ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ሠራተኞች የለውጥ ማነቃቂያ ሥልጠና ተሰጠ፤ “በመሪ ዕቅድ ለታገዘው ኹለንተናዊ ለውጥ ማዳረሻ ይኾናል፤”/ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ/

የኹሉም መምሪያዎች እና ድርጅቶች ዋና እና ምክትል ሓላፊዎች እንዲሁም መላው ሠራተኞች የተሳተፉበት መኾኑ ልዩ ያደርገዋል፤ “ሓላፊዎችና ሠራተኞች፥ ከውሸት፣ አሉባልታና መወነጃጀል ተጠብቀው ራሳቸውን በትምህርትና ሥልጠና ሊያሻሽሉ ይገባል፤” “ያዳከሙንንና ያስነቀፉንን ድክመቶች ለይተን የለውጡን መሰናክሎች ለማስወገድና ሒደቱን ለመለካት የሚያስችል ፍኖተ ካርታ ያስፈልገናል፤” “ከፖሊቲካ ራቅን እያልን ቤተ ክርስቲያንን ከተጽዕኖ ፈጣሪነትና ተጠቃሚነት ወደ ኋላ ያስቀረንበትን አካሔድ በማረም መሪነትንና ቀድሞ መገኘትን …