በሱዳንና በደቡብ ሱዳን ሀገራት የይገባኛል ጥያቄ በሚቀርብባት በአብዬ ግዛት በተፈጸመ ጥቃት፣ 32 ሰዎች እንደተገደሉ፣ የግዛቲቱ መንግሥት ተወካይ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የምትገኘውና በነዳጅ የበለጸገችው ግዛት መንግሥት ተወካይ፣ ትላንት እሑድ የተፈጸመውን ጥቃት አውግዘዋል። ጥቃቱን የፈጸሙት፣ የደቡብ ሱዳንን ሠራዊት መለዮ የለበሱ ሚሊሺያዎች ናቸው፤ ተብሏል።
ከጥቃቱ ሰለባዎች ው…