በፓትርያርኩ የደኅንነት ስጋት ጥያቄ መንግሥት የመንበረ ፓትርያርኩን ጥበቃ ያጠናክራል፤ “ዋናው መፍትሔ ለውጡን ማፋጠን ነው”/ጠ/ሚኒስትሩ/

  መዋቅርን ባልጠበቁ አቤቱታዎችና በዘገባዎች ማጨናነቅን በስጋቱ ምንጭነት ጠቅሰዋል፤ ስጋታቸውን ለጠ/ሚኒስትሩ ማቅረባቸውን ተከትሎ፣ፌዴራል ፖሊስ የጥበቃ ኀይል መደበ፤ በሰልፍ የተደገፉ አቤቱታዎች ተገቢነትና የውስጥ ጥበቃ ሥርዐቱ እንደሚፈተሽ ተጠቆመ፤ ዋናው መፍትሔ፣ ለውጥን ማፋጠንና ፈጥኖ መላሽነት እንደኾነ ጠ/ሚኒስትሩ መከሯቸው፤ ለውጥን እንደማይቃወሙና ለመሪ ዕቅዱ ተፈጻሚነት እንደሚሠሩ ለጠ/ሚሩ አረጋግጠዋል፤ “የስጋታቸው ተጨባጭነቱ ባይታየንም ለጥበቃው መተባበር ይቻላል፤ ለለውጡና ፍትሕ ዐጣሁ ለሚለው ሕዝብ እርሳቸውም …