ሰበር ዜና – ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ከምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ተነሡ!

ከቀትር በፊት አጀንዳው መታየት እንደ ጀመረ፣ “ሰበር ዜና: አንሡኝ፤ ለቀቅሁላችሁ፤ እንደፈለጋችሁ አድርጉት” ብለው ቢጠይቁም ፓትርያርኩ፣ አይነሡም፤ በማለታቸው አነጋግሮ ነበር፤ ካህናቱና የምእመናኑ አቤቱታ ቀርቦ ተሰምቷል፤ ለ13 ጊዜያት ያህል ወደ መንበረ ፓትርያርኩ በመመላለስ የተንገላቱበት ጉዳይ ምላሽ አግኝቷል፤ ፓትርያርኩ፣ መነሣታቸውን ቢቃወሙም፣ ሓላፊነት ይወስዳሉ ወይ? ተብለው ሲጠየቁ ፈቃደኛ አልኾኑም፤ የሀገረ ስብከቱን ምእመናን አንድነት ለመጠበቅ ትኩረት እንዲሰጥ ምልዓተ ጉባኤው አሳሰበ፡፡ …