የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።

–
ከሰሞኑም በጅምላ በግፍ የተገደሉ ወገኖቻችን እሬሳ በጅምላ በግሬደር እየተጋዘ ጉድጓድ ውስጥ መጣሉና መቀበሩ የበለጠ ግፉን አግዝፎታል። በባህላችን እሬሳ ክብር አለው። ለዚህም አጸያፊ ድርጊት ትእዛዝ የሰጡና ያስፈጸሙ ባለስልጣናት ተጠያቂ መሆን ይገባቸዋል። ይሁንና ይሄንን ግፍ ለፖለቲካ ትርፍ ሲባል ብቻ መነጻጸር ከማይገባው ጉዳይ ጋር ማነጻጸር ልዩነትንና ቅራኔን በህዝቦች መካከል የበለጠ ከማስፋት የዘለለ ፋይዳ የለውም።
–

–
የቤንሻንጉሉ ግፍና ጣልያን የተፈጸመው ወንጀል ሁለቱም እኩይ የሆኑ የጭካኔ ድርጊቶች ሲሆኑ የራሳቸው ታሪክና ትርክት ያላቸው ክስተቶች ናቸው። አንዱ ከሌላው ጋር ምንም አይነት ዝምድናና ግንኙነት የለውም።
–
የግፍ ሰለባ የሆኑ ሁሉ ፍትህ እንዲያገኙ በጋራ መስራትና ድምጽ ማሰማት ቅራኔን ለማስፋትና የፖለቲካ ትርፍ ከማነፍነፍ የተሻለ ሰብአዊነትን ይገልጻል። ቅራኔን በትንሹም በትልቁም ለማስፋት እየተጉ ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሄ ማፈላለግ ፈጽሞ አይቻልም።
–
የአገራችን ፖለቲካ ገና ብዙ መጽዳት የሚገባው የዘር፣ የጭፍን ስሜት፣ የሴራና የአጥፍቶ መጥፋት እሳቤ ቅይጥ ቆሻሻ መሆኑን መዘንጋት አይገባም።
–
ለሁሉም ነፍስ ይማር። አበበ ገላው