ትግራይ የረድዔት ተደራሽነት እየተሻሻለ ቢሆንም እንቅስቃሴው አሁንም የተገደበ ነው – የተባበሩት መንግሥታት

ትግራይ ውስጥ እንደ አውሮፓውያን የቀን አቆጣጠር ካለፈው ሰኔ ወር ወዲህ የረድዔት ተደራሽነት እየተሻሻለ ቢሆንም የሰብዓዊ ረድዔት አጋሮቻችን እንደሚነግሩን ወደ ክልሉ የመግባት እና የመውጣት እንቅስቃሴው አሁንም የተገደበ ነው” ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምክትል ቃል አቀባይ ገለጹ። ይህ መሆኑ ደግሞ የዕርዳታ አቅርቦቶች ለማስገባት እና የርዳታ ሥራው እንዲቀጥል ሠራተኞች ለማንቀሳቀስ አዳጋች ያደርግባቸዋል ብለዋል።

በሌላ በኩል ከአሁን ቀደም ለመድረስ አስቸጋሪ ወደነበሩት አካባቢዎች በአሁን ወቅት መድረስ መቻሉን የመንግስታቱ ድርጅት ምክትል ቃል አቀባዩ ፋርሃን ሃክ ተናግረዋል። ርዳታ ከሚያስፈልጋቸው 5.2 ሚሊዮን ሰዎች መካከል 4 ሚሊዮኑ (ማለትም ሰባ አምስት ከመቶው) ያሉባቸው አካባቢዎች ባሁኑ ወቅት የሰብዓዊ ረድዔት እንቅስቃሴ መድረስ የሚቻል መሆኑን የጠቀሱት ቃል አቀባዩ ባለፈው ግንቦት ወር ግን ለመድረስ የሚቻለው ሰላሳ ከመቶውን ብቻ ነበር ብለዋል።

አክለውም የመንግሥታቱ ድርጅት ቃል አቀባይ ፋርሃን ሃክ በመኪና ርዳት ማጓጓዝ የሚቻለው በክልል እና በፌዴራል መንግሥት ከባድ ቁጥጥር በሚድረግበት በአፋር ክልል በኩል ብቻ በመሆኑ ክልሉ ውስጥ ያለው የርዳታ አቅርቦት በፍጥነት እያለቀ ነው ብለዋል። ከሁለት ሳምን ከሚበልጥ ጊዜ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዘ ባለፈው ሳምንት የርዳታ አቅርቦቶች የጫኑ ሃምሳ አራት መኪናዎች መቀሌ እንደደረሱ ያስታወሱት ፋርሃን ሃክ፤ ያ በቂ ስላልሆነ በየቀኑ ከዚያ በላይ ርዳታ የያዙ ተሽከርካሪዎች መድረስ ይኖርባቸዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ፈቃድ ከሰጠ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ረድዔት በረራ አገልግሎት ባለፈው ቅዳሜ ወደትግራይ የተሳካ የሙከራ በረራ ማደረጉን ገልጸው መደበኛ በረራዎች ከነገ ጀምሮ እንደሚቀጥል ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።

አያያዘውም “በክልሉ ያለው የሰብዓዊ ሁኔታ እንዳይባባስ መሰረታዊ አገልግሎቶች፤ የኤሌትሪክ፣ የመገናኛ የባንክ አገልግሎቶች እንዲሁም መደበኛ በረራዎች እንዲቀጠሉ ጥሪ ማሰማታችንን እናቀጥላለን፥ አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍም ያስፈልጋል” ብለዋል። “እስከዚህ የአውሮፓ 2021 ዓ.ም ማብቂያ ባለው ጊዜ ለትግራይ ሰብዓዊ ረድኤት ከሚያስፈልገው አጠቃላይ ወጪ ከግማሽ በላዩን የሚይዘው ከ430 ሚሊዮን ዶላር በላይ ድጋፍ እንዲሰጠን አሁንም መጠየቃችንን እንቀጥላለን” ብለዋል።

(መረጃው ከመንግሥታቱ ድርጅት ምክትል ቃል አቀባይ የዛሬ ዕለታዊ መደበኛ ገለጻ የተገኘ ነው)

ETHIOPIA 
In Ethiopia, the Office for the Coordination of Humanitarian Affairs says that, despite recent improvements in access within Tigray since the end of June, movements in and out of the region remain restricted. This affects the ability of aid workers to replenish supplies and mobilize personnel to sustain aid operations.

Inside Tigray, access is currently possible to areas that were previously hard-to-reach.
An estimated 75 per cent of people who need assistance – this is 4 million out of 5.2 million people in need – are now in zones where humanitarian operations can take place, compared to 30 per cent in May.

Humanitarian supplies, however, are rapidly being depleted inside Tigray, with road access only possible through Afar Region with heavy control by regional and federal authorities.
Last week, a 54-truck humanitarian convoy carrying food, fuel, medical supplies and other vital items arrived in Mekelle, the first to reach the region in more than two weeks. However, the supplies are far from adequate to sustain humanitarian assistance. Many more trucks should be arriving every day to meet the needs of people who need help.

Following approval from the Government of Ethiopia, the UN Humanitarian Air Service successfully conducted a test flight Saturday to Tigray. Regular flights are scheduled to resume on July 21st.
In the meantime, the U.N. continues to call for the restoration of basic services, electricity, communications, commercial flights and banking system to prevent further deterioration in the humanitarian situation.
Funding is also urgently needed. More than $430 million – half of the total requirement- is still required for the humanitarian response in Tigray until the end of the year.

https://www.un.org/