ፓትርያርኩ አላግባብ ያሳለፉትን ወቅቱን ያላገናዘበ ለውጥ አደናቃፊ እገዳ እንዲያነሡ ዋና ሥራ አስኪያጁ አሳሰቡ

ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ “የቤተ ክርስቲያን ሀብት ያለ ሥነ ሥርዓት ለከፍተኛ ብክነት እንዳይዳረግ ጥብቅ ቁጥጥር  ማድረግ” በሚል ከትላንት በስቲያ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ላይ ያሳለፉትን እገዳ፣ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ዛሬ ዓርብ፣ መጋቢት 13 ቀን በሰጠው ማብራሪያና ምላሽ ተቃውሞታል፡፡ ዋና ዋና ነጥቦች፡- የሱባኤውንና የአገርን ወቅታዊ ኹኔታ ያላገናዘበና ከርእሰ አበው የማይጠበቅ እገዳ ነው፤ ለሕዝብ ሰላምና አንድነት የምንጸልይበት …