Blog Archives

ባድመ  (ቴዎድሮስ ኀይለ ማርያም (ዶ/ር))

ባድመ  (ቴዎድሮስ ኀይለ ማርያም (ዶ/ር)) የኢሕአዴግ ዱብዳ መግለጫ የወጣበት ግንቦት 28 ቀን 2010 ዓ.ም. አቶ መለስ ዜናዊ የዛሬ ሃያ ዓመት በግንቦት 28 ቀን 1990 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሠራዊት በወራሪው የኤርትራ ጦር ላይ እርምጃ እንዲወስድ ትዕዛዝ የሰጡባት ዕለት ናት፡፡ ሕወሓትም አጀንዳውን የቆሰቆሰው ልክ ያችን ታሪካዊ ቀን ቆጥሮ ይመስላል፡፡ ደርግን 17 ዓመት ታግዬ የጣልኩት 64 ሺሕ ወጣቶችን ገብሬ ነው እያለ 27 ዓመት ሲያደነቁረን የኖረው ወያኔ፣ የኢትዮ-ኤርትራ ተኩስ ማቆም ስምምነት እስከተፈረመበት ሰኔ 11 ቀን 1992 ባሉት ሁለት ዓመታት ብቻ ያለቀውን ከ70 ሺሕ በላይ የኢትዮጵያ ወጣት አስታውሶት አያውቅም፡፡ በጠቅላላው ያ አሰቃቂ ጦርነት ከአነሳሱ እስከ አጨራረሱ ታሪክ ይቅር በማይላቸው ሸፍጦችና ክህደቶች የተሞላ ነው፡፡ የጦርነቱ ምክንያት *** የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ኹለት ሌቦች የቀሰቀሱት የጥጋብ ጦርነት ነበር፡፡ ሻዕብያና ሕወሓት ፍጹም ባልጠበቁት ሁኔታ በለስ ቀንቷቸው ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ.ም ምኒልክ ቤተመንግሥት ሲገቡ ከዘመነ መሣፍንት ጭፍራ የተሻለ አቋምም ዓላማም አልነበራቸውም፡፡ ኢትዮጵያን ምን እንደሚያደርጓት ግራ ገብቷቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ለጊዜው በየፊናቸው የቻሉትን ያክል በመዝረፍ ላይ ተስማሙ፡፡ አንዱ ወደ ትግራይ ሌላው ወደ ኤርትራ የአገሪቱን አንጡራ ሀብት ያግዙ ጀመር፡፡ ይህ ዝርፊያ ኤርትራ ከሚያዝያ 15-17 ቀን 1985 ዓ.ም ባደረገችው የተጭበረበረ ሕዝበ ውሳኔ ነጻነቷን በይፋ ካወጀች በኋላም ሊቆም አልቻለም፡፡ መለስና ጭፍሮቹ ኤርትራን በቶሎ ሸኝተው ሲሳያቸውን ለብቻቸው ለማጣጣም በነበራቸው ቅጥ ያጣ ስግብግብነት በኢትዮጵያ ላይ የፈፀመት ደባ ራሱን የቻለ ርዕስ ስለሚፈልግ ልለፈው፡፡ ዋናው ቁምነገር ሻዕቢያ እግሩ ከወጣም በኋላ
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የሕወሓት አባላትና ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ሊያደርጉት ያቀዱት ሰልፍ መሰረዙ ተሰማ።

  በሕወሓት ጥያቄ መሰረት የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ በኢትዮ ኤርትራ ድንበር ጉዳይ ላይ የወሰነውን ውሳኔ ለመቃወም የሕወሓት አባላትና ደጋፊዎች በአዲስ አበባ ሊያደርጉት ያቀዱት ሰልፍ መሰረዙ ተሰማ። የተሰረዘው በደሕንነት ስጋት ነው ብለዋል። የሕዝብን ደሕንነትና ሰላም ሲገፉ ኖረው ዛሬ ተገልብጦ ለነሱ ስጋት መሆኑ አስገራሚ የፖለቲካ ሂደት ነው። የሕወሓት አባላትና ደጋፊዎች የኢሕአዴግ ምክር ቤት በባድመና በድንበር ከተሞች ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ በመቃውም በመስቀል አደባባይ ሊያደርጉት ያቀዱትን ሰልፍ መሰረዙን የሕወሓት አፈቀላጤ የሆነው ሆርን አፍየርስ በድረ ገጹ ይፋ አድርጓል። በሕወሓት ጥያቄ መሰረት የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ በትግራይ ክልል የሚገኙ የድንበር ከተሞችን ለኤርትራ በ አልጀርሱ ስምምነት መሰረት አሳልፎ ለመስጠት መወሰኑ የሚታወስ ሲሆን ለኤርትራ ይሰጣሉ የተባሉትም ባድመ ኢሮብ ፆረና ዛላንበሳን ጨርሞ አስራ ሰባት ወረዳዎች ሲሆኑ ይህንን በመቃወም በተለያዩ የትግራይ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች ተደርገዋል።
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በመቀሌ ባድመን አሳልፈን አንሰጥም በሚል ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ። (ቪድዮ)

  ሰላማዊ ሰልፍ በመቀሌ  ተደረገ ። “መሬታችን አሳልፈን አንሰጥም” “እቃ እንጂ አገርና ህዝብ አይሸጥም” “ዘሄግ ያስተላለፈው ውሳኔና የአልጀርስ ስምምነት በጭራሽ አንቀበልም”
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሕወሓት ምስጢራዊ ስብሰባ ይዞ በጭንቀት ያምጣል ፤ ትግራይ በሰላማዊ ሰልፎች እየተጥለቀለቀች ነው

የሕወሓት ሳቦታጅ አንዱ ክፍል የመረጃ ቀውስ መፍጠር ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የፖለቲካና የኢኮኖሚ ውጥረት ከኢሕአዴግ የፖለቲካ ባሕሪይ አንጻር መለካት መጭውን ጊዜ ለማወቅ ይረዳል። ሕወሓት ምስጢራዊ ስብሰባ ይዞ በጭንቀት ያምጣል ፤ ትግራይ በሰላማዊ ሰልፎች እየተጥለቀለቀች ነው ፤ ለሕዝቡ የድንበር ውሳኔውን አጀንዳ ስለሰጠው ይህን ያሕል አይሰጋም ፤ አጃቢው አረና አጀንዳውን በሰላማዊ ሰልፍ ያደምቅለታል። በሰበር ዜናና በተባራሪ ዘገባዎች የመረጃ ቀውስ ተፈጥሮ የተቃዋሚዎች ትግል የእንቅልፍ ላይ የቅዠት መወራጨት አድርጎታል ። ለኤርትራ ይሰጣሉ የተባሉት መሬቶች ሕጋዊ የውሳኔና የማስረከብ ፕሮሰሳቸው መስመሩን የተከተሉ አይደሉም ፤ ስለዚሕም ኤርትራ የሚፈለገውን ከመናገር ተቆጥባለች ፤ ሕጋዊ መስመሩ ኢሕአደግ ውሳኔው ለተመድ ቀጥታ ማሳወቅ ነበረበት ፤ ተመድም ለኤርትራ መንግስት ያስተላልፍና የኤርትራን መልስና መግለጫ ተከትሎ ሕጋዊ አግባቡ ይተረጎማል ። ወያኔ ግን ይህንን ሕጋዊ መስመር ካለመከተሉም በላይ የወሰነው ውሳኔ የሐገር ውስጡን ትኩሳት ለማብረድና በሰበር ዜናና በሰልፎች ሐገሩን ማመስ ይዟል። ወያኔ ኢሕአደግ በተከታይነት ሕዝቤ በውሳኔው ስላልተስማማ ተመልሼ ላጢነው የሚል ተመሳሳይ መግለጫዎችን ይለቃል ። #MinilikSalsawi
Tagged with: , , , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የኩናማ ሕዝብ የሕወሓት ኢሕአዴግን ውሳኔ የአገር ክሕደት ነው ሲል በሰላማዊ ሰልፍ ገለፀ።

የኩናማ ሕዝብ የሕወሓት ኢሕአዴግን ውሳኔ የአገር ክሕደት ነው ሲል በሰላማዊ ሰልፍ ገለፀ። በትግራይ የኩናማ ሕዝብ በቅርቡ ኢሕአደግ ለኤርትራ መንግሰት አሳልፎ ሊሰጣቸው የወሰነባቸው የባድመንና 17 የአከባቢው የድንበር ወረዳዎችን ውሳኔ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉ ተገለፀ። በሉኣላውነታችን ኣንደራደርም ! ጀግናው የዓዲ ፀፀር ኩናማ ህዝብ ” በመሬታችንና ሉኣላዊነታችን ኣንደራደርም” ብለዋል። ለሰልፍ የወጡት የኩናማ ሕዝቦች ።  
Tagged with: , , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የባድመ ሕዝብ የኢህኣዴግ ውሳኔ የአገር ክህደት ነው በሚል መሪ ቃል የተቃውሞ ሰልፍ አደረገ ።

የባድመ ሕዝብ በሕወሓት ተረቆ በኢሕአዴግ ውሳኔ የተሰጠበትን የባድመንና 17 የድንበር ወረዳዎች ለኤርትራ አሳልፎ የሚሰጠውን ውሳኔ የተቃወመ ሲሆን የኢህኣዴግ ውሳኔ የአገር ክህደት ነው  ብሎታል ። የባድሜ ህዝብ ዛሬ ሰኞ 04/10/2010 ዓ/ም የኢህኣዴግ ስራ ኣስፈፃሚ ኮሚቴ በኣልጀርስ ውል ላይ ያሳለፈው ውሳኔ ተቃውመውን በሰልፍ ገልፀዋል። * የራሳችን ኣንሰጥም የሌላ ኣንፈልግም ! * የኢህኣዴግ ውሳኔ የአገር ክህደት ነው !
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የባድሜ ፖለቲካ እና ወልቃይት – የሺሀሳብ አበራ

ሻዕቢያ የትህነግ የበላይ ሆኖ በሰላም መኖርን ይመርጥ ነበር፡፡ነገር ግን ተመሳሳይ ፋብሪካዎች በመቀሌ እና በአዲግራት፣በአስመራ ስለተከፈተ ሁለቱም ሻጭ ሲሆኑ ገበያ ጠፋ፡፡ ሻዕቢያ ትህነግ ካልተመችኝ የምኒሊክን ቤተመንግስት ለኦነግ እሰጣለሁ እያለም ዛተ፡፡ኢሳያስ አፈወርቂ በህይዎቴ የሚቆጨኝ ነገር የምኒሊክን ቤተመንግስት ለኦነግ መስጠት እየተገባኝ ለትህነግ መስጠቴ ነው ሲል ከርሟል፡፡ትህነግ እና ሻዕቢያ ወዳጆች ነበሩ፡፡በ 1972 ጀብሃን አስመራ ላይ በጋራ ቀብረውታል፡፡ትህነግ በ 1968 በፃፈችው ማንፊስቶ የኤርትራን መገንጠል አውጃለች፡፡ተቀብላለች፡፡ ሻዕቢያ በሽግግር መንግስቱ ወቅት ትህነግን እንደ ቅንጣት እየቆጠረ ለመኮርኮም ሲሯሯጥ ፣አስመራን ይዞ የበላይነቱን እንዲያነሳ ተወሰነ፡፡እስከ 1989 ግንኙነቱ መልካም ነበር፡፡በ1990 ጀምሮ የኢኮኖሚ ጦርነት በድንበር ሰበብ ተቀሰቀሰ፡፡ ባድሜም የሁለቱ ሃገራት የፉክክር ሜዳ ሆነች፡፡በ 1993 አቶ መለስ እና አቶ ኢሳያስ በአልጀሪያ ባድሜ የኤርትራ እንደሆነች ተስማሙ፡፡የዛኔው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ስዮም መስፍን ባድሜ የኛ ናት፡፡አልሰጠንም ብለው መላው ኢትዮጲያን በደስታ አሰለፉ፡፡አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ላይ ህዝቡ ደስታውን ገለፀ፡፡ ከ 70 ሺ በላይ ዜጎች ቢገደሉም መሬታችን ተመልሷል የሚለው ዘፈን ሾላ በድፍን ለ17 ዓመት ቀጠለ፡፡ዘንድሮ ከ 17 ዓመት በኃላ ኤርትራ መሬትሽን ውሰጅ ተባለች፡፡ በዚህ ውሳኔ ውስጥ የህወሓት የአንበሳውን ሚና ይጫዋታል፡፡እንደተጫዎተም የሰጠው መግለጫ ያሳያል፡፡ ህዎኃት በምዕራብ በወልቃይት፣በሰሜን በባድሜ፣በምስራቅ በኩል ከወሎ እና ከአፋር የእኔነት ጥያቂዎች ተነስተውበታል፡፡የአፋር ወጣቶች ወረዳችን ያላግባብ ተካሏል ብለው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ናቸው፡፡ባድሜም ከ 1989 ጀምሮ የኤርትራ ጦር አዳምኖባት ቆይቷል፡፡ወልቃይት እና ራያ በተለያየ አቅጣጫ ከ 1972 ጀምሮ የማንነት ጥያቄዎች ተነስተውበታል፡፡ ባድሜ በአልጀርስ ቀድሞ ከ 17 ዓመት በፊት
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

መለስ ዜናው ያቦካውን ዶ/ር አብይ ጋገረው ! (ይድነቃቸው ከበደ)

መለስ ዜናው ያቦካውን ዶ/ር አብይ ጋገረው ! — በቃ የሆነው ይሄ ነው ፤ ለመውቀስ እና ለማሞገስ በሃቅ ላይ የተመሰረተ ምክንያት ሊኖረን ይገባል ። እንዴት ያላችሁኝ እንደሆነ የሆነዉ እንዲህ ነው ! . ~ መጀመሪያ ~ ተገንጣይ አስገንጣይ ወንበዴ አገራችንን ኢትዮጵያን በ1983 ‘ነጻ አወጡ’ ፤ እነኚህ ወንበዴዎች በሃገራችን ላይ ሴራቸውን ጎነጎን ። ነፃነት ወይም ባርነት የሚሉ ሁለት ሰማይና ምድር የሆኑ አማራጮች በማቅረብ “ሪፈረንደም” ተብየውን በማካሄድ ግንቦት 16/1985 ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠል አደረጉ ። አገራችን ወደብ አልባ አደረጓት ፤ ይህ ደባ በአገራችን ላይ ሲፈጸም ኢትዮጵያ መንግስት አልባ ነበረች ፤ በወቅቱ የነበረዉ ወያኔ “የሽግግር መንግስት” ነኝ እያለ ነበር ፤ የአቶ መለስ ክፉ ሥራ አንዱ ይሄ ነው። . ~ ነገሩ ሲቀጥል~ የሆነው እንዲህ ነው ፤ ሻዕቢያ ሄጃለው ካለ ከ6 ዓመት በኋላ “ሌባ ሲሰርቅ እንጂ ሲካፈል አይሰማማም” እንደሚባለው ፤ ተገንጣይ ወንበዴዉ ሻዕቢያ በታንክና በመድፍ የታጀበ ሰራዊት ልኮ ባድመንና ሽራሮን ይዞ የእኔ ነው አለ ። ይህም ተሳክቶለት ዛሬ ባድመን በጁ ሊያደርግ ዉሳኔን አግኝቷል፣ነገ ደግሞ ማንን እና የት ?! የሚል የሉዓላዊነት ጉዳይ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ትልቅ ጥያቄ ጫረ በዚህም ምክንያት በ1991 ጦርነት ተካሄደ ። . ~ እናስ ያላችሁ እንደሆነ~ ኢትዮጵያውያን ጦርነተን በአሸናፊነት ተወጡ ! ነገር ግን ያ’ ሟቹ ሰውዬ በኢትዮጵያ ላይ ሸፍጥ ሰራ ፤ በጦርነቱ ኢትዮጵያውያን ባድመን ማስመለስ ብቻ ሣይሆን አሰብ ወደባችንን የራስ የማድረግ ህጋዊ መብት ጫፍ የደረሰውን መልካም አጋጣሚ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ግልፅ ደብዳቤ ለኢህአዴግ ባለስልጣናት ከፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ጂግሳ

ግልፅ ደብዳቤ ለኢህአዴግ ባለስልጣናት ከፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ ጂግሳ ጉዳዩ– ባድመን አስመልክቶ አምባሳደር ስዩም መስፍን እውነትን ስለመናገራቸው ውድ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ሆይ በቅርቡ በተካሄደው ልዩ ስብሰባችሁ ላይ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋራ ለመታረቅ ባድመን፣ ዛላንበሳን፣ ኢሮብን፣ ፆረናን እና በጠቅላላው 17 ግዛቶችን ለኤርትራ ለመቸር ማቀዳችሁን በዜና አደመጥኩ። እባካችሁ ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል? የዛሬ 18 ዐመት አካባቢ የባድመ ጦርነት አልቆ፣ የመሬት ይገባኛሉ ሙግት ለዐለምእቀፍ ፍርድቤት ቀርቦ ለኢትዮጵያ እንደተፈረደላት ለኢትዮጵያ ህዝብ አብስራችሁ ነበር። በዛን ወቅት የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር የነበሩት አምብሳደር ስዩም መስፍን በዐለምአቀፉ ፍርድቤት ኢትዮጵያ ማሸነፏን ያበሰሩን እናንተን ኢሀአደጎችን እና የወቅቱን ጠቅላይ ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊን ወክለው መሆኑ ግልፅ ነው። መቼም አቶ ስዩም መስፍን የመንግሥታቸውን ድምፅ ከመንግሥታቸው ታዘው ያንፀባርቃሉ እንጂ ከራሳቸው አንደበት ብቻ አፍልቀው አይናገሩም። ዳሩ ግን ይሄን ሰሞን አምባሳደር ስዩም ስለባድመ ዋሽተዋል፣ በአልጅርስ የተሰየመው ፍርድቤት ባድመን እና ዙሪያውን የሰጠው ለኤርትራ ነው፣ የሚል ወሬ ይናፈሳል። ይህ ወሬ እናንተን እና እናንተን ወክለው ኢትዮጵያ ተበየነላት ብለው ያበሰሩንን አምባሳደር ስዩምን ዋሾ ያደርጋል። አምባሳደር ስዩምን የመሰሉ ትልቅ ሰው ይዋሻሉ ብዬ አላስብም። እናንተ ኢህአደጎችም ትቀጥፋላችሁ ብዬ ሸክ እይገባኝም። ቃላችሁ እውነት መሆኑን አልጠራጠርም። የላዩን ለመድገም፣ እናንተን ወክለው የተናገሩትን አምባሳደር ስዩም መስፍንን ይዋሻሉ ማለት እናንተም ሃሰተኞች ናችሁ ማለት ነው። አምባሳደር ስዩም መስፍን በአንድ ቃል የአሉት ”የጫካ ህግ በደንብ ህግ ትሸንፏል። ኤርትራ ያቀረበችውን የመሬት ጥያቄ የዐለምአቀፉ ፍርድቤት ለኢትዮጵያ በይኗል” የሚል ነው። ለማስረጃ፣ የተናገሩበትን ሺዲዮ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ባድመ እና ባድማ (ጌታቸው ሺፈራው)

~ትህነግና ሻዕቢያ እስኪጠግቡ ድረስ ኢትዮጵያን ዘረፉ፣ ኢትዮጵያውያንን ገረፉ። ጥጋብ ስትመጣ ኢትዮጵያን እየቦጨቁ መነካከስ ጀመሩ። ~ኢትዮጵያውያን የባድመ ጦርነትን ያህል የተሞኙበት ጊዜ ያለ አይመስለኝም። ሁለቱ ጥጋበኞች ኢትዮጵያውያንን ያሻቸውን ካደረጉ በኋላ ሲጣሉ ትህነግ/ህወሓት ኢትዮጵያውያንን በስስ ጎናቸው ገባ። ዳር ድንበር ተደፈረ ብሎ ለፈፈ። ዳርድንበር ማስጠበቅ የለመደ ሕዝብ ጠላቱ ትህነግን አምኖ ወደ ጠላት ሰፈር ጎረፈ! ሻዕቢያና ትህነግ ወደሚባሉ ሁለት ጅቦች ቀጠና! ~ዳር ድንበር ተደፈረ ብሎ የለፈፈው ትህነግ/ህወሓት ከኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር ሆኖ ኢትዮጵያን ሊበትን እንደነበር ተረሳ። ገንጣይ፣ አስገንጣይ እንደነበር ተዘነጋ። ኢትዮጵያውያን በስስ ጎናቸው ዳር ድንበር ተደፈረ ብለው ዘመቱ። ድሃው ገበሬ ከሻዕቢያና ትህነግ የተረፈውን ሀብቱን ለጦርነቱ አበረከተ። ከትህነግና ሻዕቢያ ጭፍጨፈ የተረፉ ወጣቶች ወደ ጦርነት ተመሙ። ዳርድንበር እያስጠበቁ እያለ ጊዜአሸንፏቸው የወደቁና ጠላት ተብለው ከጦር ሰራዊቱ የተባረሩ የድሮው ጦር አባላት ቁስላቸውን ረስተው ከትህነግ አዛዦች ስር ሆነው ህይወታቸውን ሰጡ። ~ሻዕቢያና ትህነግ ከጋምቤላ እስከ ኦጋዴን፣ ከወልቃይት እስከ ቦረና ያለውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ተባብረው እንዳልዘረፉ፣ ይህን በጋራ የዘረፉት ሕዝብ ባድመ የሚባል ድነጋያማ ቦታ “የእኔ ነው የእኔ ነው” ብለው አጫረሱት! ~ያ ሁሉ ሕዝብ ካለቀ በኋላ፣ ያ ሁሉ ንብረት ከወደመ በኋላ ትህነግ ህዝብን በቀሰቀሰበት ህብረ ዜማ ስልጣኑን አጠናከረ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆ ብሎ በወጋው ሻዕቢያ ስም በርካታ የአማራ፣ ኦሮሞ፣ የጉራጌ፣ …ወጣቶች እስር ቤት ገቡ። ሻዕቢያን የወጉ ወጣቶች ከሻዕቢያ ጋር ተባብረው፣ ከኤርትራ ሰልጥነው ኢትዮጵያን ሊወጉ ነው ተብለው ሁለት አስርት አመታትን የስቃይ ጥግ አዩ ~”ባድመ የኢትዮጵያ ነው” እያለ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News