ለመሪ ዕቅዱ ትግበራ ውጤታማነት አገልጋዮችና ምእመናን የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጥሪ አቀረበ፤ አድመኞችን አስጠነቀቀ!

በአዲሱና መጪው ትውልድ ውስጥ ኦርቶዶክሳዊ ማንነቷን ጠብቃ እንድትቀጥል ያደርጋታል፤ ለመሠረታዊ ሐዋርያዊ ተልእኮዋ ቅድሚያ በመስጠት በብቃት እንድታከናውነው ያስችላታል፤ ሀብቷን ከብክነትና ከምዝበራ በመጠበቅ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለመፈጸም ያበቃታል፤ የአገርንና የሕዝብን አንድነትና ሰላም ለምታጸናበት የእናትነት ሚናዋ ተደማጭነቷን ያጎላዋል፤ የካህናትንና የሊቃውንትን መብት ያስጠብቃል፤ከሥራ አያፈናቅልም፤ለእንግልት አይዳርግም፤ *** በጠቅላይ ጽ/ቤቱ የተቋቋመው የአመራርና ትግበራ ዐቢይ ኮሚቴ፣ የመተዳደርያ ቻርተሩን አጸደቀ፤ የትግበራ ፕሮጀክቱን አስተባባሪዎችና …