬንስ የተተነተነው፣ የግሉን ኢኮኖሚ በብሔራዊ ኢኮኖሚ ፖሊሲና በመንግሥት ቁጥጥር መምራት የሚለው ጽንሰ ሐሳብ፣ በሃያኛው ክፍለ ዘመን ከኹለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተጀመረው የገበያ ኢኮኖሚ ኹለተኛ ምዕራፍ ነው፡፡ የሊብራል ነጻ ገበያ ኢኮኖሚ ገበያዎች በራሳቸው የፍላጎትና የአቅርቦት መስተጋብር ሕግጋቶች የገበያ ማጣሪያ ወይም የተመረተው ሁሉ የሚሸጥበት የተረጋጋ የሸቀጦች ዋጋ ፈጥረው የሚስተካከሉ ስለሆነ የመንግሥትን በፖሊሲም ሆነ በቁጥጥር ማስተካከያ ጣልቃ ገብነት አይሹም የሚል ነው፡፡ በኢትዮጵያ ገበያዎች ውስጥ በዓመት በዓል ወቅቶች ሽንኩርት ዶሮና በግ ቅቤ የመሳሰሉ የስጋና የወተት ዘሮች ዋጋዎች ሲወዥቁ እናያለን፡፡ ይህ የሚያመለክተው ገበያው ራሱን በራሱ ሊያስተካክል የገበያ ማጣሪያ የሸቀጥ ዋጋ ሊፈጥር አለመቻሉን ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ፍላጎት ከአቅርቦት መብለጡ ነው፡፡ ከዓመት በዓል
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የስታቲስቲክሱና የገበያው መለያየት እንቆቅልሽ – ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ)

ጌታቸው አስፋው / Black Lion (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) Related image በገበያ የቀረበው የገንዘብ መጠን በገበያ ዋጋ ካልተለካው ምርት ጋር ሊመጣጠን ባለመቻሉ በዋጋ ግሽበት የሰደድ እሳት ተቃጠልን፣ በሸቀጥ ዋጋ ጭቅጭቅና ንትርክ ውስጥ ገባን፣ ዋጋዎች በቀናትና በሳምንታት ተለዋወጡብን፡፡ ገቢ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ቢሆንም የገቢ ዕድገት ከምርታማነት ዕድገት በላይ ስለሆነ ገንዘቡ ዋጋ አጣ፡፡ ግልጽ ሥራ አጥነት በስውር ሥራ አጥነት ተተክቶ ምርታማነትን ቀነሰ፡፡ በጥቃቅን የተደራጁት ወጣቶች በሙሉ አቅማቸው ሳይሰሩ በነርሱ ላይ ሌሎች ማደራጀት የቀድሞዎቹንም አዲሶቹንም በሙሉ አቅማቸው ሠርተው ምርታማ እንዳይሆኑ አደረጋቸው፡፡ ሥራ ፈጠራ በብሎኬት ምርት፣ መስኮትና በር መግጠም፣ አልባሳት፣ ቦርሳና ቀበቶን የመሳሰሉ የግል መጠቀሚያዎችን ማምረት ጀምሮ አሁን ወደ ጀበና ቡና፣ ቦርዴ (ሻሜታ) ጠመቃ፣ የዐረብ ሱቅ፣ በቆርቆሮ ግድግዳ ደሳሳ ጎጆ የሆቴል ኪዎስክ ወርዷል ከዚህ በታች ወዴት እንደሚወርድ አይታወቅም፡፡ በየመንገድ ዳሩ ጠላ ጠምቆ መሸጥ ይሆናል፡፡ አምርቶ ገንዘብ ማግኘት ካልተቻለ አጭበርብሮም ቀምቶም ሰርቆም የሰው አካልን ደልሎም ገንዘብ ለማግኘት ይሞከራል፡፡ በውድድር ሳይሆን በሽሚያ ገንዘብ ለማግኘት ለመክበር መስገብገብ መሻማት መሻሻጥ መታወቂያችን ሆኗል፡፡ በሦስት ሺሕ ብር ሥራ ጀምሮ በዓመቱ ሦስት ሚልዮን ብር ካፒታል ማስመዝገብ፣ መቶ ሺሕ ብር ለደላላ ከፍሎ ወደሞት ለመሄድ መደራደር፣ ለደቂቃዎች መዝናኛ በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ማውጣት፣ ቅጥ ላጣ የውጭ አገር ጉዞ የቅንጦት ወጪ ማድረግ፣ ጥሬ ገንዘብ ከጓሮ የሚሸመጠጥ ቅጠል አስመስሏል፡፡ በየቴሌቪዥኑ መዝናኛ ፕሮግራም አቅራቢዎች ለእንግዶቻቸው የሃያ ሺሕ ብር ሐምሳ ሺሕ ብር የቀን ውሎ ጉርሻ ሲሰጡ ታይቷል፡፡ በ1960ዎቹ ቦሌ አስፋልት
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ጥሬ ገንዘብ አሠራር ፤ አቶ ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ)

ጥሬ ገንዘብ አሠራር *** አቶ ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) *** በሳለፍነው ሩብ ምዕተ ዓመት እንደ የዋጋ ንረት የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲያሰቃይ የኖረ ነገር የለም፡፡ የዋጋ ንረት ብዙ አቅመ ደካሞችን አስለቅሷል ብዙ ወጣቶችን አገር አስለቅቆ አስኮብልሏል፡፡ ብዙዎች የዋጋ ንረት የነጋዴ ስግብግብነት ይመስላቸዋል፡፡ የዋጋ ንረት የነጋዴ ስግብግብነት ብቻ ከሆነ ሁላችንም ስግብግብ ነን ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ሁላችንም ያለንን ነገር ሽጠን የምንፈልገውን ሸቀጥ የምንገዛበትን ጥሬ ገንዘብ የምናገኝ ነጋዴዎች ነን፡፡ ራሳችንን ስግብግብ ከማድረጋችን በፊት የዋጋ ንረት ትክክለኛ ምክንያት ምን እንደሆነ ማወቅ ይጠቅማል፡፡ በእርግጥ ማንኛውም ነጋዴ በጥሬ ዕቃ ዋጋ ጭማሪ፣ በመንግሥት ግብር ጭማሪ፣ በደሞዝ ጭማሪና በሌሎች ምክንያቶች የጨመረበትን የማምረቻ ወጪ ወደ ሸማቹ ያስተላልፋል፡፡ የቀን ሙያተኞች ዋጋ ሲዋዋሉ ለድርድር የሚያቀርቡት በሆቴል ቤት የምግብ ዋጋ መጨመሩን ነው፡፡ የሌሎች ሸቀጦችን ዋጋ ጭማሪ መነሻ በማድረግ በመሸጫ ሸቀጥ ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ ምክንያቶች ሁለተኛ ደረጃ ምክንያቶች ናቸው፣ ዋናውና አንደኛ ደረጃ የዋጋ ንረት ምክንያት በገበያው ውስጥ የጥሬ ገንዘብ አቅርቦት መጠን መብዛት ነው፡፡ የዋጋ ንረት ማለት በእያንዳንዱ ሰው ኪስ ውስጥ ብዙ ጥሬ ገንዘብ ማስቀመጥ ማለት ነው፣ የጥሬገንዘቡ የመግዛት አቅም መቀነስ ማለት ነው፡፡ ብዙ ብሮች ጥቂት ሸቀጦችን ያስድዳሉ ማለት ነው፡፡ ይኽ ነው ዋናውና የመጀመሪያው የዋጋ ንረት ምክንያት፡፡ ሌሎቹ ሁሉ ኹለተኛና ሶስተኛ ምክንያቶች ወይም ውጤቶች ናቸው፡፡ ጥሬ ገንዘብን የሚያሰራጩት እንማን ናቸው ለምንስ ነው ኑሮን በሚያንር ደረጃ ብዙ ጥሬገንዘብ የሚያሰራጩት፣ ብዙ ጥሬገንዘብ አሰራጭተው ኑሮን እንዳያስወድዱ
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሁሉንም ሰዎች ሁሌም ማታለል አይቻልም – ( ጌታቸው አስፋው)

ሁሉንም ሰዎች ሁሌም ማታለል አይቻልም ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) ብዙ ሰው መንግሥት ስለ ኢኮኖሚው ዕድገት የሚያቀርበው መረጃ እውነት ነውን? ለምንስ ሁልጊዜ በዐሥራ አንድ በመቶ ያድጋል? የሚል ጥያቄ በጭንቅላቱ ውስጥ ይመላለሳል፡፡ ዐሥራ ሦስት ዓመታት ድርቅ ሲኖርም ሳይኖርም፣ የውጭ ምንዛሪ እየተሟጠጠም፣ ሥራ አጥነት እየበረከተም፣ ኢኮኖሚው በዐሥራ አንድ በመቶ አደገ ይባላል፡፡ ይኽ የሕዝብ እንቆቅልሽ መፈታት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ ራስ ለራስ ምስክር መሆን አይከብድም፡፡ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ የዓለምን አምስት እጥፍ የአፍሪካን ሁለት እጥፍ በሆነ የዕድገት መጣኝ በየዓመቱ እያሳደግን ለዐሥራ ሦስት ዓመታት ያህል ዘልቀናል፤ ከሚሉት የራስ ለራስ ምስክርነት የኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ መረጃዎች ተነስተን፣ ከገበያው ሁኔታ ጋር አነጻጽረን የተደበቀውን እውነት ከተሸፈነበት መጠቅለያ በመግፈፍ እርቃኑን እናያለን፡፡ ዓይን ራሱ በቀጥታ አይቶ ስለሚለካና ስለሚገምት እንደ ጆሮ ከሌላ ሰው በሰማው አይታለልም፡፡ ራሱ ባዘጋጀው ስታቲስቲክስ ከራሱ ከመንግሥት ባለሟል አፍና በሁለት ቀን ቆይታው የተነገረውን መልሶ ከሚነግር የውጭ እንግዳ የኢትዮጵያ ሕዝብ አልታለልም ካለ ቆይቷል፡፡ ቀባጣሪዎች ብዙ ቀባጥረው ስለ ኢኮኖሚው የተባለው ሁሉ ውሸት ሆኖ ራሳቸውን ሊቆጫቸውም አየጀመረ ነው፡፡ የመጀመሪያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ኢኮኖሚው ከ2003 እስከ 2007 ለአምስት ዓመታት በየዓመቱ በአማካይ በ10.1 በመቶ አድጓል ተባለ፡፡ ዓመታዊ አማካይ የነፍስ-ወከፍ ገቢ በ2002 ከነበረበት 377 የአሜሪካን ዶላር በ2007 መጨረሻ ወደ 691 የአሜሪካን ዶላር አድጓል፤ በ2017 ዓ.ም. መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ የማሰለፍ አገራዊ ራዕይ ተይዟል ተባለ፡፡ እነ ጂቡቲ፣ እነ የመንና እነ አፍጋኒስታን ኢትዮጵያን ቀድመው መካከለኛ ገቢ ውስጥ ይገባሉ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ልማት እና የኢኮኖሚ ልማት (አቶ ጌታቸው አስፋው)

ልማት እና የኢኮኖሚ ልማት አቶ ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) እንዲህ ነው፡፡ ልማትንና የኢኮኖሚ ልማትን በሚመለከት የኢኮኖሚ ባለሙያዎችና ፖለቲከኞች የሚያወሩት በጣም ይራራቃል፡፡ በልማት ጠበብት ትምህርት፣ ልማት የሰው ልጅ ሁለንተናዊ ለውጥ ሲሆን ፖለቲከኞቹ ግን ልማት ብለው የሚያወሩት ስለ ኢኮኖሚ ልማት ብቻ ነበር፡፡ ኢሕአዴጎች በፖለቲካውና በማኅበራዊ አገልግሎቱ አንዳንድ ድክመቶች ቢታዩብንም በልማቱ ግን ማንም የማይክደው የተዋጣለት ስኬት አስመዝግበናል እየተባለ ነው፡፡ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ይኽንን አምነው ተቀብለዋል፡፡ የልማት ጠበብት ይኽንን ጠባብ የኢሕአዴግ ኢኮኖሚ ልማት እንደ ሁለንተናዊ የልማት ስኬት አድርገው አይቀበሉም፡፡ ምክንያቱም ልማት በሁለንተናዊ ትርጉሙ ፖለቲካዊም፣ ኢኮኖሚያዊም፣ ማኅበራዊም፣ መንፈሳዊም ጉዳይ ነውና ነው፡፡ ገና ከአውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር 1950ዎቹና 1960ዎቹ ጀምሮ ሲሞን ኩዝኔትስ፣ ጉናር ሚርዳል፣ አርተር ሌዊ፣ ሮስቶ፣ ቼነሪ እና ሌሎችም የልማት ጠበብት ልማትንና የኢኮኖሚ ልማትን በሰፊው የሁለንታዊ ልማት ትርጉምና በጠባቡ የኢኮኖሚ ልማት ትርጉም ለያይተው ያስተምሩ ነበር፡፡ በሰፊው ሁለንተናዊ የልማት ትርጉም የሰው ልማት ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ ማኅበራዊ እና መንፈሳዊ ለውጥ ማለት ሲሆን ከአራትና አምስት መገለጫዎቹ አንዱ የለማ ሰው በአምሳሉ ለተፈጠረው ለሌላ ፍጡር ሰው ለመኖር ወይም ለእንጀራ ሲል አቀንቃኝና አጎብዳጅ ከመሆን ይልቅ በውስጡ በራስ መተማመን ይኖረዋል የሚል ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ የልማት ጠበብቶች አውራውና የኖቬል ተሸላሚው አማርተያ ሴንም ልማትን ሲተረጉሙ ሰው ሕጋዊ የሆነን ማንኛውም ነገር በራሱ ለመሥራት አቅምና ነፃነት ማግኘቱ ነው፡፡ የሁለቱም የቀድሞውና የዚህ ዘመን ትረጉምና አመለካከት ተመሳሳይ ሆኖ ልማት በግለሰብ ላይ የሚታይ በኑሮ ራስን በራስ የመቻል አቅምና ነፃነት
Tagged with: , ,
Posted in Ethiopian News

የኢኮኖሚ ፖሊሲና ስትራቴጂ ውጥንቅጥ ( አቶ ጌታቸው አስፋው)

የኢኮኖሚ ፖሊሲና ስትራቴጂ ውጥንቅጥ አቶ ጌታቸው አስፋው (የብሔራዊ ኢኮኖሚ ዕቅድ ባለሙያ) የልማት ኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ግቦችና ዓላማዎች እንደ የገበያ ኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ግቦችና ዓላማዎች በጽንሰ-ሐሳቦች ትንታኔና ጥናት ላይ ተመርኩዘው በባለሙያዎች ብቻ የሚነደፉ አይደሉም፡፡ በሐሳብና በአስተያየት ላይ ስለሚመሠረቱ የፖሊሲ መሣሪያዎቹ በተቻለ መጠን የብዙ ሰዎችን፣ በተለይም የተጠቃሚዎችን በቂ ተሳትፎ ይፈልጋሉ፤ አንድ ወጥም አይደሉም፡፡ ስለሆነም የልማት ኢኮኖሚ ፖሊሲ መሣሪያዎች በአብዛኛው የሐሳብ ማስፈጸሚያ የጉዞ ካርታ ከሆኑ ስትራቴጂዎች ጋር የሚመሳሰሉ ናቸው፡፡ የልማት ኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ግቦችና ዓላማዎች መሠረተልማትን መገንባት፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ማቅረብ፤ ድህነትን መቅረፍ፣ የሕዝቡን የኑሮ ደረጃ ማሻሻል፣ ገበያው ሊያቀርባቸው ያልቻሉ ምርቶችን በቀጥታ በመንግሥት ድርጅቶች ማምረት የመሳሰሉ ናቸው፡፡ የእነኚህ ግቦችና ዓላማዎች የፖሊሲ መሣሪያዎች ስትራቴጂዎች በዝርዝር የተዘጋጁ የአምስት ሦስትና ሁለት ዓመታት ብሔራዊ ዕቅዶች ይባላሉ፡፡ የልማት ቅንብሮቹ እንደየአገሩ ተጨባጭ ሁኔታ የሚለያዩ እንጂ ወጥ የሆነ ዓለም ዐቀፋዊ ጽንሰ-ሐሳብ የላቸውም፡፡ ፖሊሲ ዓላማን፣ የተፈጻሚነት ጊዜና ቦታን፣ አስፈጻሚው አካል ማን እንደሆነ ጠቅሶና ሥልጣን ባለው ከፍተኛ የአመራር አካል ተደንግጎ በኦፊሴላዊ ዶኩሜንት የሚወጣ ሕግ ሲሆን፣ ስትራቴጂ ግን የተመረጠ የልማት ግብ ላይ ለመድረስ በከፍተኛ ወይም በመካከለኛ ባለሥልጣን ውሳኔ፣ የሰውና የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም የሚደለደልበት የጉዞ ካርታ ወይም ዕቅድ ነው፡፡ ስትራቴጂዎች እንደ ፖሊሲዎች በበላይ አካል ተነድፈው እንዲተገበሩ ለበታች አካላት እንደ ሕግ የሚሰጡ ትዕዛዞች ሳይሆኑ የፈጻሚው የቅርብ አለቃና ፈጻሚው ከብዙ አማራጮች ውስጥ ሥራችንን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን ይረዱናል ብለው የሚመርጧቸው ከሌሎች አማራጮች የሚሻሉ ናቸው የሚሏቸው መንገዶች ናቸው፡፡ አማራጮቹን መርጠው ለማስጸደቅ
Tagged with: ,
Posted in Ethiopian News