የቅማንት ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት 16 አሽከርካሪዎችን ገደሉ

በአማራ ክልል ከጎንደር መተማ መንገድ ላይ “መቃ” በተባለች ሥፍራ የቅማንት ታጣቂዎች ሰኞ’ለት በፈጸሙት ጥቃት 16 አሽከርካሪዎች ተገድለው በርካቶች መቁሰላቸውን ታውቋል። በቅማንት ታጣቂዎች ከተገደሉት ሾፌሮች በተጨማሪ ተሳፋሪዎችና በርካታ አሽከርካሪዎች ታፍነው መወሰዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል። አብዛኞቹ አሽከርካሪዎች የተገደሉት፣ ከጥቃቱ ለማምለጥ ጥረት በማድረግ ላይ ሳሉ በእሩምታ ተኩስ እንደኾነ ተነግሯል። የፋኖ ታጣቂዎች  በመተማ ወረዳ ከቅማንት ብሄረሰብ ታጣቂዎች ዘረፋ ለማስቆም  የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ምንጮች ተናግረዋል። የቅማንት ታጣቂዎች በአብይ አሕመድ ድጋፍ እየተደረገላቸው በዘረፋ እና እገታ ላይ መሰማራታቸው የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።